አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ማምሻ


#ክፍል_ሦስት


#በአሌክስ_አብርሃም


ጀብድ ሠርቶ እንዳመለጠ የግፍ እስረኛ፣ በአድናቆትና እንኳን ተሳካላቸው ሰሚል ስሜት
የተሞላ ነበር፡፡

እማማ ዓምድነሽ፣ ልጃቸውን ማምሻን አይገቡ ገብተው አሳደጓት: ሰው ቤት ልብስ እያጠቡ፣ ጉሊት እየቸረቸሩ ትምህርቷን ሊያስተምሯት ጣሩ፡፡ ማምሻ ግን ትምህርቱም ብዙ አልሆነላትም፡፡ የሰፈሩ ማንጓጠጥ ትምህርት ቤትም ተከትሏት ነበር፡፡ እየወደቀች እየተነሳች እንደምንም ዘጠነኛ ክፍል ደርሳ አቆመች:: የሻይ ቤት አስተናጋጅነት ሥራ እንዲያፈላልግላት ደላላውን በሽርን ብትጠይቀው፣ ያንን ጫት የተለሰነበት ጥርሱን
እየገለፈጠ “ማምሻ! በዚህ ፊት አስተናጋጅነት!?…”አላት አሉ፡፡ ይህም አንድ ሰሞን
ተሳቀበት…በኋላ በወር ሰማንያ ብር እየተካፈላት የሰፈራችን ቦኖ ውሀ አስቀጅ ሆነች::
ውሀ አታፍስሱ ያለቻቸው የመንደሩ ሴቶች ያንኑ ቁሰሏን በሽሙጥ ስንጥር እየነካኩ፣
በመልከጥፉነቷ እያሸሞሩ ቁጡ አደረጓት፡፡
“ቆጥባ መልከ ጥፉነቷን ልታጥብብት ነው?
እያሉ:: በነጋ በጠባ ጸብ ሆነ፡፡

አንድ ቀን ማምሻ አንዷን አሽሙረኛ እንደ ነብር ዘልላ ተከመረችባት፡፡ ማን ያላቅቃት?
የዘመናት ብሶቷን እዚያች ዕጣው እወደቀባት ሴት ላይ አራገፈችው፡፡ በትርምሱ የውሀ
መቅጃ እንስራም አልተረፈ፣ ተከለከከለ፡፡ ከዚያቹም ሥራ ተባረረች፡፡ ደግሞ የማባረሪያ
ምክንያቱ ግነት! “ሕዝብ እንድታገልገል በተቀመጠችበት ቦታ፣ ሥልጣኗን ተገን
በማድረግ፣ ተጠቃሚውን ኅብረተሰብ በመደብደብና ንብረት በማውደም ቦንብ ጣይ
አውሮፕላን እያበረረች አንድ ከተማ ሕዝብ የደበደበች ዓይነት! ኅብረተሰቡን
በመደብደብ እና ንብረት በማውደም!”

ተራ ፌዝና ስላቃችን አንገት ያስደፋት ማምሻ፣ ሁሉንም እርግፍ አድርጋ ትታ፣ ባልቴት
እናቷ በየሰው ቤት ሠርተው በሚያመጧት ሳንቲም ኑሮዋን እየገፋች የወጣት ጡረተኛ ሆና እቤት ተቀመጠች፡፡ ይኼ መገፋት አጉብጧት እንዳቀረቀረች፤ እንጀራዋን እዚያው ባቀረቀረችበት አገኘችው፡፡ ልክ እንዲሰምጥ ወደ ባሕር የገፈተሩት ሰው የሚያስጎመዥ ዓሣ ይዞ የመውጣት ዓይነት ነበር ነገሩ፡፡ ማምሻ እንዳቀረቀረች ኪሮሽና ክር አነሳች፡፡እንዳቀረቀረች መርፌና ክር ታጥቃ በመራሩ ድህነት ላይ ዘመተች፡፡ በሰፊው የድህንትጥቁር ሸማ ላይ ውበትን ዘራችለት፡፡ ከዚያ የተገፋ ልብ፣ ያ ውበት እንዴት ወጣ?እላለሁ አንዳንዴ፡፡
ውበታቸው የመንደሩን ብቻ ሳይሆን፣ ከየትና የት ድረስ የሚመጡ የከተማውን ሴቶችን የሚያሻማ፣ ከምሶብ ዳንቴል እስከ ኤልጋ ልብስ፣ ከኩርሲ እስከሶፋ ልብስ፣ ከመጋረጃ እስከ ሐበሻ ቀሚስ ድረስ የጥልፍ ማጎተሟን አሳረፈች፡፡ ሰፈራችን በሙሉ በማምሻ የእጅ ሥራዎቿ ተጥለቀለቀ፡፡ የማምሻ ጥልፍ ያረፈባቸው መጋረጃወች በየመስኮቱ ተሰቅለው ሲታዩ፣ ማምሻ ገፊዎቿን በእጁ ጥበብ ድል ነስታ፣ ባንዲራዋን በድል
እድራጊነት በየቤቱ የሰቀለች ይመስል ነበር፡፡

በመቋጨት ይሁን በመጥለፍ፣ የማምሻ እጅ ያረፈበትን የባህል ቀሚስ ይሁን ነጠላ ለብሳ
ያልተውረገረገች፣ አንድ የመንደሩ ሴት ብትኖር፣ ማምሻ ራሷ ብቻ ነበረች። እንዲህ እያገባኝ ገብቼ የማምሻን የእጅ ሥራዎች ስመለከት፣ ከሌሎች ጥልፎች የተለዩ ይሆኑብኝ ነበር። ፍዝዝ ያለ ቀለም ባላቸው ክሮች፣ ደማቅ መደብ ላይ የምትጠልፋቸው አበቦች የራሷን ምስል የምትስል ሠዓሊ እስክትመስለኝ፣ አንዳች የሚያሳዝን ስሜት ውስጥ የሚያስገቡ ነበሩ:: በዚህም ሥራዋ እራሷን ባልቴት እናቷን በክር ጎትታ፣አንገታቸው
ከድህነት አዘቅት ብቅ እንዲል አደረገች፡፡ እናቷ በየሰው ቤት መንከራተት አቁመው እቤታቸው አረፉ፡፡ መንደርተኛውም ከማምሻ መልክ ይልቅ የእጅ ሥራዎቿ ዓይኖቹን ጋርደውት ከመዝለፍ ይልቅ ወደማድነቅ እና ማክበር የተሸጋገረ መሰለ፡፡ በእርግጥም ማምሻ መልከጥፉ ፊቷን በብርቱ እጆቿ ሽፍናው ነበር፡፡

ስም ውስጥ ሟርት አለ፡፡ ማምሻ እንደስሟ ማምሻ ሆነች: ሁሉም ነገር የተቀያየረው ድንገት ነበር፡፡ የእጅ ሥራዎቿን ሙሉ ለሙሉ ከገበያ ውጭ የሚያደርግ አጋጣሚ። ፈጣን እና በኤሌክትሪክ የሚሠሩ የጥልፍ መኪኖች በከተማው ውስጥ እንደ አሸን ፈሉ።
በአንድ ጀምበር ድፍን መንደር የሚያለብሱ፣ በደማቅ ከሮች ፎቶ የመሳሰሉ አበቦችን
የሚጠልፉ የ “ሲንጀር መኪኖች፡፡ የማምሻ ተስፋ ሟሸሽ! ጥበቧም ከምንም እስከ ሲንጀር መኪና ባለው ክፍተት መሀል ማምሻ መሸጋገሪያ ሆነ። በኑሮ አድማሷ ላይ ድንገት ብቅ ያለች ጀምበሯ፣ ሙቀትና ብርሃኗን በቅጡ ሳታጣጥማት ድርግም ብላ ጠፍታ፣ ዳግም የድህነትና የማንጓጠጥ ዝናብ ያዘለ ደመና በላይዋ ላይ ያንዣብብ
ጀመረ፡፡ ዳግም ወደ ማቀርቀር፣ ዳግም አንገት ወደ መድፋት ተመለሰች፡፡ ግና ምንም ያልተነኩ ቱባ ክሮችን ሰብስሳ ወስዳ ለባለሱቁ ከድሩ በርካሽ ሸጠችለት ተባለ፡፡ ያም የማምሻ የጥልፍ ሥራ ማብቂያ ሆኖ በጎረቤቱ ዘንድ ተወራ፡፡ በዚህም ተቀለደ፡፡ “ማምሻ ኪሮሽ ሰቀለችተባለ፡፡ የእግር ኳስ ተጫዋቾች መጫወት ሲያቆሙ
ጫማ ስቀሉ” እንደሚባለው መሆኑ ነው፡፡ቀስ በቀስ እናቷ ወደ ሰው ቤት ሥራ ተመለሱ፣ ማምሻም እናቷን ለማገዝ እንጀራ መጋርና መሸጥ ጀመረች፡፡ ታዲያ በዚህ መሃል ትንሽ በጎነት ያሳየቻት ሴት ብትኖር፣ ሎዛ ነበረች፡፡ ከአባቷ ጣውላ ቤት የእንጀራ መጋገሪያ ሳጋቱራ በነፃ እንድትወስድ አስፈቅዳላት ነበር፡፡

ባልገባኝ ምክንያት የሎዛ ዓይኖች ሁልጊዜ ማምሻ ላይ ነበሩ፡፡ የሰፈሩ ሰው ርግፍ አድርጎ
በተዋቸው ሰዓት እንኳን የማምሻ እጅ ስራ የተጠለፈባቸው ልብሶችን ትለብስ የነበረች
ሴት ሎዛ ብቻ ነበረች፡፡ እንደውም ለእኔም ከማምሻ የገዛችውን አንድ የባህል ልብስ
ስጦታ ሰጥታኝ ነበር…ለብሸው ግን አላውቅም፡፡
።።።።።።።።።።።
ሎዛ ደውላ ሄይ አብርሽ… ከሥራ ስትወጣ እቤት እመጣለሁ፣ ጠብቀኝ አለችኝ፡፡
ከሥራ ስመለስ ቀድማኝ እኛ ቤት ደርሳ፣ የምትወደውን የጦስኝ ሻይ እየጠጣች ከእናቴ
ጋር ሲያወሩ ደረስኩ፡፡ እናቴ ፊት ብትስቅም ገና ሳያት እንዳኮረፈች ገብቶኝ ነበር፡፡
"ሙሽሪት” አልኩና በትከሻዬ ገፋ አድረጊያት ገባሁ፡፡ እናቴን ተሰናብታ ተያይዘን እንደወጣን፣ “ማምሻ ጋ አካሂደኝ አለችኝ፡፡

ለምን?

“ሚዜነቷ እንደቀረ ልነግራት!”

ቀረ እንዴ?” ዞር ብላ በብስጭት አይታኝ፣

“ደስ አለህ?” አለችኝ፡፡

“ለምን ደስ ይለኛል? …ግን አለ አይደል …”

በውስጤ ግን ደስ ብሎኝ ነበር፡፡ በትዝብት አይታኝ፣

በቃ ቀርቷል፡፡ አባባ ተዪው አለኝ፡፡ ማሚ አሳምናው መሆን አለበት፡፡ማንም ሰው ከጎኔ
አልቆመም፣ ደከመኝ” አለች፡፡ ስልችት ያላት ትመስል ነበር፡፡ ተያይዘን እነማምሻ ቤት
ስንደርስ፣ ማምሻ የዘመመችው የጭቃ ቤታቸው ጋር ተያይዛ ከላስቲክ እና ከቆርቆሮ
ተሠራች ማድ ቤት ውስጥ ከጭስ ጋር እየታገለች እንጀራ ስትጋግር አገኘናት፡፡
ከማድ ቤቷ አጎንብሳ ስትወጣና አይታን ፈገግ ስትል ዓይኔን ማሳረፊያ ሌላ ቦታ ፈለግሁ፡፡
የማይለመድ መልከ ጥፉነት ነው ያላት፡፡ መልከ ጥፉ ብቻ አይደለችም… የሆነ በቀለኛ አጋንንት
ፊቷን በአጉሊ መነጽር እያየ ትንሽ ሰው ሊስብ ይችላል ያለውን ነገር ሁሉ እየለቀመ ያፈራረሰው ነበር የሚመስለው፡፡ እኔ ነኝ ያለ ደራሲ ይቅርና ፎቶ አንሺ እራሱ የማምሻን መልከ ጥፉነት በበቂ ሁኔታ አሳይቶ መጨረስ የሚችል እስከማይመስለኝ፣ ፊታ እንደ አዲስ አስገረመኝ፡፡ ምን ይሳነዋል ልሥራው ካለ ይሠረዋል፤ ላበላሸው ካለ ያበላሸዋል እላለሁ ለራሴ::

ወደ ቤታቸው እየመራች አስገባችን፣ የቤቷ ውስጥ ካሰብኩት በላይ እጅግ ንጹሕና በሥርዓት የተዘጋጀ ነበር የማምሻ ዘመን ያለፈባቸው ጥልፎች እንደሙዚየም ከአልጋ እስከ ኩርሲ በሥርዓት ለብሰው ተቀምጠዋል
👍3
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሦስት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ


ለምን እንደሆነ ባይገባትም ሳታስበው! ሳትጠብቀው ከልቧ ወዳዋለች፣ ጭራው የማይያዝ፤ የማይጠመድ፧ከእጅ የማይገባ ጋማውን እያመስ የሚፈነጭ የዱር ፈረስ ነው የሆነባት።

ይህን እያወቀች የመጨረሻ ውሳኔዋ ላይ መድረሷ እብደት መሰላት፡፡ ገደል ግቢ' ብሎ ቢተዋትስ? “ኡፍ…” በረጅሙ ተነፈሰች፡፡

በወፍራሙ ቅቤ የቀባቸውን ዳቦ ያለርህራሄ ግምጥ አደረገችና
ከትኩሱ ወፍራም ቡና በረጅሙ ፉት አለችበት፡፡ ነፍሷ መለስ አለች፡፡

ከናትናኤል ጋር እንዴት እንደተገናኘች ስታስታውስ፤ ግንኙነታቸው ሲጀመር የነበራት ዓላማና የአሁኑን ስሜቷን ስታስብ ድንቅ ይላታል፡፡
ልታጠምደው ተዘጋጅታ ቀርባ እሷ ራሷ እንዴት ልትጠመድ እንደቻለች ጭራሽ አይገባትም ያደረገችውን ሁሉ የግል ጉዳይ ነው እያለች ራሷን ለማሳመን ብትታገልም ህሊናዋ ሊያርፍ አልቻለም
ቀድማ የዘረጋችውን መረብ ሳትሰበስብ ሌላ መረብ መጣሏ ለራሷም አስፈርቷታል።

ሶስና ባዘጋጀችው የልደት በአሏ ላይ ነበር ከናትናኤል ጋር የተዋወቁት አርፍዶ ነበር የመጣው:: ውስጥ እንደገባ በግራው
ያንጠለጠለ በስጦታ ወረጭት የተጠቀለለውን ለሶስና አቀብሎ ግራ
ጉንጫን ላይ ሳማትና ተያይዘው ወደ ውስጥ ዘለቁ፡፡ ዓይኗ የገባውና
ለይታ ያወቀችው ገና ከበር ነበር። መረቧን ጣለች፡፡ ቀጠን ብሎ ረዘም ያለ ነው ስልክክ ያለ ፊቱ ቅንድቦቹና ሽፋሽፍቶቹ
እንደጎርፍ በአገጩ ዙርያ ፏ ብሎ ግጥም ያለው ጥቁር ጺሙ በሩቅ ሳቧት።
.
“ሶስና እውነቷን ነው አሰበች እርብቃ ደስ የሚል ልጅ ላይ ነው የጣላት እግዜሩ አስጠሊታ ፍጡር ቢሆንም ኖሮ ገብሬልዬ!”

