አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ


#ክፍል_አስራ_ሰባት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


እንደተለመደው እቤቴ አልጋዬ ላይ በጀርባዬ ተዘርሬ በመተኛት ጣፋጮና ተወዳጇ ልጄ በቴሌግራም የላከችልኝን የእናቷን ዲያሪ በከፍተኛ ተመስጦና ውስጥን በሚሸረካክት የልብ ድማት ያለፈ ታሪኬን እያነበብኩ ነው፡፡
////
ማትሪክ በተቀበልን  በአንድ ወር ውስጥ  ለሰርግ ሽር ጉድ ተጀመረ..፡፡ለሠርጉ 15 ቀን ሲቀረው ጨነቀኝ..፡፡በረሽ ጥፊ ጥፊ..ወይም እራስሽን አጥፊ የሚል ስሜት ይተናነቀኝ ጀመር...፡፡እስቲ በፈረሰኛው በግድ  ካላገባሽ  እቆራርጥሻለሁ ብሎ ያስፈራራኝ ሰው የለ... ሁሉንም ያደረኩት በራሴ ፍቃድና ምርጫ ነው። እንደውም ቤተሠቦቼ በዚህ ሀሳብ እንዲስማሙ ለማሳመን ብዙ ነገር ቀባጥሬ ነበር...እና ታዲያ  ?የቁርጡ ቀን ሲመጣ ምነውሳ...?ዋናው ጉዳይ ከእዬቤ እንዴት አድርጌ የምር እለያለሁ ?የሚለው ሀሳብ ነው እረፍት የነሳኝ....፡፡ እርግጥ አውቃለሁ ወደ ጋብቻው የገባሁበት ዋና አላማ ከእዬብ ለመራቅ ከአምላክ የተላከ ልዩና ረቂቅ ዘዴ አድርጌ በደፈናው ተቀብዬው ነበር እንጂ ዝርዝር ጉዳዬች ላይ በደንብ  ያሰብኩባቸው አልነበረም። ይታያችሁ ባል ካገባው እኮ አብሮ ማደር ከዛም ያለፈ ነገር ማድረግ የግድ ነው ፡፡ በህልሜም ሆነ በእውኔ ከእዬብ ገላ ውጭ የወንድ ገላ  ታስቦኝ በፍፁም አያውቅም።የሚገርመው እናትና አባቴን ጨምሮ የቤቱ ሰው ሁሉ በደስታ ሰክሮ ለድግሱ መሳካት ጠብ እርግፍ ሲል እዬቤ ግን ልክ  እንደእኔ በተመሳሳይ ሁኔታ ድባቴ ውስጥ ገብቶ ነበር።አሳዘነኝ።እሱም እንደ እኔ ያፈቅረኝ ይሆን እንዴ?ለመጀመሪያ ጊዜ በአእምሮዬ የተሠነቀረ አስደሳች ጥርጣሬ ነበር ፡፡

ለማንኛውም የሰርጉ ቀን ደረሰ በተክሊል ስለምንጋባ ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ ለሊት ስምንት ሰዓት ነው ቤተክርስቲያን የሄድነው። ግን በተክሊል እንዴት ልንጋባ ወሰንን? እርግጥ ሀሳብን ቀድሞ ያቀረበው መስፋን ነው።ግን እኔም ያለምንም ማቅማማት ነበር እሺ ያልኩት ፡፡ለዚህም ምክንያቴ በዋናነት ሁለት ነው። አንደኛው በተክሊል መጋባት ጋብቻውን ጥብቅ ስለሚያደርገው ወለም ዘለም የሚለውን ልቤን ያቃናልኛል ወይም መስመር ያስገባልኛል ብዬ ስላመንኩ ነው።ሁለተኛው ብዙ የሠንበት ት/ቤት ጓደኞቼ በተክሊል ሲያገቡ ሚዜም ሆነ አጃቢ ሆኚ አይቼ ስለነበረ እኔም አንድ ቀን እንደዚህ አገባ ይሆን የሚል የተደበቀ ምኞት በውስጤ ስለነበረ ያንን ምኞቴን ለማሳካት ያገኘሁትን እድል ለመጠቀም ነበር።

ስርዓቱም ከቅዳሴው ጥዋት ሶስት ሰዓት ተጠናቀቀ።በሰንበት ት/ቤት መዘምራን የሠርግ መዝሙር በመታጀብ ወደ የቤታችን ሄድን።እንግዲህ  ምሳ ሰዓት ላይ ሙሽራው ከሚዜዎቹና አጃቢዎቹ ጋር መጥተው እስኪወስድን የተወሰነ ለማረፍና ለመዘገጃጀት የሚሆን ጊዜ ይኖረናል ብዬ ነው።እቤት ከገባን በኃላ ትንሽ ለማረፍ ሞከርኩ እንቅልፍ ሊወስደኝ ግን አልቻለም፡፡ ተነሳሁና እየተኳኳሉና እየተቆነጃጅ ካሉት ሚዜዎቼ ጋር ተቀላቀልኩ።እኔም መዘገጃጀት ስላለብኝ ያሳምሩኝ ጀመር...፡፡ሁሉም ደስተኛ ይመስላል... የተከፈተ ጥርስ..የፈገገ ፊት...በማይክራፎን የተለቀቀ መዝሙር እኔ ግን ቅር እንዳለኝ ነው ።ከቤተ ክርስቲያን መልስ ጀምሮ እዬቤን አላየሁትም።የት ገባ?ከአሁኑ በጣም ነው የናፈቀኝ።እህቴን ጠራኋትና ጠየቅኳት..እንዳላየችው ነገረችኝ።ሌላ የምትሰራውን ስራ ሁሉ ትታ እሱን ፈልጋ እንድትጠራልኝ ጠየቅኳት...ሌላ ቀን ቢሆን የራስሽ ጉዳይ ነበር የምትለኝ።በእለቱ ግን ያው የቤቱ ንግስት ነኝና  ጥያቄዬን በእሺታ ተቀብላ ልትፈልገው ወጣች።

15 ከሚሆኑ ደቂቃዎች በኃላ ይመስለኛል እየተጎተተ በግድ የፈገገ ግን ደግሞ የዳመነ ፊቱን ይዞ መጣ..ሴቶች የሞሉበትን ክፍል በራፍ ላይ ቆሞ አንገቱን ወደውስጥ አስግጎ  ‹‹ሪች ፈለግሺኝ" ሲል ጠየቀ….ገና ድምፁ ጆሮዬ ከመድረሱ ሰውነቴ በጠቅላላ ነዘረኝ፡፡

‹‹አዎ ግባ››

‹‹ወዴት ልግባ..?››

‹‹ጥፋሬን ቀለም እየተቀባሁ ስለሆነ እኮ ነው..ግባ የማታውቀው ሰው የለም "ብዬ አደፋፈርኩት፡፡ገባና ወደእኔ ቀረበ..እንዲቀመጥ ኩርሲ ከጎኔ አስቀመጥኩለት እያቅማማ ተቀመጠ።እዛች ክፍል ውስጥ የተጠቀጠቁት ሴቶች ጆሮና አይን በጠቅላላ እኛ ላይ እንደሰፈረ አውቃለሁ። ቢሆንም ምርጫ የለኝም።ድምፄን ቀነስ አድርጌ በሹክሹክታ መጠን

"የት ጠፍተህ ነው? ናፈቅከኝ እኮ"አልኩት

"ደክሞኝ ተኝቼ ነበር"

"የት?"ይህንን ጥያቄ የጠየቅኩት የእኔና የእሱን የጋራ ክፍል አሁን እያተረማመሰነው ስለሆነ ብዬ ነው፡፡

"እቴቴ ክፍል"

"አይንህ ግን ምንም የተኛ ሰው አይን አይመስልም"
እንደዛ ያልኩት አይኑ በርበሬ ይመስላል እንደሚባለው ቀይ ሆኖ ስለደፈራረሰ ነው።

"ተኝቼ ነበር እኮ አልኩሽ...አሁን ለምን ፈለግሺኝ?"ቆጣ አለ፡፡

"አትቆጣኛ"

"አልተቆጣሁሽም"

"አብረኸን ትሄዳለህ አይደል?"

ደንግጦ"የት?"

ለእሱ መልስ ከመመለሴ በፊት ‹‹ተነሡ ተነሱ ሰርገኛው ደረሰ ተዘጋጅ ..››የሚል የማንቂያ ድምፅ ከውጭ ተሰማ…ትርምስምስ ተፈጠረ... የእሱን አደነጋገጥ እስከዛሬም በፊቴ ላይ አለ።በርግጎ ተነስቶ ፊቴ ተገተረ...እኔም ተነስቼ ቆምኩ።ተጠመጠምኩበት..ጭምቅ አድርጎ አቀፈኝ።እንባዬን ዘረገፍኩት እሱም ተንሰቅስቆ ማልቀስ ጀመረ።ሊያላቅቁን መሀላችን ገቡ።

‹‹አረ ቆርበሽ እንዴት ታለቅሺያለሽ?››

"አገባች እንጂ አልሞተች… የምን ሟርት ነው?።››

"አረ ተው ነውር ነው።››
ሁሉም የመሰለውን ተንጣጣ...አላቀቁን ።እዬቤ ተስፈንጥሮ ክፍሉን ለቆ ተፈተለከ።ከፋኝ ።በጣም ከፋኝ።ፈፅሞ ጥሎኝ እንዲሄድ አልፈለኩም ነበር።እጥፍጥፍ አድርጌ ጡቶቼ መሀከል ከትቼ በየሄድኩበት ይዤው ብሄድ  ደስተኛ ነበርኩ።..የምሳ ፕሮግራሙ ሲካሄድም ሆነ እኛ ቤት የነበረው  ዝግጅት ተጠናቆ ከእኛ ቤት ወጥተን ስንሄድ አይኔ ቢንከራተትም እዬቤን ዳግመኛ ሳላየው ነበር የእናትና አባቴን ቤት ለዘላለም በሚመስል  መንገድ ለቅቄ  በቅርብ ከተዋወቅኩት እና በቅጡ እንኳን ያለመድኩትን ሰው ተከትዬ የሄድኩት።

ሙሽራው ሙሽሪት..እንኳን ደስ ያላችሁ
የአብርሀም የሳራ-ይሁን ጋብቻችሁ።

እንደዛ እንደዛ እያለ ሰርጉ ተጠናቀቀ ..መሸ ጫጉላ ቤት ገባን ..እግዚያብሄር ይመስገን ፡፡ በተክሊል ስለተጋባንና በእለቱም ስለቆረብኩ ግንኙነት ማድረግ አይፈቀድም ነበርና አንድ አልጋ ላይ ብንተኛም ሰውነታችንን እንኳን ሳናነካካ ተራርቀን ተኛን ፡፡የሁለት ቀን የተጠራቀመ እንቅልፍ ስለነበረብኝ የት እንዳደርኩ አላውቅም ነበረ ።የሚገርመው ጥዋት እንደነቃሁ በእጆቼ የሞጨሞጩ አይኖቼን እያሻሸው"እዬብ ነጋ እንዴ?"ብዬ ነበር ጠየቅኩት ።ደግነቱ ክፍል ውስጥ ማንም ስላልነበረ የሰማኝ ሰው አልነበረም። እንደምንም አልጋዬን ለቅቄ በመውረድ ልብሴን እየለበሰኩ ሳለ በሩ ተከፈተና መስፍኔ ገባ፡

"እንዴ ተነሳሽ እንዴ?"ዝም አልኩት።

"ምነው አመመሽ እንዴ?"አለኝ ወደእኔ እየተጠጋ።

ጭራሽ እየታገልኩት የነበረውን ስሜቴን ነቅንቆ አደፈራረሠው...እንባዬን ዘረገፍኩት።

"እንዴ ምነው?ምን ተፈጠረ?"

"እዬቤ"

"እዬቤ ምን ሆነ?››
👍768🥰1😢1
#ባል_አስይዞ_ቁማር


#ክፍል_አስራ_ሰባት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

///
ልዩ ቃል ቤት ነው ያለችው….እየሳቁና እየተጫወቱ  ሳለ ድንገት በራፍ ተንኳኳ
"ቆይ አንዴ..›› አለና ሄዶ ከፈተ::
"እንዴ ጊፍቲ ከየት ተገኘሽ?"ጎትቶ አስገባትና እቅፉ ውስጥ ሸጎጦ አወዛወዛት፡፡
በተቀመጠችበት ወንበር ወደ ውስጥ   እየሠመጠባት ያለ መስሎ ተሠማት.. ‹‹ፍቅረኛው ይህቺ ነች  ማለት ነው?››ስትል እራሷን ጠየቀች፡፡ከአመታት በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአንጀቷ  ፀለየች.. "እባክህ አምላኬ..ምን አለ እጮኛው ከምትሆን እህቱ ሆና በሆነ..››ደግሞ በምናቧ ከሳለቻት በላይ ቆንጆ ሆና ታየቻት…‹‹ ከእሱ ጋር አንድ ላይ ሲታዩ መንታ እህቱ ነው የምትመስለው"አለች
ቃል ጊፍቲን አቅፎ ብቻ አልበቃውም ጉንጯን እያገላበጠ ሳመትና ወደእሷ ይዞት መጣ...
ከእሷ አንድ ሶስት አመት በለጥ ትላለች ..እንደእሱ ጥንቅቅ ያለች ነገር ነች።‹‹ልዩ ተዋወቂያት ..ጊፋቲ ማለት በጣሞ የምወዳት የልጅነት ጓደኛዬ ነች"..
ልዩ እጮኛዬ ነች ይላል ብላ ነበር የጠበቀችው… ጓደኛዬ ነች ስላላት ደስ አለት…ከተቀመጠችበት እንደመነሳት ብላ  እጇን ለሠላምታ ዘረጋችላት፤እሷም በተመሳሳይ  ድንግርግር ያለ ስሜት ላይ ያለች ይመስላል.. .የዘረጋችላትን እጇን በስሱ ጨበጠችና‹‹ ጊፍቲ እባላለሁ"አላቻት።
"ልዪ"
ሁለቱም ፊት ለፊት ተፋጠው ተቀመጡ
ቃል "ሱቅ ደርሼ መጣሁ..ተጫወቱ›› ብሎቸው ወጥቶ ሄደ..ይሄንን ያደረገው ሆነ ብሎ ነው…
በራፉን አልፎ ከአይናቸው እስኪሰወር ሁለቱም አይናቸው እየተንከራተተ ነበር።ለሆኑ ደቂቃዎች  በዝምታ ከተገማገምን በኃላ ጊፍቲ ቅድሚያውን ወስደ ‹‹"ከቃልዬ ጋር እንዴት ተዋወቃችሁ...?የመስሪያ ቤት ጓደኛው ነሽ?"ስትል ያልጠበቀችውን ጥያቄ ጠየቀቻት፡፡
"ቃልዬ" ብላ ስትጠራው ቃሉ አፎ ውስጥ ሚቀልጥ ነው የሚመስለው
ልዩም ‹‹…አይ የስራ ባለደረባው  አይደለሁም ...ጓደኛው ነኝ"አለቻት ኮስተር ብላ.. ነገር አጨመላልቃለሁ ብላ ነው እንጂ ‹‹ፍቅረኛው ነኝ›› ልትላት ሁሉ ቃጥቷት ነበር፡፡
ጊፍቲ "ጓደኛው..."አለች በማሽሞጠጥ ቃና፡፡
"እ ምነው ...?ችግር አለው?"
"አረ በፍፅም የእኔ ቆንጆ...ብቻ የቃልዬ ነገር ይገርመኛል… ከልጅነታችን ጀምሮ በየጊዜው አዳዲስ ጓደኞች በማፍራት እንዳስገረመኝ ነው...ይሄው ለስራ ጉዳይ ለአንድ ወር ከስሩ ዞር ስል አንቺን የመሰለች አዲስ ጓደኛ አፍርቶ ጠበቀኝ።"
ልዩ ይህቺን ሴት ጠላቻት ‹‹..አሮጊት ነገር ነች .. እዩት በአንድ አረፍተነገር መናገር የፈለገችውን ሁሉ ስትናገር...ከልጅነት ጀምሮ እንደሚተዋወቁ...የእኔ እና የእሱ ትውውቅ ደግሞ ከአንድ ወር በላይ ዕድሜ እንደሌለው እርግጠኛ እንደሆነች አሳወቀቺኝ።›› ስትል በውስጧ ስለጊፍቲ  ንግግር የተሰማትን አብሰለሰለች፡፡
የመቆየት አፕታይቷ ተዘጋ...ቦርሳዋን ያዝችና ከመቀመጫዋ ተነሳች...፡፡
"እንዴ ምነው..?ቃልዬ ሳይመጣ ልትሄጂ ነው…ብና ወይ ሻይ ላፈላልሽ ነበር አኮ …?"አለቻት..ከፊቷ መፈገግ የሚናገረው ግን ተቃራኒውን ነው፡፡አዎ ጊፍቲ በልዩ መሄድ በጣም ደስተኛ እንደሆነች ነው፡፡
"በፊትም ልሄድ ስል ነው የመጣሺው...ቀጠሮ አለብኝ…ሻይ ደግሞ እደመጣሁ ነው ቃል አፍልቶ የጠጣነው"አለቻት…እንደዛ ስትል ቃል ቢሰማ ምን ሊያስብ እንደሚችል ታሰባትና ሽምቅቅ አለች...ምክንያቱም ከመጣች መምንም አይነት ሻይም ሆነ ቡና አልቀመሱም፡፡
"ካልሽ እሺ..አትጥፊ እዚህ ስትመጪ ታገኚኛለሽ"አለቻት…እሷስ መች የዋዛ…‹‹ለምን እዚህ ብቻ የቃል ጓደኛ ከሆንሽ የእኔም ጓደኛ ነሽ..ቁጥርሽን ስጪኝና እንደዋወል"
ቁጥሯን መስጠቷን እንዳልፈለገችው በሚያሳብቅ የድምፅ ቅላፄ "ይሻላል"አለቻት...
ልዩ  ግግም አለችባት...በውስጧ‹‹እንደው ከእዚህ ወጥቼ ባልደውልላት እንኳን እንዳበሳጨቺኝ ላበሳጫት።››ብላ ነው፡፡
ጊፍቲም እንደማትለቃት ሲገባት ቶሎ   እንድትወጣላት የፈለገች መሆኗን በሚያሳብቅ ፍጥነት ጥድፍ ጥድፍ ብላ ነገረቻት።
ጎንበስ ብላ ጉንጯን ሳመችትና ‹‹ቃልን እንዲህ ስመሽ ይቅርታ ጠይቂልኝ...ላንቺ ሰሞኑን ደውልልሻለሁ"
ጊፍቲ ምን እንደምትመልስልኝ በማሰላሠል ላይ እያለች ፈጠን ብላ እቤቱን ለቃ ወጣች።መኪናዋን ከጊቢ ውጭ ስላቆመች ቀጥታ ወደእዛ ሄዳ ለጠበቀላት ሊስትሮ ትንሽ ሳንቲም አስጨብጣ ቃል መንገድ ላይ አግኝቶ በጥያቄ እ ንዳያጣድፋት ስለፈለገች ፈጠን ብላ ሰፈሩን ለቃ ወጣች፡፡

