አትሮኖስ
282K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
488 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ

..የሞተ ተጎዳ እንዲሉ ከአደጋው መድረስ በኋላ ሳምንት እንኳን ሳይሞላ ሀዘን በረድ፤ ቀዝቀዝ እያለ ሄደ። ድንኳኖች ሁሉ ተነቃቅለው ወደ መጋዘን ተመለሱ፡፡ ሀዘንተኛ ሁሉ ወደ ሥራ ገባ፡፡ ከሩቅ የመጣ ሁሉ ወደየመጣበት ተመለሰ፡፡
እንባ ቆሞ በንፈር መምጠጥ ተተካ፡፡ መብረድ ቀርቶ ይባስ
እየተቀጣጠለ የሚሄደው በሽዋዩ ቤት ውስጥ የተነሳው እሳት ብቻ።

ሔዋን ስደት ላይ ነች፥ በታፈሡ ቤት፡፡ አስቻለዉን በተመለከተ
የተፈጠረባት ጭንቅና ሥጋት በልሁ ከወደ አዲስ አበባ የስልክ መልዕክት ካስተላለፈበት ጊዜ ጀምሮ ቀለል ያለላት ቢሆንም የወደፊት አኗኗሯ ግን ጨለማ
ሆኖባታል። አስቻለው በደረሰበት አደጋ ምክንያት ወድ ክብረ መንግስት ያሰበችውን
ጉዞ ለጊዜው ትተዋለች። ግን ደግሞ ወደ ሸዋዬ ቤት መመለሻው መንገድ ይጨንቃታል። ሸዋዬ ለቤተሰቦቿ የፃፈችባት ደብዳቤም የጎን ውጋት ሆኖባታል።በስጋት እንቅልፍ አጥታ ተቸግራለች፡፡ መንፈሷም ዕረፍት አጥቷል።
ሽዋዬ በበኩሏ በተምታቱ ሀሳቦች ውስጥ ገብታ ራሷም ተምታቶባታል። በአስቻለው መትረፍ ባትከፋም ከመትረፉ ጋር ተያይዞ የሚመጣባትን አደጋ
ስታስበው እንደ ገደል ፈርተዋለች:: ሔዋን አስቻለው ቤት በማደራ ምክንያት የወሰደችባትን ርምጃ ሲመለስ መስማቱ አይቀርምና ምናልባት አስቻለውም
ተናድዶ፤ ሔዋንም ወደ ቤቷ ለመመለስ ፈርታ በዚህ አጋጣሚ ቢጠቃለሉስ? ሽዋዬ ከቅናት በተጨማሪ ያ የምትፈራው የማህበራዊ ህይወት ቀውስ በአቋራጭ ከች ሊልባት ነው:: ከዚህ አደጋ ማምለጫዋ መንገድ አንድ ብቻ ሆኗል! እስቻለው
ህክምናውን ጨርሶ ሳይመለስ ሔዋንን በዚያም በዚህም ብላ ወደ ቤቷ መመለስና በእጇ ማስገባት፡፡ ምንም እንኳ ቀልቧ የጠላቸው ቢሆንም ሔዋንን ከታፈሡ ቤት አምጥተው ለማስታረቅ የሚችሉ ወይዘሮ ዘነቡ ብቻ መሆናቸውን በማመን ተስፋዋን በእሳቸው ላይ ጣለች። ልክ አደጋው በደረሰ ሳምንት በዕለተ ሐሙስ ዓይኗን በጨው
አጥባ ወደ ቤታቸው ጎራ በማለት
«እማማ ዘነብ!» አለቻቸው።
«ወይ የኔ ልጅ»
«መቼም የሰሞኑን ጉዴን ሳይሰመት አይቀሩም»
«የምን ጉድ?» አሏት ሆዳቸው እየጠረጠረ ነገር ግን እሷው ትዘርዝረው በሚል ሐሳብ።
«እህቴን ከቤት እንዳባረርኩ አልሰሙም?»
«መስማቱን ሰማሁ ልጄ! ግን ምን አድርጋ ይሆን?» አሉና ጉንጫቸውን በእጃቸው መዳፍ ደገፍ አድርገው ያዩዋት ጀመር።
«በጣም በጣም ባለገችብኝ፡፡»
«እንዴት?»