ሶስና ግራ እጁን ይዛ እየጎተተች ወደ እንግዳ መቀበያው ክፍል መሃል ወሰደችው፡፡ በክፍሉ ውስጥ የሚተራመሰው እንግዳ አይትያይም!
ሁሉም በቡድን በቡድን ጨዋታውን ያቀልጠዋል፡፡ ናትናኤል ብዙ የሚያውቀው ሰው ያለው አይመስልም፡፡ ቢሆንም የመደናገር ! ግራ የመጋባት መልክ አልታየበትም፡፡

ሶስና እጁን ይዛ እየጎተተች ኮጓደኞቿ ጋር ስታስተዋውቀው ዞሮ ዞሮ የመመጣው እሷውጋ መሆኑ ታስባትና ፈገግ አለች ርብቃ::

ኬክ ከተቆረሰ ሰኋላ ነበር የተዋወቁት፡፡

“ተዋወቃት:: ርብቃ ትባላለች፡፡ ጓደኛዬ ናት:: ርብቃ አብሬው ነው የምሠራው:: ናትናኤል ይባላል፡፡" አለች ሶስና አሁንም እጁን እየጎተተች አምጥታው፡፡

“ናትናኤል ግርማ፡፡” አላት እጁን ዘርግቶ፣ አስቂኝ ወሬ እንደሰማ ሁሉ ፈገግ ብሎ፡፡ በትክክል የተደረደሩ የሚያማምሩ ትናንሽ ነጫጭ ጥርሶች አሉት፡፡

“ርብቃ ዮሃንስ፡” እጇን ዘረጋችለት፡፡ ጠበት ኣድርጎ ጨበጣት፡፡

ሶስና ድንገት ወደ ጆሮዋ ጠጋ ተጠንቀቂ ታዲያ ዱርዬ ነው” አለችና “በሉ ተጫወቱ::” ብላቸው ከሰው መሃል ተደባልቃ ተሰወረች::

ዱርየው!” ይህ ነበር የምትፈልገው የማስጠንቀቂያ ቃል፡፡ ፈገግ አለች ርብቃ::

“ስምሽን ከዚህ በፊት የማውቀው መሰለኝ አላት ድንገት
“እ በሬድዮ ሰምተኸው ይሆናል ጋዜጠኛ ነኝ::” :
“አ! የአፍሪካ ምጣኔ ሀብት ላይ አላት እጇን ጠበቅ አድርጎ ጨብጦ፡፡

“አዎ፡፡” አለች ፈገግ ብላ ብሬድዮ የምታዘጋጀውን ፕሮግራም ስም
ያለስህተት በመጥራቱ ኮራ ብላ፡፡

“በጣም ነው የምጠላው እሱን ፕሮግራም::”

የሰማችውን ማመን አልቻለችም፡፡ እንደዚህ ዓይነት ድፍረት ሲያጋጥማት የመጀመሪያ ጊዜዋ ነበር፡፡ መልስ አልጠበቀችም እጇን ከእጁ ውስጥ መንጭቃ ማውጣት ፈለገች፡፡ ነገር ግን ትክ ብለው የሚያይዋት ዓይኖቹ አልሰበር፤ አፋታ አልሰጥ አሏት፡፡

'ብሽቅ' አለች በል፡፡

“ትዝ ይለኛል… በአንድ ወቅት የብዙሁን ፓርቲ ስርዓትና የኢኮኖሚ እድገት በአፍሪካ በሜል ርዕስ አንድ ተከታታይ ዝግጅት አቅርበሽ ነበር…መላቅጡ የጠፋው ዝግጅት ነበር።” አላት ናትናኤል፡፡ ርብቃ ንዴቷን ልትቋቋመው አልቻለችም፡፡

“ካልወደድከው ለምን ትከታተለዋለህ ታዲያ?" አለች ደርዝ ባለው ድምፅ፡፡

“ድምፅሽን ስለምወደው ይሆናል...? አለና ድንገት ከት ብሎ ሳቀ፡፡ወዲያው ኮስተር አለና “ስራዬ አፍሪካ አጠቃላይ ሁኔታ ጋር የሚያገናኘኝ ነው። ስለዚህ ወደድኩትም አልወደድኩትም ፕሮግራምሽ እንዲያመልጠኝ አልፈልግም:: በተለይ እንግዶች ጋብዘሽ ቃለ ምልልስ በምታደርጊበት ወቅት፡፡” አለ ከጎናቸው ካሰ ጠረረጴዛ ላይ ከተደረደሩት በመጠጥ ከተሞሉት ብርጭቆዎች ሁለቱን አንስቶ አንዱን እያሳለፈላት፡፡ “የሚሰማኝን በግልፅ በመናገሬ እንዳልተቀየምሽኝ እርግጠኛ ነኝ፡፡”

“እህእ...” ትከሻዋን ነቀነቀች፡፡ “ግድ የለኝም የፈለከውን ብትቀባጥር
ለማለት

የምታዘጋጂያቸው ፕሮግራሞች እንደተረዳሁት በአመዛኙ ለአፊሪካ ማንሰራራት ዋነኛ ተስፋ አድርገሽ የምትወስጂው በአፍሪካ አገሮች መሀል
ነው:: አገሮች በተናጠል ለሚያደርጉት ጥረት ቦታ የሰጠሽው አይመስለኝም።

ትክክል ነህ እውነቱ መራሪ ቢሆንም ልቀበለው ስለደፈርኩ ነው።አለች ርብቃ ለዘብ ብላ።

“ምንድን ነው እውነቱ?"

“የአፍሪካ አንድ ተስፋ የለሽ መሆናቸው ከገቡበት አዘቅት መቼም ቢሆን ሊወጡ አለመቻላቸው ተስፋ ያላት አንድ አፍሪካ ብቻ መሆኗ ነው እውነቱ::

“አልገባኝም!” አለ ናትናኤል ቅንድቦቹን አጠጋግቶ።

በአጭሩ በኔሬሬ አፍ እንደተባለው የአፍሪካ ነፃነት የሚገኘው በተዋሀደ እንቅስቃሴ ብቻ ነው::”

ጨርሽዋ!” አለ ናትናኤል ፈገግ ብሎ “ኔሪሪ ያለው ያንን ብቻ አይደለም'ኮ፡፡ ውህደቱ ሊጠናከር የሚችለው በኢኮኖሚያዊ መተባበር የግንኙነት መስመሮችን በማሻሻል በመጨረሻም በፖለቲካ ውህደት ነው መሰለኝ ያለው ኔሬሬ፡፡ ለዚህ ደግሞ እያንዳንዱ የአፍሪካ አገር በተናጠል የሚያደርገው ጥረት ዋጋ ሊሠጠው ይገባል፡፡
“የትኛው ይቅደም መሠለኝ ጥያቄው፡፡” አሀች ርብቃ በስሱ የገጠመቻቸውን ከንፈሮቿን አላቃ፡፡

“ከምኑና ከምኑ?" ጠየቃት ናትናኤል።
“ከኢኮኖሚው ትብብርና ከፖለቲካው ውህደት።”

ይህማ ግልፅ ነው:: የፖለቲካ ውህደት በኢኮኖሚና በሌሎችም ትብብሮች ላይ የሚገነባ : ነው፡፡ ስለዚህ ኢኮኖሚያዊ ትብብር ይቀድማል።”

“እንደ መጽሐፍ ከሆነ ልክ ነህ መሰለኝ፡፡ ኢኮኖሚያዊ ጥንካሬና ትብብር ለፖለቲካ
ውህደት አንድ መሰረት መሆኑ አያጠራጥርም ጥያቄው ግን መፅሐፍ ላይ የተፃፈው ሳይሰራ ሲቀርስ? የፓለቲካ አቋም ልዩነት በራሱ ለኢኮኖሚው ጥንካሬና ለትብብሩም እንቅፋት ሆኖ ሲገኝስ መድሃኒቱ ምን ይሆናል :: የሚለው ነው፡፡ በአፍሪካ የሚታየው ችግር ይህ ይመስለኛል፡፡
አተኩራ ተመለከተችው፡፡ “መልስልኝ እንጂ፡፡” አለች ናትናኤል ያመነታ
ሲመስላት:: .
“ያገባኛል! ይባኛል እርግጥ የፖለቲካ አለመጣጣም…" ናትናኤል እያመነታ ጀመረ፡፡

“አንዱ የአፍሪካ አገር አለመጣጠማቸው
ለወጭ አራዊቶች ቅጥረኛ እየሆነ የጎረቤቶቹኝ ሰላም ሲያውክስ ኢኮኖሚ ሲያደቅስ አልፎ ተርፎ በገዛ አፍሪካውያን ወንድሞቹ ላይ ጦር ሲሰብቅ
መድሐኒቱ ምን ይሆናል?የተማሩ የተመራመሩ ቅምጥል የአፍሪካ ልጆች አፍሪካ ጥቁር አፈር ሲገለማቸውስ? ነጭ አፈር ፍለጋ ሲዘምቱስ? ጋሻ መከታ መኩሪያ መመኪያ መሪዎቻቸውን፣ በአፍሪካ ቦሀቃ የጠለቁትን ሊጥ በስዊዝ ባንክ ካልጋገርነው ሲሉስ? ፖለቲካ መድህኒት መሆኑ ቀርቶ የነአለብላቢት ጭልፊት፣ የነጎርሶ አይጠግቡ፤ የነውጦ አይጠረቁ ጋሻ ጃግሬ አጋፋሪ ሲሆንስ? መድሀኒቱ ምን ይሆናል? መጽሐፉ እንደሚለው ትብብር ይሁን እፈጠጠችበት።

ይገባኛልኮ ችግሮች መኖራቸውማ ያለ ነገር ነው ግን አለ ናትናኤል፡፡

“በማን ጀርባ ላይ እየተጨፈረ ያለ ነገር ነው? ወንድም ወንድሙን እያስማማ ፧ ከነጭ ወል እየተጋባ፤ ወንድም ወንድሙን እየቸበቸብ ከባዕድ ጡጥ
👍3
#የወድያነሽ


#ክፍል_ሦስት


#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል

የጨቅላ ልጅ ቡጢ ያህል የፈጠጠው ቁርጭምጭሚቷ ተረከዝዋ በላይ የሚገኘው ወፍራም ወጣሪ ጅማቷ በኑሮ መጎዳትዋና መጎሳቆሏን በሚገባ ለማሳወቅ የቀረቡ አስረጂዎች ናቸው።
ከሳምንት በፊት እናቴና ወይዘሮ የውብዳር ሲነጋገሩ ካመጡልኝ አይቀር
ችግረኛዋንና ምንም ዘመድ የሌላትን የራባትንና እህል እህል ያሰኛትን ነው» ብላ
አደራ ያለቻቸው ትዝ አለኝና «ችግርንና እጦትን ረሃብንና እርዛትን ማስፈራርያ
እያደረገች ልትገዛት ፈልጋ ነው» በማለት መሪር ትዝብቴን ለራሴ አዋየሁት።
መላ ሰውነቴ በርኅራኄና በሃዘን ተነካ፡፡ ልቤ በትካዜ ሟሸሸች። በሥራ ብዛት
የተደቆስኩ ያህል ሕሊናዩ ዛለ፡፡

አዲሲቷ ሠራተኛ ያሳለፈችው ውራጅ ሕይወትና የዘቀጠ ኑሮ እስከ አጥንቷ ዘልቆ ታየኝ። ነገር ግን በእኔ ዕውቀትና በአጭር ጊዜ የምርምር ችሎታ
ገና በወጣትነቷ ለጨለመው ሕይወቷ አመርቂ ፍቺ አጣሁለት። ከዚያ ቀደም
ለማንም በዚያ ዐይነት አዘኔታና ልባዊ የስሜት ጭንቀት አንጎሌ ተብሰክስኮና
ተጠቦ አያውቅም፡፡

እናቴ የሠራተኛይቱን ሰውነትና ጠቅላላ ሁኔታ በመመልከት «ውይ! ምን በወጣኝ፡ ምን በደልኩዎት! ይቺማ በሽተኛ ናት፡. አልፈልግም» ሳትል በመቅረቷ በጣም ተገረምኩ፡፡

የውብነሽ አልጋዎቹን አንጥፋ ስትመለስ ልክ አራት ሰዓት ከሩብ ሆነ፡፡ እንግዳይቱ ሠራተኛ የየውብነሽን መምጣት ስታይ ጠንቀቅ ብላ በንቃት ቆመች።
ከእናቴ በታች አዛዥ መሆንዋን ማወቋ ነበር። የውብነሽ ያን አጠር ብሉ ከርደድ
ያለ ጸጉሯን በግራ እጅዋ ይዛ እያሻሽች ከተመለከተችኝ በኋላ «ተነጥፎልሃል
መተኛት ትችላለህ» አለችኝ፡፡ እጅዋን ወደ ኋላ መልሳ ከግድግዳው ጋር ተለጥቃ
ወደ ቆመችው ሠራተኛ ዘወር ብላ «አንቺም ዕቃ ቤት ውስጥ ከዚያ ከትልቁ
በርሜል አጠገብ አንጥፈሽ ተኚ» ብላ ለማሳየት ወደ ዕቃ ቤት ገባች።
ሠራተኛይቱ ተከትላ ስትገባ ንፋስ እንደሚያወዛውዛት መቃ ወገቧ ልምጥ ልምጥ ሲል ቀዳዳው ቀሚሷ ከወዲያ ወዲህ ተወናወነ፡፡

ቁጥጥር ለማድረግ የታዘዝኩ ይመስል ተከትያቸው ገባሁ፡፡ የውብነሽ
ግድግዳው ላይ ወደ ተንጠለጠለው አጎዛ እያመለከተች «ነገና ከነገ ወዲያ ሌላ
ምንጣፍ ፈልገን እስከምንሰጥሽ ድረስ ለዛሬው ያን አጐዛ እዚህ ወለሉ ላይ ጣል
አድርጊና ተኚ። አይዞሽ አትፍሪ፡ ትለምጃለሽ» አለቻት፡፡

ሠራተኛይቱ አጐዛውን ከተንጠለጠለበት ምስማር ላይ ተንጠራርታ አወረደችው:: አጐዛው መኻል ላይ ቁልቁል የተሸረከተ የሕፃን ጭንቅላት የሚያሾልክ ትልቅ ቀዳዳ አለ። ቀዳዳውን እንዳየሁ አንድ ነገር ትዝ አለኝ።
የቤታችን ዘበኛ የነበረው ዘለቀ በግ ሲገፍ ሳት ብሎት ቆዳውን በሹል ቢላዋ ስለ
ሽረከተው አባቴ በዚያች የተነሣ ከሥራ እንዳባረረው ታወሰኝ። ከውስጣዊ
ፍርሃትና ጭንቀት የተነሣ ያ ከሲታ ፊቷ ከመጠን በላይ ጠውልጐ ይብስኑ
ሕይወት አልባ መሰለ።

