አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_ሀያ_ሰባት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ

ብጠጣለት የሚጎዳኝ ይመስልሃል?"

ወራጅ ውሃ እኮ ነው። እፅዋት በልምላሜ ፈክተው ጎንበስ ቀና እያሉ የሚወዛወዙበት አራዊት እየፈነደቁ የሚፈነጥዙበት
ዋኔ ዳክዬዎች ብቅ ጥልቅ እያሉ ተጎንጭተው የሚንሳፈፉበት ወደ
ሰማዬ ሰማያት ጉነው የሚበሩበት... ውሃ የሚጎዳሽ አይመስለኝም፡፡
ስለዚህ ይህን ከብክለት ነፃ የሆነ ውሃ በእጆችሽ መዳፍ እያፈሰሽ ተጎጭው  ማሬ አላት፡፡

ኮንችት እድሜዋ ባጠረ ግርምታ ተመሰከተችውና፡-

“ይገባኛል ገና አልተበከለም ገና አልቆሸሽም… ስልጣኔ
ኩሉን አልጣላበትም ቅርሻቱን አልደፋበትም… በእርግጥ ሳልፈራ መጠጣት ነበረብኝ ብላ በርከክ ብላ ሁለት እጆችዋን እንደ አካፋ አሹላ በእፍኝዋ የቀዳችውን ውሃ እንደ ወፎቹ አንጋጣ ወደ ጉሮሮዋ
አንቀረቆረችው፡ ጎርፍ መሳዩ ንፁህ ውሃ ጉሮሮዋን እያቀዘቀዛት ቁልቁል ወረደ ደስ አላት ጣማት፡፡ ስለዚህ እየደጋገመች ተጎነጨችው፡፡

ቀና ብላ አየች ሰማያዊው ሰማይ ተውቧል ! ወደ ዳርና
ዳር እፅዋትን ተመለከተች  የቆላ ዋንዛ፡ ጥቁር እንጨት እንኮይ ጠዪ. ቃጫ. . . በአረንጓዴ ልምላሜ ተሞልተው ምድሯን
አስውበዋታል፡ ጉጉት ድርጭት ጂግራ ቆቅ… ወፎች ይዘምራሉ ይጯሀሉ ይስቃሉ… አቦ ሽማኔ አንበሳው ቆርኪው ዝንጀሮው ጦጣና ጉሬዛው. በእዕዋት ስር ሲርመሰመሱ፡ በእዕዋት ቅርንጫፎች
ላይ እየተንጨዋለሉ ሲወናጨፉ ይታያሉ፡፡
እባቡ እንሽላሊቱ… በዕፅዋት ግንድ
ይልወሰወሳሉ፡፡ ኦሞ ወንዝ ላይ አዞው ራሱን አውጥቶ ይንሳፈፋል፧አሶች ብቅ እያሉ ጥቡሉቅ ይላሉ….

ተፈጥሮ እንደ ሙሽራ ደምቃለች አምራለች ፈክታለች...እንደ ማራኪው የአዳም ዘመን ገነት ኑሮ! ኮንችት ያን ድንቅ ውበት
በአይኗ  በጆሮዋ ባጠቃላይ በስሜት ሕዋሶችዋ እየኮረሻሽመች በላችው  እንዳያንቃት ከወንዙ ውሃ ተጎነጨለት….

“…ገና ካሁኑ አያቴ ያጣውን ተረዳሁለት" አለች ወደ ሶራ
ዙራ፡

“ድንግል ውበትን ነፃነትን እርጋታን… ነበር አያቴ ያጣው'' እንባዋ በአይኖችዋ ሞላ፡፡ “ሁካታ የሌለበት ዓለም አንዱ ሌላውን
የማይጎዳበት ተፈጥሮ ቅኝቱ የተዋሃደ ቅላፄ ነበር አያቴ ያጣው ለካ" እየሳቀች አለቀሰች፡፡ እንባዋ እየፈሰሰ ጥርሶችዋ ግን ተገለጡ
ሰዎች እውነተኛ ስሜት ሲሰማቸው ስሜታቸው ይደበላለቃል" ይህች
ፕላኔት የሚለቀስባት ካልያም የሚሳቅባት ብቻ አይደለችም፤ ደስታና
ሐዘን ሣቀና ልቅሶ እንደ ሳንቲም ገፅታ አብረው የሚኖሩባት ናት፤እና እውነተኛው የተፈጥሮ ስሜት ኮንችት ላይም ደረሰ
እንደ አያቷ ትናንትን ዛሬ ላይ ቁማ አለመችው፧ እንደ
ልጆችዋ ዛሬ ላይ ቆማ ነገን አሰበችው ተፈጥሮ እንደ ሰው አታረጅ ይሆናል እሚያቆሽሻት ሰው እስካለ ግን እንደ ትናንቱ ዛሬ
አታምርም፡ እንደ ዛሬው የውበት ፀዳሏ ለነገ አይደርስም፡፡ እና
ኮንችት ከመሃል ሆነች ከኢትዮጵያዊው አያቷና ካልወለደችው ልጅዋ መካከል!

ኮንችት የእፎይታ ትንፋሽዋን አንቦለቦለችና ሃዘንና ደስታዋን ሙሉ በሙሉ የተካ ፈገግታ ለውቡ ተፈጥሮ አበርክታ ሶራን ተመለከተችው፡፡

ኮንችት እንደ ከብቶች፥ እንደ አዕዋፍ እንደ እፅዋት ራቁቷን ብትሆን ትመረጣለች በተለይ በእንዲህ ዓይነቱ ተፈጥሮአዊ ተፈጥሮ… መመሳሰል ያረካታል።

ፓንትና ጡት ማሲያዣ ሲቀር
ሁሉንም ልብሷን አወለቀችው ልብስ ገመናን ሃፍረተ ሥጋን መሸፈኛ ነው።
እውነተኛው ተፈጥሮ ግን ገመና ሃፍረተ ስጋ የለም፡፡ ተፈጥሮ ገነት ናት አዳምና ሄዋን ዕፀ በላሷን ከመብላታቸው በፊት
እንደነበሩት።

ቤጫ መስመር በጎንና ጎኗ የተጋደመባት ሰማያዊ ቀለም ያላት የፕላስቲክ ጀልባ እየተጀነነ በኩራት ቁልቁል ይሁን ሽቅብ
መፍስሱ ግራ በሚያጋባው የኦሞ ወንዝ ላይ እንደ ቄብ ዶሮ ቂብ ብላ በአፍንጫዋ ውሃውን ግራና ቀኝ እየከፈለች ትንሳፈፋለች፡

ኮንችት አጠር ያለውንና ቢጫውን መቅዘፊያ ካስቀመጠችበት
አንስታ ከሶራ ጎን ካለው ቦታ ቁጭ ብላ በግራ እጅዋ የመቅዘፊያውን እጀታ ጨብጣ ውሃውን ሶስቴ
ገፋችና ወደ ሶራ ዞራ ፈገግ አለች፡፡ ሶራም በመቅዘፊያው ውሃውን
ወደ ኋላ እየገፋ ፈገግ አለላት፡፡

ኮንችት ከተቀመጠችበት ተነስታ ቆመችና ወደ ወንዙ ዘለለች ወደ ኦሞ ቁልቁል ሰጠመች፤ እግርና እጅዋ በስልት እየተንቀሳቀ
እንደ አሶች ውስጥ ለውስጥ ዋኘች፡፡

ሶራ መቅዘፉን አቁሞ ኮንችት ካለ ህይወት አድን ጃኬት ባዶዋን ወንዝ ውስጥ በመግባቷ ደነገጠ፡፡ ልብሱን ከመቅጽበት አውልቆ አያት ገና ብቅ አላለችም፡፡ ዘሎ ውሃው ውስጥ ገባና
በውሃው ውስጥ ለውስጥ ፈለጋት፡፡ ስማያዊዋ ጀልባ ግራ ቀኝ ተወዛወዘ ቀስ በቀስ ተረጋግታ ተንሳፈፈች፡፡ ሶራ የሆነ ድምፅ ሰማና
ሽቀብ ወደላይ ቀዘፈ:

እህ! እህ. በድካም እያቃሰተች ኮንችት ትስቃለች፡፡እሱም አብሯት ሳቀ፡ ውሃው ውስጥ ተጠጋጉ፡ ሳቀ ሳቀች ፍርስ
እያሉ ተሳሳቁ ውሃ ተራጩ የአፍሪካ ንሥር አየሩ ላይ
ይንሳፈፋል፡፡ ከዳር በኩል ውሃ ሲጠጡ የነበሩት ዝሆኖች በአድናቆት
ተመለከቷቸው
“ዝሆን የአፍሪካ ዝሆን ጆሮ ሰፊው የዝሆን ጉዞ' በሚል
በልዕልት ሚድታውን ታናል' ስርከስ ላይ ከቀረቡት ዝሆኖች ሁሉ እጅግ የገዘፈ' ብላ ኮንችት ዝሆኖችን በአድናቆት ተመሰከተቻቸው፡፡

ሶራና ኮንችት ጀልባዋ ላይ ወጡ፡፡ ሰውነታቸው በውሃ
ነጠብጣብ ተሞልቷል፡ ዝሆኖች ለምለም ጨሌ ሣር ከሚታይበት ሜዳ ወጣ አሉና አንድ ኮርማ ዝሆንና አንዲት ሴት ዝሆን መዳራት
ጀመሩ፡፡ ከጥቂት ማሽኮርመም በኋላ ወንዱ ዝሆን ያን ግዙፍ ሰውነቱን ወደ ላይ አንስቶ በኋላ እግሩ ቆመና የፊት እግሮቹን ሴቷ
ዝሆን ላይ ጭኖ የእንግሊዘኛውን ኤስ' ፊደል ቅርፅ ያለውን ብልቱን
እንደምንም ብሎ ሴቷ ብልት አስገባና ሰረራት፡፡

ኮንችትና ሶራ ያን ተፈጥሮአዊ ትርኢት አፋቸውን ከፍተው
ሲያዩ ላያቸው ላይ የነበረው የውሃ ነጠብጣብ ደረቀላቸው፡፡ የጫካው
የተፈጥሮ ድሪያ ሳባቸው፡፡ ተፈጥሮ ውስጥ የተፈጥሮ ድሪያ ያስጎመዣል ...

ኮንችት ለስላሳና ቀጥ ያሉ ጭኖችዋን አጥፋ የመቅዘፊያውን እጀታ አንስታ ለመቅዘፍ ጠምዘዝ ስትል ሰፋ ያለው ዳሌዋ ሰርጓዳው ወገቧ ጠባቡ ትከሻዋ ሰውነቷ ላይ የተለጠፈው ዞማ ፀጉሯን…
አየው! ተስገበገበ… ኮንችት እንዲህ የውበቷን ሰዲቃ ሲቋደስ ዞር ብላ ፈገግታዋን አከለችለት፡

ከወንዙ ውሃ ግራና ቀኝ ካሉት የውበት ፀዳሎች ጋር
የተጣጣመው ውበቷ እንደ ፍላፃ ሕሊናውን ወጋው፡፡ ዞር አለች እንደገና፤ ሶራ ከንፈሮቹን በቀስታ ግራና ቀኝ እንደ ላስቲክ እየለጠጠ
ዘርዘር ያሉ ጥርሶቹን አሳያት እሷም ፈገግ አለች  ፈገግታዋ በመቀጣጠል ላይ ያለውን ስሜቱን ቤንዚን እንደጨመሩበት እሳት
ባንዴ ቦግ አደረገው፡፡ ሰደዱ እሷ ህሊናም በቅጽበት ደርሶ እሷንም ለበለባት…ሳይታወቃቸው እሳታቸውን ለማብረድ ሁለቱም
ከንፈሮቻቸውን በምላሳቸው አረጠቡ የአይናቸው ቆብ ቁልቁል እየወረደ ተከደነ… ዝሆኑ ሽቅብ ተነሳ. ሴቷ ተጠጋችው፡
የሚመነጭቀው እንዳለ ሁሉ ጥብቅ አድርጎ አቀፋት… ዝሆኑ!
አእዋፍ ያፏጫሉ ጀልባዋ
ትንሳፈፋለች እንቁራሪቶች
ያንቆርራሉ ኮንችት የሶራን
የእጅ ጡንቻዎች ሳም ሳም ስታደርግለት እሱ አካሏን እየላሰ ሎሚውን በእጁ ጣቶች እያሻሽ ከንፈሩና ከንፈሯ ተገናኘ ኮንችት ይበልጥ እየሰረሰረች ተጠጋችው !
ያኔ! ጎርበጥ ያለው ነገር ቆረቆራት የቆረቆራትን የቀኝ እጅዋን ሰዳ ከተደበቀበት ስታወጣው እንደ ህፃን ልጅ ፈነደቀ…

ኦሞ ወንዝ በኵራት ይፈሳል እፅዋት በንፋስ ይወዛወዛሉ
+ፈጥሮ አራዊትና አዕዋፍ ይዳራሉ:: ብርጉዱ እጣኍ ጠጅ ሳሩ ጤናዳሙ ጽጌረዳው የበረሃ እጣነ አካባቢውን አልባብ አልባብ
እሸተ† ድንቅ የተፈጥሮ ህይወት ታምር ይታያል!
👍19
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_ሀያ_ስምንት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ

ኮንችትና ሶራ የሶስተኛ ቀን የኦሞ ወንዝ ላይ ጉዟቸውን
ሲጀምሩ አየሩ ጨፍገግ ያለና ሰማዩ በጥቁር ዳመናዎች የተሸፈነ
ነበር፡፡

“ብንቆይ አይሻልም  ኮንችት"

“አይ! አስቸጋሪውን ጉዞ ብንጋፈጠው ይሻላል፡፡ ምናልባት እየተጓዝን ዝናቡን ልናመልጠው እንችል ይሆናል፡፡ስለዚህ ቶሉ
መንቀሳቀሳችን ይሻላል፡"

“ወንዙ ላይ ዝናቡ ከያዘንስ?''

