#የወዲያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...አስታውሳለሁ ግን እኮ ታዲያ...” ብዩ ሙሉ ሐሳቤን ሳልገልጽላት ዝም አልኩ።የዝምታዬ መነሾና ጥጥር ምክንያት ግን አዲሱ እኔ በመሆኑ እሷ ልታውቀው
አትችልም፡፡
«ና በል እንሒድ ቶሉ እንመለሳለን» አለችና ተነሣች። የእኔ ጉዳይ
በእርሷና በእናቴ መካከል ተመክሮበት ያለቀ በመሆኑ እንግዲህ አደራሽን እንደዚያቹ እንደ ምክራችን አድርገሽ ንገሪው፡፡ እኔና አንቺ እንደ ተባባልነው
ቢሆን ይሻላል፡፡ ከዚያ በኋላ ደግሞ እኔ ደኅና አድርጌ እነግረዋለሁ፤ አደራሽን አደራችሁን» ብላ እናቴ በዐይኗ ሸኘችኝ፡፡ «ሂዱ» የምትለን ወደ እኔ ቤት መሆኑን አወቅሁ፡፡ የወዲያነሽን ለመጠበቅ ቆምኩ። «ሂዱ እንጂ ምን ቀረህ?
እናቷ እኮ ነኝ! ሌላ እናት ያላት መሰለህ? አይዞህ! ለሌላ ሰው አልሰጥብህም፣ እሷም በጀ አትልም» ብላ ስቃ አሣቀችኝ፡፡ የወዲያነሽ እናቴን በዐይኗ እየጠበቀች 'የሂዱ' ምልክት በጣቷ አሳየችኝ። ምርቱን እንደከተተ ሰው ተደስቼ ወጣሁ፡፡ወደ እኔ ቤት የመሄዱን ነገር ሰርዘን መኪና ውስጥ ተቀመጥን።
«አባቴ ስለ አንተና ስለ የወዲያነሽ ምንም ነገር ፈጽሞ እንዳልሰማና እስከ ዛሬም እንዳላወቀ ታውቃለህ:: ምስጢሩን የቀበርነው ሁላችንም ስለ ፈራነው ነው»
በማለት ንግግሯን ጀመረች፡፡ ጠንቃቃነቴንና ለጉዳዩ ያለኝን ከፍተኛ ግምት በግልጽ ለማስረዳት «አንቺና እማማስ ብትሆኑ ካባረራችኋት በኋላ ስለ እርሷ ምን የምታውቁት ነገር ነበር? ምስጢሩ ያልተነዛው ከእርሷ ጋር በመባረሩና እስር ቤት
በመውረዱ ነበር» ብዩ ተራ ለቀቅሁ፡፡
«ነገሩን በብልሃትና በዘዴ ካላስኬድነው በስተቀር ከአባታችን ጋር ብዙ ንትርክና ጭቅጭቅ እንደሚነሳ የታወቀ ነው፡፡ እኛ ግን ስለ ነገሩ ፍንጭ አግኝቶ
እንዲጠራጠር በማድረግ ጉዳዩን ለመጀመር አስበናል፡፡ ከዚያ በኋላ ደግሞ አንተም እኛም ጥሩ ጥሩ ሽማግሌዎች መርጠን...» ብላ ሳትጨርስ «የብልሃቴ አቀነባባሪ እኔ ነኝ፡፡ የአዲሱ ሕይወቴ ጎዳና ቀያሽና ደልዳይ ራሴ ነኝ።
እያስፈልግም፡ በቃኝ! አባቴንም እንደ እናቴ በማስማልና በፍርሃት
እየተርበደበድኩ በመጠጋት የሚለኝንና የሚወስንብኝን ሁሉ አቀርቅሬ በመስማት ዕድል ለሚሏት አጋጣሚ ነገር አልንበረከክም! መጠራጠር ማለት ስለ አንድ ነገር ቢያንስ በጥቂቱ ማወቅ ወይም መገመት ማለት ነው። የትላንቱን ስሕተቴን ዛሬና
ነገ መድገም የለብኝም፡፡ አታስቡ! እኔ ለአባቴ የራሴ ዝግጅት አለኝ፡፡ በቀጥታ ቀርቤ ፊት ለፊት አስረዳዋለሁ፡፡ ለጥያቄዎቹም መልስ እሰጣለሁ» በማለት ጣልቃ
ገብቼ ተናገርኩ። ድንገት ደሟ ፈላና «ከንትርክና ብዙ ጣጣን ከሚያስከትል ጭቅጭቅ ይልቅ መግባባት ይበልጣል። በንትርክና በአሻፈረኝ ባይነት የምታገኘው
ድል አድራጊነት ሁሉ እስከ መጨረሻው አያረካህም፡፡ አባቴ በመጀመሪያ ጋሻዬነን አይቶ ከተደሰተና የሐሳቡ አቅጣጫ ካማረ ሁሉም ነገር ይሳካልናል።
የወዲያነሽንና የአንተን ግንኙነት፣ የደረሰባትን መከራና ሥቃይ ሁሉ ቀስ በቀስ እተርክለታለሁ፡፡ ልቡ ካዘነና መንፈሱ በርህራሄ ከተነካ፡ በሉ ሂዱና አምጧት ይላል” ብላ ነገሯን ልታራዝም ስትል «አይቻልም! ማን አስተርጓሚ አደረገሽና!
መሸሸግም ሆነ መደበቅ የለበትም፡፡ አልለማመጥም:: እጅግ አርኪው ድል አድራጊነትም ከትግልና ከሥቃይ በኋላ የሚገኝ ድል አድራጊነት ነው፡፡ እኔና
የወዲያነሽ ጋሻዬነህን አስከትለን ባንድ ላይ እንቀርባለን፡፡ ይህ ከመሆኑ በፊት “እንቺም ሆንሽ እናቴ አንዲት ቃል መናገርም ሆነ ማሰማት የለባችሁም፡፡ በምንቀርብበት ቀን እንግዶች ቢኖሩም ባይኖሩም ግድ የለኝም። እንዲያውም ወሬው እንዲስፋፋና እንዲዛመት ብዙ ሰዎች ቢኖሩ በጣም ጥሩ ነው:: በዚህ ብትስማሙ ተስማሙ፡ አለበለዚያ ግን የማደርገውንና የማላደርገውን እኔ ራሴ አውቃለሁ፡፡ እኔ የምፈልገው እንዲያውቅ ብቻ እንጂ እንዲስማማ ወይም መርቆ
እንዲቀበለን አይደለም፡፡ ከባለቤቴ ጋር ባለን ግንኙነት ውስጥ ጣልቃ ገብቶ አስተያየትም ሆነ ሌላ ሐሳብ እንዲያቀርብ አይደለም» በማለት ቀጥ እንዳለ አቀበት ስትፈራው የቆየችውን ጉዳይ አውላላ ሜዳ አደረግሁላት፡፡ በእኔ ላይ የነበራት ግምትና አስተሳሰብ ሁሉ ነፋስ እንደ መታው ልም ዱቄት ተበተነ፡፡በሁለታችን መካከል በጣም ግዙፍ የሆነ የሐሳብ ልዩነት ተፈጠረ፡፡ በእኔ ላይ የሐሳብ በላይነት ለማግኘት ባለመቻሏ ተከዘች። ምክራቸውንና መላቸውን ሁሉ ባለምቀበሌ ንዴቷ ናረ። የመዥገር ሞት ያህል አላሳዘነችኝም፡፡ ቁርጡን ለማወቅ
የጓጓው አእምሮዋ ራሱ የዘጋውን የዝምታ በር ከፈተው፡፡ «እኔ እና የግሌን የአቀራረብ መንገድና ሐሳብ አዘጋጃለሁ እንጂ የእናንተን አልቀበልም ማለትህ ነው?» ብላ ሁኔታዬንም አብራ ለመረዳት ፊቷን ወደ እኔ አዞረች፡፡
ባጭሩና በቀላሉ ”አዎ” አልኩና ተጨማሪ ምክንያትና ማብራሪያ
ለማቅረብ ስዘጋጅ «በቃኝ አያስፈልገኝም! አልሰማም ቀኙን ሲያሳዩህ ግራ ግራውን ትመርጣለህ፡፡ እኔን ያናደደኝ ያንተ እምቢታና የመጣው ይምጣ ባይነት ሳይሆን በዚሀ ይሻላል በዚያ፡ ይኸ ያዋጣል ያኛው ይበልጣል እያልኩ ከእናቴ ጋር
ስነታረክና ስከራከር መሰንበቴ ነው» ብላ ፊቷን አዞረች።
አልደነገጥኩም፡፡ «የአንቺም ይሁን የእናቴ ርዳታ እያስፈልገኝም፡፡ ጥገና እና ድረታ አልፈልግም፡ ጥገና አይዋጥልኝም! ጥገና ማለት ውስጠ ሰባራ ማለት ነው፡፡
ከሆነላችሁ እናንተም ተደርባችሁ በጥያቄና መልስ አዋከቡኝ! ዝግጁ ነኝ። ነገር ግን እኔ በማልገኝበት ወቅት አባቴን እንድትለምኑልኝና እኔን፣ ባለቤቴንና ልጄን ዝቅ አድርጋችሁ እንድትለማመጡልኝ አልፈልግም፡፡ እኔ ራሴ ባለጉዳዩ ፍላጎቴንና ውሳኔዩን ለማስረዳት በሚገባ ዝግጁ ሆኛለሁ» ብዬ ፋታ ሰጠሁ፡፡
«አያዋጣም እንጂ ቢያዋጣማ ጥሩ ነው:: ለፍተህ ለፍተህ እዚህ ከደረስክ በኋላ እንዴት እንዲህ በቀላሉ ትገነፍላለህ?» ብላ ራሷን ነቀነቀች።
«በቃኝ ነው የምልሽ! በሐሳቤና በእምነቴ እንድትስማሚ አላስገድድሽም። የገዛ መብቴን አልመፀወትም:: የሕሊናዬን ቁስል የማድንበትን መድኃኒት ቀስ በቀስ እያወቅሁ ነው:: ከአባቴ መሠረተቢስ እምነት ጋር እንድጋጭና እንድታተር
እንጂ እንደ ከዚህ ቀደሙ አንገቴን ሰብሬ የሚኖረው የሚያቀርበውን
ዝባዝንኪ ሐሳብ ሁሉ ያለ አንዳች ክርክር እንድቀበል አልፈልግም! ጨቋኝ ግዴታውን አልቀበልም:: ሐሳባችሁንም ሰርዙ። ከዚህ አሁን ከነገርኩሽ አፈጻጻም ውጪ አንዳችም የምቀበለውና የምስማማበት ሐሳብ ስለ ሌለ ነገር ሳናንዛዛ ወደ ቤት እንግባ» አልኩና ለጠላቱ የመጭረሻ ማስጠንቀቂያ እንደሚሰጥ
ሰው የማያወላዳውን ነገርኳት። ለወለላ ገሥግላ ፊት ዛቀች!
ያለውን ይበል ብላ እንዴት አታስብም? እንዴት አይገባህም? ነገሩን ረጋ ብለህ ተመልከተው፡ ራስህን ብቻ አትውደድ፡ ይኸማ ይበጣበጡ' ይጣሉ፡ ይጋደሉ ማለትህ እኮ ነው? ስንትና ስንት ዓመት ሙሉ ምስጢሩን ደብቀህ
ከኖርክ በኋላ አሁን በመጨረሻ ጣጣን አመጣህ። ለካስ በጄም በግሬም ገብተህ የተለማመጥከኝ እንዲህ ለመሆን ኖሯል? አሁን አንተ በምትለው ሁኔታ ከሆነ
አገር ምድሩን እንደሚበጠብጥ አውቃለሁ፡፡ እናቴ ግን ያን ሁሉ አድራጎት ያደረገችው ላንተው ስትል እንደነበር ታውቃለህ» ብላ ፊት ለፊት ወደ ጨለማው
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...አስታውሳለሁ ግን እኮ ታዲያ...” ብዩ ሙሉ ሐሳቤን ሳልገልጽላት ዝም አልኩ።የዝምታዬ መነሾና ጥጥር ምክንያት ግን አዲሱ እኔ በመሆኑ እሷ ልታውቀው
አትችልም፡፡
«ና በል እንሒድ ቶሉ እንመለሳለን» አለችና ተነሣች። የእኔ ጉዳይ
በእርሷና በእናቴ መካከል ተመክሮበት ያለቀ በመሆኑ እንግዲህ አደራሽን እንደዚያቹ እንደ ምክራችን አድርገሽ ንገሪው፡፡ እኔና አንቺ እንደ ተባባልነው
ቢሆን ይሻላል፡፡ ከዚያ በኋላ ደግሞ እኔ ደኅና አድርጌ እነግረዋለሁ፤ አደራሽን አደራችሁን» ብላ እናቴ በዐይኗ ሸኘችኝ፡፡ «ሂዱ» የምትለን ወደ እኔ ቤት መሆኑን አወቅሁ፡፡ የወዲያነሽን ለመጠበቅ ቆምኩ። «ሂዱ እንጂ ምን ቀረህ?
እናቷ እኮ ነኝ! ሌላ እናት ያላት መሰለህ? አይዞህ! ለሌላ ሰው አልሰጥብህም፣ እሷም በጀ አትልም» ብላ ስቃ አሣቀችኝ፡፡ የወዲያነሽ እናቴን በዐይኗ እየጠበቀች 'የሂዱ' ምልክት በጣቷ አሳየችኝ። ምርቱን እንደከተተ ሰው ተደስቼ ወጣሁ፡፡ወደ እኔ ቤት የመሄዱን ነገር ሰርዘን መኪና ውስጥ ተቀመጥን።
«አባቴ ስለ አንተና ስለ የወዲያነሽ ምንም ነገር ፈጽሞ እንዳልሰማና እስከ ዛሬም እንዳላወቀ ታውቃለህ:: ምስጢሩን የቀበርነው ሁላችንም ስለ ፈራነው ነው»
በማለት ንግግሯን ጀመረች፡፡ ጠንቃቃነቴንና ለጉዳዩ ያለኝን ከፍተኛ ግምት በግልጽ ለማስረዳት «አንቺና እማማስ ብትሆኑ ካባረራችኋት በኋላ ስለ እርሷ ምን የምታውቁት ነገር ነበር? ምስጢሩ ያልተነዛው ከእርሷ ጋር በመባረሩና እስር ቤት
በመውረዱ ነበር» ብዩ ተራ ለቀቅሁ፡፡
«ነገሩን በብልሃትና በዘዴ ካላስኬድነው በስተቀር ከአባታችን ጋር ብዙ ንትርክና ጭቅጭቅ እንደሚነሳ የታወቀ ነው፡፡ እኛ ግን ስለ ነገሩ ፍንጭ አግኝቶ
እንዲጠራጠር በማድረግ ጉዳዩን ለመጀመር አስበናል፡፡ ከዚያ በኋላ ደግሞ አንተም እኛም ጥሩ ጥሩ ሽማግሌዎች መርጠን...» ብላ ሳትጨርስ «የብልሃቴ አቀነባባሪ እኔ ነኝ፡፡ የአዲሱ ሕይወቴ ጎዳና ቀያሽና ደልዳይ ራሴ ነኝ።
እያስፈልግም፡ በቃኝ! አባቴንም እንደ እናቴ በማስማልና በፍርሃት
እየተርበደበድኩ በመጠጋት የሚለኝንና የሚወስንብኝን ሁሉ አቀርቅሬ በመስማት ዕድል ለሚሏት አጋጣሚ ነገር አልንበረከክም! መጠራጠር ማለት ስለ አንድ ነገር ቢያንስ በጥቂቱ ማወቅ ወይም መገመት ማለት ነው። የትላንቱን ስሕተቴን ዛሬና
ነገ መድገም የለብኝም፡፡ አታስቡ! እኔ ለአባቴ የራሴ ዝግጅት አለኝ፡፡ በቀጥታ ቀርቤ ፊት ለፊት አስረዳዋለሁ፡፡ ለጥያቄዎቹም መልስ እሰጣለሁ» በማለት ጣልቃ
ገብቼ ተናገርኩ። ድንገት ደሟ ፈላና «ከንትርክና ብዙ ጣጣን ከሚያስከትል ጭቅጭቅ ይልቅ መግባባት ይበልጣል። በንትርክና በአሻፈረኝ ባይነት የምታገኘው
ድል አድራጊነት ሁሉ እስከ መጨረሻው አያረካህም፡፡ አባቴ በመጀመሪያ ጋሻዬነን አይቶ ከተደሰተና የሐሳቡ አቅጣጫ ካማረ ሁሉም ነገር ይሳካልናል።
የወዲያነሽንና የአንተን ግንኙነት፣ የደረሰባትን መከራና ሥቃይ ሁሉ ቀስ በቀስ እተርክለታለሁ፡፡ ልቡ ካዘነና መንፈሱ በርህራሄ ከተነካ፡ በሉ ሂዱና አምጧት ይላል” ብላ ነገሯን ልታራዝም ስትል «አይቻልም! ማን አስተርጓሚ አደረገሽና!
መሸሸግም ሆነ መደበቅ የለበትም፡፡ አልለማመጥም:: እጅግ አርኪው ድል አድራጊነትም ከትግልና ከሥቃይ በኋላ የሚገኝ ድል አድራጊነት ነው፡፡ እኔና
የወዲያነሽ ጋሻዬነህን አስከትለን ባንድ ላይ እንቀርባለን፡፡ ይህ ከመሆኑ በፊት “እንቺም ሆንሽ እናቴ አንዲት ቃል መናገርም ሆነ ማሰማት የለባችሁም፡፡ በምንቀርብበት ቀን እንግዶች ቢኖሩም ባይኖሩም ግድ የለኝም። እንዲያውም ወሬው እንዲስፋፋና እንዲዛመት ብዙ ሰዎች ቢኖሩ በጣም ጥሩ ነው:: በዚህ ብትስማሙ ተስማሙ፡ አለበለዚያ ግን የማደርገውንና የማላደርገውን እኔ ራሴ አውቃለሁ፡፡ እኔ የምፈልገው እንዲያውቅ ብቻ እንጂ እንዲስማማ ወይም መርቆ
እንዲቀበለን አይደለም፡፡ ከባለቤቴ ጋር ባለን ግንኙነት ውስጥ ጣልቃ ገብቶ አስተያየትም ሆነ ሌላ ሐሳብ እንዲያቀርብ አይደለም» በማለት ቀጥ እንዳለ አቀበት ስትፈራው የቆየችውን ጉዳይ አውላላ ሜዳ አደረግሁላት፡፡ በእኔ ላይ የነበራት ግምትና አስተሳሰብ ሁሉ ነፋስ እንደ መታው ልም ዱቄት ተበተነ፡፡በሁለታችን መካከል በጣም ግዙፍ የሆነ የሐሳብ ልዩነት ተፈጠረ፡፡ በእኔ ላይ የሐሳብ በላይነት ለማግኘት ባለመቻሏ ተከዘች። ምክራቸውንና መላቸውን ሁሉ ባለምቀበሌ ንዴቷ ናረ። የመዥገር ሞት ያህል አላሳዘነችኝም፡፡ ቁርጡን ለማወቅ
የጓጓው አእምሮዋ ራሱ የዘጋውን የዝምታ በር ከፈተው፡፡ «እኔ እና የግሌን የአቀራረብ መንገድና ሐሳብ አዘጋጃለሁ እንጂ የእናንተን አልቀበልም ማለትህ ነው?» ብላ ሁኔታዬንም አብራ ለመረዳት ፊቷን ወደ እኔ አዞረች፡፡
ባጭሩና በቀላሉ ”አዎ” አልኩና ተጨማሪ ምክንያትና ማብራሪያ
ለማቅረብ ስዘጋጅ «በቃኝ አያስፈልገኝም! አልሰማም ቀኙን ሲያሳዩህ ግራ ግራውን ትመርጣለህ፡፡ እኔን ያናደደኝ ያንተ እምቢታና የመጣው ይምጣ ባይነት ሳይሆን በዚሀ ይሻላል በዚያ፡ ይኸ ያዋጣል ያኛው ይበልጣል እያልኩ ከእናቴ ጋር
ስነታረክና ስከራከር መሰንበቴ ነው» ብላ ፊቷን አዞረች።
አልደነገጥኩም፡፡ «የአንቺም ይሁን የእናቴ ርዳታ እያስፈልገኝም፡፡ ጥገና እና ድረታ አልፈልግም፡ ጥገና አይዋጥልኝም! ጥገና ማለት ውስጠ ሰባራ ማለት ነው፡፡
ከሆነላችሁ እናንተም ተደርባችሁ በጥያቄና መልስ አዋከቡኝ! ዝግጁ ነኝ። ነገር ግን እኔ በማልገኝበት ወቅት አባቴን እንድትለምኑልኝና እኔን፣ ባለቤቴንና ልጄን ዝቅ አድርጋችሁ እንድትለማመጡልኝ አልፈልግም፡፡ እኔ ራሴ ባለጉዳዩ ፍላጎቴንና ውሳኔዩን ለማስረዳት በሚገባ ዝግጁ ሆኛለሁ» ብዬ ፋታ ሰጠሁ፡፡
«አያዋጣም እንጂ ቢያዋጣማ ጥሩ ነው:: ለፍተህ ለፍተህ እዚህ ከደረስክ በኋላ እንዴት እንዲህ በቀላሉ ትገነፍላለህ?» ብላ ራሷን ነቀነቀች።
«በቃኝ ነው የምልሽ! በሐሳቤና በእምነቴ እንድትስማሚ አላስገድድሽም። የገዛ መብቴን አልመፀወትም:: የሕሊናዬን ቁስል የማድንበትን መድኃኒት ቀስ በቀስ እያወቅሁ ነው:: ከአባቴ መሠረተቢስ እምነት ጋር እንድጋጭና እንድታተር
እንጂ እንደ ከዚህ ቀደሙ አንገቴን ሰብሬ የሚኖረው የሚያቀርበውን
ዝባዝንኪ ሐሳብ ሁሉ ያለ አንዳች ክርክር እንድቀበል አልፈልግም! ጨቋኝ ግዴታውን አልቀበልም:: ሐሳባችሁንም ሰርዙ። ከዚህ አሁን ከነገርኩሽ አፈጻጻም ውጪ አንዳችም የምቀበለውና የምስማማበት ሐሳብ ስለ ሌለ ነገር ሳናንዛዛ ወደ ቤት እንግባ» አልኩና ለጠላቱ የመጭረሻ ማስጠንቀቂያ እንደሚሰጥ
ሰው የማያወላዳውን ነገርኳት። ለወለላ ገሥግላ ፊት ዛቀች!
ያለውን ይበል ብላ እንዴት አታስብም? እንዴት አይገባህም? ነገሩን ረጋ ብለህ ተመልከተው፡ ራስህን ብቻ አትውደድ፡ ይኸማ ይበጣበጡ' ይጣሉ፡ ይጋደሉ ማለትህ እኮ ነው? ስንትና ስንት ዓመት ሙሉ ምስጢሩን ደብቀህ
ከኖርክ በኋላ አሁን በመጨረሻ ጣጣን አመጣህ። ለካስ በጄም በግሬም ገብተህ የተለማመጥከኝ እንዲህ ለመሆን ኖሯል? አሁን አንተ በምትለው ሁኔታ ከሆነ
አገር ምድሩን እንደሚበጠብጥ አውቃለሁ፡፡ እናቴ ግን ያን ሁሉ አድራጎት ያደረገችው ላንተው ስትል እንደነበር ታውቃለህ» ብላ ፊት ለፊት ወደ ጨለማው
👍3
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
.....አምናን ካቻምናን ከዚያ በፊት የተቆጠሩ ዓመታትን ጨምሮ ለብዙ ጊዜ የደከሙበት ትምህርት የሚቋጨው ዘንድሮ ነው። ጌትነትና አማረች ከጓደኞቻቸው ጋር በቡድን በቡድን ሆነው እያሽመቁ ጥናታቸውን ሲለበልቡ የከረሙበት ላለፉት ረጅም አመታት ትምህርታቸውን በመከታተልና የሚሰጣቸውን አድካሚ የቤት ስራዎችን ከመደበኛ ሥራቸው ጋር አጣምረው በመስራት ከፍተኛ ዋጋ የከፈሉበት የነዚያ ሁሉ አመታት ልፋት ድምር ውጤት የሚደመደምበትና የሚመረቁበት አመት ዘንድሮ ነው።
ሁለቱ ፍቅረኛሞች በአዋሳ ላንጋኖ ሃይቅ ውስጥ ተክለው ያለመለሙት ፍቅራቸው የሚያስቀና ሆኗል። ጌትነት የመልካሙ ተበጀ አዋሳ ላንጋኖ
ዘፈን አስቀድሞ የሚወደው ቢሆንም ለሱ የተዘፈነለት እስከሚመስለው ድረስ በይበልጥ የወደደውና አብሮ ማቀንቀን የጀመረው ከላንጋኖ ሽርሽር
በኋላ ነው።
አዋሳ ላንጋኖ ለሽርሽር ሄጄ ያየሁሽ፣
የሲዳሞ ቆንጆ እንዴት ነሽ?
ሽንጥና ተረከዝ ዳሌና ጡትሽ...