ይቀጥላል
👍9916🤔6😢3🔥2👏2
#ተአምራተ_ኬድሮን


#ክፍል_አስራ_ሰባት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

///

ኬድሮን ካደረገቻቸው ሀገር አቋረጭ ጉዞዋች ውስጥ በጣም ድንቁና በህይወቷ መቼም የማተረሳው ወደታንዛኒያ ያደረገችው ጉዞ ነው ፡፡15 ዓመት ስትደፍን ሙሉ ወጣት ሴት ሆነች..የሰውነቷ ግዝፈትና የቁመቷ መመዝ ብቻ ሳይሆን የውበቷም መድመቅና መጉላት በሰፈሯም ብቻ ሳይሆን በከተማዋም በቀላሉ ሚለይና ልክ እንደሰንደቅ ምልክት ሆና መታየት ጀመረች…ከንስሯ ጋር ያለት መናበብና ቁርኝት በቃላትም የሚገለፅ አይነት አይደለም፡፡በተለይ የፈለገችውን ቦታ ወስዶ ስለሚያዝናናትና ስለሚሳያት በጣም ደስተኛ ብቻ ሳይሆን ስለአለም ያላት ግንዛቤና ስለተፈጥሮ ያላት ዕውቀት በጣም ጥልቅና በመገረም የተሞላ ሆነ ፡፡በትምሀርቷም በቀላሉ በሳምንት ሶስትና አራት ቀን ብቻ ክፍል ገባታ እየተማረች በትምህርት ቤቱ ታሪክ ታይታ የማታውቅ ኳከብና ተወዳጅ ተማሪ ሆነች፡አንደኛ ሴሚስተር ፈተና እንደተፈተነችና ትምህርት ቤት ለሳምንት እንደተዘጋ ረዘም ያለ ጉዞ ልትሄድ አሰበች፡ብዙ ቦታ በእምሮዋ መጥተው ነበር፤መጨረሻ ግን የአፍሪካ ጣሪያ በመባል ሚታወቀው ኪሊማንጀሮ ተራራን ሄዳ ለማየት ወሰነች፡፡ለእናቷ ለሶስት ቀን እንደማትኖር ተናገረችና በአነስተኛ ሻንጣ አንድ ሁለት ቀሚስና ፎጣ ነገር ያዘች… ዝግጁ ሆና ተነሳች..እናትዬው ወ.ሮ በሬዱ በመካከለኛ መጠን ባለው አገልግል የተጠቀጠቀ ጩኮ አስያዘቻት፡፡
‹‹እማ አሁን እኔና ንስሬ የምንራብ ይመስልሻል?››

‹ገራ ኮ እንደማይርባችሁ አውቀለሁ… .ግን ደግሞ ከእሱ ጋር ስጋ እየተናጠቁ መመገብ ብቻ ጤነኛ አመጋገብ አይሆንልሽም..አንቺ የእኔ ልጅ ነሽ …ሰው ነሽ እና እህልም  በመጠኑም ቢሆን ሰውነትሽ ማግኘት አለበት፡››

‹እሺ እማ..ብላ የእናቷን ጉንጭ ስማ ንሰሯን አቅፋ ሻንጣዋን በአንድ ትከሻዋ አገልግሏን ደግሞ በሌላዋ ትከሻዋ በማንጠልጠል ንስሯን ከደረቷ አስጠግታ በጡቶቾ መካከል ለጥፋ ከሰፈር ወጥታ ሄደች…  የያዘችው አቅጣጫ ወደምትሄድበትን የሚያመራ አይደለም….ስለዛ የምትጨነቅበት ምንም ምክንያት የለም…እሷ ሰፈሯን ለቃ ጭር ወደ አለ ጫካ ስፍራ ለመድረስ ነው እቅዷ.. ከዛ ንስሯን በአየር ላይ ለቀቀችው …ተርገፍግፎ ወደ ላይ በረረና አየሩን እየሰነጠቀ የተወሰነ ርቀት እየተገለባበጠ ለህዝቡ ትሪኢት እንደሚያሳይ የአንድ ሀገር አየር ኃይል ጀቶች የመከረባት ትርኢት አሳየና ወደእሷ እየተምዘገዘገ መጣ‹‹…ሰውነትህን እያሞሞቅክ መሆኑ ነው ›ስትል ፈገግ አለች…እሷ ግን ለእሷ ፈገግታ ምላሽ ሳይሰጥ በተለመደው ሁኔታ ማጅራቷ አካባቢ የለበሰችውን ልብስ ያዘና ከተሸከመችው ሻንጣና አገልግል ጋር አንድ ላይ በአየር ላይ አንጠለጠላትና ሽምጥ ወደላይ ተመነጠቀ…ከዛ በተለመደው ዘዴ ወደ ላይ ወርውሮ እየተምዘገዘገች ወደታች ስትወርድ ከኃላዋ ዞረና ጀርባዋ ላይ ተጣበቀባት…ከዛ ክንፍ ሆናት ማለት ነው፡፡ ከዛ በኃላ አቅጣጫውን ወደ ደቡብ  አስተካክላት እሷም  በተዝናኖት መብረር ጀመረች ፤መዳወላቡን ፤ነጌሌ ቦረናን፤ ሞያሌን በሩቁና በጭልጭልታ እያየች የኢትየጵያን ድንበር አቆርጠው ኬንያ ገቡ..የተወሰነ እንደተጎዙ በጣም ቀልብ ሚስብ ቦታ እይታዋ ውስጥ ገባ፡፡
ጀግናዬ እዛ ቦታ አረፍ ብንል ምን ይመስልሀል? ስትለው ከፍታውን እየቀነሰ ወደጎን እየተጎዘ ሄደና 20 የሚሆኑ ዝሆኖች ጀርባ ላይ ቁጭ አደረጋት ከጀርባዋ ተገንጥሎ ተለየና በራሱ መብረር ጀመረ .ደነገጠች.እሱ ከጭንቅላቷ በላይ በአምስት ሜትር እርቀት እየዞራት ነው፡፡ዝሆኑ እላዩ ላይ ዝንብ ያረፈበትም ሳይመስል ተረጋግቶ ከመሰሎቹ ጋር ወደፊት ጎምለል ጎምለል እያለ ይጓዛል…እሷ መረጋጋት አልቻለችም.. ዘላ እንዳትወርድ  ከግራም ሆነ ከቀኝ መአት ዝሆኖች ናቸው ያሉት መሬት አርፋ ተስተካክላ ከመቆሞ በፊት በግዙፈ እግሮቻቸው ሚጨፈልቋት መስሎ ተሰማት...እራሷን በጣም ግዙፍና የሰማይ ስባሪ አድርጋ ትቆጥር ነበር.አሁን ከከበቧት ዝሆኖች ጋር እራሷን ስታነፃፅር ግን በዳዴ ሚሄድ ህጸን ልጅ የሆነች መስሎ ተሰማት፡፡

‹‹ጀግናዬ ና አንሳኝ ብዬሀለው. ና››
ንሰሯ ላይ ጮኸችበት …እየተመዘገዘገ ወደእሷ መጠና ትከሻዋን በክንፎቹ ቸብ አድርጎት መልሶ ወደላይ ተነሳ
‹‹አንተ ጫወታ ነው እንዴ የያዝከው ?ስወድህ….?የእኔ ጀግና በእኔ ትጨክናለህ….አላሳዝንህም››ተለማመጠችው፡፡

መልሶ ተከርብቶ መጣና ማጅራቷን ይዞ ወደ ላይ ተነሳና ከዝሆኖቹ መንጋ 20 ሜትር ያህል ራቅ አድርጎ ለምለም ሳር መካከል ቁጭ አደረጋት፡፡ግራና ቀኝ ትከሻዋ ላይ ያለውን ሻንጣዋንና አገልግሏን ከላዮ ላይ አውልቃ ጥላ በጀርባዋ ተዘረረች…ወደ ውስጧና ወደውጭ ደጋግማ አየር እየሰባች ወደውጭ በመልቀቅ ውስጧ በንፅህ አየር ብቻ ሳይሆን መረጋጋትም እንዲነግስባት መሞከር ጀመረች…ንስሯ ከጎኗ መጥቶ ተረጋግጦ ተቀመጠ
ለመረገጋጋት 10 ደቂቃ ያህል ከወሰደች በኃላ 
አሁን ያረፉት መርሳቤት ብሄራዊ ፓርክ ነው፡፡ፓርኩ  ከናይሮቢ 540ሜትር  በስተሰሜን  አርቆ ሚገኝ አጠቃላይ ስፋቱ 600 ሜ.እስኬር ስፋት ያለው በመርሳቤት ተራራ ማሀከል አድርጎ በሰሜን ኬንያ  የሚገኘው ድንቅ ቦታ ኬድሮንና ንስሯ ከዚህ በፊትም አዘውትረው የሚጎበኙት  በጣም ተመራጭ ስፍራቸው ነበር.ይህ ከእኛው ሞያሌ በቅርብ እርቀት ላይ የሚገኘው ፓርክ በልዩ ተፈጥሮ የበለፀገ ስፍራ ነው፤፤ቦታው በጥቅጥቅ ደን የተሸፈነ፤ 3 ሀይቆች ያሉት በተለይ  ወፎችን በተመለከተ መነኸሪያቸው ነው ማለት ይቻላል.. ብዛታቸው የማይቆጠር ቀለምና አይነታቸው አስደማሚ ብቻ ሳይሆን ልብንም ስልብ የሚያደርግ ነው፤ከወፎች ቀጥሎ ዝሆኖች በብዛትና  በምቾት የሚንጎማለሉበት ስፍራ ነው፡: 
ልክ ስምንት ሰዓት ሲሆን አካባቢውን ለቀው ወደ ደቡብ ኬንያ ጉዞቸውን ቀጠሉ…የሚገኙበት በሌላ ጎን በአፍሪካም ሆነ በሀገረ ታንዛኒያ ሁለተኛው ረጅሙ ተራራ ከባህር ጠል በላይ 4566 ኪ.ሜት የሚረዝመው ሜሩ ብለው ሚጠሩት ተራራ የሚገኝበት የሚንዠቀዠቁ ያዶትን እና ዋቤ ሸበሌን መሰል ወንዞች የሚገኙበት የተፈጥሮ ገፀበረከት ቢፌ የሆነ ቦታ ነው ግን በመጠን ብዙም ሰፊ ያለሆነ አርሻ የሚባል ብሄራዊ ፓርክ ነው ከዛ ድንገት ኪሊ ማጀሮ ተራራ ትዝ አላት
አካባቢውን እስኪበቃቸው ከጎበኙና በኃላ ንስሯ እስከፈለገው ጥግ ያለማቆርጥ የመጓዝ ችግር ባይኖርባትም እሷ ከድካሟ የተነሳ ሰውነቷ ስለዛለ ከዛ በላይ መጓዝ አልፈለግችም..በአካባቢው ቅርብ ወደአለ ከተማ ሔደው  ማደር ቢችሉም ግን ደግሞ በተለየ ለንስሯ ደህንነት አሳሳቢ ከመሆኑም በተጨማሪ ለእሷ ለራሷም  ወደሰው ሀገር ለመግባት የሚያስችል ምንም አይነት ቢዛም ሆነ ፍቃድ ስሌላት እንደዛ ማድረግ አልመረጠች፣  
‹‹ጀግናዬ እዚሁ ነው የምናድረው… ዞር ዞር ብለህ እራትህ ፈልግና  ና.. እኔ የእናቴን ጩኮ  በዚህች ምንጭ ውሀ እያወራረድኩ እበላለሁ›› አለችው…ትዕዛዟን አክብሮ በረረ …እሷም በያዘችው ኮዳ እየተንኳለለ ከሚወርደው የምንጭ ውሀ ቀዳችና በአካባቢው ከሚገኝ ግዙፍ ዛፍ ስር ተጠግታ አረፍ በማለት አገልግሏን ከፈተች…ውስጡ በባለው ማንኪያ እየቆረሰች በቂቤ ተነክሮ የተሰረራውን የእናቷን ተወዳጅ ምግብ በደስታ እያጣጠመች በልታ..ሳትጨርስ ንስሯ የራሱን ግዳይ  በመንቁሩ አንገቱን አንቆ ይዞ መጣና  ሰሯ  አረፈ …ከዛ መሞቱን ካረጋገጠ እየዘነጣጠለ እስፈሪ በሆነ መንገድ መብላት ጀመረ

‹‹አረ ቀስ በል…..የት ትሄዳለህ?››አለችው፡፡
 
ይቀጥላል
👍1496🥰3🔥2😁2
#ትንግርት


#ክፍል_አስራ_ሰባት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


‹‹የግድ እኮ ወንድ ጓደኛህ መሆን የለበትም፤ሴትም ጓደኛህ ልትሆን ትችላለች...የመጨረሻ አንድ ማሳሰቢያ ሞባይል ስልኬን በመከታተል ጊዜ እዳታጠፋ...የተመዘገበው በእኔ ስም ሳይሆን እኔም በማላውቀው በሌላ ሰው ስም ነው፡፡አረብ አገር በሄደ ሰው ስም፡፡ለማንኛውም ቻው፡፡ ዝርዝር ህጎችን ቀኑን ስትወስን እንነጋገራለን፡፡ >> ሰልኩ ተዘጋ፡፡

