አትሮኖስ
280K subscribers
109 photos
3 videos
41 files
460 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_አስራ_ስድስት


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው

...አንዲት ስኬታማ የሆነች ተዋናይን አግብቶ እና ሁለት ወንድ ልጆችን ወልዶ
የሚኖር ቢሆንም ከላና ጋር የሚያደርገውን ወሲብ አልተወም፡፡

ላና በመስኮቱ ውጪውን አሻግራ እየተመለከተች
“ደውሎልኝም ሆነ ተገናኝተን አናውቅም” ብላ መለሰችላት፡፡

ላና እየዋሸች እንደሆነ ከሁኔታዋ የተረዳችው ኒኪም በጥያቄ አይን
ስትመለከት ላና ኒኪ እንድታምናት ብላ
ነገርኩሽ እኮ ስልኩን ብሎክ አድርጌዋለሁ፡፡ በቃ እሱን እንደሞተ ነው
የምቆጥረው።” አለቻት፡፡

“መቼ ነው ለመጨረሻ ጊዜ እሱን ያገኘሽው?” ብላ ኒኪ ጠየቀቻት፡፡

ላና ከፍተኛ የሆነ ንዴት ውስጥ ስትገባ በሚያዋርድ መልኩ ወሲብን ከተለያዩ ሰዎች ጋር እንደምትፈፅም ኒኪ ስለምታቅም ነበር ይህን ጥያቄ
የጠየቀቻት፡፡ ከእነዚህ እያወረዱ ከሚወስቧት ሰዎች ውስጥ ደግሞ አንዱ
የቀድሞ ፍቅረኛዋ ጆኒ ነው::

“ምናልባት ወር አልፎናል” ብላ ላና ዋሽቻት፡፡

“ላና ስለ መለወጥ በድጋሚ እንድታስቢ እና ለመለወጥ እንድትሞክሪም
እፈልጋለሁ፡፡ ይህ የቤት ሥራሽ ነው፡፡ ስሜቶችሽን እንዴት እንደምታስተውያቸው ማወቅ ይኖርብሻል፡፡ በቃ ንዴትሽን ባናደዱሽ ሰዎች ላይ ነው መሆን ያለባቸው እንጂ በሌሎች ሰዎች ላይ ንዴትሽን ለመወጣት መሞከረሽን ማቆም ይኖርብሻል፡፡” ብላ መከረቻት፡፡

“ምን እየሰራሽ እንዳለሽ አልገባኝም!” ብላ በንዴት መለሰችላት፡፡ ኒኪም “ሞክሪው እስቲ፡፡ ይህንን ሳምንት በዚህ መልኩ ስሜቶችሽን ለመግለፅ ጥረት አድርጊ፡፡” ብላት ስታሰናብታትም ላና ከህክምና ቢሮው የወጣችው ይበልጥ ተናድዳ በመሆኑ ኒኪ ላናን “ራስሽን ጠብቂ” አለቻት፡፡

ይህንን ማለቷ ደግሞ ትክክል ነው:: ምክንያቱም በዙሪያዋ ብዙ ሰዎች
እየሞቱ ነው:: ስለዚህም ታካሚዋ ላና ህይወቷን አደጋ ላይ የሚጥል ነገርን
እንድታደርግ አትፈልግም፡፡

ላና ግሬይ የኒኪ ቢሮ ከሚገኝበት ህንፃ የኪራይ መኪናዋን እየነዳች ስትወጣ ጉድማን ተመለከታት፡፡ ተዋናይዋ በጣም ብዙ ዕዳዎች እንዳሉባት ስለእሷ በሰበሰበው መረጃ መሰረት ለማወቅ በቅቷል፡፡ የቪክቶሪያ ቤክሀምንም
ከተዋሰችበት ቦታ መልሳ እና በስልክ ካወራችው ሰው ጋርም ወሲብ ፈፅማ ነው ወደ ኒኪ ቢሮ ያመራችው፡፡ ታዲያ ላና በጣም ብዙ ዕዳ ካለባት ከየት አምጥታ ነው ለኒኪ ሮበርትስ ክፍያዋን የምትፈፅመው?

