#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...ሽዋዬ ከቤቷ ስትወጣ የት መሄድ እንደነበረባት አቅዳ አልነበረም። ሰሞኑን ነገሮች ሁሉ ረገብ ብለው ስታይ ትንሽም ቢሆን ቀዝቀዝ ብላ የነበረ ቢሆንም የዛሬው አስቻለው ቤቷ ድረስ መምጣት ግን እሳት ለኩሰባት ንዴቷን ቀስትሶባታል፡፡
ከወጣችም በኋሳ ጅው ብላ መሄዷ አስቻለውና ሔዋን ብስጭቷን አይተው ለወደፊቱም እንዲፈሩ ማድረግ ነበር፡፡ ያ ሁሉ ሆኖ አሁንም ጉዞዋን ወደፊት
ቀጠለች። የዲላ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱን ወደ ቀኝ በመተው ሂዳ ሂዳ ወደ ኳስ ሜዳው ደረሰች። በሜዳው እሻግራ ፊት ለፊት ስትመለከት የዲላ ሆስፒታል ለጥ ባለ ሜዳ ላይ ተንጣሎ ታያት፡፡ ያኔ ባርናባስ ወየሶ ትዝ አላት፡፡
««አሃ» አለኝ ቀጥ ብላ በመቆም ብቻዋን እየተነጋገረች፡፡ አሁንም ለራሷ
«ለምን ባርኒ ጋ አልሄድም?» አለች። ባርናባስን ስታቆላምጠው ባርኔ እያለች ነው፡፡
ለኳስ ሜዳ ተብሎ የተናደውን ገደል ተንደርድራ ወረደችው፡ ሜዳዋንም አቋርጣት አለፈች። እዚያም አልፋ ከዲላ ወደ ሞያሌ የሚወስደውን የአስፋልት
መንገድ ተሻገረች:: ብላ ብላ የቆፌን የኮረንኮች መንገድ ትውረገረገበት ጀመር፡፡
ደግነቱ ከቤቷ የወጣችው ትምህርት ቤት ስትሄድ የለበሰችውን ልብስ እንደለበስች
ስለሆነ አለባበሷ ወዴትም ብትሄድ አያሳፍራትም፡፡ ከቦርሳ በስተቀር የሚቀራት ነገር የለምና :: አንገቷ ላይ ቀላ ያለ ቡኒ ቀለም ያላት ስካርፍ አጣፍታለች፡፡
ለሆስፒታሉ እንግዳ ናት:: ታማ ልትታከም ወይም ታማሚ ልትጠይቅ እንኳ ገብታበት አታውቅም፡፡ ይሁን እንጂ ሆስፒታሉ አደናጋሪ ሁኔታ የለውም፡፡
ህንፃዎቹ በአንድ አካባቢ ችምችም ብለው የተሰሩ ናቸው። ቀሪው ደግሞ ወለል ያለ
ሜዳ፡፡ ቀጥታ ወደ ህንጻዎቹ ስትጠጋ የተጓዘችበት መንገድ ከድንገተኛ መቀበያ ክፍሎች አካባቢ አደረሳት።
ሰዓቱ ወደ ስምንት ተኩል ገደማ ይሆናል። በርካታ ህመምተኞት በአግዳሚ ወንበሮቻ ላይ ተቀምጠው ወረፋቸውን ይጠባበቃሉ፡፡ የህመምተኞቹ ጀርባ ቆም ብላ ወደ ቀኝ አቅጣጫ ስትመለከት ረጅም የመተላለፊያ ኮሪደር ታያት፡፡ ጎርደድ ልትልበት አስባ ጥቂት ከተራመደች በኋላ አሁን ወደ አስተዳደር አገልግሎት ሃላፊ» የሚል የቢሮ መለያ አነበበች፡፡
«አሃ! የባርኔ ቢሮ ይኸ መሆን አለበት» አለችና ቆም ብላ ወደ በሩ ስትመለከት ከኋላ በል የሰው እጅ ትክሻዋ ላይ ቸብ አደረጋት፤ ባርናባስ ወየሶ፣
ሽዋ'ዩ ድንግጥ አለች ። «እንዴ! አለህ እንዴ?» ስትል ጠየቀችው ምን እያለች እንደሆነ ለሷም ሳይገባት።
«የሸዋ ዛሬ ከየት ተገኘሽን»አለና ባርናባስ እጇን ጨብጦ እንደገና ደረት ልደረት ተሳሳመ።: ባርናባስ ሸዋዬን ሲያቆላምጥ የሸዋ እያለ ነው፡፡
«ጉብኝት መጥቼ::» አለችው ሸዋዬ ሳቅ እያለች።
ጥሩ ነዋ! የሚጎበኝም ሞልቷል የሚያስጎበኝም አለ።» አላት ባርናባስ እጁን ትክሻዋ ላይ ጣል አድርጎ በረጅም ቁመቱ ቁልቁል እየተመለከታት፡፡
«አለፈልኛ! ኪኪኪኪ ……!
እኔ ጋ ነው የመጣሽው?» ሲል ጠየቃት እሷንም ቢሮውንም ተራ በተራ እየተመለከተ፡
«አይ!» ሽዋዬ ተሽኮረመመች።
«ቢሮዬ አጠገብ ቆመሽ ሳገኝሽ ጊዜ እኮ ነወ፡፡ ጎራ በያ፣ ሻይ በና ልበልሽ»
«በዚህ ሙቀት ሻይ ቡና?»