አዲስ አበባ ውስጥ ለሁለት አመታት ሲመኛት ቢኖርም በፍቅር ያወቃት በአዋሳ ላንጋኖ ሀይቅ ውስጥ ነበረና ያንን ዘፈን ሲሰማ የአዋሳ ላንጋኖው ሃይቅና ያ ውብና ምንጊዜም ከህሊና የማይጠፋ አስደሳች ዓለም ከነሙሉ
ጓዙ ተጠቅልሎ በሃሳቡ እየመጣበት ዘፈኑን ነፍሱ ምንጥቅ ብላ እስከምትወጣ ድረስ ወደደው። በዚህ የተነሳ የሲዳሞ ቆንጆ በሚለው ምትክ የአዲስ አበባ ቆንጆ እንዴት ነሽ በሚል ተክቶ ከዘፋኙ ጋራ አብሮ ሲያቀነቅን የሚሰማው ስሜት የተለዬ ነበር፡፡ አማረች ለሁለት አመታት ስትመኘው የነበረው ጉዳይ በመሳካቱ እጅግ ደስተኛ ከመሆኗ በላይ ከምትወደው ልጅ ጋር በትዳር ተሳስራ በመኖር የወላጆቿን ፍላጎት ለማሟላት
የሚያስችላት መልካም አጋጣሚ መፈጠሩ በአንድ ጠጠር ሁለት ወፍ ሆኖላታል። ወላጆቿ ልጃቸው ትዳር እንድትይዝላቸው ከፍተኛ ጉጉት አላቸው፡፡ “መቼ ይሆን የአያትነት ወግ ማእረግ የምታሳይኝ ልጄ? እንግዲህ ጀርባዬ ሳይጎብጥ ጉልበቴ ሳይዝል ጥሩ እስክስታ እንድመታልሽ ከፈለግሽ ይሄን ጊዜ ነው ጉልበቴን መሻማት” እያሉ የሚወተውቷት አባቷ
ይህንን ውሳኔዋን ሲሰሙ ደስታቸው ወደር እንደማይኖረው ጥርጥር አልነበራትም፡፡እናቷ አማረችን የሚያይዋት እንደ ልጃቸው ሳይሆን እንደ ታናሽ እህታቸው ነው። አማረችም እናቷን እንደ ታላቅ እህት እንጂ
እንደ እናት አይደለም የምታያቸው፡፡ ታሪኩን ያጫወተቻቸውም እሳቸው
በነገር ወጋ አድርገዋት ነው፡፡
“አማሩዬ? እኔ የምለው? እኛ የምናመጣልሽ ባል እንደማይኖር
በጠዋቱ አስጠነቀቅሽን
አንቺ የምታመጭውን ብንጠብቅ ደግሞ የማሚታይ ነገር ጠፋ።
ምን ይሻላል ልጄ? የሁልጊዜ ምክንያትሽ ትምህርቴን ልጨርስ ነው። ትዳር ተይዞ መማርን ምን ይከለክለዋል? አባትሽ ትዳር ትዳር እያልኩ ስጨቀጭቃት ሸክም ሆንሽብኝ ያልኳት እንዳይመስላት እንዳትሳቀቅብኝ እያለ እየፈራ እንጂ ከኔ የበለጠ የቸኮለ እሱ ነው፡፡ እንዲያው ለጤናው ያድርግለት ችኩል ብሏል”
የትዳሯ ነገር ያጓጓቸው፤ የሰርጉ ቀን የናፈቃቸው መሆኑን አጫወቷት።አማረች ቀኝ ክንዷን በቀኝ ጉልበቷ ላይ አገጯን በመዳፏ ደገፍ አድርጋ
በፍቅር ዐይን ዐይናቸውን እየተመለከተች ነበር የምታዳምጣቸው፡፡
ፊቷ ወይን ጠጅ መስሏል፡፡ ከረጅም ጊዜ ሚስጥር በኋላ እጮኛ ያላት መሆኑን ወላጆቿ ያላወቁት የትዳር ጥንስስ በልቧ ውስጥ ተጠንስሶ መቆየቱን ልትነግራቸው ፈለገች። ከዘንድሮ ምረቃ በኋላ ለትዳር የወጠነቸው
ጓደኛ ያላት መሆኑን ለእናቷ ለማብሰር ፈለገችና ጥርት ያለው ፊቷ በእፍረት ሲቀላባት የወይን ጠጅ መልክ እየያዘ ሄደ።
ከአማረች የመኝታ ክፍል ውስጥ ሆነው ነበር የሚጨዋወቱት፡፡ አማረች ስለፍቅረኛዋ ማስረዳቱን ቀጠለች፡፡ የዐይነ ህሊናዋ ካሜራ በጌትነት ላይ አነጣጥሮ ያሳለፉትን ጣፋጭ የፍቅር ጊዚያት አንድ በአንድ እንደ ፊልም
እየቀረፀና የአዋሳው ትዝታ ፊቷ ላይ ድቅን እያለ፡ “ትንሽ ነው የቀረኝ በጣም ትንሽ ጊዜ፡፡ በጣት የሚጠለቀውን ቀለበት አላጠለኩም እንጂ ታጭቻለሁ። ለረጅም ጊዜ የተዋወቅኩት የምወደው ፍቅረኛ አለኝ፡፡ እስከ አሁን በደንብ ተጠናንተናል። ተግባብተናል። ተዋደናል። ያንቺና የአባዬ ብቻ ሳይሆን በትዳር የመኖሩ ጉጉት በኔ ብሷል። ዩኒቨርስቲ አብሮኝ የሚማር
ልጅ ነው፡፡ ላንቺም ለአባዬም የማስተዋውቅበት ጊዜው ደርሷል። ሁላታችንም በዚህ ዓመት እንመረቃለን፡፡ እስከዛሬም የደበቅኩሽ ትምህርቴን
ከመጨረሴ በፊት ሠርጉ ይፋጠን የሚል ጥያቄ እንዳታቅርቡልኝ ነው።አሁንም ቢሆን ላንቺ ብቻ ነው የምነግረው፡፡ ለአባዬ ጊዜው ሲደርስ አንቺ ትነግሪዋለሽ” የአማረች እናት ልባቸው በደስታ ዘለለች። እንኳን የተማረ! እንኳን ያፈቀረችውን ይቅርና ሱሪ ይልበስ እንጂ እሷ ተመችቶኛል ትዳር
መያዝ እፈልጋለሁ ብላ ፈቃደኝነቷን ከገለፀች ከማንም ጋር ቢሆን ድል ባለ ሠርግ ሊድሯት ሁሌም የሚቃዡበት ምኞታቸው ነበረና፣ እንደ
ዕድሜ እኩዮቻቸው “ልጃችንን ዳርናት” እያሉ አፋቸውን ሞላ አድርገው ለመናገርና እርጅና ከመምጣቱ በፊት የአያትነት ወግ ማእረግ ሊያገኙ ነውና የሰሙት የምስራች እንደ ትንሽ ልጅ እያስቦረቃቸው የባለቤታቸውን ደስታ ጭምር አገላብጠው ሳሟት፡፡
“ለምን የፈለገው አይሆንም አማሩዬ? ይህችን አሁን ያሰማሽኝን የምስራች ይቺን እኔ የሰማኋትን ሚስጥር እሱም ቢሰማ ኖሮ በደስታ አስር
ዓመት ወደ ኋላ ያስቆጥር ነበር” በዜናው እጅግ ተደስተው ወደር የማይገኝለት የእናትነት ፍቅራቸውን እቅፍ አድርገው በመሳም ገለፁላት።አባቷ የሚወዷት የመጀመሪያ ልጃቸው ትምህርቷን ጨርሳ በዲግሪ ተመርቃ
የምትወደውን ፀባየ ሸጋና ጠንበለል ልጅ ይዛላቸው ከተፍ ስትልሳቸው ከደስታቸው የተነሳ ቦሌ አካባቢ ያሰሩትን አምስት ክፍል ቪላ ቤት ጀባ እንደሚሏቸው ጥርጥር የለውም፡፡ ይህንን ጠንቅቃ ስለምታውቅ ጌትነትና ስለመኖሪያ ቤት እያነሳ ሲጨናነቅ በልቧ ትስቅ ነበር። አማረች የምስራቹን ለእናቷ ባደረሰችበት በመመረቂያቸው ዓመት ላይ ጌትነትና እሷ የዓመት ዕረፍት ፈቃዳቸውን ወስደው ለመጨረሻው ፈተና እየተዘ
ጋጁ ነበር።
ትናንትና ለእናቷ የነገረቻቸውን ልትነግረው ፈለገች። አሁንም እንደ
አማረች በሆነ ባልሆነው “ጌትሽ ድረስ!” ሆኗል ዜማዋ፡፡ ዕቃ ሲሰበር አዲስ ፊቷ በእፍረት እየተለወጠ እየቀላ ሄደ፡፡ አሁን አሁን ደግሞ “ጌትዬ ድረስ!" ሆኗል ዜማዋ ምናምን ካስደነገጣት ጌትሽ” ብቻ ለሁሉም ነገር "ጌትሽ
ነጠላ ዜማ ሆኗል፡፡ ይሄ ነገር እናቷንም ግራ ሲያጋባቸው የኖረ ጉዳይ ነበር፡፡ በመጨረሻው ላይ እቅጩን ነገረቻቸው እንጂ ደጋግመው ስምተዋታል "ጌትዬ! ጌትዬ" ስትል፡፡
በዩኒቨርስቲው የመማሪያ ክፍል ውስጥ ከሁለቱ በስተቀር ማንም አልነበረም፡፡ባዶ ነው።ኃይለኛ ንፋስ መስኮቱን ጓ! አደረገና አላጋው። እንደልማዷ”ጌትሽ ድረስ!” በማለት ሄዳ ልጥፍ አለችበትና” ለማዘር ነገርኳት እኮ!"
አለችው እየተፍነከነከች።የመስኮቱ ጩኸት እፍረቷን አቡንኖታል።
“ምኑን?" ፈገግ እንዳለ ዘቅዝቆ እየተመለከታት፡፡
“በቃ ላስተዋውቅህ መሆኑን? እና እንትኔ መሆንህን፡ ባሌ መሆንህን!" አንገቱን እቅፍ አድርጋ ከንፈሩን ሳመችው። ቅብጥ ስትል ያለማጋነን ደስ ትላለች። የአንዳንዱ ቅብጠት ያስጠላል። አማረች ግን የቅብጠት ቅመሙን ጣል አድርጐባት ነው መሰል ቅብጥብጥ ስትል የበለጠ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
.....አምናን ካቻምናን ከዚያ በፊት የተቆጠሩ ዓመታትን ጨምሮ ለብዙ ጊዜ የደከሙበት ትምህርት የሚቋጨው ዘንድሮ ነው። ጌትነትና አማረች ከጓደኞቻቸው ጋር በቡድን በቡድን ሆነው እያሽመቁ ጥናታቸውን ሲለበልቡ የከረሙበት ላለፉት ረጅም አመታት ትምህርታቸውን በመከታተልና የሚሰጣቸውን አድካሚ የቤት ስራዎችን ከመደበኛ ሥራቸው ጋር አጣምረው በመስራት ከፍተኛ ዋጋ የከፈሉበት የነዚያ ሁሉ አመታት ልፋት ድምር ውጤት የሚደመደምበትና የሚመረቁበት አመት ዘንድሮ ነው።
ሁለቱ ፍቅረኛሞች በአዋሳ ላንጋኖ ሃይቅ ውስጥ ተክለው ያለመለሙት ፍቅራቸው የሚያስቀና ሆኗል። ጌትነት የመልካሙ ተበጀ አዋሳ ላንጋኖ
ዘፈን አስቀድሞ የሚወደው ቢሆንም ለሱ የተዘፈነለት እስከሚመስለው ድረስ በይበልጥ የወደደውና አብሮ ማቀንቀን የጀመረው ከላንጋኖ ሽርሽር
በኋላ ነው።
አዋሳ ላንጋኖ ለሽርሽር ሄጄ ያየሁሽ፣
የሲዳሞ ቆንጆ እንዴት ነሽ?
ሽንጥና ተረከዝ ዳሌና ጡትሽ...
አዲስ አበባ ውስጥ ለሁለት አመታት ሲመኛት ቢኖርም በፍቅር ያወቃት በአዋሳ ላንጋኖ ሀይቅ ውስጥ ነበረና ያንን ዘፈን ሲሰማ የአዋሳ ላንጋኖው ሃይቅና ያ ውብና ምንጊዜም ከህሊና የማይጠፋ አስደሳች ዓለም ከነሙሉ
ጓዙ ተጠቅልሎ በሃሳቡ እየመጣበት ዘፈኑን ነፍሱ ምንጥቅ ብላ እስከምትወጣ ድረስ ወደደው። በዚህ የተነሳ የሲዳሞ ቆንጆ በሚለው ምትክ የአዲስ አበባ ቆንጆ እንዴት ነሽ በሚል ተክቶ ከዘፋኙ ጋራ አብሮ ሲያቀነቅን የሚሰማው ስሜት የተለዬ ነበር፡፡ አማረች ለሁለት አመታት ስትመኘው የነበረው ጉዳይ በመሳካቱ እጅግ ደስተኛ ከመሆኗ በላይ ከምትወደው ልጅ ጋር በትዳር ተሳስራ በመኖር የወላጆቿን ፍላጎት ለማሟላት
የሚያስችላት መልካም አጋጣሚ መፈጠሩ በአንድ ጠጠር ሁለት ወፍ ሆኖላታል። ወላጆቿ ልጃቸው ትዳር እንድትይዝላቸው ከፍተኛ ጉጉት አላቸው፡፡ “መቼ ይሆን የአያትነት ወግ ማእረግ የምታሳይኝ ልጄ? እንግዲህ ጀርባዬ ሳይጎብጥ ጉልበቴ ሳይዝል ጥሩ እስክስታ እንድመታልሽ ከፈለግሽ ይሄን ጊዜ ነው ጉልበቴን መሻማት” እያሉ የሚወተውቷት አባቷ
ይህንን ውሳኔዋን ሲሰሙ ደስታቸው ወደር እንደማይኖረው ጥርጥር አልነበራትም፡፡እናቷ አማረችን የሚያይዋት እንደ ልጃቸው ሳይሆን እንደ ታናሽ እህታቸው ነው። አማረችም እናቷን እንደ ታላቅ እህት እንጂ
እንደ እናት አይደለም የምታያቸው፡፡ ታሪኩን ያጫወተቻቸውም እሳቸው
በነገር ወጋ አድርገዋት ነው፡፡
“አማሩዬ? እኔ የምለው? እኛ የምናመጣልሽ ባል እንደማይኖር
በጠዋቱ አስጠነቀቅሽን
አንቺ የምታመጭውን ብንጠብቅ ደግሞ የማሚታይ ነገር ጠፋ።
ምን ይሻላል ልጄ? የሁልጊዜ ምክንያትሽ ትምህርቴን ልጨርስ ነው። ትዳር ተይዞ መማርን ምን ይከለክለዋል? አባትሽ ትዳር ትዳር እያልኩ ስጨቀጭቃት ሸክም ሆንሽብኝ ያልኳት እንዳይመስላት እንዳትሳቀቅብኝ እያለ እየፈራ እንጂ ከኔ የበለጠ የቸኮለ እሱ ነው፡፡ እንዲያው ለጤናው ያድርግለት ችኩል ብሏል”
የትዳሯ ነገር ያጓጓቸው፤ የሰርጉ ቀን የናፈቃቸው መሆኑን አጫወቷት።አማረች ቀኝ ክንዷን በቀኝ ጉልበቷ ላይ አገጯን በመዳፏ ደገፍ አድርጋ
በፍቅር ዐይን ዐይናቸውን እየተመለከተች ነበር የምታዳምጣቸው፡፡
ፊቷ ወይን ጠጅ መስሏል፡፡ ከረጅም ጊዜ ሚስጥር በኋላ እጮኛ ያላት መሆኑን ወላጆቿ ያላወቁት የትዳር ጥንስስ በልቧ ውስጥ ተጠንስሶ መቆየቱን ልትነግራቸው ፈለገች። ከዘንድሮ ምረቃ በኋላ ለትዳር የወጠነቸው
ጓደኛ ያላት መሆኑን ለእናቷ ለማብሰር ፈለገችና ጥርት ያለው ፊቷ በእፍረት ሲቀላባት የወይን ጠጅ መልክ እየያዘ ሄደ።
ከአማረች የመኝታ ክፍል ውስጥ ሆነው ነበር የሚጨዋወቱት፡፡ አማረች ስለፍቅረኛዋ ማስረዳቱን ቀጠለች፡፡ የዐይነ ህሊናዋ ካሜራ በጌትነት ላይ አነጣጥሮ ያሳለፉትን ጣፋጭ የፍቅር ጊዚያት አንድ በአንድ እንደ ፊልም
እየቀረፀና የአዋሳው ትዝታ ፊቷ ላይ ድቅን እያለ፡ “ትንሽ ነው የቀረኝ በጣም ትንሽ ጊዜ፡፡ በጣት የሚጠለቀውን ቀለበት አላጠለኩም እንጂ ታጭቻለሁ። ለረጅም ጊዜ የተዋወቅኩት የምወደው ፍቅረኛ አለኝ፡፡ እስከ አሁን በደንብ ተጠናንተናል። ተግባብተናል። ተዋደናል። ያንቺና የአባዬ ብቻ ሳይሆን በትዳር የመኖሩ ጉጉት በኔ ብሷል። ዩኒቨርስቲ አብሮኝ የሚማር
ልጅ ነው፡፡ ላንቺም ለአባዬም የማስተዋውቅበት ጊዜው ደርሷል። ሁላታችንም በዚህ ዓመት እንመረቃለን፡፡ እስከዛሬም የደበቅኩሽ ትምህርቴን
ከመጨረሴ በፊት ሠርጉ ይፋጠን የሚል ጥያቄ እንዳታቅርቡልኝ ነው።አሁንም ቢሆን ላንቺ ብቻ ነው የምነግረው፡፡ ለአባዬ ጊዜው ሲደርስ አንቺ ትነግሪዋለሽ” የአማረች እናት ልባቸው በደስታ ዘለለች። እንኳን የተማረ! እንኳን ያፈቀረችውን ይቅርና ሱሪ ይልበስ እንጂ እሷ ተመችቶኛል ትዳር
መያዝ እፈልጋለሁ ብላ ፈቃደኝነቷን ከገለፀች ከማንም ጋር ቢሆን ድል ባለ ሠርግ ሊድሯት ሁሌም የሚቃዡበት ምኞታቸው ነበረና፣ እንደ
ዕድሜ እኩዮቻቸው “ልጃችንን ዳርናት” እያሉ አፋቸውን ሞላ አድርገው ለመናገርና እርጅና ከመምጣቱ በፊት የአያትነት ወግ ማእረግ ሊያገኙ ነውና የሰሙት የምስራች እንደ ትንሽ ልጅ እያስቦረቃቸው የባለቤታቸውን ደስታ ጭምር አገላብጠው ሳሟት፡፡
“ለምን የፈለገው አይሆንም አማሩዬ? ይህችን አሁን ያሰማሽኝን የምስራች ይቺን እኔ የሰማኋትን ሚስጥር እሱም ቢሰማ ኖሮ በደስታ አስር
ዓመት ወደ ኋላ ያስቆጥር ነበር” በዜናው እጅግ ተደስተው ወደር የማይገኝለት የእናትነት ፍቅራቸውን እቅፍ አድርገው በመሳም ገለፁላት።አባቷ የሚወዷት የመጀመሪያ ልጃቸው ትምህርቷን ጨርሳ በዲግሪ ተመርቃ
የምትወደውን ፀባየ ሸጋና ጠንበለል ልጅ ይዛላቸው ከተፍ ስትልሳቸው ከደስታቸው የተነሳ ቦሌ አካባቢ ያሰሩትን አምስት ክፍል ቪላ ቤት ጀባ እንደሚሏቸው ጥርጥር የለውም፡፡ ይህንን ጠንቅቃ ስለምታውቅ ጌትነትና ስለመኖሪያ ቤት እያነሳ ሲጨናነቅ በልቧ ትስቅ ነበር። አማረች የምስራቹን ለእናቷ ባደረሰችበት በመመረቂያቸው ዓመት ላይ ጌትነትና እሷ የዓመት ዕረፍት ፈቃዳቸውን ወስደው ለመጨረሻው ፈተና እየተዘ
ጋጁ ነበር።
ትናንትና ለእናቷ የነገረቻቸውን ልትነግረው ፈለገች። አሁንም እንደ
አማረች በሆነ ባልሆነው “ጌትሽ ድረስ!” ሆኗል ዜማዋ፡፡ ዕቃ ሲሰበር አዲስ ፊቷ በእፍረት እየተለወጠ እየቀላ ሄደ፡፡ አሁን አሁን ደግሞ “ጌትዬ ድረስ!" ሆኗል ዜማዋ ምናምን ካስደነገጣት ጌትሽ” ብቻ ለሁሉም ነገር "ጌትሽ
ነጠላ ዜማ ሆኗል፡፡ ይሄ ነገር እናቷንም ግራ ሲያጋባቸው የኖረ ጉዳይ ነበር፡፡ በመጨረሻው ላይ እቅጩን ነገረቻቸው እንጂ ደጋግመው ስምተዋታል "ጌትዬ! ጌትዬ" ስትል፡፡
በዩኒቨርስቲው የመማሪያ ክፍል ውስጥ ከሁለቱ በስተቀር ማንም አልነበረም፡፡ባዶ ነው።ኃይለኛ ንፋስ መስኮቱን ጓ! አደረገና አላጋው። እንደልማዷ”ጌትሽ ድረስ!” በማለት ሄዳ ልጥፍ አለችበትና” ለማዘር ነገርኳት እኮ!"
አለችው እየተፍነከነከች።የመስኮቱ ጩኸት እፍረቷን አቡንኖታል።
“ምኑን?" ፈገግ እንዳለ ዘቅዝቆ እየተመለከታት፡፡
“በቃ ላስተዋውቅህ መሆኑን? እና እንትኔ መሆንህን፡ ባሌ መሆንህን!" አንገቱን እቅፍ አድርጋ ከንፈሩን ሳመችው። ቅብጥ ስትል ያለማጋነን ደስ ትላለች። የአንዳንዱ ቅብጠት ያስጠላል። አማረች ግን የቅብጠት ቅመሙን ጣል አድርጐባት ነው መሰል ቅብጥብጥ ስትል የበለጠ
👍3❤1
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...አስራ ስድስት ወራትን በክብረ መንግስት አሳልፋ ወዴ ዲላ የተመስሰችው ሔዋን ብዙ አካባቢያዊ ለውጥ ሊገጥማት እንደሚችል ገምታ ነበር፡፡ነገር ግን ከሽዋዬ ቤት በዘመናዊ የቤት እቃዎች መሞላትና ወንድ ወንድ ከመሽተት በቀር ሁሉም ነገር ያው ነው።በሸዋዬ ቤት የወንድ ኮትና ጃኬት ግድግዳ ላይ ተሰቅለው የወንድ ጫማ በአልጋ ሥር ተቀምጦና ትልቅ የወንድ ፎቶ ግራፍ ብፌ ላይ ስታይ ሸዋዬ ባል ያገባች መስሎ ተሰማት። በእርግጥም “ማንዴፍሮን ገና የገባች እለት ተዋወቀችው።
ማንደፍሮ መልኩ ጥቁር ፊቱ ጉሩድረድ ያለና አካሉ ግዙፍ
ከመሆኑ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ሲጨብጣት የእጁ አከባበድ የሚያስፈራ ሆኖባት ቢሆንም እያደር ስትግባባው ግን ባህሪው ቀላል የሆነ ሰው ነው። ይስቃል
ይጫወታል። ቀልዶቹ ይጥማሉ፡፡ እየሰነበተች ስታየው እንዲያውም በእሱ መኖር ቤቱ ድምቅ ሲል መንፈሷም ዘና እያለ መጣ፡፡ «የኔ ፍልቅልቅ» በማለት እያጫወተም ይበልጥ ያፍለቀልቃት ጀመር።
ዲላ እንደገባች በአፍንጫዋ የገባው አየር በአስቻለው የሰቀቀን ትዝታ የተለወሰው ነበር፡፡ ሆዷን ባር ባር እያለው እንባዋም ያለ ገደብ ፈስሷል። ያም ሆኖም
በተለይ ታፈሡን፣ በልሁን መርዕድንና ትርፌን አግኝታቸው በጋራ አልቅሰውና አንብተው እፎይ ካሉ ወዲህ ከፊል የመንፈስ መረጋጋትም እያደረባት ሄደ። ሸዋዬም ለአባትና ለእናቷ የገባችውን ቃል ያከበረች መሰለች! ሔዋን በማንኛውም ሰዓት ወደ
ታፈሡ ቤት ሄዳ የቱንም ያህል ጊዜ ቆይታ ብትመለስ የት ነበርሽ ምን አስቆየሽ?” አትላትም፡፡ ለሔዋን ከምንም በላይ የተመቻት ይህ የሸዋዬ ቃል ማከበር ነው።
ለአንድ አስራ አምስት ቀናት ያህል በዚህ አይነት እንፃራዊ የመንፈስ
መራጋጋት ውስጥ የሰነበተችው ሔዋን ሦስተኛው ሳምንት ሲጀመር ግን ያ በሸዋዬ ቤት የመኖር ሥጋቷ የልቧን ግድግዳ ማንኳኳት ጀመረ፣ በድሉ አሸናፊ ማንደፍሮን እየተከተለ በዚያ ቤት ውስጥ ገባ ወጣ ማለት ጀመረ፡፡ ማንደፍሮ ስለ ሔዋን ብዙ ነገር ሲነገረው ከርሟል። ከአስቻለው ጋር የነበራት ግንኙነት፣ በድሉ ሔዋንን ለመቅረብ ያደረገዉ ጥረትና የሰጠችው ምላሽ፣ በአሁኑ ወቅት አስቻለው ስለሚገኝበት ሁኔታና ሌሎችም ሁኔታዎች በዝርዝር ተገልፀውለታል፡፡ ወደፈት
የበድሉንና የሔዋንን ጉዳይ እንዲጨርስም አደራ ተጥሎበታል፡፡
ምንም እንኳ በአስቻለውና በሔዋን መካከል የነበረው ግንኙነት በተዛባ ሁኔታ የተነገረው የተሳሳተ መንገድ እንዲከተል የተገፋፋ ቢሆንም ማንደፍሮ ግን
ሆዱን ፍርሃት ፍርሃት ይለው ነበር። ሁኔታው ምንም ይሁን ምን አንድ ነገር ተገንዝቧል። ሔዋን የምታፈቅረው ሰው አላት። ያ ሰው ለጊዜው በአካባቢው ባይኖረም በተስፋ እየጠበቀችው እንደሆነ ልብ ብሏል። የተጣለበት አደራ ደግሞ ይህን ተስፋ በጥሶ ሌላ እንዲቀጥል ነው። እናም ለህሊናው እየከበደው ውስጥ ውስጡን ይጨነቃል።
በሌላ በኩል ደግሞ ጉዳዩ የበድሉ ነው፣ የሥራ ዋስትናው። እንዲሁም የሸዋዬም ጭምር ነው፤ የአፍላ ፍቅረኛው፡፡ በዚህና በመሳሰሉት ሁኔታዎች እየተገፋፋ የተጣለበትን አደራ መወጣት የሚያስችሉ መላዎችን ሲፈጥር ሰንብቷል።አንድ ቀን በተለመደው
ሁኔታ በድሉና ማንደፍሮ በሽዋዬ ቤት ጫት ለመቃም አቅደው ከሸዋዬ ጋር በተደረገ ምክክር ቤቱ በልዩ ሁኔታ ተዘጋጅቷል። ከቀኑ ስምንት ሰዓት አካባቢ ከቤቷ ሲደርሱ ማንደፍሮ ከቤቱ ወለል ላይ ቆሞ ለየት ያለ ሀሳብ አቀረበ
«ዛሬ ከምንም ነገር በፊት አንድን ነገር መፈፀም አለበት።» አለ በዚያ ሰዓት ጓዳ ውስጥ ለነበረችው ሔዋን በሚሰማ ሁኔታ ድምፁን ከፍ በማድረግ።
«ምን?» አለች ሽዋዩ እንደማታውቅ ሆና፡፡
«ሔዋን የለችም እንዴ?» ሲል ማንደፍሮ እንደገና ጠየቃት፡፡
«አለች። ጓዳ ውስጥ ናት፡፡»
«ኑ ሁላችንም ወደ እሷ እንሂድ፡፡» አለና ማንደፍሮ ቀድሞ ወደ ጓዳ
ተራመደ። በድሉና ሸዋዬም ተከተሉት::
«የኔ ፍልቅልቅ» ሲል ጠራት ማንደፍሮ ሔዋንን፡፡
«አቤት» አለች ሔዋን ድንግጥ እያለች፡፡ የዚያን ዕለት ደግሞ የልብ
ህመሟ ዘወር ብሎባት ፍራሽ ላይ ጋደም ብላለች፡፡
«አንድ ጊዜ ብድግ ብትይ!»
ሔዋን በድንጋጤ ዓይኗ ፍጥጥ እንዳለ ተነስታ በዚያው ፍራሻ ላይ
ቆመችና ከፊት ለፊቷ የተኮለኮሉትን ሁሉ ተራ በተራ ታያቸው ጀመር፡፡
«ዛሬ ዛሬ ሁሉም ነገር ገብቶኛል፡፡» አለ ማንደፍሮ ሳቅ ብሎ። “ይህ ሰውዬ!» ሲል ቀጠለ ወደ በድሉ እያመለከተ ወደዚህ ቤት በመጣ ቁጥር ስሜትሽ ለምን እንደሚቀያየር ተረድቻለሁ። ያለ ፍላጎትሽ እየጎነተለ ሲያስቀይምሽ እንደቆየ ገብቶኛል።አሁን አሁን ጥፋት መሆኑን አምኖ ተቀብሏል፡፡ ይቅርታም ሊጠይቅሽ ተዘጋጅቷል።ይቅርታውን ተቀብለሽ እንድትታረቁና ልክ እንደ አንድ ቤተሰብ እየተያየን እንድንኖር ፈልጌለሁ።» አላት።
ሔዋን ያላሰበችውና ያልጠበቀችው አቀራረብ ነበር። ለጊዜው ግን ድንግጥ ተብላ ወደ መሬት ከማቀርቀር በቀር ያለችው ነገር አልነበረም። ማንደፍር ወደ በድሉ ዞር አለና ቆጣ ባለ አነጋገር «በል እግሯ ላይ ውደቅ!» ሲል አዘዘው፡፡ በድሉ ኮቱን ወደ ኋላ መለስ አድርጎ በሔዋን እግር ላይ ወደቀ፡፡
«እልልልል» አለች ሽዋዬ። ማንደፍሮም ብቻውን አጨበጨበ። ለሔዋን ግን ትልቅ የእረብሻና የግርግር ጩኸት ወስጥ የገባች መሰላት፡፡ በድሉ በእግሯ ላይ ወድቆ ለአፍታ ሲቆይ ለመግደርደር ያህል እንኳ በቃ ተነስ አላለችውም። ሲበቃው ራሱ ተነሳ::
«ቀጥል!» አለ ማንደፍሮ ነገሩን በማሟሟቅ ዓይነት ፈንደቅ እያለ፡፡
በድሉ ቀኝ እጁን በኮቱ ኪስ አስገብቶ አንዲት በብልጭልጭ ወረቀት የተጠቀለለች ነገር አወጣ፡፡ ወረቀቱን ቀዶ ጣለ፡፡ ከማይካ የተስራች ነጭ ሙዳይ
ብቅ አለች፡፡ እሷንም ከፈታት። በቅድሚያ ጥጥ መሳይ ነገር ታየ። ቀጠለና በግምት አሥራ አራት ግራም የሚሆን የክርስቶስ የስቅለት ተምሳሌት ማጫዎች
የተንጠለጠለበት የወርቅ ሀብል አወጣና በአንገት ውስጥ ለማስገባት የተዘጋጀ በሚመስል ሁኔታ ከያዘ በኋላ ፈገግ እያለ ማንደፍርን አየት አደረገው::
«ቀጥላ! ምን ታየኛለህ?» አለ ማንደፍሮ፡፡ በድሉ እነዚያን አራት ገጣጣ ጥርሶቹን ገልፈጥ አድርጎ ወደ ሔዋን ጠጋ ሲል ሔዋን ግን ድንገት ጮኸች::
«አልፈልግም!»
