አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ትንግርት


#ክፍል_አንድ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////

ሁሴን ዕድሜው ከ 35 ትንሽ ቢዘልም ፈርጣማ የሆነው የስፖርተኛ ተክለ ሰውነቱና ግንባሩ ላይ የተደፋው ጥቁር ሉጫ ፀጉሩ የሃያ አምስት አመት ወጣት ያስመስለዋል፡፡

የመጀመሪያ ዲግሪውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሥነ ጹሁፍ ከአስር ዓመት በፊት ሲቀበል፣ሁለተኛ ዲግሪውን ደግሞ ከፈረንሳይ አገር በፍልስፍና ከሦስት ዓመት በፊት አግኝቷል፡፡ አሁን የሚኖረው እናትና አባቱ ባወረሱት ልደታ ክፍለ ከተማ በሚገኘው ባለ ሦስት መኝታ ክፍል ቪላ ቤት ውስጥ ነው፡፡ ወላጆቹ ሞተዋል፡፡እሱ ደግሞ ብቸኛ ልጃቸው ነበር፡፡በአሁኑ ሰዓት አብራው የምትኖረው ፎዚያ ነች፡፡ ሁሴን ፎዚያን እንደእህቱ ቢያያትም ምንም አይነት የስጋ ትስስር ግን የላቸውም ፡፡

ሁሴን ዋና አዘጋጅ ሆኖ በሚሰራበት ፍኖተ ጥበብ በተሠኘ ተነባቢ የግል ጋዜጣ ውስጥ ስልሳ ፐርሰንት የአክሲዬን ድርሻ አለው፡፡
ጋዜጣው ሳምንታዊ ሲሆን፤አንድ መቶ ሺ እትም በየሳምንቱ በመላው አገሪቱ ያሰራጫል፡፡ ጋዜጣው ትርፋማ ነው ብሎ ለመናገር ባያስደፍርም፤ በጣም ተወዳጅና ተነባቢ መሆኑን ግን አስረግጦ መመስከር ይቻላል፡፡

ሁሴን በህይወቱ ብዙ ሴቶች ገብተው ወጥተዋል፡፡ አብዛኞቹ ተስፋ አስቆርጧቸው ትተውት ሄደዋል፡፡ ጋብቻ አይፈልግ፣ ልጅ መውለድ አያጓጓውም፣ ቃል አይገባለቸው ፣ ተስፋ አይሰጣቸው ፤ በቃ... ፍቅርና ወሲብ ብቻ!፡፡ ታዲያ ጫንቃቸው የደህነት ዋስትና የሚሹት ሴቶች ከተወሰነ ርቀት በላይ አይታገሱትም፤ ጥለውት ይሄዳሉ፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ በጭቅጭቅና በንዝንዝ ፋታ ስለሚነሱት ያንገሸግሹታል፡፡ሲያንገሸግሹት ደግሞ ፊቱን ያዞርባቸዋል...ይተዋቸዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት በህይወቱ ውስጥ ሦስት ሴቶች ቀርተዋል፡፡ አንደኛዋ በንግድ ስራ የምትተዳደረውና አምስት ዓመት በጓደኝነት፤
ስምንት ዓመት በፍቅረኝነት አብራው የዘለቀችው ኤደን ስትሆን፣ ሁለተኛዋ እራሱን ዘና ማድረግ ሲያሠኘው የሚፈልጋት የቡና ቤቷ ትንግርት ነች፡፡ ሦስተኛዋ ደግሞ አዕምሮውን ጠቅላላ ጠፍንጋ የያዘችው፤ በፍቅር ሊቀውስላት ጥቂት የቀረው በአካል የማያውቃት የጋዜጣው አምደኛ ሚስጢር ::

ሁሴን ቀኑን ሙሉ በስራ ተጠምዶ ከዋለበት ቢሮው ለቆ በመውጣት ውጫዊ አካሏ በቀይ ቀለም የተነከረ ቪታራ መኪና ውስጥ ገብቶ ሞተሩን ለማስነሳት ቁልፉን ሲነካካ ተንቀሳቃሽ ስልኩ ተንጣረረች...አነሳው፤ደዋዩ ኢንጅነር ሠሎሞን ነበር፡፡

<<ሄሎ>>

‹‹የት ነህ ወንድም ጋዜጠኛ?››

‹‹ባክህ ገና ከቢሮ እየወጣሁ ነው...ላብድልህ ነው፤ ግራ ተጋብቻለሁ::››

‹‹ደግሞ ምን ገጠመህ?›› ሠሎሞን ነበር ጠያቂው፡፡

‹‹ሌላ ምን ይገጥመኛል ...የዛችው ልጅ ነገር ::››

‹‹ኦ!! የደንበኛህ?››

«አዎ!!>>

‹‹ዛሬም ፖስታዋ ደርሶሀል ማለት ነው?››

‹‹አዎ!! የዛሬው ደግሞ የተለየ ነው፤ልብን ስውር የሚያደርግ ሀሳብ የያዘ ፅሁፍ ነው የላከችልኝ፡፡››

<< ልብህን የሰወረህ ፅሁፍ ነው ወይስ አንተ ለእሷ ያለህ ስውር ፍቅር?››

‹‹ሁለቱም ምክንያት ትክክል ነው፡፡››

‹‹በቃ... አንተ እንደው ስለእሷ ማውራት ከጀመርክ ማብቂያ የለህም አይደል? ልታወራኝ ከፈለክ የመጠጥ ግብዣ እፈልጋለሁ…የተለመደው ቤት ተጎልቼ እየጠበቅኩህ ነው ፡፡››

‹‹እንዴ በቀኑ! ? ገና አስራ አንድ ሠዓት እኮ ነው? >>

ሠሎሞን ተበሳጨ‹‹ባክህ አትጨቅጭቀኝ፤ የምትመጣ ከሆነ ና፡፡››

‹‹እሺ ጌታው ከሃያ ደቂቃ በኃላ ከጎንህ እገኛለሁ፤እስከዛው ቻው፡፡›› ስልኩን ወደ ኪሱ መልሶ ሞተሩን አስነሳና ወደ ሜክሲኮ ከነፈ፡፡ ከሠሎሞን ጋር ከሃያ ዓመት በላይ በጓደኝነት አሳልፈዋል፡፡ በባህሪ፣ በስራ፣ በእምነትና በኑሮ ፍልስፍናቸው በጣም በተለያየ መንገድ የሚጓዙ ቢሆንም ይህ ልዩነታቸው ግን ጓደኝነታቸውን ለመበረዝ ጉልበት አልነበረውም፡፡

ኢንጅነር ሠሎሞን የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ነው፡፡ የሃይማኖቱን ህግና ሥርዓት ለማክበር ዘወትር ከልብ ይጥራል፤ግን አይሣካለትም፡፡
ህግጋቱን ይጥሳል፣ ቀኖናዋቹን ያፈርሳል፣ከዛም በፀፀት ይቃጠላል፡፡ እግዚአብሔርን በማስቀየሙ እራሱን ይቀየማል፡፡ብዙውን ጊዜ ለሥህተት ተጋላጭ እንዲሆን መነሻ ምክንያት የሚሆኑት ሁለት ነገሮች ሚስቱና ስራው ናቸው፡፡ ከየውብዳር ጋር ከተጋቡ አስር ዓመት አልፏቸዋል፡፡ በዚህ የጊዜ ሂደት ውስጥ የተትረፈረፈ ሀብት ባለቤት መሆን ከመቻላቸውም በተጨማሪ ሁለት ሴት ልጆችንም ማፍራት ችለዋል ፡፡ስምምነት ግን አልነበራቸውም፤ ሦስት ቀን በሠላም ቢያሳልፉ ተከታዮቹን ሦስት ቀናት በጥልና በኩርፊያ ጀርባ ተሠጣጥተው ይከርማሉ፡፡ በዚህ ወቅት ታዲያ ሰሎሞን ቤቱ ያስጠላዋል…ጥሎ ይወጣል፤ከወጣም ይጠጣል፤ ብክት እስኪል ይጠጣል፣ሲጠጣ ደግሞ ብዙ ይሳሳታል፣ሠው ያስቀይማል፣ ከሴት ይዳራል፣ብር ይረጫል፤ከዛ በማግስቱ ናላው እስኪዞር
በጥልቀት ይፀፀታል፡፡

ስራውን በተመለከተ ደግሞ ደረጃ ሦስት ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ (ኮንትራክተር) ነው፡፡ ሥራ ለማግኘት ጉቦ
ይሰጣል፣ሥራው ሲበላሽበት ሥህተቱን ለመሸፈን ጉቦ ይሠጣል፣ ካደረገው በኃላ ግን እንቅልፍ እስኪያጣ
ይበሳጫል፣ይፀፀታል ደግሞ ላለማድረግም ይምላል...ይገዘታል፡፡ ግን መልሶ መላልሶ በተመሳሳይ ስህተት ውስጥ ዘወትር ይዘፈቃል ፡፡ ሠሎሞን ማለት ይሄ ነው፡፡ ጥፋት፣ፀፀት… ጥፋት፣ፀፀት፡፡

ሁሴን ስለ ሠሎሞን እያሠላሠለ ሣይታወቀው የተቃጠሩበት ቦታ ደረሠ፡፡ መኪናውን ተገቢው ቦታ ካቆመ በኃላ ወደ ውስጥ ዘለቀ፡፡ ቡና ቤቱ ጭር ብሏል፡፡ ታዳሚዎቹ በቁጥር ናቸው፡፡ ወንድ አስተናጋጆች እዚና እዛ ተሠባጥረው ቆመው የሚሠጣቸውን ትዕዛዝ እየተቀበሉ ክቡራን ደንበኞቻውን በትጋት ለማስተናገድ ሲታትሩ ይታያሉ፡፡እንደገባ ነበር ሠሎሞንን የለየው፡፡ አጭር ሠላምታ ከተለዋወጡ በኃላ ፊት ለፊቱ ወንበር ስቦ ተቀመጠ፡፡

‹‹ሙሽሮቻችን አልገቡም እንዴ?›› ሁሴን ነበር ጠያቂው፡፡

‹‹አንተ ደግሞ እነሱን ካለየህ ጉሮሮህ ለመጠጥ አይከፈትም፡፡ ከደቂቃዎች በኋላ ይንጋጉልሀል፡፡ ንስርህም እንደ ንግስት በጋርዶቾ ታጅባ ከች ማለቷ አይቀርም፡፡››

ሁሴን አስተናጋጁን ጠራና ውስኪ አዘዘ፡፡

‹‹ምነው ውስኪ?›› ጠየቀ ሠሎሞን፡፡

<<እንዴት??>>

‹ለስላሳ የምታዝ መስሎኝ ነበር፤ሃይማኖትህ ይፈቅድልሃል እንዴ?›› ይሄ የሠሎሞን የሁልጊዜ ትችቱ ነው፡፡

‹‹ሃይማኖቴ ምንድነው?››

‹‹መቼም ሁሴን ብሎ ክርስቲያን የለ፡፡››

‹‹ይሄው እንግዲህ የአንተ ችግር እዚህ ላይ ነው፡፡ እርግጥ ማንም እንደሚያውቀው ቤተሰቦቼ የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ነበሩ፡፡ በዛ ምክንያት እኔ ስወለድ ምንም ሳይጠረጥሩ
ልጃችን እንደኛው ሙስሊም ስለሚሆን የሙስሊም ስም እንሸልመው ተባባሉና ሁሴን አሉኝ፡፡ እኔ ግን እንደምታውቀው ሙስሊምም፣ክርስቲያንም፣ቡዲስትም መሆን አልቻልኩም፡፡ በዚህም የተነሳ የቤተሠቦቼን ትንቢት አከሸፍኩባቸው ማለት ነው ፡፡ ይሁን እንጂ ለዚህ ስህተታቸው መታሠቢያ ይሆን ዘንድ ሙስሊማዊ ስሜን ይዤ ይሄው እየኖርኩ ነው፡፡››

አስተናጋጁ የታዘዘውን ውስኪ አምጥቶ ፊቱ አቅርቦለት ወደ መቆሚያ ቦታው ተመለሰ ፡፡ ሠሎሞን የተቋረጠ ጫወታቸውን አራዘመው፡፡‹‹ግን ለዚህች ሚስኪን ነፍስህ አንድ ማረፊያ ብታበጅላት ምን አለበት?››

‹‹እንዴት ማለት?››

‹‹ማለት አንድ የራስህ ሃይማኖት ቢኖርህ?››

‹‹እሺ በንድፈ ሃሳብ ደረጃ ሃይማኖቱ ያስፈልገኛል ብዬ ልመን፤ እስቲ ይሄኛው ሃይማኖት ትክክል ነው ብለህ አሳምነኝ እና እሱን ልከተል።.››
👍16410🔥2👏2👎1😁1
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ


#ክፍል_አንድ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ዛሬ…አሁን

ሳባ ባለ አንድ ፎቅ በሆነ የግቢዋ የአትክልት ስፋራ ከደራሲ ጳውሎስ ጋር ቁጭ ብላ እየተማከረች ነው፡፡ደራሲ ጳውሎስ ከዚህ በፊት ሁለት መፅሀፎችን ፅፎ ለህትመት ያበቃ እጅግ ድንቅ የስነ-ፅሁፍ ችሎታ ያለው ግን ደግሞ  በኑሮ  ያልተሳካለት በድህነት የታችኛው ወለል ላይ የሚገኝ ከዛም አልፎ ጉልት ቸርቻሪ በሆነች እናቱ ተጧሪ ለመሆን የተገደደ የ35 አመት ወጣት ነው፡፡

እርግጥ ሳባም ገና 33 ዓመቷ ላይ ነው የምትገኘው፡፡ግን በዚህ ዕድሜዋ ከጳውሎስ ተቃራኒ በሆነ መንገድ ሚኒዬነር ሆናለች፡፡የሀብታም ልጅ ሆና ውረስ ስላገኘች አይደለም…ድንገት ሎቶሪ ወጥቶላትም አይደለም፡፡ለአለፉት 10 አመታት ህይወት ያመቻቸችላትን እድል በአግባቡም ከአግባብ ውጭም  በመጠቀም ባገኘችው የገንዘብ ስኬት ነው፡፡
አሁን ከጳውሎስ ጋር የተገናኘችው ለድርድር ነው፡፡እሷ ብር አላት እሱ ደግሞ የስነ-ፅሁፍ ችሎታ አለው፡፡እሷ ላለፉት አንድ አመት መፅሀፍ መፃፍ  ጀምራ ነበር፡፡ልብ ወለድ አይደለም፤የግጥም መድብልም አይደለም..ፍፅም በእንደዛ አይነት ጉዳይ ላይ ምንም አይነት ፍላጎት የላትም፡፡ለአንድ አመት የደከመችበት መፅሀፍ ጭብጡ ስለሰራዋ ነው…እርግጥ በገዛ ህይወቷ ላይ  የሚያጠነጥን አይደለም፤ባለፉት አስር አመታታ ስትስራ በነበረውና ከመናጢ ድህነት ሚኒዬነር ስላደረጋት ስራ ጠቅላላ ባህሪ፤አስገራሚና አስደማሚ ምስጢራዊ ታሪኮች ነው፡፡ግን በሂደት ረቂቁን መጨረስ ብትችልም ጣዕምና ሰጥቶ፤ የሰውን የንባብ አፕታይት በሚከፍት መልኩ ውበት አላብሶ መጨረስ አልቻለችም፡፡ስንፍና ብቻ ሳይሆን ለዛ  የሚሆነ ቸሎታም ሆነ ልምድ  የላትም፡፡  ለዛም  ነው  አሁን  ከደራሲ ጰውሎስ ጋር በሰው በሰው ተገናኝታ እየተነጋረች ያለችው፡፡

