አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ሳቤላ


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ

..ሚስተር ካርይልና ሳቤላ ዊልሰንን አስከትለው በምዕራብ ፈረንሳይ ቡሎን በምትባል ከተማ ደርሰው ወደ ቤንስ ሆቴል አመሩ " ፒተር የሚስ ካርላይል አሽከር
የነበረ ሲሆን ወደ ኢስትሊን ሲዛወሩ ወደነሱ ዙሮ እንደ ነበር እዚህ መጥቀሱ ተግቢ ይሆናል " ቡሎኝ እንደገቡ ወደ ቤንስ ሆቴል ሔደው ሚስዝ ዱሲ መኖሯን ጠየቁ ቀድማ ዴርሳ ልትቀበላቸውና ሳቤላንም ልታላምድ ታስባ የነበረችው ሚስዝ ዱሲ በቤተሰብ ችግር ምክንያት ወደ ጀርመን መሔዷን ከተወችላት ደብዳቤ ተረዱ"

“ ፊቱንም ቢሆን ማወቅ ነበረብኝ እንደሷ በቃሏ የማትገኝ ሴት የለችም አለች ሳቤላ "

ሚስተር ካርላይልም እሷ ከሌለች ወደ ትሩቪል መሔድ መሻሉን አማክሯት ነበር ሳቤላ ግን አንድ ጊዜ ቡሎኝ ከገባች ከዚያው መቆየቱን መረጠች " እሱም
ቤንስ ሆቴል ግርግር ይበዛበት ስለነበር፡ ጸጥታና ክብር ያለበትን ሆቴል ፈልጎ በኤኩ መንግድ በኩል ከወደቡ አጠገብ አንድ በጣም ጥሩ ሆቴል አገኘና ወዶፈደዚያ ተዛወሩ ወዟ ቶሎ ምልስ ሲል አይቶ ሚስተር ካርላይል ጉዞው ደኅና የረዳት መሰለው እሷም ብርታት እንደ ተሰማት ነገረችው አንድ ቀን ብቻ ውሎ ለመመለስ የመጣውን
የብርታቷ መታደስና የፊቷ መለምለም ሲያይ ስለ ተደሰተ የዚያች ወጭ ወራጅ አላፊ አግዳሚ የበዛባትና የተጨናነቀችውን ከተማ ሁኔታ እያየ ጭምር ሦስት ቀን አደረ።

“ እኔ እዚህ ከማንም ጋር ለመተዋወቅ አልፈልግም
አለችው ሳቤላ ከወደቡ መድረክ አንድ ጫፍ ላይ ተቀምጠው ባጠገባቸው እየተጋፉ ሲያልፉ የነበሩትን ብዙ ደስተኛ ሥራ ፈቶችን እየተመለከቱ "

“ በደፈናው እንደዚህ ማለቱ እንኳን ደግ አይሆንም ” አላት ሲመልስላት እንዳጋጣሚ የምታውቂው ሰው ታገኚ ይሆናል " ብዙ ዐይነት ሰዎች ወደዚህ
ይመጣሉ አንዳንዶቹ ሐቀኞችና የተከበሩ ሆነው ለተከበረ ዓላማ ይመጣሉ አንዳንዶቹ ደግሞ በተግላቢጦሹ በመጥፎ ጠባያቸው ዕዳና ዱቤ በማብዛታቸው ኢንግላንድ ውስጥ መኖር ስለአልቻሉ ካገር እየሸሹ በሀብት የከበሩና የቅዱሳን ኑሮ የሚኖሩ መስለው የሚታዩ አጭበርባሪዎች ናቸው "

“ አንተ ወደ ባሕር ማዶ እንኳን መጥተህ አታውቅም እንዴት ታውቃቸለህ.. አርኪባልድ ?”

“ ቦታውን ከሚያውቁ ብዙ ሰዎች ጋር እገናኛለሁ ለምሳሌ ባክስታንን ተመልከቼው እሱም አይቶኛል " ወደፊት በመምጣት ወይም ወደ ኋላ በመሸሽ መካከል ሊቆርጥ አልቻለም ።

"ማን ? የቱ ነው እሱ ?”

“ ያ ረጂም ጸጉረ ቀይ ደኅና ልብስ ለብሶ በሰዓቱ ማሰሪያ ብዙ ጌጥ ያንጠለጠለው " ሚስቱ ደግሞ ከሌሎች ሴቶች ጋር ሆና ስትከተለው ተመልከቻት
የለበሰችው ልብስ ያጠለቀቻቸው ሐብሎችና በእጅዋ ያደረገቻቸው አምባሮች ሁሉ ሰው አማኝ ከሆኑ ነጋዴዎች በማጭበርበር የተወሰዱ ናቸው " እዚህ ባለው የእንግሊዝ ኅብረተሰብ መኻል ግን ትልልቅ ስዎች መስለው ለመታየት እንደሚሞክሩ አይጠረጠርም ደከመሽ እንዴ ? አላት ።

"አዎን ትንሽ ! እንግዲህ ወደ ቤት ብገባ ይሻለኛል "

ከወደቡ መድረክ ክንድ ለክንድ ተያይዘው ቀስ እያሉ ሲወርዱ በጠቅላላ ሁኔታቸው ዐይነ ገቦች ሆኑና ብዙ ሰው አተኩሮ ይመለከታቸው ጀመር "

በበነጋው ጧት በሁለት ሰዓት በሚነሣው ጀልባ ወደ ኢንግላንድ ለመመለስ ሲሰናበታት : “ ደኅና ሁኚ . . . የኔ ፍቅር” አላትና ዝቅ ብሎ ከሳማት በኋላ “ራስሽን ጠብቂ አላት ።

“ ልጆቼን ሳምልኝ ... አርኪባልድ እና እ ... እና .. እ. እ” “ እና ምን ? ” አላት “ ሰዓት ደረሰብኝ ”

“ እኔ አለመኖሬን አይተህ ከባርባራ ሔር ጋር እንዳትዳራ ” አለችው የቀ
ለደች መስላ " እሱም እንደ ቀልድ ወሰደውና እየሣቀ ወጣ አነጋሯ ከልቧ መሆኑ አልገባውም "

ሳቤላ ተነሥታ ለቁርስ እንደ ተቀመጠች የቀሩትን ሳምንቶች እንዴት እንደ ምታሳልፋቸው ጨንቋት ትተክዝ ጀመር ። ከደሬሰችበት ቀን ጀምሮ ሁለት ጊዜ ከባሕሩ ሔዳ ታጥባ ነበር : ግን ጭንቀትና እንቅጥቅጥ ለቀቀባትና የሚስማማት ስላልመሰላት አቋረጠችው "

አየሩ በጣምደስ የሚል ስለነበር ማታ ከባሏ ጋር ካመሹበት የወደብ መድረክ ዘልቃ ለመሞከር አሰበች " ስለዚህም ፒተርን አስከትላ ሔዳ ከተቀመጠች በኋላ አንድ ሰዓት ቆይቶ እንዲመጣ ነግራ መለሰችው እሷ ከዚያ የተለያዩ ተላላፊዎችን ትመለከት ጀመር " አንድ እግረ በሺተኛ ሰውዬ በጨርቅ ማማ ሲሔድ አየች " ቀጠሉና ሦስት ቆነጃጂት ከሞግዚታቸው ጋር ብቅ አሉ ከዚያ ዴግሞ ዳንዴ ዳንዴ የሆኑ ጎረምሶች የአደን ጃኪት ለብሰው መነጽር አድርገው መጡ ሳቤላን ትንሽ ትኩር አድርገው ካዩዋት በኋላ ዐልፈው ሔዱ " ከነሱ በኋላ ትንሽ ቆይቶ ደግሞ ከሁኔታው ትልቅ ሰው የመሰለ · አንድ ረጂም መልከኛ ሰውዬ ዘለቀ » ሳቤላ
ገና ስታየው ዐይኖቿን ጣለችበት " ያ እስከዚያ ድረስ ገና ከልቧ ያልጠፋው ሰው መሆኑን ስታይ ' የጠቅላላ ሰውነቷ ሥሮች ተርገፈገፉ።

ካፔቴን ሌቪስን በበኩሉ ገና ሲያያት እንዴት ያለች ቆንጆ ነች ? ማን ትሆን?” እያለ ወደ ተቀመጠችበት መድረክ አድናቆቱንና አክብሮቱን በግንባሩ እየገለጸ ሲጠጋ ማን መሆኗን አወቃት ወዲያው ባርኔጣውን አንሥቶ' ፊቱ በፈገግታ ፈክቶ
እጁን ለሰላምታ እየዘረጋ፡ “ ከእመቤት ሳቤላ ቬን ጋር እንደገና ለመገናኘት እንደታደልኩ አልጠራጠርም ” አላት

እሷም መንፈሷ ተሸብሮ የምትናገረው ጠፋት » እጅዋን ለሰላምታ ስትዘረጋላት ጥቂት ቃሎች በማልጐምጐም መለሰችለት "

ይቅርታ አድርጊልኝ ... እመቤት ሳቤላ ፡ ካርላይል ማለት ነበረብኝ ከተለያየን ብዙ ጊዜ ሆነና አሁን እንዲህ ድንገት ሳገኝሽ ጊዜ ከደስታዬ ብዛት የተነሣ
አንቺን ያሰብኩሽ ልክ ያን ዘመን እንደ ነበርሽው አድርጌ ነው "

እንደገና ተቀመጠች " በስሜት ፍላት ጉንጮቿን አልብሷት የነበረው ቅላት ቀስ በቀስ ለቀቀ " ፍራንሊዝ ሌቪሰን ከዚያ በፊት ካያት ጀምሮ እንደሷ ያማረ ፊት
አይቶ የሚያውቅ አልመሰለውም።

ከዚህ ምን እግር ጣለሽ ?” አላት ከጐኗ እየተቀመጠ ።

አመመኝና ወደ ባሕር ዳርቻ እንድሔድ ታዘዝኩ ሚስዝ ዱሊን ከዚህ እናገኛታለን ብለን ባንጠብቅ ኖሮ አንመጣም ነበር ሚስተር ካርላይልም አብሮኝ መጥቶ ሦስት ቀን ቆየና ዛሬ ጧት ተመልሶ ሔደ „

ሚስዝ ዱሲማ ወደ ኤምዝ ሄዶች እነሱን ዐልፎ 0ልፎ አያቸዋለሁ
ለጥቂት ጊዜ ፓሪስ ተቀምጠው ነበር " እውነትም የታመምሽ ትመስያለሽ ልጄ " ኣላት አስተዛዝኖ “ በጣም ታመሻል " እኔ የምረዳሽ ነገር አለ ?

እሱን ስታይ ድንገት የያዛት ድንጋጤና የመንፈስ መረበሽ እየለቀቃት ሲሔድ ደም መስሎ የነበረው ፊቷ ዐመድ ሲያለብሰው ከመጠን በላይ የታመመች
መምሰሏን ለሷም ታውቋት ነበር ። ከሱ ጋር ስለ ተገናኘች መንፈሷ በመረበሹ በራሷ በጣም ተናደደች እስከዚያች ቅጽበት ድረስ ለፍራንሲዝ ሌቬስን የተዳፈነ ስሜት ይዛ መኖሯን አልታወቃትም ነበር።

“ምናልባት በጥዋት ለመምጣት በመድፈሬ ይሆናል " አለችው እንዳዲስ ያመማት ለመምሰሏ ምክንያት ስትሰጥ “ ልመለስ መሰለኝ " አሽከሬን አገኘዋለሁ " ደኅና ዋል .. . ካፒቴን ሌቪሰን”

ግን ብቻሺን በእግርሽ ችለሽ መሔድ የምትችይ አትመስይም ስለዚህ ከቤትሽ ድረስ እንድሸኝሽ ፈቃድሽ ይሁን "

ድሮ ሲገናኙ ያደርገው እንደ ነበረው ክንዷን ሳብ አድርጎ ከብብቱ አስገብቶ
ከወደቡ መድረክ እየደገፈ አወረዳት በርግጥ ከሱ ጋር እንዶዚያ ተያይዛ መሔዱ'
ደግ ያለ መሆኑ ቢታወቃትም እሱም የቤተሰቧ ዘመድ ብዙ ስለሆነ ክንዷን ለመከልከል የምትሰጠው ምክንያት አልተገለጸላትም
👍11🔥1🥰1
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#ትርጉሜ_ሀኒም_ኤልያስ

...ልታገኝ ስለምትፈልገው ነገር ስትል ድራማ የምትሰራ አድርጌ የማስባት ለምንድነው? እኔን ችላ ብላ ክሪስን ተመለከተች።

ለሚቀጥለው ልደትህ ኢንሳይክሎፒድያ አዝዤልሀለው። ማተምያው ድረስ ራሴ ሄጄ ነው ያዘዝኩት ስምህንና ቀኑን ሰጥቺያቸዋለሁ ግን ወደዚህ በቀጥታ መላክ አይችሉም:: የሆነ ሰው ሊቀበላቸው ይገባል ልክ ሁልጊዜ ራስህን ለማስተማር ምርጡን ልሰጥህ እንደምፈልግ ሁሉ የሚያስደስትህን ስጦታ ሳስብ ሳስብ ቆይቼ ነው ያዘዝኩልህ”

ክሪስ የሚናገረውን አጣ ፊቱ ላይ የሚታየው ድብልቅልቅ ስሜት ነበር፤አይኖቹ ግራ የተጋቡና የፈዘዙ መሰሉ። አምላኬ! ካደረገችው ነገር በኋላ እንኳን ይወዳታል ማለት ነው::

ስሜቶቹ ቀጥታ ናቸው:: በቁጣ ነደድኩ እንደዚህ አይነት መፅሀፍት ከአንድ
ሺ ዶላር በላይ ይፈጃል: ምናልባትም ሁለት ወይም ሶስት ሺም ሊፈጅ ይችላል። ይህንን ገንዘብ ለምን የማምለጫ ገንዘባችን ውስጥ አትጨምረውም?
ልክ ኬሪ ስትቃወም እንደምታደርገው ልጮህ ስል ክሪስ አይኖች ላይ ያየሁት ነገር አፌን እንድዘጋ አደረገኝ፡ ሁልጊዜ እነዚያ መፃህፍት እንዲኖሩት ይፈልግ ነበር፡ በዚያ ላይ አንድ ጊዜ ታዟል: አሁን ለሷ ገንዘብ ምኗም አይደለም፧
ምናልባት እንዲያው ምናልባት አያታችን ዛሬ ወይም ነገ ሊሞት ስለሚችል አፓርታማ መከራየትም ሆነ ቤት መግዛት አያስፈልጋት ይሆናል፡

ጥርጣሬዬ ተሰምቷታል።

እናታችን ጭንቅላቷን ቀና አደረገችና ወደ በሩ ተራመደች። ስጦታዎቻችንን
ገና አልከፈትንም፤ ስንከፍት የሚኖረንን ስሜት ለመመልከትም አልቆየችም።
እየጠላኋት ለምንድነው በውስጤ የማለቅሰው? አሁን አልወዳትም አልወዳትም።

በሩጋ ደርሳ እየከፈተች “ዛሬ ስለፈጠራችሁብኝ ህመም ስታስቡና እንደገና
በፍቅርና በአክብሮት ልታስተናግዱኝ ስትችሉ ተመልሼ እመጣለሁ ከዚያ
በፊት ግን አይሆንም::” አለች።

መጣች።

ሄደች።

መጥታ ስትመለስ
ኬሪና ኮሪን አልነካቻቸውም አልሳመቻቸውም አላናገረቻቸውም ለምን እንደሆነ አውቄያለሁ፤ ሀብት ማግኘት መንትዮቹን ምን ያህል ዋጋ እንዳስከፈላቸው ማየት መቋቋም ባለመቻሏ ነበር።

ከጠረጴዛው አጠገብ ተነስተው እየሮጡ ወደ እኔ መጡና ቀሚሴን እየጎተቱ
ፊቴ ላይ አፈጠጡ ትንንሽ ፊቶቻቸው ጭንቀትና ፍርሀት አጥልቶባቸዋል።
እነሱም ደስታ እንዲሰማቸው መደሰቴን ለማየት ፊቴን እያጠኑ ነው:
ተንበርክኬ እሷ የጎዳቻቸውን በመሳምና በማቀፍ አጥለቀለቅኳቸው።
መልካችን ያስጠላል?" ጠየቀች ኬሪ በመጨነቅ፤ ትንንሽ እጆቿ እጄን
ይዘውኛል

“አይ በጭራሽ! አንቺና ኮሪ ቤት ውስጥ ብዙ በመቆየታችሁ ትንሽ የገረጣችሁ ትመስላላችሁ”

“በደንብ አድገናል?”