ሽዋዬ የነበረውን ሁኔታ ሁሉ ዝርዝር አድርጋ ከነገረቻቸው በኋላ «ታዲያ ይኸ አያናድድም እማማ ዘነብ?» ስትል ጠየቀቻቸው።

ወይዘሮ ዘነቡ ለሽዋዬ ጥያቄ መልስ ከመስጠት ይልቅ በውስጣቸው ይጉላላ ለነበረው ሀሳብ መልስ ለማግኘት ሲሉ «አሁን ታዲያ የት ነው ያለችው!» ሲሉ ጠየቋት።

«አንድ ታፈሡ የምትባል መርዝ አለች፡፡ እሷ ጋር ሳትሆን አትቀርም፡፡»
ወይዘሮ ዘነቡ በሽዋይ አነጋገር ውስጣቸው ቅይም አለ፡፡ ታፈሡን
ያውቋታልና የመርዘኛነት ባህሪ እንደሌላት ያውቃሉ፡፡ ይልቁንም ሲያዩዋትም ሆነ ሲያነጋግሯት ደስ ትላቸዋለች፡፡ የተዋወቁትም እዚያው ሽዋዬ ጋ ስትመጣ በነበረበት ወቅት ነው፡፡ አሁንም የሆዳቸውን በሆዳቸው አድርገው፡-
«ያቺ ደርባባ ጓደኛሽ?» ሲሉ ጠየቋት፡፡
«አንዳች ያንደርባትና ሲያዩዋትማ ትመስላለች፡፡» አለችና ሽዋዬ ከንፈሯን ንክስ አድርጋ ወደ ሰማይ አንጋጣ ማየት ጀመረች። ወይዘሮ ዘነቡ ግን ታፈሡን ….ደርባባ የምትመስሰው፡ በማለት ብቻ ሊረኩ አልቻሉም፡፡ እንደው ጥሎብኝ እወዳታለሁ ልጄ! ከመልክ ቢሉ መልክ፣ ከጠባይ ቢሉ ጠባይ፣ ትትናውንም ሁሉ
አስተካክሎ አንድዬ የሰጣት እመቤት» በማለት ለታፈሡ ያላቸውን ትክክለኛ ስሜት
ከገለፁ በኋላ «ከአንቺስ ጋር ሰላም አልነበራችሁም ነበር እንዴ?» ሲሉ ጠየቋት፡፡
«በዚችው በእህቴ የተነሳ ተጣላን፡፡» አለቻቸው ወይዘሮ ዘነቡ ስለ ታፈሡ የሰጡት አስተየየት ሆድ ሆዷን እየቆጫት፡፡ «እሷ አይደለች እህቴን እንደ ዓይን
እልም አድርጋ ያጠፋችብኝ» ብላ ፊቷን ወደ ወይዘሮ ዘነቡ መሰስ በማድረግ «አሁን ሽማግሌ ሁኑኝ፤» አለቻቸው፡፡
«የምን ሽምግልና?»
ይቺኑ እህቴን ከተወሽቀችበት ጎትተው ቢያወጡልኝ ብዬ ነዋ!
ያለበለዚያማ ትምህርቷም መቋረጡ ነው::»
ወይዘሮ ዘነቡ አሁንም ጉንጫቸውን በመዳፋቸው ደገፍ አድርገው ረጋ ባለ አነጋገር «ሰማሽ ልጄ!» አሏት ከአንገታቸው ዘንበል ብለው እያዩዋት።

«እ»
«ከአንቺም በኩል ጥፋት አየሁ፡፡»
«ምን አደረኩ?» አለቻቸው ሽዋዬ ፊቷን ኮስተርተር በማድረግ እያየቻቸው፡፡
«መቸም ሁላችንም ልጅ ሆነን አድገናል። ልጅነት ደግሞ የተስፋ ዘመን ነው። ልጆች ሁሉን ነገር የሚያዩት በበጎ ነው። መስሎ የታያቸውን ነገር ከመፈጠም አይመለሱም። በተለይ ሴት ልጅ አንዴ እግሯ ከወጣ የልቧን ሳታደርስ አትመለስም::
ስለዚህ ዘመድ ነኝ የሚል ሰው ከፊት ከፊቷ እየቀደመ መንገዷን
ቢያመቻችላት ይሻላል እንጂ ተመለሽ ብሎ ከእሷ ጋር እልሀ መያያዝ… » ብለው ሳይጨርሱ ሸዋዬ አቋረጠቻቸው::
«አልገባኝም!» አለች ቆጣ ባለ አነጋገር፡፡
«ትዳር ሳትይዝ እንዳትጠንስ መላ መላውን መንገር፣ የወደደ ቢጠላት
ተበሳጭታ አንድ ነገር እንዳትሆን ማጥናናትና --» ብለው ሳይጨርሱ ሽዋዬ አሁንም ቀደመቻቸው
«ቁም ነገሩን ብናወራስ እማማ!»