«ተይ እንጂ የኔ ፍልቅልቅ አለ ማንደፍሮ እሱም ደንግጥ አያለ፡፡
«እምቢ! አልፈልግም» ሔዋን አሁንም፡፡ ፊቷን ክስክስ አድርጋ በድሉን በጥላቻ ዓይን ታየው ጀመር።
«አይ እንግዲህ!" አለና ማንደፍሮ ሔዋንን ወደ ራሱ ጎተት አደረገና ሁለት እጆቿን ያዝ በማድረግ «አጥልቅላት » አለው በድሉን።
በድሉ የሔዋን እጆቿ እንደተያዙለት ሀብሉን በአንገቷ ላይ የመጣል ያህል አስገብቶ ወደ ኋላው ፈግፈግ አለ።ማንደፍሮና ሸዋዬ አጨበጨቡ፡፡ ማንደፍሮ በሔዋን አንገት ላይ ያረፊቱን ሀብል በእጁ ያዝ አድርጎ ወርቁንም ሔዋንንም
ተራ በተራ እየተመለከተ«አንቺን ለመሰለች ቆንጆ የሚገባ ልዩ ስጦታ!» አላት።
ሔዋን ግን ዓይኖቿ በእንባ ሞሉ፡፡ ግንባሯን በከንዷ ጋርዳ ወደ መሬት
በማቀርቀር ታለቅስ ጀመር።
«ሔዋን እንዳንቀያየም» አላት ማንደፍሮ። ሔዋን መልስ አልሰጠችውም፡፡አሁንም አጎንብሳ ታለቅስ ጀመር፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...አስራ ስድስት ወራትን በክብረ መንግስት አሳልፋ ወዴ ዲላ የተመስሰችው ሔዋን ብዙ አካባቢያዊ ለውጥ ሊገጥማት እንደሚችል ገምታ ነበር፡፡ነገር ግን ከሽዋዬ ቤት በዘመናዊ የቤት እቃዎች መሞላትና ወንድ ወንድ ከመሽተት በቀር ሁሉም ነገር ያው ነው።በሸዋዬ ቤት የወንድ ኮትና ጃኬት ግድግዳ ላይ ተሰቅለው የወንድ ጫማ በአልጋ ሥር ተቀምጦና ትልቅ የወንድ ፎቶ ግራፍ ብፌ ላይ ስታይ ሸዋዬ ባል ያገባች መስሎ ተሰማት። በእርግጥም “ማንዴፍሮን ገና የገባች እለት ተዋወቀችው።
ማንደፍሮ መልኩ ጥቁር ፊቱ ጉሩድረድ ያለና አካሉ ግዙፍ
ከመሆኑ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ሲጨብጣት የእጁ አከባበድ የሚያስፈራ ሆኖባት ቢሆንም እያደር ስትግባባው ግን ባህሪው ቀላል የሆነ ሰው ነው። ይስቃል
ይጫወታል። ቀልዶቹ ይጥማሉ፡፡ እየሰነበተች ስታየው እንዲያውም በእሱ መኖር ቤቱ ድምቅ ሲል መንፈሷም ዘና እያለ መጣ፡፡ «የኔ ፍልቅልቅ» በማለት እያጫወተም ይበልጥ ያፍለቀልቃት ጀመር።
ዲላ እንደገባች በአፍንጫዋ የገባው አየር በአስቻለው የሰቀቀን ትዝታ የተለወሰው ነበር፡፡ ሆዷን ባር ባር እያለው እንባዋም ያለ ገደብ ፈስሷል። ያም ሆኖም
በተለይ ታፈሡን፣ በልሁን መርዕድንና ትርፌን አግኝታቸው በጋራ አልቅሰውና አንብተው እፎይ ካሉ ወዲህ ከፊል የመንፈስ መረጋጋትም እያደረባት ሄደ። ሸዋዬም ለአባትና ለእናቷ የገባችውን ቃል ያከበረች መሰለች! ሔዋን በማንኛውም ሰዓት ወደ
ታፈሡ ቤት ሄዳ የቱንም ያህል ጊዜ ቆይታ ብትመለስ የት ነበርሽ ምን አስቆየሽ?” አትላትም፡፡ ለሔዋን ከምንም በላይ የተመቻት ይህ የሸዋዬ ቃል ማከበር ነው።
ለአንድ አስራ አምስት ቀናት ያህል በዚህ አይነት እንፃራዊ የመንፈስ
መራጋጋት ውስጥ የሰነበተችው ሔዋን ሦስተኛው ሳምንት ሲጀመር ግን ያ በሸዋዬ ቤት የመኖር ሥጋቷ የልቧን ግድግዳ ማንኳኳት ጀመረ፣ በድሉ አሸናፊ ማንደፍሮን እየተከተለ በዚያ ቤት ውስጥ ገባ ወጣ ማለት ጀመረ፡፡ ማንደፍሮ ስለ ሔዋን ብዙ ነገር ሲነገረው ከርሟል። ከአስቻለው ጋር የነበራት ግንኙነት፣ በድሉ ሔዋንን ለመቅረብ ያደረገዉ ጥረትና የሰጠችው ምላሽ፣ በአሁኑ ወቅት አስቻለው ስለሚገኝበት ሁኔታና ሌሎችም ሁኔታዎች በዝርዝር ተገልፀውለታል፡፡ ወደፈት
የበድሉንና የሔዋንን ጉዳይ እንዲጨርስም አደራ ተጥሎበታል፡፡
ምንም እንኳ በአስቻለውና በሔዋን መካከል የነበረው ግንኙነት በተዛባ ሁኔታ የተነገረው የተሳሳተ መንገድ እንዲከተል የተገፋፋ ቢሆንም ማንደፍሮ ግን
ሆዱን ፍርሃት ፍርሃት ይለው ነበር። ሁኔታው ምንም ይሁን ምን አንድ ነገር ተገንዝቧል። ሔዋን የምታፈቅረው ሰው አላት። ያ ሰው ለጊዜው በአካባቢው ባይኖረም በተስፋ እየጠበቀችው እንደሆነ ልብ ብሏል። የተጣለበት አደራ ደግሞ ይህን ተስፋ በጥሶ ሌላ እንዲቀጥል ነው። እናም ለህሊናው እየከበደው ውስጥ ውስጡን ይጨነቃል።
በሌላ በኩል ደግሞ ጉዳዩ የበድሉ ነው፣ የሥራ ዋስትናው። እንዲሁም የሸዋዬም ጭምር ነው፤ የአፍላ ፍቅረኛው፡፡ በዚህና በመሳሰሉት ሁኔታዎች እየተገፋፋ የተጣለበትን አደራ መወጣት የሚያስችሉ መላዎችን ሲፈጥር ሰንብቷል።አንድ ቀን በተለመደው
ሁኔታ በድሉና ማንደፍሮ በሽዋዬ ቤት ጫት ለመቃም አቅደው ከሸዋዬ ጋር በተደረገ ምክክር ቤቱ በልዩ ሁኔታ ተዘጋጅቷል። ከቀኑ ስምንት ሰዓት አካባቢ ከቤቷ ሲደርሱ ማንደፍሮ ከቤቱ ወለል ላይ ቆሞ ለየት ያለ ሀሳብ አቀረበ
«ዛሬ ከምንም ነገር በፊት አንድን ነገር መፈፀም አለበት።» አለ በዚያ ሰዓት ጓዳ ውስጥ ለነበረችው ሔዋን በሚሰማ ሁኔታ ድምፁን ከፍ በማድረግ።
«ምን?» አለች ሽዋዩ እንደማታውቅ ሆና፡፡
«ሔዋን የለችም እንዴ?» ሲል ማንደፍሮ እንደገና ጠየቃት፡፡
«አለች። ጓዳ ውስጥ ናት፡፡»
«ኑ ሁላችንም ወደ እሷ እንሂድ፡፡» አለና ማንደፍሮ ቀድሞ ወደ ጓዳ
ተራመደ። በድሉና ሸዋዬም ተከተሉት::
«የኔ ፍልቅልቅ» ሲል ጠራት ማንደፍሮ ሔዋንን፡፡
«አቤት» አለች ሔዋን ድንግጥ እያለች፡፡ የዚያን ዕለት ደግሞ የልብ
ህመሟ ዘወር ብሎባት ፍራሽ ላይ ጋደም ብላለች፡፡
«አንድ ጊዜ ብድግ ብትይ!»
ሔዋን በድንጋጤ ዓይኗ ፍጥጥ እንዳለ ተነስታ በዚያው ፍራሻ ላይ
ቆመችና ከፊት ለፊቷ የተኮለኮሉትን ሁሉ ተራ በተራ ታያቸው ጀመር፡፡
«ዛሬ ዛሬ ሁሉም ነገር ገብቶኛል፡፡» አለ ማንደፍሮ ሳቅ ብሎ። “ይህ ሰውዬ!» ሲል ቀጠለ ወደ በድሉ እያመለከተ ወደዚህ ቤት በመጣ ቁጥር ስሜትሽ ለምን እንደሚቀያየር ተረድቻለሁ። ያለ ፍላጎትሽ እየጎነተለ ሲያስቀይምሽ እንደቆየ ገብቶኛል።አሁን አሁን ጥፋት መሆኑን አምኖ ተቀብሏል፡፡ ይቅርታም ሊጠይቅሽ ተዘጋጅቷል።ይቅርታውን ተቀብለሽ እንድትታረቁና ልክ እንደ አንድ ቤተሰብ እየተያየን እንድንኖር ፈልጌለሁ።» አላት።
ሔዋን ያላሰበችውና ያልጠበቀችው አቀራረብ ነበር። ለጊዜው ግን ድንግጥ ተብላ ወደ መሬት ከማቀርቀር በቀር ያለችው ነገር አልነበረም። ማንደፍር ወደ በድሉ ዞር አለና ቆጣ ባለ አነጋገር «በል እግሯ ላይ ውደቅ!» ሲል አዘዘው፡፡ በድሉ ኮቱን ወደ ኋላ መለስ አድርጎ በሔዋን እግር ላይ ወደቀ፡፡
«እልልልል» አለች ሽዋዬ። ማንደፍሮም ብቻውን አጨበጨበ። ለሔዋን ግን ትልቅ የእረብሻና የግርግር ጩኸት ወስጥ የገባች መሰላት፡፡ በድሉ በእግሯ ላይ ወድቆ ለአፍታ ሲቆይ ለመግደርደር ያህል እንኳ በቃ ተነስ አላለችውም። ሲበቃው ራሱ ተነሳ::
«ቀጥል!» አለ ማንደፍሮ ነገሩን በማሟሟቅ ዓይነት ፈንደቅ እያለ፡፡
በድሉ ቀኝ እጁን በኮቱ ኪስ አስገብቶ አንዲት በብልጭልጭ ወረቀት የተጠቀለለች ነገር አወጣ፡፡ ወረቀቱን ቀዶ ጣለ፡፡ ከማይካ የተስራች ነጭ ሙዳይ
ብቅ አለች፡፡ እሷንም ከፈታት። በቅድሚያ ጥጥ መሳይ ነገር ታየ። ቀጠለና በግምት አሥራ አራት ግራም የሚሆን የክርስቶስ የስቅለት ተምሳሌት ማጫዎች
የተንጠለጠለበት የወርቅ ሀብል አወጣና በአንገት ውስጥ ለማስገባት የተዘጋጀ በሚመስል ሁኔታ ከያዘ በኋላ ፈገግ እያለ ማንደፍርን አየት አደረገው::
«ቀጥላ! ምን ታየኛለህ?» አለ ማንደፍሮ፡፡ በድሉ እነዚያን አራት ገጣጣ ጥርሶቹን ገልፈጥ አድርጎ ወደ ሔዋን ጠጋ ሲል ሔዋን ግን ድንገት ጮኸች::
«አልፈልግም!»
«ተይ እንጂ የኔ ፍልቅልቅ አለ ማንደፍሮ እሱም ደንግጥ አያለ፡፡
«እምቢ! አልፈልግም» ሔዋን አሁንም፡፡ ፊቷን ክስክስ አድርጋ በድሉን በጥላቻ ዓይን ታየው ጀመር።
«አይ እንግዲህ!" አለና ማንደፍሮ ሔዋንን ወደ ራሱ ጎተት አደረገና ሁለት እጆቿን ያዝ በማድረግ «አጥልቅላት » አለው በድሉን።
በድሉ የሔዋን እጆቿ እንደተያዙለት ሀብሉን በአንገቷ ላይ የመጣል ያህል አስገብቶ ወደ ኋላው ፈግፈግ አለ።ማንደፍሮና ሸዋዬ አጨበጨቡ፡፡ ማንደፍሮ በሔዋን አንገት ላይ ያረፊቱን ሀብል በእጁ ያዝ አድርጎ ወርቁንም ሔዋንንም
ተራ በተራ እየተመለከተ«አንቺን ለመሰለች ቆንጆ የሚገባ ልዩ ስጦታ!» አላት።
ሔዋን ግን ዓይኖቿ በእንባ ሞሉ፡፡ ግንባሯን በከንዷ ጋርዳ ወደ መሬት
በማቀርቀር ታለቅስ ጀመር።
«ሔዋን እንዳንቀያየም» አላት ማንደፍሮ። ሔዋን መልስ አልሰጠችውም፡፡አሁንም አጎንብሳ ታለቅስ ጀመር፡፡
👍8😱1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
መጨረሻው እንደ አጀማመሩ አልሆነም
ጊዜ እያለፈ ሲሄድ ኮዜት ከሀዘንዋ እያገገመች መጣች:: የጊዜው
መርዘም፣ ወጣትነትዋ፣ የአባትዋ ፍቅርና የአካባቢዋ ማማር ቀስ በቀስ ሀዘንዋን እንድትረሳ ረዱዋት:: ቀን አልፎ ቀን ሲተካ፧ ወር አልፎ ወር ሲተካ የፍቅርዋ ሙላት በየቀኑ በጠብታዎች እየጎደለ ሄደ:: ወላፈኑ በርዶ
ወደ መጥፋት ተቃረበ፡፡ ሆኖም ረመጠ ጨርሶ ስላልጠፋ ማቃጠሉ፣ ማስጨነቁና ማሰቃየቱን ትቶአታል እንጂ ጨርሶ አልተወገደም::
አንድ ቀን በድንገት ማሪየስ ታወሳት:: «ምን!» አለች:: «ደግሞ ከየት መጣ? ረስቼው አልነበረም እንዴ!» በማሪየስ በኩል ደግሞ «ምነው ከመሞቴ በፊት አንድ ጊዜ ብቻ ባየኋት!» የሚልበት ወቅት ነበር፡፡
የማን ጥፋት ነው? የማንም::
አንዳንድ ሰው ከገባበት ወጥመድ በቀላሉ መውጣት አይችልም፡፡
ማሪየስ የዚያ ዓይነት ሰው ነው:: ከደረሰበት ሀዘን እንደ ኮዜት በቀላሉ ሊላቀቅ አልቻለም:: ሀዘን ውስጥ ገብቶ እዚያው ነው ተዘፍቆ የቀረው።
አንድ አጋጣሚ ይከተላል፡፡ በትልቁ በር በኩል ከአንድ ግቢ ውስጥ
አንድ እንደ መቀመጫ የሚያገለግል ጥርብ ድንጋይ ነበር፡፡ እንደ ሴት ጎፈሬ
የተከረከመ የዛፍ አጥር በአጠገቡ ስለነበር ማንም ሰው በመንገድ ሲያልፍ ወደ ውስጥ ማየት አይችልም፡፡ ነገር ግን ከውስጥ ያለ ሰው ከፈለገ እጁን
በአጥሩ ቀዳዳ በማበጀት አሾልኮ በውጭ የሚያልፈውን ሰው ማየትና መጨበጥ ይችላል፡፡
አንድ ቀን ማታ ዣን ቫልዣ ወደ ውጭ ወጥቶ ነበር፡፡ አየሩ ጥሩ
ስለነበር መሸት ሲል ኮሴት ከዚያ ድንጋይ ላይ ተክዛ ቁጭ ብላለች፡፡ የጥንት ትዝታዋ ተቀሰቀሰባት፡፡ ጊዜው ጨለምለም ብሏል፡፡ የእናትዋ መንፈስ ከዚያ ያለ መሰላት፡፡ ከተቀመጠችበት ብድግ ብላ ሄደች::
ቀደም ሲል ዝናብ ዘንቦ ስለነበር ሳሩ ያቀዘቅዛል፡፡ «ይህስ ጉንፋን
ያሲዛል ፧ ብቀመጥ ይሻላል» ብላ ወደ ድንጋዩ መቀመጫ ስትመለስ
መቀመጫው ላይ አንድ ነገር አየች:: አንድ እጥፍጥፍ ብላ የተጠቀለለ ነገር ከትንሽ ጠጠር ጋር ተያይዟል:: ከመቀመጫው ተነስታ ስትሄድ ከዚያ
አልነበረም::
ኮዜት ገርሞኣት «ምንድነው እሱ?» ስትል ራስዋን ጠየቀች:: መቼም ሰው ካላስቀመጠው በራሱ ኃይል ሊመጣ እንደማይችል ተረዳች:: ፍርሃት፣ፍርሃት፣ አላት፡፡ ድንጋዩን መንካት አልደፈረችም:: ወደኋላ ሳታይ ቤትዋ ሮጠች፡፡ ቤትዋ ከገባች በኋላ በርና መስኮት ዘጋጋች፡፡ መቀርቀሪያዎቹን
ሁሉ ቀረቀረች:: ከጥቂት ጊዜ እረፍት በኋላ ‹አባባ ተመልሷል እንዴ?»
ስትል ቱሴይን ጠየቀቻት::
«ኧረ አልተመለሰም» አለቻት::
ክፍሎቹ በሙሉ ተዘግተው እንደሆነና ከቤት ውስጥ ሰው እንዳለ እንድታይ ቱሴይን አዘዘቻት:: አጎንብሳ ከአልጋዋ ስር እንዲሁም ቁም ሣጥንዋን ከፍታ ሰው እንዳለና እንደሌለ አጣራች:: ከተኛች በኋላ ያ ያየችው
ጠጠር ተራራ አክሉ በውስጡ ዋሻ እንዳለበት አለመች::
ጠዋት ፀሐይ ስትወጣና ጨለማ ለብርሃን ቦታዋን ስትለቅ ማታ
እንደዚያ ያስፈራሩን ነገሮች እንደሚያስቁን ይታወቃል:: ኮዜት ስትነቃ ማታ እንደዚያ ያስፈራት ነገር ቅዠት መስሎ ታያት:: ስለምን ነበር የምቃዠው?» ስትል ራስዋን ጠየቀች::
ልብስዋን ለብሳ ወደ አትክልቱ ቦታ ሄደች:: ስትፈራኛ ስትቸር ማታ
ተቀምጣበት ወደነበረው የድንጋይ መቀመጫ ሄደች:: የተጠቀለለው ነገር ከዚያው ቁጭ ብሉአል:: በመጀመሪያ ትንሽ ፈርታ ነበር:: በኋላ ግን ፍርሃቱ ተወገደላት:: ደግሞም በጨለማ የሸሸነወ ነገር በብርሃን እንጓጓለታለንና ምን እንደሆነ ለማየት ቸኩለች፡፡
«አይ ምን አስፈራኝ፤ ፈትቼ ልየዋ» አለች ለራስዋ:: የተጠቀለለውን
ነገር አንስታ ከፈታታችው በኋላ አብሮ ታስሮ የነበረውን ድንጋይ ጣለችው::
አድራሻ ያልተጻፈበትና በውስጠ ወረቀት ያለው እንደ ደብዳቤ ያለ ነገር መሆኑን ተገነዘበች:: ወረቀቱን ከውስጡ ሳታወጣ አገላብጣ አየችው:: አሁን መፍራትዋ ቀርቶ «ከውስጡ ምን አለ» በማለት በመጓጓት ለማወቅ ፈለገች::
ፖስታውን ከፍታ ከውስጡ የነበረውን ወረቀት አወጣች:: በጥሩ የእጅ ጽሑፍ እንደ ጥቅስ ያሉ ነገሮች ተጽፎበታል፡፡ የገጹ ብዛት ከአንድ በላይ ነው:: እያንዳንዱ ገጽ ላይ ቁጥር ተጽፎበታል:: ሆኖም እያንዳንዱ ገጽ ሞልቶ የተጻፈበት ሳይሆን መሐሉ ላይ ብቻ ነው የተጻፈው:: የመጻፊያ ቦታ እያለ ወደ ሚቀጥለው ገጽ ይዞራል::
ፊርማ ወይም ስም ካለበት በሚል በችኮላ ፈለገች፤ ግን አላገኘችም::
ለማነው የተጻፈው? ለራስዋ እንደሆነ ጠረጠረች፡፡ ምክንያቱም እርስዋ ተቀምጣበት ከነበረው ሥፍራ ነው የተገኘው፡፡ ታዲያ ማነው ጸሐፊው?
ግራ ገባት:: በመገላመጥ አካባቢዋን ቃኘች፡፡ ከርግቦች በስተቀር ምንም ነገር የለም:: ወረቀቱን ማንበብዋን ቀጠለች::
ቀጥሎ የተመለከተው ነበር በወረቀቶቹ ላይ የተጻፈው::
«ዓለም ተጨብጣ አንዲት ትንሽ ነገር ስትሆን፧ አንዲት ትንሽ ነገር
ደግሞ ተነፍታ እግዚአብሔርን ስታክል ፍቅር ትባላለች፡፡ ፍቅር ነፍስን ትመስላለች፤ አፈጣጠራቸው አንድ ነው፡፡ እንደ ነፍስ የመንፈስ ቅዱስ
ብልጭታ ኣለባት፡፡ እንደ ነፍስ ግን አትገድፍም፣ አትነጣጠልም
አትጠፋም፡፡ የእሳት ረመጥ ስትሆን በውስጣችን አለች፤ ዘላለማዊ ናት..ማለቂያና መደምደሚያ የላትም፡፡ ረመጥዋ በምንም ነገር አይጠፋም::
ከአጥንታችን ውስጥ እንኳን ገብታ ስትፋጅ ይሰማናል:: እንዲሁም ከሰማየ ሰማያት ወርዳ፧ ከአካል ውስጥ ዘልቃ ትገባለች፡፡ ሆኖም ስታንፀባርቅ አካላችን ውስጥ በጉልህ እናያታለን፡፡
«ፍቅር! አድናቆት! የሁለት የሚግባቡ አእምሮዎች ፣ የሁለት
የሚወሳሰቡ ልቦች፣ የሁለት አካልን ሰነጣጥቀው የሚገቡ ዓይኖች ያላት ብርሃን! አንቺ ደስታ ወደ እኔ ትመጪያለሽ ወይስ አትመጪም! ፍቅር
ብቸኝነትን ሲያጠቃ አብሮ የሚጓዝ፤ የሚንሸራሽር! የተባረኩ ቀኖች! የሰዎችን እድል፣ የሰዎችን እጣ ፈንታ ለመካፈል መላእክት ከሰማየ ሰማያት ወርደው
በዚህች ምድር ሲኖሩ በሕልሜ ያየኋቸው ነው የመሰለኝ፡፡ አይ ፍቅር!
«ዘላለማዊ ከማድረግ በስተቀር ማንም ከሁለት ከሚዋደዱ ፍጡሮች ደስታ ላይ የሚጨምረው ነገር የለም፡፡ በእርግጥ የፍቅር ዘላለማዊነት
ከፍቅር ዘመን በኋላ የሚታከል ነው:: ግን የፍቅርን መጠን፣ የፍቅርን ግለት ለማሳደግ ከፍቅረኞቹ ከራሳቸው በስተቀር ማንም ሊያስቀረው አይቻለውም፡፡ ፍቅር የሰዎች ፍጹምነት ይታይበታል፡፡
«ከዋክብትን የምናይበት ምክንያት ሁለት ነው:: ይኸውም
ስለሚያብረቀርቁ ወይም ምንነታቸውን ስለማናውቅ! ከጎናችን ግን ከከዋክብት
ይበልጥ ምሥጢሩ ያልታወቀ የላመ፣ የለሰለሰና የሚያንፀባርቅ ፍጡር አለ... ሴት::
«ድንጋይ ከሆንክ ትልቅ ድንጋይ ሁን፤ የዛፍና የቅጠላቅጠል ዘር
ከሆንክ ስሜት፤ ሰው ከሆንክ ደግሞ ፍቅር ይኑርህ::
«ወደ ሽርሽሩ ቦታ ትመጣለች? የለም ጌታዬ! በየሳምንቱ እሑድ ወደ ቤተክርስቲያን ትመጣ የለ? የለም መምጣቱን ትታለች:: አሁን ከዚሁ ቤት ውስጥ ነው የምትኖረው? የለም ለቅቃለች፡፡ አሁን ከየት ሰፈር ገባች?
አድራሻዋ አይታወቅም፡፡ ስትሄድ አልተናገረችም? አልነገረችንም:: ምን ዓይነት የተዳፈነ ጨለማ ነው እባካችሁ የአንድን ነፍስ አድራሻ አለማወቅ!
በፍቅር ምክንያት የምትጨነቅ፣ የምትሰቃይ ነፍስ! አሁንም ውደድ፤ በይበልጥ አፍቅር፡፡ በፍቅር መሞት ማለት በፍቅር መኖር ማለት ነውና፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
መጨረሻው እንደ አጀማመሩ አልሆነም
ጊዜ እያለፈ ሲሄድ ኮዜት ከሀዘንዋ እያገገመች መጣች:: የጊዜው
መርዘም፣ ወጣትነትዋ፣ የአባትዋ ፍቅርና የአካባቢዋ ማማር ቀስ በቀስ ሀዘንዋን እንድትረሳ ረዱዋት:: ቀን አልፎ ቀን ሲተካ፧ ወር አልፎ ወር ሲተካ የፍቅርዋ ሙላት በየቀኑ በጠብታዎች እየጎደለ ሄደ:: ወላፈኑ በርዶ
ወደ መጥፋት ተቃረበ፡፡ ሆኖም ረመጠ ጨርሶ ስላልጠፋ ማቃጠሉ፣ ማስጨነቁና ማሰቃየቱን ትቶአታል እንጂ ጨርሶ አልተወገደም::
አንድ ቀን በድንገት ማሪየስ ታወሳት:: «ምን!» አለች:: «ደግሞ ከየት መጣ? ረስቼው አልነበረም እንዴ!» በማሪየስ በኩል ደግሞ «ምነው ከመሞቴ በፊት አንድ ጊዜ ብቻ ባየኋት!» የሚልበት ወቅት ነበር፡፡
የማን ጥፋት ነው? የማንም::
አንዳንድ ሰው ከገባበት ወጥመድ በቀላሉ መውጣት አይችልም፡፡
ማሪየስ የዚያ ዓይነት ሰው ነው:: ከደረሰበት ሀዘን እንደ ኮዜት በቀላሉ ሊላቀቅ አልቻለም:: ሀዘን ውስጥ ገብቶ እዚያው ነው ተዘፍቆ የቀረው።
አንድ አጋጣሚ ይከተላል፡፡ በትልቁ በር በኩል ከአንድ ግቢ ውስጥ
አንድ እንደ መቀመጫ የሚያገለግል ጥርብ ድንጋይ ነበር፡፡ እንደ ሴት ጎፈሬ
የተከረከመ የዛፍ አጥር በአጠገቡ ስለነበር ማንም ሰው በመንገድ ሲያልፍ ወደ ውስጥ ማየት አይችልም፡፡ ነገር ግን ከውስጥ ያለ ሰው ከፈለገ እጁን
በአጥሩ ቀዳዳ በማበጀት አሾልኮ በውጭ የሚያልፈውን ሰው ማየትና መጨበጥ ይችላል፡፡
አንድ ቀን ማታ ዣን ቫልዣ ወደ ውጭ ወጥቶ ነበር፡፡ አየሩ ጥሩ
ስለነበር መሸት ሲል ኮሴት ከዚያ ድንጋይ ላይ ተክዛ ቁጭ ብላለች፡፡ የጥንት ትዝታዋ ተቀሰቀሰባት፡፡ ጊዜው ጨለምለም ብሏል፡፡ የእናትዋ መንፈስ ከዚያ ያለ መሰላት፡፡ ከተቀመጠችበት ብድግ ብላ ሄደች::
ቀደም ሲል ዝናብ ዘንቦ ስለነበር ሳሩ ያቀዘቅዛል፡፡ «ይህስ ጉንፋን
ያሲዛል ፧ ብቀመጥ ይሻላል» ብላ ወደ ድንጋዩ መቀመጫ ስትመለስ
መቀመጫው ላይ አንድ ነገር አየች:: አንድ እጥፍጥፍ ብላ የተጠቀለለ ነገር ከትንሽ ጠጠር ጋር ተያይዟል:: ከመቀመጫው ተነስታ ስትሄድ ከዚያ
አልነበረም::
ኮዜት ገርሞኣት «ምንድነው እሱ?» ስትል ራስዋን ጠየቀች:: መቼም ሰው ካላስቀመጠው በራሱ ኃይል ሊመጣ እንደማይችል ተረዳች:: ፍርሃት፣ፍርሃት፣ አላት፡፡ ድንጋዩን መንካት አልደፈረችም:: ወደኋላ ሳታይ ቤትዋ ሮጠች፡፡ ቤትዋ ከገባች በኋላ በርና መስኮት ዘጋጋች፡፡ መቀርቀሪያዎቹን
ሁሉ ቀረቀረች:: ከጥቂት ጊዜ እረፍት በኋላ ‹አባባ ተመልሷል እንዴ?»
