#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
#ክፍል_አምስት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍሰሀ
===
የመጀመሪያ ቀን እይታ የሰው ልብን መአከላዊ ስፍራ ለመያዝ ወይም ለመቆጣጠር ወሳኝ ነው ይባል የለ፡ይሄንን ፕሪንስፕል ተከትዬ በሕይወቴ የመጨረሻውን መሽቀርቀር ነው የተሸቀረቀርኩት..ምን አልባት ይሄንን መልሼ የምደግመው ከእለታት አንድ ቀን ልቤን የምታቀልጥ ልእልት አግኝቼ ሚስቴ አድርጌ በማገባት ቀን ብቻ ሊሆን ይችላል፡፡የኢጣሊያን ብራንድ ሱፍ ከእንግሊዝ በልዩ ትዕዛዝ የተገዛ ጫማ ፤በየሰው እፍንጫ ሲደርስ ከልብ ውስጥ ፍቅር ..ሰላምና ፍሰሀን የሚያመነጩትን ህብረ ህዋሳቶችን የሚያነቃቃ ልዩ የፈረንሳይ ሽቶ …..በአጠቃላይ በእጄ ላይ ያደረግኩት ሰዓት በጣቴ ያጠለቅኩት የአልማዝ ቀለበት….በዩኒቨርሲት ከገበየውት ዕውቀት በተጨማሪ ያለውበትን እና የሚገባኝን የህይወት ደረጃ በትክክል የሚያንፀባርቁና የሚያረጋግጡ እንደሚሆን እርግጠኛ ሆኜ ነው ከቤቴ የወጣውት
አስደማሚውንና የተንጣለለውን ቢሮዬን ተረከብኩ….በመጀመሪያ በአስተዳዳሪው መሪነት በየክፍሉ እየዞርኩ ሰራተኞችን በመተዋወቅ ነበር የጀመርኩት..ተስፋ ሰጪና አበረታች ሁኔታ ነው ያጋጠመኝ…ከወጣት እስከአዛውንት የዕድሜ ክልል የሚገኙ ሰራተኞች እኔን በአክብሮትና በመሽቆጥቆጥ እናም ደግሞ በፍራቻ ነበር የተዋወቁኝ ..ይሄ ደግሞ አሪፍ ምልክት ነው..ሁሉን በፈለኩት መጠን ለፈለኩት ተግባር በማሰማራት ተፈላጊውን ውጤት በማምጣት አባቴን አኮራዋለው ..ይሄንን ካምፓኒም ሶስቱንም ባለድርሻ አሳምኜ በዕድሜ ልክ እርስትነት ገዢ ሆኜ እሾምበታለው….፡፡
ቀጥሎ የየክፍሉን ኃላፊዎች ነበር ቢሮዬ ሰብስቤ ስለጠቅላላው የካማፓኒው እንቅስቃሴ ገለጻ እንዲያደርጉልኝ ያደረግኩት….አራት ሰዓት አካባቢ ለሶስት ወር እሰራዋለው ብዬ ከአወጣውት ዕቅድ ላይ በአንድ ሳምንት ውስጥ መስራት የሚገባኝን የስራ ዕቅድ በወረቀት ጫር ጫር አደረግኩና ፀሀፊዎ በኮምፒተር እንድትጽፍልኝ ስለፈለኩ ጠረጰዛዬ ላይ ያለውን መጥሪያ ተጫንኩት…ተላላኪዋ መጣችና ምን እንደምፈልግ ጠየቀችኝ…
‹‹ፀሀፊዋን ፈልጌ ነበር…››
‹‹ውይ..የለችም››
‹‹የለችም ማለት..?በስራ ሰዓት የት ሄደች…?››ኮስተር ብዬ ጠየቅኩ…..አዎ ከአሁኑ ቆፍጠን እና ጠንከር ካላልኩ ከግማሽ በላይ አዛውንት ያሉበትን ከመቶ በላይ የሆኑ ሰራተኞችን በስርአት ልመራቸው አልችልም…አዎ አንዳይንቁኝ ለማንም ፊት ማሳየት የለብኝም ..ይሄ አቋሜ ነው፡፡
‹‹ጋሼ እኔ እንጃ ..ግን ትናንትም አልመጣችም..ዘመድ ሞቶባታል ሲባል ሰምቼያለው››
‹‹እሺ በቃ …በሩን ዘግተሸ ውጪልኝ››
ሹክክ ብላ ወጣችን በራፉን ዘጋችልኝ፡፡
‹‹አስተዳደሩ ጋ ስልክ ደወልኩ››
‹‹ሄሎ አቶ ሰይፉ››ቆፍጠን ብዬ
‹‹አቤት አቶ ፍሰሀ ምነው ፈለከኝ..? ልምጣ…..?››ተሸቆጠቆጡ
..አይ እቺ ወንበር..ብታዩ እኮ የስልሳ አምስት አመት የሰማይ ስባሪ የሚያህሉ ሰውዬ ናቸው…
‹‹አይ ፀሀፊዋ የለችም አሉኝ ..የሚያቀውቁት ነገር አለ…..?››
‹‹ይቅርታ ሰው መተካት ነበረብኝ..አክስቷ ሞታ የሳምንት እረፍት ወጥታለች፡፡››
‹‹ለአክስት ሞት አንድ ሰማንት…..?ለአክስት ይሄን ያህል ከፈቀዳችሁ እናት ስትሆን ደግሞ ወር ነው ማለት ነው..?››
‹‹አይ እንደሱ እንኳን አይደለም…ለቅሶው መቀሌ ነው …ራቅ ስለሚል ነው….አሁን የእኔን ጸሀፊ እልክልሀለው››
‹‹እሺ ላኩልኝ…ሌላውን በሄደት እናተካክለዋለን፡፡››ስልኩን ዘጋውት…
አያያዜ ለራሴ አስገረመኝ …..በዚሁ ከቀጠልኩማ በቃ አዳሜን ሽር ነው ማደርጋት……‹አያየዙን አይተው ጭብጦውን ቀሙት › የሚለውን ተረት እንዳይተረትብኝ ጥሩ መንገድ ላይ ነው ያለውት …አዎ ለራሴ እንደዛ ነው እየተሰማኝ ያለው …
ከ3 ደቂቃ ቡኃላ በራፉ በጥቂቱ ተንኳኳና ተከፈተ….በእኔው እድሜ አካባቢ ያለች ቸኮሌት ቀለም ያላት ልጅ እንደቀጭኔ የረዘመ አንገቷን አስቀድማ ወደውስጥ ገባች…ከአይኖቾ የሚረጨው ጨረር ልቤን ሲወጋኝ ታወቀኝ …ፀጉሯን አንድ ላይ አስራው ወደፊት በትከሻዋ በማምጣት ለቃው በደረቷ ወርዶ በጡቷቿ መካከል አልፎ እንብርቷ አካባቢ ደርሶል…አለባበሶ መጥፎም ጥሩም የማይባል መካከለኛ አይነት ነው፡፡ ‹ኖ ሜካፓ አትትቀባም ኦል…..›እንደተፈጠረች ምንም ባልነካካው በኦረጂናል ቆዳዋ ነች… ብቻ በድምሩ የሆነ ነገሯ አስደነገጠኝ….ከሁሉ በላይ ቁመቷ ያሰፈዝዛል…<ይሄን ሁሉ ቁመት ያሸከማት ምን እንድታደርግበት ነው.. ? በውስጤ የተፈጠረብኝ ጥያቄ ነበር…
‹‹አቤት ምን ነበር አልኳት››የተጨማደደ ፊቴን ሳልፈታ…. ሙሉ በሙሉ ገባችና በራፉን ዘግታ ወደ እኔ ቀረበች……ወደላይ አንጋጥጬ እያየዋት
‹‹ፊናን እባላለው…..ምንድን ነበር እንዲፃፍልህ የፈለከው..?››አለቺኝ ከእኔ በላይ በሆነ መኮሳተር
‹‹ፀሀፊዋ አንቺ ነሽ››ምንሽም ፀሀፊ አይመስል የሚል መልዕክት በሚያስተላልፍ የድምጽ ቅላፄ
‹‹አዎ ነኝ..››
‹‹ማን መሆኔን አውቀሻል….››አልኳት እስከአሁን መላው ሰራተኞቼ ለእኔ እያሳዩ የነበረውን መሽቆጥቆጥ እሩቡንም ከእሷ ስላላገኘው ስለማንነቴ ከለማወቅ ነው ብዬ በመገመት፡፡
‹‹አቶ ፍሰሀ የኤም.ዲ.ቲ ካንፓኒ ዋና ስራ አስኪያጅ…ፊት ለፊትህ እኮ ከፎቶህ ጋር ተፃፎ ይነበባል…››በሀገራችን ያልተለመደ የሚመስል ሰማያዊ ቀለም ያላቸው የዓይን ብሌን ነው ያላት.. ከሆነ ኮከብ የተሸረፍ የሚመስሉ አደገኛ ዓይኖቾን እያንከባለለችብኝ
‹‹ጥሩ ነው..አንቺ ግን የዚህ ካምፓኒ ሰራተኛ ነሽ…...?ቅድም ሰራተኞችን ስተዋወቅ ተገናኝተናል..?››ትእቢቷን ባለማመን ደግሜ ሌሎች ጥያቄዎች ጠየቅኳት
‹‹አዎ የጋሽ ሰይፉ ----ፀሀፊ ነኝ…በመጣህ ጊዜ ቢሮ አልነበርኩም..ስለዚህ አልተገናኘንም ››
‹‹በይ እዛ ወንበር ላይ ተቀመጪና በራሴ ላፕቶፕ ይሄንን ገልብጪልኝ..በፍጥነት ነው የምፈልገው፡፡
‹‹በፍጥነት ማለት..?፡፡››
‹‹በ15 ደቂቃ››አቀበልኳት….ተቀበለቺኝና ላፕቶፑ ፊት ለፊት ተቀመጠች….መጻፍ ጀመረች….ጨርሳ ስታስረክበኝ ገርሞኝ ሰዓቴን አየው 6 ደቂቃ ብቻ ነው የፈጀባት…
‹‹እየው…››አለቺኝ በተቀመጠችበት ልክ ለድርድር የመጣች ጉረኛ ባለጉዳይ አንደኛውን እግሯን በአንደኛው ላይ አፈናጣ በግምሽ እይታ እያየቺኝ…እግሮቾን በመደራረቦ የለበሰችው ጉርድ ቀሚስ በመጠኑ ወደላይ ስለተሰበሰበ ወደጭኗ የሚጠቁም የሆነ ሸለቆ አይነት ምስል አይኔ ላይ ብዥታ ፈጠረብኝ..ይህቺ አለሌ ዱርዬ ሳትሆን አትቀርም ደረጃዬን በሚመጥን ሁኔታ እራሴን መቆጣጠር ይገባኛል ›በማለት ከውስጤ ተማከርኩና
‹‹አይ ቀስ ብዬ አየዋለው….ለጊዜው ጨረስን…ስፈልግሽ ጠራሻለው ››ብዬ እንድትወጣልኝ አዘዝኮት
‹‹እሺ ..››ብላኝ ከተቀመጠችበት በመለጠጥ ተነሳችና የሆነ ኪነ-ጥበባዊ በሆነ አረማመድ ወጥታ ሄደች…ይሄ አረማመዶ ተፈጥሮዊ ነው ወይስ የተጠና በልምምደ የተገኘ…..?ሁል ጊዜ የምትጠቀምበት ነው ወይስ ለማጥመድ የፈለገችውን እንደእኔ አይነነት አጎጊ ወንድ በሚያጋጥማት የክት ቀን የምትጠቀምበት…በጊዜ ሄደት የማረጋግጠው ይሆናል፡፡
አምስት ደቂቃ ስለእሷው ሳስብ ቆየውና..ቆይ እስኪ የሰራቸውን ልየው ብዬ ላፕቶፔን ወደራሴ በማስጠጋት ከፍቼ ማየት ጀመርኩ …ልቅም አድርጋ ያለምንም እንከን ነው የሰራችው..ግን ከታች ጻፊ ያላልኳትን ጨምራ ጽፋለች፡፡
‹‹ስለ ዕቅድህ ያለኝ አስተያየት››ብሎ ይጀምራል
1/ይንን ዕቅድ ወደተግባር ለመተግበር ከመሞከርህ በፊት የካምፓኒውን የስራ አካሄዶች፤ከሌሎች ካምፓኒዎች ጋር ተደረጉ የስራ ውሎችንና ስምምነቶችን፤አሁን ካምፓኒው እጅ ላይ ያሉ ስራዎችን ወ.ዘ.ተ ቢያንስ አንድ ሳምንት ወስደህ በደንብ ብታጠና
2/የካናፓኒውን ሰራተኞች
፡
#ክፍል_አምስት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍሰሀ
===
የመጀመሪያ ቀን እይታ የሰው ልብን መአከላዊ ስፍራ ለመያዝ ወይም ለመቆጣጠር ወሳኝ ነው ይባል የለ፡ይሄንን ፕሪንስፕል ተከትዬ በሕይወቴ የመጨረሻውን መሽቀርቀር ነው የተሸቀረቀርኩት..ምን አልባት ይሄንን መልሼ የምደግመው ከእለታት አንድ ቀን ልቤን የምታቀልጥ ልእልት አግኝቼ ሚስቴ አድርጌ በማገባት ቀን ብቻ ሊሆን ይችላል፡፡የኢጣሊያን ብራንድ ሱፍ ከእንግሊዝ በልዩ ትዕዛዝ የተገዛ ጫማ ፤በየሰው እፍንጫ ሲደርስ ከልብ ውስጥ ፍቅር ..ሰላምና ፍሰሀን የሚያመነጩትን ህብረ ህዋሳቶችን የሚያነቃቃ ልዩ የፈረንሳይ ሽቶ …..በአጠቃላይ በእጄ ላይ ያደረግኩት ሰዓት በጣቴ ያጠለቅኩት የአልማዝ ቀለበት….በዩኒቨርሲት ከገበየውት ዕውቀት በተጨማሪ ያለውበትን እና የሚገባኝን የህይወት ደረጃ በትክክል የሚያንፀባርቁና የሚያረጋግጡ እንደሚሆን እርግጠኛ ሆኜ ነው ከቤቴ የወጣውት