“ያኔ ከወንዙ ወጥተን ድንኳን ወጥረን እንጠለላለን፤ እዚህ
ሆኖ ሳይሞክሩ ተሸናፊ መሆን ግን አልፈልግም" አለችው፡

“እሽ በኔ በኩል ለጉዞ ዝግጁ ነኝ፡፡"

“ቆየኝ አንዴ” ብላው ለመፀዳዳት ወደ ጫካው ገባች፡፡ ሶራ የወንዝ ላይ ጉዞ አስደሳችም አስፈሪም እንደሆነ እየተረዳ መጥቷል፡፡

በተለይ ከመጀመሪው ቀን ቀጥሎ በነበረው ውድቅት ሌሊት አንበሶች የድሪያ ወቅታቸ በመሆኑ ከድንኳናቸው ብዙም ሳይርቅ እያገሱ ሲታገሉ
ኮንችትና ሶራ ከአሁ አሁን ላያችን ላይ ወጡ ገነጣጥለው ሊቀራመቱን ነው ሲሉ እንቅልፍ በዓይናቸው ሳይዞር ነው ያደሩት።

በሁሉተኛው ቀን ደግሞ ድንገት የጣለው ከባድ ዝናብ ድንኳናቸውን በጎርፍ ውጦ ልብሳቸው በሙሉ ረጥቦ በዚያ ጥርስ
በሚፋጨው ብርድ እንደከበት ዛፍ ስር ጎን ለጎን ኵርም† ብለው
አንዱ በሌላው ትንፋሽ ሙቀት እየተጋሩ ነበር የመከራ ሌሊቱን ያሳለፉት።

ስለዚህ በነጋታው እስከ አጥንታችው ድረስ ዘልቆ የገባው ቆፈን እስኪወጣላቸው ፀይይ ላይ ተሰጥተው አረፈዱ ሰውነታቸውን ማዘዝና ማንቀሳቀስ ሲችሉ በጎርፍ የተዋጠውን ድንኳን ነቅለው
እቃውን አውጥተው… ፀሐይ ላይ አሰጡት ከዚያ ረጅም ሰዓት ቆይተው ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ ተነስተው ሰላሳ ኪሎ ሜትር ተጉዘው እንቅልፍና ድካም ተጫጭኖአችው ስለነበር ደረቅ ዳቦና ብስኩት ብቻ ተመግበው ተኙ ልክ እንደሞተ ሰው ተኝተው
አድረው ሲነቁ ስማዩ የታቀፈውን ጥላሽት የመሰለ ዳመና እላያችው
ላይ ሊዘረግፈው ተዘጋጅቷል።

የሶራ ምርጫ ዝናቡን ማሳለፍ ይሻላል ነበር ኮንችት ግን ሃሳቡን ልተቀበለችውም።

አሁን መሄድ እንችላለን የህይወት ማዳኛ ጃኬቱን ልበስ ሱሪውን አውልቀውና የዋና ፓንትህን ታጠቅ አለችው ሶራ የተባለውን እየፈፀመ አያት የለበሰችው የዋና ፓንቷን ነው
ጭኖችዋ ከምን ጊዜውም በላይ አምረዋል: ከላይ ቀይ የህይወት ማዳኛ ጃኬቷን ቀይ ሄልሜቷን ደፍታ ዮጉዞ ቦርሳን ከጀርባሞ አዝላለች ሶራም እንደ እሷ ትጥቁን እያስመረ ስማዩን ቀና ብሎ
አየው ጠቁሯል
ጀልባዋን ውሃው ላይ ካሳረፉ በኋላ ድንኳናቸው
ምግባቸውን የማብሰያ እቃቸውን… ከጀልባው መሀል አስቀምጠው
በጣም አስፈላጊ የሆነውን ቁሳቁስ በጀርባ ቦርሳቸው አዘሉት፡፡ ከዚያ “አድሪፍት" የምትለው ጀልባ ላይ ያለውን ረጅም ገመድ ወገባቸው ላይ ካለው ሰፊ ቀበቶ ጋር አያያዙት፡፡

ጀልባዋ ላይ ወጥተው ሚዛናቸውን ለመጠበቅ ከኋላ በኩል ግራና ቀኙ ተቀመጡና መቅዘፊያቸውን አንስተው አውራ ጣታቸውን
በማንሳት ዝግጁ ተባባሉና ወደ ኦሞ ወንዝ መሃል ሄደው ቁልቁል ቀዘፉ

ሰማዩ እንደ ተቆጣ ነብር ማጉረምረም ጀመረ። ድንገት ሰማዩ በቀጫጭን የብርሃን ዝግዛግ እየተሰነጣጠቀ ብልጭታው
ይታይና ብራቁ ድብልቅልቅ ብሎ መጮሁ እየጨመረ ሄደ፡፡

“ኮንችት!” ብሎ  ጠርቶ አያት፡፡ ቶሎ ቶሎ ትቀዝፋለች ለማምለጥ፡፡ ድክም ያላት መሆኑ በዚያ ቆፈን የሚወርደው ላቧ ያስታውቃል፡፡ ሶራ አዘነላት፡፡ ምን ሊያደርግላት እንደሚችል አሰበ፡፡
መላው አጥጋቢ አልመሰለውም፡፡ ይሻል ይሆናል ብሎ ገመተና ጮክ
በማለት ደግሞ ጠራት፡-

“ኮንችት…….” ሲል ሰማዩ ብልጭልጭ አለና የጆሮ
ታንቡራቸው የተነደለ እስኪመስል ብራቁ ጮኸ፡፡ሁለቱም በደመነፍስ ዝቅ አሉ በድንጋጤ፡፡

ኮንቺት አያቷ ትዝ አላት አደራው ተጭኗት ኖሯል፡፡
ማንኛውንም መስዋዕትነት ከፍላ አደራውን መፈፀም መቻል አለበት፡፡ህሊናዋ ከዚህ ግዴታዋ ውልፍት እንድትል አይፈቅድላትም፡፡ የዚያ ምስኪን ኢትዮጵያዊ አያቷን ዘመዶች ከመፈለግ ከአቅሟ በላይ በሆነ
ችግር ሞት ጥፍሩን አሽሎ መጣሁ' እያለ ቢያስፈራራትም እንኳ
ላለመሽሽ ለራሷ ቃል ገብታለች፡፡ ብዙ ጊዜ በዚህ ጉዳይ ላይ አስባ
ከማያዳግም ውሳኔ ላይ ደርሳለች፡፡

ብራቁ ካለፈ በኋላ ማጉረምረሙ እየበዛ የመጣውን ሰማይ ቀና ብሎ አየና ሶራ ኮንችትን አያት፡፡ ከዝያቡ ሊያድናት ፈለገ
ስለዚህ ጮክ ብሎ ጠራት

ኮንችት ለምን ጉዞውን አቁመን እንጠለልም፡፡ ከዚያ…" ብሎ ሃሣቡን ሳይጨርስ ገሃነም ግባ እሽ ቦቅቧቃ ፈሪ ነህ!  ወደፈለግበት መሄድ
ትችላለህ! እኔን ግን አትጥራኝ  ደደብ!" አለችው፡ ሶራ መብረቁ ጭንቅላቱ ላይ እንደወደቀ ሁሉ ክው አለ። ስላዘነላት ነበር የጠየቃት እሷ ግን አውሬ ሆነችበት ።

ሶራ እንደተወጋ አውሬ ሸቅሽቆት ውስጡ የገባው አነጋገሯ አደነዘዘው አበሸቀው።

ዝናቡ ህፃናት የሚጫወቱበትን ብይ እያካከለ ዥጉድጉድ
ብሎ መውረድ ጀመረ፡፡ ኮንችትና ሶራ ማየት እንኳ ተሳናቸው፡፡የመዋኛ መነፅራቸውን አደረጉ: ጉሙ እየሸፈነ ይበልጥ ማየት
ተሳናቸው፡ ቀስ እያለ ደግሞ አዙሪቱ ሰማያዊ ጀልባዋን ወደ ታች ሳይሆን እንባለሌ ያዞራት ጀመር፡፡

ሁለቱም ባለ ሃይላቸው ቀዘፉ አዙሪቱ ደግሞ  እነሱን
ይበልጥ እያሽከረከረ ቀዘፋቸው፡፡ ቁልቁልና ሽቅቡ ዳሩና መሃሉ እስኪጠፋቸው ድረስ ከላይ ዝናቡ ከታች ዙሪቱ ልባቸውን
አጠፈው፡

ድንገት ደግሞ ዥው ብለው በአየር ላይ ሲንሳፈፉ እነሱ
ከሥር ጀልባዋና ውሃው ከላይ ሆኑ፡፡ ከሁሉም የከፋው አዲስ መከራ
ተጀመረ፡፡ ኮንችትና ሶራ ውሃው ያላጋቸዋል ያሰጥማቸዋል። ዝናቡ
ከላይ ዶፉን ያወርደዋል፡፡ ወገባቸው ላይ ገመዷን ያሰሯት ጀልባም
ወዲህ ወዲያ ትመነጭቃቸዋለች በጀልባዋ ወለል የነበረውን
ጓዛቸውንም ኦሞ ሰለቀጠው፡፡

ሰማዩ  አልበቃውም ያጉረመርማል  ይጮሃል፤
ይወርዳል. ኦሞ ወንዝም እርጋታው ጠፍቶ ይደነፋል ይሽከረከራል እላይ ደርሶ ይፈርጣል አሶች አዞዎችና ጉማሬዎች የሚሉትና
የሆኑት አይታወቅም፡፡ ኮንችትና ሶራ ግን አበሳቸውን ያያሉ። በኒያ
ወጣቶች መሃል ውሃ ገባ በቅጽበት እንደ ተራራ የገዘፈ ችግርና መከራ ላያቸው ላይ ተከመረ ይባስ ብሎ በእንቅርት ላይ  ጆሮ ደግፍ እንዲሉ አካባቢውን ፅልመት አለበሰው፡፡ ኮንችት መከራው ሲበዛባት ያመለጠች መስሏት የጀልባዋን ገመድ ከጎኗ ፈታችው፡፡ ከዚያ ከሶራና ከጀልባዋ ተጠፋፋች… እሪ ይላል ሰማዩ፡- አካባቢው
በእሮሮ በእግዚኦታ ተዋጠ፡፡

ሶራ ጀልባዋ እየጎተተችው ብዙ ከተጓዘ በኋላ በጭንቅ ወደ ዳር ወጣ፡፡ የይወት ማዳኛ ጃኬቱና ሄልሜቱ ነፍሱን አተረፋት፡ ዝናቡ ቆሟል ቀና ብሉ ሰማዩን አየ፡፡ ሰማዩ ጠርቷልı ጨረቃ ወጥታለች ከዋክብት ብልጭ ድርግም ይላሉ፡፡ ሶራ የሆነውን ሁሉ
ለማሰብ ሞከረ፡፡

ጀልባዋ ከሱ ጋር ነች፡፡ ኮንችት ግን አብራው የለችም፡ ያች መለሎዋ ያች ኢትዮጵያዊት  ደፋርና የፍቅር ልዕልቱ አጠገቡ
የለችም፡፡ ከጀልባዋ ጋር ያያዘችው ገመድ ተበጥሷል፡፡

ሶራ ኦሞን ዞር ብሉ አየው፡፡

“ኦሞ አላማ ያለውን ሰው  እውን ትበላለህ?” ብሎት ማልቀስ ጀመረ ሶራ። ጮኸ “ፍቅሬን ምሳሌዬን… ተነጠቅሁ” ብሎ ቀና
ብሎ ሰማዩን እያዬ ተማፀነ፡፡

እኔንም መብላት አለብህ ኦሞ፡፡ልትነጣጥለን አይገባም ሲሆን እኔን ማስቀደም ነበረብህ…” እየተንቀጠቀጠ አለቀሰ፡፡

“ምነው እግዚአብሔር... ምነው! የኦሞ ወንዝ ዳርን ጭቃ እያፈሰ ፊቱን እየቀባ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ ለአምላኩ
👍16
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ

ሶራ ሲያገኛት በጭቃ ልውስውስ ብላ ሰው አትመስልም። ጦርሷቿ ይፏጫሉ ሰውነቷ ይንቀጠቀጣል አካሏ የማታዝበት በድን ሆኗል። በጀርባው ያዘለውን ፈቶ በፕላስቲክ የተጠቀለለ ስሊፒግ ባግ አውጥቶ የበሰበሰና በጭቃ የተለወሰ ልብሷን አውልቆ ፎጣ አልብሶ ስሊፒግ ባግ ውስጥ እየጎተተ አስገባት።

በውርርድ ደረቅ ቦታ የለም ደለሉ በሙሉ ጨቅይቷል ውሃ ተኝቶበታል ስለዚህ ሶራ በቶሎ ከዚህ አካባቢ መራቅ እንዳለበት አምኖ ጀልባዋን ለማምጣት ሄደ።

ሶራ የፕላስቲክ ጀልባዋን በኦሞ ወንዝ ዳር ለዳር እየቀዘፈ ኮንችት ወዳለችበት ሄደ።ከጀልባዋ ወርዷ ወደኮንቺት ሲጠጋ አትሰማም። እንቅልፍ ጭልጥ አድርጎ ወስዷታል።
የጀርባ ቦርሳቸውን ከጫነ በኋላ እሷን ጀርባው ላይ
አስተካክሎ በሰፊ ቀበቶ ከገላው ጋር አሰራትና የጀልባዋን ገመድ ፈቶ
ቀስ ብሎ ጀልባዋ ላይ ወጣ፡ hዚያ ጆልባዋ ወለል ላይ ትራስ አድርጎ
አጋደማትና ከጀልባዋ በስተኋላ እግሩን አንፈራጦ ቁጭ ካለ በኋላ መቅዘፍ ጀመረ"

ቀኑ ፀሐያማና ነፋሻማ ነው፡፡ ኮንችት ወዲያ ወዲህ ሳትል
ተንጋላለች፡ ሶራ ትንሽ ሲቀዝፍ ይቆይና ጆሮ'ውን ልቧ ላይ ይደቅናል። ከዚያ ተመልሶ ደግሞ ይቀዝፋል…
የሞላው የኦሞ ወንዝም ቁልቁል መግፋቱን እየረዳው እስከ ቀኑ አስራ አንድ ሰዓት ተኩል ድረስ ተጓዘ፡፡

ኮንችት በስፓኒሽ “ውኀ" ትለውና አንገቷን ቀና አድርጎ
ሰሰጣት ጎንጨት ታደርግና ትተኛለች፡ ርሃቡ ራሱ ሊጎዳት እንደሚችል ቢያምንም ጀልባዋን ሊያቆምበት የሚችል የተሻለ ቦታ በማጣቱ እግር ጉልበት እየጨመረለት ብዙ እንደተጓዘ ሜዳማ ደረቅ• ጨሌ ሣርና ጥላቸው ዘርፈፍ ያሉ ዛፎች ዘንድ ደረሰ፡፡ ቀስ ብሎ  እየቀዘፈ ጀልባዋን ወደ ዳር አስጠጋና ኮንችትን እንዳይጫናት
ተጠንቅቆ በጀርባው አዘላትና ቀስ ብሎ
ቁጭ አለ፡፡ ጀልባዋ
ስለምትንቀሳቀስ ጀልባዋን እንደገና ወደዳር
ይበልጥ አስጠግቶ
እንደተቀመጠ ተንጠራርቶ ወንዙ ዳር ላይ ያለ የዋርካ ሥር ያዘ ያለው እድል ያ ብቻ ነበር።

መቅዘፊያውን ከጀልባዋ ላይ ፈቶ ወደ ውሃው ውስጥ ከቶ ለካው፡፡ መሬቱን ነክቶ ለመሻገር ኮንችትን አዝሉ እስከ አንገቱ ውሃ
ውስጥ መነከር አለበት፡፡ ምናልባት ከታች ያለው መሬት ድቡሽት
ከሆነ ስለሚሰምጥ እሷን ይዞ ለመዳን ይፍጨረጨር ይሆናል፡፡ እሷን አዝሎ ግን ካልተመቸው እንደተመኘው ሁለቱም እንደተዛዘሉ
አብረው ከአስቸጋሪው ሕይወት ለዘላለም ያርፋሉ፡፡ሶራ አሁን አልፈራም፡፡ ተለያይቶ ከመሞት አብሮ መሞትን ይመረጣል፡፡
በአርግጥ ሞትን ሊያመልጥ ብዙ ተጉዟል፡ ብዙ ሸሽቷል፡፡ ሞትን ግን ሊያመልጠው አልቻለም፡፡ ለሁሉም ወረቀት ፅፎ ሊያስቀምጥ ፈለገ፡ አዎ የሷም ሆኑ የእሱ ዘመዶች ሙት እንደሆናቸው መጠን እንደማንኛውም ሰው  መሞታቸውን አውቀው ልሳቸውን በማውጣት በነሱ ላይ ያላቸው አጉል የተስፋ ህልማቸው ሊቆም ያስፈልጋል የእሱንም
የእሷንም ስም አድራሻ… ፃፈና በላስቲከ አስሮ ወገቡ ላይ ባሰረው ውሃ የማይገባው ላይነን ቀረጢት ከተተው፡፡