«ለስላሳም ይኖራል»::አለና ባርናባስ እጇን ይዟት ወደ ቢሮው አመራ::
በሽዋዬ ዓይን የባርናባስ ቢሮ ልዩ ነው፡፡ ስፋቱ፣ ጽዳቱ፣ የመስኮቶቹ
መጋረጃዎችና የወለለ ምንጣፍ ዓይን ይማርካሉ፡፡ የመጋረጃው ቀለም ነጣ ያለ ብርቱካናማ ነው ለቢሮው ልዩ ብርሃን ሰጥቶታል፡፡ እንግዳ መቀበያው ጠረጴዛ
ስፋትና የወንበሮቹ ብዛት አስደነቃት፡፡ በቢሮው የግድግዳ ጥግ ዙሪያ ተጨማሪ ወንበሮችም አሉ፡፡ ያቤሎ ጤና ጣቢያ ውስጥ በነበረበት ጊዜ በአንድ ጠበብ ባለች ክፍል ውስጥ ከአንድ ሜትር የማትበልጥ ጠረጴዛውንና የሚቀመጥባትን ደረቅ
ወንበር አስታውሳ ስታወዳድር አሁን ግን ገነት ወስጥ እንደገባ ቆጠረችው::
«አንተ! ቢሮህ ግን እንዴት ያምራል!?» አለችው የቢሮውን ዙሪያ በዓይኗ እየቃኘች፡፡
ከዚህ የበለጠ ስንት ዓይነት ቢሮ አለ እባክሽ! ደሞ ይኸ ቢሮ ሆኖ?» አለና ወንበር ሳብ አድርጎ እንድትቀመጥ ጋበዛት።
«ጡር አትናገር»
ባርናባስ በእንግዳ መቀበያው ጠረጴዛ ላይ ከሸዋዬ ፊትለፊት ቁጭ አለና በደወል ተላላኪ ጠርቶ ለእሱ ቡና ስሸዋዬ ለስላሳ አዘዘ
«ይኸ ሁሉ ወንበር ምን ያረጋል?» ስትል ጠየቀችው፡፡
ህእ! የባለ ስልጣን ቢሮ እኮ ነው፣ ስንት ዓይነት ስብሰባ የሚካሄድበትና ውሳኔ የሚሰጥበት። አለና ባርናባስ በተቀመጠበት ላይ ፈነስነስ አለ።
በምን በምን ጉዳይ ላይ ትወስናለህ?»
«በፖለቲካ በትይ፥ በአስተዳደር ጉዳይ ብትይ፣ በደረጃ ዕድገት፣
በዲስፕሊን.…ወዘተ!» አለና ሽዋዬን ፈገግ ብሎ እያየ በቀልድ ዓይነት አነጋገር፣
«በፍቅር ላይ ብቻ ነው መወሰን ያቃተኝ!» አለና ሃሃሃሃ…» ብሎ ለራሱ ስቆ ሸዋዬንም አሳቃት፡፡
«ስትልን» አለች ሽዋዪ በቅንድቧ ስር እያየችው፡፡
«የምወዳት ሴት እንዳትጠላኝ አድርጌ መወሰን! ሃሃሃሃ….
«ውይ አልቀረብህም»
"ያን ማድረግ ብችል ኖሮ አንቺ መች ታመልጪኝ ነበር» አለና እንደ ቁም ነገር አድርጎ ግን የሸዋ፡ ይህን ያህል ወራት ዲላ ውስጥ ስትኖሪ እንዴት ወደ ቢሮው ሄጄ ልጠይቀው አላልሽም?» ሲል ጠየቃት፡፡
«ሆሆይ! ደሞ የሰው ባል ለአለፈውም ይቅር ይበለኝ፡፡ ያም ቢሆን ሳላውቅ ያደረኩት ስለሆነ ኩነኔው የአንተ ነው፡፡» አለችና የቀረበላትን ሚሪንዳ ጎንጨት
አለች፡፡
ባርናባስ በስጨት እንዳለ ዓይነት እጁን ወንጨፍ እያረገ የሸዋ ደሞ ዝም ብለሽ ነው፣ ይኸን ሚስት፣ ድስት፣ ትዳር ምናምን የምትይውን ነገር ለምን አትተይም? ፍቅር በትዳርና በስማኒያ ይገለጽ መስለሽ እንዴ?” አላት ቡናውን
እያማሰለ፡፡
«ብታርፍ ይሻልሃል» .
«በተለይ በአንቺ ነገር መቼም ቢሆን የምቆርጥ አይመስለኝም።
ግን ባለቤትህ ደህና ናት?»
«ለራሷ ትኖራለች።
«እዚህ ገባህ፣ ከዚያ ወጣህ አትለኝም!»
«መረን ለቃሃለቻ!»
«ኧረ ዛሬ ከየት ተገኘሽ የሽዋ? እስቲ ስለ አንቺ እንጨዋወት?» ብሎ ቡናውን ፉት አለ፡፡
«አንተን ልጠይቅ ኪኪኪኪ...»
«ጎሽ የኔ ወለላ! አንቺ እኮ ዱሮም ቁም ነገርኛ ነሽ ሰውየው እኔ ሆኜ እንጂ» ብሉ ነገሩን ተወት ሲያደርገው ሽዋዬ ቀጠላች።
«ባትሆንስ?»
«ልብ ቢኖረኝ ኖሮ እግርሽ ላይ ወድቄ ይቅርታ መጠየቅ ነበረብኝ። ግን ዛሬነገ ስል» አለና ንግግሩን ቆረጥ አድርጎ አሁንም ቡናውን ፉት አለ፡፡
«ደሞ እንደገና?»
«የቆየ ነገር እኮ ሲታደስ ከበፊቱ ይበልጣል። ሃሃሃሃ…»
«ይልቅስ ስለ መጣሁበት ጉዳይ ልጠይቅህ!»
«ምን ልርዳሽ?»
«አንድ ሴት፣ በተለይ ልጃገረድ ማስወረድ አስማስወረዷን በሀኪም ምርመራ ማወቅ ይቻላል?» ስትል ጠየቀችው፡፡
«ሀኪሞችን አነጋግሮ መረዳት ይቻላል። ግን በዚህ ዙሪያ ምን ችግር ገጠመሽ?» ሲል ጠየቃት።
«በእናትህ ባርኔ ዶክተሮችን ጠይቅና ንገረኝ!»
«ማነጋገር እችላለሁ!»
«ይገርምሃል! በአንዲት እህቴ ገዳይ ተቸግሬአለሁ፡፡»
«አስወርዳ?»
«መሰለኝ፡፡»
«በአገር ባህል ወይስ በሀኪም?»
«አረ የእናንተ ሰራተኛ በሆነ ሰው!»