‹‹ረቂቁን አነብከው?››

‹‹አዎ አንብቤዋለው፡፡››

‹‹እና የምትሰራው ይመስልሀል?››

‹‹እሱን አትጠራጠሪ …በደንብ ሰራዋለው፡፡ግን ጥያቄ መጠየቅ እችላለሁ?››

‹‹ጠይቀኝ፡፡››

‹‹ልብ-ወለድ ነው ወይስ የተወሰነ እውነት አለው?››

ይሄ ስራ ህይወትህን የሚቀይር ጥቅም የምታገኝበት ነው፡ግን ያንን ረቂቁን አሳምረህና አስውበህ መፅሀፍ ስላደረከው ብቻ አይደለም የምከፍልህ፡፡መፅሀፉ ታትሞ ከተሰራጨ በኃላ ይዞ ሚመጣው መዘዝ ከባድ ስለሆነ ነው፡፡እያንዳንዱ በረቂቁ ያነበብከው ታሪክ መቶ ፐርሰንት እውነት  ነው፡፡  በታሪኩ  በቀጥታ በትክክለኛ ስማቸው ባይሆንም ታሪካቸው የተጠቀሱ ሰዎች ከፍተኛ  ስልጣን ያላቸው ወይ ደግሞ ሀገሪቱን የሚያሽከረክሩ ሀብታሞች ወይ ደግሞ ሚሊዬን ተከታይ ያላቸው ታዋቂ አርቲስቶች ናቸው…እና  መፅሀፉ ከታተመ እና ካነበቡት በኃላ ስማችን   እየጠፋ ነው ብለው ስለሚያስቡ   አሳደው ወይ ይገድሉሀል ወይ እስር ቤት ያስወረውሩሀል፡፡›

‹‹እንዴ…አልገባኝም፡፡ የፃፍሽው አንቺ ነሽ…. እኔ እኮ በቃ ኤዲተር በይኝ.››

‹‹አይ ደራሲውም አንተ ነህ…..መፅሀፉ በአንተ ስም ነው እንዲታተም የምፈልገው፡፡››

ፍራቻ ውስጥ ገብቶ አይኖቹን እየያቁለጨለጨ‹‹ኸረ ይሄ ነገር ካሰብከኩት በላይ  ከባድና ውስብስብ ነው…..ይቅርብኝ፡፡››አለት
‹‹ወደ ውጭ ሀገር ማለት አሜሪካ ወይም አውሮፓ ለመውጣት ብዙ ጊዜ ሞክረህ      እንዳልተሳካልህ ሰምቼያለው፡፡››

‹‹አዎ ትክክል ነሽ፡፡››

‹‹እኔ  ካናዳ ልልክህ እችላለው..መፅሀፉን በስምህ ታትሞ እንዳለቀ ከመሰራጨቱ በፊት አንተ ከሀገር እንድትወጣ አደርጋለሁ፡፡››

ያልጠበቀውን  ነገር  በመስማቱ  በደስታ  ከመቀመጫው  ተነሳና  መልሶ ተቀመጠ‹‹እርግጠኛ ነሽ እንደዛ ማድረግ ትቺያለሽ?››
‹‹አዎ በሶስት ወር ውስጥ ያንን ማድረግ እችላለሁ፡፡በዛ ጥርጣሬ አይግባህ …እኔ እንዳዛ ማድረግ ካቃተኝ..መፅሀፉ ለገበያ አይቀርብም…››

‹‹እንደዛ ከሆነ እንስማማለን፡፡››

‹‹ጥሩ… ማወቅ ያለብህ ይሄ ጉዳይ ለእኔ የህይወትና የሞት  ያህል  ወሳኝ  ነው፡፡ስለዚህ ከዛሬ ጀምሮ የሙሉ ጊዜ ስራህ ይሄ ነው የሚሆነው…ስለመፅሀፉ ከማንም ጋር አትነጋገርም…ማንም ሰው ከመፅሀፍ ግማሽ ገፅም ቢሆን ማንበብ አይችልም፡፡ለዚህም  ምቹ  እንዲሆንልህ  ቢሾፍቱ  ኩሪፍቱ  አልጋ ተይዞልህ…የፈለከው  ነገር  እዛ  ይሟላልሀል..ላፕቶፕ  ጨምሮ   አስፈላጊ   ነገሮች ሁሉ ተዘጋጅተዋል….በጣም ከራቀ ልክ የዛሬ ሁለት ወር ጨርሰህ እንድታስረክበኝ እፈልጋለሁ…ከዛሬ ጀምሮ ከእኔ ጋር በአካል አንገናኝም..ሚስጥራዊ  ቁጥር ሰጠሀለው፡፡ ስትፈልገኝ ትደውልልኛለህ… ስፈልግህ ደውልልሀለው፡፡››

በገጠመው ሎቶሪ መሰል እድል ውስጡ በደስታ እየጨፈረ..‹‹ጥሩ ነው፡፡››አላት፡፡
በዚህ ጊዜ የሳባ ሞባይል ጠራ …አየችውና…‹‹አንዴ ይሄን ስልክ ልመልስ›› በማለት ከመቀመጫዋ ተነስታ ፈንጠር አለችና አነሳችው፡፡

‹‹ሄሎ ፍቅር››

‹‹ሄሎ እንዴት ነህ?››

‹‹ሰላም ነኝ..ፈልጌሽ ነበር..ዛሬ ስራ አለሸ እንዴ?››

‹‹አይ እረፍት ነኝ፡፡››

‹‹እቤት ለምን አትመጪም?››

‹‹እቤት ነው ያልከው…ያንን ጉሮኖህን እቤት ብለህ ስትጠራ አታፍርም?››

‹‹አንቺ ደግሞ ያው እስከምኖርበት ድረስ እቤቴ ነው››

‹‹እ ነው እንዴ? አላወቅኩም ነበር..ለማንኛውም እዛ መምጣት አልችልም፡፡››

‹‹እሺ እኔ ልምጣ፡፡››

‹‹ባክህ ይቅርብህ፡፡››

‹‹ተይ እንጂ..ለሆነ ጉዳይ ፈልጌሽ እኮ ነው?››

‹‹ምነው ገንዘብ ፈለክ?››

‹‹እኔ አንቺን የምፈለግሽ ለገንዘብ ብቻ ነው እንዴ?››

‹‹እ ይቅርታ እሙሙዬ አምሮህ ነው?››

‹‹አረ በናትሽ ለቁም ነገር ነው የፈለኩሽ?››በመልሷ ምርር አለ፡፡

‹‹እሺ አትነጫነጭ. .ና››አለችው፡፡

‹‹እሺ የእኔ ቆንጆ››ብሎ ስልኩን ዘጋና ተንደረደረ፡፡ወደ እሷ ቤት፡፡

የፋሲል እና የሳባ ግንኙነት ግራ አጋቢና ውል የሌለው አይነት  ነው፡፡እሷ የምትፈልግው ለአንድ ጉዳይ ነው…በወሲብ ጎበዝ ስለሆነ በምትፈልገው መንገድና መጠን ስለሚያስደስታት ብቻ ነው፡፡እሷ  ባለፉት  አስር  አመታት  ባሳለፈችው የሥራ ህይወቷ የተነሳ የወሲብ ባህሪዋ ተበላሽቷል፡፡ ሙሉ በሙሉ  የስነ-ልቦና መፋለስ አስከትሎባት ጭምልቅልቅ ያለ ሱስ ውስጥ ገብታለች…እሱ ቋሚ ስራ ስለሌለው ገንዘብ በጣም ያስፈልገዋል...ህይወቱን የሚገፋው ከዚህና ከዛ እየቦጫጨቀ ሞላ ጎደል በመጫወት ነው፡፡ከእሷ ጋር ከተገናኘ በኃላ  ግን በአንፃራዊነት የገንዘብ ችግሩ ተቀርፎለታል፡፡በስራዋ ከምታገኘው ልክ እንደቅጠል ከሚሸመጠጥ ገቢዋ ላይ ጥቂት ቆንጠር አድርጋ በየጊዜው ስለምታስጨብጠው እሷን ለማስከፋትና ቅር ለማሰኘት ፈፅሞ አያስብም…፡፡
እሷም ለአለፉት አንድ አመት ከእሱ ጋ አስፈላጊ በሆኑ ቀናቶች በመገናኘት በምታሳለፈው ጊዜ ደስታኛ ሆነ ቆይታለች..አሁን አሁን ግን ምን ያህል አብራው እንደምትዘልቅ አልገባትም…እሱን በተመለከተ በእስከዛሬ ህይወቷ ያላደረገችውን አንዳንድ ነገሮች በማድረግ ስህተት መስራቷን ታምናለች፤ለምሳሌ እቤቷን ፈፅሞ ማሳየት እንዳልነበረባት ታምናለች..እርግጥ ስለእሷ ሚያውቀው ጥቂት ነገር ነው፡፡ሆስተስ ነኘ ብለዋለች፡፡እሱን ማግኘት በማትፈልጋቸው ቀናቶች ከሀገር ውጭ በረራ አለብኝ ለዚህን ያህል ቀን አንገናኝም ትለዋለች፡፡ስለሚፈራት ያለችውን ሁሉ አመነም አላመነም ይቀበላታል.እሷም ታዘዥነቱ ትወድለታለች፡፡በእሱ ቦታ ሌላ ለራሴ ክብር አለኝ ብሎ የሚመፃደቅ ወንዱ ቢሆን ኖሮ እሷ በምትፈልገው አይነት የተበላሸ የወሲብ ስሜቷን ያስታምምላት እንደሆነ እርግጠኛ
👍8611👏1
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)


#ክፍል_አንድ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

#ፔሩ_ሊማ

ኑሀሚ 26 አመት ላይ ያለች ማራኪ ገፅታና ሳቢ ውበት ያላት ንቁ ወጣት ናት፡፡

ከመደበኛው ትምህርት በላይ ከህይወት ብዙ የተማረችና በብዙ ፈተናና ውጣ ውረድ የበሰለች ወጣት ነች፡፡ኢትዬጳያ ውስጥ በተፈጥሮ ጥበቃ ላይ በሚንቀሳቀስ አለም አቀፍ ድርጅት ውስጥ ተቀጥራ መስራት ከጀመረች አራት አመት አልፏታል፡፡ እዚህ ድርጅት ውስጥ ከመስራቷ በፊት በሀገሪቱ የደህንነት መስሪያ ቤት ውስጥ ከ12 ዓመቷ ጀምሮ ተመልምላ ለረጅም አመት ስልጠና ከወሰደች በኃላ በተለያዩ የሽፋን ስራዎችና ተልዕኮዎች ላይ ተሳትፋ ድንቅ የተባሉ ስኬቷችን ያስመዘገበች የተዋጣላት ሰላይ ነበረች፡፡ለውጡን ተከትሎ በመስሪያ ቤቱ በተካሄደው ሪፎርም የ10 አመት የግዳጅ የአገልግሎት ዘመኗንም አጠናቀ ስለነበር..በራሷ ፍቃድ ከስራው ለቃ አሁን የምትሰራበት መስሪያ ቤት ተቀጠረች፡፡

እርግጥ አሁንም አንዳንድ ወሳኝ የሆኑ እሷ ብቻ የምትሰራቸው ስራዎች ሲያጋጥሙ በኮንትራት ሰራተኝነት ተልዕኮ ይሰጣታል፡፡ እሷም ስራውን ስለምትወደው ያለማንገራገር ተቀብላ ትሰራለች፡፡

አሁን በምትሰራው ስራም ደስተኛ ነች..ምክንያቱም ደሞዟ በዶላር ነው፡፡ጥሩ ኑሮ እንድትኖር ምክንያት ሆኗታል፡፡ በዛ ላይ ብዙ ነገር አውቃበታለች፤ብዙ ነገር ተምራበታለች፡፡አሁን በዚህ ሰዓት ከአለም አቀፍ ሀገሮች ከተውጣጡ መሰል ኤክስፐርቶች ጋር የ3ወር ስልጣና ለመውሰድ ሰሜን አሜሪካ በምትገኘው ሀገረ ፔሩ ዋና ከከተማ የሆነችው ሊማ ከከተመች አንድ ወር አልፏታል፡፡

በተፈጥሮ ጥበቃ ላይ ለሚካሄደው አለም አቀፍ ሴሚናር ፔሩና ብራዚል በጥምረት ነው አስተናጋጅ ሆነው የተመረጡት፡፡የዚህም ምክንያት ሁለቱም ሀገሮች በተፈጥሮ ሀብት ክምችታቸው ምድራዊ ገነት ስለሆኑ ነው፡፡ብራዚል 60 ፐርሰንት የሆነው የአማዞን ደን ባለቤት ስትሆን ፔሩ ደግሞ 13 ፐርሰንት የሚሆን ድርሻ አላት፡፡፡፡የአለም አንደኛውና ግዙፉ የአማዞን ወንዝ እየተጠማዘዘ የሚፈስበት እና ለአለም ህልውና መሰረት የሚሆነው ካርቦንዳይኦክሳይድ የሚመረትበትና ለመላው አለም በአምላክ እስትንፋስ ሀምሳያ የሚበተንባቸው ሀገሮች ናቸው፡፡አማዞን ወንዝ አንዴ ሸንቃጣ ጅረት እየመሰለ ደስ ሲለው ደግሞ ጋሻ መሬት ላይ ተኝቶ ሀይቅ እየፈጠረ በሁለቱም ሀገራት ምድር ላይ እንዳሻው እየተጠማዘዘና እየደነሳ ይጋልብበታል፡፡እና አለምን ከጥፋትና ከውድመት ለመታደግ የተፈጥሮ ሀብትና ደንን የባዬ-ዳይቨርሲቲ ጥበቃ እና እንክብካቤ በሙሉ አቅም ለማስተግበር ከምር ስራው መጀመር ካለበት መነሻ ቦታው ደቡብ አሜሪካ መሆን እንዳለበት የአለም አቀፉ የተፈጥሮ ጥበቃ ድርጅት ብቻ ሳይሆን እሷም በግል በተለይ መጥታ አካባቢውን በጥቂቱም ቢሆን ካየችና የአንድ ወር ስልጠናውን ከወሰደች በኃላ አምናበታለች ፡፡
ኑሀሚ ይሄንን እድል አግኝታ ወደደቡብ አሜሪካ ከመምጣቷ በፊት ስለብራዚልና አርጀንቲና ካልሆነ ስለፔሩና ሌሎች የአህጉሪቷ ሀገሮች ከስማቸው ውጭ የምታውቀው ምንም ነገር አልነበራትም፡፡ለምስሌ ስለብራዚል ባህላቸውንና የሳንባ ዳንሳቸውን ብዙ የዶክመንተሪ ፊልሞችና በተደጋጋሚ ጊዜ አይታለች፡፡ከሁሉም በላይ ደግሞ የእግርኳስ አፍቃሪ የሆነው ብቸኛ መንትያ ወንድሟ የብራዚሎች አድናቂ ነው፡፡በተለይ የአለም ዋንጫ ኖሮ የእግር ኳስ ጫወታ በሚኖርበት ጊዜ ገና ህፃን ሆነው ጀምር የብራዚሎች ደጋፊ ነበር..ለብራዚል ተጫዋቾች ያለው ፍቅር እብድ የሚያስብለው አይነት ነው፡፡ሮናልዶ..ሮናልዲኒዬ…ሮቤርቶ ካርሎስ….ሪቫልዶ….  ኒይማር  ..ገብርኤል  ጀሱስ….ማርቲሊኒ…በእሱ  እድሜ  ሙሉ የተጫወቱትን ዘርዝሮ አይጨርስም፡፡ በየጫወታቸው የሚያሳዩትን አብዶ እንደ ህጻን ልጅ ቁጭ ብድግ በማለት ማየት የዘወትር ድርጊቱ ነው፡፡እና እሷም ይሄንን ባየች ቁጥር ይገርማት ነበር፡፡ከዛ የሚያየውን አይታ በእነሱ መደመምና ትኩረት መስጠት ጀመረች፡፡ ከዛም ተጋባባት ከብሄራዊ ብድን የብራዚል… ከክለብ ደግሞ የአርሴናል ደጋፊ ሆና እራሷን በእግርኳስ አፋቃሪዎች መዝገብ ላይ አሰፈረች፡፡እና በዚህ የተነሳ የብራዚል አድናቂ ነች፡፡ታዲያ ወደደቡብ አሜሪካ እንደምትሄድ ዜናውን ስትሰማ ፔሩን ሳይሆን ብራዚልን ለማየት ነበር የጓጓችው… እንደአጋጣሚ ደግሞ ፕሮግራሙ ከፔሩ ስለተጀመረ… እስከአሁን ብራዚልን የማየት ጉጉቷ ባለበት እንዲቆይ ሆኗል፡፡