«እስኪ ትንሽ አራግፈው እለች የውብነሽ በፊቷ ላይ ጥርጣሬ እየታየ፡፡
ገና ሁለት ጊዜ መታ መታ እንዳደረገችው ያንጠለጠለችው እዛ እምልጧት
ወደቀ። አጐዛው ላይ የነበረው አቧራ በመጠኑ ቦነነ ።ደንግጥ እነሣችው::
የውብነሽ አቧራውን እየተጸየፈች እስኪ እንደገና ቀስ ብለሽ መታ መታ
አድርጊው» አለቻት፡፡ ሠራተኛይቱም ከእኛ ለመራቅ ያህል ወደ ኋላ ፈግፈግ ብላ
በወዙ በኩል ሦስት አራት ጊዜ መታታችው። ልሙ ኣቧራ ወርዶ እግሯን
አለበሰው፡፡ ዕቃ ቤቱ በአቧራ ቡናኝ ተሞላ እህቴ አፍና አፍንጫዋን በቀኝ እጇ
አፈነች። ሠራተኛይቱ የአቧራው መቡነን እኛን የሚያስቆጣን ስለ መሰላት ብናኙን
እፍ እያለችና በእጅዋ እያራገበች ለማራቅ ሞከረች። አጐዛውን ከትልቁ በርሜል
ሥር ጣል ካደረገችው በኋላ ዱር አማከለች የምታነጥፈውን አሮጌ ብርድ ልብስ አጣጥፋ አስተካከለችው፡፡ ጎንበስ ቀና ባለች ቁጥር ጉልበቷ ይንቋቋል። የውብነሽ ወደ እኔ ጠጋ ብላ ለምን ታሳፍራታለህ? ሂድ እንጂ እነጣጥፋ ትተኛበት አለችኝ፡፡ «አንድ ጊዜ እንዳይ ብዩ ነው እንጂ እሺ እሄዳለሁ» ብዬ ዐይኔን ወደ ወለሉ መለስኩት፡፡ በአሮጌ ቀሚስ የተጠቀለሉ ጨርቆች መኝታው መኻል ላይ ጣለች፡፡ ወዲያው ነጠልጠል ስታደርገው ቀደም ብዩ ካየኋቸው ይበልጥ በጣም የቆሸሹና የተቀዳደዱ ቀሚሶችና ጨርቆች ወጡ፡፡ ከሁሉም ጐላ ብሎ የሚታየው ግን እንድ ጠርዝ ጠርዙ የተሸነታተረ ዐመድማ ስስ ብርድ ልብስ ነበር፡፡

ተንበርክካ ቀሚሶችዋን ካጣጠፈች በኋላ ለትራስ እንዲሆኑ አንድ ላይ ሽበለለቻቸው፡፡ የእኔ ልብ በሥቃይ ታፍና በሃዘን ስትቀዘቅዝና ጅማቴ ሲኮማተር
ተሰማኝ፡፡ ጉንበስ ቀና ባለች ቀጥር በስተኋላዋ ያለው የቀሚሷ ትልትልና ቀዳዳ ያንን ሸካራ ገላዋን በከፊል ያሳያል። እኅቴ እነዚያን የተበታተኑ ልብሶች
እየተመለከተች «ለመሆኑ ይኸ ልብስሽ ተባይ የለበትም?» ብላ ጠየቀቻት።

በእንግድነት ኃፍረት የተሸበበው አፍዋ ዝምታን ማመቅ እንጂ ቃላት ማውጣት
ስላልሆነላት ዝም አለች፡፡ እንግዳይቱ ሠራተኛ ግን አሮጌውን ልብስ አንዴ
ወረቀት ከሽመለለችው በኋላ የእግርዋን ትቢያ ሳታራግፍ መኝታዋ ላይ
ተቀመጠች። የተጠቀለለውን ብርድ ልብስ ሳብ አድርጋ ጉልበቷን ሽፈነችው።
ተጣጥፈው በስተኋላዋ ለትራስነት የተጠቀለሉት ልብሶችዋ ማቃጠያ ውስጥ
ተከማችተው የተቃጠሉ ወረቀቶች ይመስላሉ። ግንጭሏ የታጠፈውን ጉልበቷን እስኪነካ ድረስ ካቀረቀረች በኋላ ቀሚሷን አወለቀች፡፡ ከላይኛው ቀሚሷ የባሰበትና በጣም ያረጀ የውስጥ ልብስ ብቅ አለ።

ትከሻዋ ላይ ያለው ማንገቻ ረዝሞ
በመቋጠሩ እብቱ የቄብ እንቁላል ያህላል። በእድፍ የተሰላው ልብሷ ምን ዐይነት ቀለም እንደ ነበረው አይለይም። ቀሚሷን ስታወልቅ ያንን ዐመድ መስሎ
የተጐሳቆለ ጸጉሯን ሸፍኖት የነበረው ሻሽ ከቀሚሷ ጋር ሾልኮ ዱብ አለ፡፡ አጉሯ
ወደ ፊትና ወደ ኋላ ተመነጫጨረ።አንዱ ዘለላ ጥምል ቀለም መሳይ አንገቷ
ላይ ተጥመልምሉ ወረደ። ጸጉሯ ላይ ነውር ነገር የታየበት ይመስል በጣም
ደነገጠች። ወዲያው እየተርበተበተች በዚያው በሻሽ ሸንከፍ አደረገችው። ብዙ
የኑሮ ጉስቁልና ስለ ደረሰባት የአፍላ ወጣትነቷ ጠይም ውበት ወደ ሸካራ
ጥቁረት ተለውጧል፡፡ እህቴ ያን የመሰለ ፀጉር በማየቷ በአድናቆት ተመስጣ
በውስጣዊ የቅናት ጸገግታ ተመለከተቻት:: እኔ ግን በጣም ስላሳዘነችኝ በትካዜ እንባ ባቀረሩ ዐይኖቼ ሁኔታዋን አጤንኩት። አሮጌውን የብርድ ልብስ ሳብ አድርጋ እስከ አጐጠጐጤዎቿ ካደረሰችው በኋላ ተኮራምታ ስትተኛ ጭብጥ አከለች።

የውብነሽ «ወንድም ጋሼ አንተ ብትፈልግ ቆመህ እደር፡ እኔ ምን በወጣኝ ነው» ብላ ጥላኝ ሄደች። እኔ ግን ያቺን ከፊት ለፊቴ ከበርሜል ሥር ከላይ አዳፋ ደርባ ከታች የቆሽሽ ልብስ አንጥፋ የተኛችውን ሴት ትክ ብዬ እያየሁ ሦስት ደቂቃ ያህል ቆምኩ፡፡ ለጊዜው አጥጋቢ ትርጉምና ምክንያት ያላገኘለት የሐሳብ ሞገድ አእምሮዬ ውስጥ ተነሣ፡፡ ልወጣ አቅራቢያ እንደ ራባት የውሻ ቡችላ በቀጭኗ ተንፍሳ ገልበጥ አለች። ከዚያም ምንም እንኳ የብርድ ልብሱን ዐልፌ ማየት ባልችልም እንቅስቃሴዋን ተከታተልኩ። እጅዋ ወደ ጀርባዋ ከዞረ በኋላ ከገላዋ ላይ የሚገለፈፍ ነገር ያለ ይመስል ጥፍሮቿ ያን ሲሰሙት ብቻ በድምፁ የሚያስታውቅ ሸካራ ጀርባዋን ማከክ ጀመሩ፡፡ ወዲያው ሥቃይና የስቅቅታ ፍርሃት የረመጠጣት ቀጭን ሳል ኃይሏን ወለሉ እየዋጠው ሁለት ጊዜ ተሰምታ እየሰለለች ወደመች፡፡ ከዚያ በኋላ ገመምተኛ ፀጥታ በመተካቱ መብራቱን አጥፍቼ ወጣሁ፡፡

አንጐሌ ውስጥ በቂ ኀዘናዊ ትርዒት አጭቄ ወደ መኝታ ቤቴ ገባሁ፡፡
የመጀመሪያው ቀን በዚህ ሁኔታ ተፈጽሞ ዘልዓለም ወደማይመለስበት የትዝታ
ክልል ገባ፡፡
👍4
#የተወጋ_ልብ


#ክፍል_ሦስት


#ድርሰት_በትክክል_ገና


ጌትነት አዲስ አበባ አውቶቡስ ተራ ደረሰ። በመርካቶ ትርምስ፣ በህዝቡ ግርግር፣ በመኪናው ብዛት፣ በከተማዋ ውበት በእጅጉ ተደነቀ፡፡ አቶ ዓለሙ በነገሩት መሰረት ሴቼንቶ አስቆመና ጳውሎስ ሆስፒታል” ብሎ ተሳፈረ። "ከሆስፒታሉ ዋና መግቢያ በር ፊት ለፊት ያለውን ቀጭን የእግር መንገድ ተከትለህ ጥቂት ስትራመድ በባህር ዛፍ የተከበበ ትልቅ
የመኖሪያ ግቢ ታገኛለህ ከሱ አጠገብ ደግሞ አንድ ትንሽ በሸንበቆ የታጠ
ረች ግቢ ታገኛለህ፡፡ እሷ የቶሎሳ ግቢ ነች ምንም አያሳስትህም፡፡ ምናልባት ካላወቅከው ደግሞ በዚህ ስልክ ቁጥር ጎረቤት ደውለህ ቶሎሳን ታስጠራዋለህ” በማለት ስልክ ቁጥር ሰጥተውት ነበር፡፡

አቶ ዓለሙ ከአስራ አምስት ቀን በኋላ ቅቤ ጭኜ ስለምሄድ አብረን እንሄዳለን ጠብቀኝ ብለውት ነበር፡፡ አስራ አምስት ቀን በጣም ረዝሞበት ሄጄ የዕድሌን ብሞክር ይሻላል ብሎ ቸኩሎ ነው ብቻውን የመጣው፡፡ ሴቼንቶው ጳውሎስ ሆስፒታል አጠገብ አወረደው። እንደተነገረው ከሆስፒታሉ ዋና መግቢያ በር ፊት ለፊት ቀጭኗን የእግር መንገድ ወዲያውኑ አገኛት፡፡ ደስ አለው፡፡ ትንሽ ውስጥ ውስጡን እንደተራመደ ደግሞ የተ
ባለውን በባህር ዛፍ የተከበበ ሰፊ ግቢ በርቀት ተመለከተ። በደስታ ልቡ
ፈነጠዘች፡፡ እየተቃረበ ሲመጣ ደግሞ የሸንበቆ አጥሩን በቅርብ ርቀት
አየው፡፡

"ልክ ነው ያለጥርጥር የቶሎሳ ቤት እሱ መሆን አለበት! ሰው መጠየቅም
አያስፈልገኝ" አለና በቀጥታ ሄዶ በሩን አንኳኳ። አዲስ አበባንና ቤቱን ከዚህ በፊት የሚያውቅ እንጂ ከባሌ ገጠር ከተማ ወጥቶ ለመጀመሪያ ጊዜ አዲስ አበባን የረገጠ ሰው አይመስልም ነበር። ሸዋዬ ነበረች የወጣችው፡፡ የቶሎሳ ባለቤት...ባሏ ስለ ጌትነት አጫውቷታል። በሩን ከፍታአንገቷን ብቅ እንዳደረገች ባየችው ነገር ልቧ ስንጥቅ አለባት፡፡ ለቅፅበት ወዳለፈ የአስር ዓመት ትዝታዋ ውስጥ ሰተት ብላ ገባች። በአፍላ የጉርምስና ዘመኗ ያ በፍቅር ያበደችለት ውሽማዋ ሃምሳ አለቃ አየለ ራሱ
አፈሩን አራግፎ የመጣ ነበር የመሰላት። ዛሬ መሆኑን አላወቀችም እንጂ ሰሞኑን የቶሎሳ ዘመድ ከባሌ እንደሚመጣ ግን ታውቅ ነበር፡፡

"ጌትነት የምትባለው ነህ አይደል?" ፈገግ ብላ ተውረገረገችና ስሙን ጠርታ ጨበጠችው።ጌትነት ራሱን ከማስተዋወቁ በፊት ስሙን ስትጠራው ተገረመ።
"አዎን ጌትነት ነኝ፡፡ የጋሽ ቶሎሳ ዘመድ ነኝ፡፡ ከባሌ ነው የመጣሁት" ራሱን በሚገባ አስተዋወቀ፡፡ "ቶሎሳ ስላንተ ስላጫወተኝ ነው ቶሎ ያወቅኩህ፡፡ በል ግባ ወደ ቤት" እሷ ቀደም ብላ እሱን ከኋላዋ አስከተለችው።

ሸዋዬ መልኳ የቀይ ዳማ ሲሆን ደልደል ያለው ሰውነትዋ ከማራኪ ዳሌዋ እና ከቁመትዋ ጋር በምጥን የተሰራ የደስ ደስ ያላት ዐይነ ግቡ ሴት ናት። ቶሎሳን ከማግባቷ በፊት በሴተኛ አዳሪነት የምትተዳደር ወንዶች የሚሻሙባት ጉብል ነበረች፡፡ ባሏ ቶሎሳ ከባሌ ኮብልሉ አዲስ
አበባ ከገባ በኋላ የመጨረሻ እንጀራው የሆነውን የልብስ ስፌት ስራ በመጀመር ማለፊያ የእለት ገቢ እያገኘ ሲመጣ ከሸዋዬ ጋር የጀመሩትን ትውውቅ በትዳር ትስስር አጠናክረውት በሚያገኘው ገቢ በፍቅርና በደስታ መኖር ከጀመሩ ሁለት አመት ሆኗቸዋል፡፡ ቶሎሳ ጌትነት የሚመጣበትን ቀን በእርግጠኛነት ባያውቅም ሰሞኑን ሊመጣ እንደሚችል ግን ግምት ነበረው፡፡ ለምሳ ቤቱ ሲገባ ጌትነትን ጉብ ብሎ ሲያገኘው አላመነም፡፡ በደስታ ሄዶ ጉንጩን እያገላበጠ ሳመው ከዚያም የዘመድ አዝማዱን የጋራ ሽንተረሩን የአራዊት የእንስሳቱን ታሪክ ሳይቀር በሰፊው አንስተው ሲጨዋወቱ ቆዩ። ቶሎሳ የኦሮምኛ ቋንቋ ተናጋሪ ቢሆንም ለጌትነት ሲል ተራራ የመውጣትን ያክል በሚከብደው የአማርኛ ቋንቋ ሊያዋራው ተገዶ ነበር፡፡ ከዚያም ስለ ሟቹ መኩሪያ አንስቶ ትንሽ ከተካከዙ በኋላ "ለመሆኑ ሽማጊሌ ሂንዴት ኖ?" በማለት ስለ አባቱ ጋዲሳ ጠየቀው።

"እንዴ! አባባ ጋዲሳ! በጣም ደህና ናቸው፡፡ ከሳቸው አንተ ሳታረጅ ትቀራለህ ጋሽ ቶሎሳ ?" ሲል ቀለደ ጌትነት።
“ኡነቲንኖ ጌቲነት ኢነሱኮ ቱኩስ ሆተት ቀማሚሳሉ። ሆተት ሀጢንት ጠንኪራል። ኤኛማ ሚን አላ? ሀንበሳ ሆተቲ ቢሎ ጠራ ሀረቄና በኢርድ ቢጥቢጥ በጠበጠች ኒቦቹ ፏፏቴ ሲም ሂንጂ ጢቂም ኤለም፡፡ ኒቦቹ ፏፏቴ
ሁሽቲ ኖ፡፡ ዚንቦቹ ፏፏቴ ማለት ኢሻላል፡፡ ማር ኤለም ኢርዲና ሱኳር ሰጠች ኡሃ ቢቻ! ሀንበሳ ሆተቲ ቢሎ ሞጋጊሶ ሀረቄ ሀንጀት ሊጣለች ኢንጂ ገልጊሎት ኤለም፡፡ ኡሳን በየቀኑ ቀማሚሶ ሀረጀ!” ጌትነት በቶሎሳ አነጋገር ይስቃል።