ደሞ የምን ባህል አመጣህ ያን ቤሆን ራሴ ተከታትዩ ለሕግ አቀርበው አልነበር? ያስቸገረኝ ብላ ሸዋዬ የተበሳጨች ለመምሰል ራሷን ወዘወዘች።
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...ሽዋዬ ከቤቷ ስትወጣ የት መሄድ እንደነበረባት አቅዳ አልነበረም። ሰሞኑን ነገሮች ሁሉ ረገብ ብለው ስታይ ትንሽም ቢሆን ቀዝቀዝ ብላ የነበረ ቢሆንም የዛሬው አስቻለው ቤቷ ድረስ መምጣት ግን እሳት ለኩሰባት ንዴቷን ቀስትሶባታል፡፡
ከወጣችም በኋሳ ጅው ብላ መሄዷ አስቻለውና ሔዋን ብስጭቷን አይተው ለወደፊቱም እንዲፈሩ ማድረግ ነበር፡፡ ያ ሁሉ ሆኖ አሁንም ጉዞዋን ወደፊት
ቀጠለች። የዲላ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱን ወደ ቀኝ በመተው ሂዳ ሂዳ ወደ ኳስ ሜዳው ደረሰች። በሜዳው እሻግራ ፊት ለፊት ስትመለከት የዲላ ሆስፒታል ለጥ ባለ ሜዳ ላይ ተንጣሎ ታያት፡፡ ያኔ ባርናባስ ወየሶ ትዝ አላት፡፡
««አሃ» አለኝ ቀጥ ብላ በመቆም ብቻዋን እየተነጋገረች፡፡ አሁንም ለራሷ
«ለምን ባርኒ ጋ አልሄድም?» አለች። ባርናባስን ስታቆላምጠው ባርኔ እያለች ነው፡፡
ለኳስ ሜዳ ተብሎ የተናደውን ገደል ተንደርድራ ወረደችው፡ ሜዳዋንም አቋርጣት አለፈች። እዚያም አልፋ ከዲላ ወደ ሞያሌ የሚወስደውን የአስፋልት
መንገድ ተሻገረች:: ብላ ብላ የቆፌን የኮረንኮች መንገድ ትውረገረገበት ጀመር፡፡
ደግነቱ ከቤቷ የወጣችው ትምህርት ቤት ስትሄድ የለበሰችውን ልብስ እንደለበስች
ስለሆነ አለባበሷ ወዴትም ብትሄድ አያሳፍራትም፡፡ ከቦርሳ በስተቀር የሚቀራት ነገር የለምና :: አንገቷ ላይ ቀላ ያለ ቡኒ ቀለም ያላት ስካርፍ አጣፍታለች፡፡
ለሆስፒታሉ እንግዳ ናት:: ታማ ልትታከም ወይም ታማሚ ልትጠይቅ እንኳ ገብታበት አታውቅም፡፡ ይሁን እንጂ ሆስፒታሉ አደናጋሪ ሁኔታ የለውም፡፡
ህንፃዎቹ በአንድ አካባቢ ችምችም ብለው የተሰሩ ናቸው። ቀሪው ደግሞ ወለል ያለ
ሜዳ፡፡ ቀጥታ ወደ ህንጻዎቹ ስትጠጋ የተጓዘችበት መንገድ ከድንገተኛ መቀበያ ክፍሎች አካባቢ አደረሳት።
ሰዓቱ ወደ ስምንት ተኩል ገደማ ይሆናል። በርካታ ህመምተኞት በአግዳሚ ወንበሮቻ ላይ ተቀምጠው ወረፋቸውን ይጠባበቃሉ፡፡ የህመምተኞቹ ጀርባ ቆም ብላ ወደ ቀኝ አቅጣጫ ስትመለከት ረጅም የመተላለፊያ ኮሪደር ታያት፡፡ ጎርደድ ልትልበት አስባ ጥቂት ከተራመደች በኋላ አሁን ወደ አስተዳደር አገልግሎት ሃላፊ» የሚል የቢሮ መለያ አነበበች፡፡
«አሃ! የባርኔ ቢሮ ይኸ መሆን አለበት» አለችና ቆም ብላ ወደ በሩ ስትመለከት ከኋላ በል የሰው እጅ ትክሻዋ ላይ ቸብ አደረጋት፤ ባርናባስ ወየሶ፣
ሽዋ'ዩ ድንግጥ አለች ። «እንዴ! አለህ እንዴ?» ስትል ጠየቀችው ምን እያለች እንደሆነ ለሷም ሳይገባት።
«የሸዋ ዛሬ ከየት ተገኘሽን»አለና ባርናባስ እጇን ጨብጦ እንደገና ደረት ልደረት ተሳሳመ።: ባርናባስ ሸዋዬን ሲያቆላምጥ የሸዋ እያለ ነው፡፡
«ጉብኝት መጥቼ::» አለችው ሸዋዬ ሳቅ እያለች።
ጥሩ ነዋ! የሚጎበኝም ሞልቷል የሚያስጎበኝም አለ።» አላት ባርናባስ እጁን ትክሻዋ ላይ ጣል አድርጎ በረጅም ቁመቱ ቁልቁል እየተመለከታት፡፡
«አለፈልኛ! ኪኪኪኪ ……!
እኔ ጋ ነው የመጣሽው?» ሲል ጠየቃት እሷንም ቢሮውንም ተራ በተራ እየተመለከተ፡
«አይ!» ሽዋዬ ተሽኮረመመች።
«ቢሮዬ አጠገብ ቆመሽ ሳገኝሽ ጊዜ እኮ ነወ፡፡ ጎራ በያ፣ ሻይ በና ልበልሽ»
«በዚህ ሙቀት ሻይ ቡና?»
