#እግዜር_አደራውን_ሲበላ
ግርግር ከማይወዱ ጓደኞቼ ዛብሎን አንደኛው "ነው። እይታዎቹ በወፍ በረር የተኮረጁ አይደሉም፤ ስለማያውቀው ነገር ከተወራ ይሰማል ረጋ ብሎ ስለሚያወራ፣ ስለሚያውቀው ነገር ብቻ ስለሚያወራ እያዳመጠ ስለሚያወራ፣ መናገር .. ሲጀምር የማይሰማው የለም።
ጨዋታው ብዙ ሰው ላይ ያለው እመነኝ፣ ቅዱስ ነኝ ዓይነት ስብከት የለበትም።
ክላስ አለው!!
አጠገቡ ያለ ሰው ስለማያውቀው ነገር ሲቀባጥር፣ ዛብሎን ደግሞ ስለጉዳዩ በደንብ እውቀት ካለው ለስለስ አድርጎ ቀባጣሪው የቀባጣሪነት ስሜትን ሳያሳድርበት ደርበብ ባለ መልኩ ሐሳቡ ላይ ብቻ አተኩሮ ሙግት ውስጥ ሳይገባ ስለሚያውቀው ነገር ይናገራል። እንደዚህ ዓይነት ግለሰብ ሰውዬው የበታችነት ሳይሰማው፣ አላዋቂነት ሳይታገለው የያዘውን መረጃ አልያም አቋም እንዲመረምር ያስችላል።
ዛብሎን ጺሜ አደገ፣ ጸጉሬ ተንጨባረረ ብሎ ጸጉር ቤት እንደማይሄድ የጸጉሩ መንጨባረር እና የጺሙ መንዥርገግ ምስክር ናቸው። ዘናጭ አይደለም ግን ንፁሕ ነው። ከሁሉ የሚገርመኝ ካላሳቀው አይስቅም። በጋራ ተሰብስበን ሁላችንም እየሳቅን በእርጋታ ሳቃችን እስክንጨርስ ጠብቆ በትንሽ ፈገገግታ አልገባኝም ብሎ ስለሳቅንበት ነገር ማብራሪያ ይጠይቃል፤ ተጨብጭቦለታል ብለን ለምናጨበጭብ ሰዎች አጀብ ነው ይሄ፡፡
ካፌ ውስጥ እንደተቀመጥን ዛብሎን አስተናጋጇን በምልክት ጠራትና መጥታ
'ምን ልታዘዝ'
"ተቆራጭ አምጭልኝ" አስናጋጇ ስትሄድ ጠብቄ
የገና ጾም አትጾምም እንዴ?
“አልጾምም!“
ለምን?
“እናቴ ስትሞት ነው ከመንፈሳዊ ሕይወት ጋር ያለኝ ቁርኝት የተፋታሁ፤ ተስፋ ቆረጥኩ፣ የምለፋበት ምክንያት አጣሁኝ። ድሮ ቤተክርስትያን ስሄድ ነጭ ሐበሻ ቀሚስ የለበሱ፣ ሹርባ የተሠሩ እናቶች ሳይ፣ ሥራ ስይዝ ለእናቴ እንዲህ እገዛለሁ እለው ነበር እግዚአብሔርን። ቆርበው ከቤተክርስትያን በር ላይ መኪና የሚጠብቃቸው እናቶችን ሳይ እኔ ለእናቴ እንዲህ እንደምንሆን ለእግዚአብሔር ፈገግ እያልኩ አጫውተው ነበር። ስማር እንቅልፌ እየመጣ እግሬን ውሃ ውስጥ ዘፍዝፌ የማጠናው ከእግዜር ጋር የተጨዋወትነውን ምኞቴን ለማሳካት ነበር። እሱ እኮ እሹ ታገኛላችሁ፣ አንኳኩ ይከፈትላችኋል ነው የሚለው እያልኩ።
ሱሰኛ ያልነበርኩት እናቴ ልጄ እኮ እንደዚህ ዓይነት ነገር አይወድም፤ የእኔ ልጅ እኮ ብላ እንድትጎርር ነበር። ሕልሜን ከእናቴ ጋ ብቻ ማቆራኘት አልነበረብኝም። ግን እኮ ወድጄ አይደለም፤ ቤተሰቦቿ አረገዝሽ ብለው ሲያባርሯት፣ አባትየው ሲክዳት፣ ምድረ በዳ ላይ ተነጥሎ እንደቀረ ሰው እኔን አገሯ፣ ዓለሟ አድርጋ የተዋደቀችልኝ ናት"