ከዚያ ውሃው ሲወስዳቸው እንዳይለያዩ በሌላ የዕቃ ማሰሪያ ቀበቶ በሷና እሱ ትከሻና ጉያ ስር አሰረው፡፡
“እፎይ  ድሮ ሞትን እንዴት እፈራው ነበር፡፡ አሁን ግን
ቢያንስ መሞቴ እንደማይቀርልኝ አመንሁ! ከማንም ሰው  በላይ
የመሞቻ ጊዜዬ መድረሱን ከነደቂቃው አውቄያለሁ, ከፍቅረኛ ጋር ደግሞ ወደ ሞት መሄዴ የሙት ዕድለኛ ያደርገኛል" ብሎ እዕዋቱን
ሰማዩን የማታዋን ጀንበር ከማህደሩ መግደያ ሰይፉን በመምዝ ላይ ያለውን የኦሞን ወንዝ አየና የዋርካ ስሩን ጠበቅ አድርጎ ይዞ
ከጀልባዋ ወደ ውሃው ውስጥ ገባ፡፡

የኢትዮጵያዊውን አያቷን እትብት የተቀበረበትን ለመፈለግ ደክማ ያልተሳካላትን ቆንጆ ውሃው ውስጥ እየገባ አያት፡፡ ከዚያ
ውሃው አሰመጠው? እንደፈራው ከደረቱ አላለፈም፡፡ ስለዚህ በዛፉ
ሥር አማካኝነት እየተጎተተ ወደ ውጭ ወጣ፡፡ መከራና ስቃይን ውጦ እንደጨረሰ ሁሉ ፊቱ በደስታ ፀዳል በራ፡ በቅፅበት ከመከራ
ወደ ደስታ ተመለሰ፡፡

ከዚያ ጫካ ውስጥ ገብቶ የደራረቁ እንጨቶችን ለቅሞ
አመጣና ውኃ የማያበላሸውን ክብሪት ጭሮ እሳት አቀጣጠለ፡፡
ከጀልባዋ ላይ ያለውን የጀርባ ሻንጣ አውርዶ ለኮንችት ፓንት ሣይቀር ቀይሮ እሳቱ ዳር አስተኛትና ለችግር ጊዜ ብለው የያዟትን
ትንሽ ድንኳን ዘረጋ፡፡

ከጀርባ ሻንጣው ተጣጣፊ መጥበሻና ብረት ድስት አውጥቶ ለችግር ጊዜ ካስቀመጡት ምግብ መካከል የሚበላ አዘጋጀና ሻይ  አፈላ ኮንችት ቀስ በቀስ ዓይኖቿን መግለጥ ስትጀምር የአይብና አሳ ሳንዲዊች ወደ አፏ አስጠጋላት ከጭኖቹ ደገፍ እንዳለች ሳንዱቹን ገመጠች ሻየለንም መጠጣት ጀመረች።

ከዚያ የራስ ምታታ መድሃኒት እንደዋጠች ፈሳሽ ቅባት ጀርባዋን ጭኖቿን ክንዷን ፊቷን እያሸላት  እቅልፍ ይዟት ሄደ ቀስ አድርጎ አቀፈና ድንኳን ውስጥ አስተኛት።

የሱ እስሊፒግ ባግ ካንጠለጠለበት ዛፍ ላይ ንፋሱ ሲያወዛውዘው ጠፈፍ እስኪልለት እሳቱ ዳር ጋደም አለና ሽቅብ ወደ ሰማይ አየ። ሰማዩ ጥርት ያለ ደመና አልባ ነው አየሩ በደንብ እንደበዘቀዘ እርጎ የሚገመጥ ነው ተወርዋሪ ኮኮቦች ይወረወራሉ ጨረቃ ትንሳፈፊለች ድንቁ ተፈጥሮ እንደገና የሚያስጓመጅ ሆኗል ቀናት ያልፋሉ ዛሬም አይቀርም ያልፋል ግን በሚያልፍ ጊዜ ስንቱ አዝኖ ስንቱ ይደሰታል?

እኩለ ሌሊት ላይ የትንሿ ድንኳን ዚፕ ጢዝዝዝ ብሎ ተከፈተ ጨለማው በጨረቃ ብርሃን ድል ተነስቷል የእሳቱ ነበልባል ጠፍቷል ፍሙ ግን አለ አጠገቡ ኩርምትምት ብሎ የተኛው ሶራ ነገር አለሙን ዘንግቶ እንቅለሰፉን ይለዋል።

ኮንቺት እጇን ግንባሩ ላይ አስቀመጠች ሶራ አልተንቀሳቀሰም ዝቅ ብላ አየችው። ተመልሳ ደግሞ የሆነውን ሁሉ ለማስታወስ ሞከረች ሰመመናዊ ህልሟ ሳይቀር።

ሶራ ከዚያ መአትና የጫካ አውሬ አፍ አውጥቷታል አሁን ግን ያሉበት ተፈጥሮ እየነፈሰ ስሜትን የሚኮረኩር ነው። እንደገና አየችው ሶራ የለበሰው ስሊፒግ ባግ እርጥብ በጭቃ የተለወሰ ነው።

ዝቅ ብላ ከንፈሩን ሳመችውና ቀና ብላ ላፈቅርህ በመቻሌ ደስታ ይሰማኛል አለችው እንደዚያ እንደ ዘቢብ የጣፈጠ አባባሏን ቢሰማ ኖሮ ምንኛ በደስታ በፈነጠዘ የተቃጠለ አንጀቱ እንዴት በራሰ ግን አልሰማትም መልካም ነገር እንዲህ በቀላሉ መቼ
ይሰማል!

ኮንችት ቀስ ብላ የሞቀ ትኩስ  ትንፋሽዋን በጆሮ ግንዱ እያንቦለቦለች

“ሶራ ሶራ..." አለችውና ጭቃ የተቀባባውን አንገቱን
ግንባሩን ስትስመው አይኖቹን እንደምንም ብሎ ከፈተደ።

“ሶራ" ያ ሙዚቃዊ ጣዕም ያለው ድምፅ ጆሮው ላይ
አዜመ። ለመንቃት ታገለና አያት

ኮንችት! ጥርሱ ሳቀና አይኑ እንባ ሞልቶ ወደ ጎን ወደ
ጆሮ ግንዱ ፈሰሰ፡ ኮንችት እንባውን በምላሷ ቀመሰችው በፍቅር
የተቀመመ ጣፋጭ ነው  እንባው!

“አፈቅርሃለሁ የእኔ ማር!'' አለችው። ሶራ አባባሏ
“አታፍቅሪኝ ኮንችት!  ካፈቀርሽኝ ፍቅሬ ይከብድሻል ከከበደሽ ደግሞ ወርውረሽ ትጥይውና ትጠፊብኛለሽ:: ያኔ መከራ ይውጠኛል: ስለዚህ…" ከንፈሩን በከንፈሯ ከደነችው:: ከንፈሯ
ትንፋሽዋ ምላሷ. ሙቅ ነው።

ፍቅር ይከብደኛል!
ስፈራው ስሸሸው ኖሪያለሁ:
ካለፍቅር መሞት አልፈልግም የሞትን በር ሳንኳኳ+ የሚከፍቱት
ሲንቀራፈፉ አንተ ነጥቀህ መለስኸኝ። እኔ ደግሞ ፍቅሬን ዘንጥፌ
ልሰጥህ ወሰንኩ! ላለማፍቀር ስሸሽ እንደኖርኩት! ለማፍቀር ደግሞ ቅንጣት ታክል ፍርሃት የሌለኝ ደፋር ነኝ!

ሶራ ተምታታበት፤  ሳታፈቅረው እንዳፈቀራት አብሯት ቢዞር መከራም ገፍቶ ቢመጣ ቀድሟት ቢሞት ደስተኛ ነው።
ፍቅሯን እንደተሸከመው ሁሉ አሷም ፍቅሩን ብትሸከመው ሸክሟን ወርውራ ትሸሸው ይሆን?
👍342😱1
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_ሰላሳ


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ


የሐመር ታዋቂ ሽማግሌዎች ጫማ ጣዮች አንጀት አንባቢዎች... ቡስካ ላይ እንደገና ተሰባስበው ሸፈሮ ቡና ተፈልቶ
የጋራ ምርቃቱ ተዥጎደጎደ።

ጫማ ጣዮች ደልቲ ገልዲ ያለበትን ሁኔታ ለማወቅ
ጫማቸውን እያሽከረከሩ እየወረወሩ የጫማውን አወዳደቅ ደጋግመው አዩና “ሰላም ነው፤ ወደ ኦሞ አቅጣጫ ሄዷል" አሉ፡

"አንጀት አንባቢዎች ደግሞ ትንበያቸውን ለመጀመር ሁለት ፍየሎችን አሳረዱና አንጀቱን በጥንቃቄ አነበቡት ! “አደጋ
አልደረሰበትም ሆዱ ውስጥ ግን ነገር አለ! መንገድ አሁንም እየተጓዘ ነው  ወደ ፀሐይ መውደቂያ'' አሉ።

የፍየሎች ሥጋ በሐመር ደንብ መሰረት ወጠሌ ጥብስ ተጠበሰ፡ እሳቱ ከመሐል ነደደ የሥጋው ብልቶች ጫፉ በሾለ
ረጃጅም ችካል ላይ ተሰክቶ ችካሉ  በሳቱ ዙሪያ ተተከለ: እሳቱ ሥጋውን አይነካውም፤ የእሳቱ ወላፈን ግን ሥጋውን ሙክክ አድርጎ አበሰለው።

ሽማግሌዎች የግማሽ ጨረቃ ክብ ሰርተው እንደ
እድሜያቸው ልዩነት ተቀመጡ። ከዚያ በሐመር ደንብ መሰረት የፍየሎቹ ፍሪንባ ለሽማግሌዎች ቀሪው ደግሞ ብልቱ እየተቆራረጠ እንደየ እድሜው ታደለ።

ሽማግሌዎች ሲመገቡ ጎረምሶችና ልጃገረዶች ራቅ ብለው ቁጭ አሉ። ከልጃገረዶች ውስጥ እንግሊዛዊቷ የስነ ሰብዕ ተመራማሪ አለች: ተመራማሪነቷ የሚያውቁት የማንቸስተር ዩንቨርስቲና ከሎ ሆራ ብቻ ናቸው፡ ሐመር ላይ ካርለት አንድ የሐመር ልጃገረድ ናት። የተገረፈችውን የጀርባ ላይ ምልክት ሳትሸፍን የፍየል ቆዳዋን ለብሳ ጭኖችዋን ጡቷን ለጎረምሶች እይታ ገልጣ ፀጉሯን አኖ
ተቀበታ ከሐመር ልጃገረዶች ጋር ወሬዋን እየሰለቀች የአባቷን
የሐመር ቀዩ በሣቋ የምታደምቅ ዝናብ ናት።

ካለ ዝናብ ጨሌ ሳር ካለ ጨሌ ሳር ከብት ካለ ከብት
ደግሞ ሐመሮች መኖር እንደማይችሉት ሁሉ በጨሌ በዛጎልና
በአምባር ያጌጡ ልጃገረዶች በሐመር  ምድር ካልታዩ ሳቃቸጡ ካልተሰማ ዳንኪራቸው ካልታዬ... ሐመሮች የሉም ማለት ነው:

ካርለት አልፈርድ ከልጃገረዶች ጋር ሽማግሌዎች የሚፈፅሙትን ከቅርብ ሆና ታያለች: ጎይቲ መንደር ውስጥ ናት ከሎ ሆራ ግን የሐመር ደን (ያገባ ሙሉ ወንድ) በመሆኑ
ከሽማግሌዎች ግርጌ የተሰጠውን ያላምጣል።

ስነ-ስርዓቱ ካለቀ በኋላ ደልቲን ለመፈለጉ ከሎ ሆራና አንተነ ይመር ተመረጡና ተመርቀው አደራቸውን ከተቀበሉ በኋላ
ወደ ካርለት ሄዱ።

"መሄድ እንችላለን  ካርለት"

"ምን ተባለ?”
"
“ያው እንዳየሽው ባህላዊ ትንበያው ተፈጽሟል። ወንዙን ከመሻገሩ በፊት ድረሱበት… ብለውናል" አላት።

hዚያ ተያይዘው ወደ መንደር ሄዱና ጎይቲን አገኝዋት የተባለውን ካርለት አስረዳቻት

“ጎይቲ ለብቻሽ ላናግርሽ?”

“ይእ!  እሽ ምን አዲስ ነገር ገጠመሽ?"

ይኸውልሽ አሁን እንግዲህ ለፍለጋ መሄዳችን ነው::አንች

“ይእ ካርለቴ እኔ ልቀር ማለት ነው?

"አዎ  አንቺ ቅሪ ከሎም ሊከፋው ይችላል አየሽ
እሱ .. "

“በይ በቃሽ እቴ አንችስ አንደኔ ሴት አደለሽ: የወለድሽው ልጅ አድጎ መልሶ አያገባሽ ግን ለምን ነው የምተወጂው
ለምን ነው ለልጅሽ
የምትሳሽው እኔ በርግጥ አግብችለሁ ግን
ያልወለድሁት ሽል ሆኖ ልቤ ውስጥ  የሚኖር ሰው አለኝ ሆዴ ውስጥ ሲንከላወስ የማየው . ያ ሰው ልቤን በፍቅር መዳፍ መሃል
የያዘው በገዛ ፍላጎቴ ነበር ልቤን ከፍቼለፈት ውስጤ ገባ.. አሁን ያ ሰው ሲጠፋ ከማንም በላይ በሐዘን አንጀቱ የተመተረ ከኔ በላይ
ማንም የለም:: የፍቅር ጀግናዩ ልቤ ውስጥ የታቀፍሁትም ልጄ
ነው  አውጥቼ የማልጥለው

“ይእ! እኔኮ ከንግዲህ ከእሱ ጋር የመቃበጥ እድሌ እንደ
እትብት ተቆርጧል እትብት ከመቼ ወዲህ ተመልሶ ተቀጥሎ ያውቃል ውስጤ የታቀፍኩት ግን ከገላዬ ጋር እንደተጣበቀ ነው ለልጄ  ለፍቅሬ ጌታ እሳሳ እጨነቅለታለሁ ስለዚህ የሱን መጨረሻ ሳላውቅ ጎኔ አያርፍም! ልቤ አይተኛም::

እና የኔ እህት እባክሽ ሴት ሆነሽ የሴትነት ምጥ
ይሰማሽ" ብላ  እንባዋን
ታወርደው ጀመር።

ሰውነቴ አረ ተይ ይብቃሽ አይንሽ ይጠፋል ምን
ይሆናል ብለሽ እንዲህ ቀን ከሌት የምታነቢው?