ስትል ቱሴይን ጠየቀቻት::
«ኧረ አልተመለሰም» አለቻት::
ክፍሎቹ በሙሉ ተዘግተው እንደሆነና ከቤት ውስጥ ሰው እንዳለ እንድታይ ቱሴይን አዘዘቻት:: አጎንብሳ ከአልጋዋ ስር እንዲሁም ቁም ሣጥንዋን ከፍታ ሰው እንዳለና እንደሌለ አጣራች:: ከተኛች በኋላ ያ ያየችው
ጠጠር ተራራ አክሉ በውስጡ ዋሻ እንዳለበት አለመች::
ጠዋት ፀሐይ ስትወጣና ጨለማ ለብርሃን ቦታዋን ስትለቅ ማታ
እንደዚያ ያስፈራሩን ነገሮች እንደሚያስቁን ይታወቃል:: ኮዜት ስትነቃ ማታ እንደዚያ ያስፈራት ነገር ቅዠት መስሎ ታያት:: ስለምን ነበር የምቃዠው?» ስትል ራስዋን ጠየቀች::
ልብስዋን ለብሳ ወደ አትክልቱ ቦታ ሄደች:: ስትፈራኛ ስትቸር ማታ
ተቀምጣበት ወደነበረው የድንጋይ መቀመጫ ሄደች:: የተጠቀለለው ነገር ከዚያው ቁጭ ብሉአል:: በመጀመሪያ ትንሽ ፈርታ ነበር:: በኋላ ግን ፍርሃቱ ተወገደላት:: ደግሞም በጨለማ የሸሸነወ ነገር በብርሃን እንጓጓለታለንና ምን እንደሆነ ለማየት ቸኩለች፡፡
«አይ ምን አስፈራኝ፤ ፈትቼ ልየዋ» አለች ለራስዋ:: የተጠቀለለውን
ነገር አንስታ ከፈታታችው በኋላ አብሮ ታስሮ የነበረውን ድንጋይ ጣለችው::
አድራሻ ያልተጻፈበትና በውስጠ ወረቀት ያለው እንደ ደብዳቤ ያለ ነገር መሆኑን ተገነዘበች:: ወረቀቱን ከውስጡ ሳታወጣ አገላብጣ አየችው:: አሁን መፍራትዋ ቀርቶ «ከውስጡ ምን አለ» በማለት በመጓጓት ለማወቅ ፈለገች::
ፖስታውን ከፍታ ከውስጡ የነበረውን ወረቀት አወጣች:: በጥሩ የእጅ ጽሑፍ እንደ ጥቅስ ያሉ ነገሮች ተጽፎበታል፡፡ የገጹ ብዛት ከአንድ በላይ ነው:: እያንዳንዱ ገጽ ላይ ቁጥር ተጽፎበታል:: ሆኖም እያንዳንዱ ገጽ ሞልቶ የተጻፈበት ሳይሆን መሐሉ ላይ ብቻ ነው የተጻፈው:: የመጻፊያ ቦታ እያለ ወደ ሚቀጥለው ገጽ ይዞራል::
ፊርማ ወይም ስም ካለበት በሚል በችኮላ ፈለገች፤ ግን አላገኘችም::
ለማነው የተጻፈው? ለራስዋ እንደሆነ ጠረጠረች፡፡ ምክንያቱም እርስዋ ተቀምጣበት ከነበረው ሥፍራ ነው የተገኘው፡፡ ታዲያ ማነው ጸሐፊው?
ግራ ገባት:: በመገላመጥ አካባቢዋን ቃኘች፡፡ ከርግቦች በስተቀር ምንም ነገር የለም:: ወረቀቱን ማንበብዋን ቀጠለች::
ቀጥሎ የተመለከተው ነበር በወረቀቶቹ ላይ የተጻፈው::
«ዓለም ተጨብጣ አንዲት ትንሽ ነገር ስትሆን፧ አንዲት ትንሽ ነገር
ደግሞ ተነፍታ እግዚአብሔርን ስታክል ፍቅር ትባላለች፡፡ ፍቅር ነፍስን ትመስላለች፤ አፈጣጠራቸው አንድ ነው፡፡ እንደ ነፍስ የመንፈስ ቅዱስ
ብልጭታ ኣለባት፡፡ እንደ ነፍስ ግን አትገድፍም፣ አትነጣጠልም
አትጠፋም፡፡ የእሳት ረመጥ ስትሆን በውስጣችን አለች፤ ዘላለማዊ ናት..ማለቂያና መደምደሚያ የላትም፡፡ ረመጥዋ በምንም ነገር አይጠፋም::
ከአጥንታችን ውስጥ እንኳን ገብታ ስትፋጅ ይሰማናል:: እንዲሁም ከሰማየ ሰማያት ወርዳ፧ ከአካል ውስጥ ዘልቃ ትገባለች፡፡ ሆኖም ስታንፀባርቅ አካላችን ውስጥ በጉልህ እናያታለን፡፡
«ፍቅር! አድናቆት! የሁለት የሚግባቡ አእምሮዎች ፣ የሁለት
የሚወሳሰቡ ልቦች፣ የሁለት አካልን ሰነጣጥቀው የሚገቡ ዓይኖች ያላት ብርሃን! አንቺ ደስታ ወደ እኔ ትመጪያለሽ ወይስ አትመጪም! ፍቅር
ብቸኝነትን ሲያጠቃ አብሮ የሚጓዝ፤ የሚንሸራሽር! የተባረኩ ቀኖች! የሰዎችን እድል፣ የሰዎችን እጣ ፈንታ ለመካፈል መላእክት ከሰማየ ሰማያት ወርደው
በዚህች ምድር ሲኖሩ በሕልሜ ያየኋቸው ነው የመሰለኝ፡፡ አይ ፍቅር!
«ዘላለማዊ ከማድረግ በስተቀር ማንም ከሁለት ከሚዋደዱ ፍጡሮች ደስታ ላይ የሚጨምረው ነገር የለም፡፡ በእርግጥ የፍቅር ዘላለማዊነት
ከፍቅር ዘመን በኋላ የሚታከል ነው:: ግን የፍቅርን መጠን፣ የፍቅርን ግለት ለማሳደግ ከፍቅረኞቹ ከራሳቸው በስተቀር ማንም ሊያስቀረው አይቻለውም፡፡ ፍቅር የሰዎች ፍጹምነት ይታይበታል፡፡
«ከዋክብትን የምናይበት ምክንያት ሁለት ነው:: ይኸውም
ስለሚያብረቀርቁ ወይም ምንነታቸውን ስለማናውቅ! ከጎናችን ግን ከከዋክብት
ይበልጥ ምሥጢሩ ያልታወቀ የላመ፣ የለሰለሰና የሚያንፀባርቅ ፍጡር አለ... ሴት::
«ድንጋይ ከሆንክ ትልቅ ድንጋይ ሁን፤ የዛፍና የቅጠላቅጠል ዘር
ከሆንክ ስሜት፤ ሰው ከሆንክ ደግሞ ፍቅር ይኑርህ::
«ወደ ሽርሽሩ ቦታ ትመጣለች? የለም ጌታዬ! በየሳምንቱ እሑድ ወደ ቤተክርስቲያን ትመጣ የለ? የለም መምጣቱን ትታለች:: አሁን ከዚሁ ቤት ውስጥ ነው የምትኖረው? የለም ለቅቃለች፡፡ አሁን ከየት ሰፈር ገባች?
አድራሻዋ አይታወቅም፡፡ ስትሄድ አልተናገረችም? አልነገረችንም:: ምን ዓይነት የተዳፈነ ጨለማ ነው እባካችሁ የአንድን ነፍስ አድራሻ አለማወቅ!
በፍቅር ምክንያት የምትጨነቅ፣ የምትሰቃይ ነፍስ! አሁንም ውደድ፤ በይበልጥ አፍቅር፡፡ በፍቅር መሞት ማለት በፍቅር መኖር ማለት ነውና፡፡
👍17😱1
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
ቀኖቹን ሁላ ሰማያዊ ስትቀባ አንዱን ለጥቁር ተወው።
በማንኛውም ቀን ልንሄድ ነው፡፡ እናታችን በምሽት ወጣ እላለሁ እንዳለች፣
መጓጓዝ የሚችሉ ውድ ንብረቶቿም ከእሷ ይወጣሉ። ወደ ግላድስተን
አንመለስም እዚያ አሁን ክረምት ገብቷል። ገና እስከ ግንቦት ይቆያል።ሰርከስ የሚሰሩ ሰዎች ወደሚኖሩበት ወደ ሳራሶታ እንሄዳለን፡ እዚያ ያሉ
ሰዎች ለየት ያለ የኋላ ታሪክ ላላቸው ሰዎች ደግነት በማሳየት የሚታወቁ
ናቸው ክሪስና እኔ ከፍ ያለ ቦታ ማለትም ጣራ ላይ ስለኖርን ምሰሶዎቹ
ላይ ብዙ ገመዶች የታሰሩበት በመሆኑ ለክሪስ “የዥዋዥዌ ትርኢት የምንሰራ እንሆናለን” አልኩት እየተፍለቀለቅኩ። በመጀመሪያ የሞኝ ሀሳብ እንደሆነ አስቦ ፈገግ አለ፤ ቀጥሎ ግን መንፈስን የሚቀሰቅስ ሀሳብ ብሎ ጠራው።
ኮሪ ጭንቅላቱን ቀና አደረገ፡፡ ሰማያዊ አይኖቹ በፍርሀት ፈጥጠዋል።
“አይሆንም!” አለች ኬሪ “እቅዳችሁን አልወደድነውም እንድትወድቁ አንፈልግም::”
“አንወድቅም” አለ ክሪስ፡ “እኔና ካቲ የማንቻል ቡድን ነን፡" አሻግሬ ወደ እሱ
እየተመለከትኩ መማሪያ ክፍሉ ውስጥ ከዚያም ጣሪያው ላይ ሆነን “ከአንቺ
በስተቀር ማንንም አላፈቅርም፣ ካቲ አውቀዋለሁ... እንደዚያ አይነት ስሜት ነው ያለኝ... ሁልጊዜ እኛ ብቻ:" ያለኝን አስታወስኩና በተለየ ሁኔታ ሳቅኩ። “ሞኝ አትሁን፣ በዚያ መንገድ እንደማትወደኝ ታውቃለህ፡ እና ጥፋተኝነት
ሊሰማህ ወይም ልታፍር አይገባም: የእኔም ጥፋት ነው: እንዳልተፈጠረ
ማስመሰልና በድጋሚ እንዳይፈጠር እርግጠኛ መሆን ነው ያለብን፡"
"ግን ካቲ....."
“አንቺና እኔ ሌሎች ሰዎች ሲኖሩን፣ በፍፁም… በፍፁም እርስ በርሳችን በዚህ መንገድ እንዲሰማን አይሆንም''
“እኔ ግን ስላንተ በዚህ መንገድ እንዲሰማኝ ነው የምፈልገው። እና ለእኔ ሌላ
ሰው ለማመንና ለመውደድ በጣም ዘግይቷል።”
ክሪስን መመልከት… ከዚያ መንትዮቹን. ለሁላችንም እቅድ ሳወጣና እንዴት
እንደምንሄድ ሳወራ ትልቅ የሆንኩ አይነት ስሜት ፈጠረብኝ፡ ለመኖር
የትኛውንም ነገር ለመስራት እንደምንገደድ ባውቅም እንኳን መንትዮቹ ሰላም
እንዲሰማቸው መፅናኛ ነገሮች አወራቸዋለሁ።
መስከረም አልፎ ጥቅምት ተተካ። በቅርቡ በረዶ መጣል ይጀምራል:
“ዛሬ ማታ” አለ ክሪስ፡ እናታችን በሩጋ ቆም ብላ ዞራ እንኳን ሳታየን
በግዴለሽነት ደህና ሁኑ ብላን ሄደች:: አሁን እኛን መመልከት እንኳን
መቋቋም አቅቷታል። አንዱን የትራስ ልብስ ሌላኛው ላይ ደርበን ጠንhር እንዲል አደረግን፡ በዚያ ትራስ ጨርቅ ውስጥ ክሪስ የእናታችንን ውድ
ጌጣጌጦች ሁሉ ከትቶ ያመጣል፡ እኔም ሁለት ሻንጣዎችን አሽጌ እናታችን
አሁን ወደዚያ ስለማትሄድ ጣራው ስር ያለው ክፍል ውስጥ ደብቄያለሁ።
ቀኑ መምሸት ሲጀምር ኮሪ ማስመለስ ጀመረ። እየደጋገመ ያስመልሰው
ጀመር። በመድኃኒት ማስቀመጫው ውስጥ ለሆድ የሚሆን መድኃኒት ነበረን የገረጣውን፣ የሚያንቀጠቅጠውን፣ የሚያስለቅሰውን አሰቃቂ ማስመለስ ያደረግነው ጥረት ሁሉ ሊያስቆመው አልቻለም ከዚያ ክንዶቹን በአንገቴ ዙሪያ ጠምጥሞ “እማዬ ደህና አይደለሁም::” ሲል አንሾካሾከ።
“እንዲሻልህ ምን ላድርግልህ ኮሪ?” ስል በጣም ልጅ መሆኔና ልምድ የሌለኝ መሆኔ እየተሰማኝ ጠየቅኩ።
“ሚኪ” አለ ያላመደውንና ጓደኛ ያደረገውን አይጥ በደካማ ድምፅ እየተጣራ
“ሚኪ እኔ ጋር እንዲተኛ እፈልጋለሁ”
“ግን ስትገለበጥ ላዩ ላይ ትተኛበትና ይሞትብሀል፡ እንዲሞትብህ አትፈልግም
አይደል?”
“አልፈልግም” አለ ሀሳቡ ራሱ ያስደነገጠው መሰለ፡ ከዚያ ያ አሰቃቂ መጓጠጥ
እንደገና ጀመረውና ክንዶቼ ላይ እንደያዝኩት እየቀዘቀዘ መጣ፡ በላብ የረጠበ
ፀጉሩ ግንባሩ ላይ ተለጥፏል ሰማያዊ አይኖቹ ፊቴ ላይ ተተክለው እየደጋገመ እናቱን ይጣራል። “እማዬ፣ እማዬ፣ አጥንቶቼን አሞኛል” “አይዞህ” አልኩት።
የተበላሸውን ፒጃማውን ለመቀየር ተሸክሜ ወደ አልጋው እየወሰድኩት ነው።
ሆዱ ውስጥ የቀረ ምንም ነገር ሳይኖር እንዴት ሊያስመልሰው ይችላል?
ክሪስ ይረዳሻል አትጨነቂ!” ሲለኝ ከጎኑ ጋደም ብዬ ደካማና የሚንቀጠቀጥ
ሰውነቱን በክንዶቼ አቀፍኩት::
ክሪስ ጠረጴዛው ጋ ተቀምጦ የኮሪ የህመም ምልክቶች የሚያሳየውን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያንዳንችንን ሊያጠቃን የሚችለውን ሚስጥራዊ በሽታ ለማወቅ
የሀክምና መፅሀፍ ላይ ተደፍቷል አሁን አስራ ስምንት አመት እየሆነው
ነው እኔንና ኬሪን ትታችሁን አትሂዱ! ሲል ለመነኝ፡ ጮክ ባለ ድምፅ “ክሪስ አትሂድ እዚህ ቆይ!” አለ።
ምን ማለቱ ነው? እንድናመልጥ አይፈልግም? ወይስ ለመስረቅ እንደገና
ወደ እናታችን ክፍል አትሂድ ማለቱ ይሆን? እኔና ክሪስ መንትዮቹ የምናደርጋቸውን ነገሮች በመረዳት ይመለከታሉ ብለን ያመንነው ለምንድነው?
በእርግጠኝነት እሱና ኬሪ ትተናቸው እንደማንሄድ ያውቃሉ ያንን ከማድረግ
ብንሞት ይሻለናል።
ኬሪ ነጭ ልብስ የለበሰች ትንሽ ጥላ መስላ ወደ አልጋው መጣችና በረጠቡት ትላልቅ ሰማያዊ አይኖቿ መንትያ ወንድሟን አተኩራ እየተመለከተች
ቆመች: ትንሽ ናት። በጨለማ ክፍል ውስጥ መንምና በአጭር ቀርታ ያደገች ትንሽዬ ተክል ናት።
“ከኮሪ ጋ መተኛት እችላለሁ? ምንም መጥፎ ወይም ክፉ ወይም ቅዱስ
ያልሆነ ነገር አንሰራም: እሱ አጠገብ መሆን ስለፈለግኩ ብቻ ነው” አለች።
አያትየው ትምጣና መጥፎ የምትለውን ነገር ታድርግ! ኬሪን ከኮሪ ጋር አስተኛኋት። ከዚያ እኔና ክሪስ ከትልቁ አልጋ ግራና ቀኝ ቆመን በሀዘን ተሞልተን ኮሪ ረፍት ባጣ ሁኔታ ሲቅበጠበጥና ለመተንፈስ ሲታገል እንዲሁም በቅዠት ሲጣራ እየተመለከትን ነው
እናቱንና አባቱን፣ ክሪስንና እኔን ይፈልጋል እምባዬ በሌሊት ልብሴ ኮሌታ
ላይ እየወረደ ነው ክሪስንም ስመለከተው ጉንጮቹ በእምባዬ ረጥበዋል። “ኬሪ
ኬሪ... ኬሪ የታለች?" ሲል በመደጋገም ጠየቀ እንቅልፍ ከወሰዳት ትንሽ
ቆይታለች: ፊቶቻቸው ተጠጋግተው ነበር። ቀጥታ ወደ እሷ እየተመለተ
ቢሆንም እያያት አይደለም
ቅጣት እንደሆነ አሰብኩ፡፡ እግዚአብሔር እኔና ክሪስ ስለሰራነው ነገር እየቀጣን
ነው አያትየው አስጠንቅቃን ነበር. እስክተገረፍንበት ቀን ድረስ በየቀኑ
ታስጠነቅቀን ነበር ሌሊቱን ሙሉ እኔ ክፍሉ ውስጥ ስንጎራደድ፣ ክሪስ ደግሞ ከአንዱ የህክምና መፅሀፍ ወደ ሌላው እየሄደ ሲያነብ ነበር።
በመጨረሻ ደም የመሰሉ አይኖቹን ቀና አድርጎ “የምግብ መመረዝ ነው::
ወተቱ ተበላሽቷል ማለት ነው” አለ።
“ስቀምሰውም፣ ሳሸተውም ደህና ነበር” ስል መለስኩለት ሁልጊዜ የትኛውንም ምግብ ለክሪስና ለመንትዮቹ ከማቅረቤ በፊት በጥንቃቄ አሽትቼና ቀምሼ ነበር። በሆነ ምክንያት ሁሉንም ነገር ከሚወደውና ምንም ነገር ከሚበላው
ክሪስ የተሻለ የመቅመስ ችሎታ እንዳለኝ አስባለሁ።
“ሀምበርገሩ ይሆናል፡ ለየት ያለ ጣዕም ነበረው”
“አረ ጣዕሙ ለእኔ ደህና ነበር” አልኩት ለእሱም ደህና የነበረ ይመስለኛል::
ምክንያቱም ቀኑን ሙሉ ኮሪ ምንም መብላት ስላልፈለገ የኬሪን ግማሽ ሀምበርገር ጨምሮ የኮሪንም ፋንታ ነበር የበላው ኮሪ ቀኑን ሙሉ ምንም መብላት አልፈለገም ነበር።
“ካቲ አንቺም ቀኑን ሙሉ ምንም እንዳልበላሽ አስተውያለሁ አንቺም እንደ
መንትዮቹ ያህል ከስተሻል፡ የምታመጣልን ምግብ በቂ ነው ራስሽን መበደል
አይጠበቅብሽም” አለኝ፡
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
ቀኖቹን ሁላ ሰማያዊ ስትቀባ አንዱን ለጥቁር ተወው።
በማንኛውም ቀን ልንሄድ ነው፡፡ እናታችን በምሽት ወጣ እላለሁ እንዳለች፣
መጓጓዝ የሚችሉ ውድ ንብረቶቿም ከእሷ ይወጣሉ። ወደ ግላድስተን
አንመለስም እዚያ አሁን ክረምት ገብቷል። ገና እስከ ግንቦት ይቆያል።ሰርከስ የሚሰሩ ሰዎች ወደሚኖሩበት ወደ ሳራሶታ እንሄዳለን፡ እዚያ ያሉ
ሰዎች ለየት ያለ የኋላ ታሪክ ላላቸው ሰዎች ደግነት በማሳየት የሚታወቁ
ናቸው ክሪስና እኔ ከፍ ያለ ቦታ ማለትም ጣራ ላይ ስለኖርን ምሰሶዎቹ
ላይ ብዙ ገመዶች የታሰሩበት በመሆኑ ለክሪስ “የዥዋዥዌ ትርኢት የምንሰራ እንሆናለን” አልኩት እየተፍለቀለቅኩ። በመጀመሪያ የሞኝ ሀሳብ እንደሆነ አስቦ ፈገግ አለ፤ ቀጥሎ ግን መንፈስን የሚቀሰቅስ ሀሳብ ብሎ ጠራው።
ኮሪ ጭንቅላቱን ቀና አደረገ፡፡ ሰማያዊ አይኖቹ በፍርሀት ፈጥጠዋል።
“አይሆንም!” አለች ኬሪ “እቅዳችሁን አልወደድነውም እንድትወድቁ አንፈልግም::”
“አንወድቅም” አለ ክሪስ፡ “እኔና ካቲ የማንቻል ቡድን ነን፡" አሻግሬ ወደ እሱ
እየተመለከትኩ መማሪያ ክፍሉ ውስጥ ከዚያም ጣሪያው ላይ ሆነን “ከአንቺ
በስተቀር ማንንም አላፈቅርም፣ ካቲ አውቀዋለሁ... እንደዚያ አይነት ስሜት ነው ያለኝ... ሁልጊዜ እኛ ብቻ:" ያለኝን አስታወስኩና በተለየ ሁኔታ ሳቅኩ። “ሞኝ አትሁን፣ በዚያ መንገድ እንደማትወደኝ ታውቃለህ፡ እና ጥፋተኝነት
ሊሰማህ ወይም ልታፍር አይገባም: የእኔም ጥፋት ነው: እንዳልተፈጠረ
ማስመሰልና በድጋሚ እንዳይፈጠር እርግጠኛ መሆን ነው ያለብን፡"
"ግን ካቲ....."
“አንቺና እኔ ሌሎች ሰዎች ሲኖሩን፣ በፍፁም… በፍፁም እርስ በርሳችን በዚህ መንገድ እንዲሰማን አይሆንም''
“እኔ ግን ስላንተ በዚህ መንገድ እንዲሰማኝ ነው የምፈልገው። እና ለእኔ ሌላ
ሰው ለማመንና ለመውደድ በጣም ዘግይቷል።”
ክሪስን መመልከት… ከዚያ መንትዮቹን. ለሁላችንም እቅድ ሳወጣና እንዴት
እንደምንሄድ ሳወራ ትልቅ የሆንኩ አይነት ስሜት ፈጠረብኝ፡ ለመኖር
የትኛውንም ነገር ለመስራት እንደምንገደድ ባውቅም እንኳን መንትዮቹ ሰላም
እንዲሰማቸው መፅናኛ ነገሮች አወራቸዋለሁ።
መስከረም አልፎ ጥቅምት ተተካ። በቅርቡ በረዶ መጣል ይጀምራል:
“ዛሬ ማታ” አለ ክሪስ፡ እናታችን በሩጋ ቆም ብላ ዞራ እንኳን ሳታየን
በግዴለሽነት ደህና ሁኑ ብላን ሄደች:: አሁን እኛን መመልከት እንኳን
መቋቋም አቅቷታል። አንዱን የትራስ ልብስ ሌላኛው ላይ ደርበን ጠንhር እንዲል አደረግን፡ በዚያ ትራስ ጨርቅ ውስጥ ክሪስ የእናታችንን ውድ
ጌጣጌጦች ሁሉ ከትቶ ያመጣል፡ እኔም ሁለት ሻንጣዎችን አሽጌ እናታችን
አሁን ወደዚያ ስለማትሄድ ጣራው ስር ያለው ክፍል ውስጥ ደብቄያለሁ።
ቀኑ መምሸት ሲጀምር ኮሪ ማስመለስ ጀመረ። እየደጋገመ ያስመልሰው
ጀመር። በመድኃኒት ማስቀመጫው ውስጥ ለሆድ የሚሆን መድኃኒት ነበረን የገረጣውን፣ የሚያንቀጠቅጠውን፣ የሚያስለቅሰውን አሰቃቂ ማስመለስ ያደረግነው ጥረት ሁሉ ሊያስቆመው አልቻለም ከዚያ ክንዶቹን በአንገቴ ዙሪያ ጠምጥሞ “እማዬ ደህና አይደለሁም::” ሲል አንሾካሾከ።
“እንዲሻልህ ምን ላድርግልህ ኮሪ?” ስል በጣም ልጅ መሆኔና ልምድ የሌለኝ መሆኔ እየተሰማኝ ጠየቅኩ።
“ሚኪ” አለ ያላመደውንና ጓደኛ ያደረገውን አይጥ በደካማ ድምፅ እየተጣራ
“ሚኪ እኔ ጋር እንዲተኛ እፈልጋለሁ”
“ግን ስትገለበጥ ላዩ ላይ ትተኛበትና ይሞትብሀል፡ እንዲሞትብህ አትፈልግም
አይደል?”
“አልፈልግም” አለ ሀሳቡ ራሱ ያስደነገጠው መሰለ፡ ከዚያ ያ አሰቃቂ መጓጠጥ
እንደገና ጀመረውና ክንዶቼ ላይ እንደያዝኩት እየቀዘቀዘ መጣ፡ በላብ የረጠበ
ፀጉሩ ግንባሩ ላይ ተለጥፏል ሰማያዊ አይኖቹ ፊቴ ላይ ተተክለው እየደጋገመ እናቱን ይጣራል። “እማዬ፣ እማዬ፣ አጥንቶቼን አሞኛል” “አይዞህ” አልኩት።
የተበላሸውን ፒጃማውን ለመቀየር ተሸክሜ ወደ አልጋው እየወሰድኩት ነው።
ሆዱ ውስጥ የቀረ ምንም ነገር ሳይኖር እንዴት ሊያስመልሰው ይችላል?
ክሪስ ይረዳሻል አትጨነቂ!” ሲለኝ ከጎኑ ጋደም ብዬ ደካማና የሚንቀጠቀጥ
ሰውነቱን በክንዶቼ አቀፍኩት::
ክሪስ ጠረጴዛው ጋ ተቀምጦ የኮሪ የህመም ምልክቶች የሚያሳየውን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያንዳንችንን ሊያጠቃን የሚችለውን ሚስጥራዊ በሽታ ለማወቅ
የሀክምና መፅሀፍ ላይ ተደፍቷል አሁን አስራ ስምንት አመት እየሆነው
ነው እኔንና ኬሪን ትታችሁን አትሂዱ! ሲል ለመነኝ፡ ጮክ ባለ ድምፅ “ክሪስ አትሂድ እዚህ ቆይ!” አለ።
ምን ማለቱ ነው? እንድናመልጥ አይፈልግም? ወይስ ለመስረቅ እንደገና
ወደ እናታችን ክፍል አትሂድ ማለቱ ይሆን? እኔና ክሪስ መንትዮቹ የምናደርጋቸውን ነገሮች በመረዳት ይመለከታሉ ብለን ያመንነው ለምንድነው?