ቀኑ አርብ ነው፡፡ የመጀመሪያ ዕድሉን የሚሞክርበት ቀን ነው፡፡ ቢሾፍቱ ሆራ ሀይቅ የእሬቻ በዓል የሚከበርበት ቦታ ላይ ከትንግርት ጋር ቆሞ በተመስጦ ይቃኛል፡፡ ከትንግርት ጋር ሊመጣ የቻለበት ምክንያት አካባቢውን የሚያውቅና ብቸኝነቱን የሚጋራው ሠው ይዞ እንዲመጣ ከምስጢር ጋር በተነጋገሩበት መሠረት ነው፡፡ከጓደኞቹ መካከል ደግሞ ቢሾፍቱን በጥሩ ሁኔታ የሚያውቃት ሰው አልተገኘም.… ከትንግርት በስተቀር፡፡

በመጀመሪያ ሁኔታውን ሲነግራትና አብራው እንድትሄድ ሲጠይቃት በመገረምና ብስጭት በተቀላቀለበት ስሜት አንገራግራበት ነበር፡፡ በኋላ ግን ተስማምታ እንሆ በዚህ ሠዓት ከጎኑ ትገኛለች፡፡

አሁን የሚገኙት ቢሾፍቱ ከተማ የኦሮሞ ማህበረሠብ ባህላዊ እምነት ማለት የኢሬቻ በዓል በሚከበርበት በሆራ ሀይቅ አካባቢ

ነው፡፡ እምነቱ በዓመት አንድ ጊዜ በታላቅ ክብረ በዓል በመስከረም ወር ከመስቀል ቀጥሎ ባለው እሁድ ቀን ይከበራል፡፡ ከተወሠኑ ዓመታት ወዲህ የእምነቱ ተከታዮች ብቻ ሳይሆኑ ሌሎች የሀገር ውስጥም ሆነ የውጭ አገር ቱሪስቶች የበዓሉ ተካፋይ እየሆኑ ስለመጡና መንግስትም ቱኩረት ስለሰጠው የታዳሚዎች ቁጥር በሚሊዬኖች ሆኗል ፡፡ ይህም ቁጥር ከዓመት ዓመት ዕድገት እያሳየ ነው ፡
በተጨማሪም በዚህ ቦታ በግለሠብና በግሩፕ በመሆን የተለያየ አምልኮ ስርዓቶችን ይከናወኑበታል፡፡ አካባቢው በትላልቅ ዛፎች የተከበበ ነው፡፡ከረጅም ጉብኝት በኋላ አካባቢውን ለቀው የመጀመሪያ ዕድሉን ለመሞከር ከምስጢር ጋር ወደ ተቀጣጠሩበት በቅርብ እርቀት ላይ ወደሚገኘው መኰንኖች ቁጥር ሁለት ሆቴል ሄዱ፡፡መኰንኖች ደርሠው ወንበር ይዘው ሲቀመጡ አስር ሠዓት ሊሆን አስራ አምስት ደቂቃ ነበር የሚቀረው፡፡

የሆቴሉ አፀድ ሆራ ሀይቅንና ዙሪያውን የከበቡትን ተራሮች በጽሞና ለማየት እንዲያመች ተደርጎ ነው የታነፀው፡፡ የተስተናጋጆች መቀመጫ በሦስት ደረጃ የተከፈለ ነው፡፡ከሦስቱ ደረጃዎች በተጨማሪ ሀይቁን ተጠግቶ ለመቃኘትና ፎቶዎችን ለመነሳት ሃያ አራት የሚሆኑ ደረጃዎችን ወደ ታች ተንደርድረው ከጨረሱ በኋላ እንደ መድረክ ሀይቁ ላይ በብረት ወለል የተሠራ ዙሪያውን 1.5 ሜትር ቁመት ባላቸው ነጭ ቀለም ተቀብቶ በተለያዩ ዲዛይን ባላቸው ባለብረት መከለያ ዘንጎች ተከልሏል፡ ደረጃው አካባቢ ዕድሜ ጠገብ የሚመስል ትልቅ የሾላ ዛፍ አካባቢውን በጥላ አልብሶት ልዩ ድባብ ፈጥሮበታል፡፡ ግቢው ዙሪያውን ግራና ቀኝ በተለያዩ ትላልቅና መካከለኛ መጠን ባላቸው አረንጓዴ ዛፎች የተሞላ ነው፡፡ ግቢው ብቻ ሳይሆን ሀይቁ ዙሪያውን የተደረደሩት ተራሮች አረንጓዴ የለበሱ ስለሆነ ከሀይቁ ጋር በማበር ልብን ስልብ ያደርጋሉ፡፡ሁሴንና ትንግርት

ሁሉንም ነገር በግልፅ ለማየት እንዲያመቻቸው ከላይ ነው የተቀመጡት፡፡

አስተናጋጁ መጣና ‹‹ምን ልታዘዝ?›› አላቸው፡፡

ሁሴን ስፕራይት ሲያዝ ትንግርት ቢራ አዘዘች፡፡

‹‹ምነው ስፕራይት...ጠጪ አይደለሁም ብለህ ዋሽተሀታል እንዴ?›› የአሽሙር ንግግር አሠማች፡፡

በመጠኑ ፈገግ አለ <<ባክሽ በደመነፍስ ነው ያዘዝኩት፤ችግሬ መች የመጠጥ አይነት ሆነና::>>

‹‹አሁን ካሉት ሠዎች እሷን የሚመስል ሠው አላጋጠመህም?››

‹‹ቆይ እስቲ አታጣድፊኝ፤ እያየሁ ነው፡፡ ለነገሩ ሠዓቱም አስር ደቂቃ ይቀረዋል፡፡›› በማለት አይኖቹን እነሱ በተቀመጡበት መስመር ወደ ኋላው አዙሮ አየ፡፡ ሴት የሚባል የለም፡፡ አንድ ስልሳ ዓመት የሚጠጋቸው ሽበታም ጥቁር ሠውዬ ቢራቸውን ከፊት ለፊታቸው አስቀምጠው ሲጋራቸውን ያቦናሉ፡፡

በቀኝ በኩል ዞሮ ተመለከተ፡፡ሁለት ወንበሮች የተያዙ አሉ፡፡ አንዱ ወንበር በሁለት ጎልማሳ ሲያዝ ሌላኛው በሁለት ጥንዶች ተይዞል፡፡ ዓይኖቹን ወደ ታች ላከ ወደ ሁለተኛው ዝቅታ ላይ ወደሚገኙት ተስተናጋጆች ሦስት ሴቶች የሚዝናኑበት ወንበር ከስድስት በላይ ወንድና ሴት የውጭ ዜጎች የተቀመጡበት ጠረጴዛም ታየው፡፡ ዳር ላይ አንድ ብቻዋን የተቀመጠች ሴት ሲያይ ልቡ ብትን አለበት፡፡ ዕድሜዋ በግምት ወደ ሠላሳ ይጠጋል፤ጠይም ነች፤ቆንጆም አስቀያሚም የምትባል አይደለችም፤ ጠረጴዛዋ ባዶውን ነው፤ ሞባይሏ ላይ አፍጥጣ ትጐረጉራለች፡፡

ምልከታውን ለሀይቁ ቅርብ ወደሆነው ሦስተኛው ዝቅታ አሸጋገረ፡፡ አብዛኞቹ ፍቅረኞች የሚመስሉ ጥንዶችና ነጠላ ወንዶች ይበዙበታል፡፡ ሀይቁ ላይ የተሠተረው መድረክም ባዶ ነው፡፡ ዓይኖቹን ወዳለበት
ሲመልስ ያዘዙት መጠጥ ቀርቧል፡፡ ትንግርት በአትኩሮት እያስተዋለችው መጎንጨት ጀምራለች፡፡ እሱም ፊት ለፊቱ ተከፍቶ የተቀመጠለትን ስፕራይት አነሳና አንዴ ገርገጭ በማድረግ ሊደርቅ የፈለገውን ጉሮሮውን አረጠበበት ፤ መልሶ አስቀምጦ ወደ ግራው ዞር ሲል ቅድም ያልነበረች አርባ አመት የሚዘላት አጭር ወፍራም ደማቅ ቀይ ሴት ከሽማግሌው ቀጥሎ ባለው ጠረጴዛ ላይ ተቀምጣ አያት፡፡

‹‹እንዴት ነው?›› አለችው ትንግርት፡፡

‹‹እኔ እንጃ፤እስካሁን ሁለት ሴቶች ብቻ ናቸው እዚህ ግቢ ውስጥ የሚታዩት፡፡››

‹‹የቷ እና የቷ?››

‹‹አንደኛዋ በስተግራችን ከሽማግሌው ቀጥሎ የተቀመጠችው፡፡››

ዞር ብላ አየችና ‹‹እሺ ትንሽ አሮጊት ትመስላለች፡፡››

<<ሁለተኛዋስ?>>

‹‹ሁለተኛዋ ትታይሻለች? እዛ ... >> ንግግሩን አልጨረሰም፡፡

«እዛ የት..?>>

‹‹ተይው በቃ አሁን ደግሞ ብቻዋን አይደለችም፤የሆነ ወንድ መጥቶላታል፡፡››
ከት ብላ ሳቀችና ‹‹ቆይ ግን ብቻዬን ነው የምመጣው ብላ ነግራሀለች?››

‹‹ታዲያ ከማን ጋር ትመጣለች?››

‹‹ለምሳሌ ከሴት ጓደኛዋ ጋር .. ወይም ልክ አንተ እኔን ይዘህ እንደመጣህ ፤ እሷም አንድ የድሮ ወንድ ጓደኛዋን ...>>

<የጉድ አገር ገንፎ እያደር ይፋጃል› አለ ያገሬ ሠው፡፡ እንደዛ ከሆነማ ጉድ ፈላብህ በይኝ፡፡ ምን አልባት ከሴት ጓደኛዋ ጋር ልትመጣ ትችል ይሆናል፤ከወንድ ጓደኛዋ ጋር ግን አታደርገውም፤ምክንያቱም አንድ ከወንድ ጋር ያለች ሴት እሷ መስላኝ በስህተት አበባ ባስታቅፋት እንዴት አይነት ችግር ውስጥ እንደምገባ መረዳት አያቅታትም፡፡››

‹‹ይሁንልህ፤እስቲ ቀስ ብለህ እያት ይህቺ ቦርጫሟ፡፡ ዝም ብላ ታይሀለች፤አይኖቿን በሽማግሌው አሻግራ እዚህ ነው የተከለቻቸው፡፡››

‹‹እየቀለድሽ ነው አይደል? .. ብሎ አይኑን ወደ ተባለችው ሴት ሲልክ እውነትም ዓይን ለዓይን

‹‹እውነትም አንቺ .. ይህቺ ግን አትሆንም››

‹‹እንዴት አትሆንም ..?››

‹‹እንደዛ አይነት ማራኪ ድምፅማ ከዚህች ወፍራም ሴት አይወጣም፡፡››

‹‹ባክህ እራስህን አትደልል፤ስንት ከዚህች እጥፍ የሚሠፉ ግን ደግሞ ልብን የሚሠልብ
ድምፅና ያነጋገር ለዛ የታደላቸው ብዙ ሠዎች እኔም አንተም እናውቃለን፡፡››

‹‹እሱስ ትክክል ነሽ›
👍889👎2
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ


#ክፍል_አስራ_ሰባት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

ሳባ የአሰላን ከተማ ለቃ እንደወጣች በደመነፍስ ነበር ስትነዳ የነበረው፡፡ ሀሳቧ ሁሉ ወደኃላ ተመልሷል..ያንን የተረገመ ስራ እንዴት እንደ ጀመረች አስር  አመት ወደኃላ ተመልሳ ማብላላት ጀመረች፡፡
ከ10 ዓመት በፊት
ያኔ በዛ ዘመን አዲሱን ስራዋን ለመጀመር ከሰገን  ጋር የመጨረሻ ድርድር ስታደርግ እና ሲለያዩ አንድ ምክር ሰጥታት ነበር…‹‹ድንግል ከሆንሽ ለምትወጂው ሰው ስጪው፡፡››ነበር ያለቻት…ግን በፍጥነት ማድረግ አልቻለችም ነበር…በወቅቱ የምትወደው ሰው ልቧን ሰብሮ ካሳዘናት ሰነባብቷል….‹‹ለእሱ ድንግልና ሳይሆን ከተቻለ በቀል ነው የሚገባው››ስትል  በማሰብ….ስለድንግልናዋ ማሰብና መጨነቅ ትታ…ዕቃዋን በየካርቶኑ እያስገበባች አሸገች፤ልብሶቿን በሁለት ሻንጣ ጠቅጥቃ አሳሰረች…የምትተኛበት ፍራሽ ብቻ እንደተዘረጋ ቀረ…ቀጥሎ ምን እንደምታደርግ ግራ ገባት፡፡መቼስ ይሄን ሁሉ ኮተት ይዛ በህዝብ ትራንስፖርት ተጠቅማ አሰላ ድረስ ማጓጓዝ አትችልም...እንዴት አድርጋ…‹‹ደግሞ ስኖርበት ባዶ የነበረው ቤት  አሁን ልለቅ ስል እንዴት ነው እንዲህ ሜዳውን የሞላው?››ሥትል በማሰብ ተገረመች፡፡‹‹ግን አሁን ይሄንን ሁሉ ኮተት ብረት ድስት፤ሰሀን፤ብርጭቆ ምድጃ ለምንድነው የሰበሰብኩት? ለምን ለተቸገረ አላከፋፍለውም?››ራሷን በትዝብት ጠየቀች፡፡
  ግን ደፍራ ነገ ሀብታምና  ሁሉ  ነገር  የተረፈው  እንደምትሆን  ተማምና ‹‹አይ ይሄን ኮልኮሌ አልፈልግም ላከፋፍለው››ልትል አልቻለችም…
ወሰነች.‹‹አዎ ብር አለኝ… አሰላ ድረስ የሚወስድልኝ መኪና ብፈልግ ይሻላል››ስትል አሰበች…‹‹አዎ መርካቶ ብሄድ ጭነት መኪና አላጣም….ጭነው ሲጨርሱ በዚሁ ጎራ ቢሉ ከላይ ጣል ጣል አድርገው ይወስዱልኛል….››ብላ ስሌት ሰራችና ወደመርካቶ ለመሄድ ካሰበች በኃላ ሌላ የተሻለ ያለችው ሀሳብ ብልጭ አለላት፡
ደምሳሽ ትዝ ኣላት….እርግጥ በወቅቱ ለዚህ የሚያበቃ ትውውቅም ሆነ ንግግር.አልነበራቸውም...ቢሆንም.ያው‹‹ቤተሰብ ሆነናል››ብሏት የለ. ብትጠይቀው ምንም ክፋት እንደሌለው አሰላች…ሸፌር ስለሆነ ሌሎች ሹፌሮችን ስለሚያውቅ ወደአሰላ የሚሄድ የጭነት መኪና ብዙም ሳይለፋ በስልክ ሊጨርስላት ይችላል…ስልኳን አወጣችና ደወለችለት..ከሶስት ጥሪ በኋላ ተነሳ..
‹‹ጤና ይስጥልኝ የእኔ እመቤት››

‹‹አቶ ደምሳሽ ሳባ ነኝ .አወቅከኝ?በቀደም…››

‹‹እመቤቴ አውቄሻለሁ..ማብራራት አይጠበቅብሽም…አንቺን እንዴት ልዘነጋ እችላለሁ፡፡ለዛውም ቤተሰብ ሆነን?››ነበር ያላት…
‹‹በእውነት ጥሩ ስሜት እንዲሰማኝ ነው ያደረከው››አለችው ከምሯ፡፡
‹‹አረ ምንም የተለየ ነገር አልተናገርኩም…ለማንኛውም ምን ልታዘዝ?››