“ይእ ካርለትም ከሎም ደብቂው ዋሾ ሁኚ አንጀትሽ
እየከሰለ ሳቂ በእዝነ ልቦናሽ እያየሽው በአካል ግን አ
እጥፍጥፍ ብለሽ ተቀመጭ! ፍቅርሽን አውጠሽ ድፊው እያሉ ሲታከኩብኝ አታይም
ስቅ ስቅ ብላ አለቀሰች እንደገና::
"ተዋት የኔ ልጆች
የልጅነት ጨዋታዋን ዘንጊው ማለትማ ደግ አይደለም ማንስ የልጅነት  ዘመኑን ዘንግቶት ያውቃል ምስጥ አለ አንተነህ ይመር: ወደ ልጅነት ዘመኑ
የኋልዮሽ እየተንደረደረ:: አየው የልጅነት ዘመን
ቡርቃውን…

“ሁሉ ነገር ሲለዋወጥ  ካለበት የማይንቀሳቀስ ትዝታ ነው የልጅነት ዘመን! የወጣትነት ዘመን" ብሎ አንተነህ ይመር እንደ
ልጁ እሱም ወደ ልጅነት ትዝታው የኋልዮሽ ሮጠ ሁሉ
የሚጣፍጥበት ዘመን በራስ መተማመን ጢቅ ብሎ ሞልቶ የሚኮፈስበት ዘመን ትዝ አለው:

ተዋት አትፍረድባት አፍኝው ቻይው ምጥሽን አትናገሪ
አትበሏት ብሶቷን ታውጣው: ሐዘኗን ትግለፀው። እንዲህ ሁናስ መቼ ሰላም ይኖራታል አብራን ትሃድ፤ ተነሽ መስታዋቴ ከለ። ካርለት በተናገረችው ተፀፀተች: አንተነህ ሲናገር ህሊናዋን ሐዘን እንደቁርጥማት አኘካት። መኪናዋ አራቱን ፈላጊዎች ይዛ ወደ ኦሞ
ተንቀሳቀሰች።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የወንዝ ላይ ጉዞውን ከጀመሩ ስምንት ቀን ሞላቸው። ወገቧ ላይ ቢጫ መስመር የተሰመረባት ሰማያዊ ጀልባ በኦሞ ወንዝ ላይ እየተንሳፈፈች ኩዱማ እና ማርኩል መንደሮች አደረሰቻቸው

ኮንችት አያቷ ባስጠናት መረጃ መሰረት በየመንደሩ
እየተዘዋወረች ስታስተውል አያቷ የነገራትን ፍንጭ ባለማግኘቷ ጎዞአቸውን ቀጠሉ።

ሙርሲ ማህበረሰብ ሲደርሱ ወንዶች ፀጉር
የማይወዱ የራስ  ፀጉራቸውን የወንድ ብልታቸውን ብብታቸውን
የሚላጩና ፀጉር ማሳደግ እንደ ነውር የሚቆጠርበት
የወንዱን የራሱንም ሆነ የጉያውን ፀጉር መላጨት ያለባት ሴቷ መሆኗንና
ፀጉር ቢያድግ ግን የምትወቀስ ሴቷ እንደምትሆን አዩ።
የሙርሲ ሴቶች ከሸክላ አፈር የተሰራ ክብ ገል ኸንፈራቸው ላይ ጠፍጣፋ እንጨት ጆሮአቸው ላይ ያንጠለጥላሉ: ቁጥሩ
ከአምስት ሺ የማይበልጠው የሙርሲ ማህበረሰብ የተሻለ የግጦሽ ፈና የእርሻ ቦታ በመፈለግ ከቦታ ቦታ የሚዘዋወር ከበርካታ አጎራባቾቹ ጋር በዚሁ የተሻለ ቦታ ለማግኘት ሲንቀሳቀስ የሚጠቃ ማህበረሰብ በመሆኑ በጥንቱ ዘመን ብዙውን ጊዜ የሙርሲ ሴቶች፡ ከብቶቹ
በግጭቱ ወቅት የሚዘርፍና ከሱዳን የሚመጡ ባርያ ፈንጋዮችም ሴቶቹን ስለሚወስዱባቸው ለዚያ መከላከያ የሙርሲ ሴቶች ከሌሎች ሴቶች የተለዩ እንዲሆኑ ገል ከንፈራቸው ላይ እንዲያስገቡ በማድረግ
የሴቶችን ዝርፊያ ማስቆሙ! ይኸ ጠቃሚ ዘዴ በማህበረሰቡ እንዲ
ለመድም ሰፋ ያለ ገል ከንፈራቸው ላይ የሰኩ ልጃገረዶች አነስ ያለ
ገል ካደረጉት ልጃገረዶች የበለጠ ጥሉሽ እንዲከፈልባቸው መደረጉ!
ያ ድርጊት ሴቶች በከንፈራቸውና ጆሮአቸው ገል እንዲሰኩ የተጀመ
ረው ተቀባይነት አግኝቶ እንዲቀጥል አሁን አሁን እንዲያውም ሰፊ
ገል hንፈር ላይ መሰካት ብዙ ጥሉሽ የሚያስገኝ በመሆኑ የቁንጅና
መለኪያ ተደርጎ በውጩ ማህበረሰብ እንደሚገመትም አወቁ።
👍23🥰1
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_ሰላሳ_አንድ


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ

ኮንችትና ሶራ በኦሞ ወንዝ ሲጓዙ በኡዱማ መርኩል
ጎዋ ኩረምና ሻንጋሮ ያሉትን የቦዲና የሙርሲ መንደሮች ካዩ በኋላ የደቡብ ሱዳንን አቅጣጫ  ይጓዝ የነበረው
አቅጣጫውን ከደቡብ ወደ ምስራቅ ድንገት እጥፍ በማድረግ መጓዝ ጀመረ

በአለምአቀፍ አቅጣጫ ማስተካከየዋ ጂፒ ኤስ'
ከሳተላይቶች ጋር ግንኙነት ፈጥራ ያለችበትን የኬክሮስና ኬንትሮስ
ዲግሪ ካወቀች በኋላ ማፑን ስትመለከት በጣም ከሚጠማዘዘው የኦሞ
ወንዝ ጉዞ በኋላ የካራ የሙሩሌ ዳሰነች ማህበረሰቦችና ዝቅ ብሎ
የሚታየው የቱርካና ሐይቅ ብቻ የሚቀራቸው መሆኑን ተረዳች በዚህ ጊዜ ኮንችት ትልቅ ሃሣብ ላይ ወደቀች የአያቷን ቀዬ ለማግኘት የቀራት እድል በጣም ውስን ነው  የዳሰነች ማህበረሰብ ያለው  ከቱርካና ሐይቅ ጥግ ሲሆን አያቷ ስለሃይቅ ፈፅሞ አንስቶ ስለማያውቅ የሱ ማህበረሰብ ዳሰነች ሊሆን አይችልም ስለዚህ ጥርጣሬዋ ወደ ሁለት ዝቅ አለ ከካራና ከሙረሌ
ከነዚህ አንዱ ካልሆነ ግን የአያቷን ቀዬ ለማግኘት
የምትወስደው አማራጭ
ጭልምልም ያለና  ምናልባት ሌሎች ተጨማሪ አመታትን የሚወስድ ይሆናል ስለዚህ ኮንችት ጭንቀት አንገቷን ሲያስደፋት ሶራ ችግሯ ምን እንደሆነ ገብቶት፡-

አዞይሽ ካሰብሽው ትደርሻለሽ" አላት::

ያ ሃሳብ አንዳች ውስጣዊ ሃይል ፈጠረላት አመሰግናለሁ ብላው ጉዟቸውን ቀጠሉ።

ትንሿ ድንኳናቸው ከኦሞ ወንዝ ራቅ ካለ ጉብታም ቦታ አግራር ዛፍ አቅራቢያ ተተክላለች።

ኮንችት ሁለት እግሯን እጥፍጥፍ አድርጋ ድንቁን
የተፈጥሮ ውበት የማታዋን ጀንበርና ልዩ መስህብ የተጎናፀፈውን የዳመናውን ቀለም እያየች የተፈጥሮን ሙዚቃ የአዕዋፍ ዝማሬ
የንፋሱን ሽውሽውታ... ታዳምጣለች።

ይህች አንደበት ያጣች ሃገር ምንኛ ታሳዝናለች። የሌላ
ውበት በውሸታም ካሜራ ቀርፀው ሌላውን እየኮረኮሩ ለማዬት ሲያራኮቱት ኢትዮጵያ ግን እንዲህ ትንፋሽ ቆራጭ የሆነውን
ውበቷን ቆንጥሮ ለዓለም ህዝብ የሚያሳይላት አጣች

ከጥሩው የተበላሸው  የሚበዛበት አለማችን ሳታወቅ ከተበላሽው ጥሩው የሚበዛባት አፍሪካ ግን ጨለማ ዳፍንታም
አህጉር ተባለች

“የሚዲያ ልሳን ያልተፈጠረባት ምስኪን ኢትዮጵያ ስለ ውበቷ ማን የራሱን ጥሎ የእሷን ያስተዋውቅላት ታውቃለህ ሶራ ስለ አፍሪካ ዜና በተለያዩ የዜና ማሰራጫዎች ስናይ አንበሳ ሲያገሳ ፏፏቴው ሲንፏፏ... አዕዋፍ ሲበሩ አውሬው ሲተራመስ ይታይና
ኢትዮጵያን የሚመለከት ዜና ሲመጣ ግን ሁሌ ከረጂ ድርጅቶች ዳቦ ሲታደል ማየት ብቻ የሰሃራ በርሃ አገሮች ግመላቸውና አሸዋቸው ሲታይ ኢትዮጵያ ዛፍ አይበቅልባት ፏፏቴም የላት አውሬና አዕዋፍም አይገኙባት የሚባባለው ብዙ ነው።

ለካ ኢትዮጵያ ምንም አላጣች: ሰው ግን ያላት
አይመስለኝም እንደ “ኢብንባቱታ እየዞረ እሚያስተዋውቃት
የላትም..." አለችው እያሸጋገረች አድማሱን አያዬች: ሶራ የሚላት
ጠፋው: ኢትዮጵያውያን በሄዱበት ስላላቸው ነገር ማለት እንኳን አይችሉም። ብዙ ኢትዮጵያውያን በሌላው ዓለም ይኖራሉ ፧ ግን ስለ አገራቸው ትንፍሽ አይሉም በቅኝ ግዛት የማቀቁት ህዝቦች
አንገታቸውን ቀና አድርገው መዘመር ሲጀምሩ ኢትዮጵያውያን ግን
የተውሶ ካባ ከጃማይካ ተበድረው ትዮጵያዊነታቸውን ከውስጥ
ጃማይካነታቸውን ከላይ ደርበው ተደበቁ። hገሃዱ እውነት ማስመሰሉን መረጡ።' ሶራ አዕምሮው ተረበሸ።

“ተፈጥሮን አትወድም? ሶራ
እስኪ እየው ይህን ውበት?
የሰው ኪነታዊ ጥበብ ምን ብሎ ሊገልጸው ይችላል?" አለችው።

“ያምራል ኮንችት... ብቻ ምን ይሆናል እያለን ያጣን
መሆናችን ያሳዝናል። ለቤት ማስዋቢያ በየግድግዳችን የምንለጥፈው የባህር ማዶ ስዕሉችን ነው። የባር ማዶው ህዝብን ደግሞ አንች እንዳልሽው? “ለመሆኑ አገራችሁ ዛፍ ያበቅላል ወይ! ይሉናል።

“ህይወት ሳናይ ገና የናታችንን ጡት ሳንጠግብ በባህር ማዶህይወት ለሃጫችንን እያዝረበረብን እንነሆልላለን።

“ከዚያ ማነህ? ሲሉን  ጸጥ ምን አለህ ሲሉን ቁልጭልጭ በመጨረሻ እነሱም ንቀው እንደ ምራቃቸው ይተፉናል!... የመጣበትን ያላወቀ የደረሰበትን ማን ይጠይቀዋል?.." ብሎ ፀጥ አለ::

ኮንችትና ሶራ እንዲህ በፀጥታ ድባብ ተውጠው ማራኪዋን ተፈጥሮ እየቃኙ የበኩላቸውን ሃሣብ ሲያንሰላስሉ የሆነ ድምፅ
ንፋሱ ይዞ መጣ: እንደገና ድምፁን ጠበቁት  ተመልሶ መጣ የወፍ ዝማሬ የወንዝ ኩሉልታ የእፅዋት ሽዋሽዋቴ
አይደለም።የአራዊት ድምፅ… ከሁሉም የተፈጥሮ ቅላፄዎች የተቀነባበረ የሙዚቃ ቃና ነው: ጥዑም ዜማው ይማርካል!
ይስባል! ከተፈጥሮ ጋር ተዋህዶ ልብ ይሰርቃል። ተያዩ ኮንችትና ሶራ: ድምፁ እንደገና እየተስረቀረቀ መጣ። ተጠቃቅሰው ተነስተው ማራኪውን የሙዚቃ ቃና ወደሰሙበት አቅጣጫ ሄዱ።

“ክላሽንኮቭ” መሳሪያውን ጎኑ ያጋደመ ሰው ወይሳውን'
ይነፋል። አዕዋፍ ነፍሳቱ ፀጥ እረጭ ብለው ያዳምጡታል፤ ሶራና
ኮንችትም ከተደበቁበት ሳይወጡ የዜማው እንቅፋት ሳይሆኑ ያን ጥዑም ዜማ በፀጥታ ማዳመጥ ቀጠሉ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ካርለት ካሎ ጎይቲና አንተህ ይመር ከካሮ ማህበረሰቦች
መንደር አንዷ የሆነችው ቆርጮ ዘግይተው ስለተነሱ ከመሸ በኋላ ደረሱ። ከዚያ ወደ መንደሩ ገብተው ሽማግሌዎች ከፀሐይ ቃጠሎ ከሚጠለሉበትና ከሚወያዩበት ኦሞ ወንዝ ዳር ላይ ካለው ዳስ ሄዱ

ቆርጮ ከፍ ብሎ ሜዳማ ከሆነ ቦታ  ላይ ያለች መንደር በመሆኗ ለጥ ያለውን የኦሞን ወንዝ ግርጌው ሌላውን የካሮ መንደር ዱሰን ከቀኝ የሙሩሌን ሚዳ ከግራ ማዶው ደሞ የማሽላ
አዝርዕቱን በስተ ምስራቅ ለጥ ያለውን የማንጎ ፓርክ አረንጓዴን ደን ማየት ስለሚቻል ቆርጮ ቀለል ያለችና የተፈጥሮ ውብት በትርኢት መልክ የሚቀርብባት መንደር ናት።

ከሎና አንተነህ ሽማግሌዎችን መጀመርያ ተጥሎ ጎረምሶችን የሐመሩን ደልቲ ገልዲን አይተው እንደሆን ጠየቋቸው በእርግጥ ከጎረምሶች ጥቂቶቹ እንጂ ብዙዎቹ አያውቁትም  የሚያውቁት አላየነውም አ
ሲሉ ሌሎቹ ግን ብዙ የሐመር ወንዶች ከከብቶቻቸው ጋር ሙርሌ ያሉ መሆናቸውን ነገሯቸው።

በእርግጥ ይህ ለአንተነህ  እንግዳ አልነበረም ዝናብ ሲቀንስና የግጦሽ ሳር ሲጠፋ የሐመር ከብቶች ፍየሎችና በጎች ወደ ኦሞ ወንዝ  ይመጣሉ ኦሞ ወንዝ አካባቢ ሳሩ ጥሩ ነው። በዚያ ላይ ደግሞ ከብቶች የሚጠጡት በቂ ውሃ ከኦሞ ያገኛሉ ስለዚህ የቆርጮ
መንደር ካሮዎች እንደነገራችው ሐመሮች ከብቶታቸው ጋር በሙርሌ ሜዳና በኦሞ ወንዝ ዳር አሉ::

“ታዲያ ምን ይሻላል? አለች ካርለት ከሎንና ጋልተንቤን

የሚሻለውማ ለአንድ ሶስት አራት ቀን እዚሁ አካባቢ
ማጠያየቅ ነው" አላት አንተነህ ይመር ረጋ ብሎ እያንዳንዱን ቃል
እየረጋገጠ፡

ጎይቲ ጆሮዋን በሁለት እጅዋ ይዛ እግሯን አጣጥፋ መሬት ላይ ቁጭ ብላለች:: ደልቲ ቆርጮ መንደር ነኝ ብሎ እንደነገራት ሁሉ ስትመጣ ባለመኖሩና ያለበትም አለመታወቁ ሆዷን አዋለለው ! ሆድ ባሳት...