“አዎ፣ አዎ አድጋችኋል” እየዋሸሁ እንኳን ፈገግ ብያለሁ: በዚያ የማስመሰል
ደስታና የውሸት ፈገግታ ወለሉ ላይ ከክሪስና ከመንትዮቹ ጋር ተቀምጠን
አራታችንም ልክ እንደ ገና ቀን ስጦታዎቻችንን መክፈት ጀመርን። ሁሉም
በውድ የስጦታ ወረቀቶች በሚያምር ሁኔታ የታሸጉ ናቸው።

ወረቀቱን ቀደድን ሪቫኑን ጥለን የታሸጉበትን ካርቶኖች ገነጣጥለን ውስጡ ያለውን አወጣን... በውስጡ ለእያንዳንዳችን የሚያማምሩ ልብሶች ነበሩ:
አዳዲስ መፃህፍት፣ መጫወቻዎች፣ አንድ አይነት ቅጠል የሚስል ቅርፅ ያላቸው በትልቅ ካርቶን ውስጥ የታሸጉ የስኳር ከረሜላዎች።

እንደምታስብልን ማሳያው ይኸው! ሁላችንንም በደንብ ታውቀናለች።ከመጠኖቹ በስተቀር ፍላጎታችንን፣ ማድረግ የምንፈልገውን ሁሉ ታውቃለች።
በፈቃደኝነት ሞተን ስንቀበር ማየት ደስ በሚላት ጠንቋይ አያታችን ጥበቃ ስር የተተውንባቸውን እነዚያን ባዶና ረጃጅም ወራት በስጦታዎቹ ከፈለችን።

በዚያ ላይ እናቷ ምን አይነት እናት እንደሆነች እያወቀች... የምትሰራው ሁሉ በልቧ ትክክል እንዳልሆነ እያወቀች በመጫወቻዎቹና በአሻንጉሊቶቹ
ልትደልለንና ይቅርታ ልትጠይቀን ፈለገች
በጣፋጭ የስኳር ከረሜላ መራራውን ብቸኝነታችንን ከአፋችን፣ ከልባችንና
ከአእምሯችን ልትወስድ ተስፋ አደረገች ምንም እንኳን ክሪስ መላጨት
የሚያስፈልገው እኔም ጡት መያዣ መልበስ የሚገባን እድሜ ላይ የደረስን
ቢሆንም በእሷ አስተሳሰብ አሁንም ልጆች ነን ልክ በምታመጣው መፃህፍት
ርዕስ ትንሽ አድርጋ ለዘለዓለም ልታስቀምጠን ትፈልጋለች፡

ኬሪን አዲስ ቀይ ቀሚስ ሳለብሳትና ሀምራዊ ሪቫን ሳደርግላት ፈገግ እንዳልኩ
ነበር አሁን ሁልጊዜ እንደምትፈልገው አይነት ለብሳለች የምትወዳቸውን
ቀለማት እግሮቿ ላይ ሀምራዊ ካልሲ ከነጭ አዲስ ስኒhር ጋር አለበስኳት “በጣም ታምሪያለሽ ኬሪ” እሷም ብሩህ ቀለም ያለው ልብስ በመልበሷ ተደስታለች።

ቀጥሎ ኮሪን ቀይ አጭር ሱሪና ኪሱ ቀይ የሆነ ነጭ ካኒቴራ አለበስኩት፡

ከዚያ “አንተንም ላልብስህ ክሪስቶፈር?” ስል ቀለድኩ

“ልብሽ ከፈቀደ ቆዳዬን ገልብጠሸ ማልበስ ትችያለሽ”

“ጋጠ ወጥ አትሁን!”

ኮሪ ሌላ የሙዚቃ መሳሪያ መጣለት፡ እሱ የሙዚቃ መሳሪያውን እየነካካ ኬሪ
ትዘፍንለታለች።

ሁሉም ነገር ላይ ያለኝን ደስታ የሚወስዱብኝ እግዚአብሔር የሰጠኝ ክፉ
ሀላቦች ነበሩኝ: ማንም የማያያቸው ከሆነ ቆንጆ ልብሶች ምን ይጠቅማሉ?
እኔ የምፈልገው በሚያምሩ ወረቀቶች ያልተጠቀለሉ፣ በሪቫን ያልታሰሩ፣ ሱቆች ውስጥ በካርቶን ያልተቀመጡ ነገሮችን ነው፧ የምፈልገው ገንዘብ
ሊገዛቸው የማይችላቸውን ነገሮች ነው: ጸጉሬ ከፊቴ በአጭሩ መቆረጡን
አስተውላለች? እንዴት እንደሳሳ አይታለች?የገረጣና የሳሳው ቆዳችንን እያየች
ጤነኛ እንደሆንን ታስባለች?

ለእኔ የተባሉትን ቆንጆ ቆንጆ ልብሶች ተመለከትኩ፡ ሰማያዊ ቬልቬት ቀሚስ፣ ለግብዣ የሚለበስ ሮዝና ሰማያዊ የምሽት ጋዋን አብሮት ከሚሄድ ጫማ ጋር፧ እዚያ ተቀምጬ ከረሜላውን እየበላሁ የሆነ ነገር ትዝ አለኝ፡፡
“ኢንሳክሎፒዲያ!” ለዘለዓለም እዚህ ልንኖር ይሆን?

የስኳር ከረሜላ በጣም ከምወዳቸው ነገሮች አንዱ ነው፡፡ ይህንን የከረሜላ
ካርቶን ያመጣችው ለኔ ነበር ለኔ፡ እኔ ግን መብላት የቻልኩት አንድ ብቻ
ነበር። ያንንም በጣም በችግር።

የከረሜላው ካርቶን መሀል ላይ ተቀምጦ ክሪስ ኮሪና ኬሪ ከበውት ተቀምጠው
በጣም በመደሰት ከረሜላዎቹን እያጣጣሙ ነበር፡ “ከረሜላዎቹን ሁሉ
መጨረስ አለባችሁ ለረጅም በጣም ለረጅም ጊዜ የማታዩት የመጨረሻ
ከረሜላችሁ ነው፡” አልኳቸው በመረረ ጥላቻ

ክሪስ አየት አደረገኝ ሰማያዊ አይኖቹ ደስተኛና የሚያበሩ ሆነዋል።
እምነቶቹና መተማመኑ ሁሉ እናታችን ለአጭር ጊዜ ባደረገችው ጉብኝት
እንደተመለሱለት ለማየት ቀላል ነበር፡ ስጦታዎቹ እሷ ከዚህ በኋላ ለእኛ ግድ የሌላት የመሆኑን ሀቅ የመደበቂያ መንገድ እንደሆነ ለምን ማየት አልቻለም? ከዚህ በፊት እንደነበርነው አሁን ለእሷ እውነት እንዳልሆንን እኔ
እንዳወቅኩት እንዴት አያውቅም? እኛ ልክ ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ እንዳሉት አይጦች፣ ሰዎች ሊነጋገሩባቸው ከማይፈልጓቸው ደስ የማይሉ ርዕሶች ውስጥ ነን፡

“እዚያ ቁጭ ብለሽ የማይናገር ምሰይ” አለ፡ ክሪስ ደስታውን እኔ ላይ እያንፀባረቀ: “እኛ ሶስታችን አይጦቹ መጥተው ከመብላታቸው በፊት አምሮታችንን ስንወጣ አንቺ ከረሜላውን እምቢ በይ: አንቺ ቁጭ ብለሽ ስታለቅሺ፣ ለራስሽ
ስታዝኚና ራስን መስዋዕት በማድረግ ሁኔታችንን መለወጥ እንደምትችይ ስታስመስይ ኮሪ፣ ኬሪና እኔ በልተን ጨርሰን ጥርሶቻችንን እናፀዳለን፡ ቀጥይ
ካቲ አልቅሺ! ሰማዕት ሁኚ! ተሰቃይ! ጭንቅላትሽን ከግድግዳ አላትሚ! ጩኺ እኛ እንደሆነ ወንድ አያታችን እስኪሞት እዚህ መሆናችን የማይቀር ነው::በዚያ ላይ ከረሜላዎቹ ሁሉ ያልቃሉ! ያልቃሉ! ያልቃሉ”
👍423
#ጠላፊዎቹ


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#በኬንፎሌት


#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ

ሃርትማንና ጋቦን የሎርዱ ንግግር ገርሟቸው አፈጠጡባቸው:
ማርጋሬት በድንጋጤ ፊቷ የበሰለ ቲማቲም መሰለ፡፡ አባቷ የተናገሩት ጮክ ብለው ስለነበር ሰዉ ጸጥ ረጭ አለ ማርጋሬት መሬቱ ተከፍቶ ቢውጣት ወደደች፡ ይህን የተናገሩት ፊት ለፊቷ የተቀመጡት ባለጌ፣ መሆናቸውን ሰው ሁሉ ስላወቀ ተሽማቀቀች።
አስተናጋጁን ኒኪን ቀና ብላ ስታየው መሳቀቋን አይቶ ለእሷ ማዘኑን ከፊቱ አነበበች፡ ይህም የበለጠ እፍረቷን አባባሰባት"

ባሮን ጋቦን ፊታቸው በድንጋጤ አመድ መስሏል ለሎርዱ መልስ ሊሰጡ አሰቡና ትተውት ፊታቸውን ወደ ሃርትማን መለሱ፡
ሆዳቸው እያረረ በፈገግታ አለፉት፡ ነገር ግን እሳቸው ከናዚ ጀርመን አምልጠው የመጡ በመሆናቸው ከዚህ በላይ ብዙ ክፉ ነገር የደረሰባቸው ስለሆነ ይህ ስድብ ለእሳቸው እንደ ምርቃት የሚቆጠር ነው።

ማርጋሬት ባሮን ጋቦንን ተመለከተች፡ ሎርዱ ያሉትን ከምንም ባለመቁጠር ማንኪያቸውን አንስተው ሾርባቸውን መጠጣታቸውን ቢቀጥሉም እጃቸው እየተንቀጠቀጠ ስላስቸገራቸው ሰደርያቸው ላይ ሾርባው ተንጠባጠበ፡፡ውስጣቸው
የሚንተከተከው ንዴት ግን
መጠጣት ስላላስቻላቸው ማንኪያቸውን አስቀመጡት።

ማርጋሬት የባሮኑ ብስጭት ልቧን ነካው። በአባቷም ስድብ በጣም ተናደደችና ‹‹ድፍን አውሮፓ የሚያከብራቸውን ሁለት ትላልቅ ሰዎች እንደዚህ መሳደብ የለብህም›› አለቻቸው በድፍረት።

‹‹ሁለት የታወቁ ይሁዲዎች በይ›› አሉ አባቷ።

‹‹ይሁዳዊያን አያቴን ረሳሃቸው አባባ?›› አለ ፔርሲ ሁሉን ነገር ቀልድ አድርጎ።

አባት ወደ ልጃቸው ዞሩና ጣታቸውን ፔርሲ ላይ እያወዛወዙ ‹‹እንዲህ
ያለውን የማይረባ ቀልድህን ተወኝ ሰማኸኝ!›› ሲሉ አፈጠጡበት

ፔርሲ ነገሩ ስላላማረው ‹‹መጸዳጃ ቤት ልሂድ አሞኛል›› አለና ትቷቸው ሄደ፡ ማርጋሬት እሷና ፔርሲ አባታቸውን መቃወም እንደሚችሉና ምንም እንደማያመጡ አውቃለች፡ ይህም አንድ እድገት ነው ስትል አሰበች፡

‹‹ከቤታችን አባረው እንድንሰደድ ያደረጉን እነዚህ ሰዎች መሆናቸውን
እንዳትረሺ›› አሏት አባት ማርጋሬትን፡፡ ‹‹ከኛ ጋር የሚሄዱ ከሆነ ስርዓት
መማር አለባቸው›› አሉ፡

‹‹ቃ!›› ሲል ተደመጠ አንድ ድምጽ

ማርጋሬት ድምጹ ወደመጣበት አቅጣጫ ዞረች፡ ይህን ያለው ፎየንስ
ላይ የተሳፈረው መርቪን ላቭሴይ ነው፡፡ መርቪን እሳት ጎርሶ እሳት ለብሶ
የኦክሰንፎርድን ቤተሰብ ጠረጴዛ ተደግፎ ቆሟል። አስተናጋጆቹ በድንጋጤ
ደርቀው ቆመዋል፡ ጠብ ይነሳል ብለው ፈርተዋል፡ ላቭሴይ የሰማይ ስባሪ
የሚያክል፣ ዕድሜው በአርባዎቹ ውስጥ የሚገመትና ጸጉሩ ገብስማ መልከ መልካም ሰው ነው፡፡ ሲያዩት የሚፈራው ነገር ያለ አይመስልም፡ የለበስው
ልብስ ውድ መሆኑ ያስታውቃል፡

‹‹ይህን አመለካከትህን ለራስህ ያዘው›› አላቸው በሚያስፈራ ድምጽ“

‹‹አንተን አያገባህም!›› አሉ ኦክሰንፎርድ።
‹‹ያገባኛል!››
ማርጋሬት አስተናጋጁ ውልቅ ብሎ ሲሄድ አየችው፡ የአይሮፕላኑን አስተናጋጆች ሊጠራ እንደሄደ ተገንዝባለች፡፡

‹ስለ እኚህ ሰውዬ ምንም አታውቅም፡፡ ፕሮፌሰር ሃርትማን ባንተ አፍ የሚጠሩ ሰው አይደሉም፡፡ በዓለም ላይ አሉ የሚባሉ ሳይንቲስት ናቸው››
አለ ከመቆርቆር በመነጨ ብርቱ ስሜት፡

‹‹የፈለገውን ቢሆን ግድ የለኝም›› አሉ ኦክሰንፎርድ፡
‹‹አንተ ግድ ባይኖርህ እኔ ግድ ይኖረኛል፡ ስለዚህ ይህን የከረፋ አስተሳሰብህን አስተካክል›› አለ ላቭሴይ፡

እኔ የፈለኩትን ማለት እችላለሁ›› አሉና ኦክሰንፎርድ ከመቀመጫቸው ተነሱ፡
ላቭሴይ በጠንካራ እጁ የኦክሰንፎርድን ትከሻ ተጫነና አስቀመጣቸው፡፡
እንዳንተ ካሉ ሰዎች ጋር ነው ጦርነት የገጠምነው›› አለ፡፡

ኦክስንፎርድም በደከመ ድምጽ ‹‹ልቀቀኝ! ልቀቀኝ!›› ሲሉ ተወራጩ።

‹‹አፍህን የምትዘጋ ከሆነ ነው የምለቅህ››

‹ካፒቴኑን እጠራለሁ›› አሉ ኦክሰንፎርድ፡

‹‹አያስፈልግም!›› አለ ሌላ ድምጽ፡ ካፒቴን ቤከር ሙሉ ዩኒፎርሙን ለብሶ ቆሟል የአዛዥነት መንፈስ ይታይበታል፡ ‹‹ሚስተር ላቭሴይ ወደ ቦታህ ብትመለስ?›› አለ፡

‹‹እኔ ወደ ቦታዬ እመለሳለሁ›› አለ ላቭሴይ ‹‹ነገር ግን በመላው
አውሮፓ ትልቅ ክብር የሚሰጣቸው ሳይንቲስት በዚህ ሰካራም ሲሰደቡ
በዝምታ ማለፍ አልችልም፡››

‹‹ሚስተር ላቭሴይ ወደ ቦታህ›› አለ ቤከር፡

ላቭሴይ ወደ ቦታው ተመለሰ፡፡

ካፒቴኑም ወደ ኦክሰንፎርድ ዞር አለና ‹‹ሎርድ ኦክሰንፎርድ የተናገሩት
ነገር አስነዋሪ ነው፡ አንድ ተሳፋሪ ሌላውን ተሳፋሪ መስደብ አይችልም፡››

ማርጋሬት አባቷ የቤከርን ምክር እንዲቀበሉ ብትፈልግም እሳቸው ግን
ጠብ ጠብ እንዳላቸው ነው፡፡

‹‹አንተ ይሁዲ ብዬ ነው የጠራሁት፡፡ ይሁዲነቱን ሊክድ ነው!›› ሲሉ
አምባረቁ፡፡

‹‹አባባ ምነው ዝም ብትል›› ስትል ተቆጣች ማርጋሬት፡

‹‹እዚህ አይሮፕላን ውስጥ እስካለሁ ድረስ ማንንም እንዲሳደቡ አልፈቅድም›› አለ ቤከር፡

አባት ስድባቸውን ቀጠሉ ‹‹በይሁዲነቱ ያፍራል እንዴ?›› አሉ፡

ቤከር በቁጣ ገነፈለ፡፡ ‹‹ይሄ የአሜሪካ አይሮፕላን ነው ጌታዬ እኛ ደግሞ ጥብቅ የስነ ምግባር ደንብ እንከተላለን፡፡ ሌሎች ተሳፋሪዎችን መሳደብ
ካላቆሙ አይሮፕላኑ በሚቀጥለው በሚያርፍበት ቦታ ላይ ለፖሊስ አስረክቦታለሁ፡፡ ምንም እንኳን አልፎ አልፎ የሚከሰት ቢሆንም እንዲህ
አይነት ነገር ሲገጥም አየር መንገዱ ህግ የጣሱ ሰዎችን ይከሳል›››