‹‹እየፈራሁ  ነው  የደወልኩት..ሌላ  ላስቸግረው  የምችል  ሰው  ስለሌለ  ነው እባክህ ከድፍረት አትቁጠርብኝ››

‹‹በነገራችን ላይ  አልተነገረሽም መሰለኝ?››

‹‹ምኑን?››

‹‹ከዛሬ ጀምሬ በማንኛውም ነገር አንቺን እንድጠብቅ፤እንድታዘዝና የምትፈልጊውን ነገር ሁሉ እንዳሟላልሽ ታዝዣለሁ…ስለዚህ እኔን  ማዘዙን ከዛሬው ተለማመጂው…ለአንቺ መታዘዝ ስራዬ ነው›› አላት፡፡
‹‹ማዘዙን?››

‹‹አዎ ማዘዙን››

‹‹አይ እንዳልጠየቅህ አደረከኝ…በቃ ይቅርብኝ ሌላ አማራጭ እፈልጋለሁ፡፡››

‹‹አረ ተይ ቀለል አድርጊውና የምትፈልጊውን ንገሪኝ..ካለበለዚያ አሁኑኑ ሰፈርሸ እመጣለሁ››አላት
‹‹ኸረ ተው…እሺ ያው ሹፌር  ስለሆንክ ሹፌሮችን ታውቃለህ ብዬ ነው››

‹‹አዎ በደንብ አውቃለሁ…ምን ፈለግሽ?››

‹‹የፈለኩትማ ያው ሰሞኑን ስልጠና ጠቅልዬ ስለምገባ የምኖርበትን ቤት ለቅቄያለሁ….ቤተሰቦቼ ያሉት አሰላ ነው…እቃዎቼን ወደእዛ ለመውሰድ  ፈልጌ ነበር…እና ወደዛ የሚሄድ የጭነት መኪና ፈልጌ ነበር..እንዴት እንደማገኝ  ግራ ገብቶኝ ነው››
‹‹ወይ ለዚህች ነው እንዴ..?ለመቼ ነው..?››

‹‹ከተቻለማ ለዛሬ ነው…ካልሆነም ለነገ ጠዋት…››

‹‹ስልኬን ጠብቂ…መልሼ እደውላለሁ፡፡››

‹‹በእውነት ከልቤ ነው የማመሰግነው››

‹‹በይ ቻው በቤተሰቦች መካከል መመሰጋገን የለም ››ብሎ ስልኩን ዘጋ፡፡

ከ8  ደቂቃ  በኃላ  ነበር  ስልኳ  መልሶ  የጠራው…ስታየው  ደምሳሽ  ነው..በዚህ ፍጥነት አልጠበቀችም.
አነሳችውና ‹‹ሄሎ አገኘህልኝ?››አለችው፡፡

አዎ እቃሽ ብዙ ነው እንዴ ?ማለት ፒካፕ መኪና አይችለውም..?››

‹‹አረ በደንብ ነው ሚችለው››

‹‹እንግዲያው አሁን 5 ሰዓት ሆኗል 7 ሰዓት ሰፈር ደርሶ ይደውልልሻል..እስከዛ የቀረሽ ነገር ካለ  አስተካክይ››
በደስታ ስልኩን ዘጋችና የመጨረሻውን ዝግጅት ማድረግ ጀመረች፡


ለ7 ሩብ ጉዳይ ደወለላት...ፈጥና አነሳችው

‹‹ሄሎ ደምሳሽ...እንዴት ሆነልህ?››

‹‹ያው ግሎባል ጋር ሰማያዊ ደብል ፒካኘ ቲዬታ መኪና ይዞ እየጠበቀሽ ነው።››ስልኳን እያወራች ቤቱን ለቃ ወጣች‹‹እንዴት እንደማመሰግንህ አላውቅም"
"ችግር የለውም… ስትመጪ ምሳ ትጋብዢኛለሽ"
‹‹አረ  ችግር  የለውም...ግን  ክፍያውን  እንዴት  ነው  የማደርገው  ማለቴ
ነግሮሀል?"

‹‹ዋጋው ችግር የለውም...ወላጆችሽ ምሳና ቡና ከጋበዙት ይበቃዋል››
‹‹እውነቴን እኮ ነው...ትቀልድብኛለህ አይደል?››
በዚህ ጊዜ ግሎባል ጋር ደርሳ ነበር ...በምልክት የነገራትን ፒካፕ ወዲያው አየቻት...ለሹፌሩ ወደእሷ እንዲመጣ በእጇ ምልክት ጠራችውና መኪናዋን ማንቀሳቀሱን ካየች በኃላ ፊቷን አዙራ ወደቤቷ ተንቀሳቀሰች፡፡
‹‹ሰውዬውን አግኝቼዋለሁ" ‹‹እ..ታዲያ አናገርሽው?"  ‹‹አይ አላናገርኩትም"
"ታዲያ ልደውልለትና ልጠይቅልሽ ወይስ አንቺው እዛው ትከራከሪዋለሽ?"
‹‹አይ አመሰግንሀለሁ...ከዚህ በላይማ ላስቸግርህ አልፈልግም...በቃ ቻው።››
‹‹ቻው በቃ ሚቸግርሽ ነገር ካለ ደውይ››
እሷ የቤቷ በራፍ ጋር ስትደርስ ፒካፗ አጠገቧ  ደርሳ  በስሱ  ክላክስ  ሲያደርግላት ስልኩን ፈጠን ብላ ዘጋችና ወደግቢ ገብታ የመኪና መግቢያ በራፍ ከፈተች… መኪናዋ ወደውስጥ ዘልቃ ገባችና የግቢው መሀል አካባቢ ቆማ ከገቢናዋ  ሹፌሩ ዱብ ብሎ ወረደ...በድንጋጤ እጇን አፏ ላይ ከደነች።
‹‹ምነው አስደነገጥኩሽ እንዴ?››
"እዚህ ሆነህ ነው እንዴ የምታስለፈልፈኝ...?ባለመኪናው የት አለ?"
‹‹መኪናው የድርጅቱ ነው...ሹፌሩም ደግሞ እኔ ነኝ.."
‹‹ኸረ  ደምሳሽ  እንዲህ እኮ   መቸገር  አልነበረብህም።አሰላ  ድረስ  እኮ  ነው።

"ይሄ የእኔ ሀሳብ አይደለም..ታዝዤ ነው...መኪና እየፈለግሽ እንደሆነ ለሠገን ስነግራት...ራስህ አድርስላት ብላ አዘዘቺኝ...ይልቅ አሁን ሰዓቱ እየነጎደ ስለሆነ እቃሺን ቶሎ ጫን ጫን አድርገን እንውጣ›› አላት። እየከበዳት እቃዋን ወደ ተቆለለበት ክፍል ይዛው ገባች..እቃውን ጭነው ከግቢው ለመውጣት 20 ደቂቃ ብቻ ነበር የወሰደባቸው።
///
11 ሰዓት ላይ ቤት ደረሱ እቃው እስኪወርድ፤ መክሰስ በልተው የተፈላውን ቡና ጠጥተው እስኪያጠናቅቁ ለአንድ ሰአት ሩብ ጉዳይ ሆነ...ሳባ    ከቤተሰቦቿ ጋር ስትጫወት አድራ በማግስቱ ረፈድፈድ ሲል ነበር መመለስ   የፈለገችው። ያንን ዕቅድ ያወጣችው ሹፌሩ ደምሳሽ መሆኑን ከማወቋ በፊት ነበር። በኋላ ግን ለእሷ ብሎ አሰላ ድረስ መጥቶ እንዴት ብቻውን እንዲመለስ ትተወው?ያ ነው የጨነቃት፡፡ እርግጥ እርሱም በእንግድነት እነሱ ቤት እንዲያድርና ጥዋት አብረው እንዲመለሡ ጠይቃው ነበር። እሱ በማግስቱ 12 ሰዓት አዲስ አበባ ላይ የሚሰራው ስራ ስላለ እንደማይችል ስለነገራት አብራው ለመመለስ ወሰነች። ሁሉን
👍6810🔥1
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)


#ክፍል_አስራ_ሰባት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ምስራቅ ኮስተር ብላ ‹‹አትልፈስፈስ…ጠንከር ብለህ መሆን ስለሚገባው ነገር ብቻ እንነጋር፡፡››አለችው፡፡

ናኦልም‹‹ምን የሚሆን ነገር አለና እንነጋራለን…በዚህ ምድር ላይ አንድ አለቺኝ የምላት እህቴን እንዲህ ባለ ሁኔታ አጥቼያት እኔስ በህይወት መኖሬን ቀጥላለው?››ሲል መለሰላት፡፡
‹‹አይዞህ ኑሀሚ እንደዚህ ካሉ ብዙ አደጋዎች ሰርቫይቭ የማድረግ ልምድ ያላት ልጅ ነች፤ደግሞ በምድር ላይ ያለችህ እሷ ብቻ አይደለችም..እኔም እኮ ስላለሁ መሰለኝ አሁን በዚህ የሀዘንህ ወቅት አጠገብህ ያለሁት፡፡
‹‹እሱማ እውነትሽን ነው፡፡››
‹‹እኮ ..በል ተነስና መልስ እንመልስለት፡፡››
ከተዘረፈጠበት ተነሳና ወደእሷ ቀረበ‹‹ምን ብለን?››
‹‹ያልከኸውን አደርጋለው..ለማንም ሳልናገር ያልከው ሀገር ድረስ እመጣለሁ..ግን እህቴ በህይወት መኖሯን በምን አውቃለሁ?አንድ ማረጋገጫ ስጠኝ፡፡››
‹‹አዎ እንደዛ ብንለው ይሻላል አይደል…?ወይ ተጨማሪ ፎቶ ወይ ቪዲዬ ይልክልናል፡፡ወይ ደግሞ በስልክም ሊያገናኘን ይችላል፡፡››
‹‹በቃ ራስሽ ፃፊው››

እንደማሰብ አለችና ፃፈችና ላከች፡፡መልስ እስኪመጣ ለመጠበቅ ተያይዘው ወደሳሎን ሄዱ፡፡ለሁለቱም የሚጠጣ ቢራ አቀረበና እሱን እየጠጡ በትካዜ በስልኩ ከአሁን አሁን የሚላከውን ኢሜል መጠበቅ ቀጠለ፡፡
ከሶስት ሰዓት በኃላ ተጨማሪ ፎቶ ተላከላቸው፡፡እንሱ ያላወቁት እነዛ ፎቶዎች የተመረጡት ከኑሀሚ ስልክ ውስጥ በፔሩ ቆይታዋ በተያዩ ጊዜያቶች ከተነሳቸው ውስጥ የተመረጡትን ነው፡፡
ከፎቶ ጋር አጭር መልዕክት ተልዕኮል
‹‹ባቀረብንልህ ሀሳብ ከተስማማን አሁኑኑ አሳውቀን፡፡››ይላል፡፡

‹‹እ ምን አሰብሽ? ››አለት፡፡ ከምስራቅ የተሻለ ሀሳብ ለማግኘት እየተመኘ ጠየቃት.. ምርጫ የለንም ‹‹ተስማምቼያለሁ ብለህ ላክላቸው፡፡››እንዳለችው አደረገ፡፡
በል የጉዞ ሰነዶችህን አዘጋጅ…በሶስት ቀን ውስጥ አስፈላጊውን ገንዘብ ስለምንልክልህ ሙሉ ስምህን እና አስፈላጊ መረጃዎችን ላክልን፡፡እንደተነጋገርነው ግን ይሄንን ሚስጥር ሌላ ለሶስተኛ ወገን ለመንግስት አሳልፈህ ብትሰጥ ነገሮች ሁሉ ያከትምላቸዋል….ከዛ በኃላ
እህትህን በዚህ ምድር ላይ ዳግመኛ የማግኘት እድልህ ከዜሮ በታች ይሆናል…በል ፍጠን ይላል፡፡
‹‹አነበብሽው አይደል?››
‹‹አዎ ..አነበብኩት..››አለችና ከተቀመጠችበት ተነሳች፡፡
‹‹ምነው? ››
‹‹ልሄድ ነው፡፡››
‹‹ልሄድ ነው በእንደዚህ አይነት በተሰባበርኩበት ሁኔታ ላይ ሆኜ ጥለሺኝ ልትሄጂ ነው….፡፡››
‹‹ጎረምሳው ተረጋጋ እንጂ ..ይልቅ እራስህን ለረጅምና አስቸጋሪ ጉዞ አዘጋጅ፡፡እኔ ሄጄ ለጉዞ አስፈላጊ የሆኑ ፖስፖርትና ቢዛዎችን ላዘጋጅ፡፡ ታውቃለህ እነዚህን የጉዞ ሰነዶች በአሁኑ ጊዜ በስድስት ወር ውስጥም ማግኘት አይቻልም፡፡አኔ ደግሞ ከሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማግኘት

አለብኝ፡፡ ለዚህ ደግሞ ደቂቃዎችን ሳላባክን ከአሁን ያለኝን ኃይልና መስመር ሁሉ ተጠቅሜ ማሳካት መቻል አለብኝ…እ ምን ትላለህ ጎረምሳው?››
ተንደረደረ ሄደና ተጠመጠመባት፡፡እሷም እጆቾን በአንገቱ ዙሪያ ጠመጠመቻቸው… ጭምቅ አደረጋት፡፡
‹‹አንቺ ስላለሺኝ ሁሌ ደስተኛ ነኝ፡፡ዘላለም በእቅፍሽ ውስጥ መኖር ነው ምኞቴ…በጣም ነው የምወድሽ….››አላት
‹‹….ተራጋጋ፡፡ከዚህ በላይ ከወራን እንባዬ ያመልጠኛል፡፡››አለችና ከእቅፉ ወጥታ ፈዞ በቆመበት ፊቷን አዙራ ወጥታ ሄደች፡፡በቦዘዙ አይኖቹ በስስት እያያት በሀሳቡ ሸኛት፡፡..
///

ከሶስት ቀን በኃላ በአለምአቀፍ የሀዋላ አስተላላፊዎች አማካይነት 50 ሺ ዶላር ተላከለት፡፡ያልጠበቀው ነገር ነበር፡፡ብሩ ሲደርሰው ነገሩ ሲሪዬስ እንደሆነ እሱ ብቻ ሳይሆን ምስራቅም ተገነዘበች፡፡ሁለቱም መመለስ ያቃቸው ይሄ ሁሉ አጋቾቹ ይሄን ሁሉ ኢንቨስትመንትና ጥረት የሚያደርጉት ከእሷ ምን ፈልገው ነው? የሚለውን ነው ፤የእሱንስ ወደፔሩ መሄድ ለምን ፈለጉት?››በተለይ ይሄን ጥያቄ ከአንደበቷ አውጥታ ለእሱ አትንገረው እንጂ ምስራቅንም በጣም ነው ያሳሰባት፡፡
ናኦል ገንዘቡ እንደደረሰው ካወቀ በኃላ እንቅልፍ ሊወስደው አልቻለም፡፡ሰዓቱ ገፍቶ ከለሊቱ ስድስት ሰዓት ሆኖኛል በተኛበት አልጋ ላይ እየተገላበጠ በትዝታ ወደኃላ ወደልጅነታቸው ተጓዘ፡፡ምስራቅ እሱና ተወዳጅ እህቱን ከጎዳና አንስታ እንዴት ሰላይ እዳደረገቻቸው በዝርዝር ትዝ አለው፡፡
ከ15 አመት በፊት ምስራቅ የወንድሜ ቤት ነው ብላ ከጓዳና አንስታ ጎተራ የሚገኝ ኮንደምንዬም ቤት ከወሰደቻቸው በኃላ ከአዛው ቤት ሳይወጡ ሁለት ወር ሙሉ ቆይተው
ነበር፡፡ በሶስተኛው ወር ግን ማታ እራት በልተው ቴሌቬዥን እያዩ እያለ ድንገት ሪሞቱን አንስታ ቴሌቪዝኑን አጠፋችና ፊት ለፊታቸው ቁጭ አለች፡፡
እህትና ወንድም እርስበር ተያዩ ፡፡የሆነ ነገር ልትነግራቸው እንደሆነ ገብቷቸዋል፡፡፡ግን የጠረጠሩት በቃ እስካሬ ለሁለት ወር በምቾትና በድሎት በወንድሜ ቤት አኑሬያችኋለው፤ ከአሁን በኃላ ግን ምትኖሩበት ቦታ ፈልጉ ›› ትለናለች ብለው ነበር የጠበቁት፡፡ይሄንን ጉዳይ እሷ ቤት በማትኖርበት ጊዜ እያነሱ ተወያይተውበታል..ለዛ ነው በፍጥነት ወደሁለቱም ምናብ ሀሳቡ የመጣው፡፡
‹‹ልጆች በጣም እንደምወዳችሁ ታውቃላችሁ አይደል?››