“እንግዲህ ለዛሬ እዚሁ እንደር ነገና ተነገ ወዲያ ሙርሌ ወርደን እንፈልገውና ተዚያ ወደ ሌሎች የካሮ መንደሮች ዱስና ለቡክ
እንሄድና እንፈልገዋለን!" አለና ጋልታምቤ አያቸው። ሁሉም ተስማሙ፤ ጎይቲ ግን ተነጫነጨች። እሱን ሳታይ ጎኗን ማሳረፍ
አልፈለገችም: ጀግናው እየተንጓለለ እሷ እንቅልፍ እንዴት ያሸልባት? ግን ከአቅሟ በላይ በድምፅ ብልጫ ተሸነፈችና ሁለት
ድንኳናቸውን ዘርግተው ካርለትና ጎይቲ አንዱ ድንኳን ጋልታምቤና ከሎ ደግሞ ሁለተኛው ድንኳን ሊተኙ ተስማሙ።
👍14
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ

ኮንችትና ሶራ የሰጎን ላባ የተሰካበትን የራስ ጌጥ(ጶሮ) እንደ አቦ ሸማኔ
አይን አሸጋግሮ  እየተንተገተገ የሚመለከተውን አይኑን የተተለተለ ሳንቃ ደረቱን እየተመለከቱ  ከንፈሩን አሞጥሙጦ የሚያሽለከልከው ትንፋሹ ከፍ ዝቅ በሚሉት ጣቶቹ እያንኳለለ የሚያጣው ስሜተ ሰላቢ ዜማውን ሳይንቀሳሱ ሲያዳምጡ  ወይሳ ተጨዋቾቹ ድንገት ዜማውን ቀጥ አደረገና መሳርያውን አንስቶ ሲያቀባብል ሶራና ኮንቺት
ድንግጥ ብለው ሲመለከቱ ድው አድርጎ ሲተኩስ አመዳቸው ቡን ብሎ ነፌሴ አውጪኝ መሬት ላይ ሲንበለበሉ እንደገና ተኮሰ።

ከዚያ ለጥቂጥ ሰአታት ከመሬቷ ጋር ተላትመው ጠበቁና ቀና ብለው ሲመለከቱ   ሰውየው ኦሞ ወንዝ ዳር ሄዶ ተረጋግቶ ወንዝ ዳር ሄዶ ቆሟል ኮንቺት እየተሳበች ወደ ሶራ ተጠግታ

"ለምን ተኮሰ? አለች ሶራን።

"አልገባኝም"

"አይቶን ይሆን?"

አይመስለኝም ቢያየን ወይንም ድምፅ ሰምቶረ ቢሆን ኖሮ በሁኔታው ማወቅ እንችል ነበር።

"እሱስ ልክ ነህ ቢገርመኝ እኮ ነው ተረጋግቶ መቆሙም ለጠየቅሁት ጥያቄ ፍንጭ ሰጪ አይደለም ስትለው ከኦሞ ወንዝ ማዶ ድምፅ ተሰማ ሰባቶ ጎረምሶች ናቸው። ወደ ወንዙ ሲጠጉ

"ፃሊ!” አላቸው በካሮኛ  ሰላም ናችሁ ለማለት:

'ፃሊና..." አሉትና አምስቱ ወንዙ ዳር እንደቆሙ ፤ ሁለቱ ዳር ላይ የቆመች ቀጠን ብላ ረዘም ያለች የእንጨት ታንኳ ላይ
ወጡና በረጅም ዘንግ ውሃውን ቁልቁል ሲገፉት ታንኳዋ እንደ ውሃ
እናት ውሃውን ወደ ጎን እየሰነጠቀች መጣች::

ለካ የተኮሰው እነሱን ለመጥራት ነው:: ጥሪ በተኩስ አይገርምም!” ስትል ሶራ በአድናቆት ራሱን ወዘወዘ።

“እነሱ ግን እነማን ናቸው?"

"አላውቅም ኮንችት  ብናነጋግራቸው ይሻላል?" ሲላት ወዲያው ከተደበቁበት ወጥተው ወደ ሰውዬው ሲጓዙ ፊቱን ዞሮ
የቆመው ሰው የሰው ዳና ሲሰማ ከመቅፅበት መሳሪያውን ከትከሻው
አውርዶ፡-

“ከጠን ማሲዲ" ብሎ መሣሪያውን አቀባብሉ ደገነባቸው።

“ኖት አሱስቴ" አለች ኮንችት በስፓኒሽ እጅዋን እያወዛወዘች ተረጋጋ ለማለት:

ባለመሣሪያው ትኩር ብሎ ሲያያቸው ቆየና “ነጋያ! አለ
ከተቀመጠበት ተነስቶ መሳሪያውን ወደ ትከሻው እየመለሰ: ሶራ ለሰላምታ አፀፋውን መለሰ። “...ሐመር አፎ ዴሲቲኒ"  አለው ባለመሣሪያው ሐመርኛ ትችላለህ ለማለት።

ሶራ ፈገግ ብሎ “ሊካ ሊካ ቂንሲዲ...” (ትንሽ ትንሽ
እችላለሁ) አለው። ባለመሳሪያው ፈገግ አለ: ያኔ ነብርነቱ ተለውጦ
እንደ ድንቡሽዬ ህፃን ፈገግታው የሚማርክ ሆነ

ባለመሳሪያውና ኮንችት ከሁለቱ የታንኳዋ ቀዛፊዎች ጋር ተሻግረው ሲጠብቁ ሶራ ጀልባዋን ይዞ ሄደና በጀርባቸው አዝለው
ጀልባዋን ከአምስቱ ጎረምሶች ሁለቱ እየተሳሳቁ ተሸክመው ጫካው
ውስጥ ገቡና በመስመር ሆነው በትላልቅ የግራር የኮሶ... ዛፍ ውስጥ ለውስጥ ትንሽ እንደተጓዙ ኮንችትና ሶራ ዛፍ ላይ እንደ ጦጣ የሚንጨዋለሉ ልጆች አዩ: ቆይቶ ደግሞ በቋንቋቸው ቶሎ ቶሎ
የሚናገሩ ልጃቸውን በቆዳ ብብታቸው ስር ያዘሉ እናቶችና ሽምገል
ያሉ ወንዶችን አዩ።

ጨቅላ ህፃናት ዛፍ ላይ በቆዳ ተንጠልጥለው አንዳንዶቹ ተኝተው እየተቁለጨለጩ ሲወዛወዙ እያዩ እንደ ሄዱ ከርቀት ላይ
የወፍ ጎጆ የሚመስል የኤሊ ቅርፅ ያለው ጎጆ ቤት ተመለከቱ።

ኮንችትን ሲያዩ ህፃናት  ወላጆቻቸው ጉያ እየገቡ ወደ መንደራቸው እየሮጡ አለቀሱ: ለኩዩጉ ህፃናት አስፈሪው አውሬ ቀላ ያለ ልብስ ለባሽ ሰው ነው። ከፍ ያሉት ግን የመጣው ይምጣ ብለው በቋንቋቸው ሰላም ቢሏትም ፍርሃታቸው ግን ያስታውቃል: ለጊዜው
ሰላምታቸውን ልብ ብላ አልተከታተለችም ነበር ድንገት አንድ ሽማግሌ፡-

“አሹቃ” ሲሏት አያቷ የነገራት ሰላምታ ትዝ አላት:
ኮንችት አያቷ የሚጠቀምባትን መቀመጫ የመሰለች ሁሉም
ሽማግሌዎችና ወንዶች ይዘው አየች:: ሶራን ዘወር አለችና ምን የሚባሉት ማህበረሰቦች ናቸው?" አለችው ማፕ ላይ ያየችውን ስም ለማስታወስ እየሞከረች:: ሶራ መጀመሪያ ያዩትን ባለ ዋሽንት ጠየቀው።

ሙጉጅዎች ናቸው። እነሱ ግን ራሳቸውን ኩዩጉ ነው
የሚሉት አለው ነገራት ሶራ  ለኮንችት። ማፕ ላይ መጉጅም ሆነ ኩዩጉ የሚል እንዳላየች እርግጠኛ ነች: ለማረጋገጥ ግን ወዲያው
ማፕዋን ዘርግታ አየች፤ ሁሉም እሷ ላይ አፈጠጡባት። ማፑ ላይ
የሉም። ካርታው ላይ አየች የሉም፤ ይበልጥ ደነቃት።
ኦኗኗራቸውም ልዩ ነው ፤ የጫካና የወንዝ ዳር ሰዎች: ከመንደሩ እንደደረሱ ሰዉ በአድናቆት ቆሞ አያቸው: ህፃናት ራቅ ብለው ሽሽተው ያያሉ:: አንዱ 'መጡላችሁ' ሲል ሌሎች ህፃናት ደግሞ
እየተሯሯጡ በመላቀስ ይጯጯሃሉ…..

ኮንችት ከጀርባዋ ያዘለችውን ጓዟን አውርዳ ተለቅ ተለቅ ያሉ የአያቷን ፎቶ አወጣች: የዘጠኝ ሰዓት ፀሐይ አሁንም ማቃጠሏ
እንብዛም አልቀነሰም:

ፎቶውን የያዘውን እጅዋን ወደ ህዝቡ ዘረጋችው። ፈሯት፤በምልክት እንኩ' አለቻቸው: ትክ ብለው እያዩ ዝም አሏት ከዚያ ባለዋሽንቱ ውሰዱ' አላቸው በሐመርኛ።

ሶራ ደስ አለው የራሳቸውን የሆነውን ቋንቋ ሲናገሩ
አንድም ቃል ሊገባው አልቻለም ነበር ሐመርኛ ከቻሉ ግን እሱም
ሊያናግራቸው ይችላል። ኩዩጉዎች ግን ሐመርኛን ብቻ አይደለም የሚችሉት። ሙርሲኛ ኒያንጋቶምኛም ይችላሉ።ስለዚህ ሶራ
በሐመርኛ፦

“ውሰዱና እዩ ችግር የለም” አላቸው። አሁንም ዝም ብለው ኮንችትን ሲመለከቷት ቆዩና አንዱ
ሽማግሌ ሌላውን በጆሮው አናገረው ከዚያ ብድግ ብሎ መጣና ተቀበላት።

ፎቶውን ዘቅዝቆ ስለያዘው ኮንችት አስተካክላ ሰጠችው ሽማግሌው ቀረብ እራቅ አድርጎ አየውና በቋንቋው የሆነ ነገር
ተናግሮ ወደ ሀዝቡ ሲጠጋ ለማየት ህዝቡ እንደ ንብ ዙሪያውን ከበበውና ሁካታ ሆነ: ማንም ሌላውን አያዳምጥም።

ከዚያ ሁሉም እነ ኮንችትን ጥለው እንደ ድንጉላ እምም.. እያሉ ወደ አንድ አቅጣጫ ተሯሯጡ: ኮንችትና ሶራ እርስ በርስ
ተያዩ ህዝቡ የሄደበትን ምክንያት ግን ከመካካላቸው ሊመልስ የቻለ አልነበረም።

አንድ ጎጆ ቤት ሲደርሱ ሁሉም ቆሙ። ከውስጥ የሆኑ ሽማግሌ አንጀታቸው ካጥንታቸው ጋር የተጣበቀ አጎንብሰው ወጡ ህዝቡ አሁንም ክብብ አደረጓቸው።
ከዚያ እንደገና ሁካታ ሆነና ጎረምሶች እየተሯሯጡ ርቀው ሄዱ። ፎቶዎችም በልጥ ታስረው ሽማግሌው ከወጡበት ጎጆ ፊት
ለፊት ተንጠለጠሉና ሴቶች ሰማይ ሰማይ እያዩ እልልታውን አቀለጡት ወንዶች እየዘለሉ ጭፈራ ጀመሩ።

ኮንችትና ሶራ እንደገና ተያዩ። ምን እየተሰራ እንደሆነ ማወቅ ተሳናቸው: ባለ ዋሽንቱን ጠየቁት፤ መልስ አጡ። ከዚያ
አራት አምስት መሳሪያ የያዙ ሽቅብ ተኮሱ።

ኮንችትና ሶራ ደነገጡ፡ “ምን እየሰሩ ነው ሶራ?" አለች
የሶራን ትክሻ እየወዘወዘች
በፍርሃት: ሶራ ትከሻው ከፍ ዝቅ አድርጎ አላውቅም አላት በምልክት።  ሰው ከየጫካው ተሰባሰበ !
ጥሩንባው እየተነፋ እልል መባል ጀመረ።

ጫካ የሄዱት ጎረምሶች በሾርቃ የሆነ ነገር ይዘው
እየተሯሯጡ መጡ የደከማቸው አይመስሉም የግንባራቸው ደም
ስር ግን ውሃ እንደሽረሸረው የዋርካ ስር አበጥ አበጥ ብሎ በየአቅጣጫው ተጋድሟል። እንደ ተመለሱ ከህዝቡ መሃል ገቡ
ከሌላ ጎጆ ደግሞ ማር የያዘ ትልቅ ቅልና ውሃ ሌሎች ጎረምሶች አመጡ። ውሃውና ማሩ ተቀላቀለና በእንጨት ተማሰለ።

ከዚያ ጥሩንባው እየተነፋ እልል እየተባለ እየተጨፈረ... ሁሉም የሉካዬን ስም እየጠሩ ሰማይ እያዩ ቆዩና ከሲታ ሽማግሌውን አስቀድመው ሶራ ኮንችትና ባለወይሳው ወደ ቆሙት እያሸበሸቡ
እየዘለሉ ጡሩንባው እየተነፋ መጡ።
👍18😢2👏1
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_ሰላሳ_ሦስት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ

የኩችሩ መንደር እንደደመቀች ናት:: ብዛት ያላቸው አሣዎች በወጣቶች በጦር ተወጉ ማጅራታቸውን በዱላ ተመቱ በመንጠቆ ተያዙ፤ ሣር በል የሆኑ አራዊት የሜዳ ፍየልና ውድንቢት ታድነው ተገደሉ ፤ ከጫካ ብዛት ያለው ማር ተቆረጠ፤ ቦቆሎና ማሸላ ኦሞ ወንዝ ተወስዶ ተወቃ.. ይበላል ይጠጣል
ይጨፈራል ይመረቃል።

ሉካዬ ሰማይ ላይ ሆኖ ምስሉ እየታዬ ቢሆንም ሶስት ቀን ሙሉ አልመጣም:

“ሎካዬ ለመምጣት ያስባል! ነጩ እባብ ግን “አልመጣም ብሎ አስቸግሮታል ደንቡን ሳናጓድል ሥርዓቱን ብናሟላ ግን ሁለቱም ይመጣሉ" ስላሉ ሽማግሌዎች፣ ሴት ወንዱ ይኳትናል ሰማይ ላይ ላሉት  ለሎካዬና ለነጩ እባብ በደስታ ለመፍጠር።