አሁን ተከራይታ ወደምትኖርበት አፓርታማ እንደምትሄድ ግምቱን አስቀመጠ፡፡ ቤቷ ውስጥ ብቻዋን ነው የምትኖረው ታዲያ ቤቷ ገብታ ምን ታደርግ ይሆን? ምናልባት ከሌላ ከማታውቀው ሰው ጋር ታድር ይሆን ወይስ የሚያደነዝዛት መድሀኒት ትወስድ ይሆን? ምን አይነት አሳዛኝ
ህይወት ነው ያላት ብሎም በትንሹ አሰበ፡፡ ዛሬ ላይ እስኪበቃው ተከታትሎ
ውሎዋን ስላወቀ እና አስቀድሞም ስለ እሷ የሰበሰበው መረጃ በቂ ነው ብሎ
ስላሰበ አልተከተላትም::

ጉድማን ወደ ቤቱ ለመሄድ ለአምስት ደቂቃ ያህል መኪናውን እያሽከረከረ እያለ ስልክ ተደወለለት፡፡

“ሪፖርት የምታደርግልኝ አዲስ ነገር አለ?” ብሎ ጆንሰን ከዚያኛው ጫፍ ሲያወራ ድምፁ እየተቆራረጠ ስለነበር የሚገኝበት ቦታ ኔትወርኩ ጥሩ ያልሆነ ቦታ እንደሆነ አወቀ፡፡

ነገ አገኝህና አወራሃለሁ ብዬ ነው” ብሎ ጉድማን መለሰለት እና “እሺ አንተስ ጋር ወደ ብራንዶን ግሮልሽ ስለሚወስደው መንገድ ያገኘኸው አዲስ
ነገር አለ?”

“የለም። በቃ ነገ እንገናኛለን” ብሎ ጉድማን ስልኩን ዘጋው።

ጉድማንም ስልኩን ዘጋ እና በዩ ቅርፅ መኪናዋን በመጠምዘዝ ወደ
ሴትቸሪ ሲቲ መንዳት ጀመረ፡፡ ለሃያ ደቂቃ ያህል መኪናውን አቁሞ ሲጠብቅ ቆየ፡፡ ከሃያ ደቂቃ በኋላ ግን ኒኪ ሮበርትስ መርሴዲስ መኪናዋን ይዛ ከህንፃው ከሚገኘው ማቆሚያ ወጣች እና በጠባቡ መንገድ አድርጋ ስታርስ ተብሎ በሚጠራው አስፋልት መንገድ ላይ መርሴዲሷን በፍጥነት መንዳት ጀመረች፡፡
መርማሪ ፖሊስ ሉው ጉድማንም የመኪናውን ሞተር በድጋሚ አስነስቶ
እና ከተደበቀበት መኪናዎች ውስጥ ሾልኮ በመውጣት ይከተላት ጀመር።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
አኔ ቤታማን የቫዩሊን መምቻውን ዘንግ አጥብቃ በመያዝ ከቫዩሊኑ ክር ላይ አሳረፈችው። አኔ ቫዩሊኗን የምታየው እንደ ምርጥ ጓደኛዋ እና እንደ
ፍቅረኛዋ ጭምር ነው። ቫዩሊኑ በመጀመሪያው 18ኛው ክፍለ ዘመን የተሠራ እና ምርጥ ከሚባሉ የዕደ ጥበብ ውጤቶች መካከል አንዱ መሆኑ ያስታውቃል። ባሏ ቫዩሊኑን በስጦታ መልክ ያበረከተላት ከተጋቡ ከሳምንት
በኋላ ነበር።

“ግን እኮ ይሄ ዋጋው በሚሊየን ዶላር የሚቆጠር ነው!” ብላ በስጦታው በጣም ተደስታ በራሱ ጥበብ በተሞላበት መልኩ የተሠራውን የቫዩሊን መያዥውን ጭምር በደስታ እየተመለከተች “በጣም ውብ ነው” አለችው በደስታ እየፈነደቀች።

“ልክ እንደ አንቺ አላት የአኔ ባል እሷን በጣም ስላስደስታት ደስ እያለው።

ሀይቲ ውስጥ የጫጉላ ሽርሽራቸው ላይ ነበር እንግዲህ ቫዩሊኑን በስጦታ
ያበረከተላት። እንግዲህ ስጦታውን ከተቀበለች ስምንት ዓመት አለፋት ማለት
ነው። 'ይገርማል ብላ እያሰበች አኔ ውዱን ቫዩሊን ጥብቅ አድርጋ እንደያዘችው አንድ አንድ ቀናት ደግሞ አሉ 80 ዓመት ያህል የሚረዝሙ አለች ለራሷ።

