#አልሐምዱሉላሒ_ደህና_ናት
፡
፡
#ሁለት(መጨረሻ)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...በተደጋጋሚ ስለአፍራህ ከመስማቴ ብዛት አፍራህን እኔም ላፈቅራት ምንም አልቀረኝም። እውነቱን ለመናገር የዛን ጊዜ ክላስ ውስጥ ከነበርነው ሠላሳ ምናምን ወንዶች አስራ ምናምኑ በአፍራህ ፍቅር የተለከፈ ነበር፤ ሒሳብ አስተማሪያችን ጭምር። መቼም ሒሳብ አስተማሪያችን እያካፈሉም፣ እየደመሩም፣ እየቀነሱም፣ እያባዙም ሳያስቧት አይቀሩም፡፡ አንዳንዴ ቡዝዝ ብለው መላጣቸው ላይ ላብ ፊጭ ፊጭ እያለ ሲመለከቷት ያሳዝኑኝ ነበር። “ወይኔ ምነው ያችን አመዳም አግብቼ አምስት ልጅ
ባልወለድኩ ኖሮ" እያሉ በሚስታቸው የሚቆጩ ነው የሚመስለኝ።
እኔና አል አሚን ወደ ቤት ስንሄድ አፍራህና ጓደኞቿን ከሩቅ በቀስታ ተከትለን ነው። አንድ ቀን
ታዲያ አፍራህ ማስቲካ ገዝታ (ባናና ማስቲካ) ልጣጩን ጥላው ወደ ጓደኞቿ ተቀላቀለች። እኛ
የማስቲካውን ልጣጭ የጣለችበት ቦታ ስንደርስ አል አሚን ተስገብግቦ ቢጫውን የማስቲካ መሸፈኛ ወረቀት አነሳው፡፡ የሆነ ከባድ ቅርስ ወድቆ ያገኘ ነበር የሚመስለው። ለራሴ ማመን እስከሚያቅተኝ ለሁለት ዓመት አካባቢ የማስቲካውን ልጣጭ በክብር፣ በታላቅ ክብር አስቀምጦት ነበር። ለእርሱ ብቻ
በሚታይ ስውር ቀለም የአፍራህ ምስል የታተመበት እሰኪመስለኝ።
አል አሚን እንዲሁ ሲሰቃይ ክረምት ገባ። እፍራህን ለሁለት ወራት መለየት ለአል አሚን የቁም ሞት ነበር። ሱስ ሆናበታለች፡፡ አፍራህ ዓለሙን ሁላ አጨላልማ በነፍሱ ሰማይ ብቻዋን የደመቀች ኮከብ ነበረች። ቢሆንም እንደለመደው በዝናብ ሳይቀር ከረንቦላ ቤት እየሄደ እዛው ቆሞ አፍራህን ስትወጣ ለማየት ይጣጣር ነበር። ለአስራ አምስት ቀናት ጠብቆ ኣላያትም፤ ሊያብድ ሆነ።
ታዲያ በመሀሉ በጣም የምንወዳቸው ሼህ ያሲን የሚባሉ ሰውዬ መንገድ ላይ አገኙኝ። የአል አሚን ቁርአን አስቀሪ ናቸው።
“አቡቹ ደህና ዋልክ?”