ኮንችት የሎካዬ የልጅ ልጅ መሆኗን ከሰሙም በኋላ
የመንደሩ ሰው ተስብስቦ ከአያቷ ወንድም ቤት ፊት ለፊት ተቀመጡ" የሉካዬ ፎቶ ጎጆው ላይ እንደተንጠለጠለ ነው። ከሥሩሁሌም ግልገል ፍየል ከካሮ እየመጣ ታርዶ ይቀመጥለታል።

ልጃገረዶች ኮንችትን ወደ ጎጆው ቤት ውስጥ ይዘዋት
ገብተው ውስጥ ሱሪዋንና ጡት ማስያዥዋን ሳይቀር አስወለቋት::ከውጭ ይዘፈናል እልል ይባላል. ልጃገረዶች በአኖና የዱር እጣን አላቁጠው ፀጉሯን ሰውነቷን ቀብተው የፍየል ቆዳ አለበሷት: ከዚያ
ይዛው የመጣችውን ልብሷን በእጅዋ እንድታንጠለጥል ሰጧትና ከቤት ወደተሰበሰበው ህዝብ ይዘዋት ወጡ። እሳት ነዷል.
ይጨፈራል... ሁለት ልጃገረዶች አንገታቸውን ደፍተው እጅና እጅዋን
ይዘው ልብሷን ወደ እሳቱ አስወረወሯትና እልልታቸውን ሲያስነኩት
የተሰበሰበው ህዝብ እንደገና ፈነጠዘ ዘለለ  አቅራራ.. ጡሩንባ
እልልታ ተኩስ ድብልቅልቅ አለ:

ኮንችት የተረጋጋች አትመስልም። ቆዳዋ ግን አማረባት ጡቶችዋ ቀልተው ቆሙ ለስላሳው ጭኗ... ሁለመናዋ አጓጊ ሆኗል:
ድንጋጤው ስላልለቀቃት ግን ካንገቷ በላይ ውበቷ ቀንሷል።

ሴቱም ወንዱም እየመጣ እጅዋን እየሳመ ደስታውን
እየገለፀላት ወደ ጭፈራው ሲገባ እንደቆዬ ሰው ሰላምታ እየሰጣት
ኩዩጉነቷን አንድነታቸውን እያረጋገጠላት ከሄደ በኋላ ሶራ እየሳቀ ወደ ኮንችት ተጠግቶ አቀፋት: ሽጉጥ አለች ወደ ደረቱ እንደ
እንቦቀቅላ  ህፃን፡ አይቷት እንደማያወቅ ሁሉ በሁለት እጆቹ ጡቶችዋን እንደያዘ ፈገግ ብሎ ቁልቁል አያት: ልትስመው ስትል
የሆነች ሴት መጥታ መነጨቀቻት። የኩዩጉ ሴት ወንድን በአደባባይ
አትስምማ!

“እሺ!” አለች ኮንችት
የሴትዮዋ ግሣፄ ስለገባት።

“ለምን ልብሴን አወለቁ?  ለምንስ እንዳቃጥለው አደረጉ?''አለችው እሏና ሶራ ከእቅፎቻቸው ከተላቀቁ በኋላ

“የአያትሽን ባህል ረድኤት ለማካፈል! ተፈጥሮአዊ ፀጋሽን ለመመለስ ጎረምሶች ፍቅራቸውን እንደ ወለላ ማር እንዲያውጡሽ….
ለማድረግም" አላት ሶራ እየሳቀ
ባለወይሳው ኮንችትን ባህላዊ ልብስ ለብሳ ሲያያት ደስ አለው። ስለዚ ፈገግ ብሎ ከሌላው ጊዜ በተለዬ ሁኔታ ቀረባትና

ካርለትን አይተሻታል ወይ? ብለህ ጠይቃት" አለው ሶራን።ሶራ የነገረውን ለኮንችት ሲተረጉምላት ተኩስ ተሰማ ተኩሱ
ተደገመ።

ጎረምሶች እየተሯሯጡ ወደ ኦሞ ወንዝ ሄዱ። ጭፈራው
ግን አልቆመም። ባለወይሳው ከሌላ አካባቢ የመጣች ፀጉረ ረጅም
ልብስ ለባሽ... ሁሉ እሱ የሚያውቃትን ካርለትን ያውቃል ብሎ አምኗል።

“ካርለት! ማነች ካርለት? የአባቷስ ስም? ዜግነቷስ?”
ኮንችት በስም ብቻ አውቃለሁ፤ አላውቅም  ማለት ትክክል
እንዳልሆነ ታውቃለች: በያገሩ ስንት  ካርለት
ዴቪድ... ሊኖር ፥ይችላል። መጀመሪያ ስም  አገር ሥራ የሚኖርበት አድራሻ...
ለማንነት መለያ ይጠቅማል: በተረፈ በደፈናው ይከብዳል።ባለወይሳው ግን “አውቃታለሁ' አለማለቷ አስከፋው:

ምን የማረጋት መሰላት ካርለት ልጃገረድ ናት!
ብታጠፋም አላገባኋት ጥሎሽ መክፈል አልጀመርሁ... እና-
አላዝባት አልቀጣት... ይህን እያወቅች መደበቋ ምን ይሉታል? ብሎ አስቦ አዘነባት በኮንችት:

በኦሞ ወንዝ ዳር ካለው ጫካ የሆኑ ሰዎች ብቅ ሲሉ ህዝቡ ተንጫጫ። ኮንችት ቀና ብላ ታይ የኩዩጉ ጎረምሶች እንግዶችን
እየመሩ ይመጣሉ። ለኩዩጉ መንደር በሩ ኦሞ ወንዝ የበሩ ደወል ተኩስ መሆኑ ኮንችትን እንዳስደነቃት ነው።

እንግዶቹ ሲጠጉ አንዷ ነጭ ናት ሁለት ወንዶችና
አንዲት ሴት አብረዋት አሉ። እነሱ ከነጭዋ አንፃር ጥቁር ናቸው።እንግዶቹ እንደቀረቡ ባለወይሳው ዘወር ብሎ አያቸውና ከመቅፅበት
አይኑን እንደ አውሬ አፍጦ አንገቱን እንደ ሰጎን መዘዘው
ሁለቱ ሴቶች ባለወይሳውን ሲያዩ ፊታቸው በደስታ ፀዳል አበራ ቸኩለው ግን ወደ እሱ አልተጠጉም።
ከዚያ ነጯ እንደቆመች ሌላዋ ሴት ቀረብ አለችና፡-

“አያ ደልቲ!'' አለችው
በሐመርኛ:ጎይ ቲ"

ረጋ ብሎ ከተቀመጠበት ተነሳ ላዩ ላይ ተጠመጠመችበት: እቅፍ አድርጓት ቆየና ለቀቃት:: ነጭዋንም ካርለት" ብሉ አቀፋት፤ እሷም አቀፈችው ...

የኩችሩ መንደር ኗሪ በሁኔታው ተደንቆ ጭፈራውን አቁሞ
ያያል።

ካርለት! አለች ወገቧን ወደኋላ ለጥጣ በአድናቆት አፏን እንደከፈተች ኮንችት።

ኮንችት! ካርለት ኮንችትን ከእግር ጥፍሯ እስከ ፀጉሯ
በአድናቆት እያየቻት ቆየችና

“አገኘሻቸው?" አለቻት

“አዎ ተገናኘን” ብላ ኮንችት ሳቀች ተሳሳቁ ኮንችትና
ካርለት! ህዝቡም አብሯቸው ሳቁ! መንደሯም በሣቅ ሙላት ተጥለቀለቀች

“ኮንችት እንዴት ልታገኛቸው ቻልሽ?''

“..በጀልባ ነበር እኔና ሶራ የምንጓዘው፤ እና ባጋጣሚ እዚህ ደረስን

“ማንም ሳይመራሽ?'

“ባገኘሁት ማፕም ሆነ ካርታ ኩዩጉዎች ለመኖራቸው ፍንጭ የሚሰጥ ምልክት የለም:: አያቴ የስጠኝ የአደራ ምልክቶች ግን እንደ ኮኮብ መርተውኛል ያም ሆኖ ግን ባጋጣሚ ኩዩጉዎችን
የሚፈልገው ሰው ተኩሶ እነሱ ሲመጡ ማየት ባንችልና ተጠራጥረን
አብረን ባንመጣ ልፋቴ መና ሆኖ! ስሜቴ በስለት ቢላዋ ለሁለት ተተርትሮ ወደ መጣሁበት እየቆዘምኩ እመለስ ነበር። አጋጣሚው
ግን ረዳን፤ ተገናኘን:

“እንዴት አገኘሻቸው ታዲያ?

“ደግ ሩህሩህና ተግባቢዎች ናቸው:: ኑሯቸው በኦሞ ደለል ላይ ማሸላ በማብቀል ከጫካ ማር በመቁረጥና አሣ በማጥመድ ነው።
ከብት ፍየል የላቸውም፤ ይህ ደግሞ ከብት በሚያረቡት የአጎራባች
ያስንቃቸዋል:: ቁጥራቸው
ማህበረሰቦች ማነሱ ከብት
ባለማርባታቸው የሚያጠቃቸው ብዙ ነው። ስለዚህ የሚኖሩት
በጠባቂ ሞግዚት ነው"

“በሞግዚት?”

“አዎ ካርለት!  ጥንት ሞግዚታቸው ካሮ ማህበረሰብ ነበር። አሁን
ግን የካሮዎች ኃይል እየደከመ የኒያንጋቶሞች
(ቡሜዎች) ኃይል እየበረታ በመምጣቱ ኩዩጉዎች ወደ ኒያንጋቶሞች በመጠጋት ከአጎራባች ማህበረሰቦች የሚደርስባቸውን ጥቃት
ሞግዚታቸው ኒያንጋቶሞች ይከላከሉላቸዋል።

“ታዲያ ለሃያሉ ሞግዚታቸው ማር እህል  ከሚሰፍሩት ሌላ ልጃገረዶቻቸውን ካለጥሎሽና ካለ አንዳች ክፍያ ኒያንጋቶሞች
በሚስትነት ይሰጣሉ። ኩዩጉዎች ግን ከኒያንጋቶሞች ካሮዎች.. ጋርዐመጋባት አይችሉም ስለሚናቁ።

“ኩዩጉዎች የሌላቸውን የማይመኙ በዚህ ኑሯቸውም ከአቅም በላይ ለሆኑ ነገሮች የማይሰጉና የማይጨነቁ ናቸው። ከሁሉም በላይ ባህላቸውን አክብረው ራሳቸውን ሆነው መኖርን ይመርጣሉ።
የሚገርምሽ በልጅነቱ ከነሱ የተለየው አያቴ እንኳን እንደ
ዘይትና ውሃ ለረጅም ጊዜ ከኖረበት ስልጣኔና ባል ጋር ሳይዋሃድ ነው ወደ መቃብሩ የወረደወ:
👍261👎1🥰1
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_ሰላሳ_አራት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ


“ይህ ክላሲካል ዋሽንት ተጫዋች ማነው?"

ሐመሩ የፍቅር ጓደኛዬ ነው ዋሽንት ግን መጫወት
ይችላል?

“ያውም ልብን በሚሰልብ ቅላፄ ነዋ የአጨዋወት ስልቱ ልብሽን የሚሰውርበት አካልሽን የሚያንሳፍፍበት... አንዳች ኃይል አለው:: ከርቀት የሚቀሰቅስሽ የሚንጥሽ…"

“እንኳን ደስ አለሽ በይኛ!በፍቅር ክንዱ አፍቃሪዎቹን
በተራ ያሰለፈን ጀግና በሙዚቃ አርቱም የምንተኛበትንና
የምንነቃበትን ፕሮግራም ያወጣልናላ ደልቲ ገልዲ…

ምን

የሱ ታሪክ ብዙ ነው ኮንችት: በርቀት ስታይው የፍልፈል
አፈር! እየተጠጋሽ ሄደሽ ውስጡ ስትገቢ ግን እንደ ተራራ እየገዘፈ፤ወደላይ እየተከመረ የሚሄድ የሚስጥር ዓለም ነው።''

“እውነትሽን ነው"

“አዎ  ኮንችት"

ኮንችት ደነቃት ገረማት ፍቅራቸውን ልታየው ሞከረች አንዴ ካርለትን
ተመልሳ ደልቲን… አየችው አጠጋጋቻቸው አሰተቃቀፈቻቸው
አሳሳመቻቸው… በሃሳቧ ምራቋን እየዋጠች፡፡

“ምነው ኮንችት? ካርለት ኮንችትበብ ጭልጥ ስል
እየሳቀች ቀስቅሳ ጠየቀቻት።

“እንጃ! ግን." ኮንችት ሃሣቧን ገደበችው ዋጠችው ካርለት እንደገና ሳቀች። ሳቋ ደልቲን ጎሻሸመው። ዞር ብሎ ፈገግ
ሲል የኮንችት አይኖች ጥርሶቹ ላይ ተሰኩ! እንደ በረዶ ጥርሱ ነጭ ነው።

“ታፈቅሪዋለሽ?” ሞኝ ሆነች ኮንችት

"አዎ የፍቅር እንጥሌን ሌሎቹ ተንጠራርተው ሲያጡት ተቀምጦ የነካው እሱ ብቻ ነው ተሳሳቁ ካርለትና ኮንችት::

'እንጥሌን እምም...” ኮንችት እንደገና ምራቋን ዋጠች።

“እሱም ያፈቅርሻል?”

“እኔ እንጃ... ቢሆንም አይላኝም እኔ ለእሱ ገና
ያልተገራሁ ባዝራ ነኝ: ስለዚህ ከኔ ይልቅ እሷን ይወዳታል:"

ካርለት በአገጯ ጎይቲን ለኮንችት አሳየቻት
ኮንችት ጎይቲን እስከ አሁን ለምን እንዳላስተዋለቻት
ገረማት የጠይም ቆንጀ እግሮችዋና ወገቧ የሚያምር ችምችም
ያሉት የወተት አረፋ ጥርሶችዋ የሚያስጎመጁ ሆነባት።

ኮንችት ጎይቲን ስታያት እንደቆየች ስለ ውበት አሰበች።ስለ ሰው ልጆች የራቁት ውበት ልብስ ስላልሸፈነው ተፈጥሮአዊ ገላ አለመች:: ሰው ሁሉ በተፈጥሮው ማራኪ ነው ያምራል ይስባል...

“አሁን ግን እሷ አግብታለች ስለዚህ የደልቲን ፍቅር እንደ
ማንጎ እየጋጥሁ እረካባታለሁ ስል ጀግናው ሌላ ቆንጆ በፍቅሩ ግዳይ
ጥሎ ቆንጀዋ ልቡን ሰብራ ልትገባ ስትፈልጠው ደረስሁ... ሳቀች

ካርለት: ሳቋ ኮንችትን ስለውበት ከምታልምበት የፍልስፍና ዓለም ቀሰቀሳት።

"እሷ ደግሞ ማን ናት?"

“ዳራ ትባላለች ሐመር ናት: ልቅም ያለች ቆንጆ!...”