የዴስኒ ኮንሰርት አዳራሽ ውስጥ ለኦርኬስትራ በተመደበው ቦታ ላይ
ቁጭ ብላለች። የመጀመሪያው ሪኸርሳል ሲጀመር ትንሽ ጊዜ ነው የቀረው።

አኔ የኮንሰርት ላይ ቫዩሊን ሙዚቃዎችን አበጥራ የምታውቅ እና የምትጫወት ምርጥ ሙዚቀኛ ናት፡፡ ግን ያው ሁሌም ትላልቅ ኮንሰርቶች ላይ ሙዚቃዋን ስታቀርብ የሚሰማት የደስታ እና የፍርሃት ስሜት ተቀላቅለው ነው። ስለዚህ ፍርሃቷ ለዶክተር ሮበርትስ ነግራት ነበር። ግን
ኒኪ (ኒኪ ብለሽ ጥሪኝ ብላ ነግራታለች) የፍርሃት ስሜቷን ከአኔ ባል ጋር አያይዛ ነበር የመለሰችላት፡፡ ኒኪ ለአኔ ስለ ባሏ የምትነግራት “ወደ ኋላ መንሸራተት” በሚል ሀረግ ነበር።

“ምን ያህል ረዥም ርቀት ተጉዘሽ እንደመጣሽ አስቢው እስቲ” ብላ ኒኪ
በመቀጠልም “ይሄንን ነፃነትሽን ለማግኘት ምን ያህል ዋጋ እንደከፈልሽ
አስቢው እስቲ፡፡ እና እንደዚህ ብዙ የለፋሽለትን ነገር በመተው እሱን ወደ
አንቺ ህይወት ለማስገባት ትፈልጊያለሽ?”

“በእውነቱ እኔ አላውቅም” ብላ አኔ ከልቧ መለሰችላት።

“ለምን ይህን ነገር እንደምታደርጊ እስኪ ራስሽን ጠይቂው?” ብላ ኒኪ
በማስከተልም
“እውነቱን ነው” ብላም አኔ ለኒኪ ነግራት ነበር የቴራፒ አገልግሎትን እያገኘች በነበረችበት ጊዜ ላይ፡፡ “ደግሞም በጊዜው እንዳለው አድርጎልኝ
ነበር፡፡ በእውነቱም ሞክሮ ነበር” ብላት ነበር ከባሏ ጋር አብረው ስላሳለፉት
የደስታ ጊዜ በማስታወስ፡፡

ነገር ግን የአኔ ባል በተፈጥሮው ሰዎችን መቆጣጠር የሚወድ ሰው ነበር፡፡ ይህንን ነገሮችንም ሆነ ሰዎችን የመቆጣጠር ተፈጥሮውን ደግሞ ሊያስወግደው አይችልም። ለአዲሱ ወጣት ሚስቱ ያለውን ፍቅር ውስጡ የነበረውን ፍላጎቱን በማነሳሳቷም ይህንን ስሜቱን እና እሷን ጭምር እንዲፈራት ሆኗል። ስለዚህም ከጥቂት ወራት በኋላ በዙሪያዋ አጥር
ማጠሩን ጀመረ፡፡ በመጀመሪያ ላይ ጥቂት የመረጣቸው ኮንሰርቶች ላይ ብቻ
ሙዚቃዋን እንድትጫወት ይፈቅድላት የነበረ ቢሆንም በኋላ ላይ ግን
የትኛውም ኮንሰርቶች ላይ ሙዚቃ እንዳትጫወት ከለከላት፡፡

“የእኔ መልአክ በዚህ ዓመት ፓሪስ አትሂጂ” “ለምንድን ነው ፓሪስ ሄጄ ሙዚቃ የማልጫወተው?” ብላ ኮስተር ብላ ትመለከተው እና
“የግድ መሄድ ይኖርብኛል፡፡ ልጫወት ቀጠሮ ይዤያለሁ፡፡”