እዚህ ፔሩ ባሳለፈችበት አንድ ወር ውስጥ አብዛኛውን ጊዜ ጥብቅ በሆነ ስልጠና እና ትምህርታዊ ሴሚናር ያሳለፈች ቢሆንም አልፎ አልፎ ወጣ ብላ ዞር ዞር በማለት የመዝናናት እድሉ አጋጥሟታል፡፡ሊማ  የፓስፊክ ውቅያኖስን በአንድ ጎኗ ታካ የተመሠረተች ጥንታዊውንና ዘመናዊውን ስልጣኔን ጎን ለጎን አቻችላ የላቲኒንና የዬሮፖዎችን ባህልና ቋንቋ ቀይጣ የተመሰረተች የፔሩ ዋና ከተማ ነች።ኑሀሚ ከተማዋን ገና እንዳየቻት ነው የወደደቻት።እርግጥ የመጣችው ለጉብኝት ሳይሆን ለትምህርታዊ ሴሚናር ነው።በዛም ምክንያት የቀኑን የበዛ ጊዜዎን በትምህርታዊ ሴሚናሮችና የወርክሾፕ ስልሰጠናዎች ላይ ነው የምታሣልፈው።ግን ባገኘችው ጥቂት ጊዜም ቢሆን በተለይ ምሽቱ ላይ እዛው ከተዋወቀቻቸው የሀገሬው ተወላጅ ሠልጣኝ ጋር ሹልክ ብላ ትወጣለች።
ሊማ ከተማን እንደታዘበቻት ከሆነ ከወገብ በላይ ውብና ዘመናዊ ከወገብ በታች ጎስቋላና ቆሻሻ ሆና ስላገኘቻት በጣም ተደምማበታለች፡፡በጉብኝቷ ወቅት እጅግ ካስገረሟትና አይኗንም ቀልቧንም ከተቆጣጠሯት ብዙ ነገሮች መካከል ጥቂቱ
1)  ካቴድራል ዲ ሊማ የተባለ በጥንታዊ የአውሮፓዎች የህንፃ ዲዛይን የተሠራ ግዙፍና ውብ ሙዚዬም ነው።ሙዚዬሙ በረቀቀ ጥበባቸው ልብን ስልብ በሚያደርጉ በተለያየ የስዕል
ክምችቶች የተሞላ ነው።ከዛም በተጨማሪ ቁጥር ስፍር የሌላቸው ቅርሶች፤ ልዩ ልዩ አይነት መስቀሎች፤ሀውልቶችና .. ታሪካቸውንና ጀግንነታቸውን የሚዘክሩበት በሰው የራስ ቅል ክምችቶች የተሞላ ነው።
2)  ልላው ፕላዛ ዳ ራና የሚባለው አካባቢ ነው።ይሄ የሀገሬው መንግስት ቤተመንግስት የሚገኝበት እና የሊማ ዋና አደባባይ ያለበት እንደ ዳውን ታውን የሚታይ የከተማዋ ማእከላዊ ስፍራ ነው።በዚህ አደባባይ ላይ ከእድሜ ጠገቦቹ ህንፃዎች ፊት ለፊት ለቀቅ ብሎ በተንጣለለው ሰፊ የኮንክሪት ሜዳ ላይ በእርግባች እና በቱሪስቶች መካከል በመረጋጋት እና በስክነት የተሞላ ጫወታን ማየት ልዩ ደስታን ለልብ ይሰጣል።ቱሪስቶች ለወፎቹ ጥራጥሬና ምግብ ሲበትኑላቸው..ወፎቹ ግር ብለው መጥተው አካባቢውን ሲወሩትና ምግቡን ከወለሉ ላይ ሲለቅሙ ማየት ልዩ አይነት ስሜት ይፈጥራል፡፡

3/ፓርክ ኬኔዲ…በአካባቢው ያለው የህንፃዎች ውበት ፤የአበቦችና የአረንጓዴ ዛፎች እይታ አካባቢውን የሚያላብሰው ውበት እንዳለ ሆኖ የዚህ ፓርክ ድንቁ ነገር ድመቶች ናቸው።ፓርኩ ጠቅላላ በድመቶች የተሞላ ነው ማለት ይቻላል።ደግሞ አንድ መቀመጫ ላይ ተቀምጦ ከአስር በላይ የድመት ዝርያ መመልከት ይቻላል፡፡ሲንቀሳቀሱ ደግሞ ሌላ አይነት።በአለም ላይ የሚገኙትን የድመት ዝርያዎች በጠቅላላ ከየቦታው እየለቀሙ በማማምጣት እዚህ የበተኗቸው ነው የሚመስለው.፡፡ይንን ሁሉ የድመት ዝርያ በአንድ ቦታ አይቶ ማንም የማይደመም ሰው አይኖርም።በዛ ላይ ስለ ድመት የማውቀው ብሎ አስጎብኚዋ የነገራት ነገሮች በጣም ነው ያስገረማት፡፡ለምሳሌ ድመት ማረጥ የሚባል ነገር እንደማታውቅና እድሜ ልኳን መውለድ እንደምትችል ነግሯታል፡፡አንድ ድመት የሆነ ቀዳዳ ለመሹለክ ከመሞከሯ በፊት መጀመሪያ ቀዳዳው እንደሚያሾልካት ለክታ እርግጠኛ ስትሆን ብቻ እንደምታደርገው
👍15518👏4😁3🔥1
#ጉዞ_በፀሎት
(አቃቂ እና ቦሌ)


#ክፍል_አንድ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧

22 አመቷ ነው፡፡እንዲሁ ከውጭ ለሚመለከታት ሰው ሁሉ የተሟላላት እንከን አልባ ውበት ይዛ እንከን አልባ ኑሮ እየኖረች በእንከን አልባ ደስታ የምትሰቃይ ቅምጥልጥል እድለኛ ነው የምትመስለው፡፡ ግን ቀርቦ ህይወቷን በጥልቀት ላጠና እህ ብሎ የውስጧን ላደማጠ ምን ያህል የማይደረስበት ሽንቁር በህይወቷ እንዳለ በቀላሉ ይረዳል…ግን ያንን እሷን የመቅረብን እድል የሚያገኝ ሰው ጥቂት ነው ..ወይም ጭሩሱኑ የለም……እንዴት ተደርጎ..፡፡

አባቷ በሀገሪቱ ከሚገኙ ጥቂት ቢሊዬነሮች አንድ ናቸው፡፡ቢሊዬን ብር ያላቸው ሰውዬ የወለዱት አንድ ልጅ ብቻ ነው…አንድ ብቸኛ ሴት ልጅ፡፡በዛ የተነሳ የበዛ እንክብካቤ፤ ለከቱን ያለፈ ክትትልና ቁጥጥር እየተደረገባት ያለች ልጅ ነች፡፡እርግጥ ቁጥጥሩ ከጊዜ በኋላ የመጣ ነው፡፡እስከ15 ዓመቷ ድረስ በነፃነት ነፃ ሆና ያደገች ልጅ ነበረች…ከ15 ዓመቷ በኋላ ግን ከጤንነቷ ጋር በተያያዘ ነገሮች የተለየ መልክ ያዙ….፡፡

በፀሎት የልብ ህመምተኛ መሆኗ የታወቀው ከ15 ዓመቷ በኋላ ነበር ፡፡ 17 ዓመት ከሞላት በኋላ ግን ነገሮች ፈር ለቀቁና ህመሟ ከፍተኛ ደረጃ ደረሰ…በየሄደችበት ቦታ የተለየ ነገር ገጥሟት ትንሽ ስትጨናነቅ መውደቅና እራሷን መሳት ስትጀምር…24 ሰዓት በክትትል ስር እንድትሆንና ጠባቂዎች ከአጠገቧ እንዳይለዩና በመንገዷ ሆነ በማንኛውም እንቅስቃሴዋ ምንም አይነት እንከን እንዳያጋጥማትና ካጋጠማትም በፍጥነት አፋፍሰው ሆስፒታል እንዲወስዷት የታቀደ የጥንቃቄ እርምጃ በአባቷ ተወሰደ ..በዚህ ውሳኔ መሰረት ሳትወድ በግዷ ነፃነቷም ተነጠቀ፡፡

በፀሎት በአስተዳደጓ ምክንያት ገና የታዳጊነት ህይወቷን ሳታገባድድ ነው  ህይወት ስልችት ያለቻት፡፡ አቶ ኃይለ መለኮት ስጦታው ሀብታቸውን ተከትሎ ባለዝና እና ታዋቂ ከመሆናቸውም በላይ የተናገሩት የሚደመጥላቸው፤ ያዘዙት የሚፈፀምላቸው ተፈሪ ሰው ናቸው፡ወይዘሮ ስንዱ መሸሻ የአቶ ኃይለ መለኮት የትዳር አጋር ናቸው..አብረው በጋብቻ 28 ዓመት አሳልፈዋል፡፡

ከዚህ ውስጥ በዚህ ትዳር ውስጥ ፍቅር አብሯቸው የነበረው ለስምንት ዓመት ያህል ብቻ ነበር፡፡ከዛ በኋላ አንድ ቤት በጋራ ተጋርተው ከሚኖሩ ዳባሎች የተለየ ትርጉም ያለው ትዳር አልነበረም..አንደውም እርስ በርስ በእየእለቱ እያደገ የሚሄድ ጥላቻ…አንዱ ሌለኛውን ለማበሳጨትና ደስታ ለመንጠቅ የሚደረግ ተንኳልና አሻጥር እናም ደግሞ ከዛም አልፎ አንዱ ሌለኛውን ለማስወገድ እስከመመኘት የሚደረስ የበቀል ስሜት …..በቃ በጋብቻቸው ውስጥ ያለው ነገር ይሄ ነው፡፡አዎ ሁለቱም ወላጆቾ በመረረ የእርስ በርስ ጥላቻ ነፍሳቸው የበከተ..አንደኛው የሌለኛውን ጉዳት ብቻ ሳይሆን ሞትም ጭምር አምርሮ የሚመኝ.. አንድ ህንፃ ውስጥ በሚገኝ ሁለት ክፍል ውስጥ ተነጣጥለው የሚተኙ….የጋራ ጣሪያና የጋራ ሳሎን ስለሚጠቀሙ የሚቀፋቸው…..የሁለት አለም ሰዎች ናቸው..ወላጆቾ፡፡ግን ይህ ሁሉ ሆኖ ሁለቱም በእኩል ደረጃ ከልባቸው የሚያፈቅሩት አንድ ነገር አለ..ልጃቸውን፡፡ብቸኛ ልጃቸው በፀሎት…፡፡ ከተጋቡ ከስድስት አመት በኃላ በስንት ስለትና የህክምና እርዳታ ነው የወለዷት..ስሟንም በፀሎት ያሏት በፀሎት አገኘንሽ ለማለት ፈልገው ነው፡፡ከእሷ በፊትም ሆነ ከእሷ በኋላ ሁለቱም ሌላ ልጅ አልወለዱም….ሳይፈልጉ ቀርቶ አይደለም…እንዴትስ ላይፈልጉ ይችላሉ?፡፡ የዚህን ሁሉ ሀብት ወራሽ ሚሆን ስድስት ሰባት ልጆች ቢኖራቸው ምን አልባት በመሀከላቸው ያለው መራራቅና ጥላቻ የዚህን ያህል ሊንቦረቀቅ አይችልም ነበር ብላው ብዙዎች ያወራሉ….…ያም ሆነ ይህ አሁን በዚህ ወቅት ከ28 ዓመት የጋብቻ ቆይታ በኃኋላ ሆድ ከጀርባ በሆነ ግንኙነት የ22 ዓመት ልጃቸው የልደት በዓል በጋራ በአማረ እና በሸበረቀ ሁኔታ ለማክበር ሽርጉድ እያሉ ነው፡፡

አዎ በፀሎት ዛሬ የልደቷ ቀኗ ነው ፡፡ የ22 ዓመት የልደት በዓሏ፡፡በዚህም ምክንያት ቦሌ ከመድኃንያለም ቤተክርስቴያን ጀርባ ሁለተኛ መንገድ ላይ በሚገኘው ቤታቸው ድል ያለ የልደት ዝግጅት አዘጋጅተው ከ100 በላይ ሰዎች ተጠርተዋል፡፡እርግጥ ይሄን የልደት ዝግጅት ቀደም ብላ አልፈለገችውም ነበር፡፡አቧቷ ነው ችክ ብሎ ካልተደገሰ ያለው፡፡በኋላ እሷም በዝግጅቱ ደስተኛ ሆነች፡፡በዝግጅቱ ላይ ከታደሙት መካከል ግማሽ ያህሉ የእሷ የዩኒቨርሲት ጎደኞቾ እና መሰል እኩዬቾ ናቸው፡፡ቀሪዎቹ ደግሞ የሁለት ተፃራሪ ፓርቲ የጋራ ስብሰባ ላይ የታደሙ የሚመስለው የእናቷ እና የአባቷ የቅርብ ሰዎችና የስራ ባለደረቦች ናቸው፡፡
የድግሱን መስተንግዶ ሆነ የመጠጥና የምግብን ዝግጅት በሀላፊነት ወስዶ እያዘጋጀ ያለው በከተማው አሉ ከተባሉት ሆቴሎች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ዲጄ ከመቀጠሩም በላይ የራሱ ባንድ ያለው አንድ ታዋቂ ድምፃዊ በዝግጅቱ ላይ ተገኝቶ ዘፈኑን እንዲያቀርብ ተደርጎል፡፡ለአንድ የ21 አመት ቀንበጥ ወጣት ልደት 3 ሚሊዬን ብር ወጪ ሆኗል ቢባል ማን ያምናል…?ግን የሆነው እንደዛ ነው፡፡