አስደማሚውንና የተንጣለለውን ቢሮዬን ተረከብኩ….በመጀመሪያ በአስተዳዳሪው መሪነት በየክፍሉ እየዞርኩ ሰራተኞችን በመተዋወቅ ነበር የጀመርኩት..ተስፋ ሰጪና አበረታች ሁኔታ ነው ያጋጠመኝ…ከወጣት እስከአዛውንት የዕድሜ ክልል የሚገኙ ሰራተኞች እኔን በአክብሮትና በመሽቆጥቆጥ እናም ደግሞ በፍራቻ ነበር የተዋወቁኝ ..ይሄ ደግሞ አሪፍ ምልክት ነው..ሁሉን በፈለኩት መጠን ለፈለኩት ተግባር በማሰማራት ተፈላጊውን ውጤት በማምጣት አባቴን አኮራዋለው ..ይሄንን ካምፓኒም ሶስቱንም ባለድርሻ አሳምኜ በዕድሜ ልክ እርስትነት ገዢ ሆኜ እሾምበታለው….፡፡
ቀጥሎ የየክፍሉን ኃላፊዎች ነበር ቢሮዬ ሰብስቤ ስለጠቅላላው የካማፓኒው እንቅስቃሴ ገለጻ እንዲያደርጉልኝ ያደረግኩት….አራት ሰዓት አካባቢ ለሶስት ወር እሰራዋለው ብዬ ከአወጣውት ዕቅድ ላይ በአንድ ሳምንት ውስጥ መስራት የሚገባኝን የስራ ዕቅድ በወረቀት ጫር ጫር አደረግኩና ፀሀፊዎ በኮምፒተር እንድትጽፍልኝ ስለፈለኩ ጠረጰዛዬ ላይ ያለውን መጥሪያ ተጫንኩት…ተላላኪዋ መጣችና ምን እንደምፈልግ ጠየቀችኝ…
‹‹ፀሀፊዋን ፈልጌ ነበር…››
‹‹ውይ..የለችም››
‹‹የለችም ማለት..?በስራ ሰዓት የት ሄደች…?››ኮስተር ብዬ ጠየቅኩ…..አዎ ከአሁኑ ቆፍጠን እና ጠንከር ካላልኩ ከግማሽ በላይ አዛውንት ያሉበትን ከመቶ በላይ የሆኑ ሰራተኞችን በስርአት ልመራቸው አልችልም…አዎ አንዳይንቁኝ ለማንም ፊት ማሳየት የለብኝም ..ይሄ አቋሜ ነው፡፡
‹‹ጋሼ እኔ እንጃ ..ግን ትናንትም አልመጣችም..ዘመድ ሞቶባታል ሲባል ሰምቼያለው››
‹‹እሺ በቃ …በሩን ዘግተሸ ውጪልኝ››
ሹክክ ብላ ወጣችን በራፉን ዘጋችልኝ፡፡
‹‹አስተዳደሩ ጋ ስልክ ደወልኩ››
‹‹ሄሎ አቶ ሰይፉ››ቆፍጠን ብዬ
‹‹አቤት አቶ ፍሰሀ ምነው ፈለከኝ..? ልምጣ…..?››ተሸቆጠቆጡ
..አይ እቺ ወንበር..ብታዩ እኮ የስልሳ አምስት አመት የሰማይ ስባሪ የሚያህሉ ሰውዬ ናቸው…
‹‹አይ ፀሀፊዋ የለችም አሉኝ ..የሚያቀውቁት ነገር አለ…..?››
‹‹ይቅርታ ሰው መተካት ነበረብኝ..አክስቷ ሞታ የሳምንት እረፍት ወጥታለች፡፡››
‹‹ለአክስት ሞት አንድ ሰማንት…..?ለአክስት ይሄን ያህል ከፈቀዳችሁ እናት ስትሆን ደግሞ ወር ነው ማለት ነው..?››
‹‹አይ እንደሱ እንኳን አይደለም…ለቅሶው መቀሌ ነው …ራቅ ስለሚል ነው….አሁን የእኔን ጸሀፊ እልክልሀለው››
‹‹እሺ ላኩልኝ…ሌላውን በሄደት እናተካክለዋለን፡፡››ስልኩን ዘጋውት…
አያያዜ ለራሴ አስገረመኝ …..በዚሁ ከቀጠልኩማ በቃ አዳሜን ሽር ነው ማደርጋት……‹አያየዙን አይተው ጭብጦውን ቀሙት › የሚለውን ተረት እንዳይተረትብኝ ጥሩ መንገድ ላይ ነው ያለውት …አዎ ለራሴ እንደዛ ነው እየተሰማኝ ያለው …
ከ3 ደቂቃ ቡኃላ በራፉ በጥቂቱ ተንኳኳና ተከፈተ….በእኔው እድሜ አካባቢ ያለች ቸኮሌት ቀለም ያላት ልጅ እንደቀጭኔ የረዘመ አንገቷን አስቀድማ ወደውስጥ ገባች…ከአይኖቾ የሚረጨው ጨረር ልቤን ሲወጋኝ ታወቀኝ …ፀጉሯን አንድ ላይ አስራው ወደፊት በትከሻዋ በማምጣት ለቃው በደረቷ ወርዶ በጡቷቿ መካከል አልፎ እንብርቷ አካባቢ ደርሶል…አለባበሶ መጥፎም ጥሩም የማይባል መካከለኛ አይነት ነው፡፡ ‹ኖ ሜካፓ አትትቀባም ኦል…..›እንደተፈጠረች ምንም ባልነካካው በኦረጂናል ቆዳዋ ነች… ብቻ በድምሩ የሆነ ነገሯ አስደነገጠኝ….ከሁሉ በላይ ቁመቷ ያሰፈዝዛል…<ይሄን ሁሉ ቁመት ያሸከማት ምን እንድታደርግበት ነው.. ? በውስጤ የተፈጠረብኝ ጥያቄ ነበር…
‹‹አቤት ምን ነበር አልኳት››የተጨማደደ ፊቴን ሳልፈታ…. ሙሉ በሙሉ ገባችና በራፉን ዘግታ ወደ እኔ ቀረበች……ወደላይ አንጋጥጬ እያየዋት
‹‹ፊናን እባላለው…..ምንድን ነበር እንዲፃፍልህ የፈለከው..?››አለቺኝ ከእኔ በላይ በሆነ መኮሳተር
‹‹ፀሀፊዋ አንቺ ነሽ››ምንሽም ፀሀፊ አይመስል የሚል መልዕክት በሚያስተላልፍ የድምጽ ቅላፄ
‹‹አዎ ነኝ..››
‹‹ማን መሆኔን አውቀሻል….››አልኳት እስከአሁን መላው ሰራተኞቼ ለእኔ እያሳዩ የነበረውን መሽቆጥቆጥ እሩቡንም ከእሷ ስላላገኘው ስለማንነቴ ከለማወቅ ነው ብዬ በመገመት፡፡
‹‹አቶ ፍሰሀ የኤም.ዲ.ቲ ካንፓኒ ዋና ስራ አስኪያጅ…ፊት ለፊትህ እኮ ከፎቶህ ጋር ተፃፎ ይነበባል…››በሀገራችን ያልተለመደ የሚመስል ሰማያዊ ቀለም ያላቸው የዓይን ብሌን ነው ያላት.. ከሆነ ኮከብ የተሸረፍ የሚመስሉ አደገኛ ዓይኖቾን እያንከባለለችብኝ
‹‹ጥሩ ነው..አንቺ ግን የዚህ ካምፓኒ ሰራተኛ ነሽ…...?ቅድም ሰራተኞችን ስተዋወቅ ተገናኝተናል..?››ትእቢቷን ባለማመን ደግሜ ሌሎች ጥያቄዎች ጠየቅኳት
‹‹አዎ የጋሽ ሰይፉ ----ፀሀፊ ነኝ…በመጣህ ጊዜ ቢሮ አልነበርኩም..ስለዚህ አልተገናኘንም ››
‹‹በይ እዛ ወንበር ላይ ተቀመጪና በራሴ ላፕቶፕ ይሄንን ገልብጪልኝ..በፍጥነት ነው የምፈልገው፡፡
‹‹በፍጥነት ማለት..?፡፡››
‹‹በ15 ደቂቃ››አቀበልኳት….ተቀበለቺኝና ላፕቶፑ ፊት ለፊት ተቀመጠች….መጻፍ ጀመረች….ጨርሳ ስታስረክበኝ ገርሞኝ ሰዓቴን አየው 6 ደቂቃ ብቻ ነው የፈጀባት…
‹‹እየው…››አለቺኝ በተቀመጠችበት ልክ ለድርድር የመጣች ጉረኛ ባለጉዳይ አንደኛውን እግሯን በአንደኛው ላይ አፈናጣ በግምሽ እይታ እያየቺኝ…እግሮቾን በመደራረቦ የለበሰችው ጉርድ ቀሚስ በመጠኑ ወደላይ ስለተሰበሰበ ወደጭኗ የሚጠቁም የሆነ ሸለቆ አይነት ምስል አይኔ ላይ ብዥታ ፈጠረብኝ..ይህቺ አለሌ ዱርዬ ሳትሆን አትቀርም ደረጃዬን በሚመጥን ሁኔታ እራሴን መቆጣጠር ይገባኛል ›በማለት ከውስጤ ተማከርኩና
‹‹አይ ቀስ ብዬ አየዋለው….ለጊዜው ጨረስን…ስፈልግሽ ጠራሻለው ››ብዬ እንድትወጣልኝ አዘዝኮት
‹‹እሺ ..››ብላኝ ከተቀመጠችበት በመለጠጥ ተነሳችና የሆነ ኪነ-ጥበባዊ በሆነ አረማመድ ወጥታ ሄደች…ይሄ አረማመዶ ተፈጥሮዊ ነው ወይስ የተጠና በልምምደ የተገኘ…..?ሁል ጊዜ የምትጠቀምበት ነው ወይስ ለማጥመድ የፈለገችውን እንደእኔ አይነነት አጎጊ ወንድ በሚያጋጥማት የክት ቀን የምትጠቀምበት…በጊዜ ሄደት የማረጋግጠው ይሆናል፡፡
አምስት ደቂቃ ስለእሷው ሳስብ ቆየውና..ቆይ እስኪ የሰራቸውን ልየው ብዬ ላፕቶፔን ወደራሴ በማስጠጋት ከፍቼ ማየት ጀመርኩ …ልቅም አድርጋ ያለምንም እንከን ነው የሰራችው..ግን ከታች ጻፊ ያላልኳትን ጨምራ ጽፋለች፡፡
‹‹ስለ ዕቅድህ ያለኝ አስተያየት››ብሎ ይጀምራል
1/ይንን ዕቅድ ወደተግባር ለመተግበር ከመሞከርህ በፊት የካምፓኒውን የስራ አካሄዶች፤ከሌሎች ካምፓኒዎች ጋር ተደረጉ የስራ ውሎችንና ስምምነቶችን፤አሁን ካምፓኒው እጅ ላይ ያሉ ስራዎችን ወ.ዘ.ተ ቢያንስ አንድ ሳምንት ወስደህ በደንብ ብታጠና
2/የካናፓኒውን ሰራተኞች
👍6
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍስሀ
===
ስልኬን አነሳውና ደወልኩ አስተዳደሩ ቢሮ
‹‹…ሄሎ የሴት ድምጽ ነው››
‹‹ማነች ፀሀፊዋን ቢሮ ባስቸኮይ ነይ በያት››
‹‹ፀሀፊዋ ነኝ››
‹‹እንግዲያው ቶሎ ነይ…ከአለቃሽ ጋር..አሁኑኑ ››ጆሮዋ ላይ ጠረቀምኩባት…ልክ አስገባቸዋለው..ሁለቱንም ለድፍረታቸው ተገቢውን ትምህርት ሰጪ ቅጣት ያገኟታል…
እኛ ኢትዬጵያውያን ለወሬ ያለን ፍቅር ለራሳችን ካለን ፍቅር በብዙ እጥፍ ይበልጣል፡፡እንደህዝብ ብቻ ሳይሆን በከፍተኛ ደረጃ ተምረዋል በሚባሉት የህብረተሰብ ደረጃ ጨምር የ<critical thinking >ልምምድ የለንም… የሰማነውን ወሬ ‹‹ለምን?›› ‹‹እንዴት?›› ‹‹የት?›› ‹‹ መቼ?›› ብለን በመጠየቅ የነገሩን ብልት በታትነን ለማየት የምናደርገው ጥረት ለዜሮ የቀረበ ነው፡፡የሰማነውን ወሬ ወይም መረጃ በዚህ መጠን መመርመር ደግሞ የመረጃዎችን ጥራት ለመጨመር..እርግጠኝነቱን አስተማማኝ ለማድረግ እና እወነተኝነቱን በአስተማማኝ መንገድ ለማረጋገጥ ወሳኝ መንገዶች ናቸው፡፡ ሰምተን ሳንጨርስ ለሌላው መናገር እንጀምራለን፡፡
መጡ‹‹ዝጉትና ቁጭ በሉ…››
ፊት ለፊት ተቀመጡ
‹‹ምን እየተሰራ ነው አቶ ሰይፉ››
‹‹ምን አጠፋን ጌታዬ…››በሚርበተበት አንደበት
‹‹እንደዚህች አይነት ሰራተኛ ይልኩብኛል…ነው ወይስ ይህንን እንድታደርግ እርሶ ነዎት የላኳት››
በቆሪጥ የእሷን መርበትበት ለማየት አይኖቼን ወደእሷ ስልክ ጭራሽ የምለውንም እየሰማች አይመስልም…ዘና ብላ የእጆቾን ጣቶች እየዘረጋችና እያጠፈች ከራሷ ጋር ትጫወታለች፡፡
<አረ እኔ…ለመሆኑ ምን አጠፋች?››
<በቃ ቡኃላ አናግሮታለው ከእሷ ጋር ልጨርስ> አመሰግናለው››
‹‹እሺ አቶ ፍሰሀ››ሹክክ ብለው ወጥተው ሄዱ…
ምን ልበላት እንድትደነግጥ እንዴት ልጩህባት እያልኩ በውስጤ ቃላት ስምርጥ
‹‹አንድ ነገር ልምከርህ›› አለቺኝ….