“አይሆንም” ብሎ እጁን እያወናጨፈም “እዚያ እኮ በጣም ሩቅ ነው
👍4
#የወድያነሽ


#ክፍል_አስራ_ስድስት


#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል

....የማለዳዋ የጥር ወር ፀሐይ በመሬት ወለል አካባቢ ከየሚዳው! ከየተራራው፣ ከየዛፉ፣ ከየቤቱ፣ ከየጉራንጉሩ ቀዝቃዛ አየር ጋር ትንቅንቅ ገጥማለች። ተፈጥሮ ራሷን በራሷ የምታስተካክልበትና የምትለዋውጥበት ተፈራራቂ ኃይል ስላላት ቀዝቃዛው አየሩ ቀስ በቀስ ተረታ። ለውጥ የተፃራሪ ኃይሎች የግብግብ ውጤት ነው::

በእኔ ሕይወት ውስጥ ግን ጎልቶ የሚጠቀስ ለውጥ ባለመገኘቱ ሕሊናዩ
እየቀዘቀዘ ከመሔድ በቀር የብርታት ለውጥ አልታየብኝም፡፡ ከመኝታዬ ተነሥቼ
ልብሴን ስለባብስ ሰውነቴ ቀነቀነኝ፡፡ እውነተኛዎቹ የሐሳቤ ቅንቅኖች ግን አንጎሌ ውስጥ ይርመሰመሳሉ። የሥራ ቀን ነበር፡፡

መንገዱ የሚያልቅልኝ ስላልመስለኝ ቀደም ብዬ ተነሣሁ፡፡ ወደ ሕጋዊ ፍርድ ቤት ሳይሆን ወደ ግፈኞች የመከራ ሽንጎ የምገሠግሥ መሰለኝ፡፡ ከአራት ኪሎ እስከ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያለውን ርቀት በሁለት ታክሲ አጠቃለልኩት፡፡
ጠበቆች፣ ዳኞች፣ ጸሐፊዎች፣ ነገረ ፈጆችና ወኪሎች፣ ተሟጋቾችና አማላጆች፣ “ጫማ ጠራጊዎችና ሥራ ፈቶች፣ እንደየ ኑሮ ደረጃቸው ለብሰው ተራ በተራ ሁለትና ሦስት እየሆኑ በመምጣት የፍርድ ቤቱን አካባቢ የበጋ ወራት ገብያ
አስመሰሉት፡፡ አንዳንዶቹ ሰዎች የለበሱት ነጠላና ጋቢ በጣም ከመቆሸሹ የተነሣ
ዳግመኛ ታጥቦ የሚነጣ አይመስልም፡፡ ጥለቱ የተንዘለዘለ፣ ዐልፎ ዐልፎ አይጥ
የበላው ይመስል የተቀዳደደ፣ እንደ አረጀ ሻሽ አለቅጥ የሳሳ ልብስ፣ በተለያየ
የጨርቅ ዐይነት የተጣጣፈ ኮትና ሱሪ፣ ከታጠበ ብዙ ዓመታት ዐልፈውት እድፉ
እንደ ማሰሻ የተላከከበት ሱፍ ኮት፣ ከተወለወለ ወራት ያለፉትና የቆዳው ቀለም የተገጣጠባ ከወደ አፍንጫው በእንቅፋት አልቆ ቀዳዳው የደረቀ የዓሣ አፍ የመሰለ፡ ከወደ ተረከዙ ወይም ከወደ ጎኑ ባንድ ወገን ተበልቶ የተንጋደደ ጫማ፣
በፀሐይ ሐሩርና በውርጭ፣ በአቧራና በእንክርት ቀለሙ ጠፍቶ የነተበ ባርኔጣ፣
የለበሱ ያደረጉና የደፉ ሰዎች በተስፋ መቁረጥ ስሜት እዚህም እዚያም
ቆመዋል፡፡ ለአያሌ ወራትና ዓመታት የተንገላቱና የተጎሳቆሉ ባለጉዳዮች ናቸው::በረሃብና በጥማት በርዛትና በንዴት በመጎዳታቸው አብዛኛዎቹ ውርጭ ላይ ያደረ አንጋሬ ይመስላሉ፡፡ ሕይወታቸው በትካዜ በመሞላቱ የገጽታቸው ፈገግታ ደርቋል፡፡