በእርግጠኝነት እሱና ኬሪ ትተናቸው እንደማንሄድ ያውቃሉ ያንን ከማድረግ
ብንሞት ይሻለናል።
ኬሪ ነጭ ልብስ የለበሰች ትንሽ ጥላ መስላ ወደ አልጋው መጣችና በረጠቡት ትላልቅ ሰማያዊ አይኖቿ መንትያ ወንድሟን አተኩራ እየተመለከተች
ቆመች: ትንሽ ናት። በጨለማ ክፍል ውስጥ መንምና በአጭር ቀርታ ያደገች ትንሽዬ ተክል ናት።
“ከኮሪ ጋ መተኛት እችላለሁ? ምንም መጥፎ ወይም ክፉ ወይም ቅዱስ
ያልሆነ ነገር አንሰራም: እሱ አጠገብ መሆን ስለፈለግኩ ብቻ ነው” አለች።
አያትየው ትምጣና መጥፎ የምትለውን ነገር ታድርግ! ኬሪን ከኮሪ ጋር አስተኛኋት። ከዚያ እኔና ክሪስ ከትልቁ አልጋ ግራና ቀኝ ቆመን በሀዘን ተሞልተን ኮሪ ረፍት ባጣ ሁኔታ ሲቅበጠበጥና ለመተንፈስ ሲታገል እንዲሁም በቅዠት ሲጣራ እየተመለከትን ነው
እናቱንና አባቱን፣ ክሪስንና እኔን ይፈልጋል እምባዬ በሌሊት ልብሴ ኮሌታ
ላይ እየወረደ ነው ክሪስንም ስመለከተው ጉንጮቹ በእምባዬ ረጥበዋል። “ኬሪ
ኬሪ... ኬሪ የታለች?" ሲል በመደጋገም ጠየቀ እንቅልፍ ከወሰዳት ትንሽ
ቆይታለች: ፊቶቻቸው ተጠጋግተው ነበር። ቀጥታ ወደ እሷ እየተመለተ
ቢሆንም እያያት አይደለም
ቅጣት እንደሆነ አሰብኩ፡፡ እግዚአብሔር እኔና ክሪስ ስለሰራነው ነገር እየቀጣን
ነው አያትየው አስጠንቅቃን ነበር. እስክተገረፍንበት ቀን ድረስ በየቀኑ
ታስጠነቅቀን ነበር ሌሊቱን ሙሉ እኔ ክፍሉ ውስጥ ስንጎራደድ፣ ክሪስ ደግሞ ከአንዱ የህክምና መፅሀፍ ወደ ሌላው እየሄደ ሲያነብ ነበር።
በመጨረሻ ደም የመሰሉ አይኖቹን ቀና አድርጎ “የምግብ መመረዝ ነው::
ወተቱ ተበላሽቷል ማለት ነው” አለ።
“ስቀምሰውም፣ ሳሸተውም ደህና ነበር” ስል መለስኩለት ሁልጊዜ የትኛውንም ምግብ ለክሪስና ለመንትዮቹ ከማቅረቤ በፊት በጥንቃቄ አሽትቼና ቀምሼ ነበር። በሆነ ምክንያት ሁሉንም ነገር ከሚወደውና ምንም ነገር ከሚበላው
ክሪስ የተሻለ የመቅመስ ችሎታ እንዳለኝ አስባለሁ።
“ሀምበርገሩ ይሆናል፡ ለየት ያለ ጣዕም ነበረው”
“አረ ጣዕሙ ለእኔ ደህና ነበር” አልኩት ለእሱም ደህና የነበረ ይመስለኛል::
ምክንያቱም ቀኑን ሙሉ ኮሪ ምንም መብላት ስላልፈለገ የኬሪን ግማሽ ሀምበርገር ጨምሮ የኮሪንም ፋንታ ነበር የበላው ኮሪ ቀኑን ሙሉ ምንም መብላት አልፈለገም ነበር።
“ካቲ አንቺም ቀኑን ሙሉ ምንም እንዳልበላሽ አስተውያለሁ አንቺም እንደ
መንትዮቹ ያህል ከስተሻል፡ የምታመጣልን ምግብ በቂ ነው ራስሽን መበደል
አይጠበቅብሽም” አለኝ፡
👍34❤3🥰1
#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
ደቂቃዎች በረሩ ላራት ሰዓት ሩብ ጕዳይ አራት ተሩብ አሁንም ሪቻርድ ሔር ከእናቱ ጋር እንዳለ ነው " ሚስተር ካርላይልና ባርባራም በአትክልቱ ቦታ መኽል ባለዉ እግር መንገድ እስከዚያ ሰዓት ድረስ በትዕግሥት ይመላለሳሉ አራት ሰዓት ተሩብ ላይ ሪቻርድ ሔር ከናቱ ተሰናብቶ መጣ " ባርባራም ዕንባዋን እያወረደች ተሰናበተችው በመጣበት ለመሔድ ወደ ዐፀዱ ገባ "
“ በይ ባርባራ . . . ደኅና እደሪ " በጣም ስለመሸ ሚስዝ ሔርን አልተሰናበትኳቸውም " ሆኖም ሁሉ ነገር ደኅና በመሳካቱ የተሰማኝን ደስታ ንገሪልኝ ”ብሏት ሔደ እሱ በሰው እየተራመደ ወደ ቤቱ ሲገሠግሥ ባርባራ ብሶቷ በዕንባ እስኪወጣላት ድረስ ከበሩ ብረት ተደግፋ ማንም
ሳያቋርጣት እያነባች ዐሥር ደቂቃ ያህል ቆየች " እናቷም የራሷን የውስጥ ብሶት ስታስተነትን ፈጽማ ረስታት ኖሯል። ባርባራ ከዚያ እንደ ቆመች ፈጣን የእግር ዳና ስትሰማ በጣም ድንግጥ አለች ወዲያው ግን ሚስተር ካርላይል መሆኑን ዐወቀችው "
“ በውስጡ አንድ ብራና የያዘ ጥቅል ትቼ ነበር እባክሽ አምጭልኝ” ባርባራ
ስትበር ሔዳ አመጣችለት ሚስተር ካርላይልም ተቀበለና ባጭሩ አመስግኖ ወደ ቤቱ ገሠገሠ ። እሷም እንደ ነበረችው ከበሩ ተደግፋ በካርላይል መምጣት ተቋርጦ
የነበረውን ዕንባዋን ትለቀው ጀመር በወንድሟ ነገር አንጀቷ አሯል ይሆናል ተብሎ የተጠበቀው ካፒቴን ቶርን ሳይሆን በመቅረቱ የባሰውን በግናለች አሁንም ግና የአባቷ ዳና አልተሰማም እሷም ቁማ መጠበቋን ቀጠለች » ትንሽ ቆይታ በቁጥቋጦቹ ታኮ አንድ ስው ከሩቅ ታያት " እሷም የድንጋጤ ሀይኖቿን አፍጣ ተመለከተች " ልቧ ነጥሮ የሚወጣ እስኪመስል ይመታ ጀመር " ሪቻርድ መሆኑን ስታውቅ
ምን ጉዳይ አሳብዶ እንደ መለሰው ገረማት አሁንም ከደጅ ሲያገኛት ጊዜ ያባቱን
አለመግባት አረጋገጠና ያለ ሥጋት ተጠጋ " የሠራ አካላቱ እየተንቀጠቀጠ ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ እያለ የሚሆነው ጠፍቶታል "
“ ባርባራ ! ባርባራ !.... ” አላት በኃይል እየቃተተ “ቶርንን አየሁት !
ራሱን ቶርንን በአካል አገኘሁት ”
ባርባራ እንግዳ ነገር ሆነባትና አፍጣ ታየው ጀመር
“ልክ ከዚህ እንደ ወጣሁ ሰው ስለማይበዛበት ከዚህኛው መንገድ ይሻላል
በማለት ወደ ቢን ሌን አቋርጨ ስሔድ አንድ ሰው ከሩቅ ሲመጣ አየሁ ምንም እንኳን ሌላ ለመምሰል ብሞክርም ማንም እንዲያገኘው ስለ አልፈለግሁ ወደ ዛፎቹ
ዘወር አልኩ እሱ መኻል መንገዱን ይዞ ወዶ ዌስትሊን ሲሔድ አየሁት ግና ከአጠገቤ ሳይደርስ ዐወቅሁት "
የሠራ አካላቴን ወረረኝ " እያንዳንዷ የደሜ ጠብታ የምትሯሯጥብኝ መሰለኝ" ዘለህ እነቀው የሆሊጆን ገዳይ ነው ብለህ አስይዘው የሚል ሐሳብ መጣብኝ
ሁኔታውን ገምግሜ ቀጥቅጦ እንዳይገለኝ ፈራሁና ተውኩት አየሽ... ደሞኮ አንድ ጊዜ ነፍስ ያጠፋ ሰው ሁለተኛ ለመድገም ወደ ኋላ አይልም አላት። "
«ሪቻርድ እርግጠኛ ነህ ? ስለ ቶርን ብዙ ስለምትናገር እንዲያው በሐሳብህ
መጥቶብህ እንዳይሆን ?አለችው "
ምን ነካሽ ... ባርባራ ሐሳብ? ከዚህ ተቀርጿል አላልኩሽም ? አላት ወደ
ልቡ እያመለከተ " በየጥላው ሥር ቶርንን አየሁ የምል ሰው በለበት ሰው የሚታየኝ ሕፃን መሰልኩሽ ወይንስ ዕብድ? በአንድ እጁ ባርኔጣውን ይዞ በሌላው ፀጉሩን ከግንባሩ የኋሊት እያስተኛ አሁንም አሁንም ጸጕሩን የኋሊት የመግፋት
ልምድ አለው በጣም እየተጣደፈ ይራመድ ነበር ጸጉሩን እንደዚያ ወደ ኋላ
በሚመልስበት ጊዜ የጣቱ አልማዝ በጨረቃው ብርሃን ይፈልቅ ነበር " ምንም አትጠራጠሪ።
ባርባራ በደንብ ካዳመጠችው በኋላ እሷም እንደሱ ስሜቷ ተቀሰቀሰ ድንጋጤዉ እንቅቃጤዉ ጥድፊያዉ ጉጉቱ እንዳለ ተጋባባት ። ማሰብ ማማዘን
ቦታ ለቀቁ።
በግብታዊ ስሜት ብቻ ተነዳች " የሪቻርድ አባባል ሙሉ በሙሉ እንዳመነችቐት
ምን እንደምታደርግ በማሰብ ጊዜ ማባከን አልፈለገችም :
ምናልባት በዚያ ሰዓት ሰው ቢያገኛት ምን እንደሚላት በመዘንጋት አባቷ ከቤት ሲገባ ቢያጣት ምን እንደሚል በመርሳት ሪቻርድ ሔር ቀስ ብሎ ዙሪውን እያስተዋለ በሩቁ እየተከተላት ወደ ሚስተር ካርላይል እየሮጠች ሔዶች ገና ኢስትሊን በር ሊገባ ሲል ደረሰችበት "
“ባርባራ. . . ምን ነው በደኅናሽ ነው ?”
“ አርኪባልድ ! አርኪባልድ ! አለች ከትንፋሿ ጋር እየተናነቀች " እሱስ
ደኅና ነኝ' አንድ ጊዜ ሪቻርድን አነጋግረው ቶርንን አይቶታል ”
ሚስተር ካርላይል ምልስ አለና ወደ ቁጥቋጦች ዘወር ብለው ሪቻርድ ያየውን
ነገር ዝርዝር አድርጎ አጫወተው እሱም ምናልባት ሪቻርድን ላለማስከፋት ብሎ
እንደሆነም አይታወቅም : ልክ እንደ ባርባራ ሙሉ በሙሉ ሳይጠራጠር ያመነው መሰለ "
“ ሪቻርድ ... ዛሬ ማታ ከቢሮዬ ካየኸው ሰው በቀር በዚህ አካባቢ ቶርን የሚባል ሰው ጭራሽ የለም” አለው ካርላይል ትንሽ ካሰበ በኋላ “ የሚገርም ነገር ነው …”
“ አሁን ያገኘሁት ሰው ቶርን ለመሆኑ አልጠራጠርም ምናልባት እሱ እዚ
ያለው በሌላ ስም ሊሆን ይችላል።
አለባበሱ ምን ይመስል ነበር ? አለው ካርላይል።
እንደ ፈለገ ቢለብሰው ሰውየው አያሳስትም ” አለ ሪቻርድ “ የማታ ልብስ ለብሶ ቀጭን ካፖርት ብጤ ትከሻው ላይ ጣል አድርጎ ነበር " ለባርባራ እንደነገርኳት ጸጉሩን ከግንባሩ ወደ ኋላው በመግፋት ልምዱ ብቻ በቀላሉ ዐውቀዋለሁ
በተጨማሪ ደግሞ ለስላሳ ነጭ የሆነው እጁና የሚያንጸባርቀው የአልማዝ
ቀለበቱ ዋና ምልክቶች ናቸው ”
"በል እንግዲያው ሪቻርድ ... እኔ አሁን የምመክርህ ከዚህ አንድ
ቀን ሰንብትና ይህን ሰውዬ ፈልገው » ድንገት ያየኸው እንዪሆነ የት እንደሚገባ
ተከታተለው ከተቻለ የዚህን ሰው ማንነት ማወቅ በጣም አስፌላጊ ነው አለው
በሚስተር ካርይል
"ብገኝ የሚጠብቀኝ አደጋሳ ?”
አንተ ደግሞ በጣም ስለ ተለዋወጥክ ቀን ለቀን በአደባባይ ብትሔድ እንኳን
የሚያውቅህ አይገኝም : "
ሪቻርድ በሚስተር ካርይል አነጋገር ሊተማመን ስለ አልቻለ ስለአየው ሰውዬ
ምልክት ዝርዝር አድርጎ ከገለጸላቸው በኋላ ለማንኛውም አስፈላጊ ነገር
የሎንዶን አድራሻውን ሰጥቶ ሔደ "
“ በይ እንግዲሀ ልሸኝሽ እንጂ .. ባርባራ ” አለ ሚስተር ካርላይል "
“ በጭራሽ አይሆንም ! እንደዚህ ጊዜው መሽቶ አንተ ደክሞህ እያለህ ሁለተኛ መንገድ አላስመታህም " አሁንም ስመጣ ብቻዬን ነበርኩ " ሪቻርድም እንኳን አብሮኝ አልነበረም ።
ስትመጭ ምንም ነገር ማድረግ ባልችልም አሁን ከሌሊቱ እምስት ሰዓት
ላይ በአውራ ጐዳና ብቻሽን ስትሔጅ ዝም ብዬ አላይሽም ” አለና ክንዱን ዘረጋላት " ተያይዘው ጉዞ ጀመሩ "
“አቤት ይህን ያህል አምሽተህ ስትገባ እቤት ሳቤላ ምን ትልህ ይሆን?”
“ እስካሁን ከግብዣው የምትመለስ አይመስለኝም ደሞም አንዴ ብቻ በአንድ ምክንያት ማምሸቴ ይህን ያህልም አይደለም ”
ከበሩ አድርሷት ተመለሰ እሷ ከቤት ስትገባ አባቷ አሁንም ገና አልመጣም
ነበር "
ሚስተር ካርይል ከቤቱ ሲደርስ ሳቤላ ከመልበሻ ክፍሏ ውስጥ ተቀምጣ ስትጽፍ አገኛት " ስለ ግብዣው አንዳንድ ነገር ጠይቋት ባጭሩ ቁርጥ ቁርጥ እያደረገች
መለሰችለት " በመጨረሻም ለምን እንደማትተኛ ጠየቃት
“ እንቅልፌ አልመጣም ”
“ እኔ ግን ቶሎ መተኛት አለብኝ " ... ሳቤላ ሙትት ብዬ ደክሜአለሁ ”
" ትችላለህ ” አለችው "
ሊስማት ጐንበስ ሲል ፊቷን በዘዴ ዞር አደረገችበት ወደ ግብዣው አብሯት ባለመሔዱ የተቆጣች መሰለውና እጁን ከትከሻዋ ጣል አድርጎ ፈገግ አለ "
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
ደቂቃዎች በረሩ ላራት ሰዓት ሩብ ጕዳይ አራት ተሩብ አሁንም ሪቻርድ ሔር ከእናቱ ጋር እንዳለ ነው " ሚስተር ካርላይልና ባርባራም በአትክልቱ ቦታ መኽል ባለዉ እግር መንገድ እስከዚያ ሰዓት ድረስ በትዕግሥት ይመላለሳሉ አራት ሰዓት ተሩብ ላይ ሪቻርድ ሔር ከናቱ ተሰናብቶ መጣ " ባርባራም ዕንባዋን እያወረደች ተሰናበተችው በመጣበት ለመሔድ ወደ ዐፀዱ ገባ "
“ በይ ባርባራ . . . ደኅና እደሪ " በጣም ስለመሸ ሚስዝ ሔርን አልተሰናበትኳቸውም " ሆኖም ሁሉ ነገር ደኅና በመሳካቱ የተሰማኝን ደስታ ንገሪልኝ ”ብሏት ሔደ እሱ በሰው እየተራመደ ወደ ቤቱ ሲገሠግሥ ባርባራ ብሶቷ በዕንባ እስኪወጣላት ድረስ ከበሩ ብረት ተደግፋ ማንም
ሳያቋርጣት እያነባች ዐሥር ደቂቃ ያህል ቆየች " እናቷም የራሷን የውስጥ ብሶት ስታስተነትን ፈጽማ ረስታት ኖሯል። ባርባራ ከዚያ እንደ ቆመች ፈጣን የእግር ዳና ስትሰማ በጣም ድንግጥ አለች ወዲያው ግን ሚስተር ካርላይል መሆኑን ዐወቀችው "
“ በውስጡ አንድ ብራና የያዘ ጥቅል ትቼ ነበር እባክሽ አምጭልኝ” ባርባራ
ስትበር ሔዳ አመጣችለት ሚስተር ካርላይልም ተቀበለና ባጭሩ አመስግኖ ወደ ቤቱ ገሠገሠ ። እሷም እንደ ነበረችው ከበሩ ተደግፋ በካርላይል መምጣት ተቋርጦ
የነበረውን ዕንባዋን ትለቀው ጀመር በወንድሟ ነገር አንጀቷ አሯል ይሆናል ተብሎ የተጠበቀው ካፒቴን ቶርን ሳይሆን በመቅረቱ የባሰውን በግናለች አሁንም ግና የአባቷ ዳና አልተሰማም እሷም ቁማ መጠበቋን ቀጠለች » ትንሽ ቆይታ በቁጥቋጦቹ ታኮ አንድ ስው ከሩቅ ታያት " እሷም የድንጋጤ ሀይኖቿን አፍጣ ተመለከተች " ልቧ ነጥሮ የሚወጣ እስኪመስል ይመታ ጀመር " ሪቻርድ መሆኑን ስታውቅ
ምን ጉዳይ አሳብዶ እንደ መለሰው ገረማት አሁንም ከደጅ ሲያገኛት ጊዜ ያባቱን
አለመግባት አረጋገጠና ያለ ሥጋት ተጠጋ " የሠራ አካላቱ እየተንቀጠቀጠ ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ እያለ የሚሆነው ጠፍቶታል "
“ ባርባራ ! ባርባራ !.... ” አላት በኃይል እየቃተተ “ቶርንን አየሁት !
ራሱን ቶርንን በአካል አገኘሁት ”
ባርባራ እንግዳ ነገር ሆነባትና አፍጣ ታየው ጀመር
“ልክ ከዚህ እንደ ወጣሁ ሰው ስለማይበዛበት ከዚህኛው መንገድ ይሻላል
በማለት ወደ ቢን ሌን አቋርጨ ስሔድ አንድ ሰው ከሩቅ ሲመጣ አየሁ ምንም እንኳን ሌላ ለመምሰል ብሞክርም ማንም እንዲያገኘው ስለ አልፈለግሁ ወደ ዛፎቹ
ዘወር አልኩ እሱ መኻል መንገዱን ይዞ ወዶ ዌስትሊን ሲሔድ አየሁት ግና ከአጠገቤ ሳይደርስ ዐወቅሁት "
የሠራ አካላቴን ወረረኝ " እያንዳንዷ የደሜ ጠብታ የምትሯሯጥብኝ መሰለኝ" ዘለህ እነቀው የሆሊጆን ገዳይ ነው ብለህ አስይዘው የሚል ሐሳብ መጣብኝ
ሁኔታውን ገምግሜ ቀጥቅጦ እንዳይገለኝ ፈራሁና ተውኩት አየሽ... ደሞኮ አንድ ጊዜ ነፍስ ያጠፋ ሰው ሁለተኛ ለመድገም ወደ ኋላ አይልም አላት። "
«ሪቻርድ እርግጠኛ ነህ ? ስለ ቶርን ብዙ ስለምትናገር እንዲያው በሐሳብህ
መጥቶብህ እንዳይሆን ?አለችው "
ምን ነካሽ ... ባርባራ ሐሳብ? ከዚህ ተቀርጿል አላልኩሽም ? አላት ወደ
ልቡ እያመለከተ " በየጥላው ሥር ቶርንን አየሁ የምል ሰው በለበት ሰው የሚታየኝ ሕፃን መሰልኩሽ ወይንስ ዕብድ? በአንድ እጁ ባርኔጣውን ይዞ በሌላው ፀጉሩን ከግንባሩ የኋሊት እያስተኛ አሁንም አሁንም ጸጕሩን የኋሊት የመግፋት
ልምድ አለው በጣም እየተጣደፈ ይራመድ ነበር ጸጉሩን እንደዚያ ወደ ኋላ
በሚመልስበት ጊዜ የጣቱ አልማዝ በጨረቃው ብርሃን ይፈልቅ ነበር " ምንም አትጠራጠሪ።
ባርባራ በደንብ ካዳመጠችው በኋላ እሷም እንደሱ ስሜቷ ተቀሰቀሰ ድንጋጤዉ እንቅቃጤዉ ጥድፊያዉ ጉጉቱ እንዳለ ተጋባባት ። ማሰብ ማማዘን
ቦታ ለቀቁ።
በግብታዊ ስሜት ብቻ ተነዳች " የሪቻርድ አባባል ሙሉ በሙሉ እንዳመነችቐት
ምን እንደምታደርግ በማሰብ ጊዜ ማባከን አልፈለገችም :
ምናልባት በዚያ ሰዓት ሰው ቢያገኛት ምን እንደሚላት በመዘንጋት አባቷ ከቤት ሲገባ ቢያጣት ምን እንደሚል በመርሳት ሪቻርድ ሔር ቀስ ብሎ ዙሪውን እያስተዋለ በሩቁ እየተከተላት ወደ ሚስተር ካርላይል እየሮጠች ሔዶች ገና ኢስትሊን በር ሊገባ ሲል ደረሰችበት "
“ባርባራ. . . ምን ነው በደኅናሽ ነው ?”
“ አርኪባልድ ! አርኪባልድ ! አለች ከትንፋሿ ጋር እየተናነቀች " እሱስ
ደኅና ነኝ' አንድ ጊዜ ሪቻርድን አነጋግረው ቶርንን አይቶታል ”
ሚስተር ካርላይል ምልስ አለና ወደ ቁጥቋጦች ዘወር ብለው ሪቻርድ ያየውን
ነገር ዝርዝር አድርጎ አጫወተው እሱም ምናልባት ሪቻርድን ላለማስከፋት ብሎ
እንደሆነም አይታወቅም : ልክ እንደ ባርባራ ሙሉ በሙሉ ሳይጠራጠር ያመነው መሰለ "
“ ሪቻርድ ... ዛሬ ማታ ከቢሮዬ ካየኸው ሰው በቀር በዚህ አካባቢ ቶርን የሚባል ሰው ጭራሽ የለም” አለው ካርላይል ትንሽ ካሰበ በኋላ “ የሚገርም ነገር ነው …”
“ አሁን ያገኘሁት ሰው ቶርን ለመሆኑ አልጠራጠርም ምናልባት እሱ እዚ
ያለው በሌላ ስም ሊሆን ይችላል።
አለባበሱ ምን ይመስል ነበር ? አለው ካርላይል።
እንደ ፈለገ ቢለብሰው ሰውየው አያሳስትም ” አለ ሪቻርድ “ የማታ ልብስ ለብሶ ቀጭን ካፖርት ብጤ ትከሻው ላይ ጣል አድርጎ ነበር " ለባርባራ እንደነገርኳት ጸጉሩን ከግንባሩ ወደ ኋላው በመግፋት ልምዱ ብቻ በቀላሉ ዐውቀዋለሁ
በተጨማሪ ደግሞ ለስላሳ ነጭ የሆነው እጁና የሚያንጸባርቀው የአልማዝ
ቀለበቱ ዋና ምልክቶች ናቸው ”
"በል እንግዲያው ሪቻርድ ... እኔ አሁን የምመክርህ ከዚህ አንድ
ቀን ሰንብትና ይህን ሰውዬ ፈልገው » ድንገት ያየኸው እንዪሆነ የት እንደሚገባ
ተከታተለው ከተቻለ የዚህን ሰው ማንነት ማወቅ በጣም አስፌላጊ ነው አለው
በሚስተር ካርይል
"ብገኝ የሚጠብቀኝ አደጋሳ ?”
አንተ ደግሞ በጣም ስለ ተለዋወጥክ ቀን ለቀን በአደባባይ ብትሔድ እንኳን
የሚያውቅህ አይገኝም : "
ሪቻርድ በሚስተር ካርይል አነጋገር ሊተማመን ስለ አልቻለ ስለአየው ሰውዬ
ምልክት ዝርዝር አድርጎ ከገለጸላቸው በኋላ ለማንኛውም አስፈላጊ ነገር
የሎንዶን አድራሻውን ሰጥቶ ሔደ "
“ በይ እንግዲሀ ልሸኝሽ እንጂ .. ባርባራ ” አለ ሚስተር ካርላይል "
“ በጭራሽ አይሆንም ! እንደዚህ ጊዜው መሽቶ አንተ ደክሞህ እያለህ ሁለተኛ መንገድ አላስመታህም " አሁንም ስመጣ ብቻዬን ነበርኩ " ሪቻርድም እንኳን አብሮኝ አልነበረም ።
ስትመጭ ምንም ነገር ማድረግ ባልችልም አሁን ከሌሊቱ እምስት ሰዓት
ላይ በአውራ ጐዳና ብቻሽን ስትሔጅ ዝም ብዬ አላይሽም ” አለና ክንዱን ዘረጋላት " ተያይዘው ጉዞ ጀመሩ "
“አቤት ይህን ያህል አምሽተህ ስትገባ እቤት ሳቤላ ምን ትልህ ይሆን?”
“ እስካሁን ከግብዣው የምትመለስ አይመስለኝም ደሞም አንዴ ብቻ በአንድ ምክንያት ማምሸቴ ይህን ያህልም አይደለም ”
ከበሩ አድርሷት ተመለሰ እሷ ከቤት ስትገባ አባቷ አሁንም ገና አልመጣም
ነበር "
ሚስተር ካርይል ከቤቱ ሲደርስ ሳቤላ ከመልበሻ ክፍሏ ውስጥ ተቀምጣ ስትጽፍ አገኛት " ስለ ግብዣው አንዳንድ ነገር ጠይቋት ባጭሩ ቁርጥ ቁርጥ እያደረገች
መለሰችለት " በመጨረሻም ለምን እንደማትተኛ ጠየቃት
“ እንቅልፌ አልመጣም ”
“ እኔ ግን ቶሎ መተኛት አለብኝ " ... ሳቤላ ሙትት ብዬ ደክሜአለሁ ”
" ትችላለህ ” አለችው "
ሊስማት ጐንበስ ሲል ፊቷን በዘዴ ዞር አደረገችበት ወደ ግብዣው አብሯት ባለመሔዱ የተቆጣች መሰለውና እጁን ከትከሻዋ ጣል አድርጎ ፈገግ አለ "
👍12
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ወጀቡ እስኪጠፋ ወለሉ ላይ ተቃቅፈው ቆዩና ‹‹መርቪን አልጋው ላይ
እንውጣ ከወለሉ ይልቅ እዚያ ይመቸናል›› አለ፡
ናንሲ በመስማማት ራሷን ነቀነቀች፡፡ ከዚያም በጉልበቷ እየዳኸች
አልጋው ላይ ወጣች፡፡ መርቪንም ተከተላትና አልጋው ላይ አብሯት ወጣ፡፡
እሱም እቅፍ አድርጎ ያዛት፡፡
በወጀቡ ምክንያት አይሮፕላኑ በተናወጠ ቁጥር ልክ መርከበኛ የጀልባ
ውን ምሰሶ እንደሚይዝ ሁሉ ናንሲ መርቪንን ጭምቅ አድርጋ ትይዛለች፡፡
ወጀቡ ሲቀንስና ዘና ስትል እሱም ሰውነቷን በፍቅር ይነካካቸዋል ከዚያ ትንሽ ቆየችና እንቅልፍ ይዟት ሄደ፡፡.