ይህቺ ልጅማ ጤነኛ አይደለችም…‹‹ምን አልሺኝ››
በምንም አይነት ሁኔታ ተራ ሰራተኞች ፊት የማናጅመንት አባላቶችህን እንዲህ ዝቅ አድርገህ አትናገር..ስህተት ቢሰሩም ጥፋት ቢኖርባቸውም ብቻቸውን ጠርተህ ነው ማነጋገር ያለብህ..ምክንያቱም አንተ ስታበሻቕጣቸው ያየ የበታች ሰራተኛ በትክክል ሊታዘዛቸው አይችልም. ያ ደግሞ ዞሮ ዞሮ የካማፓኒውን እፊሸንሲ ያወርደዋል…ያ ማለት ደግሞ ዞሮ ዞሮ በሰተመጨረሻ ያንተኑ አፈፃፀም ነው የሚጎዳው››
‹‹ጨረሽ››
‹‹አዎ ጨርሼያለው…ለምንድነበር የፈለከኝ?››
‹‹ማን ስለሆንሽ ነው ያለዘዝኩሽንን የሰራሽው?››
‹‹ምነው..? ላግዝህ ብዬ ነው››
‹‹ማን ስለሆንሽ ነው ምታግዤኝ?››
<አንድ ሰውን ለማገዝ እኮ ማንም መሆንን አይጠይቅም …ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው..››
ባክሽ አትቀባጥሪ ..ያ ሽማጊሌ ነው አይደል እንዲህ እንድታደርጊ የነገረሽ?..››…..በጥቂት ቀን ውስጥ ማን መሆኔን አሳየዋለው..አንቺ ግን ለእንጀራሽ ስትይ አደብ ግዤ>>
<<አንተም ለካንፓኒው ህልውና ሆነ ለራስህ የስራ ስኬት ስትል ምክሬን ስማ…..ደግሞ ለሽማግሌው ክብር ይኑርህ..ቅድም በስልክ ስታበሻቅጣቸው ላብ ሲያሰምጣቸው ነበረ…ለእሳቸው ሳይሆን ለራስህ ስትል አክብራቸው ..ደህና ሁን..››ብላኝ መቀመጫዋን ለቃ ወጥታ በራፍን በላዬ ላይ ዘግታ ሄደች…
አሁን አልተናደድኩም ..በጣም ደነገጥኩ…..ምንድነች ይህቺ ልጅ ..?ማንን ተማምና ነው እንዲህ መስመር የለቀቀችው…?እራሴን አመመኝ …ከዚህ በላይ ማሰብ ስላልቻልኩ ቢሮዬን ለቅቄ ወጣው ..ልጠጣና ልረሳት..እና ነገ አባርራታለው››
===
በጥዋት እንደገባው…አስጠራዋት….
‹‹እሺ ይህቺን ደብዳቤ ፃፊልኝ››
ቃል ሳትተነፍስ ተቀበለቺኝና ላፓቶፑ ፊትለፊት ተቀመጠችና መፀፋ ጀመረች…እየተከታተልኳት ነው….ስትባሳጭ ስትደነግጥ ለማየት ነበር በትኩረት እየተከታተልኮት የነበረው…ምንም አይነት የስሜት ለውጥ አልታየባትም …ደብዳቤው ስለ እሷ እንደሆነ አልገባትም ማለት ነው…ስሞን እያነበበች እንዴት አይገባትም…..?
‹‹ለወ/ሪት ፌናን ገመዳ
ጉዳዩ ፡ከስራ መሰናበትን ይመለከታል፡፡
ከላይ በርዕሱ ለመግለጽ እንደተሞከረው ካምፓኒውን ወደተሻለ ደረጃ ለማሳደግ አንድአንድ ለውጦች ማድረግ የግድ አስፈላጊ ስለሆነና ለለውጡ የሚመጥኑ ሰራተኞችና ማሰማራት የግድ በመሆኑ ይህ ደብዳቤ ከደረሶት ቀን አንስቶ ከስራ የተሰበናበቱ መሆንን አሳውቃለው፡፡
‹ከሰላምታ ጋር›
ፍሰሀ
ዋና ስራ አስኪያጅ
**
ይንን ነበር እንድትጽፍ የሰጠዋት..ለትዕቢተኛ እና ለስረአት አልበኛ ምህረት እንደሌለኝ እሷንም ሆነ ቀሪ ሰራተኞችን ማስተማር እፈልጋለው..እርግጥ የሰራችው ስራ ስህተት መሆኑን ተረድታ ይቅርታ ከጠየቀቺኝ ..በመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ልምራት እችላለው..አሁን ሳያት ግን ይቅርታ ለመጠየቅ ማሰቧን የሚጠቁም ምንም አይነት ምልክት አላየውም፡፡
‹‹ጨርሼያለው ፕሪንት ላድርገው››አለችኝ ጭራሽ የደሞዝ ማሻሻያ ደብዳቤ እንደደረሰው ሰራተኛ ፈገግ ብላ
‹‹አዎ አድርጊውና ልፈርም››
አዘዘችና ወደሚቀጥለው ክፍል ሄደች..ፕሪንተሩ ያለው የሚቀጥለው ክፍል ነው፡፡
ይዛ መጣችና አቀበለቺኝ… ልትወጣ ስትል‹‹ቆይ ልፈርምና መዝገብ ቤት ትወስጂዋለሽ››አልኳት ቆማ ትጠብቀኝ ጀመር..
በዚህ አይነት ስሜት ውስጥም እያለው የተመዘዘ ቁመቷን አለማድነቅ አልቻልኩም…..
ከመፈረሜ በፊት ማንበብ ጀመርኩ…‹‹እንዴ ምንድነው የጻፍሺው…?››እስኪ የሰጠውሽን ረቂቅ ስጪኝ…ወረቀቱን ልታነሳ ጎንበስ ስታል ጡቷቾ ተጋልጠው እይታዬ ውስጥ ገቡ..እርግጠኛ ነኝ ጡት ማስያዥ አላደረገችም….ብታደርግማ ይሄን ሁሉ የጡቶን ክፍል በግልፅ ማየት አልችልም ነበር……ከጠረጳዛው ላይ አነሳችና ሰጠቺኝ….
ከስራ መሰናበትን ይመለከታል ነው የሚለው..አንቺ የ30 ቀን ማስጠንቀቂያ መስጠትን ይመለከታ ብለሽ ነው የጻፍሺው…
ዝም ብለህ በፀባይ ብትጠይቀኝ ኖሮ ከነገ ጀምሮ ቀርልህ ነበር….ግን ነገም በሌላ ሰራተኛ ላይ ተመሳሳዩን ላርግ ስለምትል ህጉን እያስተማርኩህ ነው…‹‹ዝም ብለህ በፈለከው ሰዓት የፈለከውን ሰራተኛ ማባረር አትችልም….አንደኛ ይሄን ስራ ያንተ ሳይሆን የአስተዳደሩ ስለሆነ ለእሳቸው ብትተውላቸው….በስልጣንህ ተመክተህ አይ እኔ መስራት አለብኝ የምትል ከሆነ ደግሞ አንደኛ የሀገሪቱን የአሰሪና ሰራተኛ ህግ ሁለተኛ ሰራተኞች ከካንፓኒው ጋር የገቡትን የቅጥር ውል አንብበህ በውሉ ላይ በሰፈረው ህግ እና ደንብ መሰረት ነው እርምጃ መውሰድ የምትችለው…እንደ አንድ ማናጀር ሰውን ሳይሆን ኮንትራትን ነው ማስተዳደር ያለብህ …
በቃ ውጪልኝ..ደብዳቤውን ቀዳድጄ ቅርጫት ውስጥ ከተትኩና ቤሮውን ለቅቄ ወጣው ..በዚህ ስሜት ሌላ ምንም አይነት ስራ መስራት አልችልም….
ምን እየሆንኩ ነው…..አንድ ተራ ፀሀፊ መስመር ማስገባት ያልቻልኩ ሌሎቹን ምክትል ስራአስኪያጁን ጨምሮ የየክፍል ሀላፊዎች እንዴት አድርጌ ልመራ ነው…?አካሄዴንማ ማስተካከል አለብኝ...
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን መልካም ምሽት🙏
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍስሀ
===
ስልኬን አነሳውና ደወልኩ አስተዳደሩ ቢሮ
‹‹…ሄሎ የሴት ድምጽ ነው››
‹‹ማነች ፀሀፊዋን ቢሮ ባስቸኮይ ነይ በያት››
‹‹ፀሀፊዋ ነኝ››
‹‹እንግዲያው ቶሎ ነይ…ከአለቃሽ ጋር..አሁኑኑ ››ጆሮዋ ላይ ጠረቀምኩባት…ልክ አስገባቸዋለው..ሁለቱንም ለድፍረታቸው ተገቢውን ትምህርት ሰጪ ቅጣት ያገኟታል…
እኛ ኢትዬጵያውያን ለወሬ ያለን ፍቅር ለራሳችን ካለን ፍቅር በብዙ እጥፍ ይበልጣል፡፡እንደህዝብ ብቻ ሳይሆን በከፍተኛ ደረጃ ተምረዋል በሚባሉት የህብረተሰብ ደረጃ ጨምር የ<critical thinking >ልምምድ የለንም… የሰማነውን ወሬ ‹‹ለምን?›› ‹‹እንዴት?›› ‹‹የት?›› ‹‹ መቼ?›› ብለን በመጠየቅ የነገሩን ብልት በታትነን ለማየት የምናደርገው ጥረት ለዜሮ የቀረበ ነው፡፡የሰማነውን ወሬ ወይም መረጃ በዚህ መጠን መመርመር ደግሞ የመረጃዎችን ጥራት ለመጨመር..እርግጠኝነቱን አስተማማኝ ለማድረግ እና እወነተኝነቱን በአስተማማኝ መንገድ ለማረጋገጥ ወሳኝ መንገዶች ናቸው፡፡ ሰምተን ሳንጨርስ ለሌላው መናገር እንጀምራለን፡፡
መጡ‹‹ዝጉትና ቁጭ በሉ…››
ፊት ለፊት ተቀመጡ
‹‹ምን እየተሰራ ነው አቶ ሰይፉ››
‹‹ምን አጠፋን ጌታዬ…››በሚርበተበት አንደበት
‹‹እንደዚህች አይነት ሰራተኛ ይልኩብኛል…ነው ወይስ ይህንን እንድታደርግ እርሶ ነዎት የላኳት››
በቆሪጥ የእሷን መርበትበት ለማየት አይኖቼን ወደእሷ ስልክ ጭራሽ የምለውንም እየሰማች አይመስልም…ዘና ብላ የእጆቾን ጣቶች እየዘረጋችና እያጠፈች ከራሷ ጋር ትጫወታለች፡፡
<አረ እኔ…ለመሆኑ ምን አጠፋች?››
<በቃ ቡኃላ አናግሮታለው ከእሷ ጋር ልጨርስ> አመሰግናለው››
‹‹እሺ አቶ ፍሰሀ››ሹክክ ብለው ወጥተው ሄዱ…
ምን ልበላት እንድትደነግጥ እንዴት ልጩህባት እያልኩ በውስጤ ቃላት ስምርጥ
‹‹አንድ ነገር ልምከርህ›› አለቺኝ….
ይህቺ ልጅማ ጤነኛ አይደለችም…‹‹ምን አልሺኝ››
በምንም አይነት ሁኔታ ተራ ሰራተኞች ፊት የማናጅመንት አባላቶችህን እንዲህ ዝቅ አድርገህ አትናገር..ስህተት ቢሰሩም ጥፋት ቢኖርባቸውም ብቻቸውን ጠርተህ ነው ማነጋገር ያለብህ..ምክንያቱም አንተ ስታበሻቕጣቸው ያየ የበታች ሰራተኛ በትክክል ሊታዘዛቸው አይችልም. ያ ደግሞ ዞሮ ዞሮ የካማፓኒውን እፊሸንሲ ያወርደዋል…ያ ማለት ደግሞ ዞሮ ዞሮ በሰተመጨረሻ ያንተኑ አፈፃፀም ነው የሚጎዳው››
‹‹ጨረሽ››
‹‹አዎ ጨርሼያለው…ለምንድነበር የፈለከኝ?››
‹‹ማን ስለሆንሽ ነው ያለዘዝኩሽንን የሰራሽው?››
‹‹ምነው..? ላግዝህ ብዬ ነው››
‹‹ማን ስለሆንሽ ነው ምታግዤኝ?››
<አንድ ሰውን ለማገዝ እኮ ማንም መሆንን አይጠይቅም …ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው..››
ባክሽ አትቀባጥሪ ..ያ ሽማጊሌ ነው አይደል እንዲህ እንድታደርጊ የነገረሽ?..››…..በጥቂት ቀን ውስጥ ማን መሆኔን አሳየዋለው..አንቺ ግን ለእንጀራሽ ስትይ አደብ ግዤ>>
<<አንተም ለካንፓኒው ህልውና ሆነ ለራስህ የስራ ስኬት ስትል ምክሬን ስማ…..ደግሞ ለሽማግሌው ክብር ይኑርህ..ቅድም በስልክ ስታበሻቅጣቸው ላብ ሲያሰምጣቸው ነበረ…ለእሳቸው ሳይሆን ለራስህ ስትል አክብራቸው ..ደህና ሁን..››ብላኝ መቀመጫዋን ለቃ ወጥታ በራፍን በላዬ ላይ ዘግታ ሄደች…
አሁን አልተናደድኩም ..በጣም ደነገጥኩ…..ምንድነች ይህቺ ልጅ ..?ማንን ተማምና ነው እንዲህ መስመር የለቀቀችው…?እራሴን አመመኝ …ከዚህ በላይ ማሰብ ስላልቻልኩ ቢሮዬን ለቅቄ ወጣው ..ልጠጣና ልረሳት..እና ነገ አባርራታለው››
===
በጥዋት እንደገባው…አስጠራዋት….