«ለስላሳም ይኖራል»::አለና ባርናባስ እጇን ይዟት ወደ ቢሮው አመራ::
በሽዋዬ ዓይን የባርናባስ ቢሮ ልዩ ነው፡፡ ስፋቱ፣ ጽዳቱ፣ የመስኮቶቹ
መጋረጃዎችና የወለለ ምንጣፍ ዓይን ይማርካሉ፡፡ የመጋረጃው ቀለም ነጣ ያለ ብርቱካናማ ነው ለቢሮው ልዩ ብርሃን ሰጥቶታል፡፡ እንግዳ መቀበያው ጠረጴዛ
ስፋትና የወንበሮቹ ብዛት አስደነቃት፡፡ በቢሮው የግድግዳ ጥግ ዙሪያ ተጨማሪ ወንበሮችም አሉ፡፡ ያቤሎ ጤና ጣቢያ ውስጥ በነበረበት ጊዜ በአንድ ጠበብ ባለች ክፍል ውስጥ ከአንድ ሜትር የማትበልጥ ጠረጴዛውንና የሚቀመጥባትን ደረቅ
ወንበር አስታውሳ ስታወዳድር አሁን ግን ገነት ወስጥ እንደገባ ቆጠረችው::
«አንተ! ቢሮህ ግን እንዴት ያምራል!?» አለችው የቢሮውን ዙሪያ በዓይኗ እየቃኘች፡፡
ከዚህ የበለጠ ስንት ዓይነት ቢሮ አለ እባክሽ! ደሞ ይኸ ቢሮ ሆኖ?» አለና ወንበር ሳብ አድርጎ እንድትቀመጥ ጋበዛት።
«ጡር አትናገር»
ባርናባስ በእንግዳ መቀበያው ጠረጴዛ ላይ ከሸዋዬ ፊትለፊት ቁጭ አለና በደወል ተላላኪ ጠርቶ ለእሱ ቡና ስሸዋዬ ለስላሳ አዘዘ
«ይኸ ሁሉ ወንበር ምን ያረጋል?» ስትል ጠየቀችው፡፡
ህእ! የባለ ስልጣን ቢሮ እኮ ነው፣ ስንት ዓይነት ስብሰባ የሚካሄድበትና ውሳኔ የሚሰጥበት። አለና ባርናባስ በተቀመጠበት ላይ ፈነስነስ አለ።
በምን በምን ጉዳይ ላይ ትወስናለህ?»
«በፖለቲካ በትይ፥ በአስተዳደር ጉዳይ ብትይ፣ በደረጃ ዕድገት፣
በዲስፕሊን.…ወዘተ!» አለና ሽዋዬን ፈገግ ብሎ እያየ በቀልድ ዓይነት አነጋገር፣
«በፍቅር ላይ ብቻ ነው መወሰን ያቃተኝ!» አለና ሃሃሃሃ…» ብሎ ለራሱ ስቆ ሸዋዬንም አሳቃት፡፡
«ስትልን» አለች ሽዋዪ በቅንድቧ ስር እያየችው፡፡
«የምወዳት ሴት እንዳትጠላኝ አድርጌ መወሰን! ሃሃሃሃ….
«ውይ አልቀረብህም»
"ያን ማድረግ ብችል ኖሮ አንቺ መች ታመልጪኝ ነበር» አለና እንደ ቁም ነገር አድርጎ ግን የሸዋ፡ ይህን ያህል ወራት ዲላ ውስጥ ስትኖሪ እንዴት ወደ ቢሮው ሄጄ ልጠይቀው አላልሽም?» ሲል ጠየቃት፡፡
«ሆሆይ! ደሞ የሰው ባል ለአለፈውም ይቅር ይበለኝ፡፡ ያም ቢሆን ሳላውቅ ያደረኩት ስለሆነ ኩነኔው የአንተ ነው፡፡» አለችና የቀረበላትን ሚሪንዳ ጎንጨት
አለች፡፡
ባርናባስ በስጨት እንዳለ ዓይነት እጁን ወንጨፍ እያረገ የሸዋ ደሞ ዝም ብለሽ ነው፣ ይኸን ሚስት፣ ድስት፣ ትዳር ምናምን የምትይውን ነገር ለምን አትተይም? ፍቅር በትዳርና በስማኒያ ይገለጽ መስለሽ እንዴ?” አላት ቡናውን
እያማሰለ፡፡
«ብታርፍ ይሻልሃል» .
«በተለይ በአንቺ ነገር መቼም ቢሆን የምቆርጥ አይመስለኝም።
ግን ባለቤትህ ደህና ናት?»
«ለራሷ ትኖራለች።
«እዚህ ገባህ፣ ከዚያ ወጣህ አትለኝም!»
«መረን ለቃሃለቻ!»
«ኧረ ዛሬ ከየት ተገኘሽ የሽዋ? እስቲ ስለ አንቺ እንጨዋወት?» ብሎ ቡናውን ፉት አለ፡፡
«አንተን ልጠይቅ ኪኪኪኪ...»
«ጎሽ የኔ ወለላ! አንቺ እኮ ዱሮም ቁም ነገርኛ ነሽ ሰውየው እኔ ሆኜ እንጂ» ብሉ ነገሩን ተወት ሲያደርገው ሽዋዬ ቀጠላች።
«ባትሆንስ?»
«ልብ ቢኖረኝ ኖሮ እግርሽ ላይ ወድቄ ይቅርታ መጠየቅ ነበረብኝ። ግን ዛሬነገ ስል» አለና ንግግሩን ቆረጥ አድርጎ አሁንም ቡናውን ፉት አለ፡፡
«ደሞ እንደገና?»
«የቆየ ነገር እኮ ሲታደስ ከበፊቱ ይበልጣል። ሃሃሃሃ…»
«ይልቅስ ስለ መጣሁበት ጉዳይ ልጠይቅህ!»
«ምን ልርዳሽ?»
«አንድ ሴት፣ በተለይ ልጃገረድ ማስወረድ አስማስወረዷን በሀኪም ምርመራ ማወቅ ይቻላል?» ስትል ጠየቀችው፡፡
«ሀኪሞችን አነጋግሮ መረዳት ይቻላል። ግን በዚህ ዙሪያ ምን ችግር ገጠመሽ?» ሲል ጠየቃት።
«በእናትህ ባርኔ ዶክተሮችን ጠይቅና ንገረኝ!»
«ማነጋገር እችላለሁ!»
«ይገርምሃል! በአንዲት እህቴ ገዳይ ተቸግሬአለሁ፡፡»
«አስወርዳ?»
«መሰለኝ፡፡»
«በአገር ባህል ወይስ በሀኪም?»
«አረ የእናንተ ሰራተኛ በሆነ ሰው!»