“ደህና ዋሉ ሸሃችን "
"አልሃምዱሊላሂ…. እስቲ ወዲህ የማወጋህ ጕዳይ አለኝ” አሉና ከመንገዱ ወደ ዳር ወስደው እንዲህ አሉኝ፣ “ ጓደኛህ አል አሚን ምን ነክቶት ነው ልጄ? ከቀልቡም አይደለም፤ ቁርአን ቤትም መምጣት ካቆመ ስንት ጊዜው! …ተበላሽቷል ይሄ ልጅ ጭራሽ ዛሬ እዛ ቁማር የሚጫወቱበት ቤት ቁሞ አየሁት። ጓደኛው ነህ፤ አትመክረውም? ኧረ ቀልቡ ደረቀ…።” ብለው ነገሩኝ። በአል አሚን አዘንኩ።ማን ያውቃል የልጁን ጉዳት። የዋልንበት ቦታ ሁሉ ያለን እየመሰላቸው ስንቶች በዋልንበት ፈረጁኝ…
አል አሚን አንድ ቀን እየተጣደፈ ቤት መጣ። ከመቸኮሉ ብዛት ድመታችንን በሩ ሥር እንደተኛት
ጀራቷን ረግጦ ካቅሟ በላይ እስጮኻት፤
"አቡቹ…! አቡቹ! አይገርምም የነአፍራህ ቤት ለካ በሩ እኔ ከምቆምበት በኩል አይደለም፤ …
ከኋላ በኩል በዘይት ቤቱ ጋ ነው፤ በዛ በኩል ነው የምትወጣው… ሂሂሂ ተሸውጄ " አለኝ፤ ሲያወራ
በደስታ ፊቱ በርቶ ነበር። “…ዛሬ ባጋጣሚ በታች በኩል ስሄድ ከእናቷ ጋር ሆና ፌ…ት ለፊት፣
እንደዚህና እንደዛ …በቃ ተያየን፣ ወ…ላሂ አቡቹ ግጥምጥም ነው ያልነው፣ አኡዙቢላሂ …ልሮጥ ነበር ሂሂሂሂሂሂሂ አለና ፍርፍር ብሎ ሳቀ። ድንገት ተነስቶ ቆመና ደግሞ “እስኪ እየኝ፣ እንዲህ ሆኜ እኮ ነው ያየችኝ፤ እደብራለሁ እንዴ …?” አለኝ። ሁለት እጆቹን ግራና ቀኝ እንደ ከንፍ ዘርግቶ አንዴ እኔን
እንዴ ራሱን ቁልቁል እየተመለከተ። አሳዘነኝ። የአፍራህን ቅንጡ አለባበስ እና የአላሚንን የተንሻፈፈ
ሸራ ጫማ፣ ያረጀች እና የወየበች ቪ ቅርፅ ቲሸርት በውጤ እያሰብኩ፣
ኧረ እይደብርም!" አልኩት።
እንደ ሕፃን እየተፍነከነከ መጥቶ አጠገቤ ኩርምት ብሎ ተቀመጠ። “…አይገርምም ከእናቷ ጋር ሆና
በቃ እንደዚህ እና እንደዛ ፊት ለፊት…! እንዴት አምሮባታል አቡቹ ብታያት…ወላሂ ያች የምታውቃት
አፍራህ አይደለችም! በቃ እንደዚህና እንደዛ እኮ ነው…" እጆቹ ይንቀጠቀጣሉ፤ ዓይኖቹ የደስታ! የሐዘን፣ የሐፍረት፣ የምኞት ብርሃን ይረጫሉ። ፊቱ ላይ ደስታ እንደረበበት ልሸኘው ውጣሁ።
ልንለያይ ስንል፣ “..አቡቹ ሁለት ብር አለህ እንዴ?” አለኝ እየፈራ። አል አሚን እንኳን ደፍሮ ብር
መጠየቅ፣ ያዋሰውን ደብተሩን እንኳን መልሱልኝ ለማለት የሚፈራ ልጅ ነበር፡፡ ብር ስላልያዝኩ…ወደ
ቤት ተመልሰን ከእናቴ ተቀብዬ ሰጠሁት። ደስ ብሎት ሄደ።
ቆይቼ ስሰማ በአዲሱ የእነአፍራህ በር በኩል አንድ ሻይ ቤት አለች! ሻይ ሃምሳ ሳንቲም ነው!
በሰጠሁት ብር ሻይ እያዘዘ ቁጭ ብሎ አፍራሀን ሲጠብቅ ነበር፤ አራቱንም ቀን ግን አላያትም።
እናም ከረንቦላ ቤት አካባቢ ያገኘውን የእነእፍራህን ሰፈር ልጅ ጠይቆ አፍራህ አዲስ ኣበባ ለእረፍት እንደሄደችና ትምሕርት ሲያልቅ እንደምትመጣ አረዳው፡ ቅስሙ ተሰበረ። ቢሆንም እነአፍራህ ሰፈር መሄድ አላቆመም። በየቀኑ ያንን ሰፈር ሳይረግጥ አይውልም። ሸርፍ ተራ ትርምሱ፣ ግርግሩ፣ ጫት
ተራው፣ መኪናው፣ የደሴ አንደኛ “ቀውጢ" ሰፈር… ይሄ ሁሉ ግርግር ግን ከአፍራህ አይበልጥም። አፍራህ ብቻዋን የአንድ ትምሕርት ቤት ወንዶች ነፍስ የተደረደረባት ገበያ አይደለች እንዴ ።
“እሷ ከሌለች ለምን ትሄዳለህ?” እለዋለሁ፤
“እኔንጃ” ነው መልሱ፤ ያሳዝነኛል !!