በጸሎት ለልደት በዓሏ በልዩ ትዕዛዝ በሀገሪቱ አለች በተባለች ዲዛይነር የተዘጋጀላትን ውብ ቀሚስ ለብሳ ብዙም ያልደመቀ የተወሰነ ሚካፕ ነካ ነካ አድርጋ የምትወደውን ከፈረንሳይ የተላከለላትን ሽቶ ነስነስ አድርጋ አጠር ባለ ፀጉሯ ላይ 50 ሺ ብር የተገዛ ዘንፋላ ባለ ወርቃማ ቀለም የኢጣልያን ፀጉር ደርባበት በከፊል የተለወጠና የተቀየረ መልኳን ይዛ ከክፍሏ ወጣች..አንደኛ ፎቅ ላይ ካለ መኝታ ቤቷ ቀጥታ የልደት ዝግጅቱ ወደሚካሄድበት ምድር ቤት ወደሚገኘው ግዙፉ ሳሎን ከመሄዷ በፊት ወላጆቾ ወደታች መውረድ አለመውረዳቸውን ለማረጋገጥ ከእሷ መኝታ ቤት በተቃራኒው ኮርነር ጎን ለጎን ወደሚገኘው የወላጆቾ መኝታ ቤት አመራች፡፡መጀመሪያ የሚገኘው የእናቷ መኝታ ቤት ስለሆነ በቀስታ ቆረቆረች..ከውስጥ መልስ እየጠበቀች ሳለች ቀጥሎ ካለው የአባቷ መኝታ ቤት የእናቷን ድምፅ ሰማች…፡፡…ግራ ገባት››

‹‹ውይ..ዛሬ ሰላም ሰፍኗል ማለት ነው… እንደዛ ባይሆን እማዬ አባዬ መኝታ ቤት አትገባም ነበር››ብላ አሰበችና በደስታ ፈገግ ብላ ወላጆቾን ላለመረበሽ ፊቷን አዙራ ልትመለስ ስታስብ በጆሮዋ ሾልኮ የገባው ጠንከር ያለ የእናትዬው ንግግር ከእርምጃዋ ገታት፡፡

ቆም አለች ….ጥርት ብሎ እየተሰማት አይደለም..ፊቷን መለሰችና ወደአባቷ መኝታ ቤት ቀረበች..ጆሮዋን በራፉ ላይ ለጠፈች….ሰቅጣጭ ንግግር እየተመላለሱ ነው፡፡

‹‹እስኪ ከውሽሞችህ መካከል አንዷን እንኳን መርጠህ ብትጠራ ምን አለበት…? ሶስት ውሽሞችህን በአንድ ቤት፣እኔን እሺ ግድ የለም ለእነሱ ስሜት አትጨነቅም…ነው እርስ በርስ አይተዋወቁም..?››

‹‹አሁን ለምንድነው የምትነዘንዢኝ…….?ከፈለግሽ አንቺም ውሽሞችሽን መጥራት ትቺያለሽ››

‹‹በእውነት እንዴት ደግ ነህ እባክህ…..እንኳን ውሽማዬን ወንድ ጓደኞቼን መጥራት እንደማልችል አንተም እኔም እናውቀዋለን››

‹‹ለምን ?ምን ችግር አለው..?ድግሱ እንደሆነ የተትረፈረፈ ነው!!››በሹፈት ቃና የታሸውን የአባትዬውን መልስ ሰማች፡፡

‹‹አዎ የተትረፈረፈ ነው…ግን ውሽማ የለኝም እንጂ ቢኖረኝም ላንተ ስለማስብ አልጠራውም››

‹‹ለምን ?››

‹‹ሌላ የሰው ነፍስ በእጅ እንዲጠፋ አልፈልግም....ምን አይነት ቀናተኛና በሽተኛ እንደሆንክ እኔም አንተም እናውቃለን…እስከዛሬ ገና ለገና ከአንቺ ጋር አወሩ ብለህ ስንት ወዳጆቼን አስገደልክ?፡፡››
👍13412😱3🥰2🤔2👎1🔥1
#ወይ_አጋጣሚ(አጭር ልብወለድ)


#ክፍል_አንድ


#ድርሰት_በዘሪሁን
==========================
ዛሬ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ድክምክም ብሎኛል፡፡ብዙ ስራ እየሰራሁ ስለዋልኩ አይደለም..እንደውም በተቃራኒው ስቀመጥ ስለዋኩ ይመስለኛል ዛል እስክል የደከመኝ፡፡ ‹‹መቀመጥ መቆመጥ ነው››ትል ነበር አንድ ኑሮዋ ጠቅላላ ተረት በተረት የሆነባት ተራች አክስቴ፡፡ ሰዓቱ 12፡35….ሆኗል ፡፡ምሽቱ ደረስኩ እያለ ነው፡፡ስቀመጥ ከዋልኩበት ቢሮዬ ለሊቱን ስተኛ ወደማሳልፍበት ቤቴ ቀጥታ ማምራት ስላልፈለግኩ ለምን ትንሽ ወክ አላደርግም አልኩና ወደ ቤቴ አቅጣጫ በጣም በዝግታ ማዝገም ጀመርኩ፡፡እርምጃዬ ጽሞና የታከለበት እንዲሆን ስለፈለኩ ዋናውን የአስፓልት መንገድ ለቀቅኩና በሁለተኛው መንገድ መጓዝ ጀመርኩ.፡፡እሱም በባጃጅና በመንገደኛ ሰዎች ስለተሞላ አልተመቸኝም ወደ 3ተኛው መንገድ ተሸጋገርኩ፡፡አዎ ይሄ ይሻላል.. እሬሳን ወደ የዘላለም ማረፊያው ወደ ሆነው ቀብሩ እንደሚሸኝ ሰው ወይም በመንግስት ወታደሮች እጅ ወድቆ እጁ በሰንሰለት ወደኃላ እንደተጠፈረ አሸባሪ ተብዬ እጆቼን ወደኃላ አጣምሬ በዝግታና በፀጥታ እጓዛለሁ፡፡አካባቢው ፀጥ ያለ ነው፡፡አዕምሮዬ ግን በጫጫታ የተሞላ ነው፡፡ዝም ብሎ ህልሙንም እውኑንም ይፈተፍታል፡፡

ድንገት ከአንዱ መንገድ ተጠምዝዤ ወደ አንዱ ስገባ ዓይኔ አየ.. ምን ዓየ …..?አትሉኝም፡፡ልክ ለዘመናት እንደተራብኩት የእናቴ ጡት ዓይነት ነገር፣ልክ በፀሎት እና በእምነት አማኞች እንደሚናፍቆት ገነት ዓይነት ፣ልክ ፖለቲከኞች ለዘመናት ይመኙት እንደነበረው የቤተ መንግስት ወንበር ዓይነት… አይገርምም…፡፡ ያየሁት እኮ አሁን እንደጠቀስኩላችሁ ዓይነት ነገር ሆኖ አይደለም..እኔን ግን ውስጤን የተሰማኝ…በወቅቱ አደነዛዘዜ ፤ አደነጋገጤ እንደዛ ነው ያስመሰለብኝ፡፡ …ወፈር ደልደል ያለ ቀይ ቂጥ ነው ያየሁት..….ያየሁት ከገባሁበት መንገድ በግራ ጠርዝ በኩል በግምት 100ሜትር ርቀት ላይ የቀበሌውን ጽ/ቤት አጥር ተጠግቶ ነው፡፡እኔ ያልኳችሁ ፍም ቂጥ ብቻ አየሁ አይደል..?ግን የዘነጋሁት ወይም ያልነገርኳችሁ አንድ ነገር የቂጡንም ባለቤት ማየቴን ነው፡፡ግራ ቀኝ ስታማትር እሷም እኔን አይታኛለች፡፡ግራ የተጋባች ይመስላል፡፡የለበሰችውን ቡኒ ጅንስ ሱሪ አውልቃ ጉልበቷ ጋር አድርሳዋላች ፣በእርቃን ቂጧ እና ወልቆ ጉልበቷ ጋር በደረሰው ሱሪዋ መሀከል ሆኖ የሚዋልል ሌላ ቀይ ነገር ይታየኛል..አዎ ፓንቷ ነው ፡፡ ግራ ገብቷት ወይም የራሱ ጉዳይ ብላ መሰለኝ ችላ አለቺኝና ቁጢጥ አለች፡፡
እኔም የእራሴው እርቃን በአደባባይ እየታየብኝ ያለ ይመስል ሽምቅቅ ብዬ የ100 ሜትሩን ርቀት ወደ 70 ሜትር ካጠበብኩት በኃላ ቆምኩ፡፡..በቃ  ዝም  ብዬ  ቆምኩ፡፡ ቆሜም  ማሰላሰል  ጀመርኩ፡፡ እሷም አንዴ ወደ መሬት አንዴ ወደ እኔ እያች የኩላሊቷን ጥዝጣዜ ና የፊኛዋን ውጥረት ማስተንፈስ ቀጠለች….‹‹ሾሾ… ሾ… ዋዋ›› የሚል የሽንት ድምፅ ተሰማኝ..፡፡እርግጠኛ ግን አይደለሁም፡፡ ብቻ የሰማሁ መስሎኛል፡፡
ግን በፊት ቅምቅም አያቶቻችን ለወንድ ሱሪ ለሴት ቀሚስ የሚባል ልብስ ለምን እንዲኖር እንዳደረጉ ዛሬ ነው ፍንትው ብሎ የገባኝ.፡፡ይሄኔ እኮ ይህቺ ሚስኪን ሴት ቀሚስ ለብሳ ቢሆን ኖሮ እሷም አትጋለጥም.. እኔም አልደነግጥም ነበር፡፡ቁጭ ብላ ቀሚሷን ገለብ ታደርግና ‹ሾዋ..ዋ…ዋ› በማድርግ ከተነፈሰች በኃላ ምንም እንዳልተፈጠረ ተነስታ ትሄድ ነበር፡፡
ወይ..ሀሳቤን ሳልጨርስ ጨርሳ ቆመች፡፡ፊቷን ከእኔ በተቃራኒው  አዞረችና መጀመሪያ ቀዩን  ፓንቷን ወደ ላይ ስባ  ቀዩን ቂጧን ሸፈነችው፤  አቤት  በፓንትም  ሲታጠር  ያምራል፣ምራቄን  ገርገጭ አደረግኩ፡፡ ከዛ ሱሪዋን ወደ ላይ እየጎተተች ለበሰች፡፡ከጨረሰች በኃላ ቀጥታ ወደ እኔ አቅጣጫ መጣች፡፡ግራ ገባኝ፡፡ ወደ ኃላ ልመለስ ወይስ ወደ ፊት ልቀጥል…?፡፡ከሁለቱ እግሮቼ የትኛውን ላስቀድም?፡፡ እያልኩ በሀሳብ እየተጨነቅኩ ስዋልል እሷ ቀድማኝ ስሬ ደረሰች፡፡አትኩሬ አየኋት… ቂጧም ብቻ ሳይሆን መልኳም ቀይ ነው፡፡የሆነ ክልስ ነገር ሳትሆን አትቀርም…፡፡ፈርዶብኝ ቀይ ሴቶች ልቤን በቀላሉ ብትንትን ያደርጉታል ፡፡ፍቅረኛዬ ሀይሚም እንደዚህችው ነች፡፡ ዓይኖቾ ጐላ ጐላ ያሉ ባለ ሉጫ ፀጉር ነች..፡፡አደንዛዥ ፈገግታ መግባኝ ታካኝ አልፋኝ ሄደች፡፡ እኔም ቀኝ ኃላ ዞሬ ተከተልኳት፡፡ ውሳኔዬ እሷን መከተል እንዲሆን ያስገደደኝ የቂጧ ቀይነት ይሁን የፈገግታዋ ጉዳይ አልገባኝም፡፡ደረስኩባት እና ዝም ብዬ ከጎኗ መራመድ ጀመርኩ፡፡
ግራ ገባቷት‹‹እንተዋወቃለን?››አለቺኝ፡፡

‹‹አሁን ተዋወቅን አይደል እንዴ?››መለስኩላት፡፡

‹‹አሁን የት ?››

‹‹እዛ ነዋ.. እኔ ፈዝዤ ተገትሬ አንቺ ቁጢጥ ብለሽ፡፡››

ከት ብላ ሳቀች… ሳቋ ያምራል‹‹…ጉደኛ ነህ!!! ትንሽ እንኳን አታፍርም እንዴ..?እኔስ ተጨንቄ ነው አንተ ምን አለ ዞር ብትልልኝ  ኖሮ?››

‹‹ወዴት ዞር ልበል..?ከተጠጋሁሽ እኮ ይበልጥ አይሻለሁ ብዬ ነው  የቆምኩት፡፡››

‹‹ዞረህ በሌላ መንገድ አትሄድም እንዴ?››

‹‹አኸ እንደዛም ይቻል ነበር ለካ..?እሱ እንኳን ትዝ አላለኝም፡፡››

‹‹ደንዝዘህ እንዴት ትዝ ይልሀል..?ወይ ወንዶች ስትባሉ!!!›› አለችኝ፡፡ይህቺን‹ ወይ ወንዶች ስትባሉ!!! › ቢያንስ ከ100 ሴቶች ሰምቼያታለሁ ፡፡ግን ወንዶች ስንባል እንዴት ነን..? ያው እንደዛ የሚሉን ሴቶች እራሳቸው ይመልሱት ፡፡

‹‹ግን ያምራል›› አልኳት፡፡

የድንጋጤም የእፍረትም ሳቅ እየሳቀች‹‹ምኑ?›› አለችኝ፡፡

‹‹ያየሁት ››አልኳት… አኔም በተራዬ እንደማፈር ብዬ፡፡

‹‹የትኛውን አይተህ የትኛውን እንደዘለልክ በምን አውቃለሁ?›››

‹‹ከወርቃማዋ ሸለቆሽ በስተቀር ሁሉንም አይቼያለሁ››

አቤት የሳቀችው ሳቅ… እንባዋ እስኪንጠባጠብ ነው ተንፈራፍራ የሳቀችልኝ፤ሴት  ልጅ  እንደዚህ  ስትስቅልኝ  ለመጀመሪያ  ጊዜ ይመስለኛል፡፡ ባይገርማችሁ ከቤቴ መንገድ በተቃራኒው ይህቺን ባለ ቀይ ቂጥ ሴትዬ ተከትዬ ለ24 ደቂቃ ተጉዤያለሁ፡፡

‹‹ምትገርም ልጅ ነህ ..ለማንኛውም የምሄድበት ቦታ ደርሼያለሁ በዚህ ነው የምጠመዘዘው፡፡ ››

‹‹እንዴ!!! እኔስ?›› አልኳት ደንግጬ፡፡

‹‹አንተ ምን..?ወደምትሄድበት ሂዳ፡፡››

‹‹የምሄደውማ ወደ ቤቴ ነበር …ቅድም እሄድበት በነበረው አቅጣጫ፡፡››

‹‹በል እንግዲህ የቂጥ አምላክን እየረገምክ ቀኝ ኃላ ዙርና ንካው›› አለችኝ፡፡

‹‹ስልክ ቁጥርሽን ስጪኛ?››

‹‹ምን ልታደርገው?››

‹‹በቃ እንዲሁ፡፡››

‹‹ባለትዳር ብሆንስ?››የማልመልሰውን ጥያቄ ጠየቀችኝ፡፡

‹‹ሁኚያ..እኔ እንዲሁ ነው የፈለኩት አልኩሽ እኮ፡፡›› እንዲሁ መፈለግ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ብትጠይቀኝ ግን መልስ አልነበረኝም፡፡