ደሞ የምን ባህል አመጣህ ያን ቤሆን ራሴ ተከታትዩ ለሕግ አቀርበው አልነበር? ያስቸገረኝ ብላ ሸዋዬ የተበሳጨች ለመምሰል ራሷን ወዘወዘች።
👍2
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“እምዬ ጐንደር እንግዳ ተቀባይ እኮ ናት።”
ጥላዬ፣ እምነቱንና ተስፋውን ጐንደር ላይ ጥሎ ሐሙስ ቀን እዚያች ብርቅየ ከተማ ገባ። ጨለማ የከተማዋን ሰማይ ለማልበስ በመጣደፍ ላይ
ነው። ጐንደሬዎች ቤታቸው ለመከተት ፈጠን ፈጠን እያሉ ሲራመዱ፣ጥላዬ፣ ብዛታቸው ብቻ ሳይሆን ዓይነታቸው አስደነቀው። እንደ ግሪኮች፣ አርመኖች፣ ህንዶችና አረቦች የመሳሰሉ የውጭ ሃገር ዜጎች ሕዝቡ መሃል ውር ውር ሲሉ፣ የቆዳቸው፣ የመልካቸውና የአለባበሳቸው
መለየት አስደመመው።
ጭቃ ምርጎቹን ባለሳር ክዳን ጎጆዎች ትክ ብሎ አያቸው። ባዘቶ
የለበሱ የሚመስሉ ዋንዛ ዛፎች ስር ችምችም ማለታቸውና እንደ ቋራ ተሰባጥረው አለመቀመጣቸው ገረመው። በየቦታው ጣል ጣል ያሉት
የድንጋይ ግንቦችና ነገሥታት ብቻ የታደሉባቸው የኖራ ቅብ ቤቶች
የከተማዋ ጌጥ መስለው ታዩት። ያየው ሁሉ ከቋራ የተለየ ሆነበት።
ጐንደር ልዩ ስፍራ ሆነችበት፤ አስገረመችው።
ዐዲስ ሕይወት ልትሰጠው ቃል ኪዳን ገባችለት። እየተዘዋወረ ከተማዋን ማየት ፈልጎ ጨለማው በፍጥነት ማደሪያ እንዲፈልግ አስገደደው። ቤተክርስቲያን ፍለጋ ዐይኑን ሲያዘዋውር፣ አንድ የቆሎ ተማሪ በፍጥነት ሲራመድ አየና ሮጦ ደረሰበት።
“ከርመህ ነው? ላገሩ እንግዳ፣ ለሰዉ ባዳ ነኝ። ማደሪያ ሚሆነኝ
ደጀሰላም ባገኝ ብየ” አለው።
“ኸደብረብርሃን ሥላሤ ማታድር? ምን የመሰለ ዛኒጋባ በቤተክሲያን
ዙሪያ እያለልህ። ወደዛው ነው ምኸድ፤ በል ና። አገርህ ወየት ነው?”
“እማር ብየ መጥቸ” አለ ጥላዬ፣ መናገር አልፈለገም።
“ጐንደር ደሞ ለትምርት። ኸየቦታው ሚመጡ ተማሮች፣ ሊቃውንት፣ ካህናትና መምህሮች ሁሉ ኸዝሁ ማዶል ያሉት?” ብሎ ነጫጭ ጥርሶቹን አሳየው፣ ተማሪው።
ገራ ገር ፈገግታው ጥላዬን ማረከው። ዕድሜ ልኩን የሚያውቀው መስሎ ተሰማው። ቀደም ብሎ ማደሪያውን ሲያስብ ባይተዋርነት የተሰማውን ያህል፣ ከትከሻው ሸክም እንደወረደ ሁሉ ቀለል አለው።
“ቅኔ ልትማር ነው የመጣህ?”
“ሥዕል ልማር ብየ ነው የመጣሁ።”
“ዛዲያ ጐንደር ምን ገዷት! እደብረብርሃን ሥላሤ መምህሮቹም ተማሮቹም አሉልህ፡፡”
ጥላዬ ተደሰተ። ተማሪው ገዱ ሆኖ ተሰማው። ልባዊ ፈገግታው ደግ
ሰው እጅ ላይ እንደወደቀ ጠቆመው። “ምን እየተማርህ ነው?” ሲል ጠየቀው።
“ቅኔ እየተማርሁ ነው። መወድስ እያኸድሁ ነው።”
“ደሕና አኸደሀል።”
“አንተስ ሞካክረኻል?”
“ሥላሤ ደርሻለሁ። ማድርበት ደጀሰላም የት አገኝ ይሆን እያልሁ?”
“ጐንደር መጥተህ ነው ስጋት ሚያድርብህ? አንተስ አለማወቅህ ...እምዬ ጐንደር እንግዳ ተቀባይ እኮ ናት። ሴቶች ወጥ ሲሰሩ ኸደረስህ
ይሽተዋል ብለው ሳትበላ ማትኸድባት አገር እኮ ናት። ጐንደር የሁሉ ናት፤ ማንም ኸየት መጣ ኸየት ቤቴ፣ የኔ ብሎ ሚኖርባት። አልሰማህም
እንዴ፣
ቤተስኪያን ስሞ ለመኖር፣
መልካም አገር ነው ጐንደር።
ሲባልላት?” እያለ ግጥሙን በዜማ አወረደለት።
ጥላዬ ሳቅ አለና፣ “ገና መድረሴ፣ ምኔ ሰምቸ? ጐንደሬ ሁሉ እንዳንተ
ጥሩ ነው?” ሲል ጠየቀው።
“እኔስ ኸተምብየን ነው የመጣሁ። ዐራት ዓመት አርጌያለሁ ኸዝኸ።”
ተማሪው ከላይ የደረበውን ለምድ፣ ትከሻው ላይ ያንጠለጠለውን
አኮፋዳና ለውሻ መከላከያ የያዛቸውን ሁለት በትሮች ጥላዬ ትክ ብሎ ተመለከተና ከልመና እንደመጣ ገባው። ወደ ቤተክርስቲያኑ ሲደርሱ
ደጀሰላሙን ተሳልመው ውስጥ ገቡ።
“እንዴት ያለ ቤተክሲያን ነው በል” አለው፣ ጥላዬ።
“አጤ አድያም ሰገድ ኢያሱ መዠመሪያ አሠሩትና ተቃጠለ። ኸዚያ በኋላ፣ ልዣቸው... ሦስተኛው ሚባሉት አጤ ዳዊት እንደገና አሠሩት።