አንድቀን ደግሞ ቤት መጣና አቡቹ ሥራ ልጀምር ነው" አለኝ፣ በደስታ ፍንክንክ ብሎ።
“የምን ሥራ አልኩት፤
“አይሱዙ መኪና ላይ ረዳትነት”
“ትቀልዳለህ !?"
“ወላሂ እውነቴን ነው። ካአዲስ አበባ ደሴ የሚምሳለስ አይሱዙ ላይ ሥራ ልጀምር ነው። እናቴንም
ነግሬያት ኣሳምኛታለሁ። መኪናው ቅዳሜ ወደ አዲስ አበባ ይወጣል። አብሬው እሄዳለሁ። ብታይ ቀላል እኮ ነው ሥራው።” ፊቱ ላይ ተስፋ ይንቀለቀላል። በቀጫጭን እጆቹ ሸራ ሲጎትት፡ የጎማ ብሎን ሲያጠብቅ አሰብኩት፤ አል አሚን ትንታጉ ተማሪ። ይሄ ፍቅር የሚሉት ነገር ግን ምናይነት ልክፍት ነው
በእግዚእብሔር!!
አልአሚን ገና በመጀመሪያ ጉዞው ከመኪና ላይ ሲወርድ ወድቆ ግንባሩ ተፈንከቶና ከንዱ ተላልጦ
መጣ። ሰው ሁሉ እንኳን አላህ አተረፈህ!” እያለ አዘነለት። እንዲህ ካልተላላጡና ካልተፈነከቱ የልብን
ስብራት፣ የመንፈስን መድቀቅ ዓይቶ የሚያስታምም የለም መቼም። እንዲህ አለኝ፣ አሮጌ ፍራሹ ላይ እንደተኛ “አንተ … አፍራህ ያንን ሁሉ መንገድ አልፋ ነው አዲስ አበባ የሄደችው…? እነዛን ተራራዎች ዓይታቸዋለች…፣ ያንን ገደል እያየች ፈርታለች ፣ ደብረሲና ምሳ በልታለች፤ ቆሎም ገዝታ ሊሆን ይችላል….እዛ ጨለማ ዋሻ ውስጥ ስትገባ በፍርሃት ተንቀጥቃጣም ይሆናልኮ። ኡፍፍፍፍ አንጀቴን
በላው፡፡ ከላይ እንደእቃ ተጭኖ አፍራህ ባረፈችበት መንገድ በማለፉ ምናባዊ ዳናዋን ተከትሎ ሲነጉድ ታየኝ። ሚስኪን አልአሚን !
ቀስ በቀስ አልአሚን ነገሮች ሁሉ ተቀላቀሉበት። አንድ ቀን ትምሕርት ቤት ሄደና ጭርር ያለው በር ላይ ያገኛቸውን የትምሕርት ቤታችን ጥበቃ ጋሽ ደምሴን፣ “ትምሕርት መቼ ነው የሚጀመረው?” አላቸው፤
“ምን አውቄ ብለህ ልጄ” አሉት። ቀጠል አድረገውም…የኔ ልጅ ኳስ ሰራገጥ ይውላል፣ አንተ ትምርት
ናፍቆህ.የወለዱህ ኣባትና እናት ምንኛ ይኮሩ!! እሰይ!! እሰይ!”
ትቷቸው ወደ ቤት ተመለሰ፤ በቃ መረጋጋት አቃተው ተወዛገበ።
8ኛ ክፍል በተመሳሳይ ለአፍራህ ፍቅሩን ሳይነግራት በየቀኑ እያያት በዓይኖቹ ተስፋ ነፍሱን አፋፍቶ
ኖረ። አንድ ቀን ለአፍራህ ስጦታ ልሰጣት አሰብኩ" አለኝ። ገረመኝ ! ወይኔ ፍቅር ጉድለት አይገባው፣ ድህነት እያልኩ ሳስብ አልአሚን አንድ የሃምሳ ብርና ሦስት አስር አስር ብሮች ከኪሱ አውጥቶ አሳየኝ።
“ከየት አመጣኸው?"