በሩ ተቆርቁሮ «አስተናጋጅ መቷል» የሚል ድምፅ ስትሰማ ከእንቅልፏ ነቃች።
ዓይኖቿን ስትከፍታቸው መርቪን ደረት ላይ መተኛቷን አወቀች
‹ወይ አምላኬ! አለች እየተርበተበተች፡
መርቪን ከተኛችበት እንድትነሳ በእጁ ገፋ አደረጋትና ‹‹ትንሽ ጠብቀን
አስተናጋጅ›› አለ፡፡
ከበሩ ውጭ የቆመው አስተናጋጅ በተደናገጠ ድምፅ እሺ ጌታዬ
እጠብቃለሁ›› አለ፡፡
መርቪን ከአልጋው ወረደና በአልጋ ልብስ ናንሲን ሸፈናት::
በዚህ አድራጎቱ በሆዷ አመሰገነችው፡፡ አስተናጋጁ እንዳያያት ፊቷን ወደ ግድግዳው አዞረች፡፡
መርቪን በሩን ሲከፍት አስተናጋጁ ገባና ‹‹እንዴት አደራችሁ›› አለ በፈገግታ፡፡
የትኩስ ቡና መዓዛ ናንሲን አወዳት፡፡ ‹‹በእንግሊዝ የሰዓት አቆጣጠር
የሶስት ሰዓት ተኩል ወደ ኋላ ነው ማለት ነው?›› አለ አስተናጋጁን
‹‹ልክ ነው ጌታዬ የኒውፋውንድ ላንድ የሰዓት አቆጣጠር ከግሪንዊች
የሰዓት አቆጣጠር ሶስት ሰዓት ተኩል ወደ ኋላ ይዘገያል፡››
‹‹መቼም የአየር መንገዶችን የጉዞ መርሃ ግብር ለሚያዘጋጁ ሰዎች ይህ የሰዓት አቆጣጠር ችግር
ሳይፈጥርባቸው አይቀርም፡፡ ባህር ላይ ለማረፍ ምን
ያህል ሰዓት ይቀረናል?›› ሲል ጠየቀ መርቪን
‹‹ከግማሽ ሰዓት በኋላ እናርፋለን፡ ከመርሃ ግብሩ አንድ ሰዓት ጉዟችን
የዘገየው በወጀቡ ምክንያት ነው›› አለና አስተናጋጁ በሩን ዘግቶ ወጣ፡
ናንሲ በሩ ከተዘጋ በኋላ ‹የመስኮቱን መጋረጃ ክፈተው፡ ነግቷል››
አለችው:፡ መርቪን ቡና ሲቀዳ የትናንት ምሽት አዳራቸው ፊቱ ላይ መጥቶ
ድቅን አለ፡፡ ወጀቡ በተነሳ ቁጥር መርቪን እጇን የሚይዛት፣ ወለሉ ላይ
የሚወድቁት፣ የመርቪን እጆች ጡቶቿን ሲጨብጥ፣ አይሮፕላኑ ሲናወጥ፣
እሱ ደረት ላይ ልጥፍ የምትለውና እየደባበሰ የሚያስተኛት ትዝ አላት:
ይህን ሰው በጣም ወድጄዋለሁ› አለች በሆዷ።
‹‹ቡና እንደወረደ ወይስ ከወተት ጋር ነው የምትፈልጊው?›› ሲል
ጠየቃት፡፡
‹‹ጥቁር ቡና ይሁንልኝ፡ ስኳር አልፈልግም››
‹‹እንደ እኔ›› አለና ቡናዋን አቀበላት ናንሲ አመስግና ቡናዋን ጠጣች፡፡
ናንሲ ስለ መርቪን በደንብ ማወቅ ፈለገች፡፡ ቡናውን እየጠጣ ስለእሱ ልማዶች ግምቷን አስቀመጠች፡፡ ቴኒስ ይጫወታል፣ ልብ ወለድ ብዙ ማንበብ አይወድም፣ ገበያ መሄድም እንደዚሁ፣ ቁማር ጨዋታ የሚሳካለት ይመስላል፣ ዳንስ ግን የሚችል አይመስልም፡፡›
‹‹ምንድን ነው የምታውጠነጥኚው?›› ሲል
ጠየቀ ለሕይወት ኢንሹራንስ አደገኛ እንደሆንኩ አድርገሽ የምታይኝ መሰለኝ፡፡››
ናንሲ ቀልዱ አሳቃት፡፡ ‹‹ምን አይነት ሙዚቃ ነው የምትወደው?›› ለሙዚቃ ጆሮ አልሰጥም›› አለ ‹‹መደነስ ባልጠላም ጥሩ ደናሽ ግን አይደለሁም፡፡ አንቺስ?››
እኔ ድሮ ደንሼያለሁ፡መደነስም ነበረብኝ፡፡ እሁድ እሁድ ሱፍ ከሚለብሱ ወንዶች ልጆች ጋር በዳንስ ትምህርት ቤት ዳንስ እማር ነበር፡፡ከላይኛው መደብ የቦስተን ማህበረሰቦች ጋር ለመግባባት ብቸኛው መንገድ ይህ ብቻ እንደሆነ እናቴ ትነግረኝ ነበር፡ እኔ ግን ከዛ ማህበረሰብ ውስጥ
ብገባ ባልገባ ግድ አልነበረኝም፡: የኔ ቀልብ ያለው ከአባቴ ፋብሪካ ጋር ነው፡፡ እናቴ ደግሞ ይሄን ባህሪዬን አትወደውም ነበር፡››
ሁለቱ አዲስ ፍቅረኛሞች ተያዩ፡፡ መርቪንም ትናንት ማታ እንዴት ሲላፉና ሲላላሱ እንዳመሹ እንደሚያስብ ነቃችበት፡፡ ይህም ሀሳብ እፍረት
ውስጥ ከተታትና ፊቷን ወደ መስኮቱ ስታዞር መሬት ታያት፡፡ አይሮፕላኑ
ቦትውድ ሲያርፍ ህይወቷን የሚለውጠውን የስልክ ጥሪ ማድረግ እንዳለባት ትዝ አላት፡ ‹‹ደርሰናል›› አለችና ከመኝታዋ ዘላ ተነሳች ‹‹ልብሴን ልልበስ›› አለች፡፡
‹‹እኔ ቀድሜ ልውጣ›› አለ መርቪን ‹‹ለአንቺ ጥሩ ነው››
እሺ፧ አሁንስ ምን ቀልብ አለኝ አለች በሀሳቧ። ይህን ለእሱ አልነገረችውም፡፡ መርቪን ልብሱን ስበሰበ፡፡ በሩን ከፍቶ ሊወጣ ሲል
ተጠራጠረና ቆመ፡፡ እሷም እንደገና ሊስማት እንደፈለገ አውቃ ወደ እሱ ሄደችና ከንፈሯን ሰጠችው፡፡ ‹‹ሌሊቱን በሙሉ እቅፍ አድርገህ ስላስተኛኸኝ
አመሰግንሃለሁ›› አለችው:
መርቪን ከአንገቱ ዝቅ አለና ሳማት፡፡ አሳሳሙ ልስልስ ያለ ነበር፡ አፏን በአፉ ግጥም አድርጎ ነው የሳማት፡፡ እየተሳሳሙ ትንሽ ቆዩና ተላቀቁ፡፡
ናንሲ በሩን ከፍታ ያዘችለትና ወጥቶ ሄደ፡፡
በሩን እንደዘጋች የደስታ ሲቃ ተናነቃት፡ ከዚህ ሰው ፍቅር ሊይዘኝ ነው አለች፡ በመስኮቱ ስታማትር አይሮፕላኑ ቀስ በቀስ እየወረደ ነው፡፡
መፍጠን አለባት፡፡
መስታወቱ ፊት ቆማ ፀጉሯን ቶሎ አሰረችና የመዋቢያ ዕቃዎቿን ይዛ የሙሽሮቹ ክፍል አጠገብ ወደሚገኘው ወደ ሴቶች መታጠቢያ ቤት ሄደች፡፡እዚያ ሉሉ ቤልንና አንድ ሌላ ሴት አገኘች፡፡ የመርቪን ሚስት ግን የለችም:
ናንሲ ፊቷን እየታጠበች ጧት ከመርቪን ጋር ያደረገችውን ውይይት
አስታወሰች፡፡ እሱን ስታስብ ደስታ ቢሰማትም ደስታው የተሟላ ባለመሆኑ
ከጭንቀት ሊገላግላት አልቻለም፡፡ ስለሚስቱ ምንም አላለም፡፡ ትናንት ማታ ስለእሷ ስትጠይቀው ድንግርግር እንዳለው ነው የነገራት፡፡ ከዚያ በኋላ ግን
ይወዳት ይሆን? ትናንት ማታ ሌሊቱን ሙሉ ደረቱ ላይ ለጥፎ ነው ያሳደራት ይህ ብቻውን ጋብቻን ይፍቃል ማለት ግን አይደለም፡
እኔ የምፈልገው ምንድን ነው? ስትል ራሷን ጠየቀች፡፡ ‹መርቪንን እንደገና ማግኘት እፈልጋለሁ ከእሱ ጋር ድብቅ ወዳጅነት ልመስርት?ታዲያ ለኔ ብሎ ጋብቻውን እንዲያፈርስ እፈልጋለሁ? ከአንድ ሌሊት
ወሲባዊ ልፊያና መሳሳም በኋላ ይህን እንዴት ማወቅ እችላለሁ?
ሊፕስቲክ ለመቀባት መስታወቱ ላይ አፈጠጠች ናንሲ መጠራጠርሽን አቁሚ
ስትል ለራሷ አሳሰበች እውነታውን ታውቂዋለሽ፤ ይሄን ሰው በጣም ፈልገሽዋል፧ ከአስር ዓመት ወዲህ እጅሽን የሰጠሸው ለዚህ ሰው ነው፡:
አሁን አርባ አመትሽን ደፍነሻል፡ አሁን ተገቢውን ሰው አግኝተሻል፡ እዚህ
እዚያ መርገጥሽን ትተሽ ይህን ሰው በእጅሽ አድርጊ፡፡›
ሰውነቷ ላይ ሽቶ አርከፈከፈችና ወጣች፡
ስትወጣ ከመታጠቢያ ቤቱ አጠገብ የተቀመጡትን ናት ሪጅዌይና ወንድሟን ፒተርን አገኘቻቸው ናት ‹‹ደህና አደርሽ ናንሲ›› አላት::
ይህን ስትሰማ ከአምስት ዓመት በፊት በዚህ ሰው የነበራትን ስሜት
አስታወሳት፡፡ እኔ ከእሱ ፍቅር ይዞኝ ነበር፡፡ እሱ ግን ከእኔ ይልቅ የፈለገው
ብላክ ቡትስ ኩባንያን ነበር፡፡ አሁንም ኩባንያውን በእጁ ለማስገባት
የሚፈልገውን ያህል እኔን አይፈልገኝም፡፡ ለሰላምታው በራስ ንቅናቄ ብቻ
አፀፋዊ ሰላምታ ሰጥታው ወደ ክፍሏ ሄደች፡፡
አስተናጋጆቹ መኝታዎቹን ወደ ሶፋነት ለውጠዋቸዋል። መርቪን ጢሙን ተላጭቶና በነጭ ሽሚዝ ላይ ሱፍ ልብሱን ለብሶ ሶፋ ላይ ቁጭ ብሏል፡፡ ‹‹በመስኮት ተመልከች ደርሰናል›› አላት፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ወጀቡ እስኪጠፋ ወለሉ ላይ ተቃቅፈው ቆዩና ‹‹መርቪን አልጋው ላይ
እንውጣ ከወለሉ ይልቅ እዚያ ይመቸናል›› አለ፡
ናንሲ በመስማማት ራሷን ነቀነቀች፡፡ ከዚያም በጉልበቷ እየዳኸች
አልጋው ላይ ወጣች፡፡ መርቪንም ተከተላትና አልጋው ላይ አብሯት ወጣ፡፡
እሱም እቅፍ አድርጎ ያዛት፡፡
በወጀቡ ምክንያት አይሮፕላኑ በተናወጠ ቁጥር ልክ መርከበኛ የጀልባ
ውን ምሰሶ እንደሚይዝ ሁሉ ናንሲ መርቪንን ጭምቅ አድርጋ ትይዛለች፡፡
ወጀቡ ሲቀንስና ዘና ስትል እሱም ሰውነቷን በፍቅር ይነካካቸዋል ከዚያ ትንሽ ቆየችና እንቅልፍ ይዟት ሄደ፡፡.
በሩ ተቆርቁሮ «አስተናጋጅ መቷል» የሚል ድምፅ ስትሰማ ከእንቅልፏ ነቃች።
ዓይኖቿን ስትከፍታቸው መርቪን ደረት ላይ መተኛቷን አወቀች
‹ወይ አምላኬ! አለች እየተርበተበተች፡
መርቪን ከተኛችበት እንድትነሳ በእጁ ገፋ አደረጋትና ‹‹ትንሽ ጠብቀን
አስተናጋጅ›› አለ፡፡
ከበሩ ውጭ የቆመው አስተናጋጅ በተደናገጠ ድምፅ እሺ ጌታዬ
እጠብቃለሁ›› አለ፡፡
መርቪን ከአልጋው ወረደና በአልጋ ልብስ ናንሲን ሸፈናት::
በዚህ አድራጎቱ በሆዷ አመሰገነችው፡፡ አስተናጋጁ እንዳያያት ፊቷን ወደ ግድግዳው አዞረች፡፡
መርቪን በሩን ሲከፍት አስተናጋጁ ገባና ‹‹እንዴት አደራችሁ›› አለ በፈገግታ፡፡
የትኩስ ቡና መዓዛ ናንሲን አወዳት፡፡ ‹‹በእንግሊዝ የሰዓት አቆጣጠር
የሶስት ሰዓት ተኩል ወደ ኋላ ነው ማለት ነው?›› አለ አስተናጋጁን
‹‹ልክ ነው ጌታዬ የኒውፋውንድ ላንድ የሰዓት አቆጣጠር ከግሪንዊች
የሰዓት አቆጣጠር ሶስት ሰዓት ተኩል ወደ ኋላ ይዘገያል፡››
‹‹መቼም የአየር መንገዶችን የጉዞ መርሃ ግብር ለሚያዘጋጁ ሰዎች ይህ የሰዓት አቆጣጠር ችግር
ሳይፈጥርባቸው አይቀርም፡፡ ባህር ላይ ለማረፍ ምን
ያህል ሰዓት ይቀረናል?›› ሲል ጠየቀ መርቪን
‹‹ከግማሽ ሰዓት በኋላ እናርፋለን፡ ከመርሃ ግብሩ አንድ ሰዓት ጉዟችን
የዘገየው በወጀቡ ምክንያት ነው›› አለና አስተናጋጁ በሩን ዘግቶ ወጣ፡
ናንሲ በሩ ከተዘጋ በኋላ ‹የመስኮቱን መጋረጃ ክፈተው፡ ነግቷል››
አለችው:፡ መርቪን ቡና ሲቀዳ የትናንት ምሽት አዳራቸው ፊቱ ላይ መጥቶ
ድቅን አለ፡፡ ወጀቡ በተነሳ ቁጥር መርቪን እጇን የሚይዛት፣ ወለሉ ላይ
የሚወድቁት፣ የመርቪን እጆች ጡቶቿን ሲጨብጥ፣ አይሮፕላኑ ሲናወጥ፣
እሱ ደረት ላይ ልጥፍ የምትለውና እየደባበሰ የሚያስተኛት ትዝ አላት:
ይህን ሰው በጣም ወድጄዋለሁ› አለች በሆዷ።
‹‹ቡና እንደወረደ ወይስ ከወተት ጋር ነው የምትፈልጊው?›› ሲል
ጠየቃት፡፡
‹‹ጥቁር ቡና ይሁንልኝ፡ ስኳር አልፈልግም››
‹‹እንደ እኔ›› አለና ቡናዋን አቀበላት ናንሲ አመስግና ቡናዋን ጠጣች፡፡
ናንሲ ስለ መርቪን በደንብ ማወቅ ፈለገች፡፡ ቡናውን እየጠጣ ስለእሱ ልማዶች ግምቷን አስቀመጠች፡፡ ቴኒስ ይጫወታል፣ ልብ ወለድ ብዙ ማንበብ አይወድም፣ ገበያ መሄድም እንደዚሁ፣ ቁማር ጨዋታ የሚሳካለት ይመስላል፣ ዳንስ ግን የሚችል አይመስልም፡፡›
‹‹ምንድን ነው የምታውጠነጥኚው?›› ሲል
ጠየቀ ለሕይወት ኢንሹራንስ አደገኛ እንደሆንኩ አድርገሽ የምታይኝ መሰለኝ፡፡››
ናንሲ ቀልዱ አሳቃት፡፡ ‹‹ምን አይነት ሙዚቃ ነው የምትወደው?›› ለሙዚቃ ጆሮ አልሰጥም›› አለ ‹‹መደነስ ባልጠላም ጥሩ ደናሽ ግን አይደለሁም፡፡ አንቺስ?››
እኔ ድሮ ደንሼያለሁ፡መደነስም ነበረብኝ፡፡ እሁድ እሁድ ሱፍ ከሚለብሱ ወንዶች ልጆች ጋር በዳንስ ትምህርት ቤት ዳንስ እማር ነበር፡፡ከላይኛው መደብ የቦስተን ማህበረሰቦች ጋር ለመግባባት ብቸኛው መንገድ ይህ ብቻ እንደሆነ እናቴ ትነግረኝ ነበር፡ እኔ ግን ከዛ ማህበረሰብ ውስጥ
ብገባ ባልገባ ግድ አልነበረኝም፡: የኔ ቀልብ ያለው ከአባቴ ፋብሪካ ጋር ነው፡፡ እናቴ ደግሞ ይሄን ባህሪዬን አትወደውም ነበር፡››
ሁለቱ አዲስ ፍቅረኛሞች ተያዩ፡፡ መርቪንም ትናንት ማታ እንዴት ሲላፉና ሲላላሱ እንዳመሹ እንደሚያስብ ነቃችበት፡፡ ይህም ሀሳብ እፍረት
ውስጥ ከተታትና ፊቷን ወደ መስኮቱ ስታዞር መሬት ታያት፡፡ አይሮፕላኑ
ቦትውድ ሲያርፍ ህይወቷን የሚለውጠውን የስልክ ጥሪ ማድረግ እንዳለባት ትዝ አላት፡ ‹‹ደርሰናል›› አለችና ከመኝታዋ ዘላ ተነሳች ‹‹ልብሴን ልልበስ›› አለች፡፡
‹‹እኔ ቀድሜ ልውጣ›› አለ መርቪን ‹‹ለአንቺ ጥሩ ነው››
እሺ፧ አሁንስ ምን ቀልብ አለኝ አለች በሀሳቧ። ይህን ለእሱ አልነገረችውም፡፡ መርቪን ልብሱን ስበሰበ፡፡ በሩን ከፍቶ ሊወጣ ሲል
ተጠራጠረና ቆመ፡፡ እሷም እንደገና ሊስማት እንደፈለገ አውቃ ወደ እሱ ሄደችና ከንፈሯን ሰጠችው፡፡ ‹‹ሌሊቱን በሙሉ እቅፍ አድርገህ ስላስተኛኸኝ
አመሰግንሃለሁ›› አለችው:
መርቪን ከአንገቱ ዝቅ አለና ሳማት፡፡ አሳሳሙ ልስልስ ያለ ነበር፡ አፏን በአፉ ግጥም አድርጎ ነው የሳማት፡፡ እየተሳሳሙ ትንሽ ቆዩና ተላቀቁ፡፡
ናንሲ በሩን ከፍታ ያዘችለትና ወጥቶ ሄደ፡፡
በሩን እንደዘጋች የደስታ ሲቃ ተናነቃት፡ ከዚህ ሰው ፍቅር ሊይዘኝ ነው አለች፡ በመስኮቱ ስታማትር አይሮፕላኑ ቀስ በቀስ እየወረደ ነው፡፡
መፍጠን አለባት፡፡
መስታወቱ ፊት ቆማ ፀጉሯን ቶሎ አሰረችና የመዋቢያ ዕቃዎቿን ይዛ የሙሽሮቹ ክፍል አጠገብ ወደሚገኘው ወደ ሴቶች መታጠቢያ ቤት ሄደች፡፡እዚያ ሉሉ ቤልንና አንድ ሌላ ሴት አገኘች፡፡ የመርቪን ሚስት ግን የለችም:
ናንሲ ፊቷን እየታጠበች ጧት ከመርቪን ጋር ያደረገችውን ውይይት
አስታወሰች፡፡ እሱን ስታስብ ደስታ ቢሰማትም ደስታው የተሟላ ባለመሆኑ
ከጭንቀት ሊገላግላት አልቻለም፡፡ ስለሚስቱ ምንም አላለም፡፡ ትናንት ማታ ስለእሷ ስትጠይቀው ድንግርግር እንዳለው ነው የነገራት፡፡ ከዚያ በኋላ ግን
ይወዳት ይሆን? ትናንት ማታ ሌሊቱን ሙሉ ደረቱ ላይ ለጥፎ ነው ያሳደራት ይህ ብቻውን ጋብቻን ይፍቃል ማለት ግን አይደለም፡
እኔ የምፈልገው ምንድን ነው? ስትል ራሷን ጠየቀች፡፡ ‹መርቪንን እንደገና ማግኘት እፈልጋለሁ ከእሱ ጋር ድብቅ ወዳጅነት ልመስርት?ታዲያ ለኔ ብሎ ጋብቻውን እንዲያፈርስ እፈልጋለሁ? ከአንድ ሌሊት
ወሲባዊ ልፊያና መሳሳም በኋላ ይህን እንዴት ማወቅ እችላለሁ?
ሊፕስቲክ ለመቀባት መስታወቱ ላይ አፈጠጠች ናንሲ መጠራጠርሽን አቁሚ
ስትል ለራሷ አሳሰበች እውነታውን ታውቂዋለሽ፤ ይሄን ሰው በጣም ፈልገሽዋል፧ ከአስር ዓመት ወዲህ እጅሽን የሰጠሸው ለዚህ ሰው ነው፡:
አሁን አርባ አመትሽን ደፍነሻል፡ አሁን ተገቢውን ሰው አግኝተሻል፡ እዚህ
እዚያ መርገጥሽን ትተሽ ይህን ሰው በእጅሽ አድርጊ፡፡›
ሰውነቷ ላይ ሽቶ አርከፈከፈችና ወጣች፡
ስትወጣ ከመታጠቢያ ቤቱ አጠገብ የተቀመጡትን ናት ሪጅዌይና ወንድሟን ፒተርን አገኘቻቸው ናት ‹‹ደህና አደርሽ ናንሲ›› አላት::
ይህን ስትሰማ ከአምስት ዓመት በፊት በዚህ ሰው የነበራትን ስሜት
አስታወሳት፡፡ እኔ ከእሱ ፍቅር ይዞኝ ነበር፡፡ እሱ ግን ከእኔ ይልቅ የፈለገው
ብላክ ቡትስ ኩባንያን ነበር፡፡ አሁንም ኩባንያውን በእጁ ለማስገባት
የሚፈልገውን ያህል እኔን አይፈልገኝም፡፡ ለሰላምታው በራስ ንቅናቄ ብቻ
አፀፋዊ ሰላምታ ሰጥታው ወደ ክፍሏ ሄደች፡፡
አስተናጋጆቹ መኝታዎቹን ወደ ሶፋነት ለውጠዋቸዋል። መርቪን ጢሙን ተላጭቶና በነጭ ሽሚዝ ላይ ሱፍ ልብሱን ለብሶ ሶፋ ላይ ቁጭ ብሏል፡፡ ‹‹በመስኮት ተመልከች ደርሰናል›› አላት፡፡
👍19
#ባል_አስይዞ_ቁማር
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
..ይገርማል እሱ በማንኛውም አእምሮዋ በሚያመርታቸው ሀሳቦች ውስጥ የሆነ ቦታ ፈልጎ ተሸንቅሮ ሲወጣ ነው የምታየው....ስለሰማይም ታስብ ስለምድር…ስለእግዚያብሄር ይሁን ስለሰይጣን እሱ አለበት….፡፡.ደግሞ በሀሳቧ ብቻ አይደለም በህልሟም ጭምር እንጂ…..ህልሟ እኮ ስለ ምንም ሊሆን ይችላል ብቻ እሱ አለበት…ለምሳሌ እሷ እናቷ መኝታ ቤት አልጋዋ ላይ ወጥታ ፀጉሯን ስትዳብሳት በህልሟ ብታይ እሱም ወይ በመስኮት ተደብቆ ሲያያት..ወይ ደግሞ እራሱን ወደቢራቢሮ ቀይሮ ክንፉን እያማታ መጥቶ ግንባራ ላይ ሲያርፍ ታየዋለች፡፡ይሄ ሁሌ ለራሷም ሳታስበው ግርም ይላታል፡፡እንዴት የሆነ ቦታ ላይ አትረሳውም…እንዴት የሆነ ሀሳብ አሰናድታ አጣጥፋ ስትጨርስ ድንገት ከሆነ ቦታ ተስፈንጥሮ መጥቶ ከላይ በቀላሉ ይደረባል…?ይሄ እንግዲህ በዚህ ከተማ በዚህ ቤት ውስጥ ሲኖር ነበር..አሁንስ ሁሉን ነገር ጣጥሎ ከሄደ በኃላ…….ምንድነው የምትሆነው?የቀንም ሆነ የሌት ህልሟ እንደሆነ ይቀጥላል? ከቀጠለስ እንዴት ልትቋቋመው ትችላለች?
እጇን ዘረጋችና አጠገቧ የተኛችውን የጊፊቲ ሆድ ላይ በቀስታ አሳረፈች…ጊፍቲም ከትራሷ ገልበጥ አለችና ፊቷን ወደእሷ ዞራ በሀዘኔታ አየቻት፡፡
‹‹ምን አለ እኔም እንደአንቺ ለቃልዬ አርግዤ ቢሆን…ማለት ልጅ አስረግዞኝ ጥሎልኝ ቢሄድ?››
‹‹እኔም አንድ ነገር ልንገርሽ…››
‹‹ምንድነው ንገሪኝ››
‹የቃልዬን እስከ ወዲያኛው ጥሎኝ መሄድን ስሰማ ወደውስጤ ከመጣው የፀፀት ሀሳብ አንዱ ምን አለ ይሄ የፀነስኩት ልጅ የቃልዬ በሆነ የሚል ነበር..እርግጥ መድህኔ በጣም ጥሩ ኃላፊነት የሚሰማው መልካም አባት እንደሚሆን አውቃለሁ…እሱን ስላገኘሁም እራሴን እንደእድለኛ ነው የምቆጥረው…የልጅነት ህልሜንና የዘመናት ፍላጎቴን ሁሉ ሊያሞላልኝ የሚችል ሰው ነው…ግን መድህኔን የማፈቅርበት ጥልቀት የኩሬ ያህል ሲሆን የቃልዬ ግን ውቅያኖስ አይነት ነው..እና ለዛ ነው እንደዛ ልመኝ የቻልኩት››
ዝም ብዬ ፈዛ አየቻት..ይሄን የተናገረችው ከቀናቶች በፊት በሰላሙ ጊዜ ቢሆን ኖሮ በርግጠኝነት ልዩ አንገቷን ፈጥርቃት ልትገላት ሁሉ ትችል ነበር..አሁን ግን ያንን ማድረጉም ብቻ ሳይሆን እንደዛ አይነት ስሜት ማስተናገዱም ጥቅም አልባ እንደሆነ ተረድታለች....በዛ ለይ በመንፈስም ሆነ በስጋዋ ደንዝዛለች…
‹‹ግን ከቃልዬ ይሄን ሁሉ አመት ሳታረግዤ እንዴት በዚህች በጥቂት ወራት ከመድህኔ ልታረግዢ ቻልሽ?፡፡››
‹‹ከቀል ጋር በትንፋሽ ነው ማረግዘው?…››
‹‹ማለት….?››
‹‹እኔና ቃል እኮ ወሲብ ፈፅመን አናውቅም››
‹‹ማለት…ብዙ ቀን እኮ እሱ ጋር አድረሽ እንደወጣሽ… ሲያደክመኝ እንዳደረ ምናምን እያልሽ ስትጎሪርብኝ ነበር››
‹‹ፈርቼሽ ነዋ…..ቃልዬን እንዳትመኚውና እንዳትቀሚኝ ..ተስፋ ላስቆርጥሽ ብዬ ነው…ማለት ከአመታት በፊት አብሬው ብዙ ጊዜ አድር ነበር..በኃላ ግን ዝም ብሎ ማደሩ ስቃይ ስለሆነብኝ ወስኜ አቆምኩ…..››
‹‹አረ የምን ጉድ ነው..ቆይ ለምን…..?››
‹‹ምነው ገረመሽ..አንቺስ ከመድህኔ ጋር ለምን;?››
‹‹እኔ እንጃ ብቻ የእናንተን በጣም ደጋግሜ ስላመነዠግኩት ነው መሰለኝ አልተዋጠልኝም…››
‹‹መድህኔን ስለወደድኩት..ወይም ቃልዬ ሀብታም ስላልሆነ ይመስልሻል ከቃልዬ ጋር አቋርጬ ከመድህኔ ጋር የሆንኩት ነው ወይስ አንቺ ስላለስፈራራሺኝ…?››
‹‹እና ለምንድነው?››
‹‹ሳላውቅ ድንገት ከመድህኔ ጋር ተሳሳትኩና ወሲብ ፈፀምኩ..ድንግልናዬን አስረከብኩት ….ወደቃልዬ ጋር እንዴት ልመሰለስ .. ?ሌላ ሰው ቢሆን ችግር የለውም ቃልዬ ግን?