ወዛቸው እንደ ቅቤ ቅል የሚቅለጠለጥ ፊታቸው በዶሮ ጮማ እንደተወለወለ የወይራ በትር የሚያበራ፣ ቦርጫቸው የመንፈቅ ርጉዝ መስሎ ሱሪያቸው መታጠቂያው ላይ የሪቅ አፍ የሚያህል፣ አለባበሳቸው ሁሉ በጣም ያማረና የተዋበ ደንደሳሞች፣ በየደቂቃው በሚረባና በማይረባው ሁሉ የሚሥቁ በጣም መሠሪ ሰዎች ከየቢጤዎቻቸው ጋር ሰብሰብ ከምችት ብለው አፍ ለአፍ
ገጥመው ያወራሉ። የያዙት የሰነዶች መያዣ ኮሮጆ እንደ ባለቤቶቹ የፀዳ ሲሆን
የልፋት እንክርት አልነካውም፡፡ የተሰበሰበውን ሰው በዝርዝር ሲያዩት እያንዳንዱ ብቻውን ቆሞ እጁን እያወራጨ ከራሱ ጋር ይሟገታል።

አብዛኛው ጨርቅ ለባሽ በሌላ ሰው ወረቀት እያስነበበ ይኽ ልክ ነው
የለም ይኽ ሐሰት ነው! ለዚህ በቂ ነቃሽ አለኝ! ያያት የቅድመ አያቴ ነው ይግባኝ እላለሁ፡ ከዳኛው ጋር ተዋውለው ነው። ወላዲተ አምላክን!” እያለ እሰጥ
አገባ ይላል። ሁሉም ከሕይወት ወዲያ ማዶ በውሸት ዓለም ውስጥ የሚንቀሳቀሱ እንጂ በርግጠኛ ሕይወት በእውነተኛ ዓለም የሚኖሩ አልመሰሉኝም

የመጥፎ ነገር ጥቀርሻ በጥብጠው የጋቱኝ ይመስል አእምሮዩ ተጨነቀ፡፡
የማያቋርጠው የጊዜ ጎርፍ እየጋፈረ መጓዙን ቀጠለ። ደቂቃ የደቂቃ ርካብ ረግጣ እየተፈናጠጠች ላትመለስ ትጋልባለች።

ጎነ ረጂሙ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ግዙፍ ሕንፃ ታላቅ የመከራ ተራራ መስሎ ፊት ለፊት ተገትሯል። የማደርገውን ጥንቃቄ አሟልቼ አካባቢዬን ገልመጥ እያልኩ እያየሁ መለስ ቀለስ አልኩ፡፡ ጭንቀቴና ጥበቴ እንደ ሐምሌ ጥቁር ደመና ከብዶ አንጎሌ ውስጥ አንዣሰሰ። በውስጤ የነበረው ሥጋት በድኃ ገበሬዎች አዋሳኝ እንዳለ የከበርቴ እርሻ መስፋቱን ቀጠለ። ረፈደ።

በወታደሮች ታጅበው በእግራቸውና በመኪና የመጡ አያሌ እስረኞች
በተለየ ቦታ ሰብሰብ አጀብ ብለው ቆሙ። ገር ገጭ ገጭ ገጭ፣ ሲጢጢጢጢጢ !
ካካካካካኪ! የሚል ድምፅ የምታሰማ ቮልስዋገን መጥታ አጠገቤ ቆመች፡፡ ጉልላት ነው። የየወዲያነሽ ቀነ ቀጠሮ በመሆኑ እኔና እርሱ ከፍተኛው ፍርድ ቤት
ለመገናኘት ተነጋግረን ነበር። ድክምክም ባለ እንቅስቃሴ የመኪናይቱን ቋቋቲያም
“በር ከፍቶ ወጣና ጨበጠኝ፡፡

ለአራት ሰዓት ሩብ ጉዳይ እኮ ሆኗል እስካሁን አላመጧትም እንዴ?»
አለኝ፡፡ ከንፈሬ ተጣብቆና ምላሴ አልላወስ ብሎ ቢያስቸግረኝም የለም እስካሁን አላመጧትም» ብዬ ዝም አልኩ። ውካታ በበዛበት አካባቢ ጥቂት ዝም ብለን ቆምን። ትላንት ማምሻዬን ሦስት ባለሙያ ጠበቆች አነጋግሬ ነበር። ሁሉም የሰጡኝ መልስ በጣም ተቀራራቢ ነበር፡፡ ቢበዛ አምስት ዓመት” አሉኝ። እንተስ ምን ይመስልሃል?» ብሎ ዐይኔን ማየት ጀመረ።