እሳቸው ግና ባባታቸው ስም እንዲጠራ ስለፈለጉ እኔ አሰራዋለሁ ስሙ ግን ባባቴ ይሁን አሉ።”
ጥላዬ ፈዞ ቆሞ የቤተክርስቲያኑን አሰራር ሲያደንቅ ተማሪው፣ “እኛ
ስንገባ ስንወጣ ለምደነዋል። እንግዲህ አንዱን ጥግ ይዘህ ተኛ። ኸኛ ዘንድ ምኝታ የለም ሁኖ ነው” ብሎት ሄደ።
ጥላዬ ቤተክርስቲያኑን እንደገና ተሳልሞ ዙርያውን ሲመለከት፣
እየጨለመ በመምጣቱ በወንዶቹ መግቢያ በኩል ጭንቅላቱን ጉልበቶቹ መሃል ቀብሮ ተቀመጠ። ግቢው ጭር ብሏል። መንገድ ሲመሽበት፣
“ቤት ያብርሃሙ ሥላሤ ነው” እያሉ ቁርበት ጣል፣ ትኩስ ሽሮ እንጀራ
ላይ ፈሰስ አድርገውለት፣ አለበለዚያ ቆሎ እንዲቆረጥም ወይ ቂጣ እንዲያላምጥ ሰጥተውት ያሳደሩት ሁሉ ትዝ አሉት። ከነጋ እህል አፉ አላደረገም። ሆዱ ከረሀብ ብዛት ዋይ ዋይ አለበት፤ ያለማቋረጥ
አዛጋው።
በዕድሜ ከእሱ ትንሽ ከፍ ስለሚለው ተማሪ አሰበና ባይለየው መረጠ። ስሙን እንኳ ሳይጠይቀው በመሄዱ ተቆጨ። አንገቱን እንደደፋ ሲያሰላስል ድምፅ ሰማ። ቀና ሲል ተማሪዎች ወደ መማሪያ ቦታቸው ወደ ቤተክርስቲያኑ ጀርባ ይሄዳሉ። ተማሪው ከእነሱ ነጠል ብሎ ወደእሱ ሲመጣ አየው። ሁለመናው ተበራታ።
“ራት ቢጤ አመጣሁልህ። የውሃ ቅሌን ልተውልህና ገሠሣ ሲያበቃ
መጥቸ ወስደዋለሁ። ስትተኛ ኸዚሁ ተወው። አነሳዋለሁ” ብሎት
መንገድ ሲጀምር ጥላዬ ከተቀመጠበት ተነስቶ፣ “ሥላሤ ያክብሩልኝ።ስሜንም ሳልነግርህ... ጥላዬ እባላለሁ... ከቋራ ነው የዘለቅሁ” አለው::
ቀደም ብሎ አባቱ ፈልገው እንዳያገኙት ሲል ማንነቱን ደብቆ፣
አሁን የተማሪው ደግነት ምሥጢሩን አሟሸሸበት።
“በል ነገ ያገናኘን። አብርሃ ነው ስሜ። ገሠሣ እንዳያመልጠኝ
ብሎት ተማሪዎቹ ወደሄዱበት አቅጣጫ አመራ።
ጥላዬ፣ አብርሃ የሰጠውን ፍርፋሪ በልቶ፣ ውሃውን በላዩ ቸልሶና
አምላኩን አመስግኖ የመንገድ ድካም ስለተጫጫነው አንዱ ዛኒጋባ ጋ ተጠግቶ ጋደም እንዳለ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወሰደው።
ጠዋት ድምፅ ሲሰማ ብንን አለ። የት እንዳለ ለማወቅ ጥቂት ጊዜ
ወሰደበት። የሌሊቱ ብርድ፣ ልብሱን ውሃ የነካው አስመስሉታል። አንድ ጋቢ መኝታም ከላይ የሚለበስም ሆኖ አገልግሎታል። ከተቀመጠበት
ተነስቶ የቤተክርስቲያኑን መግቢያ በር ተሳለመና ወንዶቹ መግቢያ
ትይዩ ያለ አንድ ዋንዛ ዛፍ ስር ሄዶ ዳዊቱን አውጥቶ መድገም ጀመረ።
“አድረህ ነው?” የሚል ድምፅ ሲሰማ ቀና አለ። አብርሃ ነው ።
“ደሕና... ደሕና ... ይመስገነው።”
“አንደዜ ጠሎት ላድርስና ኸየንታ ሔኖክ ዘንድ ወስድሀለሁ” ብሎት
ሄደ።
ጥላዬ፣ በእሽታ ራሱን ነቀነቀለትና ወደ ዳዊቱ ተመለሰ። የዕለቱን
አድርሶ ሲጨርስ ዳዊቱን ማኅደሩ ውስጥ ጨምሮ፣ ስንጥር አንስቶ
መሬት ላይ መሞነጫጨር ጀመረ። እንደለመደው የወለተጊዮርጊስን ምስል ሊሥል ፈልጎ እዚያ ያደረሰው ምን እንደሆነ ትዝ ሲለው
ስንጥሩን ወረወረው።
ከቤት የወጣበት ምክንያት በመንገድ ድካምና በረሐብ በአእምሮው ውስጥ እየደበዘዘ መጥቶ ነበርና አሁን ቁጭ ሲል ሁሉ ነገር ፊቱ ላይ ድቅን አለበት። ወለተጊዮርጊስ ጐንደር መግባት ከለመግባቷን የማወቅ ፍላጎቱ ጸና። እሷ ሐር ቀሚስ ለብሳ ከቤት እንደወጣችው ሳይሆን፣ እሱ
እሑድ ቤተክርስቲያን ስትሳለም እንደሚያያት የዐዘቦት ልብሷን ለብሳ፣ ነጠላ ተከናንባ በበቅሎ ስትሰግር በዓይነ ኅሊናው ታየው፤ ሆዱ ባባ።
ያርባ ቀን ዕድሌ ነው እንግዲህ ምን አረጋለሁ? አለ፣ ለራሱ።
እናቱንና አባቱን አስታወሰ። በእሱ መጥፋት እናቱ እንዴት ጨርቃቸውን እንደሚጥሉ አሰበና ሆድ ባሰው። አባቱም ቢሆኑ አመል ሆኖባቸው ይነዛነዙ እንጂ፣ የእሱ ነገር እንደማይሆንላቸው ያውቃልና ጉዳታቸው ተሰምቶት ለመጀመሪያ ጊዜ አዘነላቸው። ሳያስበው ፊቱ በእንባ ርሷል። በጋቢው ፊቱን ጠራርጎ ቀና ሲል አብርሃ ፊቱ ቆሟል።