‹‹ቃል ምን ይልሻል..?ምንም አይልሽም እኮ ነበር አንደውም በግልፅ ነበር ይቅርታ የጠየቀሽ፡››
‹‹አውቃለሁ ..ችግሩም እሱ ነው….እኔ በአእምሮው ካለሁበት ቦታ ተንሸራትቼ ወርጄያለሁ.ቃልዬ...የወርቅ ካባ አድርጎ በብር የተለበጠ ጫማ ተጫምቶ ወደቤቴ ሲመጣ ውስጤ በሀሤት ትደንሳለች ...ድንግልናዬን በክብር ልሰጠው ለዘመናት ጎጉቼያለሁ ።.እሱ ፍጽም ድንግል እንደሆነ አውቃለሁ.....ማወራሽ ስለስጋዊ ድንግልና አይደለም….ለዛ ግድ የለኝም...ልብ ከቆሻሻ ሀሳብ ጋር ያልተዋሰበ ንፅህ ፤ከክደትና ከማጭበርበር ጋር ያልተጋደመ ክብር ነው ።ለዚህም ማረጋገጫው እስሬ ሆኖ ሲያወራኝ ልቤ ውስጥ ብርሀን ሲፍለቀለቅ ይታወቅኛል….የሆነ አካሉ የሰውነቴን ጫፍ ሲነካው ነፍሴ ድረስ የሚዘልቅ ደስታ ይሰማኛል……ድንገት አግኝቼው ሰላም ሊለኝ ከንፈሩ ጉንጬን በስሱ ሲነካው እንኳን .....ከልቤ የፍቅር ደም ሲንጠባጠብ ይሰማኛል ...
‹‹ከዚህ በፊት ስለእሱ ምን እንደሚሰማኝ ነግሬሽ ነበር …? የእኔን ስሜት እኮ ነው እየነገርሺኝ ያለሽው…››
‹‹አየሽልኝ..ቃልዬ ማለት እንዲህ ነው..ሁለት ሴቶችን ጫፋቸውን ሳይነካ በተመሳሳይ የእብደት በሚመስል ስሜት አንዲያፈቅሩት ማድረግ የሚችል የተለየ ሰው ነው፡፡እሱ ለእኔ መስታወቴ ነው.. ፊት ለፊቴ ተቀምጦ በተመስጦ ሳየው በጥልቀት ርቄ ሄዳለሁ…. እያንዳንዷን የልጅነት ጊዜዬን በምልስት አስታውሳለሁ… ሀዘኔንና ደስታዬን መልሼ አጣጥማለሁ…. እንዴት እንደተሰራው…? የት ጋር ማደግ እንደጀመርኩና? የት ጋር ደግሞ እንደተሰበርኩ? ሁሉ እንዳስታውስ ያደርገኛል…እናም በዛ ምክንያት ቃልዬን ሳገኝ ነፍሴ ሀሴት ታርጋለች…ውስጤ ይፍነከነካል..፡፡ግን ይሄ ስሜት ሁሌ አይደለም የሚያስደስተኝ ..አንዳንዴ ትናንቴ ፈፅሞ የሚያስጠላኝ ጊዜ አለ..አንገቴን ወደኃላ አዙሬ አይኖቼን ትናንቴ ላይ ተክዬ ማሰላሰል የሚያስከትልብኝን ህመም መቋቋም አቅም በማጣበት ጊዜ እሱን ለማግኘት ከራሴ ጋር ትግል እገባለሁ …ምክንያት ፈጥሬ እሸሸዋለሁ….
ግን የሰዓታ ክፍተት እንኳን መቆየት ተስኖኝ ግራ ይሁን ቀኝ ልቤ ላይ ብቻ በማለውቀው ቦታ በሆነ የልቤ ክፍል ብቸኝነት ይለበልበኛል…መለብለብ ብቻም ሳይሆን እብጠትና ጥዝጣዜም አለው…ግን ደግሞ መቻል እስከምችል ደረስ እችለዋለሁ…ለአንድ ወይም ለሁለት ቀን..ከዛ መተንፈስ ሲያቅተኝና ከአቅሜ በላይ ሲሆን ያለምን ማቅማማት ወደ አለበት በርሬ እሄዳለሁ ፡፡ፊቱ እገተራለሁ…የተጨማደደ ፊቱ በደስታ ፀደል ሲፈካ…ተከርችሞ የነበረ ጥርሶቹ ተፈልቅቀው መሳቅ ሲጀምሩ አይና እደሰታለሁ....ተንደርድሬ ሄጄ እንጠለጠልበታለሁ….ያለምንም ቅሬታና ወቀሳ ወደላይ አንጠልጥሎ ልክ እንደእርግብ በአየር ላይ ያንሳፍፈኛል…..እና አሁን ያ የልጅነተ መስታወቴ ነው የተሰነጣጠቀዉ… የትዝታ ድልድዬ ነው ተንዶ የተሰበረው…..ወደትናንቴ ለመሻገር በጣም ይከብደኛል….ግማሽ ሆኜያለሁ
‹እውነትሽን ነው…..አሁን ሳስበው ቢነካንስ ኖሮ…ማለቴ ያው ነካክቶን ጥሎን ሂዶ ቢሆንስ..?››
‹‹እሰከ መጨረሻ ያበቃልን ነበራ…››ብላ መለሰችላት፡፡
‹‹እኔ እኮ አሁንም እስከመጨረሻው ነው ያበቃልኝ…›
‹‹ቆይ ግን ወደ ወሬሽ ልመልስሽና..ቃልዬንም እኮ ከዚህ በፊት ማለቴ አንቺ ከመድሀኔ ጋር ተገናኝተሸ ከመጀመርሽ በፊት ስለሁለታችሁ ግንኙነት ጠይቄው ነበር…››
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
..ይገርማል እሱ በማንኛውም አእምሮዋ በሚያመርታቸው ሀሳቦች ውስጥ የሆነ ቦታ ፈልጎ ተሸንቅሮ ሲወጣ ነው የምታየው....ስለሰማይም ታስብ ስለምድር…ስለእግዚያብሄር ይሁን ስለሰይጣን እሱ አለበት….፡፡.ደግሞ በሀሳቧ ብቻ አይደለም በህልሟም ጭምር እንጂ…..ህልሟ እኮ ስለ ምንም ሊሆን ይችላል ብቻ እሱ አለበት…ለምሳሌ እሷ እናቷ መኝታ ቤት አልጋዋ ላይ ወጥታ ፀጉሯን ስትዳብሳት በህልሟ ብታይ እሱም ወይ በመስኮት ተደብቆ ሲያያት..ወይ ደግሞ እራሱን ወደቢራቢሮ ቀይሮ ክንፉን እያማታ መጥቶ ግንባራ ላይ ሲያርፍ ታየዋለች፡፡ይሄ ሁሌ ለራሷም ሳታስበው ግርም ይላታል፡፡እንዴት የሆነ ቦታ ላይ አትረሳውም…እንዴት የሆነ ሀሳብ አሰናድታ አጣጥፋ ስትጨርስ ድንገት ከሆነ ቦታ ተስፈንጥሮ መጥቶ ከላይ በቀላሉ ይደረባል…?ይሄ እንግዲህ በዚህ ከተማ በዚህ ቤት ውስጥ ሲኖር ነበር..አሁንስ ሁሉን ነገር ጣጥሎ ከሄደ በኃላ…….ምንድነው የምትሆነው?የቀንም ሆነ የሌት ህልሟ እንደሆነ ይቀጥላል? ከቀጠለስ እንዴት ልትቋቋመው ትችላለች?
እጇን ዘረጋችና አጠገቧ የተኛችውን የጊፊቲ ሆድ ላይ በቀስታ አሳረፈች…ጊፍቲም ከትራሷ ገልበጥ አለችና ፊቷን ወደእሷ ዞራ በሀዘኔታ አየቻት፡፡
‹‹ምን አለ እኔም እንደአንቺ ለቃልዬ አርግዤ ቢሆን…ማለት ልጅ አስረግዞኝ ጥሎልኝ ቢሄድ?››
‹‹እኔም አንድ ነገር ልንገርሽ…››
‹‹ምንድነው ንገሪኝ››
‹የቃልዬን እስከ ወዲያኛው ጥሎኝ መሄድን ስሰማ ወደውስጤ ከመጣው የፀፀት ሀሳብ አንዱ ምን አለ ይሄ የፀነስኩት ልጅ የቃልዬ በሆነ የሚል ነበር..እርግጥ መድህኔ በጣም ጥሩ ኃላፊነት የሚሰማው መልካም አባት እንደሚሆን አውቃለሁ…እሱን ስላገኘሁም እራሴን እንደእድለኛ ነው የምቆጥረው…የልጅነት ህልሜንና የዘመናት ፍላጎቴን ሁሉ ሊያሞላልኝ የሚችል ሰው ነው…ግን መድህኔን የማፈቅርበት ጥልቀት የኩሬ ያህል ሲሆን የቃልዬ ግን ውቅያኖስ አይነት ነው..እና ለዛ ነው እንደዛ ልመኝ የቻልኩት››
ዝም ብዬ ፈዛ አየቻት..ይሄን የተናገረችው ከቀናቶች በፊት በሰላሙ ጊዜ ቢሆን ኖሮ በርግጠኝነት ልዩ አንገቷን ፈጥርቃት ልትገላት ሁሉ ትችል ነበር..አሁን ግን ያንን ማድረጉም ብቻ ሳይሆን እንደዛ አይነት ስሜት ማስተናገዱም ጥቅም አልባ እንደሆነ ተረድታለች....በዛ ለይ በመንፈስም ሆነ በስጋዋ ደንዝዛለች…
‹‹ግን ከቃልዬ ይሄን ሁሉ አመት ሳታረግዤ እንዴት በዚህች በጥቂት ወራት ከመድህኔ ልታረግዢ ቻልሽ?፡፡››
‹‹ከቀል ጋር በትንፋሽ ነው ማረግዘው?…››
‹‹ማለት….?››
‹‹እኔና ቃል እኮ ወሲብ ፈፅመን አናውቅም››
‹‹ማለት…ብዙ ቀን እኮ እሱ ጋር አድረሽ እንደወጣሽ… ሲያደክመኝ እንዳደረ ምናምን እያልሽ ስትጎሪርብኝ ነበር››
‹‹ፈርቼሽ ነዋ…..ቃልዬን እንዳትመኚውና እንዳትቀሚኝ ..ተስፋ ላስቆርጥሽ ብዬ ነው…ማለት ከአመታት በፊት አብሬው ብዙ ጊዜ አድር ነበር..በኃላ ግን ዝም ብሎ ማደሩ ስቃይ ስለሆነብኝ ወስኜ አቆምኩ…..››
‹‹አረ የምን ጉድ ነው..ቆይ ለምን…..?››
‹‹ምነው ገረመሽ..አንቺስ ከመድህኔ ጋር ለምን;?››
‹‹እኔ እንጃ ብቻ የእናንተን በጣም ደጋግሜ ስላመነዠግኩት ነው መሰለኝ አልተዋጠልኝም…››
‹‹መድህኔን ስለወደድኩት..ወይም ቃልዬ ሀብታም ስላልሆነ ይመስልሻል ከቃልዬ ጋር አቋርጬ ከመድህኔ ጋር የሆንኩት ነው ወይስ አንቺ ስላለስፈራራሺኝ…?››
‹‹እና ለምንድነው?››
‹‹ሳላውቅ ድንገት ከመድህኔ ጋር ተሳሳትኩና ወሲብ ፈፀምኩ..ድንግልናዬን አስረከብኩት ….ወደቃልዬ ጋር እንዴት ልመሰለስ .. ?ሌላ ሰው ቢሆን ችግር የለውም ቃልዬ ግን?
‹‹ቃል ምን ይልሻል..?ምንም አይልሽም እኮ ነበር አንደውም በግልፅ ነበር ይቅርታ የጠየቀሽ፡››
‹‹አውቃለሁ ..ችግሩም እሱ ነው….እኔ በአእምሮው ካለሁበት ቦታ ተንሸራትቼ ወርጄያለሁ.ቃልዬ...የወርቅ ካባ አድርጎ በብር የተለበጠ ጫማ ተጫምቶ ወደቤቴ ሲመጣ ውስጤ በሀሤት ትደንሳለች ...ድንግልናዬን በክብር ልሰጠው ለዘመናት ጎጉቼያለሁ ።.እሱ ፍጽም ድንግል እንደሆነ አውቃለሁ.....ማወራሽ ስለስጋዊ ድንግልና አይደለም….ለዛ ግድ የለኝም...ልብ ከቆሻሻ ሀሳብ ጋር ያልተዋሰበ ንፅህ ፤ከክደትና ከማጭበርበር ጋር ያልተጋደመ ክብር ነው ።ለዚህም ማረጋገጫው እስሬ ሆኖ ሲያወራኝ ልቤ ውስጥ ብርሀን ሲፍለቀለቅ ይታወቅኛል….የሆነ አካሉ የሰውነቴን ጫፍ ሲነካው ነፍሴ ድረስ የሚዘልቅ ደስታ ይሰማኛል……ድንገት አግኝቼው ሰላም ሊለኝ ከንፈሩ ጉንጬን በስሱ ሲነካው እንኳን .....ከልቤ የፍቅር ደም ሲንጠባጠብ ይሰማኛል ...
‹‹ከዚህ በፊት ስለእሱ ምን እንደሚሰማኝ ነግሬሽ ነበር …? የእኔን ስሜት እኮ ነው እየነገርሺኝ ያለሽው…››
‹‹አየሽልኝ..ቃልዬ ማለት እንዲህ ነው..ሁለት ሴቶችን ጫፋቸውን ሳይነካ በተመሳሳይ የእብደት በሚመስል ስሜት አንዲያፈቅሩት ማድረግ የሚችል የተለየ ሰው ነው፡፡እሱ ለእኔ መስታወቴ ነው.. ፊት ለፊቴ ተቀምጦ በተመስጦ ሳየው በጥልቀት ርቄ ሄዳለሁ…. እያንዳንዷን የልጅነት ጊዜዬን በምልስት አስታውሳለሁ… ሀዘኔንና ደስታዬን መልሼ አጣጥማለሁ…. እንዴት እንደተሰራው…? የት ጋር ማደግ እንደጀመርኩና? የት ጋር ደግሞ እንደተሰበርኩ? ሁሉ እንዳስታውስ ያደርገኛል…እናም በዛ ምክንያት ቃልዬን ሳገኝ ነፍሴ ሀሴት ታርጋለች…ውስጤ ይፍነከነካል..፡፡ግን ይሄ ስሜት ሁሌ አይደለም የሚያስደስተኝ ..አንዳንዴ ትናንቴ ፈፅሞ የሚያስጠላኝ ጊዜ አለ..አንገቴን ወደኃላ አዙሬ አይኖቼን ትናንቴ ላይ ተክዬ ማሰላሰል የሚያስከትልብኝን ህመም መቋቋም አቅም በማጣበት ጊዜ እሱን ለማግኘት ከራሴ ጋር ትግል እገባለሁ …ምክንያት ፈጥሬ እሸሸዋለሁ….
ግን የሰዓታ ክፍተት እንኳን መቆየት ተስኖኝ ግራ ይሁን ቀኝ ልቤ ላይ ብቻ በማለውቀው ቦታ በሆነ የልቤ ክፍል ብቸኝነት ይለበልበኛል…መለብለብ ብቻም ሳይሆን እብጠትና ጥዝጣዜም አለው…ግን ደግሞ መቻል እስከምችል ደረስ እችለዋለሁ…ለአንድ ወይም ለሁለት ቀን..ከዛ መተንፈስ ሲያቅተኝና ከአቅሜ በላይ ሲሆን ያለምን ማቅማማት ወደ አለበት በርሬ እሄዳለሁ ፡፡ፊቱ እገተራለሁ…የተጨማደደ ፊቱ በደስታ ፀደል ሲፈካ…ተከርችሞ የነበረ ጥርሶቹ ተፈልቅቀው መሳቅ ሲጀምሩ አይና እደሰታለሁ....ተንደርድሬ ሄጄ እንጠለጠልበታለሁ….ያለምንም ቅሬታና ወቀሳ ወደላይ አንጠልጥሎ ልክ እንደእርግብ በአየር ላይ ያንሳፍፈኛል…..እና አሁን ያ የልጅነተ መስታወቴ ነው የተሰነጣጠቀዉ… የትዝታ ድልድዬ ነው ተንዶ የተሰበረው…..ወደትናንቴ ለመሻገር በጣም ይከብደኛል….ግማሽ ሆኜያለሁ
‹እውነትሽን ነው…..አሁን ሳስበው ቢነካንስ ኖሮ…ማለቴ ያው ነካክቶን ጥሎን ሂዶ ቢሆንስ..?››
‹‹እሰከ መጨረሻ ያበቃልን ነበራ…››ብላ መለሰችላት፡፡
‹‹እኔ እኮ አሁንም እስከመጨረሻው ነው ያበቃልኝ…›
‹‹ቆይ ግን ወደ ወሬሽ ልመልስሽና..ቃልዬንም እኮ ከዚህ በፊት ማለቴ አንቺ ከመድሀኔ ጋር ተገናኝተሸ ከመጀመርሽ በፊት ስለሁለታችሁ ግንኙነት ጠይቄው ነበር…››
👍89❤10😁1
#ተአምረተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
//
ሰሚራ ለዚህ ሀሳብ ውል ሳታበጅለት ማደር አልፈለገችም….. ቦርሳዋን አንጠልጥላ ተመልሳ ወደስራዋ ቦታ ተመለሰች….መመለሷ ምን እንደሚጠቅማት ለራሷም አልገባትም ..ግን በቃ ተመለሰች..እንደደረሰች ቀጥታ መላኩ ወደተኛበት ክፍል ነበር የገባችው…በሽተኛው የተኛበት ክፍል ውስጥ የተኙ ሌሎች ሶስት ታካሚዎችና እነሱን የሚያስታሙም አስታማሚወች ነበሩ…
ቀጥታ ወደተኛበት አልጋ ተጠግታ አስተዋለችው…አይኖቹ እንደተጨፈኑ ናቸው… ጥቁር ፊቱ ላይ የሰላምና የመረጋጋት መንፈስ አርብቦበታል…በታዋቂ ቀራፂ በጥንቃቄ የተቀረፀ የሚመስለው አፍንጫው ለፊቱ ውበት አጎናጽፎት ትልቅ ግርማ ሞገስ ሆኖታል…የዓይኖቹ ሽፋ ሽፍቶች ድምቅ ያሉና የተለየ ስሜት የሚያጭሩ ሆነው ነው ያገኘቻቸው..
‹‹እንዴ እስከዛሬ ለምን እንደዚህ እትኩሬ አላስተዋልኩትም…..?›› ስትል እራሷን ጠየቀች ….እስከዛሬ ባለ እይታዋማ ከማንኛውም በሽተኛ የተለየ ምንም ነገር አልነበረውም….አሁን ግን ሁኔታዎች ተቀያይሩባት..አሁን ስሩ ቆማ የምታየው ጥቁር ቆንጆ ወጣትን ለመግደል ግማሽ ሚሊዬን ብር ተቀብላለች…ስለዚህ አሁን ለእሷ ዝም ብሎ ሰው አይደለም….‹‹ደግሞ እንዴት አባቱ ነው የሚያምረው ….…..?››አለችና ክፍሉን ለቃ ወጣች …
ወደ ዶክተር እስክንድር ቢሮ …ዶ/ር እስክንድር በእሷ እድሜ ክልል የሚገኝ አስተዋይ ወጣትና ጓደኛዋ ነው ..ይሄንን ነገር በምትፈልገው መጠን ሊረዳት እንደሚችል ያሰበችው እና ሚስጥር ጠባቂ ነው ብላ ያመነችው እሱን ነው፡፡እሱን ብቻ፡፡
ቢሮው ብቻው ቁጭ ብሎ የበሽተኞችን ፋይል እየመረመረ ነበር ያገኘችው….
‹‹እንዴ ወደቤት የሄድሽ መስሎኝ?››
‹‹ሄጄ ነበር››
‹‹ታዲያ ምን ገጠመሽ እና ተመለሽ…?››
‹‹ታአምር ተፈጥሮ››
‹‹እስቲ ቁጭ በይ እና ተአምሩን ንገሪኝ .››
በድካም ስሜት ከፊት ለፊቱ ያለውመን ወንበር ስባ ቁጭ አለች….
‹‹እሺ አጫውቺ……..?ምን ተፈጠረ…..?››
‹‹እንድታግዘኝ ነው የመጣሁት… በጣም እርዳታህን እፈልጋለሁ…››
‹‹አልገባኝም ምንድነው የምረዳሽ…..?››
‹‹ልናግር አይደል››
‹‹እያዳመጥኩሽ ነው››አላት ትኩረቱን ሰብስቦ ተመቻችቶ እየተቀመጠ
ከሰዓታት በፊት ያጋጠማትን እና እያበረረ ወደእሱ ያስመጣትን ጉዳይ ከመጀመሪያው አንስታ በዝርዝር አስረዳችው…በገረሜታ አፉን ከፍቶ አዳመጣት…ስትጨርስ
‹‹ወይኔ ጉዳችን.!!!.እንዴት ቼኩን ትቀበያለሽ…..?››
‹‹አልቀበልም ብል ዝም ሚሉኝ ይመስልሀል…ሚስጥራቸውን እንደማጋልጥባቸው ስለሚጠረጠሩ ሊያጠፍኝ ይችላሉ ብዬ ፈራኋ…››.
‹‹እሱስ ትክክል ነሽ …ለገዛ ዘመዳቸው ያላዘኑ ላንቺ አይመለሱም…..እና ምን እናድርግ›መልሶ እሷኑ ጠየቃት፡፡
‹‹እርዳኛ››
‹‹እኮ እንዴት ልርዳሽ…?››
‹‹እኔ እንጃ››
ትኩር ብሎ በጥርጣሬ አይን አይኗን እየያያት ቆየና‹‹…ልጅን እንዲሞት ትፈልጊያለሽ እንዴ….?ማለቴ በመግደል እንዳግዝሽ ነው የምትፈልጊው…..?››ሲል ጠየቃት
‹‹አረ በአላህ…..!!እንዴት እንደዛ አሰብክ..…..?››
‹‹እኔ እንጃ… ምን አልባት ብሩ ብዙ ስለሆነ….››ንግግሩን አላስጨረሰችውም
‹‹የፈለገ ብዙ ብር ቢሆን ይህን ለግላጋ ጥንቅሽ ወጣት ለመግደል ጭካኔውን ከየት አመጣለሁ…..?››
‹‹እንዴ ለግላጋ ወጣት ነው ያልሺኝ..…..? ቆንጆ ነው እንዴ..…..?››
ከንግግሩ ተነስታ የተናገረችውን ነገር በምልሰት ስታስታውስ እፈረት ተሰምቷት ‹‹….አንተ ደግሞ በዚህ ሰዓት እንዲህ አይነት ቀልድ ይቀለዳል…..?››አለችው
‹‹ቀልድ እኮ አይደለም ..አንቺው ስላልሽ ነው…ለግላጋ ባይሆን እንዲሞት ትፈቅጂ ነበር ማለት ነው.…..?ንግግርሽ እኮ እንደዛ የምትይ ነው የሚመስለው››
‹‹ይሁንልህ እስቲ አሁን እንዴት እናድርግ….…..?››
አምስት ለሚሆኑ ደቂቆዎች ሁለቱም በየፊናቸው አሰብ …ከዛ ደ/ር እስክንድር ከሀሳቡ ባኖ በፈገግታ መናገር ጀመረ‹‹…አሪፍ ሀሳብ መጣልኝ ››
‹‹ምን አይነት ሀሳብ ንገረኝ……..?.››
‹‹አሁን አልነግረሽም… መጀመሪያ እራት ጋብዢኝ››
‹‹ንገረኝና ጋብዝሀለሁ…..?››
‹‹እዚህ አልነግረሽም… በዘመናችን ምንም በነፃ የሚሰጥ ነገር የለም….ሁሉም ነገር ያስከፍላል…ስለዚህ ጋብዢኝና ልንገርሽ ወይም ደግሞ ይቅርብሽ››
‹‹ይሁንልህ እሺ … አሪፍ ምክር ይሁን እንጂ በደስታ ጋብዝሀለሁ››
‹‹አይ አንቺ ብዙ ቀን ጋብዢኝ ብዬሽ አሻፈረኝ ብለሽ ነበር..ዛሬ እጄ ገባሽ›››
‹‹ስለተሳካልህ እንኳን ደስ ያለህ››አለችውና ተያይዘው ወጡ
እራት በልተው እንዳጠናቀቁ ያሰበውን ይነግራት ጀመር
‹እንግደለው››
‹‹ምን አይነት ብሽቅ ሀሳብ ነው››
‹‹ማለቴ ለተወሰኑ ደቂቃዎች የሞተ እንዲመስል እናደረግና መሞቱን አይተው እንዲያምኑ እናድርግ››
ከቁጣዋ መለስ ብላ‹‹ከዛስ?››ስትል በጉጉጉ ጠየቀች፡
‹‹‹ከዛማ በቃ ሳጥን አምጡ እንላቸውና የሆነ ነገር አሽገን እንሰጣቸዋለን….››
‹‹ከዛስ…?››
‹‹ከዛማ ሰውዬውን የሆነ ቦታ ወስደን እስኪድን እንጠብቅና ለምን ሊገድሉት እንደፈለጉ ከራሱ እናጣራለን…ከእሱ በምናገኘው መረጃ የሆነ ነገር እናደርጋለን…ወይም እራሱ ሲድን የሆነ ነገር ያደርጋል››
ተነስታ ተጠመጠመችበት ‹‹..እንዲት ይህ ሀሳብ መጣልህ?››
‹‹እድሜ ለሆሊውድ ፊልም …ሊዚህ ለዚህ ካልተጠቀምንበት ለምን ይጠቅመናል?››
‹‹እና መቼ እናድርገው…››
ነገ ተነጋግረን የሚሆነውን እናደርጋለን››
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
//
ሰሚራ ለዚህ ሀሳብ ውል ሳታበጅለት ማደር አልፈለገችም….. ቦርሳዋን አንጠልጥላ ተመልሳ ወደስራዋ ቦታ ተመለሰች….መመለሷ ምን እንደሚጠቅማት ለራሷም አልገባትም ..ግን በቃ ተመለሰች..እንደደረሰች ቀጥታ መላኩ ወደተኛበት ክፍል ነበር የገባችው…በሽተኛው የተኛበት ክፍል ውስጥ የተኙ ሌሎች ሶስት ታካሚዎችና እነሱን የሚያስታሙም አስታማሚወች ነበሩ…
ቀጥታ ወደተኛበት አልጋ ተጠግታ አስተዋለችው…አይኖቹ እንደተጨፈኑ ናቸው… ጥቁር ፊቱ ላይ የሰላምና የመረጋጋት መንፈስ አርብቦበታል…በታዋቂ ቀራፂ በጥንቃቄ የተቀረፀ የሚመስለው አፍንጫው ለፊቱ ውበት አጎናጽፎት ትልቅ ግርማ ሞገስ ሆኖታል…የዓይኖቹ ሽፋ ሽፍቶች ድምቅ ያሉና የተለየ ስሜት የሚያጭሩ ሆነው ነው ያገኘቻቸው..
‹‹እንዴ እስከዛሬ ለምን እንደዚህ እትኩሬ አላስተዋልኩትም…..?›› ስትል እራሷን ጠየቀች ….እስከዛሬ ባለ እይታዋማ ከማንኛውም በሽተኛ የተለየ ምንም ነገር አልነበረውም….አሁን ግን ሁኔታዎች ተቀያይሩባት..አሁን ስሩ ቆማ የምታየው ጥቁር ቆንጆ ወጣትን ለመግደል ግማሽ ሚሊዬን ብር ተቀብላለች…ስለዚህ አሁን ለእሷ ዝም ብሎ ሰው አይደለም….‹‹ደግሞ እንዴት አባቱ ነው የሚያምረው ….…..?››አለችና ክፍሉን ለቃ ወጣች …
ወደ ዶክተር እስክንድር ቢሮ …ዶ/ር እስክንድር በእሷ እድሜ ክልል የሚገኝ አስተዋይ ወጣትና ጓደኛዋ ነው ..ይሄንን ነገር በምትፈልገው መጠን ሊረዳት እንደሚችል ያሰበችው እና ሚስጥር ጠባቂ ነው ብላ ያመነችው እሱን ነው፡፡እሱን ብቻ፡፡
ቢሮው ብቻው ቁጭ ብሎ የበሽተኞችን ፋይል እየመረመረ ነበር ያገኘችው….
‹‹እንዴ ወደቤት የሄድሽ መስሎኝ?››
‹‹ሄጄ ነበር››
‹‹ታዲያ ምን ገጠመሽ እና ተመለሽ…?››
‹‹ታአምር ተፈጥሮ››
‹‹እስቲ ቁጭ በይ እና ተአምሩን ንገሪኝ .››
በድካም ስሜት ከፊት ለፊቱ ያለውመን ወንበር ስባ ቁጭ አለች….