«የማወራሽ ቁም ነገር መስሎኝ!» አሏት እሳቸወም መነፅራቸውን ወለቅ አድርግው አየት እያረጓት።
«ያ ሁሉ የሚሆነው በእጀ ስትገባ አይደል!?» አለቻቸው አስተያየታች
የንዴት መስሏት ደንገጥ እያለች።
«ቁም ነገሩ በእጅ ማስገባቱ ብቻ አይደለም፣ ተመልሳ እንዳትወጣ ማድረጉ ነው።ለነገሩ እህትሽም ዕድለኛ ሳትሆን አትቀርም፤ ከእጅሽ ብትወጣም መውደቂያዋ
ያማረ። ያ ልጅ ደግሞ ባለሙያና ረጋ ያለ የልጅ አዋቂ ነው፡፡ እንዳይለያዩ ድንግል ትርዳቸው እንጂ ሁሉቱም መልካም ልጆች ናቸው:» አሏት፡፡
ሸዋዬ የበለጠ ውስጧ ጨሰ፡ በሆዷ ላይ ይቺ ፈልፈላ አሮጊት አለቻቸው በወይዘሮ ዘነቡ ላይ ዓይኗን ስክት አድርጋ።
«ለመሆን የዚያች ጓደኛሽ ቤት የት ይሆን?» ሲሉ ወይዘሮ ዘነቡ በመሀል ጠየቋት። በዚህ ጊዜ ሽዋዬ ወደ ዋናው ቁምነገር የተመለሰላት መስሏት ልቧ ትንሽ
ተንፈስ አለና እኔ ወስጄ ከሩቅ አሳይዎትና እመለሳለሁ፡፡» አለቻቸው ትንፍሿ በርክቶ አፍንጫዋ ሳብ ረገብ እያለ፡፡
«ይሁን ደግ ልጄ፣ ትንሽ፣ ጠሐዩ በረድ ይበልና ሄጄ እሞክራለሁ::»
«እንደ ምንም ብለው ይዘዋት ይምጡ፣ አደራ!»
የዚያኑ ዕለት ከአመሻሹ አሥር ሰዓት አካባቢ ሽዋዬ ወይዘሮ ዘነቡን ከታፈሡ ቤት አካባቢ አድርሳቸው ወደ ቤቷ ተመለሰች። ነገር ግን የወይዘሮ ዘነቡ
አመለካከት ቅፍፍ አላት፡፡ ሔዋንን በእጇ የማስገባት ዓላማዋ ቢሰናከል ችግሩ የከፋ
እንዳይሆን ፈርታ እንጂ ሽምግልናቸውም ቢቀርባት በወደደች ነበር።
ወይዘሮ ዘነቡ ከታፈሡ ቤት ሲደርሱ ቀኑ አሥር ሠዓት አለፍ ብሏል።
ታፈሡና ሔዋን ሶፋ ላይ ቁጭ ብለው እንጀራ በትሪ አቅርበው ሲበሉ አገኟቸው።
አስቻለውን ለመጠየቅ አዲስ አበባ ሰንብተው ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ነው ከቤታቸው የደረሱት:: ቡናም እየተፈላ ነው፡፡እራት ነው ምሣ የምትበሉት?» እያሉ ወይዘሮ ዘነቡ ወደ ቤት ገቡ።
👍12
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ


....የወይዘሮ ዘነቡና የታፈሡ ውይይት በዚህ መልኩ እየተከናወነ ባለበት ሰአት
ሸዋዬ አልጋዋ ላይ ቁጭ ብላ በሁለት እጇ ጆሮ ግንዶቿን ጠፍራ በመያዝና አተርትራ በማሰብ ላይ ናት። ታፈሡንና ወይዘሮ ዘነቡን እያሰበች ልክ በመሀላቸው ቁጭ ብላ እንደምታዳምጣቸው ዓይነት ስለ እሷ ሲያወራ በሀሳቧ "ቀንታ ነው እኮ ተቀጥላ ይስሟታል!