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“እምዬ ጐንደር እንግዳ ተቀባይ እኮ ናት።”
ጥላዬ፣ እምነቱንና ተስፋውን ጐንደር ላይ ጥሎ ሐሙስ ቀን እዚያች ብርቅየ ከተማ ገባ። ጨለማ የከተማዋን ሰማይ ለማልበስ በመጣደፍ ላይ
ነው። ጐንደሬዎች ቤታቸው ለመከተት ፈጠን ፈጠን እያሉ ሲራመዱ፣ጥላዬ፣ ብዛታቸው ብቻ ሳይሆን ዓይነታቸው አስደነቀው። እንደ ግሪኮች፣ አርመኖች፣ ህንዶችና አረቦች የመሳሰሉ የውጭ ሃገር ዜጎች ሕዝቡ መሃል ውር ውር ሲሉ፣ የቆዳቸው፣ የመልካቸውና የአለባበሳቸው
መለየት አስደመመው።
ጭቃ ምርጎቹን ባለሳር ክዳን ጎጆዎች ትክ ብሎ አያቸው። ባዘቶ
የለበሱ የሚመስሉ ዋንዛ ዛፎች ስር ችምችም ማለታቸውና እንደ ቋራ ተሰባጥረው አለመቀመጣቸው ገረመው። በየቦታው ጣል ጣል ያሉት
የድንጋይ ግንቦችና ነገሥታት ብቻ የታደሉባቸው የኖራ ቅብ ቤቶች
የከተማዋ ጌጥ መስለው ታዩት። ያየው ሁሉ ከቋራ የተለየ ሆነበት።
ጐንደር ልዩ ስፍራ ሆነችበት፤ አስገረመችው።
ዐዲስ ሕይወት ልትሰጠው ቃል ኪዳን ገባችለት። እየተዘዋወረ ከተማዋን ማየት ፈልጎ ጨለማው በፍጥነት ማደሪያ እንዲፈልግ አስገደደው። ቤተክርስቲያን ፍለጋ ዐይኑን ሲያዘዋውር፣ አንድ የቆሎ ተማሪ በፍጥነት ሲራመድ አየና ሮጦ ደረሰበት።
“ከርመህ ነው? ላገሩ እንግዳ፣ ለሰዉ ባዳ ነኝ። ማደሪያ ሚሆነኝ
ደጀሰላም ባገኝ ብየ” አለው።
“ኸደብረብርሃን ሥላሤ ማታድር? ምን የመሰለ ዛኒጋባ በቤተክሲያን
ዙሪያ እያለልህ። ወደዛው ነው ምኸድ፤ በል ና። አገርህ ወየት ነው?”
“እማር ብየ መጥቸ” አለ ጥላዬ፣ መናገር አልፈለገም።
“ጐንደር ደሞ ለትምርት። ኸየቦታው ሚመጡ ተማሮች፣ ሊቃውንት፣ ካህናትና መምህሮች ሁሉ ኸዝሁ ማዶል ያሉት?” ብሎ ነጫጭ ጥርሶቹን አሳየው፣ ተማሪው።
ገራ ገር ፈገግታው ጥላዬን ማረከው። ዕድሜ ልኩን የሚያውቀው መስሎ ተሰማው። ቀደም ብሎ ማደሪያውን ሲያስብ ባይተዋርነት የተሰማውን ያህል፣ ከትከሻው ሸክም እንደወረደ ሁሉ ቀለል አለው።
“ቅኔ ልትማር ነው የመጣህ?”
“ሥዕል ልማር ብየ ነው የመጣሁ።”
“ዛዲያ ጐንደር ምን ገዷት! እደብረብርሃን ሥላሤ መምህሮቹም ተማሮቹም አሉልህ፡፡”
ጥላዬ ተደሰተ። ተማሪው ገዱ ሆኖ ተሰማው። ልባዊ ፈገግታው ደግ
ሰው እጅ ላይ እንደወደቀ ጠቆመው። “ምን እየተማርህ ነው?” ሲል ጠየቀው።
“ቅኔ እየተማርሁ ነው። መወድስ እያኸድሁ ነው።”
“ደሕና አኸደሀል።”
“አንተስ ሞካክረኻል?”
“ሥላሤ ደርሻለሁ። ማድርበት ደጀሰላም የት አገኝ ይሆን እያልሁ?”
“ጐንደር መጥተህ ነው ስጋት ሚያድርብህ? አንተስ አለማወቅህ ...እምዬ ጐንደር እንግዳ ተቀባይ እኮ ናት። ሴቶች ወጥ ሲሰሩ ኸደረስህ
ይሽተዋል ብለው ሳትበላ ማትኸድባት አገር እኮ ናት። ጐንደር የሁሉ ናት፤ ማንም ኸየት መጣ ኸየት ቤቴ፣ የኔ ብሎ ሚኖርባት። አልሰማህም
እንዴ፣
ቤተስኪያን ስሞ ለመኖር፣
መልካም አገር ነው ጐንደር።
ሲባልላት?” እያለ ግጥሙን በዜማ አወረደለት።
ጥላዬ ሳቅ አለና፣ “ገና መድረሴ፣ ምኔ ሰምቸ? ጐንደሬ ሁሉ እንዳንተ
ጥሩ ነው?” ሲል ጠየቀው።
“እኔስ ኸተምብየን ነው የመጣሁ። ዐራት ዓመት አርጌያለሁ ኸዝኸ።”
ተማሪው ከላይ የደረበውን ለምድ፣ ትከሻው ላይ ያንጠለጠለውን
አኮፋዳና ለውሻ መከላከያ የያዛቸውን ሁለት በትሮች ጥላዬ ትክ ብሎ ተመለከተና ከልመና እንደመጣ ገባው። ወደ ቤተክርስቲያኑ ሲደርሱ
ደጀሰላሙን ተሳልመው ውስጥ ገቡ።
“እንዴት ያለ ቤተክሲያን ነው በል” አለው፣ ጥላዬ።
“አጤ አድያም ሰገድ ኢያሱ መዠመሪያ አሠሩትና ተቃጠለ። ኸዚያ በኋላ፣ ልዣቸው... ሦስተኛው ሚባሉት አጤ ዳዊት እንደገና አሠሩት።