ሎርዱ የክስ ነገር ሲነሳ ፍርሃት ፍርሃት አላቸው፡ የሚመጣውን በመፍራትም አፋቸውን ዘጉ፡፡ ማርጋሬት በእጅጉ በሃፍረት ተሽማቀቀች አባቷን ዝም ለማሰኘት ብዙ ብትጥርም የአባቷ አድራጎት አንገት
አስደፍቷታል ቅሌት ውስጥ የገቡት አባቷ ስለሆኑ::

‹‹ወደ መቀመጫችን እንመለስ›› አሉና አባት ተነሱ ወደ ሚስታቸውም ዞር ብለው ‹‹አንሄድም የኔ ውድ?›› አሏቸው።

ሁሉም ሰው ማርጋሬት ላይ አፈጠጠባት፡፡ በዚህ ጊዜ ሄሪ ከየተ መጣ ሳይባል ከመቀመጫዋ ኋላ መጥቶ ወምበሯን ያዝ አደረገላት” ሌዳ ማርጋሬት›› አለ በአክብሮት በመጠኑ አንገቱን ዝቅ አድርጎ ማርጋሬት በሄሪ አድራጎት ልቧ ተነካ፡፡

እናት ጅንን ብለው ፊታቸው ላይ ምንም የእፍረት ምልክት ሳይታይባቸው ባላቸውን አስከትለው ወጡ፡፡

ሄሪ ለማርጋሬት በጨዋ ደምብ ክንዱን ሲሰጣት ክንዷን ከክንጿ ጋ ቆላለፈች፡፡ ይሄ ትልቅ ነገር ባይሆንም ለእሷ ግን አንድ የሆነ መተማመን ፈጥሮላታል፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በእፍረት ቁንጫ አክላ የነበረችው ማርጋሬት በመጨረሻ በሄሪ እርዳታ በክብር ወደ ቦታዋ ተሸኘች፡፡ ከሄሪ ጋ ወደ መቀመጫዋ ስትመለስ ድምጹን አጥፍቶ አምባጓሮውን እንደ ትርኢት
ሲመለከት የነበረው ተሳፋሪ ከኋላ ሲንሾካሽክ ሰማች፡

‹‹አንተ ጥሩ ሰው ነህ፡፡ እንዴት እንደማመሰግንህ አላውቅም›› አለችው
ሄሪን፡፡

‹‹የተፈጠረውን አታካሮ ስመለከት ነበር፡፡ በአባትሽ አድራጎት አንገትሽን
ስትደፊ ሳይ አሳዘንሽኝ፡፡››

‹‹እንደዚህ ቀን በሃፍረት ተሸማቅቄ አላውቅም›› አለች እየተንገፈገፈች

አባቷ ግን አሁንም አደብ አልገዙም፡፡ ‹‹አንድ ቀን ይቅርታ ይጠይቁ ይሆናል እነዚህ ጅሎች!›› አሉ፡ ሚስታቸው አንድ ቃል ሳይተነፍሱ እጥግ
ተቀምጠው ባላቸውን በአግራሞት ያይዋቸዋል፡፡

‹‹ይህ ጦርነት ያበቃና! ምናለ በሉኝ›› አሉ
አባት፡፡
👍14
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ

ሶራ ሲያገኛት በጭቃ ልውስውስ ብላ ሰው አትመስልም። ጦርሷቿ ይፏጫሉ ሰውነቷ ይንቀጠቀጣል አካሏ የማታዝበት በድን ሆኗል። በጀርባው ያዘለውን ፈቶ በፕላስቲክ የተጠቀለለ ስሊፒግ ባግ አውጥቶ የበሰበሰና በጭቃ የተለወሰ ልብሷን አውልቆ ፎጣ አልብሶ ስሊፒግ ባግ ውስጥ እየጎተተ አስገባት።

በውርርድ ደረቅ ቦታ የለም ደለሉ በሙሉ ጨቅይቷል ውሃ ተኝቶበታል ስለዚህ ሶራ በቶሎ ከዚህ አካባቢ መራቅ እንዳለበት አምኖ ጀልባዋን ለማምጣት ሄደ።

ሶራ የፕላስቲክ ጀልባዋን በኦሞ ወንዝ ዳር ለዳር እየቀዘፈ ኮንችት ወዳለችበት ሄደ።ከጀልባዋ ወርዷ ወደኮንቺት ሲጠጋ አትሰማም። እንቅልፍ ጭልጥ አድርጎ ወስዷታል።
የጀርባ ቦርሳቸውን ከጫነ በኋላ እሷን ጀርባው ላይ
አስተካክሎ በሰፊ ቀበቶ ከገላው ጋር አሰራትና የጀልባዋን ገመድ ፈቶ
ቀስ ብሎ ጀልባዋ ላይ ወጣ፡ hዚያ ጆልባዋ ወለል ላይ ትራስ አድርጎ
አጋደማትና ከጀልባዋ በስተኋላ እግሩን አንፈራጦ ቁጭ ካለ በኋላ መቅዘፍ ጀመረ"

ቀኑ ፀሐያማና ነፋሻማ ነው፡፡ ኮንችት ወዲያ ወዲህ ሳትል
ተንጋላለች፡ ሶራ ትንሽ ሲቀዝፍ ይቆይና ጆሮ'ውን ልቧ ላይ ይደቅናል። ከዚያ ተመልሶ ደግሞ ይቀዝፋል…
የሞላው የኦሞ ወንዝም ቁልቁል መግፋቱን እየረዳው እስከ ቀኑ አስራ አንድ ሰዓት ተኩል ድረስ ተጓዘ፡፡

ኮንችት በስፓኒሽ “ውኀ" ትለውና አንገቷን ቀና አድርጎ
ሰሰጣት ጎንጨት ታደርግና ትተኛለች፡ ርሃቡ ራሱ ሊጎዳት እንደሚችል ቢያምንም ጀልባዋን ሊያቆምበት የሚችል የተሻለ ቦታ በማጣቱ እግር ጉልበት እየጨመረለት ብዙ እንደተጓዘ ሜዳማ ደረቅ• ጨሌ ሣርና ጥላቸው ዘርፈፍ ያሉ ዛፎች ዘንድ ደረሰ፡፡ ቀስ ብሎ  እየቀዘፈ ጀልባዋን ወደ ዳር አስጠጋና ኮንችትን እንዳይጫናት
ተጠንቅቆ በጀርባው አዘላትና ቀስ ብሎ
ቁጭ አለ፡፡ ጀልባዋ
ስለምትንቀሳቀስ ጀልባዋን እንደገና ወደዳር
ይበልጥ አስጠግቶ
እንደተቀመጠ ተንጠራርቶ ወንዙ ዳር ላይ ያለ የዋርካ ሥር ያዘ ያለው እድል ያ ብቻ ነበር።

መቅዘፊያውን ከጀልባዋ ላይ ፈቶ ወደ ውሃው ውስጥ ከቶ ለካው፡፡ መሬቱን ነክቶ ለመሻገር ኮንችትን አዝሉ እስከ አንገቱ ውሃ
ውስጥ መነከር አለበት፡፡ ምናልባት ከታች ያለው መሬት ድቡሽት
ከሆነ ስለሚሰምጥ እሷን ይዞ ለመዳን ይፍጨረጨር ይሆናል፡፡ እሷን አዝሎ ግን ካልተመቸው እንደተመኘው ሁለቱም እንደተዛዘሉ
አብረው ከአስቸጋሪው ሕይወት ለዘላለም ያርፋሉ፡፡ሶራ አሁን አልፈራም፡፡ ተለያይቶ ከመሞት አብሮ መሞትን ይመረጣል፡፡
በአርግጥ ሞትን ሊያመልጥ ብዙ ተጉዟል፡ ብዙ ሸሽቷል፡፡ ሞትን ግን ሊያመልጠው አልቻለም፡፡ ለሁሉም ወረቀት ፅፎ ሊያስቀምጥ ፈለገ፡ አዎ የሷም ሆኑ የእሱ ዘመዶች ሙት እንደሆናቸው መጠን እንደማንኛውም ሰው  መሞታቸውን አውቀው ልሳቸውን በማውጣት በነሱ ላይ ያላቸው አጉል የተስፋ ህልማቸው ሊቆም ያስፈልጋል የእሱንም
የእሷንም ስም አድራሻ… ፃፈና በላስቲከ አስሮ ወገቡ ላይ ባሰረው ውሃ የማይገባው ላይነን ቀረጢት ከተተው፡፡

ከዚያ ውሃው ሲወስዳቸው እንዳይለያዩ በሌላ የዕቃ ማሰሪያ ቀበቶ በሷና እሱ ትከሻና ጉያ ስር አሰረው፡፡
“እፎይ  ድሮ ሞትን እንዴት እፈራው ነበር፡፡ አሁን ግን
ቢያንስ መሞቴ እንደማይቀርልኝ አመንሁ! ከማንም ሰው  በላይ
የመሞቻ ጊዜዬ መድረሱን ከነደቂቃው አውቄያለሁ, ከፍቅረኛ ጋር ደግሞ ወደ ሞት መሄዴ የሙት ዕድለኛ ያደርገኛል" ብሎ እዕዋቱን
ሰማዩን የማታዋን ጀንበር ከማህደሩ መግደያ ሰይፉን በመምዝ ላይ ያለውን የኦሞን ወንዝ አየና የዋርካ ስሩን ጠበቅ አድርጎ ይዞ
ከጀልባዋ ወደ ውሃው ውስጥ ገባ፡፡

የኢትዮጵያዊውን አያቷን እትብት የተቀበረበትን ለመፈለግ ደክማ ያልተሳካላትን ቆንጆ ውሃው ውስጥ እየገባ አያት፡፡ ከዚያ
ውሃው አሰመጠው? እንደፈራው ከደረቱ አላለፈም፡፡ ስለዚህ በዛፉ
ሥር አማካኝነት እየተጎተተ ወደ ውጭ ወጣ፡፡ መከራና ስቃይን ውጦ እንደጨረሰ ሁሉ ፊቱ በደስታ ፀዳል በራ፡ በቅፅበት ከመከራ
ወደ ደስታ ተመለሰ፡፡

ከዚያ ጫካ ውስጥ ገብቶ የደራረቁ እንጨቶችን ለቅሞ
አመጣና ውኃ የማያበላሸውን ክብሪት ጭሮ እሳት አቀጣጠለ፡፡
ከጀልባዋ ላይ ያለውን የጀርባ ሻንጣ አውርዶ ለኮንችት ፓንት ሣይቀር ቀይሮ እሳቱ ዳር አስተኛትና ለችግር ጊዜ ብለው የያዟትን
ትንሽ ድንኳን ዘረጋ፡፡

ከጀርባ ሻንጣው ተጣጣፊ መጥበሻና ብረት ድስት አውጥቶ ለችግር ጊዜ ካስቀመጡት ምግብ መካከል የሚበላ አዘጋጀና ሻይ  አፈላ ኮንችት ቀስ በቀስ ዓይኖቿን መግለጥ ስትጀምር የአይብና አሳ ሳንዲዊች ወደ አፏ አስጠጋላት ከጭኖቹ ደገፍ እንዳለች ሳንዱቹን ገመጠች ሻየለንም መጠጣት ጀመረች።

ከዚያ የራስ ምታታ መድሃኒት እንደዋጠች ፈሳሽ ቅባት ጀርባዋን ጭኖቿን ክንዷን ፊቷን እያሸላት  እቅልፍ ይዟት ሄደ ቀስ አድርጎ አቀፈና ድንኳን ውስጥ አስተኛት።

የሱ እስሊፒግ ባግ ካንጠለጠለበት ዛፍ ላይ ንፋሱ ሲያወዛውዘው ጠፈፍ እስኪልለት እሳቱ ዳር ጋደም አለና ሽቅብ ወደ ሰማይ አየ። ሰማዩ ጥርት ያለ ደመና አልባ ነው አየሩ በደንብ እንደበዘቀዘ እርጎ የሚገመጥ ነው ተወርዋሪ ኮኮቦች ይወረወራሉ ጨረቃ ትንሳፈፊለች ድንቁ ተፈጥሮ እንደገና የሚያስጓመጅ ሆኗል ቀናት ያልፋሉ ዛሬም አይቀርም ያልፋል ግን በሚያልፍ ጊዜ ስንቱ አዝኖ ስንቱ ይደሰታል?

እኩለ ሌሊት ላይ የትንሿ ድንኳን ዚፕ ጢዝዝዝ ብሎ ተከፈተ ጨለማው በጨረቃ ብርሃን ድል ተነስቷል የእሳቱ ነበልባል ጠፍቷል ፍሙ ግን አለ አጠገቡ ኩርምትምት ብሎ የተኛው ሶራ ነገር አለሙን ዘንግቶ እንቅለሰፉን ይለዋል።

ኮንቺት እጇን ግንባሩ ላይ አስቀመጠች ሶራ አልተንቀሳቀሰም ዝቅ ብላ አየችው። ተመልሳ ደግሞ የሆነውን ሁሉ ለማስታወስ ሞከረች ሰመመናዊ ህልሟ ሳይቀር።

ሶራ ከዚያ መአትና የጫካ አውሬ አፍ አውጥቷታል አሁን ግን ያሉበት ተፈጥሮ እየነፈሰ ስሜትን የሚኮረኩር ነው። እንደገና አየችው ሶራ የለበሰው ስሊፒግ ባግ እርጥብ በጭቃ የተለወሰ ነው።

ዝቅ ብላ ከንፈሩን ሳመችውና ቀና ብላ ላፈቅርህ በመቻሌ ደስታ ይሰማኛል አለችው እንደዚያ እንደ ዘቢብ የጣፈጠ አባባሏን ቢሰማ ኖሮ ምንኛ በደስታ በፈነጠዘ የተቃጠለ አንጀቱ እንዴት በራሰ ግን አልሰማትም መልካም ነገር እንዲህ በቀላሉ መቼ
ይሰማል!

ኮንችት ቀስ ብላ የሞቀ ትኩስ  ትንፋሽዋን በጆሮ ግንዱ እያንቦለቦለች

“ሶራ ሶራ..." አለችውና ጭቃ የተቀባባውን አንገቱን
ግንባሩን ስትስመው አይኖቹን እንደምንም ብሎ ከፈተደ።

“ሶራ" ያ ሙዚቃዊ ጣዕም ያለው ድምፅ ጆሮው ላይ
አዜመ። ለመንቃት ታገለና አያት

ኮንችት! ጥርሱ ሳቀና አይኑ እንባ ሞልቶ ወደ ጎን ወደ
ጆሮ ግንዱ ፈሰሰ፡ ኮንችት እንባውን በምላሷ ቀመሰችው በፍቅር
የተቀመመ ጣፋጭ ነው  እንባው!

“አፈቅርሃለሁ የእኔ ማር!'' አለችው። ሶራ አባባሏ
“አታፍቅሪኝ ኮንችት!  ካፈቀርሽኝ ፍቅሬ ይከብድሻል ከከበደሽ ደግሞ ወርውረሽ ትጥይውና ትጠፊብኛለሽ:: ያኔ መከራ ይውጠኛል: ስለዚህ…" ከንፈሩን በከንፈሯ ከደነችው:: ከንፈሯ
ትንፋሽዋ ምላሷ. ሙቅ ነው።

ፍቅር ይከብደኛል!
ስፈራው ስሸሸው ኖሪያለሁ:
ካለፍቅር መሞት አልፈልግም የሞትን በር ሳንኳኳ+ የሚከፍቱት
ሲንቀራፈፉ አንተ ነጥቀህ መለስኸኝ። እኔ ደግሞ ፍቅሬን ዘንጥፌ
ልሰጥህ ወሰንኩ! ላለማፍቀር ስሸሽ እንደኖርኩት! ለማፍቀር ደግሞ ቅንጣት ታክል ፍርሃት የሌለኝ ደፋር ነኝ!