‹‹ሁላችሁም ወንዶች በመጀመሪያ እንዲሁ ነው የምትፈልጉት በኃላ እንጂ ነገር የምታመጡት፡፡››

‹‹ኸረ እንዲሁ ነው ስጪኝ፡፡››በአሳዛኝ ሁኔታ ተለማመጥኳት፡፡

እያጉረመረመች ሰጠችኝ፡፡ተሰናበተኳትና እንዳለቺኝ ቀኝ ኃላ ዞሬ ወደቤቴ ነካሁት፡፡
ለሊቱን ሙሉ የቂጧ ምስል በህልሜ ሲመላለስ እና ሲያሰቃየኝ አደረ፡፡ ምን ነካኝ ግን ?ፍቅር ሊይዘኝ ይሆን እንዴ? ኸረ አይደረግም…፡፡ ቢያንስ በ10 ዓመት እኮ ትበልጠኛለች፡፡ ግን ይሄ ምን ችግር አለው? ከስድስት ወር በፊት የጠበስኳት ቀሚ ፍቅረኛዬ የሆነችውን ሀይሚን በ10 ዓመት እበልጣት የለ?አንዷን እበልጣታለሁ አንዷ ደግሞ ትበልጠኛለች..በቃ ማቻቻል ማለት እንዲህ ነው፡፡
👍79😁2512🔥1🥰1
#የጣት_ቁስል


#ክፍል_አንድ


#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ

አማላጅ

ከራሳቸው ሃሳብ ጋር ሙግት ገጥመዋል ፡፡ እሽ ይሉኝ ይሆን ? ወይስ እንቢ ? እንደገና ደግሞ በአንዴማ እንቢም ፤ እሽም   አይሉኝም ፡፡ እያሉ ሳይታወቃቸው ቄስ መልካሙ ቤት ደረሱ፡፡ ለመጣራት ወደ አጥሩ ተጠጉ ፡፡ እንደ አጋጣሚ ሆኖ ቄስ መልካሙን ግቢያቸው ውስጥ መፅኃፍ እያነበቡ ተመለከቷቸው ፡፡

መጣራታቸውን ትተው "ደህና አደራችሁ መልካሙ" ? አሉ፡፡ ቄስ አሻግሬ ፤

አቀርቅረው ከሚያነቡት መፅሃፍ ላይ አንገታቸውን ቀና አድርገው "እግዚአብሔር ይመስገን ሰላም አደሩ" ? አሉ ፡፡ ቄስ መልካሙ፡፡ ንስሃ አባታቸው ያለወትሯቸው በጥዋት በመምጣታቸው የመደናገጥ ምልክት እየታየባቸው ፡፡ ፀበል ሊረጩን ይሆን ? ሳንነግራቸውና ሳንዘጋጅ ፤ እነሱም ሳይነግሩን ፤ በሰላም ይሆን የመጡት? ከራሳቸው ሃሳብ ሳይወጡ የተናገሩት ነበር

"አንተን ፈልጌ ነበር የመጣሁት"፡፡ እደጅ ላግኝህ አሉ ቄስ አሻግሬ ፡፡ ለስለስ ባለ አነጋገር ፡፡

"ለምን እንደተፈለጉ ባያውቁም "ምነው ደህና አይደሉም እንዴ"?

አይ ደህና ነኝ ፡፡ ለጉዳይ ፈልጌህ ነበር አሉ
ከየት መጀመር እንዳለባቸው ግራ ቢገባቸውም "አቶ ለማ ልጅህን ለልጄ እንዲሰጡኝ አማላጅ ሂድልኝ ብሎኝ ነው የመጣሁት"፡፡ ብለው ሃሳባቸውን ሳያቋርጡ በመቀጠል አቶ ለማ ሽፈራው ጥሩ ሰው ናቸው፡፡ ዘራቸውም ቢሆንም ምንም አይወጣለትም ፡፡ ልጁም የተባረከ ፤ የተመሰገነ ፤ ጨዋ ፤ ድምፁም የማይሰማ ማለፊያ ገበሬ ነው" አሉ፡፡

ቄስ መልካሙ ያልጠበቁትና ያላሰቡት ነገር ሆነባቸው፡፡ ለጊዜው ምን ማለት እንዳለባቸው አብሰለሰሉ፡፡ የማይሆን ነገር ነው፡፡ አሁን እድላዊትን አግቢ ብላት ትምህርቷን ትታ የምታገባ አይመስለኝም፡፡ ከራሳቸው ሃሳብ ጋር እየተሟገቱ ከቆዩ በኋላ "እንግዲህ
ከቤተሰብና ዘመድ ጋር መክረን መልስ ብንሰጥ ይሻላል፡፡ አሁን እኔ ለብቻየ የምወስነው ነገር የለም" አሉ፡፡ ሆዳቸው እንደመባባት እያለም ቢሆን፡፡

"ታዲያ ቀነ ቀጠሮው ለመቼ ይሁን" ? አሉ፡፡ መቼም በአንዴ እሽ እንደማይባል የአገሩ ባህልና የተለመደ መሆኑን ስለሚያውቁ ፡ተመልሰው የሚመጡበትን ቀን በጉጉት ለመስማት እየጠበቁ ፡፡

"ዛሬ ቀኑ ሮዕብ አይደለም፡፡ የዛሬ አስራ አምስት ቀን ይመለሱ፡፡ እኛም እስከዛ ብንመካከርበት ይሻላል" በማለት መልስ ሰጧቸው፡፡

ይሁን መልካም ነው፡፡ ብለው የተሰጣቸውን ቀነ ቀጠሮ ተቀብለው ከቄስ መልካሙ ጋር ተሰነባብተው ወደ ቤታቸው ተመለሱ፡፡

ንሰሃ አባታቸውን ከሸኙ በኋላ ፤ ወደ ቤታቸው ገቡ፡፡ በመጨጊያቸው ላይ ተቀመጡ፡፡ አገጫቸውን በቀኝ እጃቸው ደገፍ አደረጉ፡፡ ትክዝ ባለ አንደበት ስለልጃቸው እድላዊት በውስጣቸው ማብሰልሰል ተያያዙት፡፡

ወ/ሮ አሰገደች ከማድቤት ወጥተው ወደ መኖሪያ ቤት እየሄዱ ባለቤታቸው ከወትሯቸው በተለየ ተክዘው ተመለከቷቸው፡፡ እርምጃቸውን ገታ አድርገው "ምነው ቄስ አሻግሬ አመጣጣቸው በደህና አይደለም እንዴ"? አሉ ፤ ለባለቤታቸው ፡፡

"አይ ደህና" ናቸው ፤ አሉ፡፡ ሃዘን ይሁን ትካዜ በተቀላቀለበት ንግግር፡፡

ወ/ሮ አሰገደች የንሰሃ አባታቸው ዛሬ በጥዋት አመጣጣቸው ለምን እንደሆነ ባያውቁም የባለቤታቸው መተከዝ አስጨንቋቸዋል፡፡ "በሰላምማ አልመሰለኝም" አሉ፡፡ ወደ ባለቤታቸው እየተጠጉ፡፡

"የመጡትስ በሰላም ቢሆንም አቶ ለማ ሽፈራው አማላጅ ልከዋቸው ነው የመጡት" አሉ፡፡ የባለቤታቸውን ሁኔታ እየተመለከቱ፡፡

"የምን አማላጅ ነው?" አሉ፡፡ ሆዳቸው እንደመርበትበት እያለ፡፡ የምን አማላጅነት እንደሆነ ለመስማት በመቸኮል፡፡

የአቶ ለማን ልጅ ታውቂዋለሽ ?"፡፡

"ትንሹን ነው ትልቁን?፡፡

"አይ! ትንሹን ይሁን ትልቁን አለየሁትም፡፡ አበበ የሚባለውን፡፡

ምን እንደሆነ ሳያውቁ "በሞትኩት ምን ነካው ያምስኪን ልጅ ከሰው ተጣላ" እንዴ ?፡፡

"እሱስ አልተጣላም፡፡ አቶ ለማ ሽፈራው እድላዊትን ለአበበ ስጡኝ ብሎ ነው፡፡ ቄስ አሻግሬን አማላጅ ተልከው የመጡት"፡፡

ወ/ሮ አሰገደች ለመስማት የጓጉትና ልባቸው ተንጠልጥሎ ሲጠብቁት የነበረው ምን እንደ ሆነ ባያውቁም ከባለቤታቸው የሰሙት ያልጠበቁትና ያላሰቡት ሆነባቸው፡፡ ለጊዜው መርዶ እንደ ተነገራቸው ያህል በዝምታ ተዋጡ፡፡ በሃሳባቸው ልጄን እማ አልሰጥም አስተምራለሁ፡፡ ትምህርቷን ሳትጨርስ አልድራትም፡፡ እሷም እሽ አትልም በዛ ላይ ጎበዝ ተማሪ እየተባለች አገር የመሰከረላት ነች ፡፡ የልጃቸውን ሃሳብ እያወጡና እያወረዱ ከሔዱበት የሃሳብ ሰመመን ሳይመለሱ..

እና "አሁን ምን ይሻላል ትያለሽ? አሉ ፤ ቄስ መልካሙ፡፡ ከነጎዱበት የሃሳብ ሰመመን መለስ ብለው "እኔ ምን እላለሁ አንተ ምን አልካቸው?፡፡

"እኔማ ለዛሬ አስራምስት ቀን ተመልሰው እንዲመጡ ቀጥሪያቸዋለሁ፡፡ እኛም መመካከርና የእድላዊትን ፈቃድ ማወቅ ስላለብን ብየ ነው፡፡ ቀኑን ያስረዘምኩት፡፡ ለመሆኑ የሚሳካ ይመስልሻል ?፡፡

"እኔ እድላዊት ለማግባት እሽ የምትል አይመስለኝም፡፡በዛ ላይ ለትምህርቷ ያላት ፍላጎት ጎበዝ ተማሪ እንደሆነች ማንም ያውቃታል፡፡ እንደ እኔ ሃሳብ ትምህርቷን ከጨረሰች በኋላ፤ ብታገባ ይሻላል፡፡ ትዳር ይደረሳል፡፡ የት እንዳትሔድ ነው፡፡ ብለው አሁን አንተ ምን ወሰንክ አሉ?፡፡

"ማድረግ ያለብንማ ሁለታችንም ተመካክረን መወሰን ነው፡፡ እንደ እኔ እድላዊት እሷ እንኳን ባትፈቅድም ማግባት አለባት፡፡ ለትዳር ደርሳለች፡፡ ትምህርቷም ይበቃታል፡፡ ከአሁን በኋላ፤ ከትምህርቷ ቀርታ የቤት ሙያ መልመድ አለባት" አሉ፡፡

እድላዊት እንደ እናቷ የጠይም ቆንጆ ሰለክለክ ያለች ፤ ቁመናዋ እና ጥርሶቿ ልክ እንደ አባቷ ከሩቅ የሚያማልል ነው፡፡ ታዲያ የጠይም መልከመልካሟን ቆንጆ እንድላዊትን የሚያያት ሁሉ ሳይጎመዣት
አያልፍም ነበር ፡፡

አበበ ለማ እድላዊትን ሊያገባት አማላጅ የላከው በአጋጣሚ ከወንድሟ ከተመስገን ጋር ወደ ትምህርት ቤት ስትሄድ ባያት ማግስት ነበር፡፡ለቤተሰቦቹ ነግሮ አማላጅ እንዲላክለት ያደረገው፡፡

ወ/ሮ አሰገደች እድላዊትን አልድርም ፤ አስተምራለሁ ፤ እያሉ በሃሳባቸውም ሲፎክሩ የነበሩት በባለቤታቸው ቁጣ ያዘለ ንግግር ተቀየሩ፡፡

አንተ ከወሰንህ ታዲያ ምን አደርጋለሁ፡፡ እኔም ማግባት አለባት ባይ ነኝ፡፡ ማግባቷ ለእኔም ትጠቅመኛለች፡፡ ብታመም እንኳን ጠያቂ ዘመድ በቅርብ የለኝ፡፡ የምታገባበት ቦታ ቅርብም በመሆኑ እየመጣች ትጠይቀኛለች፡፡ በፍራትም ቢሆን ከባለቤታቸው ሃሳብ ላለመውጣት የተናገሩት ነበር፡፡

ቄስ መልካሙ የባለቤታቸውን ሃሳብና የራሳቸውን ሃሳብ አንድ ላይ ካሰባሰቡ በኋላ፤ እድላዊትን አሁን የተባባልነውን ሁሉ ከትምህርቷ ስትመጣ ንገሪያትና ከትምህርት ቀርታ የቤት ውስጥ ስራ እንድትለምድ አድርጊያት አሉ፡፡ ቁርጥና ኮስተር ባለ ንግግር፡፡

"እሽ ነግሬያት እንድትቀር አደርጋለሁ ፡፡

እድላዊትና ተመስገን

የጥዋት ተማሪ ናቸው፡፡ ወደ ትምህርት ቤት እየሔዱ እድላዊት ከወትሮው በተለየ ምክንያቱ በምን እንደሆነ አላወቀችውም፡፡ ግራ ተጋብታለች ፤ ሰውነቷ ይርበተበታል፡፡ ወደ ፊት መሔዷን ተወት አድርጋ አንዳንዴ ቆም በማለት ራሷን ለማረጋጋት ትሞክራለች፡፡

ተመስገንም በእህቱ መለዋወጥና ዝምታ ግራ ገብቶታል፡፡ ከአሁን አሁን ትነግረኛለች ብሎ ቢያስብም እድላዊት ግን የሆነችውን ለራሷ አላወቀችም፡፡ ምን እንደሆነችም ልትነግረው አልቻለችም ነበር፡፡

"ምን ሆነሽ ነው አሞሻል እንዴ?፡፡

"አላመመኝም ውስጤን ግን ፍራት ፍራት ይለኛል፡፡

"ምነው በሰላም ?፡፡
👍8912🥰1😱1🎉1
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች


#ክፍል_አንድ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
================

አላዛር አባቱን በጣም ይጠላል፡፡ለአባቱ ያለው ጥላቻ ለሰሎሜ ካለው ፍቅር ጋር በግራና  እና ቀኝ ጫፍ ላይ ካለው የሚዛኑ ዘንግ ላይ ቢንጠለጠሉ በእኩል ሌቭል ላይ ተንሳፈው ነው የሚታዩት፡፡ሰሎሜን መቼ ማፍቀር እንደጀመረ እንደማያውቀው ሁሉ አባቱንም መቼ መጥላት እንደጀመረ አያውቅም፡፡ብቻ ለአባቱ ያለው ጥላቻም ሆነ ለሰሎሜ ያለው ፍቅር በእድሜ ዘመኑ ሁሉ የነበረና ከእሱ የአካልና የአእምሮ እድገት ጋር ተያይዞ እያደገና እየጠነከረ የመጣ  ባለሁለት መልክ ስሜት  ነው፡፡