‹‹አዎ እናውቃለን፡፡ እኛም በጣም እንወድሻለን››ሲል የመለሰላት ናኦል ነበር፤ኑሀሚ ግን ይሄንን ቤት ለቀው ከወጡ በኃላ ምን ማድረግ እንዳለበባቸው ስታሰላስል ነበር፡፡ደግማኛ ወንድሟን ይዛ ወደበረናዳ ለመመለስ ፈፅሞ ፍቃደኛ አልነበረችም፡፡ትንሽም ቢሆን የራሳቸው ቤት ተከራተው መኖር እንዳለባቸው ከወሰነች ሰነባብታ ነበር፡፡ለዛ ኪራይ ቤት ክፍያ ሚሆን ገንዘብ ለማግኘት ደግሞ ማንኛውንም ስራ ለመስራት ፍቃደኛ ነበረች፡፡ ለወንድሟ ስትል ብትሰርቅም ብትገድልም ግድ አልነበራትም፡፡
ምስራቅ ንግግሯን ቀጠለች‹‹ይሄውላችሁ ምን መሳላችሁ…አንደእኔ እንደእኔ ዘላለም እዚሁ አንድ ላይ እንዲህ እየተሳሰብን በፍቅርና በደስታ መኖር ብንችል ደስ ይለኝ ነበር… ግን ያው ታውቃላችሁ አይደል?››
ቀጥታ ወደጉዳዩ ገባች‹‹ማለት የምትፈልገውን ፍርታ ማለት ባለመቻሏ ሁለቱም ላይ ጭንቀት ፈጠረች…ኑሀሚ ፈጠን አለችና‹‹ይገባናል..እስከዛሬ ስለተንከባከብሽንና በዚህ ሁኔታ እንድናገግምና ስለወደፊታችን እንድናስብ ስላደረግሽን የላለም ባለውለታችን ነሽ፤ግን ወንድሜን ይዤ ወደበረንዳ መውጣት አልፈልግም…ከቻልሽ ለእኛ ምትሆን ትንሽ ቤት
ተከራይተን መኖር እንድንችል አግዢን፡፡ማንኛውንም ያገኘነው ስራ በመስራት የቤት ኪራዩን በመክፈል እራሳችንን ማኖር አያቅተንም…እቤት ካገኘን ነገ ተነገ ወዲያ እንሄዳለን..አንቺ አታስቢ››
ምስራቅ ፈገግ አለች‹‹እንዳዛ ማለቴ አይደለም፡፡እኔ እንደምታዩት እዚህ የምኖረው ብቻዬን ነው፡፡ ቤቱም ሰፊና ለሁላችንም የሚበቃ ነው፡፡እዚህ ከእኔ ጋር በመኖራችሁ በጣም ተጠቃሚው እናናተ ሳትሆኑ እኔ ነኝ….ግን ለእናንተ የወደፊት ህይወት ሲባል የተለየ መንገድ መከተል አለብን፡፡››
ሁለቱም  ስሜታቸው  ይበልጥ  ተናቃቃ፡፡የምትላቸው  በፍፅም እየገባቸው  አይደለም፡፡
‹‹አልገባንም›› አለች..ኑሀሚ፡፡
👍858😱1
#ጉዞ_በፀሎት
(አቃቂ እና ቦሌ)


#ክፍል_አስራ_ሰባት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧

ይዘውት የሄዱት ቦታ ከቢሾፍቱ ከተማ በባቦጋያ ሀይቅ አካባቢ ከከተማው ወጣ ብሎ የሚገኝ ቪላ ነው፡፡ይህ ቪላ ቤተሰቡ ከውጥረት ረገብ ለማለት ሲፈልግ የሚገለገልበት ስፋራ ነው፡፡ለአለፉት አንድ አመት ከግማሽ ማንም ዝር ብሎበት አያውቅም ነበር፡፡ሰለሞን ስፍራውን ሲያይ ከውበትም ሆነ ከፀጥታ አንፃር ሲታይ ሙሉ በሙሉ እሱ እንደሚፈልገው አይነት ሆኖ ነው ያገኘው፡፡አንድ ሺ ካሬ ሜትር በላይ የሚሆን ቅፅር ግቢ ነው፡፡መሀከል ላይ ግዙፍና ባለግርማ ሞገስ ጥንታዊ ግን ደግሞ ጥሩ ይዞታ ላይ ያለ ግዙፍ ቪላ ቤት አለበት…ግቢው ውስጥ እድሜ ጠገብ ግዙፍ ባለግርማ ሞገስ የባህር ዛፍና የጥድ ዛፎች ስብስባ ላይ እንደተቀመጠ ታዳሚ እዚህም አዛም ዙሪያውን ተሰራጭተው ይታያሉ…ገና ግቢውስጥ ገብተው እንዳቆሙ የቤት ጠባቂዎች በልና ሚስቶች በፍጥነት መጥታው መኪናዋ አጠገቡ ቆሙ፡፡መኪናዋን ሲነዳ የነበረው እራሱ ሰሎሞን ስለነበረ….ሞተሩን

አጠፋና ቀድሞ ወረደ…አቶ ኃይለመለኮትን ወ.ሮ ስንዱም ወረዱና ከጠባቂዎቹ ጋር ሰላምታ መለዋወጥ ጀመሩ…ከዛ ቀጥታ ወደ ቤት ነው የገቡት….ቀድመው ደውለው ስለነበር..እቤቱ ምሉ በሙሉ ፀድቶና የእነሱም መኝታ ክፍል ተዘጋጅቶ ነበር የጠበቃቸው….
ታፈሰ ‹‹ጋሼ ባዘዙኝ መሰረት ሶስት ክፍል ለመኝታ አዘጋጅቼያለው…ይሄው እርሶ እዚህ ግቡ….እትዬ ደግሞ ቀጥሎ ያለው …ወንድም አንተ ደግሞ የፊት ለፊተኛው ክፍል…..ድንገት ስለሆነብን ሁሉንም ነገር ማዘጋጀት አልቻልንም….የጎደለውን ንገሩኝና ከተማ ወጣ ብዬ ገዝቼ አሟላላሁ››
አቶ ሃይለመለኮት ወደሰለሞን እያመለከቱ‹‹ተፈሰ…ይሄውልህ እዚህ 15 ቀን ነው የምንቆየው….በዚህ 15 ቀናት ውስጥ የእኛም ሆነ የአንተ ሀለቃ እሱ ነው….ምንም ነገር ቢያዝህ እሱ ያለውን ነው የምታደርገው…እኛም እንደዛው››ሲሉ መመሪያ አስተላለፉ፡፡
ታፈሰ…የአቶ ኃይለልዕልን ንግግር ከበፊት ቆፍጣና ባህሪያቸው ጋር አልሄድ ስላለው ..ግራ በመጋባት አፍጥጦ ያያቸው ጀመር…እሱ እንደሚየውቀው እኚ ግዙፍ አዛውንት ለሰው ምንም ሊሰጡ ይችላሉ የአዛዥነት ቦታቸውን ግን ፈፅሞ ሸርፈው እንኳን ለሌላ ሰው ይሰጣሉ ብሎ ማመን ይከብደዋል፡፡
‹‹ታፈሰ ..ሰምተኸኛል…የሁሉ ነገር አዛዣችን እሱ ነው››ደገሙለት፡፡
‹‹አዎ ..ገባኝ ጌታዬ…እንዳሉት ይደረጋል››
‹‹አሁን ሁላችንም ወደክፍላችን እንግባና ትንሽ አረፍ እንበል ..አይደል?››ወ.ሮ ስንዱ የሰለሞንን አይኖች በልምምጥ እያዩ ጠየቁ፡፡
ቆይ አንዴ ክፍላችሁን ልይ ብሎ..ለአቶ ኃይለልኡል የተመደበውን ከፍቶ አየው፡፡ቀጥሎ የወ.ሮ ስዱን ከፈተና አየው፡፡‹‹ጥሩ በቃ ግቡና እረፉ››
ሁለቱም ገቡና የየራሳቸውን ክፍል ዘጉ
‹‹አንተም ወደክፍልህ ግባ ጌታዬ..እኔ ደግሞ እቃችሁን ከመኪና ላውርድ››
‹‹ቆይ አብሬህ ልምጣ››ብሎ ተከተለው፡፡የታፈሰ ባለቤት ለእንግዶቹ ምግብ እያበሰለች ስለነበር ታፈሰ እቃዎቹን ማለት ይዘው የመጡትን አስቤዛ እና ሻንጣዎች ሲያወርድና ወደቤት ሲያስገባ ሰሎሞን አገዘው፡፡እንደጨረሱ፡፡‹‹ተለቅ ያለ ክፍል የለም?››ሲል ጠየቀው፡፡

‹‹ምን አይነት ክፍል…ማለቴ ለምን የሚሆን?››
‹‹ለመኝታ ቤት የሚሆን ..ሁለት አልጋ የሚያዘረጋ››
‹‹ቆይ ..ኮሪደሩ መጨረሻ ላይ ያለው ክፍል ሰፋ ይላል››
‹‹ማየት እችላለሁ?››
‹‹አዎ ይቻላል….››ብሎ ይዞት ሄደና ከፈተለት…ሰለሞን ወደውስጥ ዘልቆ ሳይገባ በራፉ ላይ በመቆም አንገቱን ወደውስጥ አስግጎ ተመለከተው….አቦራ የጠጣና ለብዙ ጊዜ ጥቅም ላይ ያልዋለ ቢሆንም የሚፈልገው አይነት ክፍል ነው፡፡››
‹‹ታፈሰ ይሄንን ክፍል በአስቸኳይ ልታስፀዳልኝ ትችላለህ….?››
‹‹እችላለሁ..አፀዳዋለው››
‹‹አይ ብቻህን ይከብድሀል..ሰው ቅጠርና በፍጥነት ወለሉም ግድግዳውም ይፅዳ….ውስጥ ያሉት እቃዎችም ወደሌላ ክፍል ይዘዋወሩ››
‹‹እሺ››
ተሰናብቶት ንፁህ አየር ሊቀበልና እግረመመንገዱን አካባቢውን ለመቃኘት ወጥቶ ሄደ፡፡
///
በማግስቱ ጥዋት 3 ሰዓት ላይ ሁለቱንም የማይጣጣሙ ባለትዳሮችን አንድ ክፍል ጎን ለጎን እንዲቀመጡ አደረገና እሱ ከፊት ለፊታቸው ተቀመጠ..ጉሮሮውን አፀዳዳና የመግቢያ ንግግሩን ጀመረ
‹‹በሰዎች መካከል ለተለያየ አለማ ተብለው የሚደረጉ የእርስ በርስ ጉድኝቶችና ቁርኝቶች አሉ፡፡ከነዛ መካከል ግን በጣም ውስብስቡ የጠበቀውና የጠለቀው ግንኙነት በአንድ ወንድ እና ሴት መካከል የሚፈጠር የጋብቻ ጉድኝት ነው፡፡በጋብቻ ውስጥ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት ሁሉ ጊዜ ቀላል የተባለ መንገድ አይገኝም….አንዱ ጋብቻ ውስጥ የሚፈጠረው ችግር ከሌላው ጋብቻ ችግር በአይነትም በይዘትም ፍፁም የተለየ በመሆን ችግሩን ለማስተካከል የሚወሰደውም እርምጃ የዛኑ ያህል የተለያ ነው፡፡በዛ ላይ ሁሉም ችግሮች እዲፈቱ  በጥንዶቹ  መካከል  ስክነት፣  ትዕግስትን፣ጥረትን  እና   እራስ  መግዛትን

ይጠይቃል፡፡አሁን ልብ በሉ ፣ጥረታችን በመካለላችሁ ያላውን ግጭትና ጭቅጭቅ ሙሉ በሙሉ ማስወገድ አይደልም..አይ እንደዛማ አይሆንም እናንተ ሰው ናቸው፣ሁለት ሰዎች ደግሞ በአንድ ጣሪያ ስር አብረው እስከኖሩ ድረስ በሆነ ነገር መነጋገራቸውና በነገሩ ላይ የተለያየ ተቃራኒ ሃሳብ ማንፀባረቃቸው አይቀርም…ስለዚህ መነጋገርና መጨቃጨቃችሁ ኖርማል ነው…አሁን ምንድነው ምናደርገው በማንኛውም ጉዳይ ላይ አለመግባባት ተከስቶ ስትነጋገሩ በምን መልኩ ነው ኮምንኬት የምታደርጉት..?ነገሩን ማስረዳትና ማሳመን ላይ ነው ትኩረታችሁ ወይስ ያንን ምክንያት አድርጎ በስድብና በዘለፋ ማጥቃትና ልብ መስበር…አያችሁ ትልቁ ችግር መጋጨታችን ሳይሆን በያንዳንዱ ግጭታችን አንዳችን ለሌላቸውን የልብ ቁስለትና የነፍስ ህመም መስጠታችን ነው፡፡ማጥፋት ያለብን እርስ በርስ መወጋጋቱን ነው…አንዳችን ሌላችን ላይ በምንም አይነት ሰበብ የሚያቆስል ጦር አስበን አይደለም አምልጦን እንኳን መወርወር የለብንም፡፡
እርስ በርስ ከፍ ባለ ቃላት በተነጋገራችሁ ቁጥር ደግሞ እየተጣላችሁ መሆኑን አታስቡት..መጣላት ቃሉ እራሱ አሉታዊ ነው፡፡እየተጣላችሁ ሳይሆን በጋለ ስሜት እየተነጋገራችሁ ነው፡፡በቃ እንዲህ ነው ማሰብ ያለባችሁ፡፡እንደዛ ካሰባችሁ ቀጥታ ችግሩ በጋለ ስሜት መነጋገራች ብቻ ስለሆነ ስሜታችሁን በማረጋጋት ነገሩን ትፈታላችሁ፡፡እየተጣላን ነው ብላችሁ ካሰባችሁ ግን ገና ይቅርታ የሚጠይቅ ሰው ወይም ሽማግሌ ልትፈልጉ ነው፡፡ልብ በሉ ጮክ ብሎ መናጋገር ሁል ጊዜ መጣላት አይደለም ..አዎ አብዛኛውን ጊዜ በጋለ ስሜት መነጋገር ነው፡፡ሌላው በምንም አይነት ሁኔታ ንግግራችሁ ሰው ፊት አይሁን፡፡የምንወደው ሰው ላይ ያለንን ቅሬታ ብቻውን በሆነበት ጊዜ ነው መናገር ያለብን…እንደዛ ሲሆን ነው ውጤታማና ጥፈቱን ለማረም ፍቃደኛ የሚሆነው…ወቀሳው..ሰው ፊት ሲሆን ግን ሰውዬው የበለጠ በእኛ ቅሬታ እንዲያድርበት መንገድ ያመቻቻል፡፡
‹‹እንግዲ ሁላተችሁም እንደምታውቁት አሁን ለእኛ እዚህ መገኘት ዋናዋ ምክንያት በፀሎት ነች፡፡እኔ በስራ በተለይ ከሀገር ውጭ በነበርኩበት ጊዜ በጣም ብዙ ባለትዳሮችን አማክሬያለሁ ትዳራችውም መካከል ያለውን ችግር በመተጋገዝ ለመፍታት ችያለሁ....በብዙዎችም ረክቼለው..ከብዙ ቤተሰቦች ጋርም እቤተሰብ ለመሆን ችያለው….ግን እመኑኝ እንዲህ እንደእናነተ የተለየ ጉዳይ ገጥሞኝ አያውቅም››
‹‹የተለየ ስትል?››
👍9215👎1
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች


#ክፍል_አስራ_ሰባት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
================

ሰሎሜና ሂሩት እንደተባባሉት ዝግጅታቸውን ጨርሰዋል፡፡ .. ሂሩት በሰበቡ እነሱ ቤት እንደምታድር ለአላዛር ነግራው በሰዓቱ እንድትገኝ አደረገች፡፡እራት በልተው መጠጥ እየቀማመሱ ካመሹ በኃላ አምስት ሰዓት አካባቢ ከእናትዬው እንደተደወለላትና እንዳመማቸው በመናገር ብቻቸውን ትታቸው ሄደች፡፡ አላዛር ልከተልሽ ቢላትም እምቢ አለችው፡፡ቀጥታ እናቷ ቤት ሳይሆን ቀን ወደዘጋጀችው ከሰፈራቸው ብዙም የማይርቅ ሆቴል ነበር የሄደችው፡፡ቀጥታ የተከራየችው ቤርጎ ገብታ  ምን ይፈጠር ይሆን እያለች ስትጨነቅና ስትገላበጥ አደረች፡፡እንቅልፍ በአይኗ ሳይዞር ነበር ንጊቱን የሚያበስሩ የወፎችን ዝማሬ የሰማችው…ሂሩትም   ገና ሰማይና ምድሩ በቅጡ ሳይላቀቅ ከለሊቱ 12 ሰዓት አካበቢ ነበር የደወለችላት፡፡ወዲያው ክፍሏን ለቃ ወጣችና የሆቴሉ ፓርኪንግ ጋር ያቆመቻትን መኪና ውስጥ ገብታ ወደነገረቻት ቦታ ተፈተለከች፡፡በወቅቱ የተከፈተ ካፍቴሪያ ወይም ሆቴል ማግኘት ስላልቻሉ ሰሎሜ መኪና ውስጥ ቁጭ ብለው ነበር ያወሩት፡፡

ሶሎሜ ስታገኛት ፈክታና ተፍለቅልቃ አገኛታለሁ ብላ ነበር ያሰበችው..ግን አኩርፋና ለምቦጯን ጥላ ነው ያገኘቻት፡፡ይሄ ደግሞ ይበልጥ አስደነገጣት፡፡‹‹የሆነ ነገር ባይፈጠርማ እንደዚህ አትነፋፋም ነበር፡፡በቃ ተሳክቶላት አሳስተዋለች..በቃ ችግሩ ከእኔ ነው››ብላ ደመደመች፡፡ድምጽ አውጥታ ብትጮህ ወይም እንባዋን ዘርግፋ ብታለቅስ ደስ ይላት ነበር፡፡ግን እንደዛ በማድረግ ሂሩት ፊት ደካማ ሆና መታየት አልፈለገችም፡፡

ከአሁን አሁን አንደበቷን አላቃ የሆነ ነገር ትለኛለች ብላ ብትጠብቅ ዝም ብላ እንዳቀረቀረች የቀኝና የግራ እጇን መዳፎች አንድ ላይ አቆላልፋ እያፍተለተለች ነው፡፡እሷን እንድትናገር መጠበቁ አሰልቺ ሆኖ ስለታያት‹‹እሺ እንዴት ሆነ?››በማለት ቃል አወጣችና ጠየቀቻት፡፡

‹‹በፊትም ተይ ይቅርብኝ ያልኩሽ ይሄን ፈርቼ ነበር…››እንባዋን ዘረገፈችው፡፡

‹‹አይዞሽ ..ምንም የሚያስለቅስ ነገር እኮ የለም..ምንም ነገር ሊፀፅትሽ አይገባም…እኔ እራሴ ፈቅጄና ገፋፍቼ እኮ ነው እንድታደርጊ ያደረኩሽ…አሁን ሁሉ ነገር ግልፅ ሆኖልኛል…… ስለሁሉም ነገር አመሰግናለሁ›› አለቻት፡፡

ከአንደበቷ እየተወረወረ የሚወጣው ቃል ለራሷ እራሱ ሻካራነቱ እየተሰማት ነበር..እስከዛሬ ለሌላ ሰው ከተናገረቻቸው ንግግሮች እጅግ  መራሩ ንግግር ነው፡፡እንደውም ንግግር እንዲህ ሊመር እንደሚችል ሲሰማት የመጀመሪያ ቀን የህይወት ልምዷ ነበር፡፡

ሂሩት የሆነ ነገር ትላለች ብላ ስትጠብቅ እሷ ግን እጇን ወደኪሷ ከተተችና ሞባይሏን በማውጣት ከፈተችና  ሰጠቻት፡፡

‹‹ምንድነው?››

‹‹እይው በቃል ከምነግርሽ   በምስል ይሻላል ብዬ አንቺ ከወጣሽ በኃላ ያለውን ትእይንት ሁሉ እሱ ሳያውቅ ቀርጬዋለሁ››

‹‹ምን ሊያደርግልኝ ነው የማየው?‹‹ገና ስታስበው ዘገነናት…የገዛ ባሏ… ቀለበት እጣቷ ላይ አጥልቆ ያጫት፤ ቬሎ ሰውነቷ ላይ አልብሶ ያገባትና አንድ ቀን ጭኗን ፈልቅቆ ማያውቀው ሰው አሁን ፊት ለፊቷ የተቀመጠችውን የገዛ ጓደኛዋን እርቃን ሰውነቷን አቅፎ ፤ቅስር ጡቶቻን እየጠባ…መቀመጫዋን እየጨመቀ…ሲያስጮኸት…እላዮ ላይ ወጥቶ ..ሁለቱም በስሜት እሳት ግለው ነበልባሉ በዙሪያቸው ሲንበለበል በምናቧ ሳላችና ዝግንን አላት..እንደምንም የሰጠቻትን ሞባይል አስጠግታ የተቀረፀውን ማየት ጀመረች፡፡ከጠበቀችው ፈፅሞ ተቃራኒ የሆነ ነገር ነው እያየች ያለችው፡፡
ሂሩት እየደነሳች ተራ በታራ ልብሷን ስታወልቅ…አላዛር ፊቱን ስልኩ ላይ አቀርቅሮ እሷን ላለማየት ሲጠነቀቅና ሲሸማቀቅ…እርቃኗን ሔዳ ስልኩን ከእጁ ነጥቃ ወደሶፋው ወርውራ እላዩ ላይ ለመቀመጥ ስትሞክር፤ከላዩ ላይ ወርውሮ ወለል ላይ ጥሏት እየተንዘረዘረ ሲናገር‹‹አንቺ ምን አይነት ክፉ ሴት ነሽ..ጓደኛሽ አንቺን አምና እኮ ነው ባሏን ጥላልሽ የሄደችው…እኔ እንኳን ልሳሳት ፈቅጄ ባስቸግርሽ አንቺ ትሞክሪዋለሽ ብዬ አስቤ አላውቅም..ደግሞ ከነዛ ሀሉ ጓደኞቾ አንቺን መርጣ ሚዜ ማድረጓ..?አዝናለሁ..እኔ ሰሎሜን በጣም ነው የማፈቅራት ስልሽ እንዲሁ ተራ ፍቅር መስሎ እንዳይሰማሽ….ነፍስ ካወቅኩበት ቀን ጀምሮ ከእናቴ ቀጥሎ ስወድና ሳፈቅራት.. በየሄደችበት እየሄድኩ ሳጅባት… ስታለቅስ አልቅሼ ስትስቅ ስስቅ እድሜዬን የፈጀሁባት ..የማንነቴ ክፋይ ነች፡፡እሷን ከዳሁ ማለት እራሴን ከዳሁ ማለት ነው፡ያ ከሚሆን ደግሞ ህይወቴን ዛሬውኑ ባጣ ይሻለኛል….በይ ልብስሽን ልበሺና እንግዳ ቤት ገብተሸ ተኚ….ይሄንን ቅሌትሽን እንዳልተፈጠረ እንርሳው…ምክንያቱም የማፈቅራት ሚስቴ በጓደኛዋ መከዳቷን አውቃ እንድታዝና አልፈልግም…››ብሎ ጥሏት አንደኛ ወለል ላይ ወደሚገኘው መኝታ ቤታቸው በመንደርደር ሲወጣ ያሳይና ቪዴዬ ይቋረጣል፡፡

‹‹ታድዬ.!!.ይወደኛል ማለት ነው..?አሁንም ከእኔ ፍቅር እደያዘው ነው››…ተንደርድራ ጉንጯ ላይ ተጣበቀችባትና፡፡ አገላብጣ ሳመቻት‹‹ሂሩትዬ አመሰግናለው….ጋንግሪን ሆኖ ሲበላኝ ከከረመ ጨለማ ጥርጣሬ ነው የገላገልሺኝ››

‹‹ችግር የለውም ..በቃ አሁን ልሂድ››

‹‹እንዴ የት ነው የምትሄጂው.?.የምትሄጂበት ላድርስሽ››

‹‹አይ የመጣሁበት ታክሲ እኮ እየጠበቀኝ ነው››መኪናውን በራፍ ከፍታ ወጣች….፡፡

‹‹ወይኔ በጌታ ቁርስ እንኳን አብረን ሳንበላ?››

‹‹አይ ቤት ሄጄ ልብስ ቀያይሬ ወደስራ መሄድ አለብኝ….ሌላ ጊዜ››
ሰሎሜ ከዚህ በላይ ልትጫናት አልፈለገችም‹‹በቃ ሰሞኑን ደውልልሽና እናወራለን አመሰግናለሁ፡››

ሄሩት ሄደችና ከኋላ ቆማ የነበረችው ታክሲ ውስጥ ገባች፡፡
///
የሰው ልጅ ለህይወት ሚያስፈልጉትን ነገሮች በራሱ ለማድረግ በተደጋጋሚ ልምምድ ይማራል…ለምሳሌ ምግብ እንዴት መመገብ እንዳለበት በወላጆቹ ሶስት አራት አመት እያጎረሱት ያለማመዱታል…ከዛ እንዴት ተጠቅልሎ እና ተዝቆ መብላት እንዳለበት መሞከርና ይጀምራል… ከዛ ይችላል…ግራ ቀኙን ለይቶ በትክክለኛው ጫማ ማድረግም እንደዛለው ሁለት ሶስት አመት ይወስድበታል….
የሰው ልጅ ምንም ሳይማር ቀጥታ ወደማድረግ እንዲሸጋገር የሚጠበቅበት ብቸኛው ለህይወት ወሳኝ የሆነው ነገር ወሲብ ነው፡፡ወሲብ ምን እንደሆነ…?እንዴት መነቃቃት..?እንዴትስ ማነቃቃት እንደሚቻል…?እንዴት መሳም እንዴት መዳበስ እንደሚገባው..?በየት በኩል እንዴት አድርጎ እንደሚያደርግ ማንም የሚያስተምረው የለም፡፡በትምህርት ቤት እንኳን ሚሰጡ ትምህርቶች ወሲብን እንደመራቢያ እና መባዣ መንገድ ብቻ በማየት እና እሱ ላይ ብቻ በማተኮር የሚሰጥ ነው፡፡ለመዋለድ ደግሞ ምንም አይነት የወሲብ ጥበብ አይጠይቅም.. ወጣ ገባ ብቻ በማድረግ ትንሽ ገባ ብሎ ዘር መድፋት ብቻ በቂ ነው፡፡ያ ግን የወሲብ አንዱ ግንጥል ጥቅም ነው፡፡ደግሞ ያ አይደለም የሚገርመው…ያለምንም ልምድ ባገኛቸው ቅንጭብጫቢ ሹክሹክታ መሰል መረጃዋች ብቻ ለመጀመሪያ ጊዜ ወሲብ ሲፈፅም ‹‹አይ የመጀመሪያው ስለሆነ ነው  ብሎ ለብቃቱ ይቅርታ የሚያደርግለት የለም…በተለይ ወንዱ የዚህ ጉዳይ ተጠቂ ነው፡፡ከመጀመሪያዋ ቅፅበት ጀምሮ ፍፅምነት ይጠበቅበታል ካልተሳካለት እንዲሸማቀቅ ይደረጋል፤ከዛ ህመሙ እየባሰበት ይሄዳል፡፡
👍525👏3
#አላገባህም