ሰው እንዴት በእህቱ ይቀናል! አረ የሷ የብቻው ነው ። አስቻለውን እንደሆነ አታገኘው ምን ያስለፋታል?» የሚሏት ይመስላታል። ወይዘሮ
ዘነቡ ታፈሡን ሲያሞካሹ!
ለአስቻለውና ለሄዋን ለሔዋን ፍቅር መልካም ሲመኙ እሷ በእሳቸው ፊት የምታሳየውን ድንጋጤና የብስጭት ስሜት ለታፈሡ ዝርዝር አድርገው ሲያወሩባት ሁሉ ይታያታል፡፡ በዚያ ልክ ቅጥል ንድድ ትችላለች፡፡
ወይዘሮ ዘነቡ ግቢያቸው ውስጥ እንዴግቡ ወደ ቢታቸው ጎራ ሳይሉ
በቀጥታ ወደ ጓሮ ዞረው ወደ ሸዋዩ ቤት አመሩ። ሸዋዬ ድንገት የሰው ኮቴ ሰምታ ከአጎነሰችበት ቀና ስትል ወይዘሮ ዘነቡ ብቻቸውን ሲመጡ አየቻቻው። ወደ
ኋላቸው ዓይኗን ስታማትር ሔዋን የለችም። እንዴ አለችና እማማ ዘነብ! » ስትል ጠራቻቸው ገና ከሩቅ ሳሉ፡፡
«ወይ»
«አልተሳካሎትም?»
ወይዘሮ ዘነቡ ዝም ብለዋት ወደ ቤት ገቡና ዱካ ላይ ቁጭ ካሉ በኋላ ትሰሚያለሽ የኔ ልጅ!» አሏት ቀልብና ስሜቷን ሰብሰብ ለማድረግ፡፡
«እሺ» አለቻቸው በጉጉትና በፍርሀት ስሜት ተውጣ፡፡
ጓደኛሽም እህትሽሃም መልካም ሰዎች ናቸው። እህትሽ ጥፋቷን አምናለች፡፡ጓደኛሽም ተቆጥታለች። አንቺ የፈለግሽውን እርቅ እነሱ የበለጠ ፈልገውታል፡፡
እውነተኛ እርቅ ደግሞ አፍን ሳይሆን ልብን ከፍቶ ስለሆነ፣ ለዚህ ብርቱ ጉዳይ አንቺም ስትዘጋጂ እደሪና ነገ ሁለታችንም አብረን እንሂድና አንቺንም ከጓደኛሽ፣ እህትሽንም ከአንቺ በማስታረቅ ሁሉንም ነገር ፈጥሠን እንመጣለን። ከዚያ በኋላ እህትሽን ይዘናት እንመጣለን፡፡» ከማለት ውጭ ሌላ ምንም ሳይጨምሩ
ከተቀመጠበት ብድግ ብለው በይ ደህና እደሪl» ብለዋት ውልቅ አሉ፡፡
ሸዋዬ ድንግጥ አለች፡፡ እንዴ አለች በሆዷ፡፡ በዓይኗ ወይዘሮ ዘነቡን
እየተከተለች ይቺ አሮጊትና ያቺ ታፈሡ የምትባል መናጢ ምን ተማክረው ይሆን?' በማለት ብቻዋን ታወራ ጀመር። ሄደች በሀሳብ አሁንም ታፈሡ ከኔ ጋር