ሁል ጊዜ ስለአባቱ ሲያስብ አንድ የሚያስጨንቀው ነገር‹‹አሁን አባቴ ቢሞት አለቅሳለሁ?…››የሚለው ጥያቄ ነበር፡፡ ምክንያቱም በአባቱ መሞት ውስጡ እንደማያዝን ያውቃል…፡፡ካላዘነ ደግሞ እንዴት ብሎ እንባው  ሊመነጭለት ይችላል….?ለገዛ አባቱ ደግሞ ማልቀስ ካልቻለው  ቀሪው  ማህበረሰቡ ምን ይለዋል…?ይሄ ጉዳይ ሁል ጊዜ እንዳሳሰበው ነው፡፡ግን ደግሞ የሚፅናናው‹‹አረ እሱ አይሞትም….እንደእሱ አይነት ክፉና ፀያፍ ሰው እንኳን ሰው ሞት እራሱ ይሸሸዋል ››በሚለው እምነቱ ነው፡
አላዛር አባቱን ለመጥላት የቻለበት ዋናው ምክንያት ከህፃንነቱ ጀምሮ በሚወዳት እናቱ ላይ ያደርሰው የነበረውን ድብደባና በደል ጥርቅም ትውስታ በአእምሮው ስለታጨቀ  ነው፡፡አባትዬው በሳምንቱ ውስጥ ካሉ ሳባት ቀኖች ቢያንስ ስድስቱን እኩለ ለሊት ካለፈ በኃላ ሰክሮና ጥንብዝ ብሎ ነው ወደቤት የሚመጣው፡፡መስከሩና ውድቅት ለሊት በራፍን እያንኳንኳ የተኛውን የሰፈሩን  ሰው ሁሉ መቀስቀሱንና መረበሹ ብቻ አይደለም የሚያበሳጨው፡፡ተከፍቶለት ወደቤት ከገባ በኋላ ለአንድና ሁለት ሰዓት የሚያደርጋቸው ድርጊቶች ናቸው ይበልጥ አስፀያፈዎች፡፡ልክ እንደጀማሪ ሰባኪ ድምጽን ከጣሪያ በላይ ከፍ በማድረግ  በቀኝ ያለው ጎረቤቱን ወይም በግራ ያለውን ስም እየጠራ ጥንብርኩስን አውጥቶ ይሳደባል፡፡ስድቡን ከአባወራው ከጀመረ ወደሚስትዬው ይሸጋገርና ልጆቹ ላይ ያበቃል.፡፡በዚህ ጊዜ ታዲያ የአላዛር እናት ዙሪያውን እየተከተለች በመሳቀቅ ልታስቆመውና ዝም ልታስብለው ትጥራለች፡፡በዚህን ጊዜ በቡጢ ሲላት ከግድግዳ ጋር ትላተማለች፡፡.ትንሽ ትረጋጋና አሁንም ልታስተኛው ትጥራለች..በጠራባ ሊያነሳት ይልና እራሱ ተንሸራቶ ወለሉ ላይ ይዘረጋፋል…እንዳይጎዳባት ሮጣ ሄዳ ከወደቀበት ልታነሳው ስትሞክር በጥፊ አይነ-ስቧዋን ያቃጥልላታል … ያዞራትና ስሩ ሄዳ ዝርግት ትላለች፡፡

ይሄንን በየቀኑ መኝታው ላይ ሆኖ..ድብን ያለ እንቅልፍ ውስጥ ያለ ይመስል ዝርግትግት ብሎ..ትንፋሹን ለራሱ እንኳን እንዳይሰማ ወደውስጥ ውጦ.. በለበሰውን ብርድልብስ ቀዳዳ አይኖቹን አጨንቁሮ ይመለከታል…ተነስቶ እራስጌው ባለው የብረት ዘነዘና ሰካራም አባቱን  አናቱን መፈርከስና አናትዬውን ነፃ ማውጣት ይፈልጋል…ግን ምኞት ብቻ ነበር፡፡ያንን ለማድረግ ወኔ አልነበረውም፡፡አይደለም እንደዛ ለማድረግ ሞክሮ ይቅርና ድንገት እንቅስቃሴ ቢያሳይ እንኳን አባትዬው ትኩረቱን ከጎረቤት ወደእሱ ይመልስና ጎትቶ ከአልጋው ያስነሳዋል…በዛ ውድቅት ለሊት የሆነ ሰበብ ፈጥሮ ተንበርከክ ይለዋል…ሲንበረካክ በኩርኩም አናቱን ያነደዋል..እናትዬው እንዳይጎዳባት በመሀከላቸው ስትገባ ቡጢውናና ጥፊውን ያለስስት ይሸልማታል… መጮጮኸና ትርምሱ በእጥፍ ይበዛል፡፡
ያንን ስለሚያውቅ ገና የአባቱን ድምፅ ከውጭ ሲሰማ በድን ሆኖ እራሱን ይቀብራል…በምንም ነገር ጣልቃ ላለመግባት እስከመጨረሻ ከስሜቱ ጋር ይታገላል.. እናቱም እንደዛ እንዲያደርግ ነው የምትመክረው..ዘወትርም የምትለምነው፡፡
አላዛር….አባቱ በእውነታው አለም ተጫባጭ ሰው አይመስሉትም፡፡.የሆነ ንክ ደራሲ ለገፀ ባህሪነት ፈልጎ አጣሞና አወላጋግዶ  የሳላቸው ንክ ሰው ነው የሚመስሉት፡፡ ምክንያቱም ሲጠጡ ሰይጣን …መጠጥ ባልቀመሱበት ሰዓት  ደግሞ ፍጽም መልአክ መሰል ሰው ናቸው፡፡
ሲሰክሩ ለሊቱን ሙሉ ሲሰድብት ያደሩትን ጎረቤት ጥዋት ተነስተው ወደስራ ሲሄዱ በራፍ ላይ ካገኙት መሬት እስኪደርሱ ለጥ ብለው ሰላም ብለውት ፤አቅፈው ተከሻውን ወዝውዘውት …ቸገረኝ ካለ ኪሳቸው ገብተው ሸጎጥ አድርገውለት …የሚስቱን ደህንነት የልጆቹን ሰላም መሆን ጠይቀውት መንገዳቸውን ይቀጥላሉ፡፡
‹‹ማታ ምነው እንዳዛ የሰደብከኝ?››ብሎ ሚጠይቃቸው ካለ…‹‹አረ በፈጣሪ..ምን ይሁነኝ ብዬ አንተን የመሰለን ወዳጄን ሰድባለው…?.እማይሆነውን››ከማለት ውጭ አንድም ነገር አያስታውሱም፡፡ብዙውን ጊዜ እንደውም ጥዋት ሲነሱ የሚስታቸው ጉንጭ አብጦ ..ወይም አይኖቻቸው ቀልቶ….ወይንም ደግሞ እጆቾ ተስብረው…ሲያዩ ኡኡ አገር ይያዝልኝ..ሚስቴን ማነው እንዲህ ያደረጋት? ብለው እስከማልቀስ ይደርሳሉ፡፡ሁለተኛ መጠጥ ላለመቅመስ ምለው ይገዘታሉ፡፡ በከንፈራቸው መሬት ስመው የሚስታቸውን ይቅርታ ጠይቀው በፀፀት እያጉረመረሙ ወደስራ ይሄዳሉ…ማታ ሲመጡ ግን እንደተለመደው ጥንብዝ ብለው  ነበር ወደቤታቸው የሚመለሱት፡፡››
በዚህም የተነሳ የሰፈር ሰው ሆነ ወዳጅ ዘመድ ሁሉ‹‹ እሱ እኮ መጠጥ ሲጠጣ አብሾ ስላለበት ነው…››በሚል  የሽፋን ምክንያት ጥፋቱን ሁሉ ይቅር ይሉታል፡፡አላዛር ግን ይሄ የአባቱ የማጭበርበሪያ ዘዴ  እንደሆነ አድርጎ ነው የሚቆጥረው… ከለሊቱ ድርጊታቸው በላይ የጥዋት ማስመሰላቸውና እንደተፀፀቱ ጠብ እርግፍ የሚሉት የማስመሰያ ድራማ እና የማደናገሪያ ዘዴያቸው እንደሆነ ስለሚያምን  ይበልጥ ይበሽቅባቸዋል፡፡የት እንዳነበበው ባያውቅም ‹‹እንደምትቀየር እርግጠኛ ካልሆንክ ይቅርታ አትጠይቅ››የሚል አባባል እንዳለ  ያስታውሰዋል፡፡አባቱ ሁል ጊዜ ጥፋት እንደሰሩ… ቀጥሎ ይቅርታ እንደጠየቁ ነው፡፡.ግን አንድም ቀን ቅንጣት ያህል እንኳን የመለወጥ ተነሳሽነት አግኝቶባቸው አያውቅም፡፡

አላዛርና እህቶቹ እያደጉ ሲመጣ ግን አባትዬውን ለመታገስ ያላቸው ትዕግስት እየተመናመነ ሄደ…አባትዬውን መክሰስ እና  ማሳሰር ….እናትዬውን ሊያጠቃ ሲል መሀከል መግባት ሲጀምሩ የአባትዬውም ተስፋ እየተሞጠጠና ብስጭታቸውም ከእለት ወደእለት እየጨመረ ሄደ፡፡በስተመጨረሻ እቤቱን ለቆላቸው ወጣና  ሌላ ሰፈር ሌላ ቤት ተከራይቶ ገባ፡፡

በዛን ጊዜ የአላዛር እድሜ 14 ዓመት አካባቢ ነበር እህቶቹ ደግሞ 19 እና 24 ዓመታቸው ፡፡በቤቱ በዘመናቸው አይተው የማያውቁት ነፃነትና ሰላም ሰፈነ…ግን ደግሞ ሌላ ሁለት ችግር ተከሰተ ፡፡አንደኛ በአባትዬው እቤቱን ለቆ መውጣትና ትዳሩን ማፍረስ እናትዬው በጣም ሀዘንተኛ ሆነች፡፡ከአሁን አሁን ተመልሶ ይመጣል ብላ በተስፋና በናፍቆት መጠበቅ..ተስፋዋ አልሰምር ሲል አይኗ እስኪደክም ማልቀስ…የነፍስ አባታቸውንና ሌሎች ሽማግሌሎችና የአባቱን ጎደኞች በየተራ  እየለመነችና እየተማፀነች ባለቤተዋ ጋር ሽምግልና መላክ…ቆሚ ስራዋ ሆነ፡፡

ይሄ የእናትዬው ድርጊት ከአላዛር የማሳብ አቅም በላይ ነበር የሆነበት፡፡አባትዬው እቤቱን ለቆ መውጣቱን ሲያውቅ መጀመሪያ በአእምሮ የመጣለት እናቱ እንዴት ከመጠን በላይ  ደስታኛ ሴት እንደምትሆን ነበር፡፡ምክንያቱም ይሄ ሰው እናቱን ቢያንስ ከሀያ አመት በላይ አሰቃይቷታል..ከሚወዷትና በድሎት ሊያኖሯት ከሚችሉ ሀብታም ቤተሰቦቾ አቋራርጧታል… ደብድቧታል….. አቁስሏታል.. አስርቧታል… ልጆቾን በመደብደብ አሳቆታል..
👍8717👎1👏1🎉1
#አላገባህም


#ክፍል_አንድ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
=====================

ከእንቅልፉ ባኖ አይኖቹን ሲገልጥ በመስኮቱ ሾልኮ የሚገባው ብርሀና መኝታ ክፍሉን አድምቆታል…ቀኝ እጅን ሊያነቃንቅ ቢሞክር አልቻለም….ጭንቅላቱን ዞር ብሎ ሲመለከት አንድ ጠይም ወጣት ክንዱ ላይ ተንተርሳ  ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ተኝታለች….ትነቃለች ብሎ ሳይጨነቅ ከላዩ ላይ ገፍትሮ ወደጥግ ገፋተራትና ከአልጋው ለመውረድ ወደግራው ሲዞር ሌላ ሴት እርቃኗን ብልቅጥቅት ባላ  ሁኔታ ተኝታ አያት፡፡አቅጣጫውን ቀየረና በግርጌ  በኩል ወረደ ፡፡

ሞባይሉን አንስቶ ሰዓት ሲያይ ሰባት ሰዓት  ሆኗል፡፡ብዙም አልገረመውም ፡፡…እስከዚህን ሰዓት መተኛት የአብዛኛው ቀን የተለመደ ተግባሩ ነው፡፡በተለይ ለሊት የናይት ክለብ ስራ በሚኖረውና እዛ አንግቶ በሚመጣ ቀን ሰባትና ስምንት ሰዓት ድረስ ካልተኛ አእምሮ ንፅህ አይሆነም……ቀጥታ ወደሻወር ቤት ሄደና ፈጣን ሻወር ወሰደ፡፡ከዛ ሲወጣ ነጭ ጋዎኑን ለብሶ ወደኪችን ነው የሄደው፡፡በጣም እርቦታል፡፡ፍሪጁን ከፈተና የሚበላ ነገር መፈለግ ጀመረ፡፡ዳቦና ጁስ ያዘና እዛው ወንበር ስቦ በመቀመጥ መመገብ ጀመረ…ወዲያው አንደኛዋ ሴት እንደእሱ እርቧት ሳይሆን አይቀርም መቀመጫዋ ላይ  ስስ ሻርፕ ነገር አገልድማ በከፊል በመሸፈን እርቃኗን ግዙፍ  ጡቷቾን እያማታች መጣችና የኪችኑ በራፍ ላይ ቆመች፡፡

‹‹እ …..የሚበላ ነገር ትፈልጊያለሽ?››

‹‹በጣም እንጂ የእኔ ፍቅር….››

‹‹ተቀመጪ….››አላትና ከተቀመጠበት ተነስቶ ወደፍሪጁ በመሄድ እንደእሱ ጁስና ዳቦ አዘጋጅቶ ይዞላት መጣና ፊት ለፊቷ አስቀመጠላት፡፡

እየተስገበገበች መብላት ጀመረች፡፡

‹‹እሱም ከፊት ለፊቷ በመቀመጥ የጀመረውን መመገቡን ቀጠለ‹‹ጓደኛሽስ?››

‹‹ምን አድርገሀት ነው..እራሷን እኮ አታውቅም፡፡››

‹‹ምን አደርጋታለው…አንቺን ያደረኩትን ነዋ፡፡››

አፏ ውስጥ ያለውን ምግብ ማላመጧን ሳታቋርጥ ‹‹ወይ …ጀግና እኮ ነህ››አለችው፡፡

‹‹አመሰግናው››

‹‹እሺ አሁን ፕሮግራማችን ምንድነው?››ስትል በአይኗቾ በመለማመጥ ጠየቀችው፡፡

‹‹ማለት….በቃ እንለያያለና…..እናንተም ወደ ጉዳያችሁ ትሄዳላችሁ..እኔም ወደስራዬ….››

‹‹በቃ…?››አለችው በቅሬታ፡፡

‹‹ምነው? የቀረ ነገር አለ እንዴ?››

‹‹ትንሽ ..››አለችና
ከተቀመጠችበት ተነስታ ወደእሱ በመቅረብ  እጇቾን በአንገቱ ዙሪያ ጠምዝዛ ጉልበቱ ላይ ተቀመጠችና ከንፈሩን ትስመው ጀመር…. አልተቃወማትም….፡፡
እንደውም ሁለት እጆቹን ሁለት ጡቷቾ ላይ አሳረፈና ያፈተለትላት ጀመር፡…ከዛ ይዟት ቆመ….እሷ አንገቱ ላይ እንደተጠመጠመች መሳሟን ቀጥላለች፡፡

ቀስ ብሎ መሬት አስቀመጣትና የለበሰውን ጋወን አውልቆ እዛው ወለሉ ላይ ተወው…አሁን እርቃኑን ቀረ…..ከዛ የእሷንም መቀመጫዋ ላይ ያገለደመችውን ሻርፕ ቋጠሮ ሲፈታው ልክ እንደእሱ ሁሉ እርቃኗን ቀረች….ከዛ ወደግድግዳው ወሰዳትና ፊቷን አዙሮ ግድግዳውን እንድትደገፍ በማድረግ ከኃላዋ አቀፋት…..‹›የእኔ ፍቅር በጣም ነው የምትችለው እሺ…በጣም›››መቃተት ጀመረች፡፡

በዚህ ጊዜ  ከወደ በራፉ የእግር ኮቴ ተሰማ….ሌለናዋ ጓደኛዋ  ነበረች….ተጣብቀው ሲዋሰቡ ስታያቸው እንደመደንገጥ ብላ ባለችበት እንደመቆም አለችና