ሶራ ተምታታበት፤  ሳታፈቅረው እንዳፈቀራት አብሯት ቢዞር መከራም ገፍቶ ቢመጣ ቀድሟት ቢሞት ደስተኛ ነው።
ፍቅሯን እንደተሸከመው ሁሉ አሷም ፍቅሩን ብትሸከመው ሸክሟን ወርውራ ትሸሸው ይሆን?
👍342😱1
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበር


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

ጥዋት የበረፍ መንኳኳት ነው ከእንቅልፌ ያባነነኘ…በርግጌ ተነሳሁና አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጥኩ…አሁንም በራፉ ይንኳኳል ግን የውጭ በራፍ ሳይሆን ከአያቴ ጋር የምንወሰነበት ተከፍቶ ያማያውቀው የውስጡ በራፍ ነው የሚንኳኳው…‹‹ውይ ልጅቷን ረስቼያት… በፈጣሪ ምን አይነት ዝፍዝፍ ሰው ነኝ? .እስከ አሁን እንግዳ እያለብኝ እንዲህ ነገር አለሙን ችላ ብዬ እተኛለሁ…?ይሄኔ እኮ እርቧት ይሆናል….?››

‹‹ማራናታ… ደህና አደርሽ?.››

‹‹አዎ ደህና አድሬያለሁ….ልግባ…ልብስህን ለብሰሀል?፡፡››ግራ አጋቢ ጥያቄ ጠየቀቺኝ፡፡

‹‹ውይ እሱ በራፍ የታሸገ ነው …ቆይ በፊት ለፊት ዞሬ መጣሁ..››

‹‹አይ እሽጉን ትናንት አያቴ አስነስቶት ነው የሄደው››…ከሚል ድምፅ ጋር የበር መንሳጠጥ ተሰማና ወለል ብሎ ተከፈተ..ውይ የተሰማኝ ስሜት…. በቅዱሳን መላዕክቱ የገነት በር ሲከፈት ፊት ለፊት በአይኖቼ እያየሁ  ያለሁ   ነው የመሰለኝ...እና ከበሩ መከፈትም በላይ በተከፈተው በራፍ አንገቷን አስቀድማ በማስገግ ብቅ ብላ ወደእኔ ግዛት የገባቸው ልጅ…  በፈጣሪ ሰይጣን አይደል እንዴ የምትመስለው፣ሰይጣን ክብሩን ከመገፈፉ በፊት…ለነገሩ ክብሩን ከተገፈፈም በኃላም ውበቱን አልተነጠቀም…

‹‹አንቺ ይገርማል..አያቴን አይደል እንዴ የምትመስይው?››ሳላስበው አድናቆት ከአንደበቴ አፈትልኮ ወጣ
‹‹ሽማግሌ ፊት ነው ያለሽ እያልከኝ ነው?››

‹‹ይቅርታ …ማለቴ በጣም ቆንጆ ነሽ ለማለት ፈልጌ ነው….››አዎ እውነቴን ነው …ልጅቷ ልክ አያቴን ነው የምትመስለው…ልቅም ያለች የጥቁር   ልጥልጥ  ውብ ነች…፡፡ልክ እንዳየኋት ልቤ ቢጫ ወባ እንደነደፈው ሰው ነው በደቂቃ ውስጥ ፍርፍር ስትል የተሰማኝ፡፡
‹‹ለማንኛወም ቁርስ መብላት ከፈለክ ና ቀርቧል….››ብላኝ በራፉን ክፍት ጥላ ተመልሳ ወደውስጥ ገባች፡፡እንግዳ ሲያፍር ባለቤት ይጋብዛል አሉ….ሲሆን ሲሆን ለሊት ተነስቶ ቁርስ በመስራት እሷን መቀስቀስ የነበረብኝ እኔ ነበርኩ..ዳሩ አጅሪቷ በየት አሲይዛ …በሁሉ ነገር ጥድፍ ጥድፍ ትላለች፡፡በፈጣሪ በዚህ አይነት አጀማመር ይህቺን አንድ ወር እንዴት ነው ተቋቁሜ የምዘልቀው…? አያቴ ምን ነካቸው..?ይሄንንማ አውቀው ሆነ ብለው እኔን ለመፈተን ያደረጉት ነገር ነው፡፡ወይ እዳዬ ለዘመናት ከዳከርኩበት እና ፍዳዬን ካየሁበት የፍቅር ታሪክ ገና ትናንትና መደምደማሚያ አበጅቼለት ተገላገልኩ ስል….

‹‹እዬቤ...››ጥሪው ከተዘፈዘፍኩበት ሀሳብ መዞ  አነቃኝ

‹‹አቤት››

‹‹ቁርሱ ቀዘቀዘ እኮ….በዛ ላይ እርቦኛል››

ተንደርድሬ ተነሳሁና ፊቴን ተለቃልቄ ልብሴንም ሳልቀይር በለበስኩት ቢጃማ ተንንርድሬ ሚቀጥለው ክፍል ገባሁ…..እንግዲህ ይታያችሁ እዚህ ቤት መኖር ከጀምርኩ ሶስተኛ አመቴ ውስጥ ብሆንም አሁን ያለሁበትን ክፍል ስረግጥና የውስጥ ገፅታውን ሳይ ዛሬ የመጀመሪያ ቀኔ ነው፡ክፍሉ በስርአት ቦታቸውን ይዘው በተቀመጡ የቤት እቃዎች የተሞላ ነው፡፡ ቢያንስ ሶስት ቦታ በመፅሀፎች የተሞሉ መደርደሪያዎች ይታያሉ…አልጋው በስርኣት ተነጥፏል፡፡  አልጋውን ተጠግቶ ያለው መካከለኛ መጠን ያለው ጠረጴዛ በምግብ ተሞልቷል…

‹‹ምን ይገትርሀል አልጋ ጠርዝ ላይ ቁጭ በል ››አለችኝ

የእሷን  ግብዣ ችላ አልኩና ግድግዳ ተደግፎ ያተቀመጠ አንድ ደረቅ ወንበር በማንሳት ወደምግብ ጠረጴዛው አስጠግቼ በመቀመጥ አንዴ የቤቱን ዙሪያ መልሼ ደግሞ እሷን ከስር አስከላይ መቃኘት ጀመርኩ… አቀራርባ ስትጨርስ ፊት ለፊቴ አልጋ ጠርዝ ላይ ቁጭ በማለት እሷም ለመብላት ዝግጁ ሆና እጇን ወደምግቡ እየሰደደች‹‹..በል ብላ››.አለችኝ..

‹‹ይሄን ሁሉ ምን ጊዜ ሰራሺው?››የገረመኝን ጥያቄ ጠየቅኳት.፡፡

‹‹እቤትህ ሰዓት የለም እንዴ..?ሶስት ሰዓት ሊሆን እኮ ነው››አመሏ ከመልኳ ተቃራኒ ነው..እስከአሁን እንዳየሆት ለየትኛውም ጥያቄ ቀና መልስ መስጠት አይሆንላትም…

‹‹ይቅርታ .እንቅልፍ ጣለኝ››

‹‹አያቴ ጠንካራ ሰራተኛ ነው እያለ ሲፎክርብህ የነበረው እንዲህ እየተኛህ ነው እንዴ?››

‹‹አጋጣሚ ሆኖ ነው..›› የጠቀለልኩትን ምግብ እየጎረስኩ መለስኩላት፡

‹‹እሺ ቢሾፍቱ ዛሬ ትወስደኛለህ ?››አዲስ ርዕስ ከፈተች

‹‹ለምን…?መሄድ ትፈልጊያለሽ?››
‹‹አይ የስራህ ቦታ እዛ አይደለ? ስራ ከሄድክ አብሬህ ለመሄድ ብዬ ነው››
‹‹እ ….እንደዛ ነው….ዛሬ ሳይሆን ነገ ነው የምሄደው ….ነገ አብረን እንሄዳለን….ዛሬ የሆነ ጓደኛዬን ከአገር ውጭ ስለምትሄድ እሷን እንሸኛለን››

‹‹እ… .ጄኔራሏን?››

‹‹ምን….?በምን አወቅሽ…?››.ደንግጬ

‹‹ይሄውልህ ስለአንተ የማላውቀው እንዲህ ቆንጆ መሆንህን ብቻ ነበር… አሁን ደግሞ እሱኑም አወቅኩ››ብለኝ እርፍ
‹‹እንዴት…?አሀ ይሄን ሁሉ የነገሩሽ አያቴ ናቸው?››

‹‹አዎ  አያትህ…በነገራችን ላይ አያቴ በየደብዳቤው ስለአንተ ሲዘበዝብልኝ በጣም እበሳጭበት ነበር››

‹‹ለምን? ቀንተሸ?››

‹‹አዎ ብቀና ይፈረድብኛል..?እኔ በአያቴ ቀልድ አላቅም...እና ብቸኛ የልጅ ልጁ ሆኜ መቀጠል ነበር ምፈልገው..››

‹‹እና አሁንስ?››ስል ጠየቅኳት በመገረም፡፡

‹‹አሁንማ አንደኛ አባቴ ከዛች የተረገመች ሚስቱ ሌላ ልጅ ስለወለደ ብቸኛ የልጅ ልጁ መሆኔ ማክተሙን አምኜ ተቀበልኩ ….ሁለተኛ እኔም ሳላስበው ታሪክህን ቀስ በቀስ ሲያስጠናኝ የእውነትም አያቴ አያትህ ይመስለኝ ጀመር…››

ተበሳጨሁ… ልጎርስ አፌ ላይ ያደረስኩትን ምግብ መልሼ ትሪው ላይ በትኜ ተነሳሁና‹‹ምን ለማለት ፈልገሽ ነው..?››አፈጠጥኩባት

‹‹አቦ ምን ለማለት ፈልገሽ ነው ማለት ምን ማለት ነው?››እሷስ መች የዋዛ ሆነችና በተቀመጠችበት መልሳ አፈጠጠችብኝ፡፡

‹‹አያቴ ስል ለማሾፍ ወይም ለፉገራ ይመስልሻል…?የእውነት አንቺ ከእኔ በላይ እራስሽን ባለመብት አድርገሽ መጎረርሽ ነው..?››ወረድኩባት
‹‹ባለመብቱንማ በተግባር አየነው እኮ…. እኔ እኮ አይደለሁም የአንድ ሚሊዬን ብር ቼክ የተፃፈልኝ…አሁን እንብር እንብር አትበል ቁጭ በልና ቁርስህን ጨርስ .ደግሞ አያቴን የነጠቅከኝ ሳያንስ ስድብ ትመርቅልኛለህ….አረ አይነፋም…››

በንግግሯ ተሸነፍኩና ተመልሼ ቁጭ አልኩ…ገና በመጀመሪያው ቀን ይሄን ያህል ከተጮጮህን ዋል አደር ስንል..ወይኔ ጉዴ…ጨነቀኝ፡፡

አንድ ክፍል ቀረው
👍17915😁11🥰4👎3🔥2
#ባል_አስይዞ_ቁማር


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///

ከክስተቱ በኃላ መድህኔ ልዩ ቤት ድረስ አይኑን በጨው አጥቦ ሊያናግራትና ይቅርታ ሊጠይቃት መጥቶ ነበር..የመኝታ ቤቷን በራፍ ግን ልትከፍትለት አልፈቀደችም…ለእናቷም የሰርግ ዝግጅቱን እንዲያቆሙና ከመድህኔ ጋርም  ፍፅም እንደማትጋባ ስትነግራቸው. መጀመሪያ በጊዜያዊ ንዴት ተገፋፍታ የተናገረችው ነው ብለው ትኩረት አልሰጡትም ነበር…ውሎ አድሮም ምንም አይነት የመርገብም ሆነ የመረጋጋት ሁኔታ ስላልታየባት እየደነገጡ ሄዱ….ከዛ ምክንያቱን እንድትነግራቸው አምርረው ጨቀጨቋት…‹‹ከጓደኛዬ ጋር ሲማግጡ አንድ አልጋ ላይ ያዝኳቸው›› ብላ እቅጩን ነገረቻቸው…ባለማመን እራሱ መድህኔ ጋር ደውለው ጠየቁት…አላደረኩትም ብሎ ሊክዳቸው አልቻለም...ከዛ እሷቸውም እጥፍ በሆነ ምሬት መድሀኔን ተቀየሙት… እሷን መጨቅጨቁንም ሆነ የሰርጉን ወሬ እርግፍ አድርገው በመተው ልጃቸው ብቻ በብስጭት አንድ ነገር እንዳትሆንባቸው  በስስት መከታተላቸውን  ቀጠሉ፡፡

ስለጊፍቲ ሁኔታ ደግሞ ቃል አንድ ሁለት ቀን  እቤቷ ድረስ በመሄድ እንዳገኛትና ያለችበት ሁኔታ የከፋ የሚባል እንደሆነ ነገሯታል….መድሀኔና ጊፍቲም ተገናኝተው እንደማያውቁ ሲነግራት ስጋት ውስጥ ገብታለች።

‹‹በዚህ የቃል ሀዘኔታ  ጊፍቲ እግሩ ላይ ወድቃ ይቅርታ ብትጠይቀው አይኑን ሳያሽ ነው ይቅር የሚላት።››ስትል ስጋት ውስጥ ነች፡፡ምን ማድረግ እንዳለባት ግራ ተጋብታለች፡፡

ጊዜ ተለዋዋጭ ነው…በተለያ ሁኔታ ውስጥ ሊለጠጥና ሊኮማተር ሊረዘምና ሊያጥር ይችላል፡፡ጊዜ በተለያዩ የሰማይ አካላት ላይ ባላቸው ፍጥነት መጠን ልክ የተለያየ መጠን አለው፡አንድ ዓመት ርዝመት  በምድር ላይ እና በማርስ ላይ በጠጣም የተለያየ ነው…
በፍጥነት በሚጓዙ .የሰማይ አካላት  ላይ ሰዓት ሲኮማተር ዝግ በሚሉ ብለው በሚጓዙት ላይ ደግሞ ጊዜ ይለጠጣል ወይም ይረዝማል፡፡
አልበርት አንስታይን በቴኦሪ ኦፍ ሪላቲቪቲ መሰረት  የአንድ ቁስ ጉዞ ከብርሀን ፍጥነት በላይ በሚሆንበት ጊዜ ወደ ትናንና  ይጓዛል የሚለውን አረጋግጧል..ይሄ ማለት   የታይም ትራቭለር ሀሳብ  በዚህ ስሌት የሚሰላ ነው ፡፡
ይሄን ያሰበችው ቃልን ከማግኘቷ በፊት ያሳለፈችው ጊዜ ሲቆጠር ረጅም አሰልቺ አይነት ሲሆን አሱን  ካገኘች በኃላ ያሳለፈችው በሚዛኑ የቀኝና የግራ ሰሀን ላይ ቢቀመጥ  የትኛው በልጦ ይገኛል? ፡፡
ከቃል ጋር እያወራች ነው..እራሱ ደውሎ ነው ከቤት እንድትወጣ ያደረጋት..ምክንያቱም በጣም ልቧ ተሰብሯል…ምክንያቱም የእሱ ጓደኛና እጮኛ የእሷን እጮኛ አማግጣባታለች...ወይንም እርስ በረሻቸው ተመጋግጠዋል….ስለዚህ አፅናኝ ትፈልጋለቸ፡፡ይሄው አሁን ቃል እያደረገ ያለውም ያንን ነው፡
‹‹ልዩ የምሬን ነው በጣም ነው ያዘንኩት ..ልብሽ እንዲሰበር ስላደረኩ ይቅርታ›› አላት አንጀት በሚበላ  አሳዛኝ ንግግር፡፡
"አንተ ምን አደረክ...?እንደውም ከእኔ እኩል ተጠቂ ነህ።"
"አይ የእኔና ያንቺ አንድ አይደለም .›አላት፡፡
.‹‹ምን? የእኔ የራሴ ጥፍት ነው"ምን ለማለት እንደፈለገ ግልፅ አልሆነላትም‹ምን ማለትህ ነው?›ስትል ጠየቀችው፡፡
"ኃላፊነቴን ባለመወጣቴ ምንም ነገር ብታደርግ በእሷ ላይ ጣቴን የመቀሰር ሞራል የለኝም..ብቻ ከአንቺ  እጮኛ ጋር ለምን እንዳደረገችው ነው ሊገባኝ ያልቻለው?"
"ከእኔ እጮኛ ጋር ሆነ ከሌላ ጋር ምን ለውጥ አለው ..ክህደት ያው ክህደት ነው?"