#ክፍል_አስራ_ሰባት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///
ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ውስጥ ነው፤ የሆነ የሚንጠጣረር ነገር እያደነቆረው ነው፡፡በመከራ ነው ከእንቅልፉ የነቃው…የበራፉ መጥሪያ ድምፅ መሆኑ አወቀ..ስልኩን ከኮመዲኖ ላይ አነሳና ሰዓቱን ተመለከተ፡፡ለአንድ ሰዓት ሩብ ጉዳይ ይላል፡፡ያልተለመደ ነገር ነው፡፡በዚህ ሰዓት ማን ነው በራፍን መጥሪያ የሚያንጣርረው?፡፡የፅዳት ሰራተኛዋ እንደማትሆን እርግጠኛ ነው፡፡እሷ አንደኛ በዚህ ሰዓት አትመጣም…ብትመጣም የራሷ የሆነ ቁልፍ ስላላት እሱን የምትቀሰቅስበት ምንም  አይነት ምክንያት የላትም….መኝታውን ለቆ ተነሳና ጋዎኑን ደርቦ መኝታ ቤቱን ለቆ ወጣ፡፡፡ሳሎን ደርሶ በራፉን ሲከፍት..እየተመለከተ ያለው  ፈፅሞ በአእምሮው ያልጠበቀውን ነው፡፡ፊቱን በጥፊ ደረቱን በጡጫ እየቀጠቀጠች ገፍትራ ወደውስጥ አስገብታ ትቦጫጭረው ጀመር….‹‹ምን አድርጌሀለው..?እንዴት በልጄ ስሜት እንደዛ ትጫወታለህ..?ምን አይነት አረመኔ ሰው ብትሆን ነው?፡፡››
እንደዚህ አውሬ የሆነች ሴት በእድሜ ዘመኑ አጋጥሞት  አያውቅም፡፡ፊቱን ከብጭሪያ ለመከላከል ሁለቱን  እጆቹን በፊቱ ዙሪያ አድርጎ ለመከላከል ሞከረ፡፡
‹‹አረ ፀዲ ተረጋጊ….››
‹‹አልረጋጋም..እንዲህ አሳብደሀኝ እንዴት ነው የምረጋጋው…..?ልጄን እንዴት እንዳሳደኩዋት ታውቃለህ…?››መደባደቧን እና ጮኸቷን አላቆረጠችም….እንባዋ ከቁጥጥሯ ውጭ ሆኖ እየረገፈ ነው፡፡ትናንት የሆነውን ከሰማችበት ደቂቃ ጀመሮ ማልቀሷን አላቆረጠችም… ለሊቱን እንቅልፍ ባይኗ ሳይዞር ስትቃጠልና ስትነፈርቅ ስላደረች የእናቱን ሞት አዲስ እንደተረዳ ሀዘንተኛ አይኖቾ ከማበጣቸውም በላይ ክፍኛ ደፍርሰዋል፡፡
ዘሚካኤል መከላከሉ ብቻ እንደማያዋጣ ገባው፡፡እንደምንም አለና ሁለት እጆቾን ያዘና ስቦ ከሰውነቱ ጋር አጣበቃት፡፡
‹‹ልቀቀኝ..ከዚህ ቀፋፊ ሰውነትህ ጋር መነካካት …..››አላስጨረሳትም የተከፈተ አፏን በአፉ ከደነው….በተቻላት መጠን ተወራጨች…ከእሱ ፈርጣማና የዳበረ ጡንቻ ማምለጥ አልቻችም…ከንፈሩን ነከሰችው….ለቀቃትና..ተስፈንጥራ ወደኃላ ልታመልጥ ስትል መልሶ በመያዝ ሙሉ በሙሉ ከስር ገብቷ ተሸከማት……እንደእፃን ልጅ በእግሯም በእጇም ተወራጨች… ወደሶፋው ይዟት ሄደ…ሶፋው ላይ ሊወረውረኝ ነው ብላ ስትጠብቅ እሷን አጥብቆ እንደያዘ እግሩን ዘረጋና ከሳፋው ላይ አንዱን ትራስ ወደወለሉ አወረደ….በፍጥነት ገለበጣትና እንደህፃን አቅፎ ወደታች በጉልበቱ ተንበረከከ እና ወለሉ ላይ አስተኛት…ሾልካ ከስሩ ለማምለጥ ታገለች… በጥንካሬ ጨምቆ ከወለሉ ላይ አጣበቃትና ጭንቅላቱን ቀና አድርጎ ትራሱ ላይ አስደገፋት …እንዳይጨፈልቃት በመጠንቀቅ እላዩዋ ላይ  ተቀመጠ…የለበሰውን ጋወን አውልቆ ወረወረው….
‹‹ምን ልታደርግ ነው?››አይኗቾ በድንጋጤ ፈጠጡ፡፡
ወደታች ጎንበስ አለና የለበሰችውን ቲሸርት ከግራና ከቀኝ ይዞ ወደታች ተረተረው….የመጨረሻውን ንዴት በመናደዷ ምክንያት ደምስሯ ተግተረተረ‹‹ምን እያደረክ ነው? ልትደፍረኝ ነው እንዴ..?እከስሀለው…ስምህን ነው ያማጠፋው….››የቀራት ብቸኛ መከላከያ ምላሷ ብቻ ነበር….ልታስፈራራው ሞከረች ፡፡ተንጠራራና ሌላ ትራስ አምጥቶ ከጎኗ በማድረግ ከላዬ ላይ ወርዶ ከጓና ተኝቶ ወደራሱ ገለበጣትና አቀፋት፡፡
ከታች እሱ በቁምጣ ሲሆን እሷ ደግሞ ልክ እንደወትሮዋ ጅንስ ሱሪ እንደለበሰች ነው፡፡
‹‹በፈጠሪ ስትበሳጪ እንዴት ነው የምታምሪው?፡፡››
‹‹እያሾፍክብኝ ነው?››
‹‹በፍፅም ..አይገባሽም እንዴ ..?ካንቺ ፍቅር ይዞኛል…ላገባሽ እፈልጋለው››
ምትሰማውን ቃል ማመን አቃታት‹‹ይሄ ደግሞ ሌላ ቀልድ መሆኑ ነው?ሕይወት እንደምትተውነው ተውኔት መሰለህ?››
‹‹እሱ እንዳያያዝሽ ነው …እኔ ግን የተናገርኩት ከልቤ ነው…ከፈለግሽ ዛሬውኑ ሄደን መጋባት እንችላለን…እንደማገባሽ እግጠኛ ስለሆንኩ ነው ምስርን ልጄ ነች ያልኩት፡፡››
‹‹እንዴት እሺ ትለኛልች ብለህ አሳብክ?››
‹‹እንደምትወጂኝ አይኖችሽ ውስጥ ስላነበብኩ››
የተፋቀረ ሁሉ ይጋባል ያለህ ማን ነው….ደግሞ እወቅ እኔ ፍቅር አልፈልግም…አሁን ልቀቀኝ ..ከአንተ እስከወዲያኛው መሸሽና መራቅ ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹አይ ከአኔ ሸሽተሸ ማምለጥ  አትችይም፡፡››
‹‹ልቀቀኝ አልኩ..›› ለመመናጨቅ ሞከረች አጥብቆ ያዛትና ከንፈሯ ላይ በድጋሚ ተጣበቀ… ሳላሳ ሰከንድ ያህል ብቻ ነው መታገል የቻለችው..ከዛ ቀስ በቀስ እየለዘበች…  የእጆቾ ጡንቻዎች እየለሰለሱ ..ከንፈሯቾ ለከንፈሮቹ መልስ እየሰጡ መጡ…እሱን ሲቧጭሩ እና ሲደበድብት የነበሩት ጣቶቹ ጀርባውናና መላ ሰውነቱን ማሻሸት ጀመሩ…ከዛ እሱ ቁምጣውን ሲያወልቅ እሷም በገዛ እጇቾ ጅንስ ሱሪዋን እያወለቀች ነበር….እዛ ግዙፍ የሳሎን ወለል ላይ 30 ለሚሆኑ ደቂቃዎች በፍቅር እየተንከባለሉ እና ከኮርነር  ኮርነር እየተሸከረከሩ በጣር የታጅበው ወሲብ ሲሰሩ በራፉ ክፍት መሆኑን እንኳን አላስተዋሉም ነበር፡፡
ከወሲብ በኃላ አርቃኗን ሆና ‹‹አንተ ምን አይነት አዚም ነው ያለህ ግን?››ስትል ባለማመን ጠየቀችው፡፡
‹‹ያው የፍቅር አዚም ነዋ››
‹‹አይ አይመስለኝም…..የሆነ  የሚያደነዝዝ አይነት መስተፋቅርማ አለህ…አሁን ሻወር ቤቱን አሳየኝ..››አለችው፡፡
ከተዘረረበት ወለል እየተነሳ ወደእሷ ሄዶ ከስር ተሸክሞ ወደምኝታ ክፍሉ ተሸክሟት ገባ….‹‹ያው ግቢና ታጠቢ››
‹‹እሺ…ቲሸርቴን ቀዳደሀዋል….አሁን ምን ልለብስ ነው?››እያለች ገባች፡፡
‹‹አታስቢ አዘጋጅልሻለው….ግን አብሬሽ ሻወር መውሰድ እፈልጋለው፡፡››
‹‹ስርአት ይዘህ የምትታጠብ ከሆነ ትችላለህ›› አለችው፡፡በደስታ እርቃኑን ገባና ተቀላቀላት…መታጠብ ጀመሩ፡፡ ቃል እንደገባው ግን ስርዓት ይዞ አልታጠበም..እሷም በቃላት አውጥታ አትናገር እንጂ ስርዓት የለሽ መሆኑን ፈልጋው ነበር..ከዛ ሻወር ቤት ለመውጣት አንድ ሰዓት በላይ ነበር የወሰደባቸው፡፡ ከዛ ተያይዘው ሲወጡ ሁለቱም ሰውነታቸውን ማዘዝ እስኪያቅታቸው ዝለው ነበር.. ርቃናቸውን ተያይዘው አልጋ ውስጥ ነው የገቡት…ሁለት ሰው መሆናቸውን መለየት እስኪከብድ ድረስ ሙሉ በሙሉ ተቃቅፈው ለሞት የተቃረበ እንቅልፍ ውስጥ ገቡ፡፡
///
ተመሳሳይ የበራፍ ተደጋግሞ መንጫረር ነበር ከእንቅልፉ ያባነነው..‹‹ዛሬ ደግሞ ምን ጉድ ነው ?››በማለት እየተነጫነጨ…እንደምንም ነቅቶ ስልኩን ሲመለከት..ከ30 በላይ ሚስኮል ነበረው…ሰዓቱን ሲመለከት 7ሰዓት ተኩል ሆኗል…ማመን አልቻለም፡፡ይሄ ሁሉ ሚስኮል ከማን ነው ብሎ ሲያየው አብዛኛው ከአዲስአለም ነው…ስለፀደይ ተጨንቃ እንደሆነ ገመተ ..አልጋውን ለቆ ሲወርድ ፀደይ እራሷን አታውቅም፡፡
ጋወኑን ቅድም ሳሎን ወለል ላይ ትቶት ስለነበረ….ቁምጣ እና ቲሸርት ለበሰና በድኑን እየጎተተ ወደ ሳሎን ሄዶ በራፉን ሲከፍት ክፍኛ የደነገጠችውና አይኗ  የፈጠጠው አዲስአለም በራፉ ላይ ተገትራለች
‹‹እዚህ አልመጣችም…?ወይኔ ጓደኛዬ….›
‹‹አረ ተረጋጊ..ግቢ ››
ወደውስጥ አስገባትና በራፉን መልሶ ዘግቶ ተመለሰ‹‹እሺ የት ሄደች ይባላል ?አንተ ደግሞ ለምንድነው ስልክህን የማታነሳው?››
‹‹አሁን ተረጋጊና ከተቻለሽ ቆንጆ ምሳ ስሪልን››
‹‹ምን እያወራህ ነው?ፀደይ ጠፍታለች እኮ ነው የምልህ››
👍6018
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ


#ክፍል_አስራ_ሰባት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

//////

ራሄል ፀጋን ስታበረታታ‹‹ነይ የኔ ማር ..አንድ ነገር መጠጣት አለብሽ››አለች ። እሷ ግን ከራሔል ደረት ጋር እንደተለጠፈች  ጭንቅላቷን ወደ ጎን አዞረች። ራሄል ትንሿን ህፃን በምቾት መያዝ አልቻለችም ሰውነቷ በጣም ሞቃት እና የሚፋጅ ነበረ….ራሄል ዔሊያስ ባሳየት ዘዴ በመጠቀም የሙቀት መጠኑን ለመቀነስ ሞክራ ነበር፣ነገር ግን ለልጁቷ ጊዜያዊ እፎይታ ቢያስገኝላትም፣ የሙቀት መጠኑ ብዙም ሳይቆይ ከደቂቃዎች በኃላ እንደገና  ይጨምሯል። ራሄል ደፍራ ለዔሊያስ  ደውላ ሁኔታውን ልትነግረው አሰበችና  ስልኩን ተመለከተች። ወዲያው ግን ትላንት ቤቱ በሄደች ጊዜ እንዴት እንዳስተናገዳትና ከህይወቱ ጭምር አሽቀንጥሮ እንዳስወገዳት  ትዝ ሲላት እጇን ሰበሰበች፡፡ እንደገና መዋረድ ስላልፈለገች ከዔሊያስ ለመራቅ ወሰነች ። ከዛ ምንም ምርጫ ስለሌላት.. የሚሆነውን መጠበቅ ጀመረች፡፡

ከአንድ ሰዓት በኃላ  ፀጋ ለውጥ እያሳየች መጣች…ከዛም በላይ እራሷን ችላ መቀመጥና በአሻንጉሊቶች መጫወት ጀመረች…ራሄል በጣም ደስ አላት..ከእሷ እቅፍ ላይ ወረደቻና ግዙፉ ሶፋ ላይ ሆና መጫወት ጀመረች…ራሄልም በተወሰነ መንገድ ስለተረጋጋችላት ተደስታ እዛው አጠገቧ ቁጭ ብላ  አንዳንድ ሰነዶችን ማየት ጀመረች…ግን ብዙም ሳይቆይ አስጠሊታ ነገር ተከሰተ ፡፡ፀጋ ከተቀመጠችበት ተነስታ ከእሷ የሸሸውን አሻንጉሊት ለመያዝ እግሯን ስታነሳ የሶፋው ቆዳ አዳለጣትና ወደኃላዋ ወደቀች…ወደኃላዋ ስትወድቅ የሶፋው እጄታ ጭንቅላቷን መታት…ለሌላ ልጅ ቢሆን ምንም አይነት ጉዳት የሚያስከትል አይነት አልነበረም…ፀጋ ግን ልትቋቋመው አልቻለችም፡፡

ራሄል እዛው አጠገቧ ስለነበረች በእጇ የያዘችውን ወረቀት በትና ተንደርድራ ሄዳ አነሳቻት…ክንዷ ላይ ዝልፍልፍ ብላ ዝርግትግት አለች..አይነቾ ግልብጥብጥ አሉ….ራሄል እሪታዋን ስታቀልጠው..ከኪችን አለምና ረዳቷ ከውጭ አትክልተኛውና ዘበኛው እያለከለኩ መጥተው ከበቧት..አለም ፀጋን ከራሄል እጅ ላይ ተቀበለች…‹‹ቶሎ በሉ አምፑላንስ ደውሉ..አንፑላንስ ደውሉ….››ተንጫጩ..ራሄል ራሷን መቆጣጠር አቃታት…ልቧ መጥታ ጉሮሮዋ ላይ እንደተወተፈች እርግጠኛ ነች…መተንፈስ ሁሉ አቃታት..በእንብርክክ ሳሎኑና ታስሰው ጀመር ..…ከ30 ደቂቃ በኃላ አምፑላንሷ ቀፋፊ የሆነ ሳይረኗን እያስጮሐች ደረሰች…ባለሞያዎቹ ከአለም እጅ ጸጋን ተቀብለው በጥንቃቄ ወደውስጥ አስገብተው አልጋው ላይ አስተኞት..ከዛ ወዲያው የመተንፈሻ መሳሪያዎቹን ይሰካኩላት ጀመር… ራሄል በደመነፍስ ተከትላ ገባች…የአምፑላንሱ በራፍ ተዘጋና ተንቀሰቀቀሱ ፡፡

ሆስፒታል ከደረሰችና ፀጋን ለሀኪሞቹ ካስረከበች ከአንድ ሰዓት በኃላ ግን ነገሮች በብዙ እጥፍ እየተባባሱ እንደመጡ መታዘብ ቻለች፡፡ወደ ውስጥ ገብታ ከሚስኪን እህቷ ጎን መሆን ፈለገች…እግሯን ስታንቀሳቅስ ግን  ‹‹እመቤት ፣ ወደእዛ  መሄድ አትችይም።››ስትን  ነርሷ አገደቻት  ፡፡

መሄድ አለባት፣ ከፀጋ ጋር መሆን ነበረባት።ነርሷ ‹‹ሀኪሞቹ  ሰራቸውን መስራት አለባቸው ልጅሽ  በጥሩ ሁኔታ ላይ ነች››አለቻት፡፡

ልጅሽ የሚለው ቃል አእምሮዋን በጦር ወጋት‹‹..አዎ የአደራ ልጄ ነች››ስትል አሰበች….‹‹ግን አንድ እናት ከማህፀኗ የወጣ ልጅ ሊሞትባት ሲያጣጥር ስታይ ምን አይነት ስሜት ይሰማት ይሆን …?እንዴትስ መቋቋም ትችላለች?››እራሷን ጠየቀች…መልሱን ማሰብ እንኳን ዘገነናት፡፡  ቃላቱ በራሔል አእምሮ ውስጥ ከላይ እንደተወረወሩ  ጠጠሮች ወደቁ።ነርሷ ያለችው ገብቷታል.. ግን አልተዋጠላትም።

‹‹ለምን ዶክተሩ ራሱ መጥቶ ምን እየተፈጠረ እንዳለ አያሳውቀኝም ?።››

ነርሷን ስታያት ወጣት እና ከእሷ በላይ አጭር ነች፣ ነገር ግን ክንዷን የጨበጠው  እጇ በሚገርም ሁኔታ ጠንካራ ነው።ራሄል ፀጋን ወደ ወሰዱበት ቦታ በጨረፍታ ተመለከተች፣ በተጨናነቀው ክፍል ዞር ብላ ስትመለከት በድንገት የጠፋች አይነት ስሜት ተሰማት። እንዴት እዚህ ደረጃ  እንደደረሰች አታውቅም። የሚወዛወዘውን አምቡላንስ በድንጋጤ አስታወሰች፣ ሁለቱ ሰዎች በፀጋ ላይ ሲያንዣብቡ፣ ወደ ኋላ እና ወደ ፊት መመሪያ ሲሰጡ ድምፃቸው ጥርት ብሎ ይሰማት ነበር።  መመሪያው በግልፅ ምትረዳቸው አልነበሩም ፡፡ከቤት ተነስተው ሆስፒታል እስኪደርሱ ነገሮች ነፍስ ግቢ ነፍስ ውጪ አይነት ነበር…

ነርሷ በእርጋታ እየመራች ወደአንድ ክፍል ይዛት ገባችና ወንበር ስባ  አስቀመጠቻት ..እሷ ከኮምፒዩተር ባሻገር ባለው ሌላ ወንበር ላይ ተቀመጠች፡፡ ከዛ ራሄል በጥያቄዎች ዝርዝር ታጣድፋት ጀመር ። አለርጂዎች የለባትም?ምን ምን  መድሃኒቶች ነው የምትወስደው?. የሚከታተላት  ዶክተር ማን ነው?።እነዚህንና መሰል ጥያቄዎችን ጠየቀቻት፡፡ቢያንስ ለነርሷ አስፈላጊውን መረጃዎች መስጠት ፀጋን በተወሰነ መጠንም ቢሆን መርዳት እንደሆነ በማሰብ በተቻላት መጠን በትኩረትና በትዕግስት መለሰችላት፡፡ በመጨረሻ ተጠናቀቀ ።