ፊቱ ቅዝቅዝ አለ... ትኩስ እንባ አይኑ ላይ ቅርርር ሲል አየሁ። ከዚህ በፊት አስተውየዋለሁ፤ ስለ አምላክ ሲወራ አስተያየት አይጎጥም። በቤተክርስቲያን ስናልፍ በእጃችን እያማተብን ከጉልበታችን ሸብረክ ስንል እሱ ግን ልክ መንገድ ላይ የምናውቀውን ሰው አግኝተን ሰላም ስንል ስለማያውቀው ብቻ እልፍ ብሎ እንደሚሄደው ልክ እንደሱ አልፎ ይሄዳል።
ውለታ የዋለለትን ሰው የእግዜር ስምን እያጠቀሰ ሲመርቀው አሜን አይልም። ተመጽዋች ምጽዋት ሲጠይቀን ከሌለን እኛ እግዜር ይስጥልን እንላለን ወደ እሱ ዞሮ ሲለምነው የለኝም ይላል።
እግዚአብሄሩን አኩርፎት እንደሆነ ካስተዋልኩ ቆየሁ። በዙሪያው የሚያፈቅረው የለም፤ አለማፍቀሩ ከፍቅር ሾልከው የሚመጡ ስጋት፣ ተስፋ እና ስስት የሚባሉትን ከውስጡ አሽሽቶለታል። አንድ ቀንም ለእግዜር ስሞታም፣ ውዳሴም ሲያቀርብ አይቼው አላውቅም። ዝም ብዬ ሳየው በለሆሳስ ብቻውን ከእግዚአብሄሩ ጋር የሚዋቀስ ነው የሚመስለኝ።
ሳየው በዝምታ እግዜሩን ለምን አደራኽን በላህ የሚለው ነው የሚመስለኝ!!!
🔘አድኀኖም ምትኩ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ግርግር ከማይወዱ ጓደኞቼ ዛብሎን አንደኛው "ነው። እይታዎቹ በወፍ በረር የተኮረጁ አይደሉም፤ ስለማያውቀው ነገር ከተወራ ይሰማል ረጋ ብሎ ስለሚያወራ፣ ስለሚያውቀው ነገር ብቻ ስለሚያወራ እያዳመጠ ስለሚያወራ፣ መናገር .. ሲጀምር የማይሰማው የለም።
ጨዋታው ብዙ ሰው ላይ ያለው እመነኝ፣ ቅዱስ ነኝ ዓይነት ስብከት የለበትም።
ክላስ አለው!!
አጠገቡ ያለ ሰው ስለማያውቀው ነገር ሲቀባጥር፣ ዛብሎን ደግሞ ስለጉዳዩ በደንብ እውቀት ካለው ለስለስ አድርጎ ቀባጣሪው የቀባጣሪነት ስሜትን ሳያሳድርበት ደርበብ ባለ መልኩ ሐሳቡ ላይ ብቻ አተኩሮ ሙግት ውስጥ ሳይገባ ስለሚያውቀው ነገር ይናገራል። እንደዚህ ዓይነት ግለሰብ ሰውዬው የበታችነት ሳይሰማው፣ አላዋቂነት ሳይታገለው የያዘውን መረጃ አልያም አቋም እንዲመረምር ያስችላል።
ዛብሎን ጺሜ አደገ፣ ጸጉሬ ተንጨባረረ ብሎ ጸጉር ቤት እንደማይሄድ የጸጉሩ መንጨባረር እና የጺሙ መንዥርገግ ምስክር ናቸው። ዘናጭ አይደለም ግን ንፁሕ ነው። ከሁሉ የሚገርመኝ ካላሳቀው አይስቅም። በጋራ ተሰብስበን ሁላችንም እየሳቅን በእርጋታ ሳቃችን እስክንጨርስ ጠብቆ በትንሽ ፈገገግታ አልገባኝም ብሎ ስለሳቅንበት ነገር ማብራሪያ ይጠይቃል፤ ተጨብጭቦለታል ብለን ለምናጨበጭብ ሰዎች አጀብ ነው ይሄ፡፡
ካፌ ውስጥ እንደተቀመጥን ዛብሎን አስተናጋጇን በምልክት ጠራትና መጥታ
'ምን ልታዘዝ'
"ተቆራጭ አምጭልኝ" አስናጋጇ ስትሄድ ጠብቄ
የገና ጾም አትጾምም እንዴ?