ካርለትና ኮንችት እንዲህ ሲጨዋወቱ ጎይቲ አንተነህ
የምታየው የምትሰማው የምትነካው የምታልመው... አንድ ሰው ነው:: ከፊት ለፊቷ የተቀመጠውን የፍቅር ጀግናዋን ትኩር ብላ
ስታስተውለው ቆይታ ወደ እሱ ሄደች።

በእጇዋ ጨሌ
አንጠልጥላለች መለሎ
አንገቱ ላይ አጠለቀችለት! ቀና ብሎ አያት እሷም ዝቅ ብላ አየችው።

አልተቀየረም  እሷም
አልተቀየረችም ትንፋሻቸው ይጥማል። የጫካ ነፃነታቸው ግን የለም ጭኗቿ አይታቀፏትም ደረቱ ላይ አትተኛም፤እሱም ዳሌዋን አያቅፍም
ጡቶችዋ እንደ እንቧይ ደረቱ ላይ አይነጥሩም...

“ይእ! እንኳን ደና ሆነህልኝ እንጂ..." ብላው እንባዋ
በአይኗ ዙሪያ ተኮለኮለ

“ምን ይሆን ብለሽ ነው አንች..." እሱም መናገሩ
አቃተው: ይህን ሲል ጎይቲ የፍቅር ትዝታው ጠቅ አድርጎ ወጋት ስለዚህ ሃዘን የሰራ አካላቷን በጨካኝ ስለቱ አብጠለጠለው። ያኔ ልቧ፣ ሲኮማተር አይኗ ዙሪያ የተኮለኮለው እንባዋ ኩልል ብሎ ወረደ።

“ይእ ባይሆን አልጣህ- አይንህን ልየው ፍቅርህ ልቤ ውስጥ ሲንፈራገጥ አንተ ሳትኖር እንደ ምጥ ያስጮኸኛል ጤና ይነሳኛል። እንኳንም ግን ፍቅርህ ተሆዴ አይወጣ! እንኳንም
አልገላገለው! እሚወለድ ቢሆን ሲያድግ ብቻዬን ጥሎኝ ይሄድ ነበር.." ትክዝ አለች እይታዋን የከለከለውን እንባዋን ጭምቅ አድርጋ
አፍስሳ።

ስሜቷ ጭምትርትር ያለውን ጎይቲን ሲያይ ደልቲም የሆነ
ነገር እሱም ሆድ እንደጉማሬ ሲገላበጥ በዓይነ ህሊናው ታየው።

“ተይው የኔ እህት! ተይው እርሽው ተንግዲህ ተሱ
ምሰይ: የአባት ደንብ ተሁሉም ይቦልጣል  ተፍቅርም!! ስለዚህ
ጉም መቼስ አይዘገን.." ብሎ የባሰ የሐዘን ቦይዋን ከፍቶ ለቀቀባት
የሚያጉረመርም ሳግ ቀጥሎ የህሊና ብራቅ ከዚያ እንባዋ አጨቀያት:
ጎይቲ እንገቷን ደፋች: እሱን ማጣቷ እውነት ነው! እውነትም የሱ የመሆን
እድሏ አክትሟል፤
አክትሟል፤እውነትም
የፍቅር ጥገታቸው
ነጥፋለች...

ጎይቲ እንባዋ ቦዩን ይዞ ፈሰሰ፣ እንባ የጠማት መሬት ደግሞ የፍቅር እንባዋን እያጣጣመች ጭልጥ አድርጋ ጠጣችው::መሬት ሰዎች ሲፋቀሩ የሚተርፋት እርግጫቸው ነው ሲያዝኑ ግን ፀሐይ ያቃጠው ጉሮሮዋን ጨዋማ እንባቸው ጥሟን ያረሰርስላታል ጥሟን ይቆርጥላታል ጣፋጩ የሰው ልጅ እንባ የጎይቲን እንባም መሬቷ አፏን ከፍታ ጠጣችው።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

' ...ይእ ተወኝ አንተ ሰው! መች አንተ ለእኔ አነስከኝ።
የአንተ መሆኔን ነጋሪ አልሻም ሰው መቼስ ካሉት በረት ሙሉ ከብቶች የሚቆረቆረውና የሚቆጨው አውሬ የበላበትን ጫካ
ያስቀረበትን ከብት አይደል! እንደማያገኘው ልቦናው ያውቀዋል ቢኖርም ለእሱ እስካላለው ድረስ በሽታ ይገለው ይሆናል: ይህን ግን
አያስብም። ዘወትር ቁጭት ብቻ ወይኔ ብቻ. እሮሮ ብቻ

“አያ ደልቲ የኔ አይደለም:: ከእንግዲህ በሴትነት መላዬ
ጀግናውን እየመራሁ ወስጄ ልቤ ውስጥ አላስተኛውም ሙቀቱን አልጋሪውም... ያች የፍቅር ጨረቃ አሁን የማይወለደውን ጨቅላ
አቅፌ እሽሩሩ….' የምልባት ብርሃን ናት: የፍቅሩን ትዝታ!
የጀግናውን ገድል፤ የማይጎረምስ ፍቅሩን፤ ጠረኑ የማይለውጥ
ፍቅሩን... የማልምባት ናት ጨረቃ!

"በእጅ ያረጉት አንባር ከእንጨት ይቆጤራል' እንዲሉ ለአያ ደልቲ ስንሰፈሰፍ ልብህ ቢከፋው አይደንቀኝም!በድየሃለሁ
"ዘንግቼሃለሁ... ግን ወድጄ አይደለም። ስቆምበት ልብህ እንደ ደረቀ
እንጨት ሲሰባበር ይሰማኛል። ወንድነትህን ብታሳዬኝ ሸንቆጥ
ብታደርገኝ አብያው ልቤ አደብ ገዝቶ ትዝታዬን እያረሰ ገለባብጦ የአንተን የፍትር ቡቃያ ያበቅለው ነበር: አንተ ግን ወኔ ከወንድነቱ
ይልቅ ወደ ሴትነቱ ያደላል፡ እንደ ወንዶች አታገሳም አትፎገራምI አትዋጋም አሯሩጠህ አትጥልም! አትጀነንምI የተከደነውን በሃይል አትከፍትም...

“እና ልቤ ሃይ ባይ አጣ ትዝታዬን የሚሽር ትዝታ
አጣሁ ይእ! አይ ልፋቴ አንተ እቅፍ ውስጥ ሆኜ ከተራራው ማዶ ሰው ፍለጋ ስንጠራራ! 'አሁንም ትወጂዋለሽ... እያልህ ከምትለኝ በወንድነት በልቤ ውስጥ የሚዋኘውን ጀግና አጥምደውና ሃሣቤን
ቆልምመው: ለእኔስ አያ ደልቲ እንዳለኝ ተአባቴ ደንብ ውጭ እሱን ማሰብ 'ጉም መዝገን' አይደል!

“አንተና እኔ ሰውነታችን እንጂ አበቃቀላችን ለየቅል ነው።መስሎህ እንጂ ማንም ትሁን ማን የደረሰ ቡቃያዋን አሽቶ ያቃማትን ሐመር አትረሳም:: ያውም ያያ ደልቲን የፋና ወጊውን የጀግናውን አንበሳ ቀጭኔ... ከገደለው እቅፍ የገባችውን... 'ተይ' ተብላ ፍቅሩን ከልቦናዋ አውጥታ ልትወረውረው ይህ የሚቻላት ሐመር የለችም።

“እኔ የኔ ጌታ በቃልህ ተይ ዘንጊው... አትበለኝ: ቅጣትህ ይሻለኛል! ልመናህ ግን ያብሰኛል.." ጎይቲ አይኖችዋን አድማሱ ላይ
ሰንቅራ ሃሳቧን ሳትጨርሰው ፀጥ አለች።
👍281
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_ሰላሳ_አምስት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ


“አፈርሁኝ በራሴ ከሎ!

“ሃፍረት ልብሳችን ሆኗል፡ በተለይ ከዚች ሃገር ወጣ ብለህ ስትመለስ የት ነን? ማን ይዞ አስቀረን?... ሺ ጥያቄ በህሊናሀ ይደረደራል። መልሱን ግን አታገኘውም! የሚመልስልህም የለም::

“መጽሐፍ ስታነብ ያለፉትን የኪነ ጥበብ ስራዎች ስታይ
በታላላቆቻችንና በኛ መካከል ያለው ግሉህ ልዩነት ያፈጥብሃል
ጠልፎ እሚጥል ! ጉቶ ይመስል እንቅፋት ሆኖ ለመስራት የሚፍጨረጨሩትን የሚያደናቅፍ ምክንያት ይኖራል! ደግሞ አለ!
ነበረም።

“ይህ ግን በእንቅልፍ ለመደበቅ በቂ ምክንያት አይደለም ችግር ሲበዛ መፍትሄውም ከውስጡ ይፈለፈላል። ለመሻሻል ምንጩ ችግር እርካታ ማጣት ነው:

“እኛ ግን ብዙ አጥተን ብዙ ነገር ካላቸው በላይ ቆመን
እናናውዛለን። ብቸኛ ሆነን አጠገባችን ያሉትን እናኮርፋለን እንኮንናለን
ከመሃከላችን ለመውጣትና እኛኑ ለመሳብ
የሚንቀሳቀሰውን ሞራል እየስጠን ከማደፋፈር ይልቅ ተጋግዘን በጠረባ እንዘርረዋለን። የኛ ደስታ የሚታየው በወደቀው ስንስቅ ነው ሌሎቹ ደግሞ በእኛ በወደቅነው ይሳለቁብናል።

“ሰው ሆነን ተፈጥረን ሰው ሆነን ከመከበር ራሳችንን
አራቅን ያለንን አናውቅም! ሌላው ቀርቶ ባለንም አኮራም፡ ከዚያ ይልቅ በተውሶ አልባሳትና ቅራቅንቦ የማስመሰል ተውኔት በባለቤቶቹና በእኛው ህዝብ ፊት እንሰራለን፡ ሁለቱም ግን ረክተው አያጨበጭቡልንም! ከሁለት ያጣ ጎመን' ነን…”
ሶራ በከሎ ሃሳብ መመሰጡና መስማማቱ በሚተናነቀው እልህ ያስታውቃል።

“ሳይጠባበቁ ለስራ መነሳት አስፈላጊ ነው" ብሎ ሶራ ትንሽ አሰብ አደረገና፡-

“ይህችን ሃገር ግን አቅጣጫዋ ወዴት ይሆን የሚለውን ለመመለስ ይከብዳል፤ ወደ ተፈጥሯዊ ሕይወት ወይንስ ወደ ዘመናዊ ኑሮን ሔ? ይህ ሃሳብ በህዝቡ ሲመለስ ህዝቡ ያሰበው ጋ ለመድረስ
መጣጣር ይጀምራል፡ አሁን ግን ያለው ነገር ዝብርቅርቁ የወጣ ነው እስኪ አስበው ጉዟችን እውነት ወዴት ነው? አለና ሃሳቡን ገቶ ከሎን አየው: ሁለቱም ጆሮ ላይ የሚያላዝን ውሻ ጩኸት
የመሰለ ኦምቧረቀ።

“ግን አንድ እውነት አለ፡ አንድ ወቅት የቀደምናቸው
አገሮች አሁን ጥለውን ተፈትልከዋል። እነሱ  ዘንድ ለመድረስ ቀጥሎም ለማለፍ በእልህ የታገዘ ጥረት ያስፈልጋል! ከኋላችን
ተነስተው አሁን ከፊት የሚገኙት ጥሩ ምሳሌ ሊሆኑን ይገባል::
መላና ዘዴ ሳንቀይስ፤ የምንነሳበትንና የምንደርስበትን... ሳናውቅ ግን በለመድናት ጠባብ ጎዳና እንጓዝ ካልን አንዱ መሄጃችን ላይ ገብቶ
ሲሰነቀር ሌላው እንደተለመደው ቆሞ ይቀራል። ለዚህ ሁሉ ግን
ከየት እንጀምር?'' አለ ሶራ ጥያቄ እያቀረበ መልሱን ራሱ ለመመለስ።

“ከራሳችን ከራሳችን መጀመር አለብን" በስሜት ያቀረበው ሃሳብ እንደ ጦር ጎኑን ወጋው። ባዶ ምኞት ወይንስ በተግባር የሚውል ህልም... ፍቅሯ ልቡን እንደ ክትፎ የበላበት ኮንችትስ?
ከሎና ሶራ አንዱ ሌላውን ይበልጥ ለማወቅ፤ ተረዳድተው የአገራቸው አለኝታ ለመሆን ህሊናቸው ቋምጧል: የውጪ ዓለም
ልምዳቸው በራስ መተማመናቸውን ብትንትኑን ቢያወጣቸውም ማንነታቸውን ግን እንደ መስታዋት ቁልጭ አድርጎ አሳይቷቸዋል።
በዚህ የአድቬንቼር ዘመን በትርኪ ምርኪው የግደለሽነት ሕይወት መኖር እንደ አበቅ አንጓሉ አንጓሉ የሐፍረት ቆሻሻ ላይ
እንደሚጥል ተረድተዋል ከሌላው መማር እንጂ እንደ ተውሳክ ጥገኛ መሆን አይንን ጨፍኖ መለመን... በቁም ከመሞት በሞራል
ከመላሸቅ በቀር የሚያመጣው ህሊናዊ ጥጋብ አለመኖሩን ከሕይወት ገጠመኞቻቸው አንፃር አንስተው ብዙ ጊዜ ተጨዋውተዋል::

በህዳሩ የመኸር ወቅት ጨረቃ እንደ ቡሄ ዳቦ ክብ ሆና ገና የብርሃን ወጋገኗን በኒያንጋቶም ተራሮች ወደ ኩዩጉ መንደር ወደ
ኩችሩ ስትፈነጥቅ ከሎና ሶራ እንደተለመደው ሃሳብ ሲለዋወጡ እንደ ቆዩ በመካከላቸው ዝምታ ሰፈነና በእዝነ ሊናቸው ሰማዩ ላይ ጎላ ብሎ የተፃፈ ነገር ተመለከቱ ያን ፅሑፍ ሁለቱም ቀና ብለው አዩት።

“የህይወት ጀልባ ከማዕበል ጋር እየታገለች በውቅያኖሶች ጉያ
አካሏን ነክራ ትንሳፈፋለች ሞት ችግር መከራ ... ያደፍቋታል፤ ደስታ እርካታ ፍቅር. እንደ እንዝርት እያሾሩ ይፈትሏታል እና ጀልባዋ በሁለቱ እጣ ፈንታ ሚዛኗን ጠብቃı የተኙትን የሚስሩት
እየረጋገጧቸው ትሰሩለች:

“በእርገጥ የጎደለው ይተካል ያጣው ያገኛል! ያፈቀረ ይጠላል! የተለጣለ ያነሳል፤የሄደ ይመጣል... በተቃራኒዎች የተወጠረችው ጀልባ የሚፈራረቁባትን ችላ ትጓዛለች።

“አቅጣጫዋ መነሻ መድረሻዋ አይታወቅም:: ጀልባዋ አልቆላታል ትባል እንጂ ከጉዞዋ ከቶ ተገታ አታውቅም: አንድ ቀን
ግን ሥቃይና ሰቆቃ፤ እብሪትና ግፍ የበዛባት ጀልባ ብልሽት
ይገጥማት ይሆናል ያኔ ተሳፋሪዎችዋን ይዛ ትዘቅጣለች  ቁልቁል!
“እሪታ ሰማዩን ያቀልጠዋል የቀስተ ዳመና ቀለሞች በሺ
ተባዝተው ሰማዩን ያስውቡታል ከዋክብት ከነበሩበት በታች ዝቅ
ብለው ብርሃናቸውን ያንተገትጋሉ ገነትና መንግሥተ ሰማያት
ይጣመራሉ።