"አይ እኔ ከድታኛለች ብዬ አላስብም...ጊፍቲ መቼም እኔን ልትከዳኝ አትችልም...ግን ከእኔ የምትጠብቀውን ለዘመናት ጠብቃ ስላጣች..ያደረገችውን ማድረጓ  ያንስባት እንደሆነ እንጂ  አይበዛባትም፡፡"

"እና አሁን ወደአንተ መጥታ ይቅርታ የምትጠይቅህ አይመስልህም"
"ይቅርታ..."
የመደነጋገር ስሜት ታየበት..‹‹ጊፈቲና መድህኔ ተበዳይ እእጂ በዳይ እይደሉም..ይቅርታ መጠየቅ ያለብን እኔና አንቺ ነን..››በማለት በውስጡ አያሰበ በአንደበቱ ግን"አይ ይቅርታ  የምጠይቃት እኔ ነኝ...... ጥፋተኛው እኔ ስለሆንኩ ላባከንኩት ጊዜዋ፤ላልከሰከስኩት ተስፋዋ፤ለሁሉም ነገር  ይቅርታ እጠይቃታለሁ።"አላት፡፡
ልዩ ሰውነቷ ሁሉ በፍርሀት መንዘርዘር ጀምሯል...ያ ሁሉ ልፋቷ ያ ሁሉ ጥረቷ   በዚህ ሰው አጉል የዎህነት ገደል  ሊገባባት እንደሆነ ታሰባትና ውስጧ በንዴት ተቃጠለ።እንዲህማ አያደርገኝም....፡፡
"እና ይቅርታህን ከተቀበለች በኃላ እንደድሯችን እንሁን ብትልህ እሺ ትላለህ?"
"ምን አልሽ? እንደውም እንደድሯችን መሆን አንችልም  ካለቺኝ  ነው እሺ ማልላት...እንደዛ መቼም አይሆንም፡፡"
"እንዴ ይሄ ምን የሚሉት ግራ የተጋባ ነገር ነው...ከእኔ ባል ጋር ፍቅር ይዞት ከሆነስ ...?እሱን ለማግባት ፈልጋለሁ ብትልህስ?›› ስትል ጭርጭር በሚያደርግ የንዴት  ጠየቀችው፡፡
"እሱን ማለቴ አይደለም... እንዳልሽው እሱን ታፍቅረውም ለማግባት ትሞክርም.. የእሷ  የራሷ መብቷ ነው። ያንን ምርጫዋን ሆነ ውሳኔዎን አከብርላታለሁ።ግን እሺ ማልላት ጓደኝነታችንን እናበላሽ ካለቺኝ ነው።…አዎ ሲሆን ሲሆን ይቅር ብላኝ ብታገባኝ ደስ ይለኛል.ከልሆና እንዳልሺው አሱን ወዳውም ከሆነ ችግር የለም ዋናው የእሷ ምቾት ነው››አላት…ቃል ንግግሩን ሆነ ብሎ የልዩን የአሸናፊነትና የስኬት ስነልቦና ለመናድ አልሞ ነው እየሰነዘረ ያለው.. እናም ደግሞ ተሳክቶለታል..ልዩ በተሸናፊነት መንፈስ እየተናጠችና በፍርሀት ስሜት እየተንቀጠቀጠች ነው፡፡

‹‹እና አንተን ጥላ መድሀኔንም አግብታ ቢሆን እንደበፊቱ ጓደኛዋ ሆነህ የመቀጠል ፅናቱ ይኖርሀል።››
"እንደዛ ካላደረኩ እኮ መጀመሪያውኑ  አልወዳትም ነበር ማለት ነው"አለትና አስደመማት።
ዝም አለች..."እኔ አሁን የመድህኔ መሳሳት የእኔ ስውር እጅ ስላለበት ይሉኝታ ይዞኝ ትንሽ ቀዝቀዝ አልኩ እንጂ ከእኔ እውቅና ውጭ  ወስልቶብኝ ቢሆን ኖሮ  ዘልዝዬ አልበላውም ነበር?›ስትል በውስጧ እራሷን ጠየቀች..፡፡
" እኔ ግን   መቼም ቢሆን መቼም ይቅር ልለውና  መልሼ እንደድሮችን ልቀበለው አልችልም።››ስትል ፍርጥም ብላ አቋሟን ለቃል ነገረችው፡
"እንደእጮኛ  ተቀበይው ብዬ  ላስገድድሽ አልችልም...ግን ከእዚህ በፊት እንዳጫወትሺኝ ከሆነ መድህኔ ፍቅረኛሽ ከመሆኑ በፊት የልጅነት ጓደኛሽ ነው። በጓደኝነት ህይወታችሁ  ብዙ መልካም ቀናትን… ብሩህ የሆኑ ትዝታዎችን አሳልፋችኋል...እና እሱን ከውስጥሽ እስከወዲያኛው ፈንቅለሽ ስትጥይ የራስሽንም መልካም ትዝታዎችንና ወርቃማ ትናንቶችሽን ነው አብረሽ የምትደመስሼያቸው... እሱን በጎዳሽው መጠን አንቺም ተጎጂያለሽ፡፡.››
"እና ምን እያልከኝ ነው?"
ከደረት ኪሱ እስኪረሪብቶና ብጣሽ ወረቀት አወጣና ሰጣት.::ግራ በመጋባት‹‹ምን ላድርገው?››ብላ ጠየቀችው፡፡
‹‹የምነግርሽን ነገሮች ለመፃፍ ተዘጋጂ››አላት፡፡
ምን ሊለኝ ነው በሚል ጉጉት እስኪርብቶውን ወረቀቱ ላይ ቀስራ መጠባበቅ ጀመርረች፡፡
‹‹መድህኔ በህይወት ጉዞዬ ጎደኛዬ በነበርክ ጊዜ…››
ቀና ብላ አየችው..
‹‹ፃፊው…፡፡››
‹‹መድህኔ በህይወት ጉዞዬ ጎደኛዬ በነበርክ ጊዜ››ብላ  ፃፈች፡
👍6711🥰2🤔1
#ተአምራተ_ኬድሮን


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////

ከልጅቷ ጋር ሲያወሩ እና ከቤት ሲወጡ ሶስት ሰዓት ሆነ….‹‹ፍቅረኛሽ አሁን የት ነው የሚኖረው?፡፡››ጠየቀቻት፡፡

‹‹እዚሁ አዲስ አበባ ቤቴል አካባቢ እቤተሰቦቹ ያወረሱት ቤት ውስጥ ነው የሚኖረው፡፡››

‹‹ፎቶው አለሽ?›› 

‹‹አዎ›› ብላት ሞባይሏን ከፈተችና አሳየቻት፡፡ሞባይሏን ተቀብላ ተመለከተችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ‹‹ተከተይኝ ››አለቻት እና  ወደበረንዳው ወጡ…ንስሯ ተረጋግቶ መቀመጫ ላይ ተቀምጦ ስታየው እንደመፍራትም ግራ እንደመጋባትም አለችና፡፡

‹‹ምን አይነት አሞራ ነው..አይፈራም እንዴ? ››

‹‹የእኔ ነው››

‹‹አሞራው?››

‹‹አዎ…ግን አሞራ ሳይሆን  ንስር ነው…የእኔ ንሰር ፡፡››

‹‹ምን ያደርግልሻል?፡፡››

‹‹እሱማ ለእኔ ብዙ ነገሬ ነው… የፈለኩትን ነገር ያደርግልኛል..እኔ እንደውም የሚገርመኝ እኔ ለእሱ ምን አደርግለታለሁ ሚለውን ነው››

‹‹ይቅርታ ግን ያስፈራል…. .በተለይ አይኖቹ እና መንቁሩ…››እሷን ችላ አለቻትና ሞባይሏ ላይ ያለውን የልጅቷን ፍቅረኛ ፎቶ ለንስሯ እያሳየች ‹‹….እንርዳት መሰለኝ…እወነቱን ማወቅ መብት አላት››ስትለው ክንፎቹን አርገፈገፈና   መቀመጫውን ለቆ በአየር ላይ ተንሳፈፈ…እሷ  በርግጋ ወደኃላዋ አፈገፈገች….ወደላይ ተምዘግዝጎ አየሩን እየሰነጠቀ ከፍታውን ለአይን መታየት እሰከማይችል ድረስ ርቆ ተሰወረ፡

‹‹ቁጭ በይ› አለቻትና በረንዳው ላይ ካለው ወንበር አንዱን እያሳየቻት እሷ ንስሯ በለቀቀላት ወንበር ላይ እየተቀመጠች፡፡

‹‹ሄደብሽ እኮ …እንዲህ እርቆ ሄዶ አሁን አውቆ ተመልሶ ይመጣል?፡፡››

‹‹አዎ የእኔ እወቀት ዘጠና ፐርሰንቱ ከእሱ የማገኘው ነው…ንስሮች በተፈጥሮቸው በጣም ልዩ የሆኑ የአእዋፋት ዝርያዎች ናቸው፡፡እይታቸውም ጥልቅ አስተሳሰባቸውም ስል እና የተሞረደ  ነው፡፡ከዛም በላይ ግን የእኔ ንስር የተለየ ነው፡፡እንዴት የሚለውን ነገር ላብራራልሽ አልችልም..ግን አሁን የሚያደርገውን ታያለሽ ..ከዛ እራስሽ ትፈርጂያለሽ››

‹‹እንዴት?››

‹‹አሁን ፍቅረኛሽን ፎቶ እያሳየሁት ሳወራው አላየሽም?››

‹‹አይቻለው.ግን እናቴም ሲጨንቃት እና በሆዷ ነገር ሲገባ ከምታልባት ላም  ጋር ታወራ ነበር…እንደውም ለእሱ ስታወሪ እናቴ ነች ትዝ ያለችኝ፡፡››

‹‹አይ ይሄ ይለያል..አሁን ያንችን ችግር ማለት ስለፍቅረኛሽ ትክክለኛ ነገር እንዲያጣራልኝ ነው የላኩት››

‹‹እንዲት አድርጎ››

‹‹በቃ የተለየ ችሎታ አለው… ማንኛውም ነገር ካተኮረበት የውስጡን ሀሳብ እና ጠቅላላ ታሪኩን ማንበብ ይችላል…እኔ ደግሞ ከሱ አዕምሮ ማንበብ እችላለሁ..ወይም እንዳውቀው አዕምሮውን ይከፍትልኛል..ቅድም ያንቺን ታሪክ ላውቅ የቻልኩት ከእሱ ነው፡፡››

‹‹እኔ አላምንም ..ንስር ይሄን ሁሉ…. እንዴት  ተደርጎ?››

‹‹አየሽ እንዳልኩሽ የእኔ ንስር ልዩ ነው..ከእኔ  ጋር ያለውም ትስስር ከተፈጥሮ ክስተቶች እንደ አንድ ነው..ያም ሆኖ ግን እንዲሁ ንስር እና የሰው ልጅ ከጥንትም ጀመሮ የመንፈስ ትስስር እንደነበራቸው ታሪክ ይመሰክራል፡፡፡ሌላውን ተይና  በሀገራችን ጥንታዊ ስነ ጽሁፍ ውስጥ ንስር የትንሳኤ ምልክት ነበር… በምጥቀት ማሰብ እና ወደ ከፍታ የመስፈንጠር መንፈስ ተምሳሌ ተደርጎ ይወሰድ ነበር፡፡በግብጽ ደግሞ መቃብራቸውን ጋንኤል እንዳይደፍረው የንስር ምስል ከመቃብሩ በራፍ ላይ ያስቀምጡ ነበር…ያ የንስር ምስል የጋንኤሉ መንፈስ አልፎት ወደውስጥ ሊጋባ ስለማይችል እሬሳቸው ከጥቃት የተጠበቀ ይሆናል ብለው ያምናሉ..፡፡
የጲላጦስ ሀገር የሆነችው ግሪክ ደግሞ ከአመልክቶቾ ውስጥ አንድ የሆነው የአማልዕክቶች ሁሉ ንጉስ የሆነው ዜዎስ በንስር ይመሰል እንደነበረ ይነገራል፡፡በጥንት ጊዜ አሜሪካኖች  ደግሞ እጅግ ለሚያከብሩት የሌላ ወገን ሰው ያለቸውን ጥልቅ ፍቅር ሚገልጽት የንስር ላባ በመስጠት ነው፡፡በመጽሀፍ ቅዱስ ሲራክም  ሶስት እራስ እና አስራ ሁለት ክንፎች ሳላለው ንስር በህልሙ ራዕይ አይቶ ነበር….የራዕይው ፍቺ በየተራ ስለሚነግሱ ነገስታት ሲገለጽለት ነበር…ንስር የኃይልን እና የስልጣን ምልክት ነው፡፡…››ስብከት የመሰለ ንግግሯዋን ተናግራ ሳትጨርስ….ዶክተሩ በራፋቸውን ከፍተው ወጡና ወደእነሱ መጡ

…‹‹.ሶፊ ደህና ነሽ?››

‹‹እንዴት አደሩ ዶክተር?››
‹‹አለሁ….ዛሬ እንግዳ ከየት አገኘሽ ?››አለት እንግዳዋ ላይ በማተኮር፡፡

‹‹አያውቋትም?››

‹‹እኔ እንጃ ከዚህ በፊት ግን ያየኋት ይመስለኛል››

‹‹አዎ ከባሌ የመጣች የአክስቴ ልጅ ነች…ከዚህ በፊትም መጥታ ስለነበረ.. ተገናኝታችኋል››
‹‹ለዛ ነዋ ፊቷ አዲስ ያልሆነብኝ….በሉ ተጫወቱ አንዲት ቀጠሮ አላለችብኝ ..ከሰዓት እንገናኛለን ..›ብለው ተሰናብተዋቸው ወደመኪናቸው ማቆሚያ ጥለዋቸው ሄዱ
ሶፊያ ሳቋ  አፍኗት  ስለነበር እንደራቁላት ለቀቀችው

…‹‹ሳያውቁኝ ቀርተው ነው ወይስ አውቀው ነው?››

‹‹አይ ተምታቶባቸዋል…ያው ማታ መጠጥም ስለሚወሳስዱ ነው ቅር አይበልሽ››

‹‹አረ ምን ቅር ይለኛል ነገራቸው ገርሞኝ እንጂ››ብትልም ቅር እንዳላት ግን በግልፅ ከንግግሯ ቃና በቀላሉ መረዳት ይቻላል፡፡

‹‹እዚህ ቤት ከጥዋት ጀምሮ የሚያጋጥምሽ ነገር ሁሉ ይገርማል አይደል?››

‹‹ምን መገረም ብቻ ከአዕምሮም በላይ ነው….እኔ እንዲህ….››ንግግሯን ሳትጨርስ  ንስሩ እየተምዘገዘገ መጣና ከእነሱ ፊት ለፊት በአምስት ሜትር ርቀት ያህል በሚገኝ የጽድ ዛፍ ላይ ሲያርፍ ስለተመለከተች  አቆረጠችና …ምን እንደሚከሰት ለማወቅ መጎጎቷን በሚያስታውቅባት መንፈስ‹‹መጣ ››አለቻት፡፡

‹‹ትንሽ ታገሺኝ ››አለቻትና አዕምሮዋን ሰብሰባ  ትኩረቷን በሙሉ  ከንስሯ ጋር በማቋራኘት እምሮውን  ማንበብ ጀመረች፡፡

‹‹መምጣትሽን ፍቅረኛሽ አያውቅም አይደል?፡፡››

‹‹አዎ..አንዴ በእሱ ክህደትና ዘረፋ የሞትኩት አንሶኝ ጭራሽ መምጣቴን ነግሬው ስሩ ቆሜ ሁለተኛ ሞት ልሙት እንዴ? አላደርገውም ….ፍቅሬን መልስልኝ ብዬ ልማፀነው..?ወይስ ብሬን መልስልኝ ልበለው?››

በንስሯ አእምሮ አሻግራ እያየች ያለችው ታሪክ አሰገርሟት፡፡‹‹ቆይ ቆይ…በዚህ ሰዓት ፍቅረኛሽ ምን እየሰራ እንደሆነ ታውቂያለሽ…?››ስትል ጠየቀቻት፡፡

‹‹ምን እየሰራ ነው..?.ከሚስቱ እየተዳራ ወይም ልጁን እያጫወተ ይሆናል››ብስጭት እና ቅናት በተቀላቀለበት ድምፀት መለሰችላት፡፡