‹‹እሺ ይህቺን ደብዳቤ ፃፊልኝ››
ቃል ሳትተነፍስ ተቀበለቺኝና ላፓቶፑ ፊትለፊት ተቀመጠችና መፀፋ ጀመረች…እየተከታተልኳት ነው….ስትባሳጭ ስትደነግጥ ለማየት ነበር በትኩረት እየተከታተልኮት የነበረው…ምንም አይነት የስሜት ለውጥ አልታየባትም …ደብዳቤው ስለ እሷ እንደሆነ አልገባትም ማለት ነው…ስሞን እያነበበች እንዴት አይገባትም…..?
‹‹ለወ/ሪት ፌናን ገመዳ
ጉዳዩ ፡ከስራ መሰናበትን ይመለከታል፡፡
ከላይ በርዕሱ ለመግለጽ እንደተሞከረው ካምፓኒውን ወደተሻለ ደረጃ ለማሳደግ አንድአንድ ለውጦች ማድረግ የግድ አስፈላጊ ስለሆነና ለለውጡ የሚመጥኑ ሰራተኞችና ማሰማራት የግድ በመሆኑ ይህ ደብዳቤ ከደረሶት ቀን አንስቶ ከስራ የተሰበናበቱ መሆንን አሳውቃለው፡፡
‹ከሰላምታ ጋር›
ፍሰሀ
ዋና ስራ አስኪያጅ
**
ይንን ነበር እንድትጽፍ የሰጠዋት..ለትዕቢተኛ እና ለስረአት አልበኛ ምህረት እንደሌለኝ እሷንም ሆነ ቀሪ ሰራተኞችን ማስተማር እፈልጋለው..እርግጥ የሰራችው ስራ ስህተት መሆኑን ተረድታ ይቅርታ ከጠየቀቺኝ ..በመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ልምራት እችላለው..አሁን ሳያት ግን ይቅርታ ለመጠየቅ ማሰቧን የሚጠቁም ምንም አይነት ምልክት አላየውም፡፡
‹‹ጨርሼያለው ፕሪንት ላድርገው››አለችኝ ጭራሽ የደሞዝ ማሻሻያ ደብዳቤ እንደደረሰው ሰራተኛ ፈገግ ብላ
‹‹አዎ አድርጊውና ልፈርም››
አዘዘችና ወደሚቀጥለው ክፍል ሄደች..ፕሪንተሩ ያለው የሚቀጥለው ክፍል ነው፡፡
ይዛ መጣችና አቀበለቺኝ… ልትወጣ ስትል‹‹ቆይ ልፈርምና መዝገብ ቤት ትወስጂዋለሽ››አልኳት ቆማ ትጠብቀኝ ጀመር..
በዚህ አይነት ስሜት ውስጥም እያለው የተመዘዘ ቁመቷን አለማድነቅ አልቻልኩም…..
ከመፈረሜ በፊት ማንበብ ጀመርኩ…‹‹እንዴ ምንድነው የጻፍሺው…?››እስኪ የሰጠውሽን ረቂቅ ስጪኝ…ወረቀቱን ልታነሳ ጎንበስ ስታል ጡቷቾ ተጋልጠው እይታዬ ውስጥ ገቡ..እርግጠኛ ነኝ ጡት ማስያዥ አላደረገችም….ብታደርግማ ይሄን ሁሉ የጡቶን ክፍል በግልፅ ማየት አልችልም ነበር……ከጠረጳዛው ላይ አነሳችና ሰጠቺኝ….
ከስራ መሰናበትን ይመለከታል ነው የሚለው..አንቺ የ30 ቀን ማስጠንቀቂያ መስጠትን ይመለከታ ብለሽ ነው የጻፍሺው…
ዝም ብለህ በፀባይ ብትጠይቀኝ ኖሮ ከነገ ጀምሮ ቀርልህ ነበር….ግን ነገም በሌላ ሰራተኛ ላይ ተመሳሳዩን ላርግ ስለምትል ህጉን እያስተማርኩህ ነው…‹‹ዝም ብለህ በፈለከው ሰዓት የፈለከውን ሰራተኛ ማባረር አትችልም….አንደኛ ይሄን ስራ ያንተ ሳይሆን የአስተዳደሩ ስለሆነ ለእሳቸው ብትተውላቸው….በስልጣንህ ተመክተህ አይ እኔ መስራት አለብኝ የምትል ከሆነ ደግሞ አንደኛ የሀገሪቱን የአሰሪና ሰራተኛ ህግ ሁለተኛ ሰራተኞች ከካንፓኒው ጋር የገቡትን የቅጥር ውል አንብበህ በውሉ ላይ በሰፈረው ህግ እና ደንብ መሰረት ነው እርምጃ መውሰድ የምትችለው…እንደ አንድ ማናጀር ሰውን ሳይሆን ኮንትራትን ነው ማስተዳደር ያለብህ …
በቃ ውጪልኝ..ደብዳቤውን ቀዳድጄ ቅርጫት ውስጥ ከተትኩና ቤሮውን ለቅቄ ወጣው ..በዚህ ስሜት ሌላ ምንም አይነት ስራ መስራት አልችልም….
ምን እየሆንኩ ነው…..አንድ ተራ ፀሀፊ መስመር ማስገባት ያልቻልኩ ሌሎቹን ምክትል ስራአስኪያጁን ጨምሮ የየክፍል ሀላፊዎች እንዴት አድርጌ ልመራ ነው…?አካሄዴንማ ማስተካከል አለብኝ...
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን መልካም ምሽት🙏
👍1
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
❤️ፌናን
===
ጥሎብኝ ውበት አድናቂ ነኝ፡፡ውበት ግን ምንድነው…?እኔ እንጃ ፡፡በስሜት ህዋሳታችን ተጠቅመን ወደ ውስጣችን ያስገባነው መረጀ ልባችን እና አዕምሮአችን ላይ በእኩል ጊዜ ሲደርስ እና መልሶ ወደ ስሜት ህዋሳታችን በመመለስ እንድንፈግ ወይም እንድንስቅ.. ወይ ደግሞ ጆሮአችን እንዲቆም ወይ ደግሞ በእግር ጥፍራችን የሚያቆም አይነት መደመም ላይ ሚጥለን ነገር ሲሆን ውበት ሚለውን ቃልን ልንጠቀም እንገደዳለን ፡፡
===
የእኔ ነገር … አሁን ስለውበት የእኔን ፍልስፍናዊ እሳቤ ልተነትንላችሁ ፈልጌ ሳይሆን ስለአዲሱ አለቃችን
ልነግራችሁ ስለፈለኩ ነው እንደዚህ ዙሪያ ጥምዝ ምሽከረከረው፡፡
ልጁ በጣም ያምራል…. በቃ የሆነ አትኩረው እንዲያዩት የሚያስገድድ ማግኔት ነገር ግንባሩ ላይ አለው…ለሆነ ሰከንዶች ያህል ደግሞ አትኩረው ሲያዩት አይን ደክም እንዲል ወይም እንዲርገበገብ የሚያደርግ አዚም አለበት….አዎ በአቅራቢያው ሲሆኑ ደግሞ ልብ በደቂቃ መምታት ከሚገባት ምት ወይም ማሰማት ከሚገባት ድውድውታ በሆነ ፐርሰንት እንዲጨምር የሚያደርግ ስውር ኃይል አለው፡፡
ጅኔራላይዝድ አረኩት አይደል…ይሄ ስሜት ስለአዲሱ ሀለቃዬን በተመለከተ እኔን የተሰማኝ ነው እንጂ የቢሮ
ሴት ሁሉ እንደዚህ እያሰባል ወይም እንዲህ ይሰማዋል ልላችሁ አይደለም….
ግን ገና ግማሽ ብስል ግማሽ ጥሬ ነገር ነው…ሙሉበሙሉ ለመብሰል ብዙ እንጨት መፍጀቱ አይቀርም… የዕውቀት ችግር የለበትም ….ያለበት የልምድ ችግር ነው፡፡ደግሞ ነፍሱ በፍራቻ እየተንፈራፈረች መሆኗን በደንብ ያስታውቅበታል…እርግጥ ይሄንን ከእኔ በስተቀር ያወቀበት ሰው የለም…ሌላው የቢሮ ሰራተኞች ስለኃይለኝነቱ….ተቆጪና ተናዳጅ ስለመሆኑ ብቻ ነው የሚያወሩት…..
አንደኛ ቁጣውም ሆነ ጩኸቱ አርቴፊሻል መሆኑን ከንግግሩ ድምጸት እና ከሰውነቱ እንቅስቃሴ በቀላሉ መረዳት ይቻላል…… ኃይለኛና ተፈሪ ለመሆን እየጣረ ነው..ሀይለኛ እና ተፈሪ መሆን የፈለገው ደግሞ ይህንን ካምፓኒ በትክክል መምራት እንደሚችል እራሱን አላሳመነም….ግን ደግሞ ሌሎቹን በቁጣና በማስፈራራትና ሊያሳምን እየጣረ ነው… እያደረገ ያለው ይሄንን ነው….፡፡ግን በዚህ መንገድ ፍጽም አይሳካለትም… ምክንያቱም ቀድሞ እራሱን መሳማን ሳይችል እንዴት ነው ሌላውን ሊያሳምን የሚችለው…?ይሄ የብዙ ሰዎች ባህሪ ነው..ሁልጊዜ የሌላው ፀባይ እንዲስታካከል..ሌላው ሰው እንዲለወጥ…ሌላው ሰው ወንጀል መስራት እንዲያቆም..እነዛ ብድኖች ከሙስና እራሳቸውን እንዲያቅብና ሀቀኛ ዜጋ እንዲሆኑ በፍትህ ታጋይ ስም እንጠይቃለን… ዜጋ ሁሉ በሀቀኝነት ለሀገር ተገቢውን ግብር እንዲከፍል እንፈልጋለን..ለዛም ባለማሰላስ ብዙዎቻችን እንጮኸለን…እንጽፋለን፡፡ግን የጥያቄያችን መንገድ የተሳሳተ ነው……እኛስ እራሳችንን ሀቀኛ ለማድረግ ወስነናል ወይ .. …?እኛስ በገዛ ቤታችን ዲሞክራሲ ለማስፋት መስራት ጀምረናል ወይ……?በዚህ አመት ገቢያችንን ሳንደብቅ ለመንግስት ተገቢውን ግብር ለመክፈል ወስነናል..…?ከቀበሌ መታወቂያ ለማውጣት ስንል የእጅ መንሻ አንከፍልም ለማለት ቁርጠኞች ነን ወይ……?
ሁላችንም በዛ መንገድ አይደለም የምናሰበው..ጉዞችን ወደ ውጤት የሚመራን አይነት አይደለም…ሌላውን ሰው የሆነ ነገር እንዲያደርግ ለማበረታታት ውጤታማው ዘዴ መጀመሪያ አድርጎ በተግባር ማሳየት ብቻ ነው….እና ይሄ አለቃዬ እራሱ ውስጡን ሳያሳምን ሰራተኞቹን በግድ እንደዛ አስቡ እያላቸው ነው…ቢሆንም እኔ እረዳዋለው…ይሄንን ካምፓኔ በብቃት የመምራት ችሎታ እንዳለው ውስጡ እንዲያምን አደርገዋለው…ግን ለምን እረዳዋለው…? እኔ እንጃ ..እንደውም እሱን ከመርዳት ይልቃ ላለመርዳት በቂ ምክንያ ነበረኝ….ምን አይነት ምክንያት…? ካላችሁኝ አሁን አልነግራችሁም….በደፈናው ግን ይሄን ካምፓኒ የመምራት ጉዳይ ባይሳክለት እኔ ተጠቃሚ ነኝ፡፡
ይሄን ሁሉ ምስቅልቅል ሀሳብ እያብሰለሰልኩ ያለውት ቢሮዬ ቁጭ ብዬ ነው….ሀሳቤን የገታውት አቶ ሰይፉ ከውጭ እያለከለኩ መጥተው በመሰላቸት መንፈስ ወንበራቸው ላይ ዝርፍጥ ብለው ረጅም የእፎይታ ትንፋሽ ሲተነፍሱ ሳይ ነው ፡፡
‹‹ምነው ጋሼ…?››እኔም ደንግጬ ጠየቅኳቸወ
‹‹ባክሽ ከእዚህ ልጅ ጋር እንዴት እንደምሰራ ግራ እየገባኝ ነው››
‹‹አይዞት ጋሼ …ጥቂት ጊዜ ነው… ይስተካከላል፡፡››
‹‹አይመስለኝም….ጡረታ መውጫ ጊዜዬ ደርሷል መሰለኝ››
‹‹አይ… ይሄን አይነት መሸነፍማ ከርሶ አልጠብቅም…አሁን ምን ተፈጠረ…?››
‹‹የሰራተኞች አመታዊ በዓል ለማክበር የተበጀተውን በጀት አላፀድቅም አለ››
‹‹ለምን አለ……?››
‹‹ብክነት ነው የሚል አመለካከት ነው ያለው…ይሄንን በዓል ላለፉት አስር አመት ስናከብር ቆይተናል.. ሰራተኞቻችን ከልጅ እስከ አዋቂው ይሄንን ቀን ልክ እንደ ሀይማኖታዊ ክብረበዓል ነው። የሚጠብቁት….ለዛውም እኮ በፕሌን ባህር ዳር ነበር ዕቅዱ..ግን ይሄንን ፈርቼ ከባጀቱ ላይ መቶ ሺ ብር ቀንሼ ወደቢሾፍቱ አዘዋውሬ ነበር ያቀረብኩለት››
‹‹እና ቁርጥ አድርጎ አይሆንም አለ…?››በብስጭት ስሜት ለማረጋገጥ ጠየቅኳቸው
‹‹አዎ ብሏል…››
‹‹የበጀቱን ሰነድ ይስጡኝ››
‹‹ምን ይረባሻል…?››
‹‹አስፈርመዋለዋ››
‹‹ጭራሽ አንቺ……?እንዴት እንደሚጠላሽ አታውቂም እንዴ……?እንድትባረሪ እንደሚፈልግ እኮ ነግሮኛል››
‹‹አውቃለው …እኔን በተመለከተ ባለው ስሜት ላይ ግራ መጋባት ውስጥ ስላለ ነው እንጂ አይጠላኝም …እንደውም ተቃራኒውን ነው…››
‹‹አይ አንቺ ልጅ…አንዴት እንደተንገሸገሸብሽ ስላላየሽ ነው….››
ከመቀመጫዬ ተነሳውን ወደ እሷቸው ወንበር ተጠጋው
‹‹ስጡኝ››
‹‹ቀዳዶ ፊትሽ ላይ እንደሚበትነው እያስጠነቀኩሽ ነው…በዛ ላይ ባንቺ የተነሳ ዳግመኛ እንዲናገረኝ አልፈልግም››
‹‹ግድ የሎትም… እርሶ ሳያዩ ከጠረጵዛ ላይ እንደወሰድኩት ነገረዋለው…››ብዬ እራሴው ወረቀቱን አነሳውና ቢሮውን ለቅቄ ወጣው…
እንደደረስኩ እንግዳ እያስተናገደ መሆኑን ፀሀፊው ስለነገረቺኝ ቁጭ ብዬ መጠበቅ ጀመርኩ..በነገራችን ላይ ፀሀፊው ከሄደችበት ለቅሶ ተመልሳለች…ከ7 ደቂቃ ቡኃላ ባለጉዳዩ ሲወጣ በዝግታ አንኳኩቼ ገባው….በተቀመጠበት ወንበር ወደኃላ ተለጥጦ ሲያዛጋ ነበር የደረስኩት….በራፉን ዘግቼ ወደወንበሩ በመሄድ ቁጨ አልኩ …ማዛጋቱን ጨረሰና እንደመስተካከል ብሎ ለሆነ ሰከናዶች ያህል ዝም ብሎ በገረሜታ ሲያየኝ ከቆየ ቡኃላ
‹‹ምነው የስራ መልቀቂያ ልታስገቢ ነው እንዴ የመጣሽው……?››አለኝ...