“ሟቹ ያን ውብ ሰማይ ርቆት ሲሄድ እማይጠገብ
ይሆንበታል! ጀልባዋ ስትዘቅጥ ተስፋ የቆረጠ ያለቅሳል... ሰሚና
ጯሂ እንዲሆ በአንድ ጀልባ ሆነው ዋይ ዋይ' ሲሉ ስቃይ እንደ ቅርጫት ላያቸው ላይ ሲከደንባቸው ይወርዳል።

“በዚያ ሰዓት ቅድስት ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ ሰማይ ትዘረጋለች አምላኳም ድምጿን ሰምቶ ህዝቧን ስለ ስንፍናው አምርሮ ይገስፀዋል።

“እጆቻችሁ ስለምን ሽባ ሆኑ! ስለምንስ ከመቀራረብ ይልቅ መራራቅን መረጣችሁ... ሆድ ብቻ. ጥቅምን ማነፍነፍ ብቻ... ብሎ አዝኖ ውቅያኖሱን ሜዳ ያደርገዋል ድህነትም በምድር ይወርዳል….ልብ ያለው ልብ ይበል" ይላል ሶራና ከሎ አይናቸውን ጨፍነው ያነበቡት።

በጥቁር የሰማይ ሰሌዳ የተፃፈውን ታምር 'ሁለቱም
እየደጋገሙ አነበቡት:
እንግዳው አጋጣሚ
አስገረማቸው አስፈራቸው ... ያ አጉራሽ የለመደው ህሊናቸው ግን ትርጉሙን በጊዜው ሊያቀርብላቸው አልቻለም።

“የምን ጽሑፍ ነው?... ማንስ ፃፈው?...በየግል የፍች "ቀመሩን ለማግኘት ዳንኪራ ረጋጭ ህሊናቸውን አስጨፈሩት። አንዱ
ለሌላው ያየውን ሚስጥር ግን አላወጣም።

ችግርን ለመናድ ማነስ የሚያመጣውን የአዕምሮ ሰንካላነት ለማስቀረት በራስ የመተማመንን ተፈጥሯዊ ፀጋ ጠብቆ ልጅ የልጅ
ልጆችን ከሃፍረት ለማዳን ሆዳምነትን አስወግዶ በእጅና አዕምሮ መጠቀም... ጀልባዋ ሳትሰጥም ደካማ ጎንን ማስተካከል እንደሚገባ
ዘግይተውም ቢሆን የተረዱ ይመስላል።

በዚያች ሰዓት ከሎና ሶራ ተያዩ! ኤርቦሬና ሐመሩ
ሁለቱ አፍሪካውያን ሊግባቡ
ሞከሩ! ሃይላቸውን ለማስተባበር ተቃቀፉደ
ፍቅራቸው ስህተታቸው ቁጭታቸው... ያስፈነደቃት ጨረቃም አላማቸውን ለማጠንhር ብርሃኗን እያሰፋች ፍጥነቷን በመጨር ጥቁሩን ሰማይ እየገለጠች ወደ እነሱ ገሠገሠች።

ከዚያ ያ ኩሩው ድፍርሱ ሚሊዮን ነፍሳትን በውስጡ
አጭቆ ቁልቁል ይሁን ሽቅብ መፍሰሱ ሳይታወቅ በፀጥታ የሚጓዘው ኦሞ ወንዝ በቁጭት አፍ አውጥቶ ሲናገር! እንደ ውሻ ሲጮህ ተሰማ።

"ኢትዮጵያ ፈላስፎቿን ተመራማሪዎቿን የንብ ተምሳሌት ታታሪ ምሁሮቿን, ማቀፍ እርስ በርሳቸው በጡንቻ ሳይሆን
👍18👏1🤔1
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት 


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ

ካርለት ከዳንሱ ቦታ ራቅ ብላ ጀግናዋን በአይኖቿ
ስትፈልገው በጆሮዋ ስልምልም የሚያደርግ የሙዚቃ ቃና ሰማች።
እንግዳ ነው ያ ሙዚቃ ለጆሮዋ! ሳባት ሙዚቃው
ተጎተተችለት: ቃናው ጆሮዋን እየላሳት ወደ ውስጧ ዘለቀ የህሊናዋን ጓዳ! የስርቆሽ በሯን ከፍታ አስገባችው። አሻት፤ ዳሰሳት…..እሷም
አንኳኳ የሆሊናዋን ጓዳ የስርቆሽ በሯን ከፍታ አስገባችው አሻት፤ ዳሰሳት
ሁለመናዋን ነካካው
አንሸራተታት ደመቅ
ደመቅመቅ... የሚለው ዜማ ፍል ውኃ ውስጥ እንደገባች ሁሉ ቁልቁል እየፈሰሰ ሰውነቷን አጋላት ደስ አላት ሰውነቷ ሲግል‥. ጡቶችዋ ግን ተቆጥተው ቆሙ፤ ዳሌዋ አኩሩፎ አበጠ ፤ ጭኗ አዝኖ ለሰለሰ… ሙዚቃና ልብ ወለድ ጽሑፍ ካለ እሳት ሰውነቷን ሲያጋግሉት ደስ ይላታል... የረሳችው ስሜት
ፈረሰኛው አረፋ እንደሚያስደፍቀው ወራጅ ወንዝ ሞተሯን አሽከረከረው፤ አቃሰተች ያኔም ስርቅርቁ ዜማ በጆሮዋ መግባቱን
አላቆመም:

እየቀረበች ስትሄድ በርኮታው ላይ ቁጭ ብሎ ወይሳውን እየነፋ ጥዑም ዜማ የሚያወጣውን ጀግና አየችው። የሙዚቃው
ቅላፄ እንደ “ቤቶሆቨን ሞዛርት ሲንፎኒ" ቃናው እየቆዬ ጣማት።እሰይ እሱ ነው ብላ አጉተመተመች..

ከዚያ ዱካዋን አጥፍታ በሙዚቃው ስልት እርምጃዋን አስተካክላ ተጠጋችው፡
ባለወይሳው አይኖቹ ከጨረቃና ከዋክብቱ ጋር ይጫወታሉ ቅላፄው
ወዲያና ወዲህ ይመላለሳል። ሙዚቃው እንኳን ሌላውን ራሱንም
መስጦታል። እውነተኛ የኪነ ጥበብ ሥራ ውጤት ስቃይና ደስታዋ፤ሐዘንና ትካዜዋ. እፍታውን ቀማሹ ጣዕሙን አስተካካዩና ፈጣሪው
ያኔው ነውና ወይሳው ደልቲን መስጦታል! ወጥሮታል...

ካርለት ደልቲን በሚጫወተው የሙዚቃ ቃና ተመስጦ በማየቷ ይበልጥ ወደደችው፡ ደልቲ
ለስሜቱ ታማኝ ነው አይቀጥፍም አያስመስልም...
ስርቅርቁ የሙዚቃ ቃና
የሚንቆረቆረው ለህሊናው እርካታ ነው::

ካርለትን የሙዚቃው ስልት አቅም አሳነሳት: ሁለመናዋ
እንቅስቃሴ ፍጥነቱን ስለጨመረ ደካከመች: ስሜቷን አፋጭቶ
ሃይሏን መልሶ ለመሳል አጋዥ ያስፈልጋታል
ባለወይሳው ያን ሰው አጥታው ከርማለች! አሁን ግን አጠገቧ ነው።

እጆችዋ ትከሻው ላይ አረፉ። ባለወይሳው ስርቅርቅ ዜማውን አቁሞ ቀና ብሎ አያት። ቆዳዋ ተገልቧል፣ ከርቀት ጠቆር
ብለ የታየው አካሏ ቁልቁል ወደሱ ሲመጣ እየጎላ ታየው። የራቀው
ሽለቆ ቀረበው።

ንጥት ያለው ገላዋ  በተለይም ጭኗን ትክ ብሎ እያዬ፡ “ካርለትት አላትና አይኖቹ ሳቁ። ሃይል ያጣችው ካርለት
የተሸበሸበ ርጥብ ከንፈሯን ለጠጥ አርጋ ደካማ ፈግታዋን አሳየችው።

ባለወይሳው አስተውሎ አያት ውስጧንም አየው
የተቀጣጠለውን ስሜቷን ነካው፡

ጭኖቹ ላይ ያለውን ወይሳ አንስቶ ለጨረቃ ሰጣት!
ጨረቃም ወይሳውን ተቀብላ እየነፋች ጥዑም ዜማዋን ማንቆርቆር ጀመረች። በጨረቃ የሙዚቃ ቃና ደልቲ ቀኝ እጁ እየተንከላወሰ ወደ
ነጩ ጭኗ ገባ። ነዘራት
በሽተኛዋን! “በሽታውን የደበቀ..." እንዲሉ እሷም ሃኪሟን ረዳችው የሚያቃጥላትን የሚቆረጥማትን እጁን
በእጅዋ ይዛ አሳየችው።
ጆሮ ግንዱን ፀጉሩን
ማጅራቱን...እየደባበሰች የእርዳኝ ጥሪዋን አሰማችው። ሀኪሟ በስሜቷ እሱም ተሽፈነ። ለጋራ በሽታቸው ግን የሚበጀውን ያውቃል። ስለዚህ ማገገሚያ ቀንዱን አቁሞ ይዞ ከተቀመጠበት ተነሳ።

ሙዚቃው ይስረቀረቃል! ዳንሱ ጦፏል... ጨረቃ
ታዜማለች ! ቅጠሉ እስክስታ ይወርዳል! ነፋሱ አታሞውን
ይደልቃል... ጥቁርና ነጭ ቀለሙ ማራኪ ዜብራም ያናፋል...

ኮንችት ጭፈራውን በጉጉት እያየች እንደቆየች ስለ ነገው
ጉዟቸው ካርለትን ለመጠየቅ ፈልጋ አጣቻት የኩችሩ መንደር ኗሪ
ጥበቃውን አላቆመም። ነጩ እባብና ሎካዬ ግን አልመጡም። ኮንችት
በየዋህነታቸው ብታዝንም ማድረግ የምትችለው ባለመኖሩ በዝምታ
ሁኔታውን ስትከታተል ሰነበተች። የመቆያ ፈቃዷ  እያለቀ ነው:: ስፔን ስትመለስ ብዙ ልትሰራ አስባለች በተለይ ስለ ኢትዮጵያ  ስለ ኩጉዩ፡ ከመሄዷ በፊት ግን ሐመርን ኤርቦሬን ከካርለት ጋር በሷ
መኪና ለማየት ተስማምታለች ጉዞዋን በተመለከተ ግን ከካርለት
ጋር መነጋገር ያለባት ቁም ነገር ነበር።

ኮንቺት ካርለትን ስታጣት ደልቲን በጨረቀዋ ብርሃን  ፈለገችው የለም:

ካርለት የሄደችው እሱ ዘንድ ይሆን?' አብረው ሆነው
ለማየት ጓጓች: ፍቅር ሲለዋወጡ እንዴት ይሆን?' ለማስብ ሞከረች:: መልሳ ደግሞ ሃጢያት እንደሰራች ሁሉ አስበችው አፈረች። ሆኖም ግን አልቻለችም ጉጉቷ ጨመረ።

በዚህ መካከል ድክምክም ያለውን የወይሳውን ድምፅ
ኮንችት ከርቀት ሰማችው። በድፍረት ሄደች  ወደ ጫካው! ድንገት ግን ክው ኦለች ! ባለበት የሚሰግር
ዜብራ አየች ፈራችው
ዜብራውን ይጋልባል ... በስሜት ተውጣ አይኖችዋን ጨፈነች:
"...የፍቅር እንጥሌን ሌሎች ተንጠራርተው ሲያጡት የነካው እሱ ብቻ ነው" ኮንችትን የነገረቻት ትዝ አላት።

“ዋው! ጎመጀች በዜብራው
ግልቢያውን አሰጋገሩን
አደነቀችው። ወደደችው ያን ስሜት ሰላቢ ጥዑም ዜማ... ፈውስ ሰጭ ዳንኪራ… ንፁህ የጫካ ፍቅር... ማራኪ ተፈጥሮ ተጋግዘው እንግዳዋን መልሀቋን አስጥለው በጉጉት ገተሯት!  ተጣራች በሲቃ ሶራ ግን አልሰማትም! ኤጭ! ብላ ከንፈሯን ጣለች። ጎደሎነት
ተሰማት ያማራትን የዜብራ ግልቢያ ግን የሚያቀምሳት አጣች.የጎመጀችለትን ያጣችው ኮንችት አዘነች። ...ዛፉ ቅጠሉም አዘነላት ላልተጠራችው ተመልካች!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

“እ. እ..." አቃሰቱ እምቡዋ እ. እ" ሳግ ተናነቃቸው
ህፃናት ወጣቶች አዛውንቶች ኦሞ ወንዝ ዳር ጫካ ተሰባስበው እንግዶች በእንጨቷ ታንኳ ኦሞን ሲያቋርጡ አያቸው።

ኮንችት እጅዋን አውለበለበችላቸው “ቻው... ባባይ... አለቻቸው። ዝም አሉ ኩዩጉዎች የነሱ የጥልቅ ፍቅር መግለጫቸው ዝምታ ነው። ሳግ ያበት “እ... እ..." እሚያሰኝ ከጥጃዋ በሃይል እንደተነጠለች ላም የሚያንሰፈስፍ ዝምታ! “እ. እ. እምቡዋ.. እያሰኘ የማይፈስ እንባ የሚያስነባ, የማይገልፁት ግን የሚታይ
የሚነካ... የመለየት ጭንቀት የሚታይበት ስሜት..

“እወዳችኋለሁ! ከናንተ በመለየቴ አዝናለሁ. ምንጊዜም አልረሳችሁም..." ኮንችት በስፓኒሽ ለመግለፅ ለፈለፈች¦ ምላሽ ግን
አልነበረም። “ፀጥታ ብቻ! ለኩዩጉዎች የመለየትን መጥፎነት የሚገልፅ ቋንቋ የላቸውም ካለ ዝምታ በቀር።

ኮንችት አነባች::
የካርለትን ትከሻ ተደግፋ አነባች አለቀለች  ሌሎች ግን ዝም ረጭ ብለዋል  እንደ ሌሎች ወንዞች
የማይጮኸው የማይደነፋው.
የኩዩጉዎች ህይወት የመልክ ማያ መስታዋታቸው የሆነው የኦሞ ወንዝም በዝምታ ድባብ እንደ ተዋጠ
ነው: ወፎች ግን ይበራሉ ያዜማሉ! እዕዋት ያሽበሽባሉ...

“እሷ ሄደች በሉ
ሉካዬንና የሰላም አድባራችን
የነበረውን ነጩን እባብ እንጠብቅ ! ተከፍተን ታዩን መምጣቱን እንዳይተዉት እንዝፈን እንጫወት.."
ሽማግሌዎች ለኩችሩ መንደር ህዝባችው ተናገሩ ኮንችት ካርለት ከሎ ሶራ… ኦሞን ከተሻገሩ በኋላ ዞር ብለው አዩ: ኩዩጉዎች የሉም!.ሲደልቁ ግን ይሰማል ለዚህች ተለዋዋጭ ዓለም ለረጅም ጊዜ አልቅሶና አዝኖስ መኖር እንዴት ይቻላል!
👍263👎1🥰1😁1