‹‹እንዴ አሁንም ትዋሰባላችሁ?አያንገሸግሻችሁም እንዴ?››አለቻቸው፡፡

እነሱ ግን ዞር ብለው ሳያዬት የጀመሩትን ቀጠሉ….እሷም ግራ ተጋባች….‹‹ሄጄ እነሱን ልቀላቀል ወይስ የሚበላ ነገር ልፈልግ?››….ስትል ከራሷ ጋር ሙግት ገጠመች‹‹ይሄ ሰውዬማ የሆነ ማግኔት ነገር አለው››ስትል አሰበች፤መጨረሻ  ስሜቷን እንደምንም ገታ የሆዷን ነገር አስቀደመችና ምግብ ወደመፈለጉ ሄደች፡፡

ለዘሚካኤል ይሄ የተለመደ ህይወቱ ነው፡፡አሁን እነዚህን ልጇች ከሶስት ቀን በኃላ የሆነ ቦታ ቢያገኛቸው….‹.የት ነበር ማውቃቸው ?›እያለ ከራሱ ጋር ውዝግብ ውስጥ መግባቱ አይቀርም..ስማቸውንማ  አሁንም ቢጠይቁት ወይ ሙሉ በሙሉ አያውቅም ወይም የአንዷ ስም ለሌለኛዋ ቀይሮ መስጠቱ አይቀርም፡፡ሴቷቹም በዛ ድርጊቱ ብዙም ሲከፈቸው አያይም…ምን አልባት እሱ የሚያገኛቸው ሴቷች ከተመሳሳይ ቦታ የሚመጡ ተመሳሳይ አይነት አመለካከት ያላቸው ሆነው ሊሆን ይችላል….በድምፃዊነቱና በፊልም ተዋናይነቱ ባገኘው ጣሪያ የነካ ዝና እና የተትረፈረፈ ሀብት ወደእሱ ገና ሲመጡ ለአንድ ቀንም ቢሆን ከእሱ ጋር ማሳለፍ ልክ ሎተሪ እንደወጣላቸው ስለሚቆጥሩ በማግስቱ ፊቱን ሲያዞርባቸው ብዙም አይከፋቸውም፡፡ወይም መከፋታቸውን በአርቴፊሻል ፈገግታቸው ደብቀው እሱ እንዳያውቅ ያደርጋሉ…ያችን ከእሱ ጋር ያሳለፉትን አንድ ቀን ለአመታት ለሌሎች አቻዎቻቸው የሚናገሩትን የሚጎርሩበት ታሪክ ስለሆነ በፀጋ እንዲቀበሉት ምክንያት ሆኗ ቸው ይሆናል፡፡እና ይሄ ጉዳይ የእሱን ባህሪ ከመስመር እንዲወጣ ገፊ ምክንያት ሆኖል፡፡
//
ከጥርብ ድንጋይ የተሰራ  መስኮት አልባ ጥንታዊ ቤት ነው፡፡ግድግዳው ከሶስት ሜትር በላይ ሲረዝም ጣሪያው ከኮንክሪት የተሰራ ነው፡፡እላይ ጥግ በግድግዳው ማብቂያና በጣሪያው መጀመሪያ መካከል ለአይጥ ማሾለኪያ ተብሎ የታሰራ የሚመስል ሶስት ትናንሽ ቀዳዶች አሉ፡፡ከዛ ውጭ ቤቱ ድፍን ነው፡፡
በዛ ላይ ከዚህ ቤት እንዴት አድርጎ ያመልጣል ብላው እንዳሰቡ አይታወቅም….ከምድር በተቀበረ ብረት ላይ የታሰረ ሰንሰለት እግሩን እና እጁን ተጠፍሯል፡፡ክፍሉ 3 በአራት ስፋት ያለው ቢሆንም እሱ መጠቀም የሚችለው ሁለት በሁለት በሆነች ቦታ ላይ ነው፡፡ በቀን ሁለቴ የብረት በሩ ላይ እንደመስኮት ያለች ትንሽ ማሾለኪያ ትከፈትና በትንሽ ሰሀን ምግብና በኩባያ ውሀ አሾልከው  ወለሉ ላይ አድርገውለት  መልሰው ይዘጉታል፡፡

ከዛ ውጭ በወር አንድ ቀን  እየመጡ የሚያናግሩት መነኩሴ አሉ፡፡ለቅጣው የእሳቸው መምጣት ልክ ገበያ የሄደች እናቱን እንደሚጠብቅ ህጻን ነው በናፍቆት የሚጠብቀው፡፡እሳቸውን ስለሚወዳቸው…ወይንም የሚሰጡትን መንፈሳዊ ትምህርትና ተግሳፅ ስለሚማርከው አይደለም….እሳቸው ሲመጡ ጠባብ መስኮት መሰል ሽንቁር ሳትሆን ዋናው በራፍ ይከፈታል፡፡አንድ ጣባቂ ክላሹን አነጣጥሮ በራፉ ላይ ይቆማል..ሌላው ባለደረባው ፈራ ተባ እያለ ወደውስጥ ይገባና ከብዙ ቁልፎች መካከል አንድን መርጦ ሰንሰለቱን ከብረቱ ጋር ያያዘውን ቁልፍ ይፈታል….ከዛ ‹‹ተነስ ጠያቂህ መጥተዋል››ይለዋል፡፡

እንደምንም ከተቀመጠበት ለመነሳት ይሞክራል….ግን የእግሮቹ ድምስሮች የተሳሰሩ ስለሆነ ቀላል አይሆንለትም…እንደምንም ግድግዳውን ተደግፎ ይቆማል..እለት በእለት ወገቡ ወደውስጥ እተቀለመመ እንደሚሄድ ይሰማዋል…እና ለመንቀሳቀስ እግሮቹን ሲያንቀሳቅስ እላዩ ላይ ተጠምጥመው የተቆለፉበት ሰንሰለት ከብደት ይፈትነዋል..ግን ደግሞ እንደምንም እየተጎተተ ወደበረንዳው ይወጣል…..በረንዳው እንደታሰረበት ክፍል የተፈጥሮ ብርሀን የማያገኝ ቢሆንም ሰው ሰራሽ ብርሀን የሚበራበት ስለሆነ አይኑን ይጨፍናል…አይኑ ብርሀንን ይፈራል…አስር እርምጃ ከተራመደ በኋላ ተከፍቶ ወደሚጠብቀው ከፍል ይገባል…ወደክፍል ከገባ በኋላ አጅበውት ከመጡት ሁለት ወታደሮች አንደኛው ክፍሉን ከውጭ ሆኖ ይቀረቅረዋል፡፡
👍7713👎4👏3🔥1
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ


#ክፍል_አንድ


#ድርሰት_ዘሪሁን_ገመቹ

ራሄል ከሁለት ረዳቷቾ ከሮቤልና ሎዛ ጋር  ስብሰባ ላይ እያለች ነበር ስልኳ የጠራው…ንግግሯን ሳታቋርጥ ስልኩን አነሳችና አየችው፤  አባቷ አቶ ቸርነት ናቸው የደወሉላት ፡፡ስብሰባ ላይ ነኝ ብላ ልትዘጋባቸው አልፈለገችም…አባቷ በጣም አስፈላጊ ጉዳይ ባይሆን ኖሮ በዚህ ሰዓት አይደውሉላትም ነበር፡፡

‹‹አንዴ ይቅርታ… ይሄንን ስልክ ማንሳት አለብኝ››ብላ ከተቀመጠችበት ግዙፍ ተሸከርካሪ ወንበር ተነሳችና ቢሮውን ለቃ ወጣችና….ከዛ ስልኩን አነሳችው፡፡

‹‹ሄሎ አባዬ ..እንዴት ነህ?››

‹‹ሰላም ነኝ ልጄ››

ድምፃቸው ተጎተተባት‹‹ምነው አባዬ? ችግር አለ እንዴ?››

‹‹አይ ልጄ ሁሉ ነገር ሰላም ነው…እኔ እና እናትሽ አንድ ነገር ልናማክርሽ ነበር››

‹‹ምንድነው?››

‹‹ይሄውልሽ ልጄ ምን መሰለሽ..እኔና እናትሽ ጡረታ ወጥተን ቤት መዋል ከጀመርን በኃላ ህይወታችንን ታውቂያለሽ…ብቸኞች ነን..አንቺም አሻፈረኝ ብለሽ በራስሽ ቤት ነው የምትኖሪው…፡፡››

ራሄል በምትሰማው ነገር ፊቷን አጨማደደች….የገመተችው አብረሽን ኑሪ የሚለውን የዘወትር ጥያቄያቸውን ደግመው ሊያነሱባት ነበር የመሰላት፡፡

አባቷ ትንፋሽ ወሰዱና ንግግራቸውን ቀጠሉ‹‹እህት እንዲኖርሽ ፈልገን ነበር››

ደነገጠች‹‹እህት!!››

‹‹አዎ ቅር ማይልሽ ከሆነ እኔ እና እናትሽ እህት እንዲኖርሽ ፈልገናል…የመጨረሻ ውሳኔ ላይ ከመድረሳችን በፊት ያንቺን አስተያየት ማወቅ ስለፈለግን ነው የደወልንልሽ፡፡››

‹‹ብዥ አለባት…እናቴ በሰባ አመቷ አረገዘች እንዴ?››ስትል በውስጧ እራሷ ጠየቀች፡፡‹‹አባቴ የአብረሀምን አይነት የዋህነት ስላለው  እግዜር በዚህ አድሜዋ የማዬን ማህፀን ቢከፍት አይገርመኝም››ስትል በራሷ ሀሳብ ሳቀችና ትኩረቷን ወደስልኩ መለሰች፡፡

‹‹አባዬ አልገባኝም..እንዴት ነው እህት ሊኖረኝ የሚችለው?››

አንድ የሁለት አመት  ቆንጅዬ ሴት ልጅ በጉዲፈቻ ልንወስድ ነው….››

‹‹በጉዲፈቻ…በጣም ደስ ይላል….ጥሩ ውሳኔ ነው የወሰናችሁት..››

ሀሳባቸውን ለመደገፍ ጥቂት ማሰብ እንኳን አላስፈለጋትም…የሁለት አመት ጣፋጭ ልጅ እዛ ግዙፍ ቪላ ቤት ውስጥ ስትሯሯጥ…አንዴ አባቷ ላይ አንዴ ደግሞ እናቷ ላይ እየተንጠለጠች ስታስቃቸውና ሰታዝናናቸው፣እነሱም ሲያሞላቅቋት…እሷን መሀላቸው አድርገው ግራና ቀኝ እጇን ይዘው ወደቤተክርስቲያን ይዘዋት ሲሄዱ .... በአይነ ህሊናዋ ታያትና በደስታ  ተፍለቀለቀች፡፡

‹‹ልጄ አሁን እሷን ልናይ   ሆስፒታል ነው ያለነው ..ከቻልሽ  ጋንዲ ነን  …ብትመጪ ደስ ይለኛል፡፡››

መልሶ መደነጋገር ውስጥ ገባች‹‹ሆስፒታል…ምን ትሰራለች?››

‹‹ትንሽ አሟታል…ከቻልሽ ነይ፡፡››ደገሙላት፡፡

‹‹በቃ መጣው››……ስልኩን ዘጋችና ወደቢሮዋ ተመልሳ ለረዳቶቾ ወደስራ እንዲመለሱ ትዕዛዝ ሰጥታ  ቦርሳውን አንጠልጥላ ወጣችና  ቀጥታ ከፓርክ መኪናዋን  በማንቀሳቀስ ስለአዲሷ እጩ እህቷ ምን እንደምትመስልና…ምኗን ታማ ሆስፒታል ልትገባ እንደቻለች እያብሰለሰለች   ወደጋንዲ  ሆስፒታል ነዳችው፡፡

ደርሳ  ወደውስጥ ስትገባ ሰውነቷ መንቀጥቀጥ ጀመረ…ይሄ የተለመደ ስሜቷ ነው…ሆሲፒታል ሂጂ ከሚሏት ጦርነት ዝመቺ ብትባል ትመርጣለች…እንደምንም ግን ወደውስጥ ዘለቀች…  አባቷን ደውላ አገኘችው…እጇን ይዞ እየመራ የተባለቸው ህፃን ወደተኛችበት ክፍል ይዟት ገባ፡፡ክፍሉ ውስጥ ከህፃኗ ጋር የገዛ እናቷ ብቻ ነች ያለችው፡፡ ከበራፉ አንድ እርምጃ ወደውስጥ ተራምዳ እንደቆመች ደንዝዛ ቀረች …ከዛ ማለፍ አልቻለችም፡፡
ፍፅም የሚባል ድንዛዜ ውስጥ ነው የገባችው…ልጅቷ ቢያንስ ከሶስት ማሽን ጋር በቱቦ ተያይዛለች…መልኳ ውብ ፀጉሯ ግንቧሯ ላይ ድፍት ያለ አጎጊ ብትሆንም ስልምልም ብላ እራሷን ስታ ተዘርራለች..እንደውም ነፍሷ ውስጧ እንዳለ እርግጠኛ መሆን አልቻለችም….
በቃ  ውስጧ ግልብጥብጥ ነው ያለባት…ከአመታት በፊት ምትወደውና ልታገባው ስታልመው የነበረው እጮኛዋ ኪሩቤል  እንዲህ እንደህፃኗ እራሱ ስቶና ዝርግትግት ብሎ በማሽን እገዛ ለመተንፈስ ሲያጣጥር የነበረው ትዝታ መጣባትና እራሷን ልትስት ተንገዳገደች..አጠገቧ ያለው አባቷ ፈጠን ብሎ ደገፋት…እናቷ በድንጋጤ ከተቀመጠችበት ተነሳችና ስሯ ደረሰች፡፡

‹‹ምነው ልጄ..አመመሽ እንዴ?››ሁለቱም ተቀባብለው ጠየቋት፡፡

‹‹አይ ደህና ነኝ …የመድሀኒት ሽታና የህክምና ማሽኖቹ ድምፅ ነው የረበሸኝ››

‹‹ቸሬ አንተ እኮ ነህ..እሷ ሆስፒታል እንዴት እንደምትጠላና እንደሚያማት እያወቅክ ነይ ያልካት፡፡››

‹‹እውነትሽን ነው አጥፍቻለው….በቃ ልጄ ነይ…ይሄን ያህል ካየሻት ይበቃሻል….ብለው እየጎተቱ ወደውጭ ወሰዷት…መኪናዋ ድረስ አደረሷት፡፡‹‹እርግጠኛ ነሽ ሰላም ነሽ…?መኪና መንዳት ትችያለሽ››

‹‹አታስብ አባዬ..ሰላም ነኝ..በቃ ተመለስ››
መኪና ውስጥ ገባታ ስትንቀሳቅስ አባትዬው ወደውስጥ ተመለሱ፡፡ቀጥታ ወደቤቷ ነው የሄደችው፡፡የልጅቷ ምስል ከአእምሮዋ ሊወጣ አልቻለም….ወላጆቾ ምን አስበው ያቺን በህይወት እና በሞት መካከል ባለች  ቀጭን ክር ተንጠልጥላ ያለችን ልጅ  በማደጎ ለመውሰድ እንዳሰቡ ሊገባት አልቻሉም…እንዴት አድርገው ሊንከባከቧት ነው…?ከለመዷትና ከወደዷት በኃላ ብትሞትባቸውስ…..?የሚወዱትን ሰው በሞት መነጠቅ እንዴት ልብን እንደሚሰብር እና ተስፋን እንደሚያከስም በራሷ ታውቀዋለች…እና በእሷ የደረሰ አይነት ሀዘን በዚህ እድሜያቸው በወላጆቾ እንዲድርስ አትፈልግም…፡፡