ራሄል ከነርሷ የቀረበላትን ውሃ  አልተቀበለችም። ‹‹እህቴን መቼ ማየት  እችላለሁ?›› ስትል ጠየቀች።

ነርሷ ተነሳች እና በፍጥነት ወደ ክፍሉ ሄደች፣ ራሄል በቁጣ እና በንዴት ተከተለቻት ። ብዛት ያላቸው   የማታውቋቸው ዶክተሮች  ፀጋ ህክምና ላይ እየሰሩ ነበር፣ ቢሆንም የገዛ እህቷን ፣የአደራ ልጇን  እንዳታይ ተከልክላለች..ያ ደግሞ በጣም ያበሳጫል።ዓይኖቿን በመጠባበቂያ ክፍል ውስጥ ካሉት ሌሎች ሰዎች ራቅ አድርጋለች። አእምሮዋም ስቃያቸውንና ጭንቀታቸውን ሊቀበል አልቻለም።በመጨረሻ ነርሷ ተመለሰች።

‹‹አሁን የተረጋጋች ነች። ወደ ህፃናት ህክምና አይሲዩ አስተላልፈዋታል።››ራሄል ደረቷ ላይ ቀዝቃዛ ክብደት  ያለው ብረት የተቀመጠባት መስሎ ተሰማት ።

‹‹ተረጋጊ ያልሽኝ መስሎኝ ነበር?።››ስትል ነርሷ ላይ አፈጠጠችባት።

‹‹ትክክል ነሽ  ተረጋጊ ብዬሻለው…ግን ጥብቅ ክትትል ሊደረግላት ይገባል።›› ነርሷ ጥንቃቄ የታከለበት ፈገግታ ፈገግ አለችላትና ። ‹‹ለአሁን… ደህና ነች ።››የሚል ንግግር አከለችበት፡፡

‹‹ለአሁኑ?››

‹‹ከፈለግሽ ወደ እሷ ልወስድሽ እችላለሁ።››

‹‹በጣም እፈልጋለው።››ራሄል ነርሷን ተከትላ ተራመደች።ሰውነቷ ኤሌክትሪክ እንደጨበጠ ሰው እየተንዘረዘረ ነው፡፡ ሰዎች ወደ ሞሉበት ኤሊቬተር ውስጥ ገቡ፣ እና ራሄል እጆቿን ተመለከተች…በቀደም በወላጆቾ ቤት ለተዘጋጀው ዝግጅት ብላ  የተቀባችው የጥፍር ቀለም ተፋፍቆ ነበር።…አለባበሷን ስታይ የበለጠ ገረማት…ለቀናት ከላዮ ላይ ያልወለቀ  የቆሸሸ እና የተጨማደደ ቲሸርት የሆነ እንዴት እንደለበሰችው እንኳን ማታውቀው አመድማ የነተበ ጅንስ ለብሳለች።በህይወቷ እንደዚህ እራሷን ጥላ እና ሙሉ በሙሉ ዘንግታ እንዳማታውቅ እርግጠኛ ነች፡፡ከመቼ ወዲህ ነው ይህቺን ልጅ እደዚህ የወደደቻት….?

ሊፍቱ ቆመና ፣ በሮቹ ተንሸራተው ተከፍቱ.. ራሄል ነርሷን ተከትላ   ወደ አንድ ክፍል ገባች
… ወደ ማጠቢያ ገንዳ ተወሰደች እና እጇን እንድትታጠብ ታዘዘች። እጆቿን በማድረቅ ነርሷ አገዘቻት ‹‹ጋውን እና ጭንብል  ማድረግ አለብሽ››አለችና አቀበለቻት ።ከዛ ነርሷ በተቆጣጣሪዎች የተከበበ አራት ትናንሽ አልጋዎችን ወደያዘ ክፍት ክፍል መርታ ወሰደቻት።
60
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_አስራ_ሰባት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

////
ነጋ አልነጋ ብላ ጥዋት ወደቢሮዋ ከመግባቷ በፊት ቀጥታ ወደኩማንደሩ ቢሮ ነው የሄደችው፡፡እንዳጋጣሚ እሱም በማለዳ እንደገባ ነገሯት፡፡ቀጥታ ወደቢሮ መራመድ ጀመረች፡፡
ኩማንደር ወደቢሮ በጥዋት ቢገባም ከጥቂት ሰኮንዶች በላይ በአንድ ሀሳቡ ላይ ትኩረት አድርጎ ማሰብ አልቻለም። የአለም ምስል በምናቡ ብልጭ ድርግም እያለ እየረበሸው ነው፡፡ወንበሩን ትቶ ወደ መስኮቱ ሄደ። መጋረጃውን ገልጦ ወደ ውጭ መመልከት ጀመረ፣የጥዋቷ ፀሐይ ደማቅና ብሩህ ነች። ትላንትን ከአለም ጋር ያሳለፈውን ጊዜ አስታወሰ
.. እሷን ጎትቶ ፈረስ ላይ ሲያወጣት እና ተፈናጥራ በእጇቾ ወገቡን ጨምድዳ ስትይዝ… ጀርባዋ ላይ ስትለጠፍበት …አናዳጅና አብሻቂ ጥያቄዎቾን ስታዥጎደጉድበት በወቅቱ ያየባት ብልሀትና ብልጠት አስገርሞታል….በተቃራኒው ደግሞ ማታ የሙስጠፋ ሬሳ ጋር በዛ በጭለማ ቦታ ሲያገኛት በጣም የፈራች ፤የምትንቀጠቀጥና ፈሪ ሴት ሆና ነው ያገኛት፡፡

‹‹ምናልባት የሙስጠፋ አሰቃቂ ግድያ ስለእናቷ ግድያ የምታደርገውን ምርመራ ፈርታ እንድታቆም ያስገድዳት ይሆናል። ምናልባት ሻሸመኔን ትታ ወደ ኋላ ላትመለስ ወደ አዲስአባዋ ትመለስ ይሆናል።››ሲል አሰበ፡፡ይህ አጋጣሚ ሊያስደስተው በተገባ ነበር። ግን አላስደሰተውም። በእሷ እና በራሱ ላይ የበለጠ ተናደደ።ትላንትን ከእሷ ጋር መሳሳሙ የደደብ ሰው ተግባር እንደፈፀመ ነው የተሰማው፡፡በወቅቱ ራሱን መቆጣጠር ፈልጎ ነበር። ግን ለስሜቱ ተገዢ ሆኖ ማድረግ የሌለበትን ነገር አድርጎል፡፡በህይወቱ እንዲህ እንዲያደርግ ያስቸለው አንድ ሌላ ሴት ብቻ ነበረች እሷም ሰሎሜ ነች። ገረመው። ለዓመታት አላሰበውም ነበር ፣ ግን አሁን በአእምሮው ውስጥ ግልፅ ሆኖ እየታየው ነው።

ሰሎሜ ትወደው ነበር።እሱም ወዷት ነበር። አንድ ቀን ሊጋቡ ተስማምተው ነበር….ፍቅራቸውን የሚያጨነግፍ ምንም አይነት እንቅፋት በመሀከላቸው እንደማይፈጠር እርግጠኞች ነበሩ….ገመዶ አይኑን በድካም እያሻሸ ወደ ጠረጴዛው ተመለሰ እና ወንበር ላይ
ተቀመጠ ። አለም ለዓመታት ውስጡ የቀበረውን  ትዝታ እየቆሰቆሰች እንዲያስታውስ እየደረገችው ስለሆነ ተበሳጨባት ፡፡ትናንት እሷን ሲስማት  ሊቀጣት እና ሊያበሳጫት ነበር አላማው ። ነገር ግን ውጤቱ ተገላቢጦሽ ነበር የሆነበት… ።ከንፈሯ ልክ እንደእናቷ በዛ መጠን  ይጣፍጣል ብሎ አልጠበቀም ነበር። ያ ጣፋጭነት አሁንም በምላሱ ላይ ቀርቷል. ድድር ጡቶቿ በዛ ልክ ስሜት ቀስቃሽ እና ለስላሳ እንደሚሆኑ እንዴት ሊገምት ይችላል? ለወደፊቱ ሁሉንም እቅዶቹን ማበላሸቷ እንደማይቀር ገመተ። ህልሙን እውን ለማድረግ በጣም ቅርቦ ነበር። ሊደርስ  ጥቂት ነበር የቀረው….።ህይወቱን በሙሉ በትጋት የሰራበት ቦታ ለመሆን አንድ የመጨረሻ እርምጃ ነበር የቀረው።በዚህ መጥፎ ጊዜ ነው እንቅፋት ሆና ከፊቱ የተገተረችው፡፡‹እና ምን ያድርግ አንቆ ይግደላት ?›ስለማነቅ ሲያስብ ዘገነነው፡፡ ሀሳቡን ሳያገባድድ የበራፍ መቆርቆር ሰማ….

‹‹ይግቡ››

በራፉን  ከፈተችና  ገባች  እና  "  እንደገባህ  ነግረውኝ  ነው  ቀጥታ  ወደእዚህ የመጣሁት››አለችው፡፡

እሷን በማያቱ እንዳልተደሰተ በሚያሳብ የድምፅ ቃና‹‹እ …ዛሬ ደግሞ ምንድነው?››ሲል ጠየቃት ፡፡አለም በሩን ዘጋችና ወደውስጥ ዘልቃ በመግባት ወንበር ይዛ ተቀመጠች፡፡

"ከደቂቃዎች በኋላ ወደ ፍርድ ቤት እንደምሄድ አልነገሩሽም? ››

‹‹አይ…አልነገሩኝም››አለችው ፈገግ ብላ…ከትናንት ማታው ሁኔታ ያገገመች ትመስላለች፡፡ " እሺ ምንድነው ጉዳይሽ?"በመሰላቸት ጠየቃት፡፡

"ስለተገደለው  ሰው  ልትጠይቁኝ  ትፈልጋላችሁ  ብዬ  ስላሰብኩ  ነው…ቃል  ልሰጥ የመጣሁት››

"በእርግጥ ተጠርጣሪ አይደለሽም። የተሳሳተ ጊዜ ላይ በተሳሳተ ቦታ ተገኝተሸ ነው ፡፡ይሄ ድግሞ ያንቺ መጥፎ ልማድ ነው።"አላት፡፡

"በእኔ እና በእሱ ግድያ መካከል ግንኙነት ያለ አይመስላችሁም?" "አይ አይመስለንም ››አላት ፍርጥም ብሎ፡፡

‹‹እኔ ደግሞ ይመስለኛል››

"ከሆነ እንስማው" አለ።

"አስቀድመህ የምታውቀው ይመስለኛል። ሙስጠፋ የሰሎሜን ግድያን አይቷል…የአይን እማኝ ምስክር ነበር።"

በበደነ እና በቀዘቀዘ ስሜት "እንዴት አወቅሽ?"ሲል ጠየቃት፡፡

"በስልክ ደውሎ ነገረኝ።"

"እሱ እኮ  ውሸታም ሰው እንደሆነ ማንም ያውቃል….ስለባህሪው የሚያውቁትን ሰዎች መጠየቅ ትችያለሽ "

"እኔ አምኜዋለሁ። በጣም የተደናገጠ እና በጣም የፈራ ይመስላል ነበር። በመጨረሻ ለመገናኘት ቀጠሮ ይዘን ነበር፣ አንተ ስትከተለኝ እንደነበረ የነገረኝ እሱ ነው…በዛን ቀን እዛ ሆቴል ባትገኝ ኖሮ የእናቴን ገዳይ በዝርዝር ይነግረኝ ነበር።"

"ታዲያ ይሄ ዝርዝር.. የሰሎሜ ገዳይ ያደርገኛል?"

"ገዳይ ባትሆን አንኳን ለገደለው ሰው እየሸፈንክለት ሊሆን ይችላል ››

"በንድፈ ሀሳብሽ ላይ ምን ችግር እንዳለ ልንገርሽ?አቶ ፍሰሀ ከስራ ካባረረው ቀን አንስቶ እሱ የበቀል ጉዞ ላይ ነበር፣ ድንገት አንቺ የእናትሽን ገዳይ እያነፈነፍሽ እንዳለ ሲሰማ በዛ ተንኮለኛ ጭንቅላቱ ነገሮችን አገጣጠመና ጥሩ ድረሰት በአእምሮ ቀምሞ ሊያጃጅልሽ ሞከረ…››

" ያ እውነት አይደለም..ሰውዬው የተገደለው. ስለእናቴ አሟሟት ለእኔ እንዳይነግረኝ አፉን ለማዘጋት ነው ፡፡ይህ ሰውዬ የእናቴን መገደል ለማየት የሚችልበት አጋጣሚ ከፍተኛ ነው…እንደሚታወቀው እናቴ የሞተችው በእርባታ ድርጅት ውስጥ በከብቶቹ በረት አካባቢ ነው..እሱ ደግሞ የከብቶቹ ተንከባካቢ ስለሆነ አብዛኛውን ጊዜ ከአካባቢው አይጠፋም፣››

‹‹የፈለግሽውን ማመን ትችያለሽ…ለማንኛውም የእሱን መገደል የተመለከተ የአይን እማኝ እንዳገኘን ነግሬሽ ነበር..እድሜ ለእሱ አሁን የሰውዬውን ገዳይ ይዘነዋል…››

ደነገጠች‹‹ይዘነዋል…..እና አመነ?››

‹‹ትንሽ ቢያቅማማም አምኗል››

‹ለምን ገደልኩት አለ?››

‹‹ሚስቴን አማግጦብኛል ..የሚል ምክንያት ነው የሰጠው…የሰውዬውን ሚስትም አግኝተን አናግረናታል…ከሟቹ ጋር የድብቅ የፍቅር ግንኙነት እንዳላት አልካደችም…..››

‹‹ይገርማል…ለሊቱን ሙሉ አልተኛህም አይደል….?በእውነት በአንድ ለሊት ይሄን ሁሉ አቀናብራችሁና አደራጅታችሁ ማደር በመቻላችሁ በራሳችሁ ልትኮሩ ይገባል….››

‹‹ምን ለማለት ፈልገሽ ነው?››የደፈረሱ አይኖቹን አጉረጠረጠባት፡፡

‹‹አንዲት ሴት የደፈረ ወንጀለኛ ለመያዝ ስድስት ወር የማይበቃችሁ በ12 ሰዓት ውስጥ ለዛውም በለሊት ገዳዩን ይዛችሁ …ምስክር አጠናቅራችሁ እንዲህ ጥንቅቅ ብላችሁ ሳያችሁ ባልደነቅ ነው የሚገርመው…..እርግጠኛ ነኝ በጥዋት መጥቼ እንደማፋጥጥህ እርግጠኛ ስለሆንክ መደረግ ያለበትን ነገር ሁሉ አድርገሀል…አድናቂህ ነኝ፡፡››

ሚመልስላት ስላልነበረው ዝም አላት..

"ሁሉንም ፕሮፌሽናል ሴቶች ትጠላለህ ወይስ በተለይ እኔ ነው የምትጠላው?"ስትል ሌላ ያልጠበቀውን ጥያቄ ጠየቀችው፡፡

‹‹በተለይ አንቺ ነው የምጠላው።"አላት ፡፡ድፍረቱ አስነዋሪ ነበር። የትናንት መሳሳማቸውን እንዳልወደደው የሚያሳይ ነገር አላነበበችበትም ፡፡በመሀከላቸው ምንም እንዳልተፈጠረ ለማስመሰል ሞከረች፡፡ ግን መርሳት አልቻለችም። ንግግሩ በጣም ጎድቷታል።

"ለምንድነው ማትወደኝ?"ስትል ጠየቀችው

"ምክንያቱም አንቺ ጣልቃ ገብ ነሽ። በሌሎች ሰዎች ህይወት ውስጥ ጣልቃ የሚገቡ ሰዎችን አልወድም።"

"ይህ ጣልቃ መግባት አይደለም… የእኔ ጉዳይ የእናቴን ገዳይ መፈለግ  ነው."
31👍5