"ኦሮጊቷስ ሂንዴት ነች ባኪ?" አሁን ደግሞ ስለ እናቱ ነው ቶሎሳ ጠይቀው።
"እንዴ እማማ እቴነሽ?ያቺ የቁርጥማት በሽታቸው አልፎ አልፎ እየተነሳች ታስቸግራቸዋለች እንጂ በጣም ደህና ናቸው፡፡ መቼም በየበአላቱ የምትልክላቸውን አዲስ ልብስ እየለበሱ በየጎረቤቱ እየዞሩ እየመረቁህና
እያስመረቁህ በደስታ ሲፈነጥዙ ነው የሚከርሙት፡፡ ዕድሜውን ያርዝምልኝ ልጄ ደርሶ ጦረኝ እያሉ። በሬሳ ውስጥ ጥሩ ስም ነው ያላህ ጋሽ ቶሎሳ!” በዚህ ጊዜ አቶ ቶሎሳ ከጥርሶቹ ፈሽረክ አለ፡፡ ፊቱ እንደ ፀሀይ አበራ። ጥቃቅን ዐይኖቹ ሳቁ... ደስ አለው።

ቶው ባኪ! ደሲ ሲሎት መሪቃሌች ጌቲነት ?!"
“ጋሽ ቶሎሳ እነሱ እኮ ብዙ አይጠብቁም፡፡ ትንሿን ነገር እንደ ትልቅ ነው የሚቆጥሩት ዋና ደስታቸው ልጄ አስታወሰኝ በሚል ነው" ቶሎሳ መልኩ ወደ ጥቁረት ያደላል። ፊቱ መጣጣ ሲሆን ዐይኖቹ ጉድ
ጓዶቻቸው ውስጥ ገብተው የተደበቁና ግንባሩ የተሸበሸበ ያለ እድሜው
ያረጀ የሚመስል የሰላሳ ስድስት አመት ሰው ነው። ሰዎች ወሬ ሲያወሩለት" ቶሌ ኢኮ?" ማለት ይወዳል።“እሺ እባክህ?” እንደማለት። በዚህ ሁኔታ ሲጨዋወቱ ቆይተው ምሳቸውን ከበሉ በኋላ ሸዋዬ ያፈላችላቸውን ቡና መጠጣት ጀመሩ፡፡ቶሎሳ ወደ ስራው ተመልሶ መሄድ አልፈ
ለገም፡፡ ይልቁንም ከጌትነት ጋር ወጣ ብሎ መዝናናት ነው ያሰኘው። ቡናውን ጠጥተው ከጨረሱ በኋላ "ሸዋዬ ኮ!" አላት።ሁሌም ሊያቆላምጣት ሲፈልግ እንደሚለው ዐይን ዐይኖቿን በፍቅር እያየ፡፡ "የኔ ሸዋዬ" ማለቱ ነው፡፡ ቀና ብላ በነዚያ በሚያባብሉ ዐይኖቿ አየችው።

“ቲኒሽ ዞር..ዞር.ሀዲርጌ ሰፈሩን ሀሳዪቼ መጣሉ” ጌትነት እንዲሰማ በዚያው በተሰባበረ አማርኛ እያዋራትና ከወደኋላዋ መጥቶ በእነዚያ ጥቃቅን ዐይኖቹ መቀመጫዋን በፍቅር እያየ ነገራት።
“በሉ እንዳታመሹ” አለች ንቅሳታሚ ሽዋዬ፡፡ በዚያ አረግራጊ ዳሌዋ ትንሽ
ወዝወዝ እያለችና የቡና ጀበናውን ለማንሳት እያጎነበሰች።

"ሀናመሺም ቶሎ ኖ ሚኒመጣ ሽዉ.ኮ ጎንበስ ስትል አጭሩ ቀሚስ ወለል ካደረገው ውብ ጭኖቿ ላይ ዐይኖቹ በስስት ተተክለው እየተንከራተቱ፡፡ ጌትነት ዐይኖቹን ዘወር አደረገ፡፡ ተያይዘው ወጡ...
“ና ሂስቲ ኢዚ ቲኒሽ ኢረፍት ኢናዲርገው" ጠጅ ቤት ከመሄድ ይልቅ ለጌትነት ክብር ሲል የመረጠውን ግሮሰሪ በጣቱ ጠቆመውና ተያይዘው ገቡ፡፡
"ኢስቲ ባኪ ሁለት ቀዘቀዘ ቢራ አመጣ!" አለ ቶሎሳ ለአስተናጋጁ፡፡
"እኔ ቢራ አልጠጣም ጋሽ ቶሎሳ !" አለ ጌትነት፡
" ባኪ ጠጣ ቢራኮ ገቢሲ ኖ፡፡ ጠላ ማለቲ ኖ" ሊያግባባው ሞከረ።
“ጋሽ ቶሎሳ ሙት!አልጠጣም፡፡ ለኔ ለስላሳ ይምጣልኝ" አስተናጋጁን
ለስላሳ እንዲያመጣለት ጠየቀው። ከዚያም ለጌትነት ኮካ ለቶሎሳ ደግሞ
ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ ተከፈተላቸው፡፡
“በጨቅጫቆ ሊቡን ደረቀ ኢስቲ ሆደ ቁም ነገሩ ጊባና ሲላንተ ጉዳይ ሚኒነጋገሮ" ጌትነት ይሄንን ርዕስ ጉዳይ በናፍቆት ሲጠባበቀው የነበረ በመሆኑ ደስ አለው። ሳያንገራግር ወደ ጉዳዩ በቀጥታ ገባ፡፡
“እንደምታውቀው አባባ ከሞተ በኋላ
👍31
#ምንትዋብ


#ክፍል_ሦስት


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ


...“ኸንጉሥ እጅ እንዴት እናመልጣለን?...”
ኢሳያስ፣ የሰማት ይመስል ወደ ጉዳዩ መግባት ፈለገ። አንዴ
ዮልያናንና እንኰዬን ሌላ ጊዜ ደግሞ ግራዝማችን ዐይኑን ተክሎ
ተመለከተ። ፊቱን ወደ ዮልያና አዞረና ፈገግታ ለገሣቸው።

ዮልያና የሆነ ነገር ሊነግረኝ ነው ብለው ጠረጠሩ፤ ለመስማት ጓጉ።

“እመቤቴ... ዋናው የመጣንበት ጉዳይ...” ብሎ እንደገና ሁሉንም
ተመለከተ። ቀጠለና፣ “እመቤቴ... ዋናው የመጣንበት ጉዳይ... ጃንሆይ...በተለይም እኔን ልከውኝ ነው። እርሶ እንዳሳደጓት ስላወቁ የልዥ ልዥዎን እጅ ስለፈለጉ እኼን ለማብሰር ነው የመጣን። ቅድም ግቢው መግቢያ ላይ ልዣችሁ መሬት ላይ ጦር ሲተከል አይታ፣ ደንግጣ ነው መሰል፣ ኸተቀመጠችበት ተነሣች። ለበጎ እንደመጣን ንጉሥ እጅ ሲጠይቅ እንደሱ መሆኑን ሳታውቅ ቀርታ” አለ።

ወለተጊዮርጊስ አመዷ ቡን አለ፤ ሰማይ ምድሩ ዞረባት። ንጉሡ?
እንዴ ንጉሡ የኔን እጅ ሊጠይቁ? እንዴት ሁኖ አለች። እንግዶቹ የሷን
እጅ ሊጠይቁ እንደመጡ ደመነፍሷ ቢነግራትም ለንጉሥ ሚስትነት መሆኑ ግን ከግምት በላይ ሆነባት፤ ተደናገጠች፤ ተርበተበተች፤ ፊቷ የበሰለ ቲማቲም መሰለ፤ ጉንጮቿ ተቃጠሉ። ዐይኖቿን ጨፍና ራሷን
ነቀነቀች፤ ሊሆን አይችልም በሚል መልክ። አንዴ በኔና በጥላዬ
ማይመጣ የለም ማለት ነው? እንባ እንባ አላት። የምታስበው ጠፋት፣ ጭንቅላቷ ባዶ ሆኖ ተሰማት። ጣሪያው ላይ አፈጠጠች- ለዚህ አስደናቂ
ለሆነባት ጉዳይ መልስ ይሰጣት ይመስል። አያቷም በሰሙት ነገር ቢደናገጡም ስሜታቸውን ሰብሰብ አድርገው፣
“እኔ ላሳድጋት እንጂ የወለዱ እኮ እነሱ ናቸው” አሉ፣ መብረቅ
የመታቸው ያህል ድርቅ ብለው የተቀመጡትን ልጃቸውንና ግራዝማችን በአገጫቸው እያመለከቱ። “እነሱ ናቸው መጠየቅ ያለባቸው” አሉ፣
ራሳቸውን እየነቀነቁ።

ኢሳያስ፣ “ርግጥ ነው። የጃንሆይም ፍላጎት ያ ነው። ኻለነሱማ እንዴት ይሆናል? ለመቤቴም ለግራማችም ነው ጥያቄው የቀረበ። እመቤቴ..
ግራማች... ዛዲያ ምን ታስባላችሁ?” አለ። ንጉሥ ልጃችሁን ስጡኝ ሲል ለማንም ቢሆን ብስራት ነው የሚል ቃና ድምጹ ላይ አክሎበት።እመቤት እንኰዬንና ግራዝማች መንበርን በተራ ተመለከተ። የዮልያናን
ቅሬታ ያዘለ አነጋገር ማርገብ ችሎም እንደሆን ፊቱን መለስ አድርጎ አያቸው።

ዮልያና ግን ሐሳባቸው ሌላጋ ከንፏል። ከዓመታት በፊት አንድ
ሌሊት አይተውት የነበረውና ምንጊዜም ቢሆን ሲያስደንቃቸውና ላገኙት ሁሉ ሲያወሩት የነበረው ሕልማቸው ትዝ ብሏቸዋል።

ያን ሌሊት፣ እንደወትሯቸው ጸሎት አድርሰው ከተኙ በኋላ፣ ፀሐይ
ቤታቸው ሰተት ብላ ገብታ ተጎናጽፈዋት ተኝተው አዩ። ከእንቅልፋቸው ብንን ብለው ነቅተው ተቀመጡ። ባዩት ሕልም ተደነቁ። ጠሐይ ቤቴ የገባችው አለነገር ማዶል። ጠሐይ መሪ ነው፤ ብርሃን ነው ይላሉ፡፡
አገር ብርሃን ትሆናለች ማለት ነው። ግና እንዴት? አሉ፤ ለራሳቸው።

የሕልማቸውን ትርጉም ለማወቅ ተመራመሩ። መቸም አለምኸኛት
እንዲህ ያለ እልም አላሳየኝም፡፡ አንድ ነገር ቢኖር ነው። እስቲ ነገ
ጠዋት እኛ መነኩሴ ዘንድ ኸጀ ሚሉትን ሰማለሁ። አይ የነእንኰዬ
አባት በኖሩ። እሳቸው እኮ ኸኔ የተሻለ እልም መፍታት ይችላሉ እያሉ ሲገላበጡ አደሩ። እንቅልፍ ባይጠግቡም፣ ማለዳ ከመኝታቸው ተነሡ።ውዳሴ ማርያማቸውንና ዳዊታቸውን ደግመው መነኩሴውጋ ለመሄድ
ሲዘገጃጁ የደስ ደስ ስሜት አቅበጠበጣቸው። ቁርስ ላድርግ ሳይሉ አሽከር አስከትለው ወጡ።
መነኩሴው ወፍታ ጊዮርጊስ ግቢ ውስጥ ጥድ ስር ተቀምጠው
መቁጠሪያ ይዘው ይጸልያሉ። ዮልያና ወደቤተክርስቲያኑ ሄደው
ከተሳለሙ በኋላ፣ መነኩሴው ጸሎታቸውን እስኪጨርሱ ድረስ ፈንጠር ብለው ድንጋይ ላይ ተቀመጡ። መነኩሴው ጸሎታቸውን ሲጨርሱ፣
ለዮልያና እጅ ነሡ። ዮልያና ተነሥተው እጅ ነሥተው ሲቆሙ
እንዲቀመጡ መነኩሴው በምልክት ነገሯቸው።

ዮልያና ድጋሚ እጅ ነሥተው ጠጋ ብለው ተቀመጡ። ስለጤንነታቸው
ከጠያየቁ በኋላ፣ “ያው መቸም ኸርሶ ዘንድ ምመጣው አንድ ነገር
ሲገጥመኝ ነው። ዛሬ ስንኳ አንድ ዘመዴ እልም አይታ ሚፈታልኝ
ብትለኝ ነው የመጣሁት። ድቅድቅ ያለ ጨለማ ይመስለኛል አለች...
ጠሐይ ኸተኛሁበት ድረስ ገብታ ቤቴንና መላ ሰውነቴን አበራችው።
ኸያ በኋላ ጠሐይቱን ተጎናጽፌያት የተኛሁ ይመስለኛል ብላ ነገረችኝ።”

መነኩሴው በጥሞና ካዳመጡ በኋላ፣ “ብርሃን ሥልጣን ነው። እኼን እልም ያየች ሴት ንጉሥ ትወልዳለች” አሏቸው።
ዮልያና ደነገጡ። “እልሙን ያየችው ሴት ኸንግዲህ መውለድ
አትችልም። ዕድሜዋ አልፏል፤ የወር አበባም የላት” አሉ።

“ኸዘር ይፈጠማል። ኸልዥ ልዥም ይሆናል።”

ዮልያና በሐሳብ ከሄዱበት ተመለሱና እልሜ ገሀድ መሆኑ ነው። ድንቅ! የእዝጊሃር ፈቃድ ይፈጠም ብለው ልጃቸውን የጎንዮሽ ተመለከቱ። ወይዘሮ እንኰዬ ግን የቅድስት ወለተጴጥሮስን ንግርት
አስታውሰው እናታቸው እያይዋቸው መሆኑን ልብ አላሉም።

በአፄ ስሱንዮስ ዘመን የቆራጣ ገዳም እመምኔት የነበረችው ቅድስት ወለተጴጥሮስ መንገድ መሽቶባት ለአንድ ምሽት አያቶቻቸው ቤት ዐርፋለች። የቤቱ እመቤት ሌሊት ላይ ድንገት ምጥ ጸንቶባት ወደ በረት ተወስዳ፣ ሴቶች መቀነቻቸውን ወንዶች መታጠቂያቸውን ፈተው ሲጸልዩ፣ ወለተጴጥሮስም መቀነቷን ፈትታ ፊቷን ወደ ምስራቅዐመልሳ አጥብቃ ጸለየች። ሴቲቱም ወንድ ልጅ በደሕና ተገላገለች።
ወለተጴጥሮስ በማግስቱ መንገድ ከመጀመሯ በፊት፣ “ኸዝኸ እጣን ዘር መልካም ዝናው ሚነሣ ንጉሥ ይወለዳል። ንግሥቲቱም በሥራዋ ስሟ ሲወሳ ይኖራል። ኸዳር እዳርም አገሯን ታስከብራለች” ብላ ቋራን፣ “ምን ግዝየም አብቅይ፣ መልካም ፍሬ ይብቀልብሽ” ብላ ተሰናብታ ወጣች።