ታርቀ ሰላ እያለች ወደ ቤቴ በመምጣት የጀመረችውን ልትጨርስ!? እኔ ሳላውቅ
ከዚች አሮጊት ጋር ገጥማ ውስጥ ለውስጥ ሊያርዱኝ? በፍጹም ይህ የማይሆን ነው። ከታፈሡ ጋር እርቅ ብሎ ነገር የለም፡፡ ብቻ ያቺ ሰላቢ እህቴ እንደምንም ብላ
በእጄ ትግባልኝ፡፡ ይህ እንዲሆን የግድ ከታፈሡ ጋር ታረቂ ብባልም ለዚያች ቀን ብቻ በማግስቱ ግን አፈርሰዋለው በቃ።
ሸዋዬ ምሽቱን ሁሉ ስለዚሁ ስታስብ ቆይታ ሌሊቱንም ሳትረሳው መልሳ መላልሳ ስታመነዥገው አደረች። ፍላጎቷ አንድ! ሔዋንን በእጇ ማስገባት፤ ፉከራዋም እንድ፤ ከታፈሡ ጋር ፈጽሞ ከልብ ላለመታረቅ። ሀሳቧ ሁሉ ከዚሁ ሳይርቅ ሌቱ ነግቶ በጠዋቱ ፈረቃ ስራ ገባች፡፡
ከሰዓት በኋላ በታፈሡ ቤት የተያዘው የቀጠሮ ሠዓት ደረሰና ከወይዘሮ ዘነቡ ጋር ወደ ታፈሡ ቤት ጉዞ ጀመሩ።
«እማማ ዘነብ!» ስትል ጠራቻቸው ከጎናቸው ሆና እየተራመደች
«ወይ»
«ለመሆኑ ታፈሡ እኔን ምን አደረገችኝ እለችዎት?»
«እረ እሷ እቴ! ምንም ያለችው ነገር የለም::»
«ታዲያ ከእሷ ጋር መታረቁ ለምን አስፈለገ?»
«በአንቺ ሆድ ውስጥ ያለ ነገር ሊኖር ይችላል ብዬ ነዋ!»
«እሱማ ብዙ አለ። ግን ዝም ነው የምለው፡፡»
«ያማ ቂመኝነት ነው:: የነገር ብዛት ባይጠቅምም የቂም ቋጠሮ ካልተፈታ እርቅ አይኖርምና ቅር ያለሽን ነገር አጠር አርግሽ መግለጥ ይኖርብሻል፡፡»
«እኔና እሷን ያቀያየመን እኮ ይሄው የእህቴ ጉዳይ ነው::»
ወይዘሮ ዘነቡ ድንገት ቁጥት አሉ፡፡ «የእህትሽ ጉዳይ የአንቺና የእሷ ጉዳይ አይደለም የራሷ ብቻ ነው:: በእሷ አታሳቡ፤ ተዋት!! አሉ ጠበቅ ባለ አነጋገር፡፡
«እንዴት እማማ ዘነበ? እኔማ የእህቴ ጉዳይ ያገባኛል::»
«ስለምታበያትና ስለምታጠጫት ተሆነ ተሳስተሻል። ሆድ የትም ይሞላል፡፡
ጭንቅላት ግን ነጣነት የሚያገኝበትን መንገድ ይፈልጋል፡፡ አትሞኚ »
«መረን ልቀቂያት ነው የሚሉኝ!»