‹‹አይደለም …ትናንትና ወደ  ጊኒጪ ሄዶ እናትሽን  አምጥቶ ግሩም ጠቅላላ  ሆስፒታል እያሳከማቸው ነው…››

‹‹የእኔን እናት .. ?ምን ሆና ነው…?››በድንጋጤና በመገረም .እናም ደግሞ ባለማመን ጠየቀች፡፡

‹‹አትደንግጪ ያው የተለመደው በሽታዋ ነው….ድሮም ከፍተኛ የጨጎራ ቁስለት እንዳለባት ታውቂያለሽ፡፡››

‹‹አዎ ትክክል ነሽ››

‹‹ግን እኔን እንዲህ አድርጎኝ እንዴት ያሰጠጉታል …እናቴ ምንም የሚያስታምማት እና ሚያሳክማት ሰው ብታጣ እንዴት ልጇን ከከዳ ሰው ጋር ትተባበረለች…?እኔ ይሄን ማመን አልችልም …፡፡ሌላው ይቅር እናቴ እንኳን ለስላሳ እና የዋህ ስለሆነች  ይቅር ልትለው ትችላለች… እህቴ ግን እርግጠኛ ነኝ ይቅር አትለውም ፤ እርግጥ ሁሉም ለእሱ የላኩለትን ብር አያውቁም …ግን በጣም እንደማፈቅረውና ላገባውም  እንደምፈልግ ከዛም አልፎ ቃል እንደተግባባን ግን በደንብ ያውቃሉ፡፡››

‹‹ትክክል ነሽ…በጣም ነው የሚያፈቅርሽ፡፡››
👍986👎2🥰2👏2🔥1😢1
#ትንግርት


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ዶ/ር ሶፊያ በማግስቱ ከምሽቱ 12፡3ዐ ላይ መኪናዋን እያሽከረከረች ታዲዮስ ቤት ደረሰች፡፡ሦስት ኩርቱ ፔስታል ሙሉ ስጦታ ይዛለች ፤ለአምስቱም ልጆች ፡፡በመከራ እየተንገዳገደች ነበር ዕቃዎቹን ተሸክማ በረንዳው ላይ ማድረስ የቻለችው፡፡መሬት አስቀመጠችውና በራፉን አንኳኳች፡፡ ሃያ አምስት ዓመት የሚሆነው ባለ ሹሩባ ፀጉር መልከ መልካም ወጣት ከፈተላት፡፡

‹‹አቤት ምን ነበር?››ዓይኑ ያልተለመደ ነገር በማየቱ የመገረም ፊት እያሳያት፡፡

‹‹ታዲዬስን ፈልጌው ነበር፡፡››

‹‹ይቅርታ ታዲ ከአንድ ሰዓት በኃላ ነው የሚመጣው፡፡››

<< አመጣጤማ ሰላምን ልጠይቃት ነበር፤የታዲ ዘመድ ነኝ፤ማታ እዚህ በነበርኩበት ሰዓት የሰላምን መታመም አይቼ ስለነበር አሳስቦኝ ነው፡፡››

ፈራ ተባ እያለ በራፉን በሰፊው ከፈተላት እና አንዱን ፔስታል ለእሷ ትቶ ሁለቱን ወደ ሳሎን ውስጥ በማስገባት ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠላት‹‹እህት .. እንግዲህ አረፍ በይ ትንሽ ስራ ላይ ነን፡፡ ››ብሏት ጥሏት ሄደና በመደዳ ካሉት ክፍሎች መሀከል ወደ መጀመሪያው ክፍል ገባ፡፡ ሶፋው ላይ ቁጭ አለች፡፡ልጁ ከገባበት ክፍል አካባቢ የፒያኖ ድምፅ ይሰማታል፤የሚመስጥ ክላሲካል ሙዚቃ፡፡ዝም ብላ በደመነፍስ ባዶውን ሳሎን ለቃ የሙዚቃውን ድምፅ ተከትላ ወደ ክፍሎቹ መራመድ ጀመረች፡፡የመጀመሪያው ክፍል በራፍ አጠገብ ስትደርስ እርምጃዋን ገታችና ቆመች፡፡በራፉ ገርበብ ብሎ ስለነበር አንገቷን አሰገገች፡፡
እንደመጣች በራፉን የከፈተላትን ልጅ ሹሩባ ቀድሞ ታያት፡፡ይበልጥ ስትጠጋ ሠላምን አየቻት፡፡ በሹክሹክታ ወደ ውስጥ ዘልቃ ገባች፡፡ሠላም ወንበር ላይ ቁጭ ብላለች፡፡ ከፊቷ የስዕል ሸራ ተወጥሮላት ፊቷ በቀረበላት የተዘበራረቀ ቀለም በቀጫጫ እጆቿ የያዘችውን ብሩሽ እያጠቀሰች የሆነ ስዕል ትስላለች፡፡ወጣቱ ቀና ብሎ ሶፊያን ተመለከታትና መልሶ ቀልቡን ሰላም ወደምትስለው ስዕል መለሰ፡፡ ልትረብሻቸው ስላልፈለገች ክፍሉን በቀስታ ለቃ ወጣች፡፡

ወደ ሳሎን ልትመለስ ካሰበች በኃላ የፒያኖው ድምፅ የሚንቆረቆረው ከሚቀጥለው ክፍል እንደሆነ ስታውቅ ሀሳቧን ቀየረችና ወደዛው አመራች፡፡ገርበብ ያለውን ክፍል በተመሳሳይ ገፋ አድርጋ ወደ ውስጥ ገባች፡፡ መሀከል ወለል ላይ አንድ መለስተኛ ፒያኖ ተመለከተች፡፡ አንድ ወጣት ግን አይነስውር የሆነች ምታምር ሴት ሁለቱን ሴት ህፃናት ተራ በተራ ጣታቸውን እየያዘች ታለማምዳቸዋለች፡፡ ግድግዳውን ተደግፋ በተመስጦ ትከታተላቸው
ጀመር፡፡ከአስር ደቂቃ ቆይታ በኃላ ዓይነ ስውሯ
አስተማሪ አዳምጡ አለቻቸውና ሁለቱን ሴት
ልጆች መቀመጫቸውን ይዘው እንዲቀመጡ

በማድረግ ጣቶቾን ፒያኖው ላይ ማርመስመስ ጀመረች፡፡ልጆቹ ብቻ ሳይሆኑ ዶ/ር ሶፊያም
ድንዝዝ ብላ ነው የተከታተለቻችው፡፡እሷ
እራሷም ከሙዚቃው ስልት ጋር ከወዲህ ወዲህ አንገቷን ስታወናጭፍ እረጅም ጥቁር ፀጉሯ በአየሩ ላይ ይበተናል፡፡የተመልካች ልብን
ስልብ ያደርጋል ፡፡ስትጨርስና ጣቶቾን
ስትሰበስብ ሳታስበው አጨበጨበችላት፡፡

ሁለቱም ህፃናት ልጆቹ እያቀፋ በመሳም
ፍቅራቸውን ገለፁላት፡፡
ሄለን ‹‹ፅዬንዬ እኔም ሳድግ እንደአንቺ መጫወት እፈልጋለሁ፡፡አንቺን መሆን ነው የምፈልገው፡፡››አለቻት፡፡
ፅዬን በግምት እጇን ወደ እሷ ላከቻና የለበሰችውን ጃኬት ይዛ ወደ ራሷ ጎትታት ጉያዋ ውስጥ ሸጉጣ አቀፈቻት ‹‹በቅርብ ቀን
እንደ እኔ ብቻ ሳይሆን ከእኔም በላይ ትጫወቺያለሽ፡፡ አንቺ ምርጥ ሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋች ሀሊማ ደግሞ ምርጥ ድምፃዊ እንደምትሆኑ እርግጠኛ ነኝ፡፡››ብላ በማበረታታት ጉንጯን ሳመቻት፡፡

ዶ/ር ሶፊያ ቀስ ብላ ክፍሉን ለቃ ወጣችና ሶስተኛው ክፍል ገባች፡፡ አንድ የአስራ ስምንት አመት ወጣት ሴት የአማርኛ ፊደል ተራ በተራ ብላክ ቦርድ ላይ እየፃፉች ሚጣን እያስተማረቻት ነው፡፡

እስከአሁን ያላየችው ወንዱን ልጅ ብቻ ነው፡፡ እሱ አራተኛው ክፍል ውስጥ ይሆናል›› ስትል ገመተች‹‹ለመሆኑ እሱስ ምን እየተማረ ይሆን?›› ለማወቅ በጣም ጓጓች.. ወደ አራተኛ ክፍል አመራች ፡፡እስከአሁን ካየቻቸው ሶስቱም ክፍሎች በተሻለ ይሄኛው በእጥፍ ሰፋት አለው፡፡ ግን ቤት ሳይሆን ኳተት ማጠራቀሚያ ክፍል ነው ማለት ይቻላል፡፡በኤሌክትሮኒክ ዕቃዎች፣በብረታ ብረት ቁርጥራጮች፣በተበላሹ ቴሌቨዢኖች፣ሬዲዬኖች
ገመዳ ገመዶች ተሞልቷል፡፡ዕድሜው ከ1ዐ የማይበልጠው የሰውነቱ ግዙፍነት ግን የ15 ዓመት ታዳጊ የሚያስመስለው ድንቡሽቡሽ ልጁ ኮተቶቹ መሀከል ወለል ላይ ተዘርፍጦ ላፕቶፕ ኮምፒተር ላይ አፍጥጧል፡፡ድምፅ ብታሰማውም ሊሰማት አልቻለም፡፡ሹክክ ብላ ወጥታ ወደ ሳሎን ተመለሰች እና ስላየችው ነገር በግርምት ማሰላሰል ጀመረች፡፡

አንድ ሰዓት ሲሆን ሁሉም የእለት ስራቸውን አጠናቀው ከየአስተማሪዎቻቸው ጋር ከየክፍላቸው ወጡ፤ ከወንድዬው ልጅ በስተቀር፡፡ ሠላምንም አስተማሪዋ ደግፎት አመጣትና ከእሷ ጐን እንድትቀመጥ ከረዳት በኃላ‹‹ይቅርታ ቅድም በስራ መሀል ስለነበርኩ በቅጡ አላናገርኩሽም…የቤቱ ህግ ነው፡፡ ከሁሉ በፊት ስራ ይቀድማል፡፡አላዛር እባላለሁ፡፡››በማለት እጁን ለሰላምታ ዘረጋላት፡፡ እሷም እየጨበጠችው‹‹ሶፊያ እባላለሁ›› አለችው፡፡

‹‹አሁን ሠላምን መጠየቅ ትችያለሽ..ያው ከጎንሽ አስቀምጪልሻለሁ፡፡ እኔ ሽንት ቤት ደርሼ መጣው›› ብሎ ወደ ጓሮ ሄደ ::

‹‹አመሰግናለሁ››ብላው የሰላምን ግንባሯን ሳመቻት፡፡

‹‹ትመጪያለሽ ብዬ ስጠብቅሽ ነበር ::>> አለቻት ሠላም በመምጣቷ መደሰቷን በፈገግታዋ እያረጋገጠችላት፡፡

‹‹ይሄው መጣሁልሽ፤ ለመሆኑ የሚያምሽ ተሻለሽ?»

‹‹አዎ ...ዛሬ ሚጠዘጥዘኝ ትቶኛል፡፡››

‹‹አይ ጥሩ ነው፡፡››ንግግሯን ሳትጨርስ ሌሎቹ ልጆች ከያሉበት መጥተው ወረሯት ፡፡ግማሹ ግንባሯን ግማሹ ጉንጮን ሳሟት፡፡እሷም በየተራ ሳመቻቸው፡፡ለሚያያቸው ዕውቂያቸው የአንድ ቀን ብቻ አይመስልም፡፡

አላዛር ከጓሮ ተመለሰና ከሚጠብቁት ጓደኞቹ ጋር ከተቀላቀለ በኃላ ድምፅን ከፍ አድርጐ << ሶፊ ልንሄድ ነው››ሲላት ልጆቹን ‹‹ቆይ አንዴ መጣሁ >>ብላ ከተቀመጠችበት ተነሳችና ወደ እነ አላዛር ሄደች፡፡

‹‹ይቅርታ እኔ የታዲ ዘመድ ነኝ፤ ከሁላችሁም ጋር ብተዋወቅ ደስ ይለኛል፡፡››

አይነስውሯ ቀድማ ለሰላምታ እጇን እየዘረጋችላት‹‹ፅዬን እባላለሁ›› አለቻት፡፡

‹‹ዶ/ር ሶፍያና፡፡››
‹‹ቤቲ..ቤተልሄም፡፡›› እባላለሁ..ሌላዋ ቀጠለች፡፡
አላዛር መሀል ገብቶ ማብራሪያ በመስጠት ቀጠለ ‹‹...ፂ እንዳየሻት አሪፍ የሙዚቃ ሰው ነች፡፡ጊታር እና ፒያኖ ነፍስ አድርጋ ትጫወታለች፡፡የያሬድ ግርፋ ነች፤ በሞያዋ የሙዚቃ አስተማሪ ነች፡፡እዚህም እንዳየሻት የሄለን እና የሚኪያ የሙዚቃ አስተማሪ ነች፡፡…

ቤቲ ደግሞ ሀይ‐ስኩል አማርኛ ቲቸር ነች፡፡
የስድስት ኪሎ ምሩቅ ነች፡፡እዚህ ያሉትን ህፃናት አማርኛም ሆነ እንግሊዘኛ ቋንቋ በፕሮግራም
ታስተምራቸዋለች፡፡አንዳንዴ
ሂሳብም ቀልቀል ለማድረግ ትሞክራለች ግን ቀሺም ነች፡፡ሂሳብ እና ጠቅላላ ዕውቀትን በተመለከተ ጂኒዬሱ ነው የሚያስተምራቸው፡፡

ጂኒዬሱ ስል ታዲዬስን ማለቴ ነው፡፡እኔ ያው
እዚህ ቤት የቀለም ሽታ የምትወድ አንድ ሰላም
የምትባል ልዩ ነፍስ ያላት ልጅ አለች ፤እሷን ስዕል አስተምራታለሁ፡፡አስተምራታለሁ ማለት
እንኳን ይከብዳል ስትስል
አያታለው፤የምትፈልገውን ቁሳቁስ አቀብላታለው ማለቱ ነው የሚሻለው ፡፡

ምክንያቱም አሁን ባለንበት ሁኔታ ችሎታችን እኩል ነው፤ከስድስት ወር በኃላ ደግሞ እኔ ቁጭ ብዬ ከእሷ መማሬ አይቀርም፡፡››
👍7811👎1👏1🤔1
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

በማሳጅ ስም እየሰራችው ያለችው ስራ ካሰበችው በጣም ውስብስብ ፤ከግምቷ በጣም የረቀ፤ ካደገችበት ስነ-ምግባር ያፈነገጠ፤ የተለየ አይነት አለም ሚያሳይ ቢሆንም ወደ ቦርሳዋ በሚፈስላት ብር ስለሚካካስ አሜን ብለ ተቀብላው ለአመታት ሰትሰራ ነበር፡፡እንጂማ ስራ ሲያስጀምሯት ማሳጅ ቤት ብለው የሰበኳት ስብከት ፌክ መሆኑን የተረዳችው ስራ በጀመረች ሶስት ወርም ሳይሞላት በፊት ነበር፡፡ምክንያቱም ከሚሰጡት አገልግሎቶች ውስጥ ትክክለኛ ያልበተበረዘና ያልተከለሰ ማሳጅ 25 ፐርሰንትም አይሆንም...አሱ ሽፋን ነው፡፡
ወደስራው ጠልቃ ከገባች በኃላ ብዙ ብዙ ገራሚ ገጠመኞችን አስትናግዳለች… አንዳንዶቹ እስከህይወቷ ፍፃሜ የማትዘነጋቸው አይነት ናቸው፡፡
ከበርካታ ያልተለመዱ አይነት ገጠመኞቾ መካከል  አንድን ለምሳሌ ያህል ለማየት ብንችል ነገሮችን ግልፅ ያደርግልናል፡፡ስራ በጀመረች በአራተኛው አመት ነው፡፡ደምበኛ እንዳላት ተነግሯት በሰዓቷ ስራ ቦታዋ ተገኝታ እየጠበቀች ነው፡፡ እንደተባለውም በሰዓቱ በራፍ ተንኳኳ… ከፈተች፡፡በራፍ ላይ በመግባትና ተመልሶ ሮጦ አካባቢውን ለቆ ለመሄድ ውዝግብ ውስጥ የገባ ስሜት ላይ ያለ ጎልማሳ  ሰው  ቆሟል..ሰውዬውን  ታውቀዋለች… በአካል አይደለም..ታዋቂ ሰው ነው..ግን ምንድነው?  ተዋናይ  ነው?  ፖለቲከኛ ነው…? ግልፅ ብሎ ሊታወሳት አልቻለም፡፡‹‹ጌታዬ እንኳን ደህና መጡ ይግቡ.›› አለችና በራፉን በሰፊው ከፈተችለት..የመዝለል ያህል ፍንጥር አለና ወደ ውስጥ ገባ…እሷም በራፉን ዘጋችና  ተከተለችው…እቤቱ  ውስጥ  ከወዲህ  ወዲያ መንጎራደድ ጀመረ‹‹…ጌታይ ችግር አለ? ››ጠየቀችው፡፡

‹‹እዚህ መምጣቴ ትክክል ነው ወይስ ስህተት አላውቅም››

‹‹ጌታዬ ስህትም  ሆነ  ትክክል  አንዴ  መጥተዋል..አረፍ  ይበሉና  ትንሽ ይረጋጉ..እዚህ መምጣቶት ስህተትም ቢሆን የሆነ ጥቅም አይጠፋውም….ደግሞ ነገሮች እንደአጠቃቀማችን ይወሰናሉ…የህይወት ጨለማ ክፍሉ ውስጥ ዳካሮ መውጣት የብርሀኗን ውበት የበለጠ እንድናጣጥም  ግንዛቤያችንን ይጨምርልናል፡፡››
‹‹እሱስ እውነትሽን ነው፡፡››ብሎ ሶፋው ላይ ቁጭ አለ፡፡ሳባም ወደፍሪጁ ሄደችና የታሸገ ውሀ በማምጣት ከጎኑ ያለ ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠችለት..ከፈተና ገርገጭ.ገርገጭ አድርጎ ግማሽ ያህሉን ከጠጣለት በኃላ ከደነና መልሶ አስቀመጠው፡፡ለእኔ እዚህ ቦታ መምጣት ቀላል አይደለም…እዚህ እንድመጣ የጠቆመኝ አንድ ወዳጄ ነው….