እሳቸው ግና ባባታቸው ስም እንዲጠራ ስለፈለጉ እኔ አሰራዋለሁ ስሙ ግን ባባቴ ይሁን አሉ።”
ጥላዬ ፈዞ ቆሞ የቤተክርስቲያኑን አሰራር ሲያደንቅ ተማሪው፣ “እኛ
ስንገባ ስንወጣ ለምደነዋል። እንግዲህ አንዱን ጥግ ይዘህ ተኛ። ኸኛ ዘንድ ምኝታ የለም ሁኖ ነው” ብሎት ሄደ።
ጥላዬ ቤተክርስቲያኑን እንደገና ተሳልሞ ዙርያውን ሲመለከት፣
እየጨለመ በመምጣቱ በወንዶቹ መግቢያ በኩል ጭንቅላቱን ጉልበቶቹ መሃል ቀብሮ ተቀመጠ። ግቢው ጭር ብሏል። መንገድ ሲመሽበት፣
“ቤት ያብርሃሙ ሥላሤ ነው” እያሉ ቁርበት ጣል፣ ትኩስ ሽሮ እንጀራ
ላይ ፈሰስ አድርገውለት፣ አለበለዚያ ቆሎ እንዲቆረጥም ወይ ቂጣ እንዲያላምጥ ሰጥተውት ያሳደሩት ሁሉ ትዝ አሉት። ከነጋ እህል አፉ አላደረገም። ሆዱ ከረሀብ ብዛት ዋይ ዋይ አለበት፤ ያለማቋረጥ
አዛጋው።
በዕድሜ ከእሱ ትንሽ ከፍ ስለሚለው ተማሪ አሰበና ባይለየው መረጠ። ስሙን እንኳ ሳይጠይቀው በመሄዱ ተቆጨ። አንገቱን እንደደፋ ሲያሰላስል ድምፅ ሰማ። ቀና ሲል ተማሪዎች ወደ መማሪያ ቦታቸው ወደ ቤተክርስቲያኑ ጀርባ ይሄዳሉ። ተማሪው ከእነሱ ነጠል ብሎ ወደእሱ ሲመጣ አየው። ሁለመናው ተበራታ።
“ራት ቢጤ አመጣሁልህ። የውሃ ቅሌን ልተውልህና ገሠሣ ሲያበቃ
መጥቸ ወስደዋለሁ። ስትተኛ ኸዚሁ ተወው። አነሳዋለሁ” ብሎት
መንገድ ሲጀምር ጥላዬ ከተቀመጠበት ተነስቶ፣ “ሥላሤ ያክብሩልኝ።ስሜንም ሳልነግርህ... ጥላዬ እባላለሁ... ከቋራ ነው የዘለቅሁ” አለው::
ቀደም ብሎ አባቱ ፈልገው እንዳያገኙት ሲል ማንነቱን ደብቆ፣
አሁን የተማሪው ደግነት ምሥጢሩን አሟሸሸበት።
“በል ነገ ያገናኘን። አብርሃ ነው ስሜ። ገሠሣ እንዳያመልጠኝ
ብሎት ተማሪዎቹ ወደሄዱበት አቅጣጫ አመራ።
ጥላዬ፣ አብርሃ የሰጠውን ፍርፋሪ በልቶ፣ ውሃውን በላዩ ቸልሶና
አምላኩን አመስግኖ የመንገድ ድካም ስለተጫጫነው አንዱ ዛኒጋባ ጋ ተጠግቶ ጋደም እንዳለ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወሰደው።
ጠዋት ድምፅ ሲሰማ ብንን አለ። የት እንዳለ ለማወቅ ጥቂት ጊዜ
ወሰደበት። የሌሊቱ ብርድ፣ ልብሱን ውሃ የነካው አስመስሉታል። አንድ ጋቢ መኝታም ከላይ የሚለበስም ሆኖ አገልግሎታል። ከተቀመጠበት
ተነስቶ የቤተክርስቲያኑን መግቢያ በር ተሳለመና ወንዶቹ መግቢያ
ትይዩ ያለ አንድ ዋንዛ ዛፍ ስር ሄዶ ዳዊቱን አውጥቶ መድገም ጀመረ።
“አድረህ ነው?” የሚል ድምፅ ሲሰማ ቀና አለ። አብርሃ ነው ።
“ደሕና... ደሕና ... ይመስገነው።”
“አንደዜ ጠሎት ላድርስና ኸየንታ ሔኖክ ዘንድ ወስድሀለሁ” ብሎት
ሄደ።
ጥላዬ፣ በእሽታ ራሱን ነቀነቀለትና ወደ ዳዊቱ ተመለሰ። የዕለቱን
አድርሶ ሲጨርስ ዳዊቱን ማኅደሩ ውስጥ ጨምሮ፣ ስንጥር አንስቶ
መሬት ላይ መሞነጫጨር ጀመረ። እንደለመደው የወለተጊዮርጊስን ምስል ሊሥል ፈልጎ እዚያ ያደረሰው ምን እንደሆነ ትዝ ሲለው
ስንጥሩን ወረወረው።
ከቤት የወጣበት ምክንያት በመንገድ ድካምና በረሐብ በአእምሮው ውስጥ እየደበዘዘ መጥቶ ነበርና አሁን ቁጭ ሲል ሁሉ ነገር ፊቱ ላይ ድቅን አለበት። ወለተጊዮርጊስ ጐንደር መግባት ከለመግባቷን የማወቅ ፍላጎቱ ጸና። እሷ ሐር ቀሚስ ለብሳ ከቤት እንደወጣችው ሳይሆን፣ እሱ
እሑድ ቤተክርስቲያን ስትሳለም እንደሚያያት የዐዘቦት ልብሷን ለብሳ፣ ነጠላ ተከናንባ በበቅሎ ስትሰግር በዓይነ ኅሊናው ታየው፤ ሆዱ ባባ።
ያርባ ቀን ዕድሌ ነው እንግዲህ ምን አረጋለሁ? አለ፣ ለራሱ።
እናቱንና አባቱን አስታወሰ። በእሱ መጥፋት እናቱ እንዴት ጨርቃቸውን እንደሚጥሉ አሰበና ሆድ ባሰው። አባቱም ቢሆኑ አመል ሆኖባቸው ይነዛነዙ እንጂ፣ የእሱ ነገር እንደማይሆንላቸው ያውቃልና ጉዳታቸው ተሰምቶት ለመጀመሪያ ጊዜ አዘነላቸው። ሳያስበው ፊቱ በእንባ ርሷል። በጋቢው ፊቱን ጠራርጎ ቀና ሲል አብርሃ ፊቱ ቆሟል።
👍15❤1