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
❤️ፌናን
===
ጥሎብኝ ውበት አድናቂ ነኝ፡፡ውበት ግን ምንድነው…?እኔ እንጃ ፡፡በስሜት ህዋሳታችን ተጠቅመን ወደ ውስጣችን ያስገባነው መረጀ ልባችን እና አዕምሮአችን ላይ በእኩል ጊዜ ሲደርስ እና መልሶ ወደ ስሜት ህዋሳታችን በመመለስ እንድንፈግ ወይም እንድንስቅ.. ወይ ደግሞ ጆሮአችን እንዲቆም ወይ ደግሞ በእግር ጥፍራችን የሚያቆም አይነት መደመም ላይ ሚጥለን ነገር ሲሆን ውበት ሚለውን ቃልን ልንጠቀም እንገደዳለን ፡፡
===
የእኔ ነገር … አሁን ስለውበት የእኔን ፍልስፍናዊ እሳቤ ልተነትንላችሁ ፈልጌ ሳይሆን ስለአዲሱ አለቃችን
ልነግራችሁ ስለፈለኩ ነው እንደዚህ ዙሪያ ጥምዝ ምሽከረከረው፡፡
ልጁ በጣም ያምራል…. በቃ የሆነ አትኩረው እንዲያዩት የሚያስገድድ ማግኔት ነገር ግንባሩ ላይ አለው…ለሆነ ሰከንዶች ያህል ደግሞ አትኩረው ሲያዩት አይን ደክም እንዲል ወይም እንዲርገበገብ የሚያደርግ አዚም አለበት….አዎ በአቅራቢያው ሲሆኑ ደግሞ ልብ በደቂቃ መምታት ከሚገባት ምት ወይም ማሰማት ከሚገባት ድውድውታ በሆነ ፐርሰንት እንዲጨምር የሚያደርግ ስውር ኃይል አለው፡፡
ጅኔራላይዝድ አረኩት አይደል…ይሄ ስሜት ስለአዲሱ ሀለቃዬን በተመለከተ እኔን የተሰማኝ ነው እንጂ የቢሮ
ሴት ሁሉ እንደዚህ እያሰባል ወይም እንዲህ ይሰማዋል ልላችሁ አይደለም….
ግን ገና ግማሽ ብስል ግማሽ ጥሬ ነገር ነው…ሙሉበሙሉ ለመብሰል ብዙ እንጨት መፍጀቱ አይቀርም… የዕውቀት ችግር የለበትም ….ያለበት የልምድ ችግር ነው፡፡ደግሞ ነፍሱ በፍራቻ እየተንፈራፈረች መሆኗን በደንብ ያስታውቅበታል…እርግጥ ይሄንን ከእኔ በስተቀር ያወቀበት ሰው የለም…ሌላው የቢሮ ሰራተኞች ስለኃይለኝነቱ….ተቆጪና ተናዳጅ ስለመሆኑ ብቻ ነው የሚያወሩት…..
አንደኛ ቁጣውም ሆነ ጩኸቱ አርቴፊሻል መሆኑን ከንግግሩ ድምጸት እና ከሰውነቱ እንቅስቃሴ በቀላሉ መረዳት ይቻላል…… ኃይለኛና ተፈሪ ለመሆን እየጣረ ነው..ሀይለኛ እና ተፈሪ መሆን የፈለገው ደግሞ ይህንን ካምፓኒ በትክክል መምራት እንደሚችል እራሱን አላሳመነም….ግን ደግሞ ሌሎቹን በቁጣና በማስፈራራትና ሊያሳምን እየጣረ ነው… እያደረገ ያለው ይሄንን ነው….፡፡ግን በዚህ መንገድ ፍጽም አይሳካለትም… ምክንያቱም ቀድሞ እራሱን መሳማን ሳይችል እንዴት ነው ሌላውን ሊያሳምን የሚችለው…?ይሄ የብዙ ሰዎች ባህሪ ነው..ሁልጊዜ የሌላው ፀባይ እንዲስታካከል..ሌላው ሰው እንዲለወጥ…ሌላው ሰው ወንጀል መስራት እንዲያቆም..እነዛ ብድኖች ከሙስና እራሳቸውን እንዲያቅብና ሀቀኛ ዜጋ እንዲሆኑ በፍትህ ታጋይ ስም እንጠይቃለን… ዜጋ ሁሉ በሀቀኝነት ለሀገር ተገቢውን ግብር እንዲከፍል እንፈልጋለን..ለዛም ባለማሰላስ ብዙዎቻችን እንጮኸለን…እንጽፋለን፡፡ግን የጥያቄያችን መንገድ የተሳሳተ ነው……እኛስ እራሳችንን ሀቀኛ ለማድረግ ወስነናል ወይ .. …?እኛስ በገዛ ቤታችን ዲሞክራሲ ለማስፋት መስራት ጀምረናል ወይ……?በዚህ አመት ገቢያችንን ሳንደብቅ ለመንግስት ተገቢውን ግብር ለመክፈል ወስነናል..…?ከቀበሌ መታወቂያ ለማውጣት ስንል የእጅ መንሻ አንከፍልም ለማለት ቁርጠኞች ነን ወይ……?
ሁላችንም በዛ መንገድ አይደለም የምናሰበው..ጉዞችን ወደ ውጤት የሚመራን አይነት አይደለም…ሌላውን ሰው የሆነ ነገር እንዲያደርግ ለማበረታታት ውጤታማው ዘዴ መጀመሪያ አድርጎ በተግባር ማሳየት ብቻ ነው….እና ይሄ አለቃዬ እራሱ ውስጡን ሳያሳምን ሰራተኞቹን በግድ እንደዛ አስቡ እያላቸው ነው…ቢሆንም እኔ እረዳዋለው…ይሄንን ካምፓኔ በብቃት የመምራት ችሎታ እንዳለው ውስጡ እንዲያምን አደርገዋለው…ግን ለምን እረዳዋለው…? እኔ እንጃ ..እንደውም እሱን ከመርዳት ይልቃ ላለመርዳት በቂ ምክንያ ነበረኝ….ምን አይነት ምክንያት…? ካላችሁኝ አሁን አልነግራችሁም….በደፈናው ግን ይሄን ካምፓኒ የመምራት ጉዳይ ባይሳክለት እኔ ተጠቃሚ ነኝ፡፡
ይሄን ሁሉ ምስቅልቅል ሀሳብ እያብሰለሰልኩ ያለውት ቢሮዬ ቁጭ ብዬ ነው….ሀሳቤን የገታውት አቶ ሰይፉ ከውጭ እያለከለኩ መጥተው በመሰላቸት መንፈስ ወንበራቸው ላይ ዝርፍጥ ብለው ረጅም የእፎይታ ትንፋሽ ሲተነፍሱ ሳይ ነው ፡፡
‹‹ምነው ጋሼ…?››እኔም ደንግጬ ጠየቅኳቸወ
‹‹ባክሽ ከእዚህ ልጅ ጋር እንዴት እንደምሰራ ግራ እየገባኝ ነው››
‹‹አይዞት ጋሼ …ጥቂት ጊዜ ነው… ይስተካከላል፡፡››
‹‹አይመስለኝም….ጡረታ መውጫ ጊዜዬ ደርሷል መሰለኝ››
‹‹አይ… ይሄን አይነት መሸነፍማ ከርሶ አልጠብቅም…አሁን ምን ተፈጠረ…?››
‹‹የሰራተኞች አመታዊ በዓል ለማክበር የተበጀተውን በጀት አላፀድቅም አለ››
‹‹ለምን አለ……?››
‹‹ብክነት ነው የሚል አመለካከት ነው ያለው…ይሄንን በዓል ላለፉት አስር አመት ስናከብር ቆይተናል.. ሰራተኞቻችን ከልጅ እስከ አዋቂው ይሄንን ቀን ልክ እንደ ሀይማኖታዊ ክብረበዓል ነው። የሚጠብቁት….ለዛውም እኮ በፕሌን ባህር ዳር ነበር ዕቅዱ..ግን ይሄንን ፈርቼ ከባጀቱ ላይ መቶ ሺ ብር ቀንሼ ወደቢሾፍቱ አዘዋውሬ ነበር ያቀረብኩለት››
‹‹እና ቁርጥ አድርጎ አይሆንም አለ…?››በብስጭት ስሜት ለማረጋገጥ ጠየቅኳቸው
‹‹አዎ ብሏል…››
‹‹የበጀቱን ሰነድ ይስጡኝ››
‹‹ምን ይረባሻል…?››
‹‹አስፈርመዋለዋ››
‹‹ጭራሽ አንቺ……?እንዴት እንደሚጠላሽ አታውቂም እንዴ……?እንድትባረሪ እንደሚፈልግ እኮ ነግሮኛል››
‹‹አውቃለው …እኔን በተመለከተ ባለው ስሜት ላይ ግራ መጋባት ውስጥ ስላለ ነው እንጂ አይጠላኝም …እንደውም ተቃራኒውን ነው…››
‹‹አይ አንቺ ልጅ…አንዴት እንደተንገሸገሸብሽ ስላላየሽ ነው….››
ከመቀመጫዬ ተነሳውን ወደ እሷቸው ወንበር ተጠጋው
‹‹ስጡኝ››
‹‹ቀዳዶ ፊትሽ ላይ እንደሚበትነው እያስጠነቀኩሽ ነው…በዛ ላይ ባንቺ የተነሳ ዳግመኛ እንዲናገረኝ አልፈልግም››
‹‹ግድ የሎትም… እርሶ ሳያዩ ከጠረጵዛ ላይ እንደወሰድኩት ነገረዋለው…››ብዬ እራሴው ወረቀቱን አነሳውና ቢሮውን ለቅቄ ወጣው…
እንደደረስኩ እንግዳ እያስተናገደ መሆኑን ፀሀፊው ስለነገረቺኝ ቁጭ ብዬ መጠበቅ ጀመርኩ..በነገራችን ላይ ፀሀፊው ከሄደችበት ለቅሶ ተመልሳለች…ከ7 ደቂቃ ቡኃላ ባለጉዳዩ ሲወጣ በዝግታ አንኳኩቼ ገባው….በተቀመጠበት ወንበር ወደኃላ ተለጥጦ ሲያዛጋ ነበር የደረስኩት….በራፉን ዘግቼ ወደወንበሩ በመሄድ ቁጨ አልኩ …ማዛጋቱን ጨረሰና እንደመስተካከል ብሎ ለሆነ ሰከናዶች ያህል ዝም ብሎ በገረሜታ ሲያየኝ ከቆየ ቡኃላ
‹‹ምነው የስራ መልቀቂያ ልታስገቢ ነው እንዴ የመጣሽው……?››አለኝ...