‹‹ጥሩ ነው…ምን አይነት አገልግሎት ነው የሚፈልጉት…ሙሉ ማሳጅ ..የእግር ማሳጅ አለ…ከአንገት በላይ ማሳጅ አለን…ሌሎች አገልግሎቶቹም አሉን.መጠጥና
…››
‹‹አይ እንዳዛ አይደለም…የዘረዘርሻቸውንም ሁሉ አንዳቸውንም አልፈልግም…እኔ የምፈልገው እንድታዳምጪኝ ብቻ ነው…ቆይ አሉና እጃቸውን ወደ ኮት ኪሳቸው በመክተት አንድ መለስተኛ ጥራዝ ያለው መፅሀፍ  አወጡና  ዘረጉላት፡፡ግራ በመጋባት ተቀበለችና አነበበችው›

‹‹የኢየሱስ ተአምራዊ የማዳን ስራ››የሚል ርዕስ አለው፡፡ጀርባውን ገልብጣ አየችው ፀሀፊ-ፓስተር ጴጥሮስ ዳንሳ ይላል፡፡ ከፊት ለፊቷ ያለው ሰው ፎቶ ገጭ ብሎበታል…እንደአዲስ ደነገጠች..ሰውዬው በደንብ ታውቀዋለች..በፕሮቴሰታንቱ መንደር በጣም ታዋቂና ዝነኘ ፓስተር ነው…በዛ ላይ የራሱ ሆነ ቴሌቬዥን ጣቢያ ስላለው.በተደጋጋሚ ስብከቱን በቴሌቪዥን መስኮት አዳምጣለች፤አሷ  ጋር መምጣቱ ለምን እንደዚህ እንደከበደው ወዲያው ነበር ግልፅ  የሆነላት..ኸረ መምጣቱ ለእሷ ለራሷ በጣም ገርሟታል..››

‹‹ፓስተር.በእውነት የአርሷ እዚህ  መምጣት  ለእኔ  ትልቅ  ክብር  ነው….እና እንዳሉኝ የሚፈልጉት እንዳዳምጧት ከሆነ በሙሉ ነፍሴ  የለምንም  ፍርድና ትዝብት እንደማዳምጧት እርግጠኛ ይሁኑ››

‹‹እሺ እንደዛ ከሆነ .ማወራሽ ስለመፅሀፉ ነው፡፡በእጅሽ ስለያዝሺው መፅሀፍ ፡፡ መፅሀፉ እውነተኛ የህይወት ገጠመኜ የሰፈረበት ነው፡ይሄ ገጠመኝ ምንም ማጣፈጫ ያልተጨመረበት ንፅህ እውነት ነው ብዬ  አምን  ነበር።ላለፍት  9 ዓመታት ሰፋ ያለ ህዝብ በታደመበት አውደ ምህረት ላይ  ያለመሰልቸት ተርኬዋለሁ። ምዕመኑም አንዳንድ ሶስቴ ሌላውም 13ቴ ደጋግሞ ሰምተውታል። ግን አይ ሰልችቶኛል የሚል የለም፡፡ ከእልልታው ጥቂት ዝንጣፊ የሚቀንስ የለም።በጌታ ሰው አንደበት የሚነገር የጌታ ተአምር እንዴት ሰለቸኝ ማለት ይቻላል...?መታሰብስ።

የዛሬ 14 አመት ለአገልግሎት ደቡብ ኢትዬጰያና ሱዳን ድንበር  አካባቢ  ወደሉ ጎሳዎች እሄዳለሁ።እርግጥ ብቻዬን ሳይሆን ከሁለት ጓደኞቼ ጋር ነበር።እና ጉዞችን ጥቅጥቅ ደን የምናቋርጥበት ከአውሬ ጋር ድብብቆሽ የምንጫወትበት አስደናቂና አስፈሪ ነበር..ግን ደግሞ ጌታ ከእኛ ጋር ስለነበር በዝምታ ሳይሆን በዝማሬ ነበር የተጓዝነው። መንገድ ከሚገኝበት የሁለት ቀን የእግር መንገድ ተሂዶ ነው የሚደረሰው። ጌታ ይመስገን በሰላም ደረስን።ጌታን አገለገልን በሶስት ወር ቆይታችን 10 ብቻ የነበሩትን አማኞች ወደ ሶስት መቶ አሳድገን በመንደሩና በአካባቢው  የጌታ  አገልጋዬች  አድርገን  ጉባኤ  አደራጅተን  ቤተክርስቲያን መስርተን አንደኛውን ጓደኛችንን እዛው  እንዲያገለግል  ትተን  የመልስ  ጉዞ ጀመርን።

በመሀል ደረቀ ጉሮሮውን ለማርጠብ ከጎኑ ካለው ጠረጴዛ ውሀውን አነሳና ላይ የተቀመጠለትን ሀይላደንድ ውሀ በመክፈት እየተጎነጨ በተመስጦና በስሜት ትረካውን ቀጥሏል…፡
…በሁለተኛው ቀን ከጓደኞቼ ነጥለው ጠለፍኝ።አንድ መፅሀፍ ቅድስ ብቻ ነበር በእጄ የያዝኩት፡፡ጌታ ሆይ አንተ ጠብቀኝ አልኩ።የጠለፍኝ ሰዎች ቋንቋቸው የማይገባ እጅግ ከሰው ተነጥለው ጥቅጥቅ ደን ውስጥ የሚኖሩ 2መቶ የማይሞላ ቁጥር ያላቸው አባላት ያላቸው ጎሳዎች ናቸው።
ከወሰዱኝ በኃላ አንድ ጠባብ ጎጆ ውስጥ ጠርቅመውብኝ በራፍን ገንጥዬ እንዳላመልጥ ሁለት ጦር የቀሰሩ ጠባቂዎች በራፍ  ላይ  አስቀመጡ።መፅሀፍ ቁዱሴን ደረቴ ላይ ለጥፌ እኔ ፀልያለሁ...ያለማቆረጥ ከጌታ ጋር አወራለሁ።ሶስታ ቀንና ሶስት ለሊት  እዛች  ጠባብ ጎጆ  ውስጥ  አሳደሩኝ፡፡  በአራተኛው ቀን የተለየ ነገር መታየት ጀመረ፡፡ ውጭ ታላቅ  ክብረ  በዓል  ለማዘጋጀት  ትርምስ  ላይ እንደሆኑ ይታየኛል።‹‹ጌታ ሆይ  ተአምራትህን  በዚህ  ዝግጅት  ላይ  አድርግ›› እያልኩ ፀሎቴን ቀጠልኩ.. ሲጨልም ምቀምሰውን ምግብ አንድ ልጃገረድ ይዛልኝ መጣች፡፡ ጠባቂዎቹ ወደውስጥ እንድታልፍ ፈቀድላት...:: ጎምበስ ብላ ምግብን እያቀረበችልኝ
"አይዞህ"አለችኝ፡፡

‹‹ እንዴ ጌታ ስራውን መስራት ጀመረ ››አልኩ...አማርኛ ትችላለች..

"ለምንድነው የያዙኝ...?ከእኔ ምን ፈልገው ነው ?"ከእሷ ባነሰ ደካማ ድምፅ ጠየቅኳት።
"ለመስዎእትነት..ለአማልዕክቱ ሊያቀርብህ ነው" አለችኝ... ያልጠበቅኩትን መልስ ነበር ያገኘሁት…የጌታ ጥበቃ በዙሪያዬ እንዳለ ባምንም..የልጅቷ በዛን ሰዓት

ከአማርኛ  ችሎታ  ጋር  ስሬ  መከሰት  አንድ  ምልክት  እንደሆነ  ባልጠራጠርም
...ሰውነቴ በፍራቻ መራድ፤አፌም በድንጋጤ መድረቁ አልቀረም ነበር።"
👍795🥰4👏1
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#በዘሪሁን_ገመቹ
================

..ፎጣዋን አገልድማ ስትወጣ እሱ ደግሞ ለመግባት እርቃን ሰውነቱን በፓንት ብቻ ሆኖ ወደእሷ አቅጣጫ ሲመጣ አየችው…ዞር ብላ መንገዱን ለቀቀችለት …ቀጥታ ወደውስጥ ገባና የሻወሩን በራፍ ዘጋው…
ባለቤቷን እንዲህ እርቃኑን ስታየው ሁሌ እንደአዲስ እንደገረማት ነው፡፡ሰለብሪቲ አክተር ወይም ታዋቂ ሞዴል እኮ ነው የሚመስለው፡፡እዚህ አካባቢ እንደዚህ ቢሆን የሚባል ቅር የሚያሰኝ የአካል ክፍል የለውም‹‹ሆሆ..ለናሙና የተፈጠረ እኮ ነው የሚመስለው››አለችና ሰውነቷን አደራርቃ በምሽቱ ሶስቱን የእድሜ ልክ አድናቂዎቾና አፍቃሪዎቾ ወንዶችን ያስደምማል ያለችውን አለባበስ ለበሰች፡፡ፀጉሯን አስተካከለች፡፡የተወሰነ ሜካፕ ተጠቀመችና ሽቶ እላዮ ላይ ነስንሳ ወደሳሎን ወጣች፡፡
አለማየሁ ሰማያዊ ቀለም ያለው ሙሉ ሱፍ ለብሶ  ዝንጥ ብሎ  ሳሎን ቁጭ ብሎ እስኪወጡ እየጠበቃቸው ነበር፡፡
እንዳየችው ‹‹እንዴ ኩማንደር….አምባሳደር መስለሀል፡፡›› አለችው፡፡

‹‹የወደፊት እጣ ፋንታዬ ምን አልባት አምባአሳደር ሊሆን ይችላል፡፡››ሲል መለሰላት፡፡

‹‹ተስፋ አደርጋለሁ፡፡››
‹‹ምነው አፍጥጠህ አየሀኝ…ልብሱ አልሄደብኝም እንዴ?››ሲል በጥርጣሬ ጠየቃት፡፡

‹‹አረ የሚያስደነግጥ አለባበስ ነው … እንከን አይወጣለትም ..በጣም ያምራል፡፡››

‹‹ልብሱ ብቻ ነው ሚያምረው?››ስትል ልስልስ በሆነ ቅንዝራም ድምፅ ጠየቀችው፡፡

‹‹ስለአንቺ አላዛር ሲመጣ ይነግርሻል….ያንን አስተያየት የመስጠት መብት ለጊዜው የእሱ ነው፡፡››

ግንባሯን ቋጠረች‹‹ለጊዜው ስትል…?››

‹‹ይሄ ጥያቄ ይዝለለኝ፡፡››

‹‹በጣም ተቀይረሀል ..ድሮ እንደዚህ አልነበርክም››

‹‹እንዴት ማለት?››

‹‹ከእኔ ጋር ለምትነጋገረው ነገር ስትጠነቀቅ አይቼህ አላውቅም ..እንደመጣልህ በነፃነት ነበር የምናወራው፡፡ትዝ ይልሀል ..አንተ እኮ ጓደኛዬ ብቻ አልነበርክም….አንድ ቤት ውስጥ አብረኸኝ ያደክ ወንድሜ ነህ፡፡››

‹‹አዎ..በልጆቼን በሞት ሳጣና አያቴም በቃኝ ብላ ገዳም ጥላኝ ስትገባ ..አንተም ልጄ ነህ ..ከልጄ ጋር አሳድግሀለው ብላ የወሰደችኝ እናትሽ እቴቴ ነች፡፡በእውነት ለእሷ በሚገባው መጠን አልተንከባከብኳትም…፡፡››

‹‹ተው ተው..እቴቴንማ በጣም ነው የተንከባከብካት፡፡.በየጊዜው ብር እንደምትልክላት ማላውቅ ይመስልሀል፡፡እዚህ ከተቀየርክ በኃላ  እንኳን እሷን ደጋግመህ አግኝተህ እኛን ግን ለማግኘት ፍቃደኛ አልነበርክም፡፡ካንተ ደግሞ ይልቅ ደግሞ የሚገርመኝ የእሷ ያንተ ተባባሪ ሆና መደበቅ፡፡ …እንደውም አንዳንዴ ከእቴቴ ጋር ስንጣላ እኮ…‹‹ከአንቺ ይልቅ የእኔን እናትነት የተረዳው አለማየሁ ነው…››እያለች ታበሳጨኛለች፡፡እና እሷ በአንተ ደስተኛ ነች…ትንሽ ቅር ሚላት በየጊዜው በአካል ሄደህ ስለማትጠይቃት ነው፡፡በዛ ከአንተ እኔ እሻላለሁ….፡፡››

‹‹ቢሆንልኝ…ለእሷ ምንም ነገር ባደርግ ይገባታል፡፡››

‹‹ለእኔስ…ለስድስት አመት የት እንዳለህ እንኳን ደውለህ አሳውቀሐኝ አታውቅም…አለማየሁ ደወሎ እንዲህ አለ…አለማየሁ ደውሎ በባንክ ይሄንን ላከ ሲባል እንጂ አንድ ቀን ሰሎሜ ሰላም ብሎሻል…?ሰሎሜ አለማየሁ ሰለአንቺ እንዲህ  ያስባል ብሎ የነገረኝ ሰው የለም..ሁል ጊዜ አእመሮዬን እንደበላኝ ነው…‹‹ምን አድርጌዋለው…?መቼ ቀን ነው ያስከፋሁት …?.የቱ ጋር ነው የተቀየመኝ? ብዬ እንደተከዝኩ ነበር..እወነቱን ለመናገር በጣም ተቀይሜህ ነበር ..ባገኝህ እንደማላናግርህ ለራሴ ቃል ገብቼ ነበር..ግን በእንደዛ አይነት ሁኔታ ስንገናኝ…ምንም ማድረግ አልቻልኩም...ተቀይሜህ እንደነበረ ራሱ ከእስር ተፈትቼ ቤቴ ከገባው በኃላ ነው ያስታወስኩት፡፡››

‹‹ጥሩ ነው፣ ቂመኛ አይደለሽም ማለት ነው…አንቺን ያላገኘሁሽ ግን ላላገኝሽ ስላልፈለኩ ሳይሆን ተገድጄ ነው››

‹‹ተገድጄ ስትል?››

‹‹ማለቴ….››ንግግሩን እንዳንጠለጠለ አላዛር ከእነሱ በበለጠ.. ልክ እንደእለቱ ሙሽራ ዝንጥ ብሎ ወደእነሱ ሲመጣ ስለተመለከተ ለንግግር የተከፈተ አፉን መልሶ ዘጋ፡፡