«ተይ አንቺ ልጅ! ኋላ እንዳልጠላሽ! እህትሽን እንኳን አንቺ እኔ አውቄአታለሁ፡፡ ሥነስራት ያላት ጨዋ ናት፡፡ የሆዷን አይታ ድንግል ያን የመሰለ ጨዋ ልጅ ሰጥታተለች:: እንደኔ ቢሆን በእነሱ መሀል ባትገቢ ጥሩ ይመስለኛል፡፡»
አሏት ፈርጠም ባለ አነጋገር፡፡
ሽዋዬ ወይዘሮ ዘነቡን ክፉኛ ጠላቻቸው፡፡ ዛሬ ሔዋንን በእጇ የማስገባት ዓላማ ባይኖርባት ኖሮ በዚያ ሠዓት ወደ ቤቷ ምልስ ብትል በወደደች ነበር፡፡ ከዚያ
በኋላ ፀጥ እንዳለች ከታፈሡ ቤት በር ላይ ደረሱ፡፡
የታፈሡ ቤት እንግዳ ለመቀበል ተዘጋጅቷል። ወለሉ ተወልውሎ- ፏ ብሏል::ከሰል ተያይዞ የቡና ዕቃዎች ቀርበዋል። ታፈሡም እምር ብላለች። ቀላ ያለ ጉርድ
ቀሚስ በነጭ ሽሚዝ ለብሳ ሀብሏ በደረቷ ላይ እንደ ፀሐይ ያበራል፡፡ ያን ረጅም የጥቁር ዞማ ፀጉሯን ጎንጉና በጀርባዋ ላይ ለቃዋለች፡፡ ወይዘሮ ዘነቡ ሸዋዬን አስከትለው ወደ ቤት ራመድ ሲሉ ፈልቀቅ ባለ ፈገግታ ተቀበለቻቸው፡፡ በዚያ
ሠዓት ሔዋን ድንግጥ ብላ ወደ ጓዳ ስትሮጥ ወይዘሮ ዘነቡ ተመልክተዋት ኖሯል።
«ዛሬ ፈርቶ መደበቅ፣ እኩርፎ መንጋደድ የለም፡፡» አሉና መሀል ወለል ላይ ቆመው «በሉ እናንተ ቀድማችሁ በይቅርባይነት ያለ ወቀሳ ተሳሳሙ፡፡» አሏቸው
ታፈሡና ሸዋዬን ግራና ቀኝ አየት አየት እያረጉ፡፡ ታፈሡ ሁለት እጆቿን ዘርግታ ወደ ሸዋዬ ጠጋ በማለት «ሸዋዬ!!
ከአጠፋሁ ይቅርታ!» ብላ እንገቷን እቅፍ አድርጋ በመሳም ጨመጨመቻት፡፡
ወይዘሮ ዘነቡ አጠገባቸው ቆመው «እሰይ እሰይ እልልል…» አሉ፡፡
ወይዘሮ ዘነቡ ታፈሡ በዚያ ዓይነት ፈገግታ እየሳመቻት ሳለች የሸዋዬ
ፊት ግን ፈታ አለማለቱ እያናደዳቸው ነገር ግን የጀመሩትን ለመጨረስ ሲሉ፡ «በይ ያቺንም አበባ ጥሪልኝ፡፡ በእህቷ እግር ላይ ትወደቅ» ብለው ሔዋን ወዳላችበት ጓዳ አይናቸውን ወረወሩ።
«አንቺ ሒዩ» ስትል ታፈሡ ተጣራችና ቀጥላም ነይ እማማ ዘነብ ይፈልጉሻል» ስትላት ሔዋን ሽቁጥቁጥ እያለች ከወደ ጓዳ ብቅ አሉች፡፡ ለአንዴም ቀና ሳትል አቀርቅራ በመራመድ ከመሀላቸው ደረሰችና ከሸዋዬ እግር ላይ ወደቀች፡፡ወይዘሮ ዘነቡና ታፈሡም እልልእልል» በማለት ዕርቁን አደመቁት ።
ወይዘሮ ዘነቡ አሁንም ሆዳቸው በገነ ሔዋን ያን ያህል በእግሯ ላይ
ስትደፋ ሸዋዬ ግን ለመግደርደር ስትል እንኳ ቀና እንድትል አልጋበዘቻትም።በሆዳቸው ምኗ ድንጋይ ናት በማሪያም አሉ፡፡
የእርቅ ስነ ሥርዓት በዚህ ሁኔታ ተጠናቆ ሔዋን ብቻ ወደ ጓዳ ፈጥና ስትመለስ ሶስቱም ሶፋ ላይ ቁጭ አሉ የታፈሡ ሠራተኛ ቡና መቁላት ጀምራለች
«ሰላም ነሽ ሸዋዬ!» አለቻት ታፈሡ ቀድማ ፈገግ ብላ እያየቻት»
«እግዜሔርን አይክፋው»
«ሰሞኑን እንደተበሳጨሽ ይገባኛል ሔዩ አጥፍታለች» አለቻት ታፈሡ
👍131