፡
፡
#ሁለት(መጨረሻ)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...በተደጋጋሚ ስለአፍራህ ከመስማቴ ብዛት አፍራህን እኔም ላፈቅራት ምንም አልቀረኝም። እውነቱን ለመናገር የዛን ጊዜ ክላስ ውስጥ ከነበርነው ሠላሳ ምናምን ወንዶች አስራ ምናምኑ በአፍራህ ፍቅር የተለከፈ ነበር፤ ሒሳብ አስተማሪያችን ጭምር። መቼም ሒሳብ አስተማሪያችን እያካፈሉም፣ እየደመሩም፣ እየቀነሱም፣ እያባዙም ሳያስቧት አይቀሩም፡፡ አንዳንዴ ቡዝዝ ብለው መላጣቸው ላይ ላብ ፊጭ ፊጭ እያለ ሲመለከቷት ያሳዝኑኝ ነበር። “ወይኔ ምነው ያችን አመዳም አግብቼ አምስት ልጅ
ባልወለድኩ ኖሮ" እያሉ በሚስታቸው የሚቆጩ ነው የሚመስለኝ።
እኔና አል አሚን ወደ ቤት ስንሄድ አፍራህና ጓደኞቿን ከሩቅ በቀስታ ተከትለን ነው። አንድ ቀን
ታዲያ አፍራህ ማስቲካ ገዝታ (ባናና ማስቲካ) ልጣጩን ጥላው ወደ ጓደኞቿ ተቀላቀለች። እኛ
የማስቲካውን ልጣጭ የጣለችበት ቦታ ስንደርስ አል አሚን ተስገብግቦ ቢጫውን የማስቲካ መሸፈኛ ወረቀት አነሳው፡፡ የሆነ ከባድ ቅርስ ወድቆ ያገኘ ነበር የሚመስለው። ለራሴ ማመን እስከሚያቅተኝ ለሁለት ዓመት አካባቢ የማስቲካውን ልጣጭ በክብር፣ በታላቅ ክብር አስቀምጦት ነበር። ለእርሱ ብቻ
በሚታይ ስውር ቀለም የአፍራህ ምስል የታተመበት እሰኪመስለኝ።
አል አሚን እንዲሁ ሲሰቃይ ክረምት ገባ። እፍራህን ለሁለት ወራት መለየት ለአል አሚን የቁም ሞት ነበር። ሱስ ሆናበታለች፡፡ አፍራህ ዓለሙን ሁላ አጨላልማ በነፍሱ ሰማይ ብቻዋን የደመቀች ኮከብ ነበረች። ቢሆንም እንደለመደው በዝናብ ሳይቀር ከረንቦላ ቤት እየሄደ እዛው ቆሞ አፍራህን ስትወጣ ለማየት ይጣጣር ነበር። ለአስራ አምስት ቀናት ጠብቆ ኣላያትም፤ ሊያብድ ሆነ።
ታዲያ በመሀሉ በጣም የምንወዳቸው ሼህ ያሲን የሚባሉ ሰውዬ መንገድ ላይ አገኙኝ። የአል አሚን ቁርአን አስቀሪ ናቸው።
“አቡቹ ደህና ዋልክ?”