“አልጾምም!“
ለምን?
“እናቴ ስትሞት ነው ከመንፈሳዊ ሕይወት ጋር ያለኝ ቁርኝት የተፋታሁ፤ ተስፋ ቆረጥኩ፣ የምለፋበት ምክንያት አጣሁኝ። ድሮ ቤተክርስትያን ስሄድ ነጭ ሐበሻ ቀሚስ የለበሱ፣ ሹርባ የተሠሩ እናቶች ሳይ፣ ሥራ ስይዝ ለእናቴ እንዲህ እገዛለሁ እለው ነበር እግዚአብሔርን። ቆርበው ከቤተክርስትያን በር ላይ መኪና የሚጠብቃቸው እናቶችን ሳይ እኔ ለእናቴ እንዲህ እንደምንሆን ለእግዚአብሔር ፈገግ እያልኩ አጫውተው ነበር። ስማር እንቅልፌ እየመጣ እግሬን ውሃ ውስጥ ዘፍዝፌ የማጠናው ከእግዜር ጋር የተጨዋወትነውን ምኞቴን ለማሳካት ነበር። እሱ እኮ እሹ ታገኛላችሁ፣ አንኳኩ ይከፈትላችኋል ነው የሚለው እያልኩ።
ሱሰኛ ያልነበርኩት እናቴ ልጄ እኮ እንደዚህ ዓይነት ነገር አይወድም፤ የእኔ ልጅ እኮ ብላ እንድትጎርር ነበር። ሕልሜን ከእናቴ ጋ ብቻ ማቆራኘት አልነበረብኝም። ግን እኮ ወድጄ አይደለም፤ ቤተሰቦቿ አረገዝሽ ብለው ሲያባርሯት፣ አባትየው ሲክዳት፣ ምድረ በዳ ላይ ተነጥሎ እንደቀረ ሰው እኔን አገሯ፣ ዓለሟ አድርጋ የተዋደቀችልኝ ናት"
ፊቱ ቅዝቅዝ አለ... ትኩስ እንባ አይኑ ላይ ቅርርር ሲል አየሁ። ከዚህ በፊት አስተውየዋለሁ፤ ስለ አምላክ ሲወራ አስተያየት አይጎጥም። በቤተክርስቲያን ስናልፍ በእጃችን እያማተብን ከጉልበታችን ሸብረክ ስንል እሱ ግን ልክ መንገድ ላይ የምናውቀውን ሰው አግኝተን ሰላም ስንል ስለማያውቀው ብቻ እልፍ ብሎ እንደሚሄደው ልክ እንደሱ አልፎ ይሄዳል።
ውለታ የዋለለትን ሰው የእግዜር ስምን እያጠቀሰ ሲመርቀው አሜን አይልም። ተመጽዋች ምጽዋት ሲጠይቀን ከሌለን እኛ እግዜር ይስጥልን እንላለን ወደ እሱ ዞሮ ሲለምነው የለኝም ይላል።
እግዚአብሄሩን አኩርፎት እንደሆነ ካስተዋልኩ ቆየሁ። በዙሪያው የሚያፈቅረው የለም፤ አለማፍቀሩ ከፍቅር ሾልከው የሚመጡ ስጋት፣ ተስፋ እና ስስት የሚባሉትን ከውስጡ አሽሽቶለታል። አንድ ቀንም ለእግዜር ስሞታም፣ ውዳሴም ሲያቀርብ አይቼው አላውቅም። ዝም ብዬ ሳየው በለሆሳስ ብቻውን ከእግዚአብሄሩ ጋር የሚዋቀስ ነው የሚመስለኝ።
ሳየው በዝምታ እግዜሩን ለምን አደራኽን በላህ የሚለው ነው የሚመስለኝ!!!
🔘አድኀኖም ምትኩ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤25🤔8👍1