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
❤️ፌናን
===
‹‹ምነው የስራ መልቀቂያ ልታስገቢ ነው እንዴ የመጣሽው……?››አለኝ
‹‹አይ አይደለም››
‹‹እና ታዲያ እኔ እንደሆነ አልጠራውሽም …ልጠራሽ የምችልበት ምክንያትም የለኝም .. መልክ መልካምነት ከልዩ ስነምግባር ጋር አሞልቶ የሰጣት ፀሀፊዬ መጥታ ገላግላኛለች….››አለኝ የአሹሙር ለዛ ባለው ንግግር
‹‹በጣም ደስ ይላል…እወነትህን ነው ትሁትና ምርጥ ልጅ ነች..በነገራችን ላይ ከባሏ ጋር አብረን ነው የተማርነው …እሱን ብታየው ደግሞ ዋው.. የሚያሰኝ ውበት ያለው አፍ አስከፋች ሸበላ ልጅ ነው፡፡››አልኩት
የተኮስኩት የነገር ጥይት በትክክል አዕምሮውን መቶታል …በግርምትም በንዴትም አይኖቹን በልጥጦ ‹‹ስለስራ እኮ ነው እያወራሁሽ ያለሁት..ፀሀፊዬ ጎበዝ ሰራተኛ ነች ተስማማታኛለች ነው ያልኩሽ..ስለባሏ ውበት በዚህ አይነት ግነት ለእኔ መንገሩ ለምን አስፈለገ……?››
‹‹አይ እንዲሁ ለጠቅላላ ዕውቀት ያህል ነው…በዛውም እኔም የእሷ አድናቂ መሆኔን እንድታውቅ ፈልጌ ነው››
‹‹የእሷ ወይስ የባሏ…?››መልሶ ተኮሰብኝ
‹‹የሁለቱም››
‹‹እሺ አሁን ለምን መጣሽ…?ስራ እየተዉ በየቢሮው መዞር የስነምግባር ብልሹነት መሆኑን አታውቂም? ››
‹‹አውቃልው ግን አመጣጤ ስታዛጋ ሰምቼ ነው …አስር ደቂቃ ካለህ እዚህ ፊት ለፊታችን ካለ ካፌ አሪፍ የጀበና ቡና ስላለ ልጋብዝህ ስለፈለኩ ነው››
‹‹ምን…?››አደነጋገጡ አብረን እንደር ያልኩት ነው ያስመሰለው…
‹‹ምነው..…?አስር ደቂቃ እኮ ነው›››
‹‹አይ ይቅርብኝ ቡና አልጠጣም…››
‹‹ማኪያቶ ግን ትጠጣለህ…››
….ምንም ሳይለኝ ከመቀመጫው ተነሳና ጃኬቱን ከማንጠልጠያ ላይ በማንሳት እየለበሰ በተቀመጥኩበት ጥሎኝ ቢሮውን ትቶ ወጣ…. ከኃላ ተከተልኩት…እርምጃዬን ከእሱ ማስተካከል አልቻልኩት…. ሊፍት ውስጥ ቀድሞ ገባ ተከትዬው ገባው…ልክ ከረሜላ ከአፉ የነጠቁት ህፃን ይመስል ለንቦጩን ጥሏል….በውስጤ የታፈነውን ሳቅ እንዳያመልጠኝ የተጨነቅኩትን ጭንቀት ልገልጽላችሁ አልችልም፡፡
ከህንፃው ወጥተን መንገዱን እንደያዝን እርምጃዬን ከእርምጃው አስተካከልኩ…ስጠመዘዝ ተጠመዘዘና ተከትሎኝ ካፌ ገባ…
‹‹ምን ይምጣልህ ……?››ወንበር ይዘን እንደተቀመጥን ጠየቅኩት
‹‹ምን አገባሽ›› አለና አስተናጋጇን ጠርቶ ማኪያቶ አዘዘ እኔ የጀበና ቡና አዘዝኩ
‹‹አሁን በትክክል ወስኜያለው››
‹‹ምኑን…? ›››አልኩት
እዚህ ካምፓኒ እግሬ እንደረገጠ አንቺን ለማባረር መወሰኔ ቀድሞውንም ትክክለኛ ውሳኔ ነበር….አሁንም ቢሆን ስራዬን በትክክል ለመሳራት ቅድሚያ ማድረግ ያለብኝ አንቺን ማሰናበት ነው…ደግሞ በመከርሺኝ መሰረት የአሰሪና ሰራተኛ ህጉን አንብቤዋለው..እናም በውል ስምምነታችን መሰረት አሁን እንደገባን የ30 ቀን ማስጠንቀቂያ እንዲደርስሽ አደርጋለው…ከዛ ደግሞ የወር እረፍት ትሞያለሽ…ከዛ ከፊቴ ገላል አደረግኩሽ ማለት ነው..ከዛ ጊዜሽ ሲያልቅ ደሞዝሽም ሆነ ሌሎች የሚገባሽን ጥቅማ ጥቅሞች ባለሽበት ይላክልሻል… አይዞሽ አትጨነቂ እኔ እንዳአንቺ አይደለውም የስራ ልምድሽ ላይ የማቃቸውን ስርዓት አልበኝነትሽን እና ታዛዤ አለመሆንሽን አልፅፍብሽም…››አለኝ…. አገኘውሽ የሚል የአሸናፊነት ኩራት ባለው ንግግር…
‹‹በነገራን ላይ የሥራ ልምድ ስትል በዚህች ሀገር ለአንድ ሰራተኛ የሚሠጥ የስራ ልምድ ማስረጃ ከሰውዬው ብቃት ጋር ሃማሳ ፐርሰንት እንኳን ተመሳሳይነት ካለው በጣም ጥሩ ነው….አንድ ሰው ስራ ለመቀጠር አምስት የስራ ልምዶች ይዞ ከመጣ በእርግጠኝነት ሶስቱ ፎርጂድ ይሆናል..የቀረው ደግሞ የሶሻሊስት ፓርቲ መፈክር ይመስል በብቃታቸው የተመሰከረላቸው…በችሎታቸው ወደርአልባ..በፀባያቸው ምስጉን የሚሉ ግነቶች የታጨቁበት በቃ ምን ልበልህ እንደውም በብዙ መስሪያ ቤቶች ደብዳው አንዴ ይፃፍል ሰራተኛው የስራ ልምድ ሲጠይቅ ስም እና የደሞዝ መጠን የሚገልፀው ቁጥር ብቻ እየተቀየረ ነው ፕሪንት በማድረግ የሚሰጠው…...እና ይሄ የስራ ልምድን ዓላማ ማርከስና ሀገርንም መግደል …ሰውዬው ገብቶ በለቀቀባቸው መስሪያ ቤቶች ሁሉ በተመሳሰሳይ ሁኔታ ስለጀግንነቱ ብቻ የሚያትት ልብ ወለዳዊ ምስክርነት የሚሠጠው ከሆነ ለምን ብሎ እራሱን ያሻሸላል……?እና ለማለት የፈለኩት አንተ ምርጥ ሀለቃ ስለሆንክ ያልከውን አታደርግም… ስለእኔ በትክክል የሆንኩትን እና ያልሆንኩትን..የምችለውንና የሚጎድለኝን በትክክል በመዘርዘር ነው የምትሸኘኝ…ጉድለቴን መፃፍህ እኮ የሚቀጥረኝ መስሪያ ቤት በመጀመሪያውኑ ስለእኔ እውነቱን አውቆት እንዲቀጥረኝና እና ጉድለቴንም እንዳሻሽል ስልጣና በማመቻቸት እንዲያግዘኝ ቅድሚያ መረጃ ይሰጠዋል፡፡
‹‹እሺ እንዳልሺን አደርጋለው…ስርዓት አልበኝነትሽን እና ወደ ላይ ያለአቅምሽ በመንጠራራት ሚስተካከልሽ እንደሌላ ቦልድ ተደርጎ እንዲፀፍልኝ አደርጋለው››አለኝ…. በዚህ ጊዜ ያዘዝነው ቡናና ማኪያቶ መጥቶልን ነበር….
‹‹አመሰግናው..ግን ከመባረሬ በፊት አንድ ነገር እንድታደርግልኘ እፈልጋለው››
‹‹ጠይቂኝ..››
‹‹ይሄንን ፈርምና ለመጨረሻ ጊዜ ዘና ብዬ ሁላችሁንም ተሰናብቼ ልልቀቅ..››ወረቀቱን አቀበልኩት…ገልጦ አየውና እስከዛሬ ካፈጠጠብኝ በላይ አፈጠጠብኝ…
‹‹ደግሞ ከአቶ ሰይፉ ሰርቄ ነው ያመጣሁት ..ለእሳቸወ ከነገርክብኝ አለቀልኝ››
‹‹ስንቴ ነው የሚያልቅልሽ……?ከእዚህ ካማፓኒ እህል ውሀሽ እኮ ተበጥሶል….ምንም የቀረሽ ነገር የለም››
‹‹ቢሆንም ..››
‹‹በይ ከሰረቅሽበት ቦታ መልሺ››ብሎ ወረቀቱን መልሶ አስታቀፈኝ
‹‹ይሄውልህ ..ይሄንን መፈረም ከማንም በላይ ላንተ ነው የሚጠቅምህ..››
‹‹እንዴት ብሎ ነው ሁለት ቀን ስራ መፍታት እና 3 መቶ ሺ ብር ማውጣት ሊጠቅመኝ የሚችለው……?››
‹‹አንደኛ ይሄ ለአስር አመት በካምፓኒው የቆየ ልምድ ነው፤ለዛውም ውጤታማ ልምድ፡፡ የካምፓኒውን የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ግባና ተመልከት …ምንጊዜም ከዚህ ዝግጅትና መዝናናት ቡኃላ ባሉ ሶስትና አራት ተከታታይ ወራቶች የእያንደንዱ ሰራተኛ የስራ አፈፃፀም ውጤት በሚገርም መጠን ነው የሚያድገው..የሄንን ያወጣሀውን 3 መቶ ሺ ብር በአንድ ወር ውስጥ እጥፍ ሆኖ ይመለሳልሀል፡፡ በአመታዊ ክብረ በዓሉ ካምፓኒው ከደሞዛቸው ውጭ በሆነ ብር የሆነ ነገር ስላደረጋቸው.የእኔነት ስሜት እንዲያድርባቸው ያደርጋል…፡፡፡ሁለተኛ ሰው በስራ በጣም ውጤታማ የሚሆነው በጣም ዘና ባለበት ጊዜ ነው…ለቀናትም ቢሆን ወደ ሆነ ሀገር ሄደው አየር መቀየራቸው ፤ ያላዩትን ነገር ማየታቸው መንፈሳቸው እንዲታደስ የስራ መነሳሳታቸው እዲጨምር እና ለህይወት ያላቸውም ጉጉት እንዲያንሰራራ ያደርጋል…፡፡ሌላው ያው ሰው ሆኖ መቼስ አንድ ላይ ሲሳራ በተለያየ ምክንያት የተጋጨ የተኮረፈ ይኖራል.. ልክ እደእኔና አንተ ማለት ነው..አንድ ላይ እየሰሩ ደግሞ ቅሬታ ውስጥ መግባት የስራ ጥራትንና ውጤትን በጣም እደሚቀንስ የታወቀ ነው፣እና እንዚህ አይነት ሰዎች ከስራ መንፈስ ውጭ ሆነው እንዲህ አይነት ቦታ ሲሄዱ መንፈሳቸው ከውጥረት የራቀና ዘና ለማለትም ዝግጁ ስለሚሆን ሁሉም ከገባበት ቅሬታ በቀላሉ ይወጣና እርስበርስ ይቅር ይባባላል፡፡ ሌላው በስራ ብቻ የሚተዋወቅ እና ግንኙነቱ በአየር ላይ የሆነ ሰው ግንኑነቱን በአንድ እስቴፕ ያሳድጋል…የተሸለ መግባባት እና አንዱ የአንደን ድክመት እና ጥንካሬ በተወሰነ መልኩ ለመረዳት እድል ያመቻችለታል… አንዳችን ያንዳችንን ፀባይ ፤ ድክመትና ጥንካሬ ማወቃችን እርስ በርስ ለመረዳዳት ተከባብረን እና ተደማምጠን ውጤታማ ለመሆን ያግዘናል...