“ደህና ዋሉ ሸሃችን "
"አልሃምዱሊላሂ…. እስቲ ወዲህ የማወጋህ ጕዳይ አለኝ” አሉና ከመንገዱ ወደ ዳር ወስደው እንዲህ አሉኝ፣ “ ጓደኛህ አል አሚን ምን ነክቶት ነው ልጄ? ከቀልቡም አይደለም፤ ቁርአን ቤትም መምጣት ካቆመ ስንት ጊዜው! …ተበላሽቷል ይሄ ልጅ ጭራሽ ዛሬ እዛ ቁማር የሚጫወቱበት ቤት ቁሞ አየሁት። ጓደኛው ነህ፤ አትመክረውም? ኧረ ቀልቡ ደረቀ…።” ብለው ነገሩኝ። በአል አሚን አዘንኩ።ማን ያውቃል የልጁን ጉዳት። የዋልንበት ቦታ ሁሉ ያለን እየመሰላቸው ስንቶች በዋልንበት ፈረጁኝ…
አል አሚን አንድ ቀን እየተጣደፈ ቤት መጣ። ከመቸኮሉ ብዛት ድመታችንን በሩ ሥር እንደተኛት
ጀራቷን ረግጦ ካቅሟ በላይ እስጮኻት፤
"አቡቹ…! አቡቹ! አይገርምም የነአፍራህ ቤት ለካ በሩ እኔ ከምቆምበት በኩል አይደለም፤ …
ከኋላ በኩል በዘይት ቤቱ ጋ ነው፤ በዛ በኩል ነው የምትወጣው… ሂሂሂ ተሸውጄ " አለኝ፤ ሲያወራ
በደስታ ፊቱ በርቶ ነበር። “…ዛሬ ባጋጣሚ በታች በኩል ስሄድ ከእናቷ ጋር ሆና ፌ…ት ለፊት፣
እንደዚህና እንደዛ …በቃ ተያየን፣ ወ…ላሂ አቡቹ ግጥምጥም ነው ያልነው፣ አኡዙቢላሂ …ልሮጥ ነበር ሂሂሂሂሂሂሂ አለና ፍርፍር ብሎ ሳቀ። ድንገት ተነስቶ ቆመና ደግሞ “እስኪ እየኝ፣ እንዲህ ሆኜ እኮ ነው ያየችኝ፤ እደብራለሁ እንዴ …?” አለኝ። ሁለት እጆቹን ግራና ቀኝ እንደ ከንፍ ዘርግቶ አንዴ እኔን
እንዴ ራሱን ቁልቁል እየተመለከተ። አሳዘነኝ። የአፍራህን ቅንጡ አለባበስ እና የአላሚንን የተንሻፈፈ
ሸራ ጫማ፣ ያረጀች እና የወየበች ቪ ቅርፅ ቲሸርት በውጤ እያሰብኩ፣
ኧረ እይደብርም!" አልኩት።
እንደ ሕፃን እየተፍነከነከ መጥቶ አጠገቤ ኩርምት ብሎ ተቀመጠ። “…አይገርምም ከእናቷ ጋር ሆና
በቃ እንደዚህ እና እንደዛ ፊት ለፊት…! እንዴት አምሮባታል አቡቹ ብታያት…ወላሂ ያች የምታውቃት
አፍራህ አይደለችም! በቃ እንደዚህና እንደዛ እኮ ነው…" እጆቹ ይንቀጠቀጣሉ፤ ዓይኖቹ የደስታ! የሐዘን፣ የሐፍረት፣ የምኞት ብርሃን ይረጫሉ። ፊቱ ላይ ደስታ እንደረበበት ልሸኘው ውጣሁ።
ልንለያይ ስንል፣ “..አቡቹ ሁለት ብር አለህ እንዴ?” አለኝ እየፈራ። አል አሚን እንኳን ደፍሮ ብር
መጠየቅ፣ ያዋሰውን ደብተሩን እንኳን መልሱልኝ ለማለት የሚፈራ ልጅ ነበር፡፡ ብር ስላልያዝኩ…ወደ
ቤት ተመልሰን ከእናቴ ተቀብዬ ሰጠሁት። ደስ ብሎት ሄደ።
ቆይቼ ስሰማ በአዲሱ የእነአፍራህ በር በኩል አንድ ሻይ ቤት አለች! ሻይ ሃምሳ ሳንቲም ነው!
በሰጠሁት ብር ሻይ እያዘዘ ቁጭ ብሎ አፍራሀን ሲጠብቅ ነበር፤ አራቱንም ቀን ግን አላያትም።
እናም ከረንቦላ ቤት አካባቢ ያገኘውን የእነእፍራህን ሰፈር ልጅ ጠይቆ አፍራህ አዲስ ኣበባ ለእረፍት እንደሄደችና ትምሕርት ሲያልቅ እንደምትመጣ አረዳው፡ ቅስሙ ተሰበረ። ቢሆንም እነአፍራህ ሰፈር መሄድ አላቆመም። በየቀኑ ያንን ሰፈር ሳይረግጥ አይውልም። ሸርፍ ተራ ትርምሱ፣ ግርግሩ፣ ጫት
ተራው፣ መኪናው፣ የደሴ አንደኛ “ቀውጢ" ሰፈር… ይሄ ሁሉ ግርግር ግን ከአፍራህ አይበልጥም። አፍራህ ብቻዋን የአንድ ትምሕርት ቤት ወንዶች ነፍስ የተደረደረባት ገበያ አይደለች እንዴ ።
“እሷ ከሌለች ለምን ትሄዳለህ?” እለዋለሁ፤
“እኔንጃ” ነው መልሱ፤ ያሳዝነኛል !!