እረገኝ ንግሥቲቱ ወለቴ መሆኗ ነው። ንጉሡ ደሞ ኸሷ ሚወለደው ነው አሉ እንኰዬ።

ኢሳያስ “ምን ታስባላችሁ?” ለሚለው ጥያቄው መልስ ባለማግኘቱ ልጠይቅ አልጠይቅ እያለ ከራሱ ጋር እየተሟገተ ቆይቶ፣ “ዛዲያ ምን አሰባችሁ ግራማች?” አላቸው።
ግራዝማች መልስ መስጠት ፈልገው ምላሳቸው ተቆለፈ። “እ... እረ.. እንዳው...መቸም...” ድምፃቸው ተቆራረጠ፤ የጀመሩትን ለመጨረስ ቃል አጠራቸው።

ኢሳያስ ካቆመበት ቀጥሎ፣ “መቸም...” ብሎ ግራዝማችን አያቸው።
“መቸም ለልዥዎ ለንጉሥ ሚስትነት ኸመታጨት የበለጠ ዕድል ኸየት ይመጣል? የጐንደር ወይዛዝርት ሆኑ የጦቢያ የነገሥታት ዘሮች ሁሉ ያላገኙትን ዕድል እኮ ነው ያገኘች” አላቸው።
ዕድል? እንዴት ሁኖ ነው ዕድል ሚሆን? አለች ወለተጊዮርጊስ፣
እያየችው። ዞር ብላ አባቷን ተመለከተቻቸው። እሳቸው የጭንቀት ስሜት አጥብቆ የተሰማቸው ይመስላሉ። ግንባራቸው ላይ ቸፍ ያለው
ላብ ቁልቁል ሊወርድ ይጋበዛል። ሆዷ ውስጥ አንዳች ነገር ተላወሰ።
ግንባሯን ያራሰውን ላብ በእጅጌዋ ጫፍ አባበሰች።

ከበድ ያለ ፀጥታ ሰፈነ።

“ግራማች ዛዲያ ምን ያስባሉ?” አሉ፣ ከሁሉም ተለቅ ያሉት እንግዳ።

እንዳው ለነገሩ ጠየቁ እንጂ ግራዝማች ምርጫ እንደሌላቸው ያውቃሉ።ግራዝማች ግን በልባቸው ወይ አንተ የወፍታው አያልቅብህ፡፡ ያ ሁሉ ባላባት ዐይናማ ልዥህን እያለ ለራሱ ሆነ ለልዡ አማላጅ ሲልክ ሁነኝ ጋር አንድ ቀን እንታረቃለን፣ ልጄን ለልዥህ ብየ ሳበቃ እንዴት
👍12
#ሳቤላ


#ክፍል_ሦስት


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ

« ለምን አልሔድም ? ሰዎች ሲጠይቁኝ አጋጣሚ መሰበሩን እንግራቸዋለሁ።

ሚስዝ ቬን ከት ብላ ሣቀችባትና
«ሰዎች ቢጠይቁኝ!» አለች በማፌዝ ድምፅ የሳቤላን አባባል በመድገም «እነሱማ የሎርድ ማውንት እስቨርን ልጅ የጌጥ
ችግረኛ ናት ብለው ከማሽሟጠጥ አልፈው ምን ሊሉ ኖረዋል ብላ አሾፈችባት።

ሳቤላ ሣቅ ብላ ራሷን ነቀነቀችና «አልማዞቹን ባለፈው የዳንስ ምሽት አይተዋቸዋል » አለቻት ።

« ይኽን በደል በኔ ላይ አድርሰሽው ቢሆን ኖሮ ፍራንሲዝ ሌቪሰን» አለችው ባልቴቷ «ለአንድ ወር ሙሉ ከቤቴ አላስደርስህም ነበር ። ምንድነው ነገሩ …...…… ኤማ? የምትሔዱ ከሆነ አሁን ሒዱ ። ዳንሱ የሚጀመረው በአራት ሰዓት ነው " በኔ ዘመን በአንድ ሰዓት ነበር የምንሔድ ፡ ዛሬ ደግሞ ሌሊቱን ወደ ቀን መለወጥ ልማድ ሆኗል ። »

« ሣልሳዊ ጆርጅ ራቱን የበግና ያትክልት ቅቅል በአንድ ሰዓት ይበላበት በነበረበት ጊዜ አለ ለአያቱ ከሚሲዝ ቬን የተሻለ አክብሮት ያልነበረው ካፒቴን ። ይኽን እየተናገሩ ደረጃዎቹን ደግፎ ሊያሳፍራት ስለፈለገ ወደ ሳቤላ ዞር አለ እንዳሰበው ይዞ ወርዶ ከሠረገላው ሲያሳፍራት ሚሲዝ ቬን ግን ብቻዋን ወርደች። በዚህ ጊዜ ይባሱን ብግን ብላ ተናደደች ።

« ደኅና እደር » አለችው ።
«ደኅና እደሩ አልላችሁም እኔም እናንተ እንደ ደረሳችሁ ተከትዬ እደርሳለሁ» አላት "

« አልመጣም ብለኸኝም አልነበር?የወንደላጤዎች ድግስ ያላችሁ መስሎኝ »

« ብዬ ነበር ግን ሐሳቤን ለወጥኩ " በይ ለአሁኑ ደኅና ሁኝ ወይዘሮ ሳቤላ "»

« እስኪ አሁን አንዲት ብጣሽ የተማሪ ሐብል አድርገሽ ያየሽ ሁሎ ምን ትመስይው ይሆን ? » አለች ሚሲዝ ቬን መነዝነዟን በመቀጠል "

« እሱስ ምንም አልነበረም ሚስዝ ቬን ? እኔን ያሳዘነኝ የመስቀሌ
መሰበር ነው ። እናቴ ልትሞት ስትል ነበር ይህን መስቀል የሰጠችኝ " ጉዳት ከማይዶርስበት ቦታ በደንብ አስቀምጬ አንዳች ችግር ሲደርስብኝ ወይም የሒሳብ እርዳታ የሚያስፈልገው ጉዳይ ሲገጥመኝ እሱን እያየሁ የእናቴን ምክር ለማስታወስ በመሞከር እንድከተላቸው ነግራኝ ነበር " አሁን ግን ተሰበረብኝ ነገሩ ደስ አላለኝም " ገዱ አላማረኝም " »

በሠረገላው ውስጥ እንዳሉ የመንገዱ የጋዝ መብራት ሳቤላ ፊት ላይ ቦግ ብሎ ሲበራ ፊቷ በዕንባ እንደ ታጠበ ሚስዝ ቬን አየቻት » «አሁንም እንደገና ማልቀስ ጀመርሽ ? እኔ ልንገርሽ ! በለቅሶ ደም የለበሱ ዐይኖችሽን እያየሁ አንቺን ይዤ ከዳርት ፎርድ መስፍን ዘንድ መቅረብ አልችልም " ስለዚህ ለቅሶን የማታቆሚ ከሆነ
ሠረገላው ወደ ቤት ይዞሽ እንዲመለስ አድርጌ እኔ ብቻዬን እሔዳለሁ »

ሳቤላ በረጂሙ ተነፈሰችና ዐይኖችዋን አብሳ ዕንባዋን አደረቀች » « ስባሪዎቹን ማስቀጠል እችላለሁ " ለኔ ግን እንግዲህ ተመልሶ እንደ ዱሮው ሊሆንልኝ አይችልም»

«ለመሆኑ ስባሪዎቹንስ ከምን አዶረግሻቸው ? » አለቻት ሚስዝ ቬን በቁጣ «ይዣቸዋለሁ እኒህውና ኪስ ስለሌለኝ ነው» አለቻትና ከምኗ ላይ እንዳኖረችው
በእጅዋ አሳየቻት "

ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ከግብዣው ቦታ ደረሱ ሳቤላም ንዴቷን ረሳችጡ ፀሐይ መስለው የበሩት ክፍሎች ልብን የሚሰውር የሕልም ዓለም መስለው ታዩአት
ምክንያቱም ልቧ ግና በአፍለኝነቱ ነበርና የመርካት ልምድ አልነበራትም የገባችበት ቦታና ሁኔታ ብርቅና ድንቅ ሆነባት ከዚያ በድምቀቱና በውበቱ ከሰወረው አዳራሽ እንደ ገባች ይቀርብላት የነበረው የአክብሮት ሰላምታ ስታይ እጅ ስትነሣ በጆሮዋ ይንቆረቆሩ የነበሩትን የውዳሴ ቃላት ስትሰማ የተሰበረውን
መስቀል እንዴት አድርጋ ታስታውሰው !

« ታዲያስ » አለ አንድ የኦክስፎርድ ተማሪ ለቫልስ ተጨዋቾች ቦታ ለቆ ወደ
ግድግዳው እየተጠጋ «እንደዚህ ወደ መሰሉ ቦታዎች መምጣት ያቆምክ መስሎኝ ነበር " »

« አዎን ትቸው ነበር » አለ ሁለተኛዉ «አሁን ግን በማፈላለግ ላይ ስለሆንኩ ሳልወድ ተመለስኩባቸው እኔ መቸም እንደ. ዳንስ አዳራሽ የሚሰለች ነገር ያለ አይመስለኝም " »

« ምንድነው የምታፈላልገው ? »

« ሚስት ነዋ ! አባቴ እስካልተሻሻልኩና እስካልታረምኩ ድረስ ዕዳ የሚባል ነገር እንደማይከፍልልኝ ለኔም አንዲት ሽልንግ እንኳን እንደማይጥልልኝ ምሎ ተገዝቶ ገንዘብ ከልክሎኛል " አሁን ለመስተካከል የመጀመሪያ ደረጃ ብሎ ያመነበት
ሚስት ማግባት ስለሆነ የምትመስለኝን መምረጥ ይዣለሁ እንዳልተወው ማንም ከሚያስበው በላይ ዕዳ ውስጥ ተዘፍቄአለሁ ።

« ታዲያ አዲሲቱን ቆንጆ አታበም እንዴ ! »

« ማናት እሷ ? »

« ሳቤላ ሼን " »

« ለጥቆማህ በጣም አመሰግናለሁ» አለው «ግን ማንም ሰው ቢሆን ክብሩን የሚጠብቅ አማት እንዲኖረው ይፈልጋል " ሎርድ ዊልያምና እኔ ተመሳሳይ አመል ስለ አለን ከዜ ብዛት ልንጋጭ እንችላለን " »

« ሁሉ ነገር እኮ ተሟልቶ አይገኝም ልጂቱ በመልኳ መሰል የላትም ።
ያ ቀጣፊ ሌቪሰን ወደ አሷ ጠጋ ጠጋ ሲል አይቸዋለሁ እሱ ዶግሞ ሴቶችን በሚመለከት ረገድ የሚያቅተው ነገር ያለ አይመስለውም" »

« ታዲያ እኮ ብዙ ጊዜ እንዳሰበ ይሆንለታል " »

« እኔ አሱን ሰውዬ አጠላዋለሁ " ጫፉን ጥቅልል እያደረገ የያበጥረሙ ጸጉሩን የሚብለጨለት ጥርሶቹንና ነጫጭ እጆቹን እያየ ያለሱ ሰው ያለ አይመስለውም » ስለ ሰው ጉዳት ምንም ስሜት የለውም ለመሆኑ ያ ተዳፍኖ የቀረ
የሚስተር ቻርተሪዝ ጉዳይ ነገሩ እንዴት ሆነ ? »

« ማን ያውቀዋል ? ሌቪሰን ከነገሩ እንዶ ዐሣ ተሙለጭልጮ ወጣ " ሴቶቹም እሱ ከፈጸመው ጥፋት በሱ የደረሰበት በደል ይበልጣል ብለው ተከራከሩለት » ከሕዝቡም ሦስት አራተኛው አመናቸው " ይኸውልህ መጣ I የዊልያም ቬን ልጅም አብራው አለች " »

ሳቤላና ሌቬሰን እየቀረቡ መጡ " ስለ መስቀሉ በድንገት መሰበር እየደጋገመ ፀፀቱን ይገልጽላት ነበር " « እንግዲህ ተመልሶ እንደ ነበረው የሚሆን አይመስለኝም» አላት ቀስ ብሎ በጆሮዋ « መቼም uመኔን በሙሎ ልባL ኀን ስልጽ
ብኖር የምተካው አይመስለኝም "

መንፈስን እያነቃቃ የደስታ ስሜትን እየነካካ ከአእምሮ የሚገባው ረጋ ያለው ሥልተኛ አነጋገሩ ጆርን የሚያስደስት ልብን የሚያሳስት አደገኛ ነበር "
ሳቤላ ቀና ብላ ስትመለከተው ዐይኖቹ ከሷ ላይ ተተክለው ሲስለመለሙ አየቻቸው እንደዚያ ያለ ቋንቋ አጋጥሟት አያውቅም ነበርና እሶም ጉንጮቿ ተለዋወጡ
ዐይኖቿ ክድን አሉ ልትናገራቸው የነበሩት ቃላት ከከንፈሯ ደርሰው ጠፉባት "

« ሰውየው አጭበርባሪ ይመስላል» አለ መኮንኑ "

« ነውና " እኔ እንኳን ስለሱ አንድ ሁለት ነገሮች ዐውቃለሁ " አሁንም ይች ልጅ ቆንጆ ስለሆነች ለዝና ሲል ልቧን ያጠፋዋል " ከሷ ለሚቀበለው ስጦታ ግን ለመመለስና የሚያስበው ውለታ የለውም».....
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ዌስት ሊን የፋብሪካ ወይም የአንድ ካቴድራል ከተማ ወይም የክልሉ አስተዳደር ዋና ከተማ አይደለችም" ነገር ግን ምንም እንኳን በጥንታዊ ልማዱና ባህሏ ወደ ኋላ ቀረት ያለች ብትሆንም ራሷን በተለይ ደህና ከተማ አድርጋ ትቆጥራለች ለፓርላማ ሁለት እንደራሴዎችን ትወክላለች
👍21👎1
#ከቡስካ_በስተጀርባ
   #ድንግል_ውበት


#ክፍል_ሦስት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ


ሁለት ሳምንት አለፈው ካርለትና ከሎ የየራሳቸውን የጕዞ ዝግጅት ሲያደርጉ ሰነበቱ። ከሎ ሐመር ሲሄድ የሚያነባቸው ልብወለድና
ታሪክ ነክ የአማርኛ መጻሕፍት፣ መጽሔቶች፣ በእንግሊዝኛ የተጻፉ
ልብወለድና የሳይንስ መጻሕፍትን እየገዛ ከፊሉንም እየተዋሰ
አዘጋጀ"