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
❤️ፌናን
===
‹‹ምነው የስራ መልቀቂያ ልታስገቢ ነው እንዴ የመጣሽው……?››አለኝ
‹‹አይ አይደለም››
‹‹እና ታዲያ እኔ እንደሆነ አልጠራውሽም …ልጠራሽ የምችልበት ምክንያትም የለኝም .. መልክ መልካምነት ከልዩ ስነምግባር ጋር አሞልቶ የሰጣት ፀሀፊዬ መጥታ ገላግላኛለች….››አለኝ የአሹሙር ለዛ ባለው ንግግር
‹‹በጣም ደስ ይላል…እወነትህን ነው ትሁትና ምርጥ ልጅ ነች..በነገራችን ላይ ከባሏ ጋር አብረን ነው የተማርነው …እሱን ብታየው ደግሞ ዋው.. የሚያሰኝ ውበት ያለው አፍ አስከፋች ሸበላ ልጅ ነው፡፡››አልኩት
የተኮስኩት የነገር ጥይት በትክክል አዕምሮውን መቶታል …በግርምትም በንዴትም አይኖቹን በልጥጦ ‹‹ስለስራ እኮ ነው እያወራሁሽ ያለሁት..ፀሀፊዬ ጎበዝ ሰራተኛ ነች ተስማማታኛለች ነው ያልኩሽ..ስለባሏ ውበት በዚህ አይነት ግነት ለእኔ መንገሩ ለምን አስፈለገ……?››
‹‹አይ እንዲሁ ለጠቅላላ ዕውቀት ያህል ነው…በዛውም እኔም የእሷ አድናቂ መሆኔን እንድታውቅ ፈልጌ ነው››
‹‹የእሷ ወይስ የባሏ…?››መልሶ ተኮሰብኝ
‹‹የሁለቱም››
‹‹እሺ አሁን ለምን መጣሽ…?ስራ እየተዉ በየቢሮው መዞር የስነምግባር ብልሹነት መሆኑን አታውቂም? ››
‹‹አውቃልው ግን አመጣጤ ስታዛጋ ሰምቼ ነው …አስር ደቂቃ ካለህ እዚህ ፊት ለፊታችን ካለ ካፌ አሪፍ የጀበና ቡና ስላለ ልጋብዝህ ስለፈለኩ ነው››
‹‹ምን…?››አደነጋገጡ አብረን እንደር ያልኩት ነው ያስመሰለው…
‹‹ምነው..…?አስር ደቂቃ እኮ ነው›››
‹‹አይ ይቅርብኝ ቡና አልጠጣም…››
‹‹ማኪያቶ ግን ትጠጣለህ…››
….ምንም ሳይለኝ ከመቀመጫው ተነሳና ጃኬቱን ከማንጠልጠያ ላይ በማንሳት እየለበሰ በተቀመጥኩበት ጥሎኝ ቢሮውን ትቶ ወጣ…. ከኃላ ተከተልኩት…እርምጃዬን ከእሱ ማስተካከል አልቻልኩት…. ሊፍት ውስጥ ቀድሞ ገባ ተከትዬው ገባው…ልክ ከረሜላ ከአፉ የነጠቁት ህፃን ይመስል ለንቦጩን ጥሏል….በውስጤ የታፈነውን ሳቅ እንዳያመልጠኝ የተጨነቅኩትን ጭንቀት ልገልጽላችሁ አልችልም፡፡
ከህንፃው ወጥተን መንገዱን እንደያዝን እርምጃዬን ከእርምጃው አስተካከልኩ…ስጠመዘዝ ተጠመዘዘና ተከትሎኝ ካፌ ገባ…
‹‹ምን ይምጣልህ ……?››ወንበር ይዘን እንደተቀመጥን ጠየቅኩት
‹‹ምን አገባሽ›› አለና አስተናጋጇን ጠርቶ ማኪያቶ አዘዘ እኔ የጀበና ቡና አዘዝኩ
‹‹አሁን በትክክል ወስኜያለው››
‹‹ምኑን…? ›››አልኩት
እዚህ ካምፓኒ እግሬ እንደረገጠ አንቺን ለማባረር መወሰኔ ቀድሞውንም ትክክለኛ ውሳኔ ነበር….አሁንም ቢሆን ስራዬን በትክክል ለመሳራት ቅድሚያ ማድረግ ያለብኝ አንቺን ማሰናበት ነው…ደግሞ በመከርሺኝ መሰረት የአሰሪና ሰራተኛ ህጉን አንብቤዋለው..እናም በውል ስምምነታችን መሰረት አሁን እንደገባን የ30 ቀን ማስጠንቀቂያ እንዲደርስሽ አደርጋለው…ከዛ ደግሞ የወር እረፍት ትሞያለሽ…ከዛ ከፊቴ ገላል አደረግኩሽ ማለት ነው..ከዛ ጊዜሽ ሲያልቅ ደሞዝሽም ሆነ ሌሎች የሚገባሽን ጥቅማ ጥቅሞች ባለሽበት ይላክልሻል… አይዞሽ አትጨነቂ እኔ እንዳአንቺ አይደለውም የስራ ልምድሽ ላይ የማቃቸውን ስርዓት አልበኝነትሽን እና ታዛዤ አለመሆንሽን አልፅፍብሽም…››አለኝ…. አገኘውሽ የሚል የአሸናፊነት ኩራት ባለው ንግግር…
‹‹በነገራን ላይ የሥራ ልምድ ስትል በዚህች ሀገር ለአንድ ሰራተኛ የሚሠጥ የስራ ልምድ ማስረጃ ከሰውዬው ብቃት ጋር ሃማሳ ፐርሰንት እንኳን ተመሳሳይነት ካለው በጣም ጥሩ ነው….አንድ ሰው ስራ ለመቀጠር አምስት የስራ ልምዶች ይዞ ከመጣ በእርግጠኝነት ሶስቱ ፎርጂድ ይሆናል..የቀረው ደግሞ የሶሻሊስት ፓርቲ መፈክር ይመስል በብቃታቸው የተመሰከረላቸው…በችሎታቸው ወደርአልባ..በፀባያቸው ምስጉን የሚሉ ግነቶች የታጨቁበት በቃ ምን ልበልህ እንደውም በብዙ መስሪያ ቤቶች ደብዳው አንዴ ይፃፍል ሰራተኛው የስራ ልምድ ሲጠይቅ ስም እና የደሞዝ መጠን የሚገልፀው ቁጥር ብቻ እየተቀየረ ነው ፕሪንት በማድረግ የሚሰጠው…...እና ይሄ የስራ ልምድን ዓላማ ማርከስና ሀገርንም መግደል …ሰውዬው ገብቶ በለቀቀባቸው መስሪያ ቤቶች ሁሉ በተመሳሰሳይ ሁኔታ ስለጀግንነቱ ብቻ የሚያትት ልብ ወለዳዊ ምስክርነት የሚሠጠው ከሆነ ለምን ብሎ እራሱን ያሻሸላል……?እና ለማለት የፈለኩት አንተ ምርጥ ሀለቃ ስለሆንክ ያልከውን አታደርግም… ስለእኔ በትክክል የሆንኩትን እና ያልሆንኩትን..የምችለውንና የሚጎድለኝን በትክክል በመዘርዘር ነው የምትሸኘኝ…ጉድለቴን መፃፍህ እኮ የሚቀጥረኝ መስሪያ ቤት በመጀመሪያውኑ ስለእኔ እውነቱን አውቆት እንዲቀጥረኝና እና ጉድለቴንም እንዳሻሽል ስልጣና በማመቻቸት እንዲያግዘኝ ቅድሚያ መረጃ ይሰጠዋል፡፡
‹‹እሺ እንዳልሺን አደርጋለው…ስርዓት አልበኝነትሽን እና ወደ ላይ ያለአቅምሽ በመንጠራራት ሚስተካከልሽ እንደሌላ ቦልድ ተደርጎ እንዲፀፍልኝ አደርጋለው››አለኝ…. በዚህ ጊዜ ያዘዝነው ቡናና ማኪያቶ መጥቶልን ነበር….
‹‹አመሰግናው..ግን ከመባረሬ በፊት አንድ ነገር እንድታደርግልኘ እፈልጋለው››
‹‹ጠይቂኝ..››
‹‹ይሄንን ፈርምና ለመጨረሻ ጊዜ ዘና ብዬ ሁላችሁንም ተሰናብቼ ልልቀቅ..››ወረቀቱን አቀበልኩት…ገልጦ አየውና እስከዛሬ ካፈጠጠብኝ በላይ አፈጠጠብኝ…
‹‹ደግሞ ከአቶ ሰይፉ ሰርቄ ነው ያመጣሁት ..ለእሳቸወ ከነገርክብኝ አለቀልኝ››
‹‹ስንቴ ነው የሚያልቅልሽ……?ከእዚህ ካማፓኒ እህል ውሀሽ እኮ ተበጥሶል….ምንም የቀረሽ ነገር የለም››
‹‹ቢሆንም ..››
‹‹በይ ከሰረቅሽበት ቦታ መልሺ››ብሎ ወረቀቱን መልሶ አስታቀፈኝ
‹‹ይሄውልህ ..ይሄንን መፈረም ከማንም በላይ ላንተ ነው የሚጠቅምህ..››
‹‹እንዴት ብሎ ነው ሁለት ቀን ስራ መፍታት እና 3 መቶ ሺ ብር ማውጣት ሊጠቅመኝ የሚችለው……?››
‹‹አንደኛ ይሄ ለአስር አመት በካምፓኒው የቆየ ልምድ ነው፤ለዛውም ውጤታማ ልምድ፡፡ የካምፓኒውን የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ግባና ተመልከት …ምንጊዜም ከዚህ ዝግጅትና መዝናናት ቡኃላ ባሉ ሶስትና አራት ተከታታይ ወራቶች የእያንደንዱ ሰራተኛ የስራ አፈፃፀም ውጤት በሚገርም መጠን ነው የሚያድገው..የሄንን ያወጣሀውን 3 መቶ ሺ ብር በአንድ ወር ውስጥ እጥፍ ሆኖ ይመለሳልሀል፡፡ በአመታዊ ክብረ በዓሉ ካምፓኒው ከደሞዛቸው ውጭ በሆነ ብር የሆነ ነገር ስላደረጋቸው.የእኔነት ስሜት እንዲያድርባቸው ያደርጋል…፡፡፡ሁለተኛ ሰው በስራ በጣም ውጤታማ የሚሆነው በጣም ዘና ባለበት ጊዜ ነው…ለቀናትም ቢሆን ወደ ሆነ ሀገር ሄደው አየር መቀየራቸው ፤ ያላዩትን ነገር ማየታቸው መንፈሳቸው እንዲታደስ የስራ መነሳሳታቸው እዲጨምር እና ለህይወት ያላቸውም ጉጉት እንዲያንሰራራ ያደርጋል…፡፡ሌላው ያው ሰው ሆኖ መቼስ አንድ ላይ ሲሳራ በተለያየ ምክንያት የተጋጨ የተኮረፈ ይኖራል.. ልክ እደእኔና አንተ ማለት ነው..አንድ ላይ እየሰሩ ደግሞ ቅሬታ ውስጥ መግባት የስራ ጥራትንና ውጤትን በጣም እደሚቀንስ የታወቀ ነው፣እና እንዚህ አይነት ሰዎች ከስራ መንፈስ ውጭ ሆነው እንዲህ አይነት ቦታ ሲሄዱ መንፈሳቸው ከውጥረት የራቀና ዘና ለማለትም ዝግጁ ስለሚሆን ሁሉም ከገባበት ቅሬታ በቀላሉ ይወጣና እርስበርስ ይቅር ይባባላል፡፡ ሌላው በስራ ብቻ የሚተዋወቅ እና ግንኙነቱ በአየር ላይ የሆነ ሰው ግንኑነቱን በአንድ እስቴፕ ያሳድጋል…የተሸለ መግባባት እና አንዱ የአንደን ድክመት እና ጥንካሬ በተወሰነ መልኩ ለመረዳት እድል ያመቻችለታል… አንዳችን ያንዳችንን ፀባይ ፤ ድክመትና ጥንካሬ ማወቃችን እርስ በርስ ለመረዳዳት ተከባብረን እና ተደማምጠን ውጤታማ ለመሆን ያግዘናል...
👍7
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
...ቀኑ እሁድ እንደመሆኑ ከእንቅልፌ የተነሳውት አረፋፍጄ ነው….አባቴ ክንዱን ከአንገቴ ዙሪያ እንዴት አድርጎ አውጥቶ፤ከደረቱ ላይ እንዴት አንሸራቶ ከስሬ እንደተነሳ አለውቅም…ከሰራተኞቻችን አንዷ ነች የቀሰቀሰቺኝ፡
‹‹ምነው ትንሽ ልተኛ››ተነጫነጭኩባት
‹‹ጋሼ ለቁርስ እየጠበቁሽ ነው..ቀስቅሺያት ብለውኝ ነው…ካለበለዚያ ጥዬሽ መውጣቴ ነው ብለውሻል››
‹‹እንዳታደርገው… መጣው ጠብቀኝ በይው…››አልኩና ተስፈንጥሬ አልጋዬን ለቅቄ ወረድኩ…..የለበስኩትን ቢጃማ እያወለቅኩና ወለል ላይ እየጣልኩ ወደሻወር ቤት ገባው.፡፡ ሰውነቴን ታጥቤ ለእርፍት ቀን የሚሆን ቀለል ያለ ልብስ ለብሼ ቁርስ ቦታ ለመድረስ ከ15 ደቂቃ በላይ ፈጀቶብኛል…አባቴ ፊት ለፊት በረንዳ ላይ ተቀምጦ መጽሀፍ እያነበበ ነበር…..
ከሶስት ቀን በፊት እንደተለየኝ በሚያስመስል ጥልቅ ስሜት ጉንጬን ሙጭሙጭ አድርጌ ሳምኩትና ከጎኑ ካለው ባዶ ወንበር ላይ ተቀመጥኩ….
‹‹በለሊት ምነው ተነሳህ…?››
‹‹በለሊት እንደምነሳ ሁሌ ታውቂያለሽ…እኔ እያየዋት ያልወጣችን ፀሀይ ቀኑን ሙሉ ምቾት ስትነሳኝ ነው የምትውለው…እንኳን በሰላም ወጣሽ ብዬ በደስታ መቀበል እና ማታ ደግሞ በሰላም ወደማደሪያሽ ግቢ ብዬ መሸኘት ለመኖር ያለኝ ጉጉቴን ይጨምርልኛል..ፀሀይ ለእኔ ያንቺ ተምሳሌት ነች፤እኩል ነው የምወዳችሁ……››
‹‹እንዴ አባ..እኔን ከፀሀይ እኩል ብቻ…እኔ እኮ ከራስህ እኩል የምትወደኝ ይመስለኝ ነበር….…?››
‹‹ለማለት የፈለኩት በትክክል ገብቶሻል…አንቺን ከእኔ እኩል መውደድ አንቺን ማሳነስ ነው…አንቺ ማለት በጣም የተስተካከለው እኔ ማለት ነሽ..አንቺ የእኔ በጣም ጥሩ ጎን ከእናትሽ ጥሩ ጎን ጋር አንድ ላይ ተቀይጦ ሲዋሀድ ማለት ነሽ…..የሁለታችንም ስህተት ሲታረም ንጥር ያለ ንጽህ እውነት ይወጣዋል… ያ እውነት ማለት ደግሞ አንቺ ነሽ…እና አንቺን ከእኔ እኩል ሳይሆን ከእኔ በላይ ነው የምወድሽ….››
ሳይቸግረኝ ቆስቁሼው በጥዋት በጣፍጭና አቅላጭ ንግግሩ እንባዬን አስመጣው…‹‹የእኔ ልዩ አባት››ብዬ ተንጠራርቼ ሳምኩት
ቁርሱ ቀረበልን እና በ10 ደቂቃ ውስጥ እያወራን በልተን ጨረስን……
‹‹አሁን መሄድ እንችላለን…?፡፡››አለኝ
‹‹አዎ ….››ብዬ ከመቀመጫዬ ተነሳውና ወደገራዥ በመሄድ የአባዬን መኪና በማውጣት እሱን ከጎኔ አስቀምጬ ከግቢው ወጣን…እኔና አባቴ እሁድን ተአምር የሚመስል አጋጣሚ ካልተፈጠረ እና አንዳችን የግድ ለብቻችን የምንሄድበት ቦታ ካልገጠመን በስተቀር አንለያይም…ለምሳሌ የእሱ ጓደኛ ጋር ለቅሶ ቢኖርና መሄድ የግድ ቢሆንበት አወቅኳቸውም አላወቅኳቸውም አብረን ነው የምንሄደው…ሰርግ እና ድግስ ተውት ከነባለቤቱ በሚለው ቦታ ባለቤቱን ወክዬ ሁሌ የምሄደው እኔ ነኝ
ከአራት ሰዓት እስከ ስምንት ሰዓት ያለው ፕሮግራማችን ከሞላ ጎደል ሁሌ ተመሳሳይ ነው….በመጀመሪያ ሆስፒታል ነው የምንሄደው…ሆስፒታሉ እንደየሁኔታው ሊለያይ ይችልላ…ግን የትኛውም ሆስፒታል ይሁን ብቻ አንዱ ጋር እንሄዳለን…..ከዛ በተቻለን መጠን የታመሙትን በየክፍሉ እየገባን መጠየቅ እንጀምራለን..ከዛ ቡኃላ በጥየቃችን ወቅት ምንም አስታማሚ የሌላቸውን አዛውንት..ወይም እናቷን የምታስታምም የዘጠኝ ዓመት ልጅ…መድሀኒት መግዣ ብር ያጣ ስንት ወንዘ አቋርጦ ከክፍለሀገር የመጣ ገበሬ …ብቻ ብዙ ብዙ ታሪክ ያላቸው ሰዎች ያጋጥሙናል….ከዛ አባቴ ይዞ የመጣውን ብር እንደየ ችግራቸው ከባድነትና እንደሚያስፈልጋቸው የብር መጠን ያከፋፍላቸዋል…
አንዳንዴ በሁኔታው ስደመም‹‹አባ ልዩ ሰው እኮ ነህ…ሰው ጤናውን ለማስመለስ በሚያደርገው ጥረት ገንዘብ ሲቸግረው…. ህክምናውን አግኝቶ መድሀኒት መግዣ ሲያጣ የሚሰማው ሀዘንና መሸማቀቅ .. በዛ ሰዓት ደግሞ አንተ ደርሰህ አይዞችሁ ስትላቸው የሚሰማቸው ደስታና እፎይታ …››ብዬ ላደንቀውም ላመሰግነውም ሞክራለው….