አንድቀን ደግሞ ቤት መጣና አቡቹ ሥራ ልጀምር ነው" አለኝ፣ በደስታ ፍንክንክ ብሎ።
“የምን ሥራ አልኩት፤
“አይሱዙ መኪና ላይ ረዳትነት”
“ትቀልዳለህ !?"
“ወላሂ እውነቴን ነው። ካአዲስ አበባ ደሴ የሚምሳለስ አይሱዙ ላይ ሥራ ልጀምር ነው። እናቴንም
ነግሬያት ኣሳምኛታለሁ። መኪናው ቅዳሜ ወደ አዲስ አበባ ይወጣል። አብሬው እሄዳለሁ። ብታይ ቀላል እኮ ነው ሥራው።” ፊቱ ላይ ተስፋ ይንቀለቀላል። በቀጫጭን እጆቹ ሸራ ሲጎትት፡ የጎማ ብሎን ሲያጠብቅ አሰብኩት፤ አል አሚን ትንታጉ ተማሪ። ይሄ ፍቅር የሚሉት ነገር ግን ምናይነት ልክፍት ነው
በእግዚእብሔር!!
አልአሚን ገና በመጀመሪያ ጉዞው ከመኪና ላይ ሲወርድ ወድቆ ግንባሩ ተፈንከቶና ከንዱ ተላልጦ
መጣ። ሰው ሁሉ እንኳን አላህ አተረፈህ!” እያለ አዘነለት። እንዲህ ካልተላላጡና ካልተፈነከቱ የልብን
ስብራት፣ የመንፈስን መድቀቅ ዓይቶ የሚያስታምም የለም መቼም። እንዲህ አለኝ፣ አሮጌ ፍራሹ ላይ እንደተኛ “አንተ … አፍራህ ያንን ሁሉ መንገድ አልፋ ነው አዲስ አበባ የሄደችው…? እነዛን ተራራዎች ዓይታቸዋለች…፣ ያንን ገደል እያየች ፈርታለች ፣ ደብረሲና ምሳ በልታለች፤ ቆሎም ገዝታ ሊሆን ይችላል….እዛ ጨለማ ዋሻ ውስጥ ስትገባ በፍርሃት ተንቀጥቃጣም ይሆናልኮ። ኡፍፍፍፍ አንጀቴን
በላው፡፡ ከላይ እንደእቃ ተጭኖ አፍራህ ባረፈችበት መንገድ በማለፉ ምናባዊ ዳናዋን ተከትሎ ሲነጉድ ታየኝ። ሚስኪን አልአሚን !
ቀስ በቀስ አልአሚን ነገሮች ሁሉ ተቀላቀሉበት። አንድ ቀን ትምሕርት ቤት ሄደና ጭርር ያለው በር ላይ ያገኛቸውን የትምሕርት ቤታችን ጥበቃ ጋሽ ደምሴን፣ “ትምሕርት መቼ ነው የሚጀመረው?” አላቸው፤
“ምን አውቄ ብለህ ልጄ” አሉት። ቀጠል አድረገውም…የኔ ልጅ ኳስ ሰራገጥ ይውላል፣ አንተ ትምርት
ናፍቆህ.የወለዱህ ኣባትና እናት ምንኛ ይኮሩ!! እሰይ!! እሰይ!”
ትቷቸው ወደ ቤት ተመለሰ፤ በቃ መረጋጋት አቃተው ተወዛገበ።
8ኛ ክፍል በተመሳሳይ ለአፍራህ ፍቅሩን ሳይነግራት በየቀኑ እያያት በዓይኖቹ ተስፋ ነፍሱን አፋፍቶ
ኖረ። አንድ ቀን ለአፍራህ ስጦታ ልሰጣት አሰብኩ" አለኝ። ገረመኝ ! ወይኔ ፍቅር ጉድለት አይገባው፣ ድህነት እያልኩ ሳስብ አልአሚን አንድ የሃምሳ ብርና ሦስት አስር አስር ብሮች ከኪሱ አውጥቶ አሳየኝ።
“ከየት አመጣኸው?"
👍28👎1