በተለይም ካርለት ኮተቷ በዛ" በማስታወሻዋ በዝርዝር ከያዘችው
አስፈላጊ የምግብ ዓይነቶች የታሸገ የዓሣ፣ የአሳማ፣ የከብት ሥጋ የድንች የዱባ፣ ያጃ ሾርባI የፓፓያ፣ የብርቱካን፣ የአናናስ
ጭማቂ ኃይል ሰጪ ንጥረ ነገር የበዛበት ብስኩት ደረቅ ብስኩት የቆርቆሮ ቢራ ወዘተ ከመድኃኒ ዓይነትም ክሎሮኪን፣ ፓልዱሪን፣ ኒቫኩይን ለወባ መከላከያI ሌሎች፣ «አንቲባዮቲክስ» መድኃኒቶችንና የመጀመሪያ ሕክምና ኪት ኮዳክ ፊልሞችI ባትሪ
ድንጋዮችI ሶፍቶች ወዘተ. በአራት የፕላስቲh ሣጥኖች ደረደረች" ካኖንና ፔንታክስ ካሜራዋንና የተለያየ መጠን ያላቸውን ሌንሶች
በእጅ በሚንጠለጠለው ቦርሳዋ ካኪ ሱሪዎች፣ ካኔትራ፣ ውስጥ
ሱሪ ፎጣ፣ ጡት ማስያዣ፣ ስሊፒንግ ባግ፣ ግራጫ  መልክ ያለው ሹራብ በአየር የሚሞላና ሌላ ተጣጣፊ ፍራሽ፣ ሳሙና፣ ኦሞ፣
ከሁለት መቶ ሃምሳ ዓመት በፊት በሞዛርት የተቀነባበሩ የፒያኖ ሶናታና የፒያኖ ኮንቸቶ የቤቶቪን ሲንፎኒ ከሦስት ጊዜ በላይ
የወርቅ ዲስክ አሸናፊው ድምፃዊ የቢሊ ጆይል፤ ከሦስት መቶ ዓመት
በፊት የነበረውና የሲንፎኒ አባቱ የሃይደን እንዲሁም ሌሎቹን የባሮክ
ክላሲካል፣ ሮማንቲክና ዘመናዊ የሙዚቃ ካሴቶችን፣ ማስታወሻ፣
ብዕር መጻሕፍትና መጽሔቶች በአራት ማዕዘኑ የብረት ሣጥን
ውስጥ ከተተች" ለሽፍን ላንድ ክሩሰር ቶዮታ መኪናዋም በሁለቱም
ታንከር ነዳጅ ሞላች“ አምስት ጀሪካን ናፍጣም ለመጠባበቂያ ያዘች
ካርለት ለሦስት ወራት የሚያስፈልጋትን ቁሳቁስ ካሟላች በኋላ
ቀሪውን ዕቃዋንና ገንዘቧን ስቲቭ በሰጣት ክፍል ውስጥ
አስቀመጠች» ለአንዳንድ ወጪ ብላ የያዘችውን ሦስት ሺህ አምስት
መቶ የኢትዮጵያ ብርም በሹራቧ ውስጥ በሰፋችው ስውር ኪስ፣
አንገቷ ላይ በምታንጠለጥለው የጨርቅ ቦርሳና ብረት ሣጥኑ ውስጥ
አhፋፍላ ያዘች
ሰኞ ጠዋት ልክ ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ላይ አራት ኪሎ ሞቢሉ
ጎን ካለው ሱቅ በር ላይ በቀጠሯቸው ተገናኙu ካርለት ልጥፍ የኋላ
ኪስ ያለው ካኪ ሱሪ፣ ተረከዙ ፕላስቲክ የሆነ ሽፍን ባለማሰሪያ
ማ፣ ቡና ዓይነት ቲ–ሸርት ለብሳ፣ አንገቷ ላይ አነስ ያለ ነጭ ፎጣ
ጣል አድርጋ፣ ከመኪናው በመውረድ የከሎን «ዩኤስኤ» የሚል
ወስፋት የነፋው የሕፃን ሆድ መስሎ የተወጠረ ቦርሳ የኋላ በሩን ከፍታ
በዕቃ ከሞላው መኪና ውስጥ በአንድ በኩል ባለው ክፍት ቦታ
አስገባችና ወደ መኪናው ውስጥ ገቡ" ካርለት የውኃ ኮዳዋን፣ ዳቦ
የያዘ ላስቲኳን አቀረበችና ከከሎና እሷ መካከል ካለው የካሴት ሣጥን
የሞዛርትን ፒያኖ ሶናታ ወደ መኪናው ቴፕ አስገብታ ማስታወሻዋን
በማውጣት የተነሡበትን ሰዓት መዘገበች" ከዚያም ፈገግ ብላ
«መሄድ እንችላለን?» አለችው።

«ኢ ህ» አላት ከሎ፣ ዝግጁ መሆኑን አንገቱን በማወዛወዝ እየገለጸ። ካርለት፣ ቀኝ እጇን ማርሹ ላይ በማስቀመጥ፣ በግራ እግሯ ፍሪሲዮኑን እረግጣ፣ የመኪናውን መስተዋት አየትየት በማድረግ
በአራት ኪሎው የድል ሐውልት ወደ ቀኝ ታጥፈው፣ በኢዮቤልዩ ቤተ መንግሥት አድርገው ቁልቁል ወደ መስቀል አደባባይ ወረዱ።
ከዚያም በደብረ ዘይት መንገድ ወደ ቃሊቲ፣ አቃቂ፣ዱከም ተጕዘው ደብረ ዘይት ከተማ ሲደርሱ ወደ ግራ ታጥፈው ሁለት ኪሎ ሜትር በመጓዝ ዠመኪናዋን ሆራ ሆቴል አቁመው ለቁርስ ወደ ውስጥ ገቡ" በስተጀርባ፣ ከሐይቁ ትይዩ የመርከብ ላይ መናፈሻ ከሚመስለው ስፍራ ሆነው የተለያዩና ቱር ቱር እያሉ በመዘመር
የሚበሩ አዕዋፍን እያዩ ቁርሳቸውን ተመግበው ወጡ" ካርለትና ከሎ
ሆራ በሞጆ ታጥፈው፣ ወደ ሻሸመኔ ጕዟቸውን ተያያዙ“ ካርለት፣በመንገዱ ግራና ቀኝ የግራር፣ የጥድ፣ የኮሶ፣ የዝግባ...ዛፎችንና
የተለያዩ ቀለም ያላቸውን እፅዋት እያየች፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ከሚኙት ከሃያ በላይ አዕዋፋት ውስጥ የምታያቸውን በመልክና
በቅርፃቸው ለማወቅ በጆን ጂ ዊሊያምስና በኖርማን አርሎት የተጻፈውን የአዕዋፍ ምስል፣ ቀለም ባሕርይና የሚገኙበትን አካባቢ እያየች ተጓዙና ለምሳ በስምጥ ሸለቆ ካሉት ሐይቆችና የመናፈሻ ቦታዎች አንዱ ወደሆነው ወደ ላንጋኖ ከመንገዱ ወደ ግራ ታጥፈው ገቡ"

ላንጋኖ ሆቴል ምግብ ቤት ብዙ የውጪ ሀገር ዜጎች፣ አፍሪቃውያንና ኢትዮጵያውያን ክብ እየሠሩ በመጫወት ይመገባሉ። ከሆቴሉ ውጪ በቀላል ድንኳን ጥግ፣ በዋና ውስጥ ሱሪና ጡት ማስያዣ
ሆነው የፀሐይ ክሬም ሰውነታቸውን የሚቀቡና ሐይቁ ዳር ለዳር
የሚዋኙ ሴትና ወንዶች ይታያሉ" ጥቁርና ነጭ ሕፃናትም በመዋኛ
ፕላስቲክ ውኃውን በማንቦራጨቅ እየተንጫጩ ይጫወታሉ ከሎና ካርለት ከምግብ ቤቱ ትይዩ የፀሐይ ጃንጥላው ውስጥ
ተቀምጠው ቡናቸውን ሲጎነጩ ቆዩና ካርለት የሐይቁን ዳር ትርምስ
አሸጋግራ ስትቃኝ ቆይታ፣ «ሐይቅ ዳር ስሆን እረካለሁI አገሬ ውስጥ ከጓደኞቼና ቤተሰቦቼ ጋር ያለሁ ስለሚመስለኝ የደስታ ስሜት ይሰማኛል" በአውሮፓ፣ ብዙዎች መዝናኛዎች የሚገኙት ባሕር ዳርቻ ነው" ብቻ...» ካርለት ከሎ ሆራን በጎን ተመለከተችው“


«ኢ ህ» አላት እግሮቹን ወደፊት በመዘርጋት ሰውነቱን ለጥጦ" ካርለት የከሎ ሆራ ጠባይ ደንቋታል ግን አልከፋትም" በቀላሉ ከምትግባባቸው ሰዎች ይልቅ አስቸጋሪ ባሕርይ ያላቸውን ታከብራለች" ሁሉም ሰው ሊረዳው የሚችል ባሕርይ ያላቸው ሰዎች ለሷ አያረኳትም" እረቀቅ ያለ ባሕርይ ያላቸውን ግን አእምሮዋን
አስደንሳ መላ ፈጥራ፣ የተለያየ ስልት በመጠቀም እንደ ግል ሬዲዮና መከፈት መዝጋት እንደ መቻል
የምትረካበት ነገር የለም።
ለዚህም ካርለት «ዘመናችን የሚርጠው ልዩና ውስብስብ አስተሳሰብ ያላቸውን ነው" ምክንያቱም የነገው ፈጠራና ብሩህ
ሕልም ህላዊነት በመዳፋቸው መሃል ያለው ከእነዚህ ዓይነት ግራ
አጋቢ ባሕርይ ካላቸው ሰዎች ነው» ብላ ታምናለች።

ከሎ ቅንና ተባባሪ ሰው መሆኑን፣ ነገር ግን ይህን ባሕሪውን የሚገልጽ የቃላት ድርደራ ችሎታ የሚጎድለው መሆኑን ተገንዝባለች" ካርለት ከሎን የተለያዩ ነገሮችን እያወራች
እየጠየቀች የቱ እንደሚያስደስተው፣ የቱ አፍንጫውን እንደሚ
ያስነፋውና ጥንካሬውን ከደካማ ጎኑ ለመለየት ምርምሯን ስለ ቀጠለች
አንድ ወጥ በሆነው የሥውር ባሕርይው ዋሻ ለመግባት ትልቁ
የድንጋይ መዝጊያ ማንቀሳቀስ ጀምራለች።

«አዎ የከሎ ባሕርይ ራሱ መጠናት የሚገባው ነው" እሱን ለማጥናት ግን አስፈላጊውን ቁልፍ ማዘጋጀት አለብኝ» አለች
ካርለት፣ ከሻሸመኔ ከተማ ወጥታ የአርባ ምንጭን መንገድ ስትይዝ"
ከሻሸመኔ ትንሽ ራቅ ብለው የአስፋልቱ ጐዳና አልቆ ኮረኮንቹን መንገድ ሲጀምሩ ግን መኪናዋ እየተገጨች ስትንሰጠሰጥና ከፊት
ለፊቷ ያሉትን መኪናዎች ስታልፍና ከእሷ ተቃራኒ የሚያልፉት መኪናዎች የሚያነሡት አቧራ መኪናዋ ውስጥ እየገባ ማፈን
ሲጀምር፣ ካርለት መኪናዋን አቁማ፣ ጸጕሯን በመሸብለል፣ ቆብ
ደፋችበትና መኪናዋን በማንቀሳቀስ ከመሪው ጋር መታገል ጀመረች"
👍20🔥1
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_ሦስት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ


ፀጥታውን አዳመጠው፡ ይንጫጫል: ስልቱ ግን ጣፈጠው።እንደገና ጆሮውን አቁሞ ሰማ... “በዚህ ትርምስ በሞላበት ዓለም
ምናለ ፀጥታም በካሴት ታትሞ ቢሸጥ?“ ተፈላሰፈ።

ኤርቦሬ ማሕበረሰብ ውስጥ እያለ ህይወቱ ቀለል ያለ
ይመስላል። በእርግጥ ይበላል: ልብስ ግን አልነበረውም:

...ይህን ግዙልኝ መጫወቻ አምጡልኝ ኬክ ቤት
ውሰዱኝ..." ብሎ አላስቸገረም ወይንም አልተቸገረም:: እራሱን
ከጓደኞቹ ጋር በዚያ የእንቦቀቅላነት ዘመኑ አላወዳደረም: ሕይወት
ተመሳሳይ ነበረች። ራቁት ሆኖ አፈር ረጭቶ አቧራ አቡኖ ከበግና ፍየል ግልገሉች ጋር ሮጦ ነበር የኖረው።

“ተማር ህይወትህን ለውጥ ለወገንሀ ጠቃሚ ዜጋ ሁን..." ብለው ከባሕሩ አስወጡት: ያኔ እንደ ዓሣ ጨነቀው:: ግን መኖር ቻለ አዲስ ንድፈ ሃሳብን አወቀ።
አወቀ።ህልሙ ግን እውነት
አልሆነለትም ማወቅና መተግበር አራምባና ቆቦ ' መሆናቸውን ተረዳ። ተቀምጦ ታሪክ በሚያወራ ተማርሁ' ብሎ ብርጭቆ
ጨብጦ የካምፓስ ሕይወት" እያለ ከሚቦተልከው ራሱን አርቆ
ለሃገሩ ለአፍሪካ ለዓለም ለዚች ፕላኔት ቤዛ የመሆን ህልሙ አስኳሉ እንደወጣ እንቁላል ኮፈኑ ብቻ ቀረ። ኮፈኑ ይለብሳል ኮፈኑ
ያጌጣል ኮፈኑ ያዝናናል... ህሊናው ግን አፍሮ ተደብቋል።

የልመና እጆች ሲበራከቱ ማጣት ሲንሰራፋ ጥላቻና በቀል ለዚህ ማዳበሪያ እየሆነ አለመግባባትን ሲያበቅሉ እያዬ ሀዝቡን
እሚያስተምረው ስለ አተሞች በአይን ስለማይታዩት ሕዋሳት ነው::
የወገኑን ህይወት ለማይቀይረው ትምህርት ለዘመናት ባዘነ  ትምህርት ግን ማውራትን እንጂ ጥጃ መጠበቅን በጦር መሬት
ወግቶ በቆሉ መዝራትን አስረሳው። እውቀት ፈጠራ የነጮቹ ወሬ መናቆር የእኛ መሆኑን አምኖ እነሱ ሰርተው ላመጡት ግኝት ዜማ ይሰጡትና ከጓደኞቹ ጋር ሆኖ እያጨበጨበ እንዲዘምር ይነግሩታል።
እና! የወር ደመወዝ የሚያገኝበትን ሲዘምር ይውላል። ከዚያ ብርጭቆ
ውስጥ ተጠቅልሉ ያመሻል። ሲሞቀው እንደ ህፃን እየተወለጋገደ
ሲኮላተፍ ይተኛል።

ነገ ግን ያው ነች:: እሱም ነገን ለውጥ እንደሌላት ያውቃል፡ በትናንት የተዘራ በዛሬ የተኮተኮተ... የለም፡ እና ከነገ እንዴት ፍሬ
ይጠበቅ!

በእርግጥ በህፃንነት ዘመኑ ማንም ሳያስተምረው ያወቀው ማልቀስን ነው: ከዚያ መሰል ተፈጥሯዊ ክስተቶች ተጨማሪ ግን
ሁሉንም ነገር ለማወቅ ህሊናው ሲፈልግ እጆቹ ሲወራጩ እግሩ ሲኳትን... የእንቦቀቅላነት ዘመኑን ያሳለፈው በደስታ ነበር። ከሁለት በላይ በሆነ ባህል ውስጥ ተሰንቅሮ ይህን አትይ ያንን አትንካ እንደዚህ አትናገር ያ መጥፎ ነው ያስቀጣል ያሳስራል... እየተባለ በአዳዲስ ሃሣቦች ሲኮረኮም ሲገሰፅ ሲቆነጠጥ ኖረ:

ህሊናን የሚያዞር የህይወት ፈተና! የመፈቀርና የመጠላት እጣ የማግኘትና የማጣት የተንኮልና የጥላቻ... አንዱ እያጣደፈ
ሲያስቀምጠው ሌላው ሲያስኮፍሰው እንደ ፊኛ ሲነፋ ቱሽ ተደርጎ ሲጎድል ሕይወት ስትጥመው ስትመረው ያዝኩሽ ሲላት
ስትርቀው ራቅሽ ሲላት ቅርብ ነኝ እያለች ስትሸነግለው ኖረ።
ዛሬና ትናንት እንዲሁ በተስፋና ቅዠት አለፉ። ነገ ደግሞ አካሉ ያረጃል መንፈሱ ይደክማል ውበቱ ይረግፋል... ያኔ ይቆዝማል
ህይወት ግን ማዕበል አሳሯን እንደሚያሳያት ጀልባ እየዋዠቀች እንኳ የምትጥም ትሆንበታለች ህሊናው ሁሉም ያልፋል በሚል እምነት ቢታጨቅም የሚተማመንበት ያጣል መኖሩን ማሪጋገጥ
አይችልም ልቡ በፍቅር ቢጠማም ጥም መቁረጫውን አያገኝም።
መስታዋት የማያ ሰበቡ ይጠፋል... ከስዎች ጋር እንዳልናረ ሁሉ ያለፈ ህይወቱን ሲከልሰው ብቻውን ጡል ጡል እያለ መኖሩን ይረዳል። ይህን ሲያስብ ያሳላፈው ህይወት ጣምናው ይጠፋዋል።
ስለዚህ “መጥኔ... አይ ህይወት...” እያለ እየተትከነከነ ወደዚያ አቀበት
ይኳትናል  ወደ ሞት ሲረግጣት የኖረችው ምድር ስትውጠው እስትንፋሉ ሲቆም. ያኔ “...ይብላኝ ለቋሚ ( ሟችስ ጣጣውን ጨርሶ ወደ እውነተኛው ዓለም ሄዴ.. ተገላገለ” ይባላል። ይህም ግን
“ይባላል" ነው። ተዚያ ወዲያ ሕይወት የግል ሚስጥር ነች ለተጓዦች!