«እኔ ምን ዐውቃለሁ፡፡ ማንም ቢሆን ከራሱ ላይ ይልቅ በሌላው ላይ
መፍረድ ይቀልለዋል። የፍርድ ሰጪዎቹን ማንነት ስታየው ግን አምስት ዓመት
የሚበዛ አይመስልም፡፡ ቢሆንም ለእኔና ለእርሷ እያንዳንዱ ደቂቃ የሕይወታችን
ማሻከሪያ ክፍለ ጊዜ መሆኗ ነው» ብዬ ዝም አልኩ፡፡

«መቼም ቢሆን» አለ ጉልላት ወደድክም ጠላህም ምን ጊዜም ቢሆን ሕግ አለ። በሕጉም የሚጠቀሙና ጥቅማቸውን የሚያስጠብቁ አሉ። አህያና ጅብ
ባንድ ላይ ሕግ አያረፉም፡፡ ለጨቋኝና ለተጨቋት በአንድ ጊዜ በእኩልነት
የሚያገለግል ሕግ የለም፣ አልነበረምም፡፡ ሕግ ስለተፃፈ ብቻ ሕጋዊ አሠራር አለ
ማለት አይቻልም። እኔና አንተ ባለንበት ሥርዓተ ማኅበር ውስጥ እጀግ በጣም
አያሌ ባለሥልጣኖችና አጫፋሪዎቻቸው በልዩ ልዩ የእሠራር ስልትና ሥልጣን
ፈጠር ከለላ ከሕግ በላይ የሆኑበትና የሚሆኑበት ሁኔታ እንዳለ መዘንጋት
የለበትም፡፡ ስለሆነም ሕግ በትክክለኛው መንገድ በሥራ ላይ እስካልዋለ ድረስ
የሌለ ያህል ነው፡፡ ይህ ጉዳይ በስፋት የሚያነጋግግር ስለሆነ አሁን ከመጣንበት
ጉዳይ ጋር በቀጥታ ተያያዥነት የለውም። ወደ መጣንበት ጉዳይ እንመለስ፡፡
ስለዚህ በሚሰጠው ፍርድ እንዳትገረም፡፡ የበዛ ወይም ያነሰ ሊሆን ይሆናል» ብሎ
ወደፊት ተራመደ፡፡ ርምጃዬን ከርምጃው ጋር አስተካክዩ ተከተልኩት።

ከእኛ ትንሽ ራቅ ብሎ አንድ ብረት ሽፍን ባለ ጥቁር ሰሌዳ አረንጓዴ መኪና ቆሟል፡፡ ጉልላት መኪናውን አሻግሮ እየተመለከተ «ለምንድን ነው አልመጣችም ያልከኝ? ያ እኮ ነው የወህኒ ቤቱ መኪና» ብሎ ጥሎኝ ሔደ፡፡
አልተከተልኩትም፡፡

መኪናው ውስጥ ከተቀመጠው ሰው ጋር ምን እንደተባባሉ ባይሰማም ጉልላት ትንሽ ራቅ ብሎ ተነጋገሩ። ወዲያው ወደ እኔ ዞር ብሉ ና ቶሉ በሚል አኳኋን ጠቀሰኝ እና ሄድኩ፡፡ እስረኞቹ ወደሚገኙበት አካባቢ እንደ ደረስን ዐይኔ
ያካባቢው የብርሃን መጠን ያነሣት ይመስል የውበት ሃያ መስኮቶቿ ተሸጎሩ።

አጠርጠር ያሉና በሰፊ የካኪ ጨርቅ ስልቻ ውስጥ የቆሙ የሚመስሉ
የወህኒ ቤት ሴት ወታደሮች እያንዳንዳቸው አጠር ያለ ዱላ ይዘው ቆመዋል። በአቅራቢያቸው አምስት ሴቶች ሰብሰብ ብለው ተቀምጠዋል። የትካዜ እሳት ያነኮታቸው ይመስላሉ። ንዳድ እንደ ተነሣበት ሰው መላ ሰውነቴ ጋየ፡፡

የሕይወቴ ክፋይ የሆነችውና የማፈቅራት የወዲያነሽ አንገቷን ሰበር አድርጋና ጀርባዋን ለረፋዷ ፀሐይ ሰጥታ መሬት ትቆረቁራለች። ጉልላት ከሴቷ ወታደር ትንሽ ራቅ ብሎ በትሕትና እጅ ነሣ ራመድ ብዬ ከጎኑ ቆመኩ

በተከዘ ፊቱ ላይ ለማስደሰት የሚፍጨረጨር ፈገግታ እያሳየ «ከነዚህ
👍31