‹‹እሺ አጫውቺ……..?ምን ተፈጠረ…..?››
‹‹እንድታግዘኝ ነው የመጣሁት… በጣም እርዳታህን እፈልጋለሁ…››
‹‹አልገባኝም ምንድነው የምረዳሽ…..?››
‹‹ልናግር አይደል››
‹‹እያዳመጥኩሽ ነው››አላት ትኩረቱን ሰብስቦ ተመቻችቶ እየተቀመጠ
ከሰዓታት በፊት ያጋጠማትን እና እያበረረ ወደእሱ ያስመጣትን ጉዳይ ከመጀመሪያው አንስታ በዝርዝር አስረዳችው…በገረሜታ አፉን ከፍቶ አዳመጣት…ስትጨርስ
‹‹ወይኔ ጉዳችን.!!!.እንዴት ቼኩን ትቀበያለሽ…..?››
‹‹አልቀበልም ብል ዝም ሚሉኝ ይመስልሀል…ሚስጥራቸውን እንደማጋልጥባቸው ስለሚጠረጠሩ ሊያጠፍኝ ይችላሉ ብዬ ፈራኋ…››.
‹‹እሱስ ትክክል ነሽ …ለገዛ ዘመዳቸው ያላዘኑ ላንቺ አይመለሱም…..እና ምን እናድርግ›መልሶ እሷኑ ጠየቃት፡፡
‹‹እርዳኛ››
‹‹እኮ እንዴት ልርዳሽ…?››
‹‹እኔ እንጃ››
ትኩር ብሎ በጥርጣሬ አይን አይኗን እየያያት ቆየና‹‹…ልጅን እንዲሞት ትፈልጊያለሽ እንዴ….?ማለቴ በመግደል እንዳግዝሽ ነው የምትፈልጊው…..?››ሲል ጠየቃት
‹‹አረ በአላህ…..!!እንዴት እንደዛ አሰብክ..…..?››
‹‹እኔ እንጃ… ምን አልባት ብሩ ብዙ ስለሆነ….››ንግግሩን አላስጨረሰችውም
‹‹የፈለገ ብዙ ብር ቢሆን ይህን ለግላጋ ጥንቅሽ ወጣት ለመግደል ጭካኔውን ከየት አመጣለሁ…..?››
‹‹እንዴ ለግላጋ ወጣት ነው ያልሺኝ..…..? ቆንጆ ነው እንዴ..…..?››
ከንግግሩ ተነስታ የተናገረችውን ነገር በምልሰት ስታስታውስ እፈረት ተሰምቷት ‹‹….አንተ ደግሞ በዚህ ሰዓት እንዲህ አይነት ቀልድ ይቀለዳል…..?››አለችው
‹‹ቀልድ እኮ አይደለም ..አንቺው ስላልሽ ነው…ለግላጋ ባይሆን እንዲሞት ትፈቅጂ ነበር ማለት ነው.…..?ንግግርሽ እኮ እንደዛ የምትይ ነው የሚመስለው››
‹‹ይሁንልህ እስቲ አሁን እንዴት እናድርግ….…..?››
አምስት ለሚሆኑ ደቂቆዎች ሁለቱም በየፊናቸው አሰብ …ከዛ ደ/ር እስክንድር ከሀሳቡ ባኖ በፈገግታ መናገር ጀመረ‹‹…አሪፍ ሀሳብ መጣልኝ ››
‹‹ምን አይነት ሀሳብ ንገረኝ……..?.››
‹‹አሁን አልነግረሽም… መጀመሪያ እራት ጋብዢኝ››
‹‹ንገረኝና ጋብዝሀለሁ…..?››
‹‹እዚህ አልነግረሽም… በዘመናችን ምንም በነፃ የሚሰጥ ነገር የለም….ሁሉም ነገር ያስከፍላል…ስለዚህ ጋብዢኝና ልንገርሽ ወይም ደግሞ ይቅርብሽ››
‹‹ይሁንልህ እሺ … አሪፍ ምክር ይሁን እንጂ በደስታ ጋብዝሀለሁ››
‹‹አይ አንቺ ብዙ ቀን ጋብዢኝ ብዬሽ አሻፈረኝ ብለሽ ነበር..ዛሬ እጄ ገባሽ›››
‹‹ስለተሳካልህ እንኳን ደስ ያለህ››አለችውና ተያይዘው ወጡ
እራት በልተው እንዳጠናቀቁ ያሰበውን ይነግራት ጀመር
‹እንግደለው››
‹‹ምን አይነት ብሽቅ ሀሳብ ነው››
‹‹ማለቴ ለተወሰኑ ደቂቃዎች የሞተ እንዲመስል እናደረግና መሞቱን አይተው እንዲያምኑ እናድርግ››
ከቁጣዋ መለስ ብላ‹‹ከዛስ?››ስትል በጉጉጉ ጠየቀች፡
‹‹‹ከዛማ በቃ ሳጥን አምጡ እንላቸውና የሆነ ነገር አሽገን እንሰጣቸዋለን….››
‹‹ከዛስ…?››
‹‹ከዛማ ሰውዬውን የሆነ ቦታ ወስደን እስኪድን እንጠብቅና ለምን ሊገድሉት እንደፈለጉ ከራሱ እናጣራለን…ከእሱ በምናገኘው መረጃ የሆነ ነገር እናደርጋለን…ወይም እራሱ ሲድን የሆነ ነገር ያደርጋል››
ተነስታ ተጠመጠመችበት ‹‹..እንዲት ይህ ሀሳብ መጣልህ?››
‹‹እድሜ ለሆሊውድ ፊልም …ሊዚህ ለዚህ ካልተጠቀምንበት ለምን ይጠቅመናል?››
‹‹እና መቼ እናድርገው…››
ነገ ተነጋግረን የሚሆነውን እናደርጋለን››
✨ይቀጥላል✨
👍129❤17😁5😱2👎1
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ዶ/ር ሶፊያ የተኛችበት ሆስፒታል አልጋ ላይ ሆና በኤልያስ በኩል ከትንግርት የተላከላትን ዲያሪ ማንበብ ጀመረች፡፡
ጥቅምት 25 1999ዓ.ም
የሁለተኛ አመት የዩኒቨርሲቲ ትምህርት ከጀመርን አንድ ወር ሊሞላን ነው፡፡አምና ፍቅረኛ ነበረኝ፡፡ጌዲ ከኔ ጋር ነበር..አሁን ግን ብቻዬን ነኝ፡፡ቢሆንም ምርጥ የሴት ጓደኛ ማግኘት ችያለሁ፡፡ሶፊያ ትባላለች፡፡አንድ ዶርም ነው የምንጋራው፡፡እርግጥ ሌሎች አራት ልጆችም አብረውን ይኖራሉ..በአርባ ምንጭ ሙቀት አንድ ዶርም ውስጥ ስድስት ሰው ታጭቆ መኖር ይከብዳል..ቢሆንም እየኖርን ነው፡፡
ሶፊ የምትገርም ልጅ ነች…የተወለደችውም ያደገችውም አሜሪካ ነው፡፡ በዲሞሽን ወደ
ኢትዬጵያ ከተወረወረች ሶስተኛ አመቷ ነው፡፡ አንድ አመት ሃይስኩል የተቀሩትን ሁለት ዓመት እዚህ ዩኒቨርሲቲ እንዳሳለፈች አጫውታኛለች፡፡
ስለእሷ ሳስብ ሚገርመኝ የኢትዬጵያ ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ውጭ ለመላክ አፈር ድሜ ይግጣሉ..የእሷ ወላጆች እሷን ባህሏን እረሳች..ፀባዮ ተበላሸ ...መረን ለቀቀች በሚል ሰበብ ወደ ኢትዬጵያ ላኳት..ልክ እንደ ፀባይ ማረሚያ..አይ ሚስኪኗ ሶፊያ፡፡
ህዳር-5 1999 ዓም
ከሶፊ ጋር ዛሬ ወደ ከተማ ወጥተን ነበር..ሲቀላ ፡፡ ዋናው የሄድንበት ምክንያት አባቷ ከአሜሪካ ዶላር ልኮላት ስለነበር ያንን ለመቀበል ነው፡፡ አንድ ሺ ዶላር ነበር የላከላት፡፡ከዛ ምሳ ጋበዘችኝ..ወይን ጠጣን…ለእሷ አንድ ሱሪ ብቻ ስትገዛ ለእኔ ሁለት ሱሪና ሁለት ቀሚስ ገዛችልኝ፡፡ግርም ነው ያለኝ፡፡ ማነው ለጓደኛው እንዲህ የሚያደርገው…?በዛ ላይ የእሷን ያህል አይሁን እንጂ እኔም ከውጭ በሚላክ ዶላር የምማር ልጅ ነኝ፤ሌላው ደግሞ አንድ ደርዘን የሚያማምሩ ፓንቶች ገዛችና ስድስቱና ለእኔ ስድስቱን ለራሷ ወሰደች፡፡በእውነት የዋህ ነች እንዳልል ለሌሎች ጓደኞቿ እንደዛ ስታደርግ አይቼት አላውቅም፡፡ብቻ እኔ ወደድኳት፡፡ጥሩ ጓደኛዬም አድርጌ ከልብ ተቀብዬታለሁ፡፡
ህዳር 29 1999 ዓ ም
የሚቀርቡን የዩኒቨርቲ የወንድ ጓደኞቻችን ከተማ ካልወጣን አሉን፡፡አስር ሆነን ወጣን.... አራት ሴት ስድስት ወንድ፡፡ከግቢ ስንወጣ እራሱ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ሆኖ ነበር፡፡ከግቢ በታክሲ ሲቀላ... ከሲቀላ ደግሞ ሼቻ አመራን፡፡ በመጀመሪያ ወደ በቀለ ሞላ ሆቴል ነው ያመራነው፡፡፡
ሆቴሉን ጥለን ወደ ጓሮ አለፍንና ውጭ ወንበር ከበን በመቀመጥ እራት አዘዝን፡፡ከፍታ ቦታ ላይ ያለው የበቀለ ሞላ ሆቴል ወደ ታች የነጭ ሳርን የተንጣለለ ደን፤ በእግዜር ድልድይ የተከፈሉትን አባያና ጫሞ ሀይቅን፤ በግሩም
ሁኔታ ማየት የሚያስችል እስትራቴጂካዊ ቦታ ላይ ነው የታነፀው ..ከዛ ከዝቅታው የተፈጥሮ ሙዚዬም ወደ ላይ ሚነፍሰው ቀዝቃዛና ነፋሻማ አየርም ልብን ስውር ያደርጋል፡፡ እራታችንን በልትን ስናጠናቅቅ እና የበቀለ ሞላን ሆቴል ለቀን ስንወጣ 2፡45 ሆኖ ነበር፡፡ ቀጥሎ ሞቅ ወዳለው ጫሞ ሆቴል ነው የገባነው፡፡በተለያ አጋጣሚዋች ሶስት ቀን እዚህ ቤት መጥቼያለሁ....በተለይ ከጊዲዬን ጋር የመጣሁባቸው ሁለት ቀናት አይረሱኝም፡፡
መጠጥ መጠጣት በቢራ ነው የተጀመረው፡፡ ጨወታው፣ ተረቡ ደስ ይል ነበር፡፡ በተለይ የሶፊ ደስታ ልዩ ነበር፡፡በፊትም እኔ ስለማጣጥልባት እንጂ እንዲህ አይነት ቸበርቻቻ ነፍሷ ነው፡፡ ..አራት ሰዓት አካባቢ መቀመጫው ላይ ማንም አልነበረም፡፡ ሁሉም በሙዚቃ ምት በመታገዝ ጭፈራውን እየቀወጠው ነው፡፡አንዳንዱም መጠጡን ከቢራ ወደ አልኮል ቀይሮታል….. እየሰከረ ያለም አለ፡፡ወንዶቹ የመረጧትን እና ቀልባቸውን የተመኛት ሴት ዙሪያ ይሽከረከራሉ… ይጎነታትላሉ ...ይጀነጅናሉ፡፡
ሁለቱ ሴቶች ከሁለቱ ወንዶች ጋር ተግባብተው እየተላላሱ ነው፡ኃይሌ የሚባል የመቀሌ ልጅ እኔን እየጀነጀነኝ ነው..በጣም ያምራል..፡፡ለምን እንደሆነ አላውቅም ይሄን ልጅ ካወቅኩት ቀን ጀምሮ የሆነ ነገሩ ይመቸኛል፡፡እና እንዲሁ በሴትነቴ እግደረደራለሁ እንጂ ቀልቤ ፈቅዶታል..፡፡እሱም እየተግደረደርኩ መሆኔ ገብቶት መሰለኝ ጥረቱን አጠናከረ..ቀስ በቀስ እየደከምኩለት መጣሁ..<በቃ ዛሬ አብሬው ማደሬ ቁርጥ ነው› ስል አስቤ ነበር በውቅቱ ፡፡ ባዛ ላይ ከጌዲዬን ከተለያየው ስድስት ወር ሆኖኛል ...ስድስት ወር ሙሉ ምንም አላገኘሁም ..በጣም አምሮኛል፡፡
ሶፊያ ሶስት ወንዶች እየተሻሙባት ነው፡፡የሆነ ሙድ እየያዘችባቸው መሰለኝ፡፡እዚህኛው ላይ ትንጠለጠላለች.... ያኛውን ትጠቅሰዋለች.. ደግሞ ከዛኛው ጋር ትጎነታተላለች፡፡በመጨረሻ ጓደኛ የሆኑት ሶስቱ ወንዶች እርስ በርስ
መገለማመጥ ጀመሩ…..ስድስት ሰዓት ሲሆን
ሁላችንም በስካር ጥንብዝ ብለን ሆቴሉን ለቀን
ወደ ቤርጓችን ሄድን ፡፡አምስት ክፍል በመደዳ
ነበር የተያዘው፡፡እንዲህ እንዲሆን የወንዶቹ
ዕቅድ ነው ፡፡ዕድል የቀናቸው አራቱ ወንዶች
አንዳንድ ሴት ይዘው ይተኛሉ ምስኪኖቹ ሁለት ወንዶች የቀረችው አንድ አልጋ ላይ አብረው ያድራሉ.. በሚል ስሌት ነበር የተሰላው፡፡....
.......................
እዚህ ጋር ከደረሲው እውቅና ውጪ ቢሆንም ለአንባቢው የሚጎረብጡ ሐሳቦች የተነሱበት ክፍል ስለሆነ ቆርጬ አውጥቼዋለሁ ለምን ተቆረጠ የሚልም አይጠፋምና ከወዲሁ ይቅርታ እጠይቃለሁ
........"በየጓዲያችን ቀስ በቀስ እየገባ ያለ ነገር ሆኖ ሳለ ቃሉን አናንሳ ..ጭራሽ በጆሮችን አንስማ ማለት አግባብም አይደለም አያዋጣንምም ብዬ አምናለሁ ፡፡
ይልቅ ችግሩ በቤታችን አለ...? አዎ አለ ፡፡… አግባብ ያልሆነ እና መቅረት ያለበት አካሄድ ነው ወይ..? አዋ ነው፡፡..ስለዚህ ውስጡ ያሉትን እንዴት አግዘናቸው ከህይወቱ እንዲወጡ ማድረግ እንችላለን…?ሊገቡ ቋፍ ላይ ያሉትንስ ሳይቃጠል በቅጠል እንዴት ነው ከገደሉ አፋፍ ልንመልሳቸው የምንችለው…? መልሱ ችግሩ በመሀከላችን መኖሩን በግልፅ ስናምን..በችግሩ ላይ በግልፅ መነጋገር
መወያት እና መግባባት ስንችል ነው መፍትሄውን በእጃችን መጨበጥ የምንችለው፡፡ እራሳችንንም ከችግሩ የምናድንበት መድሀኒት ማግኘት የምንችለው ... መጪውን ትውልድንም መታደግ የምንችለው የዛን ጊዜ ነው፡፡››
ካለበለዚያ እንዲሁ በጭፍን ባህላችን አጎደፉት .... እርኩሶች ናቸው፤ ይጨፍጨፉ….ይመንጠሩ በማለት ቅንጣት ውጤት ማምጣት አንችልም፡፡እንደውም ስለዚህ ነገር ሳስብ
1980ዎቹ ቤት አካባቢ የነበረውን የኤች. አይ ቪ ጥፋት ያስታውሰኛል ፡፡የዛኔ ጊዜም ስለበሽታው በአደባባይ አውጥተን መወያየትና መፍትሔ መፈለግ ሲገባን በየጓዲያው በማንሾካሾክ ....አውሬ መጣላችሁ፣ጭራቅ መጣላችሁ እያልን ለተጠቂዎች ሲኦልን
ስንሸልማቸው..እኛም በፍርሀት ታፍነን በቁም
ስንንዘፈዘፍ ስንት እና ስንት ህይወት ረገፈ ….?
ስንቱ አፍላ ወጣት ለውይይትና ለምክክር ዝግ
በሆነው ባህላችን ምክንያት በየጓዳው ባክኖ ቀረ...?ቤት ይቁጠረው፡፡ዛሬም ከዛ ውድመት አልተማርንም፡፡መቼም እርግማን ሆኖብን አንድ ችግር የህዝባችንን እሩብ ካልጨረሰ በስተቀር መፍትሄው አይገለፅልንም፡፡
‹‹ትክክል ነህ .…እኔም ባንተ ሀሳብ እስማማለሁ፡፡›› አለችው ዶ/ር ሶፍያ፡፡
‹‹ጥሩ.. በይ አሁን ተነሺ እንውጣ፡፡››
‹‹ጨረስክ እንዴ ፕሮሰሱን?››
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ዶ/ር ሶፊያ የተኛችበት ሆስፒታል አልጋ ላይ ሆና በኤልያስ በኩል ከትንግርት የተላከላትን ዲያሪ ማንበብ ጀመረች፡፡
ጥቅምት 25 1999ዓ.ም
የሁለተኛ አመት የዩኒቨርሲቲ ትምህርት ከጀመርን አንድ ወር ሊሞላን ነው፡፡አምና ፍቅረኛ ነበረኝ፡፡ጌዲ ከኔ ጋር ነበር..አሁን ግን ብቻዬን ነኝ፡፡ቢሆንም ምርጥ የሴት ጓደኛ ማግኘት ችያለሁ፡፡ሶፊያ ትባላለች፡፡አንድ ዶርም ነው የምንጋራው፡፡እርግጥ ሌሎች አራት ልጆችም አብረውን ይኖራሉ..በአርባ ምንጭ ሙቀት አንድ ዶርም ውስጥ ስድስት ሰው ታጭቆ መኖር ይከብዳል..ቢሆንም እየኖርን ነው፡፡
ሶፊ የምትገርም ልጅ ነች…የተወለደችውም ያደገችውም አሜሪካ ነው፡፡ በዲሞሽን ወደ
ኢትዬጵያ ከተወረወረች ሶስተኛ አመቷ ነው፡፡ አንድ አመት ሃይስኩል የተቀሩትን ሁለት ዓመት እዚህ ዩኒቨርሲቲ እንዳሳለፈች አጫውታኛለች፡፡
ስለእሷ ሳስብ ሚገርመኝ የኢትዬጵያ ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ውጭ ለመላክ አፈር ድሜ ይግጣሉ..የእሷ ወላጆች እሷን ባህሏን እረሳች..ፀባዮ ተበላሸ ...መረን ለቀቀች በሚል ሰበብ ወደ ኢትዬጵያ ላኳት..ልክ እንደ ፀባይ ማረሚያ..አይ ሚስኪኗ ሶፊያ፡፡
ህዳር-5 1999 ዓም
ከሶፊ ጋር ዛሬ ወደ ከተማ ወጥተን ነበር..ሲቀላ ፡፡ ዋናው የሄድንበት ምክንያት አባቷ ከአሜሪካ ዶላር ልኮላት ስለነበር ያንን ለመቀበል ነው፡፡ አንድ ሺ ዶላር ነበር የላከላት፡፡ከዛ ምሳ ጋበዘችኝ..ወይን ጠጣን…ለእሷ አንድ ሱሪ ብቻ ስትገዛ ለእኔ ሁለት ሱሪና ሁለት ቀሚስ ገዛችልኝ፡፡ግርም ነው ያለኝ፡፡ ማነው ለጓደኛው እንዲህ የሚያደርገው…?በዛ ላይ የእሷን ያህል አይሁን እንጂ እኔም ከውጭ በሚላክ ዶላር የምማር ልጅ ነኝ፤ሌላው ደግሞ አንድ ደርዘን የሚያማምሩ ፓንቶች ገዛችና ስድስቱና ለእኔ ስድስቱን ለራሷ ወሰደች፡፡በእውነት የዋህ ነች እንዳልል ለሌሎች ጓደኞቿ እንደዛ ስታደርግ አይቼት አላውቅም፡፡ብቻ እኔ ወደድኳት፡፡ጥሩ ጓደኛዬም አድርጌ ከልብ ተቀብዬታለሁ፡፡
ህዳር 29 1999 ዓ ም
የሚቀርቡን የዩኒቨርቲ የወንድ ጓደኞቻችን ከተማ ካልወጣን አሉን፡፡አስር ሆነን ወጣን.... አራት ሴት ስድስት ወንድ፡፡ከግቢ ስንወጣ እራሱ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ሆኖ ነበር፡፡ከግቢ በታክሲ ሲቀላ... ከሲቀላ ደግሞ ሼቻ አመራን፡፡ በመጀመሪያ ወደ በቀለ ሞላ ሆቴል ነው ያመራነው፡፡፡
ሆቴሉን ጥለን ወደ ጓሮ አለፍንና ውጭ ወንበር ከበን በመቀመጥ እራት አዘዝን፡፡ከፍታ ቦታ ላይ ያለው የበቀለ ሞላ ሆቴል ወደ ታች የነጭ ሳርን የተንጣለለ ደን፤ በእግዜር ድልድይ የተከፈሉትን አባያና ጫሞ ሀይቅን፤ በግሩም
ሁኔታ ማየት የሚያስችል እስትራቴጂካዊ ቦታ ላይ ነው የታነፀው ..ከዛ ከዝቅታው የተፈጥሮ ሙዚዬም ወደ ላይ ሚነፍሰው ቀዝቃዛና ነፋሻማ አየርም ልብን ስውር ያደርጋል፡፡ እራታችንን በልትን ስናጠናቅቅ እና የበቀለ ሞላን ሆቴል ለቀን ስንወጣ 2፡45 ሆኖ ነበር፡፡ ቀጥሎ ሞቅ ወዳለው ጫሞ ሆቴል ነው የገባነው፡፡በተለያ አጋጣሚዋች ሶስት ቀን እዚህ ቤት መጥቼያለሁ....በተለይ ከጊዲዬን ጋር የመጣሁባቸው ሁለት ቀናት አይረሱኝም፡፡
መጠጥ መጠጣት በቢራ ነው የተጀመረው፡፡ ጨወታው፣ ተረቡ ደስ ይል ነበር፡፡ በተለይ የሶፊ ደስታ ልዩ ነበር፡፡በፊትም እኔ ስለማጣጥልባት እንጂ እንዲህ አይነት ቸበርቻቻ ነፍሷ ነው፡፡ ..አራት ሰዓት አካባቢ መቀመጫው ላይ ማንም አልነበረም፡፡ ሁሉም በሙዚቃ ምት በመታገዝ ጭፈራውን እየቀወጠው ነው፡፡አንዳንዱም መጠጡን ከቢራ ወደ አልኮል ቀይሮታል….. እየሰከረ ያለም አለ፡፡ወንዶቹ የመረጧትን እና ቀልባቸውን የተመኛት ሴት ዙሪያ ይሽከረከራሉ… ይጎነታትላሉ ...ይጀነጅናሉ፡፡
ሁለቱ ሴቶች ከሁለቱ ወንዶች ጋር ተግባብተው እየተላላሱ ነው፡ኃይሌ የሚባል የመቀሌ ልጅ እኔን እየጀነጀነኝ ነው..በጣም ያምራል..፡፡ለምን እንደሆነ አላውቅም ይሄን ልጅ ካወቅኩት ቀን ጀምሮ የሆነ ነገሩ ይመቸኛል፡፡እና እንዲሁ በሴትነቴ እግደረደራለሁ እንጂ ቀልቤ ፈቅዶታል..፡፡እሱም እየተግደረደርኩ መሆኔ ገብቶት መሰለኝ ጥረቱን አጠናከረ..ቀስ በቀስ እየደከምኩለት መጣሁ..<በቃ ዛሬ አብሬው ማደሬ ቁርጥ ነው› ስል አስቤ ነበር በውቅቱ ፡፡ ባዛ ላይ ከጌዲዬን ከተለያየው ስድስት ወር ሆኖኛል ...ስድስት ወር ሙሉ ምንም አላገኘሁም ..በጣም አምሮኛል፡፡
ሶፊያ ሶስት ወንዶች እየተሻሙባት ነው፡፡የሆነ ሙድ እየያዘችባቸው መሰለኝ፡፡እዚህኛው ላይ ትንጠለጠላለች.... ያኛውን ትጠቅሰዋለች.. ደግሞ ከዛኛው ጋር ትጎነታተላለች፡፡በመጨረሻ ጓደኛ የሆኑት ሶስቱ ወንዶች እርስ በርስ
መገለማመጥ ጀመሩ…..ስድስት ሰዓት ሲሆን
ሁላችንም በስካር ጥንብዝ ብለን ሆቴሉን ለቀን
ወደ ቤርጓችን ሄድን ፡፡አምስት ክፍል በመደዳ
ነበር የተያዘው፡፡እንዲህ እንዲሆን የወንዶቹ
ዕቅድ ነው ፡፡ዕድል የቀናቸው አራቱ ወንዶች
አንዳንድ ሴት ይዘው ይተኛሉ ምስኪኖቹ ሁለት ወንዶች የቀረችው አንድ አልጋ ላይ አብረው ያድራሉ.. በሚል ስሌት ነበር የተሰላው፡፡....
.......................
እዚህ ጋር ከደረሲው እውቅና ውጪ ቢሆንም ለአንባቢው የሚጎረብጡ ሐሳቦች የተነሱበት ክፍል ስለሆነ ቆርጬ አውጥቼዋለሁ ለምን ተቆረጠ የሚልም አይጠፋምና ከወዲሁ ይቅርታ እጠይቃለሁ
........"በየጓዲያችን ቀስ በቀስ እየገባ ያለ ነገር ሆኖ ሳለ ቃሉን አናንሳ ..ጭራሽ በጆሮችን አንስማ ማለት አግባብም አይደለም አያዋጣንምም ብዬ አምናለሁ ፡፡
ይልቅ ችግሩ በቤታችን አለ...? አዎ አለ ፡፡… አግባብ ያልሆነ እና መቅረት ያለበት አካሄድ ነው ወይ..? አዋ ነው፡፡..ስለዚህ ውስጡ ያሉትን እንዴት አግዘናቸው ከህይወቱ እንዲወጡ ማድረግ እንችላለን…?ሊገቡ ቋፍ ላይ ያሉትንስ ሳይቃጠል በቅጠል እንዴት ነው ከገደሉ አፋፍ ልንመልሳቸው የምንችለው…? መልሱ ችግሩ በመሀከላችን መኖሩን በግልፅ ስናምን..በችግሩ ላይ በግልፅ መነጋገር
መወያት እና መግባባት ስንችል ነው መፍትሄውን በእጃችን መጨበጥ የምንችለው፡፡ እራሳችንንም ከችግሩ የምናድንበት መድሀኒት ማግኘት የምንችለው ... መጪውን ትውልድንም መታደግ የምንችለው የዛን ጊዜ ነው፡፡››
ካለበለዚያ እንዲሁ በጭፍን ባህላችን አጎደፉት .... እርኩሶች ናቸው፤ ይጨፍጨፉ….ይመንጠሩ በማለት ቅንጣት ውጤት ማምጣት አንችልም፡፡እንደውም ስለዚህ ነገር ሳስብ
1980ዎቹ ቤት አካባቢ የነበረውን የኤች. አይ ቪ ጥፋት ያስታውሰኛል ፡፡የዛኔ ጊዜም ስለበሽታው በአደባባይ አውጥተን መወያየትና መፍትሔ መፈለግ ሲገባን በየጓዲያው በማንሾካሾክ ....አውሬ መጣላችሁ፣ጭራቅ መጣላችሁ እያልን ለተጠቂዎች ሲኦልን
ስንሸልማቸው..እኛም በፍርሀት ታፍነን በቁም
ስንንዘፈዘፍ ስንት እና ስንት ህይወት ረገፈ ….?
ስንቱ አፍላ ወጣት ለውይይትና ለምክክር ዝግ
በሆነው ባህላችን ምክንያት በየጓዳው ባክኖ ቀረ...?ቤት ይቁጠረው፡፡ዛሬም ከዛ ውድመት አልተማርንም፡፡መቼም እርግማን ሆኖብን አንድ ችግር የህዝባችንን እሩብ ካልጨረሰ በስተቀር መፍትሄው አይገለፅልንም፡፡
‹‹ትክክል ነህ .…እኔም ባንተ ሀሳብ እስማማለሁ፡፡›› አለችው ዶ/ር ሶፍያ፡፡
‹‹ጥሩ.. በይ አሁን ተነሺ እንውጣ፡፡››
‹‹ጨረስክ እንዴ ፕሮሰሱን?››
👍73❤4👎1😁1