ሶራም ይህን ተራራ መውጣቱን ተያይዞታል: ጫፉ ዳመና  ውስጥ የገባው ተራራ ግን መንገድ አልባ እሾህ የበዛበት
የሚያንሸራትተው የበረከተ... አስፈሪ ነው:: ያለፉበትን ሲያዩት ያስፈራል
ገና የሚወጡት ደግሞ ከማስፈራራትም ያስጨንቃል: በዚያ ላይ የሚፈራረቀው ብርሐንና ጨለማ ቆፈንና ሙቀት. ያታከታል።

መፅናኛው ግን ብዙ ነው: ጠኔ ያስቸገረው አካለ ስንኩሉ የእለት ጉርሱ ያጣው በሽተኛው ያን ሲያዘይ የሙከራ ጥረቱ
ይጨምራል... ካሰበው ቦታ ስለመድረሱ ግን ማረጋገጫ ያለው የለም።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ህሊናው አካሉን እየቧጨረ እየታገለ... እረፍት ሲነሳው
እንደቆየ የቤቱ በር ተንኳኳ።

“ይግቡ...” አለ በታከተ ድምፅ ቅላፄ። ደሞ ማን ይሆን እንደ መርዶ ነጋሪ በጠዋቱ የመጣብኝ' እያለ በር በሩን እያዬ በሩ በዝግታ ሲጢጥ…” ብሉ ሲከፈት ተረከዘ ሎሚ ከበሩ ግርጌ
ተመለከተ።

ማናት...?” አለ ግራ እየገባው ከዚያ ከተጋደመበት ቀና
ብሎ አይኑን እንደ አበያ በሬ አፍጥጦ ጆሮውን እንደ ጥንቸል ቀሰረ:

ግቢ... ማን ልበል?"  ያላሰበውን ዓረፍተ  ነገር ከራሱ አንደበት ሲወጣ ተስማው። እንግዳዋ ረጋ ብላ ወደ ውስጥ ዘለቀች።

“ይቅርታ!... ካለቀጠሮ በመምጣቴ...” አለችው የቤቱ ብርሃን ደብዘዝ ስላለባት አይኖችዋን ፈጠጥ አድርጋ፡

"ምንም አይደለም” ብሎ ፈገግ አለ፡ ማንነቷን ለማወቅ ህሊናውን ውለዳት ቢለውም ሊያገኛት ሊያውቃት አልቻለም።
ከመቀመጫው ተነሳና ወንበር ቀረብ አድርጎላት! “እዚህ ላይ አረፍ በያ! እያለ እሁንም ሊያስታውሳት ሞከረ: መልኳን ከዚህ በፊት
ያየው መሰለው። የት ነው የማውቃት?' ጠየቀ ራሱን።

"ካለቀጠሮ በመምጣቴ ይቅርታ" አለችውና አንገቷን ደፋች፡፡ “ለነገሩ  ቀጠሮ  አስፈላጊ ነበር ለማለትም ይከብደኛል" ቀና ብላ
አይታው አሁንም ሃሳቧን ገታችበት።
በሃሳቡ! ቀጠሮ የምን ቀጠሮ?' ብሎ እንዳሰበ በመላምት ህሊናውን አገለባበጠና ሃሳቡን ማጠቃለያ ላይ ለጊዜው ደረሰ: ልቡን ደስ አለው፡ ሴት ልጅ አፈቀርሁህ ብላው አታውቅም እሱ ግን ብዙ
ሌሊት ኮርኒሱን በአይኑ ሲቧጥጥ ቀን ላይ እንደ ክምር ፈጅ ገመሬ
ዝንጀሮ በአይኑ መሬት ሲያርስ ኖሯል፡

“ለጊዜው የኔም ቤት  የተከራየሁት ማለቴ ነው ከዚህ ብዙም አይቀርም። የማልኮራበትም ስራ አለኝ አለችና አሁንም በስርቆሽ ተመለከተችው።

ላቡ ግንባሩ ላይ ተንቸረፈፈ: ተቀጥቶ አፍህን ያዝ
እንደተባለ ህፃንም የፍርሃቱ ሳግ ላይ ላይ ሲያቃትተው

“ምን ነካኝ?” ብሎ
ተወራጨ። እግሮቹን እየቀያየረ አነባበራቸው፡ እጆቹን እንደ ሙሾ አውራጅ አወዛወዛቸው:

“ተናኘ... ተናኘ ወርቅ
እባላለሁ። ቶምም ይሉኛል
የሚቀርቡኝ:: ብዙ ጊዜ እንደ ቶማስ ሳላይ አላምንም ስለምል: ስለ ቶማስ ታውቃለህ መቼም? ቀና ብላ አየችው:

“አዎ! እየሱስ ሞትን ነስቶ ወደ ደቀመዝሙሮቹ መጥቶ
“እኔ ነኝ' ሲላቸው ካላየሁ አላምንም' ያለውን ነው" አላት። ፈገግ ብላ ትክክል መሆኑን አረጋገጠችለት “ሻይ ቡና” ምርጫ አቀረበላት:

“ኡፍ አንተም የሞቀ ውሃ ሰጥተህ የሚተናነቀኝን ቁልቁል ልታወርደው ትፈልጋለህ?" ነብር ሆነችበት አራስ ነብር::
👍26😁3
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


#ክፍል_ሦስት

አስተናጋጅ ሆኜ ከተቀጠርኩ አንድ አመት  አለፈኝ።በሲቪዬ ላይ የስራ ልምድ በሚለው ርዕስ ስር የንብረት ክፍል ተቆጣጣሪ እና የሆቴል አስተናጋጅነት የአንድ አመት የስራ ልምድ የሚለውን አስገብቼ መፃፍ እችላለሁ፤አዎ ይሄ ቀላል ነገር አይደለም።እያንዳንዱን የሠው ትዕዛዝ በትሪ ይዤ አቀርብና በዛው ትሪ ባህሪያቸውን  ያስረክቡኛል። ትሁቱ... ቁጡ.. ጉረኛ... ጋግርታም... እርብትብት... ለጋስ...ንፉግና ተነጫናጭ...በየቀኑ ፀባዩ የሚገለባበጥ ሙልጭልጭ በቃ እኔ ትምህርት ሚኒስቴርን ብሆን ኖሮ ሳይኮሎጂ እና ሶሾሎጂ ለሚያጠኑ  ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ቢያንስ ለስድስት ወር እንደዚህ አይነት ቦታ አፓረንት እንዲወጡ አደርጋቸው ነበር..ሆቴል ማለት የሠው ባህሪ በብፌ መልክ የሚቀርብበት ቦታ እኮ   ነው።

አሁን ከምሽቱ አራት ሰዓት ሆኗል ፡፡ባሩ ውስጥ አንድ ተስተናጋጅ ብቻ ነው ያለው፡፡ ለዛውም ሴት ደንበኛ...፡፡ይሄንን ብላክ ሌብል  ትጋተዋለች ።አሁን አሷ ብትወጣልን ሌላ የቀረን ስራ ስለሌለን ወደየቤታችን እንሄድና አረፍ እንል  ነበር ስል አሰብኩ ስናስተናግድ ከነበረነው  ስምንት ሴትና አራት ወንድ አስተናጋጆች መካከል አምስቱ ሴት ቀድመው መውጫ ቆርጠው ሄደዋል?ምን? መውጫ ምንድነው ?አላችሁኝ... መውጫ ማለት አንድ ሴት አብሯት የሚያድር ሰው አግኝታ የስራ ሰዓቷ ከመጠናቀቁ በፊት መውጣትና ከደንበኛዋ ጋር መሄድ ከፈለገች እንደሰዓቱ እየታየ ከምታገኘው ላይ እንድትከፍል ይደረጋል...ያው ግብር በሉት ።
ብዙውን ጊዜ በኢትዬጵያ የቡና ቤት ሴቶች ግብር አይከፍሉም ይባላል..እኔም እንደዛ አምን ነበር፡፡ አሁን ግን እንዲህ ተጠግቼ ሳይ አመት እስከ አመት እንደውም እንደእነሱ የሚከፍል የለም? ያው ግብር ማለት ከደሀው  መቀነት  ተቀንሶ  ለኃያላኑ ጡንቻ ማፈርጠሚያ  በግዳጅም ይሁን በይሁንታ የሚሰጥ መባ ነው።ኃያሉ መንግስት ሊሆን ይችላል..ባለሀብት ሊሆን ይችላል...የሠፈር አስተዳዳሪ ባለጡንቻ ሊሆን ይችላል...፡፡  ሁሉም በሚስኪኑ ደሀ ጫንቃ ላይ ተፈናጦ ከርሱን የሚሞላ  ብልጉ አውሬ ነው...ውይ በማሪያም አለቃዬን ነው ከሌላው ባለጉልበት ጨምሬ እንዲህ የጨፈጨፍኩት .አምላክ ሰምቶ ውለታ ቢስ ብሎ እንዳይቀየመኝ፡፡

አሁን ሆቴል ውስጥ የቀረነው ሁለት ወንድ  አስተናጋጆች እና አንድ ሴት አስተናጋጅ እና ደግሞ የእለቱን የተሰራ ሂሳብ ተረክቦ   እየደመረ ያለው ባሉካ ብቻ ነኝ...ሽኩክ ብዬ ወደእሱ ሄድኩና ፡፡
"ጋሼ እንዴት ነው?"

"ስለምኑ ነው የምትጠይቀኝ ጎረምሳው?"

‹‹ስድስት ሰዓት ሊሆን ነው...ተስተናጋጇን ልንዘጋ ነው ልበላት እንዴ?"

"አይ አይሆንም...ትልቅ ደንበኛችን ነች ..ቅር እንዲላት አልፈልግም.."

"አይ ለእሷም ቢሆን ይመሽባታል ብዬ እኮ ነው፡፡"

"የእኔ አሳቢ አይመሽባትም... ከተቀመጠችበት ተነስትታ አስር እርምጃ ከተራመደች የተከራየችበት ቤርጎ ትደርሳለች"

"ኦ ረስቼው… ለካ እዚህ ነው አልጋ የያዘችው"

"አዎ ባይሆን ልጇቹ ይግቡ ..ንገራቸው፡፡"

"እሺ ግን ጋሼ እሷ እስክትሄድ ብቻህን ልትሆን ነው?"

"አይ እኔ አይደለሁም ቀርቼ የማስተናግዳት ...አንተነህ.፡፡..በራሷ  ጊዜ በቅቷት ስትሄድ ቆላልፍና ሂድ...እኔ ሚስቴ ትጠብቀኛለች ...አንተ ከአይጥ ጋር ድብብቆሽ ለመጫወት ምን አስቸኮለህ?››

‹‹እንዴ ጋሼ ከጓደኞቼ ጋር የማወራው ነገር ተደብቆ ይሰማል እንዴ...?"ስል በውስጤ አልጎመጎምኩ፡፡ከሶስት ቀን በፊት ነበር ለሴቶቹ አንድ አይጥ አላስተኛ እንዳለቺኝና ልክ ስተኛ ጆሮዬን እየቀረጠፈች፤ ከንፈሬን እየነከሰች  አስቸገረችኝ ብዬ ያወራኋቸው...እነሱ ደግሞ አፍቅራህ ነው እያሉ ሲያሾፍብኝ ነበር..ይሄው አሁን ጋሼም ተቀላቀላቸው...
ጋሼ ሂሳቡን ሰርቶ ጨርሶ ለመሄድ ተነሳ፡፡

"ጋሼ ለመቆየቱ ግን ካሌብ አይሻልም?"

"ጓረምሳው ንብረቴን ለማን አምኜ ጥዬ እንደምሄድ የመወሰኑ መብት የእኔ መሰለኝ?...መልካም አዳር"ብሎኝ ጥሎኝ ወጣ...፡፡እኔም ሌሎቹ እንዲሄዱ ተናግሬ በዛ ውድቅት ለሊት ከአንድ እንስት ተስተናጋጅ ጋር ተፋጥጬ ተቀመጥኩ...፡፡
እኔም እንደሌሎች በዚህ ሰአት ክፍሌ ገብቼ አረፍ ባለማለቴ ከፍቶኛል ..ግን ደግሞ ጋሼ የተናገራት ነገር ልቤ ላይ አሪፍ  ደስታና ኩራትን አርከፋክፋብኛለች "ጓረምሳው ንብረቴን ለማን አምኜ ጥዬ እንደምሄድ የመወሰኑ መብት የእኔ መሰለኝ?ነበር ያለኝ አይደል?፡፡ "በእውነት መታመን ያስደስታል" ለዛውም አንድ አመት ባልበለጠው ጊዜ ውስጥ ይህን መሳይ ክብር ማግኘት ተስፋው ለፈረሰበት ሰውም ቢሆን  በህይወቱ ጥቂት መነቃቃትን ይፈጥራል፡፡

ጠረጴዛው ተንኳኳ ከነበርኩበት ባንኮኒ ውስጥ ፡ሮጬ ወጣሁና  ወደ ተጠራሁበት ቀርቤ፤ እጇቼን ወደኃላዬ አጣምሬ፤ ከጉልበቴ ሸብረክ ፤ ከአንገቴ ጎንበስ ብዬ"አቤት ምን ጎደለ ? ምን ላምጣ?"አልኩ፡፡

"እ ..ምንድነበር..?."በፈጣሪ ሰክራለች መሠለኝ ..?ለምን እንደጠራችኝ እንኳን  አታውቅም፡፡
"አዎ..ሙዚቃውን በጣም ቀንሰው እናም አንድ ብርጭቆ አምጣልኝ"
ወይ ፈጣሪዬ ሴትዬዋ ገና መጠጣት ልትጀምር ነው..ለዛውም በሁለት ብርጭቆ…. እንዳለችኝ የሙዚቃውን ድምፅ  ቀነስኩና ብርጭቆውን አጣጥቤ ይዤላት ሄጄ ጠረጴዛዋ ላይ አስቀመጥኩላትና ልመለስ ስል "ተቀመጥ"አለችኝ...
ተቀመጥ በሚለው ቃሏ ውስጥ ምንም አይነት ትህትናም ሆነ ሀዘኔታ አይነበብም፡፡.