‹‹በሉ…እንሂድና …ቀደም ብለን እዛው አካባቢ ደርሰን ብንጠብቀው ይሻለል፡፡››

አለማየሁ አላዛር መጥቶ ማውራት ከማይፈልገው ነገር ስለገላገለው በመደሰት ‹‹ጥሩ …እንሂድ››አለና ከተቀመጠበት  ተነሳ፡፡ርምጃውን ከአላዛር አስተካክሎ ወደውጭ መራመድ ጀመረ.፡፡ሰሎሜ ከኃላ ሁለቱንም በትኩረት እያየች ተከተለቻቸው፡፡ሁለቱም ፈርጣማና ወንዳወንድ የሚባሉ ናቸው፡፡ግን አላዛር ወደላይ የተሳበ መለሎ ነው፡፡
//
ከ30 ደቂቃ ጥበቃ  በኋላ የተጠበቀው ሁሴን ግዙፍ ሻንጣውን በጋሪ እየገፋ ከተርሚናሉ ሲወጣ ሶስቱም በእኩል አዩት…በደስታና በጩኸት እንዲያያቸው እጃቸውን አውለበለቡለት…ሁሴን ከዛሬ ስድስት   አመት  በፊት እደሚያውቁት አይነት ነው፡፡ እንዳዛው ውልምጭምጭ ቀጫጫ…ባለትልቅ ጭንቅላትና ሉጫ ፀጉር…የህፃን የመሰለ ፍልቅልቅ ፊት…ነጭ ከሩቅ አይን የሚስብ  በረዶ መሳይ ጥርስ ……
ሶስቱም በየተራ እየተጠመጠሙበት ሰላምታ ከሰጡትና ይዘው የመጡትን የእንኳን በሰላም መጣህ ምኞታቸውን የሚገልፅ  አበባ አስታቀፉት፡፡ከዛ በኃላ አለማየሁና አላዘር ሻንጣውን ተቀብለው  ወደመኪናው ወሰዱና ከኋላ ጫኑለት፡፡…በአላዛር ሹፌርነት ሰሎሜ ገቢና ከእሱ ጎን ተቀምጣ አለማየሁና ሁሴን ከኋላ ሆነው ወደቤት ጉዞ ጀመሩ፡፡

ድንገት‹‹ይገርማል…?››አለ ሁሴን፡፡

አለማየሁ‹‹ምኑ ነው የገረመህ?ከተማዋ ልደቷን የምታከብር የቢሊዬነር ብቸኛ ልጅ መሰለችህ አይደል…?››አለው፡፡

‹‹ማለት?››

‹‹አሸብርቃና ተኳኩላ …በደማቅ መብራቷች ተንቆጥቁጣ ስታያት ገርሞህ እንደሆነ ብዬ ነዋ?››

‹‹..አዎ ያልከው ነገር በጣም አስገርሞኛል..ግን እኔ ለማውራት የፈለኩት ሶስታችሁን በአንድነት መጥታችሁ ትቀበሉኛላቹሁ የሚል ምንም አይነት ግምት ስላልነበረኝ በዛ መደነቄን ነው፡፡፡፡›

ልክ እንደሁሴን እሷም ሶስቱም የልጅነት እና የአፍላ ወጣትነት ጓደኞቾ እና አፍቃሪዎቾ ከበርካታ አመታት በኋላ እንዲህ አንድ ላይ ተሰብስበው አይናቸው እሷ ላይ ሲያቁለጨለጩ በመመለከቷ እየተገረመች‹‹ምን ማለት ነው? ሶስታችንም እኩል ጓደኞችህ አይደለንም እንዴ…?ለመሆኑ መጥቶ ይቀበለኛል ብለህ የገመትከው ማንን ነው?››ስትል ጠየቀችው፡፡

‹‹ያው አሌክስን ነበር፡፡እናንተን በማግስቱ ባገኛችሁ ብዬ ነበር ያሰብኩት፡፡››

‹‹አንተ …ከእኛ ይልቅ አሌክስ ቁምነገረኛ የሆነው ከመቼ ወዲህ ነው…?ነው ሰው ሀገር ከሄድክ በኃላ ፀባያችን ተምታታብህ››አለችው ሰሎሜ በመገረም፡፡

አለማየው በፈገግታ‹‹አንቺ …ሰው ሁሉ ስለእኔ ልክ እንደአንቺ የተሳሳተ ግምት ያለው ይመስልሻል እንዴ?››አላት፡፡

‹‹ተው ተው…ከመሀከላችንማ አንደኛው ቁምነገረኛና ኃላፊነትን የሚወስደው አላዛር ነው…አንተ እንደውም በዚህ ጉዳይ  የመጨረሻው ሰው ነህ››አለው ሁሴን፡፡

‹‹አንተ ዲያስፖራ ለመሆኑ ዜግነትህን ቀይረሀል?››ሲል ጠየቀው፡፡
ያልጠበቀውን ጥያቄ ስለተጠየቀው ግራ ተጋባ‹‹አይ አልቀየርኩም…ግን ለምን ጠየቅከኝ?››
‹‹አይ ኢትዬጵያዊ ዲያስፖራ ከሆንክ  የሚጮህልህ ኤምባሲ ስለሌለ ለዚህ ንግግርህ የሆነ ሰበብ ፈልጌ ከርቸሌ ልወረውርህ ነዋ….እንደድሮ አለማየሁ ብቻ አይደለሁም..ኩማንደር አለማየሁ ነኝ፡፡››
👍638👎2🔥1🥰1
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ


///
‹‹ልጄ አንተ እንዲሁ ሰበብ ሆናብህ እንጂ ሰሎሜን የገደልካት አንተ አይደለህም››

‹‹እማዬ አሁን በቃሽ …ባበቃለት ጉዳይ ላይ ምንም ለውጥ ላታመጪ አትድከሚ››

‹‹አይደለም..ሰሎሜን የገደልናለት እኔና ስርጉት ተባብረን ነው.››ስርጉት በተቀመጠችበት ሆና አቃሰተች….ዳኛው መተንፈስ ከበዳቸው፡፡ሳራ ግን ለማናቸውም ግድ አልነበራትም..የእሷ ዋናው ትኩረት ልጇን ከእስር ማዳን ብቻ ነው..እና ንግግሯን ቀጠለች፡፡

‹‹.የዛን ቀን አንተ እኛን ወደቤታችን ከመሸኘትህ በፊት መጠጧ ውስጥ መድሀኒት ጨምረንባት ነበር..ከ30 ደቂቃ በኃላ እንደማሳበድ አድርጓት በአንድ ሰአት ውስጥ ሙሉ በሙሉ የሚገድላት መድሀኒት ነበር፡፡እሷ  የተቀየረችብህና ከመስታወት ላይ ግንባሮሯን የከሰከሰችው በመድሀኒቱ ተጽዕኖ ነው…መስታወቱ ሆዷ ውስጥ ቢሻጥ እንኳን  አልሞተችም ነበር…አባትህ መጥቶ ሀኪም ቤት ሊወስዳት መኪናው ውስጥ አስገብቶ መንገድ ከጀመረች በኃላ ነው እስትንፋሷ የተቋረጠው…ያም የሆነው በተወጋችው ውግ ወይም በፈሰሳት ደም ሳይሆን በጠጣችው መርዝ ምክንያት ነው፡፡

‹‹እማዬ ይሄን እንዴት እሰከዛሬ ሳላውቅ…?አባዬ አንተ እንዲህ መሆኑን ታውቃለህ?››ሲል አባቱ ላይ አፈጠጠበት፡፡
አቀርቅሮ የነበረው አቶ ፍሰሀ በከፊል ቀና አለና ‹‹ከአንተ እና ከአለም በስተቀር ይሄንን ጉዳይ እዚህ ቤት ያለው ሁሉም ሰው ያውቃል፡፡››ሲል እውነቱን ፍርጥም ብሎ መለሰለት፡፡

‹‹ምን አረገቻችሁ ቆይ …?ምናችሁ ላይ ደረሰች?››አለም በእንባ ታጥባ እየነፈረቀች ሳራ ላይ አፈጠጠችባት፡፡

ሳራ እሷን ችላ ብላ ወደልጇ እየተመለከተች‹‹አንተን እንዳታገባህ እና ከስርህ እንድትርቅ ለአመታት ለመናት.. አስጠነቀቅናት፤ እሷ ግን ሌላ ሰው አግብታ ወልዳ እንኳን ልትተውህ አልቻለችም…የልጄ ህይወት በእንደዛ አይነት ሁኔታ ሲበላሽ ቆሜ ማየት አልቻልኩም፡፡እኔ ስርጉትን እንድታገባ ነበር ምፈልገው፣ከልቧ በጣም የሚታፈቅርህ ሰሎሜ ሳትሆን ስርጉት እንደሆነች በደምብ አውቃለው..››
ወዲያው ሳራ ንግግሯን እንዳገባደደች ኩማንደር ተቀበላት‹‹ያው እንግዲህ መጠኑ ይለያይ እንጂ በእናትሽ ግድያ ሁላችንን የየድርሻችንን ተወጥተናል…እኔ በእለቱ እስከእራት ሰዓት ድረስ ብቻ ነበር አብሬቸው የቆየሁት…ከለሊቱ ዘጠንኝ ሰዓት ጋሽ ፍሰሀ ደወለልኝ.. ስመጣ
…እናትሽ ጋሼ መኪናው ውስጥ እጥፍጥፍ ብላና በደም ተበክላ ነበር…ጋሼ የሆነውን በአጭሩ አስረዳኝና የሚሆነውን እንዳደርግ ሀላፊነቱን ለእኔ ሰጠኝ ….ነገሩ ወደህግ ከሄደ ጁኒዬር፤ሳራም ሆነች ስርጉት ዘብጥያ መውረዳቸው አይቀርም …ምን ማድረግ እንዳለብኝ ሳስብ ያ ሊቁ የተባለው እብድ በዛ ውድቅት ለሊት እየለፈለፍ በእርባታ ድርጅቱ ፊት ለፊት ባለው መንገድ ሲያልፍ አየሁት..ወዲያው ሀሳብ ብልጭ አለልኝ..ሮጥኩና ይዤው ወደውስጥ ገባው..ከማታ እራት የተረፈ ምግብና መጠጥ ስለነበረ እሱን ሰጠሁትና ስለማደርገው ነገር መዘጋጀት ጀመርኩ..የምጠቀምበት እቃ ስፈልግ የእንስሳት ዶክተሩ የህክምና ቁሳቁስ የሚይዝበትን ሳጥን በረንዳ ላይ ተቀምጦ ነበር፤አይኔ ውስጥ ገባ፣ ቶሎ አልኩና ከፈትኩት ፡፡ የቀዶ ህክምን ሚገለገሉበትን ቢላዋ አገኘሁና .. በወቅቱ በጣም ተደናግጬ ስለነበረ የማደርገውን ሁሉ የማደርገው በደመነፍስ ነበር….እና ያው ልጅ እንደገደላት እንዲመስል አደረኩና ጥዋት ለፖሊስ ተደወለ.. በኃላ ነገሮች በጥሩ ሁኔታ እየተጓዙ ሳለ አያትሽ ልጄን የገደላት እብዱ ሳይሆን እነሱ ናቸው… የሚል ወሬ መንዛት እና
አቤቱታ ማሰማት ጀመሩ…ከዛ ጉዳዩ በሚመለከታቸው ሰዎች ዘንድ አንዳንድ ጥርጣሬዎች ብልጭ ማለት ጀመሩ..ሬሳው በደንብ ይመርመር የሚል ግሩፕ ተነሳ…ከዛ ከጋሼ ጋር ተማከርንና የሆስፒታሉ የሬሳ ማስቀመጫ ክፍል እሳት እንዲነሳና እሬሳውም እንዲቃጠል አደረግን..በስተመጨረሻም አያትሽን ይሄንን ሀገር ለቀው ካልሄዱ አንቺን ነጥቀን እስከወዲያኛው እንዳያገኙሽ እንደምናደርግ አስፈራርተናቸው ዝም እንዲሉና ከተማውንም ለቀው እንዲሄዱ አደረግን…እናም በተጨማሪ ስለእናትሽ አሟሟት ሊነግርሽ ነበረውን ሙስጠፋንም የገደልኩት እኔ ነኝ!!የዛን ቀን እኛ ሳናየው እዛ ተደብቆ እያንዳንዱን ነገር ሲያይ ነበር….ይሄን ሁሉ ነገር ግን ፍርድ ቤት ቀርቦ ያምንልኛል ብለሽ እንዳትጠብቂ…››ሲል ንግግሩን አገባደደ፡፡

አለም ደም በለበሱ አስፈሪ አይኖቾን ኩማንደሩ ላይ አፍጥጣ‹‹ቆይ ቆይ እስኪ…ልጁ የገደላት ለማስመሰል ከሞተች በኃላ በዛ የቀዶ ጥገና ቢላዋ ደጋግመህ ወጋሀት አይደል?
…?ከዛ ደሟ ሲንፎለፎል በእጅህ እየዘቅክ እዛ ሚስኪን ልጅ ልብስ ላይ አዳረስከው …እንዳዛ አይደል ያደረከው?በቁሟ እያለች በፍቅር ልብህን ስለሰበራች ልትበቀላት ታስብ ነበር፣ግን ለማድረግ ወኔ አልነበረህም..በዛን ወቅት ግን አጋጣሚው ተመቻቸልህ..ነፍሷ ውስጧ ባይኖርም ደጋግመህ ሰጋዋን በመበሳሳት ንዴትህን ተወጣህባት….ከዛ ሬሳዋ ለምርመራ ሆስፒታል ገባ ..አንዳንድ ጥርጣሬ የሚያስነሱ ነገሮች መፈጠር ሲጀምሩ እራሳችሁን ከማንኛውም አደጋ ጥርጣሬ ለመጠበቅ አስፈላጊ ስለነበረ ጋሼ ፍሰሀ ደግሞ የሆስፒታሉ የሆነ ክፍል በእሳት እንዲያያዝ እና ሬሳዋም እንዲቃጠል እና አመድ እንዲሆነ አደረገ..ከዛ አቶ ዳኛ በዚህ ወንጀል ውስጥ ልጁ ስላለችበት ይህንን ወንጀል እንዳይጋለጥ ባለህ ስልጣን ሁሉ ተጠቅመህ ፋይሉ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲዘጋ አደረክ…፡፡በትክክል ተረድቼችኋለው አይደል..?እንዲህ ነው ያደረጋችሁት?
‹‹ሁሉም በመሸማቀቅ አንገታቸውን አቀርቅረው ነበር የሚሰሟት‹‹እስከአሁን እንደሰማሁት ከሆነ እኮ ጁኒዬር ብቻ አይደለም ራሱን ለህግ አሳልፎ መስጠት ያለበት …ሁላችሁም ናችሁ..እና እኔ ዳኛ ብሆን በጣም ትንሹን ፍርድ የምፈርደው በእሱ ላይ ነው….እሱ ሳያስበው…በድንገተኛ አደጋ የፈጠረው ወንጀል ነው…ሌለቻችሁ ግን አስባችሁ እና አቅድ አውጥታችሁ ደግማችሁ ደጋግማችሁ እናቴን በነፍስም በስጋም አጥፍታችኃታል….እና ነገ ወደከተማ ስንመለስ ምን እንደምታደርጉ ለማየት በጣም ጎጉቼለው….፡፡››

‹‹መቼስ ሁላችንም ሳታጠፊን እንቅልፍ አይወስድሽም አይደል…?ደስ ይበልሽ ይሄው ተሳካልሽ››አሉ ዳኛው ቅስማቸው ስብርብር ብሎ፡፡

‹‹ደስ ይበልሽ !!….ጭራሽ ደስ ይበልሽ…?.ፍርድን በአደባባይ ሲሸጦት ያዛን ጊዜ ማሰብ ነበረቦት››

‹‹አይ መሬት ያለ ሰው….በእኔ ላይ የደረሰውን ወላጅ ስትሆኚ ነው የምታውቂው….ልጄን ከእስርና ከእንግልት ለማዳን ስል ነው እዚህ ውጥንቅጥ ውስጥ የገባሁት››

‹‹አይ ልጆትን ከእስር ለማትረፍ ብቻ አይደለም….ከሶሌ ኢንተርፕራይዝም የ10 ፐርሰንት የአክሲዬን ድርሻ በልጆት ስም ማግኘት ችለዋል፡፡››

‹‹ይህ ፍፁም እውነት አይደለም…ያንን አክሲዬን የገዛሁት በራሴ ብር ነው….ከወላጆቼ በውርስ ያገኘሁትን ንብረት በጠቅላላ ሸጬ ነው የገዛሁት…ያንንም ፈልጌው ሳይሆን ኩማንደሩ እና ፍሰሀ አስገድደውኝ ነው፡፡በልጄ አስፈራርተውኝ ነው››

ዳኛው የሚናገሩትን ባለማመን ቀና አለችና ኩማንደሩ ላይ አፈጠጠችበት፡፡
‹‹አዎ..እውነቱን ነው፡፡ይሄንን ወንጀል ዛላለም በመሀከላችን እንደተቀበረ እንዲቆይ እርስ በርስ የበለጠ መተሳሰር አለብን ብለን አሰብን…ከዛ ከጁኒዬር እና ከሳራ ድርሻ ላይ ተቀንሶ በስርጉት ስም አክሲዬን እንዲገዙ አደረግን….ባይሆን እኔ ቀጥታ ጠይቄ ባይሆንም ከእናትሽ ሞት በኃላ የአክሲዬን ድርሻዬ ወደ30 ፐርሰንት እንዲያድግ ሆኗል….››
46👍5😱2