‹‹ግን ምን ማድረግ እችላለው?››ስትል እራሷን ጠየቀች፡፡እንዲሁ ስትብሰለሰል አደረች…ሳምንት ሙሉ አሰበችበት..አንድ ውሳኔ ወስና ለወላጆቾ ምንም ነገር ማለት ሳትችል…ወላጆቹ ህጋዊ የአሳዳጊነት ፕሮሰሱን ጨርሰው ልጅቷን ወደቤታቸው እንደወሰዱ ሰማች፡፡በቃ ከዛ በጊዜ ሂደት የሚሆነውን ጠብቃ ለመመልከት ወሰነችና ወደወላጇቾ ቤት ሄዳ አዲሷን እህቷን አየቻት…ምንም እንኳን ከዛ ሁሉ ማሽን ነፃ ሆና ብታያትም..አሁንም ግን  በጣም ደካማ እና የሰለለ ሰውነት ያለት ሆና ነው ያገኘቻት፡፡ግን ደግሞ በዛው ልክ አሳዛኝና ተወዳጅ ልጅ መሆኗን መካድ አልቻለችም፡፡
============
ራሄል ከረዳቷ ጋር እያወራች  ነው፡፡
‹‹ሮቤል ወ.ሮ ላምሮት ልገሳዋን  ለእኛ ፋውንዴሽን  እንድታደርግ አሁን በስልክ አናግሬታለው፡፡እሷን ማሳመን ከቻልኩ እና ውሳኔዋ ለእኛ ለመለገስ ከሆነ ለፋውንዴሽናችን ትልቅ ስኬት ነው››

ራሄል  ወረቀቶቿን ወደ ቦርሳዋ አስገባች፣ አንድ አይኗ  በእንጨት በተሸፈነው የቢሮዋ ግድግዳ ላይ በተሰቀለው ሰዓት ላይ ተሰክቶ ነበር።

‹‹ ለማውራት ጊዜ የለኝም። በሃያ ደቂቃ ውስጥ በወላጆቼ መኖሪያ ቤት በተዘጋጀው የምሳ ግብዣ ላይ መገኘት አለብኝ ››አለች፡፡
ረዳቷ ማንኛውንም አይነት ቅሬታ ከማንሳቱ በፊት  አቋረጠችውና  ‹‹ እንደገና ሴትዬዋ ከደወለች  ብቻ አሳውቀኝ።››አለችው፡፡
ስልኳን ዘጋችና ሞባይሏን  ቦርሳዋ ውስጥ ለትንሿ እህቷ ጸጋ ከገዛችው ትንሽ ስጦታ ጋር  አስቀመጠችው፣ ፀጋ ወላጇቾ ሊያሳድጓት በቅርብ የተረከቧት  እህቷ ነች፡፡ ራሄል ወደ መኪና ማቆሚያ ጋራዥ በፍጥነት በምትወርድበት ጊዜ የኖብል ፋውንዴሽን ቢሮዎችና ኮሪደሮች በፀጥታ ተውጠው  ነበር።
108🔥3😱2
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_አንድ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///

አለም የሆቴሉን የተወሰነ ክፍል አገልግሎት ዝርዝር የሚያሳየውን ካርድ አንስታ ተመለከተች። የአርብ ምሽት የአካባቢው ዘመናዊና ባህላዊ ባንድ በጥምረት ከምሽቱ አንድ ሰዓት እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ የሙዚቃ ድግስ እና ትርኢት ያሳያሉ።
ክፍል 125 ተከራይታ ጓዟን አሳረፈችና ልብሷን መቀያየርና እራሷን ማስዋብ ጀመረች፡፡ የመዋቢያ እቃዎቾን ከያዘው ሻንጣ ግርጌ ላይ የጥፍር መቁረጫ  አገኘች። ጥፍሯን ከሞረደች በኃላ አለባበሷን እና ጠቅላላ አቋሟን ለማየት መስታወት ፊት በመቆም ለመጨረሻ ጊዜ እራሷን ተመለከተች...።

በምትገናኛቸው ሰዎች ላይ የመጀመሪያ አስደናቂ የስሜት ትስስር ለመፍጠር ትፈልጋለች። ማንነቷን ስትነግራቸው በጣም እንደሚገረሙ እርግጠኛ ነች፣ ነገር ግን የበለጠ  ጠንካራ  ተጽእኖ  መፍጠር  ፈልጋለች።ከዚህ  ቀደም  ከሚያውቋት  ሴት ጋር እንደሚያነፃፅሯት ጥርጥር የለውም። እሷ ያንን መከላከል አትችልም፤አትፈልግምም፡፡. እሷን በትክክል መመዘንና መገምገም ከቻሉ እርግጠኛ ነች ሰሎሜ ጎይቶምን ለማስታወስ ይገደዳሉ ።የምትለብሰውን በጥንቃቄ መርጣለች። ሁሉም መዋቢያዎችና ጌጣጌጦች በተገቢው ልኬትና መጠን ተጠቅማለች፡፡በዛም የተነሳ በጣም ጥሩ የሚባል የተለየ እይታ እና ልዩ አይነት ውበት እንደተላበሰች ተሰምቷታል ። ሴትነቷን በጥበብ አጉልቶ የሚያሳይ ልዩ አይነት ብርሀን የሚንቦገቦግባት የውበት መቅረዝ ነው የምትመስለው፡፡

ግቧ መጀመሪያ እነሱን ማስደነቅ ነበር፣ እዚህ ወደ ሻሸመኔ በመምጣቷ እንዲገረሙ ብቻ ሳይሆን በዛው ልክም እንዲደነግጡ ነው የምትፈልገው።ከመጣችበት የሀገሪቱ ዋና ከተማ አዲስአበባ ጋር ሲነፃፀር ሻሸመኔ የአንድ ክፍለከተማን ያህል እንኳን ስፋት የሌላት ከተማ ነች፡፡ግን ደግሞ በሀገሪቱ ካሉ ማንኛውም ከተሞች የበለጠ ፤ከፍተኛ የንግድ እንቅስቃሴ የሚደረግባት…በየቀኑ በሚሊዬን የሚቆጠሩ ሰዎች ገብተው የሚወጡባት በጣም ደማቅ ከተማ ነች፡፡እና አሁን ፊት ፊት የምትጋፈጣቸው ሰዎች የዚህ ከተማ የጡት አባት ተደርገው የሚታዩ….ናቸው፡፡

አለም ያሰበችው ስራ በስኬት ካጠናቀቀች በሀገሪቱ የመገናኛ ብዙሀን ዜናዎችን በዋናነት የሚቆጣጠር ርዕሰ አንቀፅ እንደሚሆን እርግጠኛ ነች።ለበርካታ ደቂቆች መኝታ ክፍሏ ባለው መስታወት ፊት እየተሸከረከረች መልኳን ሆነ ጠቅላላ ቁመናዋን ደጋግማ ካየች በኃላ ሁለ ነገሯ እንከን ሊወጣለት እንደማይችል በመደምደም የእጅ ቦርሳዋን ትከሻዋ ላይ አንጠልጥላ ፣ የፍይል መያዣ ፎልደሯን አነሳችና እና የክፍል ቁልፍ እንደያዘች እርግጠኛ ሆና  ወጣች፡፡  የክፍሉን  በር  ዘጋችው።  የሆቴሉን  ህንፃ  ለቃ  ወጣችና ቀጥታ ወደመኪናዋ በመግባት መሃል ከተማውን እየሰነጠቀች ወደቀጠሮ ቦታ መንዳት ጀመረች፡፡ይሄንን ስብሰባ ያዘጋጀላት የዞኑ ዋና አቃቢ ህግ ነው፣ያንንም ስላደረገላት ለእሱ ታላቅ ምስጋና አላት፡፡ የትምህርት ቤት መለቀቂያ ሰዓት ስለሆነና ..አስፓልቱን በሰዎችና በተማሪዎች ስለተጨናነቀ እንድልቧ በፈለገችው ፍጥነት ለመንዳት ከባድ ሆኗባት ነበር፡፡

አለም ወደእዚህች ውብ ከተማ የመጣችው ለጉብኝት አይደለም፡፡ወይንም ዓላማዋን ከግብ እስክታደርስ ድረስ በእንግድነት አይደለም፡፡የከተማዋ ምክትል አቃቢ ህግ ሆና በመመደቧ ምክንያት ነው የመጣችው፡፡የትምህርት ዝግጅቷን እና ብቃቷን በማየት ይህን ሹመት የተሰጣት የአካባቢውን ህብረተሰብ ፍትህ እንዲያገኝ እንድታግዝ ነው፡፡ የእሷ ተልእኮ ግን የተለየ ነው፡፡የራሷ የሆነ አላማ እና ፍላጎት ባይኖራት ኖሮ በሞያዋ ለመስራትና ለማገልገል ከአደገችበት እና እድሜዋን ሙሉ ካሳለፈችባት አዲስአበባ እግሯን አታነሳም ነበር፡፡ የእሷ ተልእኮ እና ዓላም ለህብረተሰቡ ምንም ረብ እንደሌለው ስታስብ ትፀፀታለች። እሷ ለምን ወደእዚህ እንደመጣች ባስታወሰች ጊዜ የሚሰማትን የጥፋተኝነት ስሜት ነው፤ግን ደግሞ ምርጫ የላትም፡፡
በህይወቷ ውስጥ ወደዚህ ደረጃ እንድትደርስ ገፊ ምክንያት የሆናትን ጉዳይ ለአንድ ሰከንድ እንኳን ከረሳች እና ችላ ካለች ራሷን መቼም ይቅር ለማለት አትችልም፡፡ አካባቢው ስትደርስ ወደቀኝ ታጠፈችና ወደመዘጋጃ የሚወስደውን ጠባብ የአስፓልት መንገድ ተያያዘችው፡፡መዘጋጃ ጽ/ቤት ከመድረሷ በፊት አሁንም ወደቀኝ ታጠፈችና ከቀበሌ ጽ/ቤት ጎን ካለው የፍርድ ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ መኪናዋን አስገባችና ምቹ ቦታ ፈልጋ በማቆም
… ሞተሩን አጥፍታ ቦርሳዋንና የፋይል ፎልደሯና ይዛ ወረደች፡፡ በግቢው ውስጥ ያሉ የቢሮ ሰራተኞች ሆኑ የባለጉዳይ አይኖች ሁሉ እሷ ላይ ሲንከራተት ይታወቃታል…ብዙም ትኩረት ያልሰጠቻችው በማስመሰል ወደውስጥ ገባች፡፡

የፍርድ ቤቱን በር አልፋ ወደውስጥ ገባች፡፡ የተላላጠ ቀለምና የተፋፋቀ ግድግዳ እያየች ኮሪደሩን አቋርጣ ወደአንድ ክፍል ገባች፡፡
የፍርድ ቤቱ እንግዳ ተቀባይ የተለየ አይነት ሽቶ ስለሸተተው በደስታ ካቀረቀረበት ቀና አለ
…ቆንጆ መልክና ማራኪ አለባበስ የለበሰች ውብ ሴት ወደእሱ ስትመጣ ተመለከተ..ለሴቶች ስስ ልብ ያለው ወጣት ፀሀፊ በተቀመጠበት ተቁነጠነጠ፡፡

….አለም ወደፀሀፊው እየተራመደች በጎሪጥ ቀጣዩን ቢሮ በጉጉት ተመለከተች።

ስሩ ደረሰችና ‹‹ጤና ይስጥልኝ››አለችው፡፡

‹‹አቤት የእኔ እመቤት ….እንዴት ነሽ….?ይሄንን የመሰለ ውበት ይዘሽ መቼስ ተከሰሽ አይሆንም ወደዚህ የመጣሽው?››አላት፡፡

‹‹አረ በፍፅም››ስትል መለሰችለት፡፡

‹‹እና ከሰሽ ነው?››

ስለመቅለብለብ እያሰበች ‹‹እንደዛም አይደለም››ስትል መለሰችለት፡፡

‹‹እና….እኔን ፈልገሽ ብቻ እንዳይሆን?››

ከንግግግሩ በላይ ጉንጭ ውስጥ እያላመጠ ያለው ማስቲካ ሲታኘክ የሚያሰማው ድምፅ ምቾት ነሳት።ቢሆንም ፈገግ አለችለትና ሌላ ነገር ለመናገር እየተቅለበለበ እያለ፡፡"እኔ ከዞኑ አቃቢ ህግ ቢሮ ነው የመጣሁት። ዋና አቃቢ ህጉ ክቡር ግርማ ጠያቂነት ክብሩ ዳኛው የጠሩት ስብሰባ ነበር ››

ፈጎ የነበረው ፊቱ ሲኮሳተር እና ልቅ የነበረው ንግግሩ ሲሰበሰብ ታወቃት….

"ከአቃቢ ህግ ቢሮ ሰው እንደሚልኩ ተነግሮኝ ነበር…ግን ተወክሎ የሚመጣው ሰው ወንድ ይሆናል ብለን ነበር የጠበቅነው"አላት፡፡

"እንደምታየው እኔ ነኝ የመጣሁት…ምነው የክብሩ ግርማ ምክትል መሆኔ አላሳመነህም?ነው ወይስ አላስደሰተህም?፡፡››ሰውዬው ሴት አውል ከመሆኑም በተጨማሪ የወንድ ትምክት እንዳለበት ተረዳች፡፡እናም አበሳጫት፡፡

ከተቀመጠበት  አሻግሮ  ጉልበቷ  ጋር  የቀረውን  አጭር  ቀሚሷን  እየተመለከተ…"ደህና
..በቀጠሮ ሰዓት ነው የተገኘሽው። "ስሜ ቶሌራ ይባላል። ቡና ትፈልጊያለሽ? ››አላት ፡ የእሱን ግብዣ ችላ ብላ "የተጠሩት ሁሉም እንግዶች መጥተዋል?"
ከእሱ መልስ ከመስማቷ በፊት ከተዘጋው በር የፈነዳ ተንከትካች የወንዷች ሳቅ ተሰማ ።

‹‹አዎ…ሁሉም ተገኝተዋል!!››

‹‹ለቡናው አመሰግናለው….መግባት አለብኝ ››አለችና ቦታውን ለቃ ወደክፍሉ ተራመደች…አለም በህይወቷ ውስጥ በጣም ወሳኝ ለሆነው ስብሰባ ራሷን አበርትታ ወደ ቢሮ ተጠጋች።በስሱ ስታንኳኳ ሳቁ ተቋረጠና ፀጥታ ሰፈነ፡፡ገፋ አድርጋ አንገቷን አስቀድማ ወደውስጥ ገባች ፡፡በክፍሉ ውስጥ ያሉት ወንዶች ሌላ ወንድ ሲጠብቁ እንደነበረ ከተረጋጋ መንፈሳቸው በግልፅ መረዳት ችላ ነበር። በራፉን ተሻግራ ወደውስጥ በገባች ቅጽበት በራፉ ከኃላዋ ሲዘጋ ተሰማት፡፡.የአራት ሰዎች ጥንድ ስምንት አይኖች እሷ ላይ ተተከሉ….በሁሉም ላይ ተመሳሳይ አይነት ግራ የመጋባት እና የመደነቅ ስሜት አነበበች…የፈለገችውም እንደዛ እንዲሆን ነው፡፡
57👍5