"ምን አልሺኝ እመቤቴ?"

"ቁጭ በል..ንግግሬ አይሰማም እንዴ?"

"ኸረ በደንብ ይሰማል"ብዬ ትዕዛዟን በማክበር ሽኩክ ብዬ ቁጭ አልኩ..ፊቷ የተቀመጠውን  የተጋመሰ ብላክ ሌብል ጠርሙስ አነሳችና አዲስ ያመጣሁት ብርጭቆ ውስጥ አንደቀደቀችው፤ስትጨርስ  ወደፊት ለፊቴ አሽከርክራ አሰጠጋችው።

"ኸረ ይሄ ነገር ለእኔ አይሆንም?"

"ባክህ አትንጠባረር ..ዝም ብለህ ጠጣ "ብላኝ እርፍ...
አሁን ይሄ ግብዠ ነው አስገድዷ ደፈራ፡፡ፈራኋት መሠለኝ አነስሁና አንዴ ጎንጨት አልኩለት...
.፡፡‹‹እራት መቼ ነበር የበላሁት?›› ስል እራሴን ጠየቅኩ፡፡ አዎ 12፡30 አካባቢ....‹‹ምንድ ነበር የበላሁት?›› ዳቦ በሙዝ ...፡፡.ሶስት ሙዝና ሁለት ዶቦ....፡፡‹‹አሁን ከስድስት ሰዓት በኃላ ምን እየጠጣሁ ነው›› ውስኪ፡፡...‹‹ይህቺ ጋባዤ አራት ሰዓት አካባቢ ምንድነበር ያዘዘችው..?››ለማስታወስ ሞከርኩ...አዎ ክትፎ ነበረ ያዘዘችው እናም ግማሹን በልታ ግማሹ እንደተመለሠ አይቼያለሁ....አሁን ኪችን ብገባ ግማሹን ትራፊ አገኝ ይሆን?

"እዚህ ሀገር ለስራ መጥተሽ ነው?"ጥያቄውን መጠየቅ ፈልጌ ሳይሆን ዝም ብሎ መቀመጥ ስለጨነቀኝ ነው የቀባጠርኩት። ቢዝነስ የሚሰሩ ሴት  አስተናጋጆች ግን  እንዴት ብለው ነው ከማያውቁት ሰው ፊት ለፊት ተቀምጠው ዘና ብለው የሚጠጡት...ከዛም አልፎ የሚስቁት፤ የሚጫወቱት?ለዛውም በየቀኑ…፡፡ጥያቄዬን ሰምታ ሲጋራዋን ለኮሰች ...እናም ጭሱን አትጎልጉላ እላዬ ላይ በተነችብኝ ፡፡...ልክ እንደቤተመቅደስ ማዕጠንት ዝም ብዬ በፀጋ ተቀበልኩና ወደውስጤ ማግኩት?

"ምሽቱ ደስ ይላል..."ሌላ የማይረባ አስተያየት ከአንደበቴ ድንገት ሾለከ፡፡

"ምሽቱ አንተን ነው የሚመስለው?"አለችኝ፡፡
👍522👎1👏1
#የዘርሲዎች_ፍቅር


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ


#ክፍል_ሦስት

ካርለት መሳተፍ የማትችለውን የሽማግሎች ስብሰባ በርቀት
እየተመለከተች አልፎ አልፎም የካሜራ ችፕስ  በተደረገበት ባለዙም ካሜራዋ ፎቶ ስታነሳ ቆይታ ጎይቲን ፍለጋ ወደ መንደር
ተመለሰች

"ካርለት ነጋያ ... ነጋያ ... ያ ፈያው" አሉ ህፃናት የካርለትን ነጭ እጅ ለመያዝ እየተሽቀዳደሙ "ነጋያኒ  ጎይቲ ዳ! ደህና ነኝ
ጎይቲ አለች ብላ ጠየቀቻቸው በሐመርኛ

"እእ  ዳኒ" አለች አንዷ ህፃን ራሷን ዝቅ አድርጋ ሽቅብ
በመናጥ አለች ለማለት ካርለት  መዝጊያ ወደሌለው መግቢያ ጎንበስ ብላ በጠባቧ በር ወደ ውስጥ ስታይ ምርግ በሌለው የእንጨት መከታ መሐል ለመሐል በሚገባው ብርሃን ጎይቲ በርከክ ብላ እጆችደ
ከወፍጮው መጅ ላይ ሳይነሱ ራሷን ብቻ ወደ በሩ መልሳ አየቻትደ ካርለት የጎይቲን ማራኪ ፈገግታና የምትወደውን ጥርሷን ስታይ የደስታ ስሜት ውርር አድርጓት እሷም ሳቀች  ተሳሳቁ"

"አርዳ?" አለች ጎይቲ በአንገቷ እንደምትስባት ሁሉ አገጯን ወደ ታች እየሰበቀች ካርለት ፈገግ እንዳለች እሷን፥ ከኋላዋ
የተንጠለጠሉትን የቁርበት ልብሶች ግርግሙ ላይ የተንጠለጠሉትን
ዶላዎች (የወተት መያዣዎች) ግልጥጥ ያለውን የምድጃ ፍም:
በቀበቶው ጉጥ ላይ ቁልቁል የተንጠለጠለውን ክላሽንኮቭ ጠመንጃ
ልጆች አመዱን በውሃ በጥብጠው መግቢያው ጥግ ባለው የግድግዳ
ልጥፍ ላይ ያዩትን ለመሳል ያደረጉትን ጥረት ... በዐይኗ ስትቃኝ.

"አርዳ!" አለች ጎይቲ ደግማ አትገቢም! ለማለት ቃሉን ረገጥ አድርጋ።

"ፈያኔ" ብላ ካርለት እንደ ጅራት ከኋላዋ የተንጠለጠለውን
የፍዬል ቆዳዋን በግራ እጅዋ ወደ እግሮችዋ መሐል አስገብታ ቀኝ
እግሯን በማስቀደም በጠባቧ በር ሹልክ ብላ ገባች የሐመር ቤት
መዝጊያ የለውም  ቀንም ሆነ ማታ እንግዳ የአባት ሙት መንፈስ ከመጣ ሁሌም ሳይጠብቅ: ደጅ ሳይጠና ሰተት ብሎ መግባት አለበት ትንሽዋ በር ደፍዋ ከፍ ያለ በመሆኑ ለከብትም ሆነ ለአውሬ
ለመግባት አታመችም ቤት ለሐመሮች መቀመጫና መተኛ እንጂ መቆሚያ  አይደለም"  ሁሉም ነገር ትርጉም  ሊኖረው ይገባል
ስለሆነም ካለ ህፃናት በስተቀር በጣም አጭር ሰው እንኳ ጎንበስ ብሎ
ካልሆነ መቆም አይችልም ይህ የሆነው ደግሞ እንጨት ጠፍቶ ቦታ
ጠቦ ሳይሆን ለትርጉሙ ነው"

"ጎይቲ?"

"ዬ!"

ምነው ዛሬስ ስትፈጭ መዝፈን: ማንጎራጎሩን ተውሽው?" ብላ ጠይቃት ካርለት ፈገግ ብላ ጎይቲን ሳመቻት እንደ
ሐመር ሴቶች የልብ ሰላምታ ጎይቲ ካርለት ለጠየቀቻት መልስ  ሳትሰጥ አንገቷን ደፍታ እጅዋ ወፍጮው
መጅ ላይ እንዳለ በተመስጦ ስታስብ ቆይታ በቀኝ እጅዋ ማሽላውን ግራና ቀኝ ሰብስባ  ወደ ወፍጮው ጥርስ አስገብታ
ወገቧን ወደ ኋላና ወደ ፊት
እያረገረገች "ሸርደም: ሸርደም አድርጋ ፈጨችውና ብርኩማዋ ላይ ተቀመጠች
ከዚያ እኒያን ሐጫ በረዶ የመሳሰሉ ጥርሶችዋን
ገልጣ ለዓመል ያህል ፈርጠም አለችና

"ይእ!ካርለቴ ኧረ አሁን ሳንጎራጉር ነበር መቼ
እንጉርጉሮዬን እንደ አቆምኩት ግን እንጃ! አዝኜ እንኳን ቢሆን ሁልጊዜ መፍጨት ስጀምር እህሉ ከታች ሲደቅ እኔ ከላይ ትዝታዬን እየጨመርሁ እንጉርጉሮዬን አቀልጠው ነበር አሁን እኮ ኮቶ እግሯ
ወጣ ከማለቱ ነው አንች የመጣሽ ከኮቶ ጋር እየተከራከርን ሁላ እዘፍን ነበር  በኋላ ግን ኮቶ ለመሄድ ስትቁነጠነጥ እያወራች እንድትቆይ ብዙ
ክርክር ገጠምኋት
ታውቂያታለሽ ተከራክራ ተከራክራ ካልረታች እንደ ፍየል ልዋጋ ስትል ታስቀኛለች ስለዚህ ጥላኝ ከምትሄድ ብዬ ነገር ጀመርኋት

"ኮቶ ከተማ አትሄጅም?" ስላት

"ይእ! ኧረ ምን አልሁሽ እቴ እኔስ ያገሬ ጅብ ይብላኝ
አለችኝ ትንሽ ላስለፍልፋት ብዬ እኔ ግን መበላቴ ታልቀረ የጅብ ዘመድ አልመርጥም አልኋት አይምሰልሽ ጅሊት! ያገርሽ ጅብ ገሎ ነው የሚበላሽ  የሰው አገር ጅብ ግን እየበላ ነው የሚገልሽ ስትለኝ ይእ! አንች ምነው ታልጠፋ አውሬ ጅብን እንዲህ ዘመድ
አዋቂ አደረግሽው?
አልኳት‥ ይሄ እንኳ ምሳሌ ነው ስትለኝ ሞጥሟጤ  ምሳሌሽን ቀይሪያ!ታለበለዚያ ካለ
ጥንባቸው ሌላ
የማያውቁትን ጅቦች ካለስማቸው
ስም ሰጥተሽ ቅዱስ አድርገሽ ታውሬው ሁሉ አታቀያይሚያቸው" ብላት ወገቤን ደቅታኝ ሹልክ ብላ ሄደች ከዚያ ማንጎራጎር ጀምሬ ነበር ወዲያው ግን ድምፄ ለከት የለሽ ሆኖ ልቤ ግንድ የሚያመሽክ ምስጥ ይርመሰመስበት ጀመር

"ምን ሆነሽ ነው ጎይቲ የምን ጭንቀት ነው?"

"ወደው አይስቁ አለ ያገሬ ሰው ..." ብላ ጎይቲ ከትከት ብላ ስቃ።

"ይእ! ምነው እንዳንች ጅል ሆኜ እድሜ ልኬን ስጠይቅ
በኖርሁ" ስትላት ተያይዘው እንደገና ተሳሳቁ

"ካርለቴ! እውን ሴት ልጅ እግርና እጅዋ የሚያጥረው፥
ቀትረ ቀላል ሆና ድምጿ የሚሰለው ... ለምን እንደሆን አታውቂም?

"አላውቅም ጎይቲ ለምንድን ነው?"

"ይእ! እንግዲያ ዝናብ እንደበዛበት ማሽላ ታለ ፍሬ መለል ብለሽ ያደግሽ አገዳ ነሻ! ሙች አንችስ ተህፃን አትሻይም አንቺ እኮ! ተንግዲህ ወዲያ ትልቅ ሰው ነሽ! ጉያሽና ልብሽ ላይ የትዝታ ምሰሶ የተተከለ
ፈጭተሽ የምታበይ ጭሮሽ ውሃ ቀድተሽ ለጥም
መቁረጫ የምታጠጭ
የወንድ ልብ ሲጎመራ ጫካ መሃል ገብተሽ የምትካፈይ
ፍቅርሽን እንደ ህፃን ልጅሽ የምትግች ትልቅ ሴት እኮ ነሽ?" ትልቅ ሴት እኮ ነሽ?"

"ጎይቲ የባሰ ግራ ገባኝ?"

"ይእ! እንዲያ ይሻላል! ቁም ነገር አታውቂም ብዬ ተመንገር ሌላ እህ ላሳይሽ?"  ብላ ጎይቲ በአድናቆት ጨብጨብ ጨብጨብ አድርጋ በሣቅ ተፍለቀለቀች

ካርለት ከተቀመጠችበት
ፈገግ ብላ ተነስታ ጎይቲን ገፋ አድርጋት የወፍጮውን መጅ በግራ እጅዋ ይዛ ከሾርቃው በቀኝ
እጅዋ ማሽላውን አፍሳ ጨምራ

"እሽ እኔ እፈጫለሁ አንች ንገሪኝ?" አለቻት

"ይእ! እውነት ታላወቅሽውማ እነግርሻለሁ  እንጂ ብላ እግሯን ዘርግታ ቁርበቱ ላይ ቁጭ አለች ጎይቲ ወደ ቁምነገር
ስትመለስ የሚያስጨንቃትን
ለመናገር ስትዘጋጅ ውስጧን የሚጎማምደው ችግሯ የፈገግታ ፀዳሏን እየቸለሰ አከሰመው ደሟ
እንደቀትር ማዕበል ደረቱን ገልብጦ እየዘለለ በመፍረጥ አረፋ ደፈቀ
ታወከ
"ሐመር ላይ ሴት ልጅ የግል ችግር የለባትም እምትበላውን መሬቷ እምትጠጣውን ላሞች: ፍቅርን ደግሞ የሐመር ወንዶች እንደ ማሽላ ገንፎ እያድበለበሉ ያውጧታል ሴት ልጅ ወንዝ
ብትሄድ እንጨት ለቀማ ጫካ ብትገባ እህል ልታቀና ገበያ ብትወጣ ብቻዋን አትሆንም ሰው ከብቶች: ዛፎች አሉላት ሴት ብቻዋን ችግር የሚገጥማት የማትወልድ ስትሆን ነው መሐንነት ትታይሻለች ያች ፀሐይ " ዝቅ ብላ በግርግዳው ቀዳዳ ጮራዋን ፈንጥቃ የምትንቦገቦገውን የረፋድ ፀሐይ እያሳየቻት

"ይኸውልሽ መሐንነት ያችን በሙቀት የምትነድ እሳት ዘላለም እንደ ጨቅላ ህፃን ደረትሽ ላይ ታቅፈሽ መኖር: ታቅፈሽ መሞት ነው" ተዚያ እድሜ ልክሽን መቃጠል: መንደድ ነው"

"መሐንነቱ የመጣብሽ ሳታስቢው የሴት ብልትሽን ውሃ ነክቶት ይሆናል ሆን ብለሽ ባታደርጊውም ትዕዛዝ ነውና ቅጣቱ ቃጠሎው ወደ ገለብ ብትሮጭም አታመልጭውም ስትቃጠይ ደግሞ ሰው የሻጉራ እያዬ ይሸሽሻል ባይሆን ከቃጠሎሽ  ባይጠቅምሽም
ለእነሱም ባይጠቅማቸውም ለአባትሽ ለእናትሽ ለእህትሽ
ለዘመዶችሽ ታካፍያቸዋለሽ የተረገመ ቤተሰብ እያሰኘሽ" ብላ ዝም አለች ጎይቲ  እንደተላጠ ጣውላ ሰውነቷ ሟሾ

ግዙፍነት ለካ በአጥንትና ስጋ ብቻ አይደለምና  መጠንም በህሊና ይወሰናል ውበትና ቁመና ህሊና በሚፈጥረው መተማመን ተገዥ ነውና! እያለች ካርለት ጎይቲን እያየች ስታስብ
👍19👎1