‹‹እኔ እኮ ምንም አላደረኩላቸውም..ደላላ በይኝ››ይለኛል
‹‹አልገባኝም››
‹‹ደላላ ማለት የሆነ ገዢን ከሻጭ አገናኝቶ ኮሚሽን የሚቀበል እና ባገኘው ኮሚሽን ደስተኛ የሚሆን ሰው አይደል…?እኔም ችግር ላይ ባሉ ሰዎች እና በእናትሽ መካከል አገናኝ ድልድይ በይኝ..ዋናዋ ተመስጋኝ ባለብሯ እናትሽ ነች፡፡ እኔ ከእሷ ብሩን እቀበላለው መጥቼ ልቤ በፈቀደው መንገድ እየመደብኩ አከፋፍላለው… የድለላዬን ዋጋ ሰዎቹ የማይገባኝን አይነት ሙገሳና ፤ መንግሰተ ሰማያት መሬት ለመግዛት የሚያስችለኝን አይነት ምርቃት ያሸክሙኛል..››ይለኛል
‹‹አይ አባ..እናቴ እኮ ብሩን ለሰዎቹ ብላ ሳይሆን አንተን ለማስደሰት ስትል ነው የምትሰጥህ…ለምሳሌ ይሄንን ብር ከጓደኞችህ ጋር ውስኪ ለመራጨት ብትጠቀምበትም እሷ ደንታዋ አይደለም…አረ ውሽማ ኖሮህ ለእሷም ብትሰጣት እንኳን ምንም የሚመስላት አይመስለኝም ….ደግሞ ማላውቅ እንዳይመስልህ››
‹‹ምኑን…? ››
‹‹ይሄንን ባህሪህን ከእናቴም ከመገናኘትህ በፊት ፤ ምንም ብር ባልነበረህም ጊዜ በዝርዝር ሳንቲሞች ደረቅ ዳቦ እየገዛህ በሽተኞችን እንደምትጠይቅ አዎቃለው..››
‹‹እሱስ ትክክል ነሽ›› ብሎ ትክዝ ይላል፡፡››
===
አባቴ ዝም ብሎ አይደለም የዚህ ባህሪ ባለቤት የሆነው…ታሪኩን እሱ ለእናቴ ነግሯት እሷ ደግሞ ለእኔ ነግራኛላች… እኔ ደግሞ አሁን አጠር አድርጌ ለእናንተ ልንገራችሁ…
አባቴ የአጄ ልጅ ነው፡፡አጄ በሻሸመኔ እና በአላባ መካከል የምትገኝ መለስተኛ ከተማ ነች ፡፡ለእናትና አባቱ አንድ ብቸኛ ልጅ ነበር.፡፡አባትዬው ህፃን ሳለ ነበር የሞቱት፡፡እናትዬው ግን አባት አልባ መሆኑን እንዳይሰማው ፊታቸው በማድያት እስኪሸፈን፤ ወገባቸው ያለእድሜያቸው እስኪጎብጥ እንደወንድ እያረሱ..እንደሴት እየፈተሉ ፤እንደገበሬ እያመረቱ ፤እደ ነጋዴ እየቸረቸሩ ምንም ሳይጎድልበት እስተማሩት ..እሱም ልፋታቸውን መሬት እንዲበተን አላደረገም… ጥሩ ውጤት አምጥቶ ዩኒቨርሲቲ ገባ፡፡ሁሉም ነገር መልካም ሆኖ ከቀጠለ ቡኃላ የመጨረሻ የመመረቂያው አመት ላይ ያልተጠበቀ ጨለማ ነገር ተፈጠረ….
ለእናቴ ደረስኩላት ብሎ ፈንጠዝያ ላይ ባለበት ጊዜ…..የአለምን ሁሉ ጥሩ ነገር በሚገባት መጠን ለአናቴ አደርግላታለው ብሎ በጉጉት በሚናጥበት ጊዜ ፡፤ እናቴን ስንድ እመቤት አድርጌ በምቾትና በድሎት እንድትኖር አደርጋታለው ብሎ ዝግጅት ላይ ባለበት ጊዜ በአስቸኳይ ድረስ ተብሎ ከዩኒቨርሲቲ ተጠራ…ሲደርስ እናቱ በሞትና በህይወት መካከል ስታጣጥር ነበር የደረሰው….ከዛ ያደረገው የአካባቢው ሰዎች ባዋጡት እና እናትዬውም እጅ ላይ በነበረች ጥቂት ገንዘብ ለተሻለ ህክምን ወደሻሸመኔ ሆስፒታል ይዞቸው መሄድ ነበር…በምርመራው የበሽታቸው አይነት ተለይቶ መድሀኒት ይታዘዝላቸዋል …ሶስት መድሀኒት 950 ብር…ያ ብር ከየት ይምጣ..…?አቅም ያላቸው የአባቱም ሆኑ የእናቱ ዘመዶች ጋር እየደወለም እራሱም በአካል እየሄደ እደጅ ቢጠና ከአስርና ከሃያ ብር በላይ ሊሰጠው የሚችል አዛኝ ልብ ያለው ሰው ማግኘት አልቻለም..ከዛ የመጨረሻ አማራጭ በሽተኛ እናቱን አስፓልት ዳር አስተኝቶ እናቴን አድኑልኝ እያለ ምድሀኒት መግዣ መለመን ነበር…ግን የተፈላገው ዘጠኝ መቶ ሃምሳ ብር ከማግኘቱ በፊት እዛው አስፓልት ላይ እናቱ ትሞትበታላች…ያ አባቴ ሙሉ በሙሉ የተቀየረበት ወቅት ነበር..ለገንዘብም ለህይወትም የነበረው ምልከታ ከስር መሰረቱ የተደረማመሰበት …ያ ወቅት አባቴ ዘመድ አልባ ብቸኛ ሰው እንደሆነ የተቀበለበት ጊዜ ነበር…
ትምህርቱን አጠናቆ ወደሀገሩ አልተመለሰም ….ዝም ብሎ ወደማያውቀው አዲስ አበባ ዲግሪውን
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
...ቀኑ እሁድ እንደመሆኑ ከእንቅልፌ የተነሳውት አረፋፍጄ ነው….አባቴ ክንዱን ከአንገቴ ዙሪያ እንዴት አድርጎ አውጥቶ፤ከደረቱ ላይ እንዴት አንሸራቶ ከስሬ እንደተነሳ አለውቅም…ከሰራተኞቻችን አንዷ ነች የቀሰቀሰቺኝ፡
‹‹ምነው ትንሽ ልተኛ››ተነጫነጭኩባት
‹‹ጋሼ ለቁርስ እየጠበቁሽ ነው..ቀስቅሺያት ብለውኝ ነው…ካለበለዚያ ጥዬሽ መውጣቴ ነው ብለውሻል››
‹‹እንዳታደርገው… መጣው ጠብቀኝ በይው…››አልኩና ተስፈንጥሬ አልጋዬን ለቅቄ ወረድኩ…..የለበስኩትን ቢጃማ እያወለቅኩና ወለል ላይ እየጣልኩ ወደሻወር ቤት ገባው.፡፡ ሰውነቴን ታጥቤ ለእርፍት ቀን የሚሆን ቀለል ያለ ልብስ ለብሼ ቁርስ ቦታ ለመድረስ ከ15 ደቂቃ በላይ ፈጀቶብኛል…አባቴ ፊት ለፊት በረንዳ ላይ ተቀምጦ መጽሀፍ እያነበበ ነበር…..
ከሶስት ቀን በፊት እንደተለየኝ በሚያስመስል ጥልቅ ስሜት ጉንጬን ሙጭሙጭ አድርጌ ሳምኩትና ከጎኑ ካለው ባዶ ወንበር ላይ ተቀመጥኩ….
‹‹በለሊት ምነው ተነሳህ…?››
‹‹በለሊት እንደምነሳ ሁሌ ታውቂያለሽ…እኔ እያየዋት ያልወጣችን ፀሀይ ቀኑን ሙሉ ምቾት ስትነሳኝ ነው የምትውለው…እንኳን በሰላም ወጣሽ ብዬ በደስታ መቀበል እና ማታ ደግሞ በሰላም ወደማደሪያሽ ግቢ ብዬ መሸኘት ለመኖር ያለኝ ጉጉቴን ይጨምርልኛል..ፀሀይ ለእኔ ያንቺ ተምሳሌት ነች፤እኩል ነው የምወዳችሁ……››
‹‹እንዴ አባ..እኔን ከፀሀይ እኩል ብቻ…እኔ እኮ ከራስህ እኩል የምትወደኝ ይመስለኝ ነበር….…?››
‹‹ለማለት የፈለኩት በትክክል ገብቶሻል…አንቺን ከእኔ እኩል መውደድ አንቺን ማሳነስ ነው…አንቺ ማለት በጣም የተስተካከለው እኔ ማለት ነሽ..አንቺ የእኔ በጣም ጥሩ ጎን ከእናትሽ ጥሩ ጎን ጋር አንድ ላይ ተቀይጦ ሲዋሀድ ማለት ነሽ…..የሁለታችንም ስህተት ሲታረም ንጥር ያለ ንጽህ እውነት ይወጣዋል… ያ እውነት ማለት ደግሞ አንቺ ነሽ…እና አንቺን ከእኔ እኩል ሳይሆን ከእኔ በላይ ነው የምወድሽ….››
ሳይቸግረኝ ቆስቁሼው በጥዋት በጣፍጭና አቅላጭ ንግግሩ እንባዬን አስመጣው…‹‹የእኔ ልዩ አባት››ብዬ ተንጠራርቼ ሳምኩት
ቁርሱ ቀረበልን እና በ10 ደቂቃ ውስጥ እያወራን በልተን ጨረስን……
‹‹አሁን መሄድ እንችላለን…?፡፡››አለኝ
‹‹አዎ ….››ብዬ ከመቀመጫዬ ተነሳውና ወደገራዥ በመሄድ የአባዬን መኪና በማውጣት እሱን ከጎኔ አስቀምጬ ከግቢው ወጣን…እኔና አባቴ እሁድን ተአምር የሚመስል አጋጣሚ ካልተፈጠረ እና አንዳችን የግድ ለብቻችን የምንሄድበት ቦታ ካልገጠመን በስተቀር አንለያይም…ለምሳሌ የእሱ ጓደኛ ጋር ለቅሶ ቢኖርና መሄድ የግድ ቢሆንበት አወቅኳቸውም አላወቅኳቸውም አብረን ነው የምንሄደው…ሰርግ እና ድግስ ተውት ከነባለቤቱ በሚለው ቦታ ባለቤቱን ወክዬ ሁሌ የምሄደው እኔ ነኝ
ከአራት ሰዓት እስከ ስምንት ሰዓት ያለው ፕሮግራማችን ከሞላ ጎደል ሁሌ ተመሳሳይ ነው….በመጀመሪያ ሆስፒታል ነው የምንሄደው…ሆስፒታሉ እንደየሁኔታው ሊለያይ ይችልላ…ግን የትኛውም ሆስፒታል ይሁን ብቻ አንዱ ጋር እንሄዳለን…..ከዛ በተቻለን መጠን የታመሙትን በየክፍሉ እየገባን መጠየቅ እንጀምራለን..ከዛ ቡኃላ በጥየቃችን ወቅት ምንም አስታማሚ የሌላቸውን አዛውንት..ወይም እናቷን የምታስታምም የዘጠኝ ዓመት ልጅ…መድሀኒት መግዣ ብር ያጣ ስንት ወንዘ አቋርጦ ከክፍለሀገር የመጣ ገበሬ …ብቻ ብዙ ብዙ ታሪክ ያላቸው ሰዎች ያጋጥሙናል….ከዛ አባቴ ይዞ የመጣውን ብር እንደየ ችግራቸው ከባድነትና እንደሚያስፈልጋቸው የብር መጠን ያከፋፍላቸዋል…
አንዳንዴ በሁኔታው ስደመም‹‹አባ ልዩ ሰው እኮ ነህ…ሰው ጤናውን ለማስመለስ በሚያደርገው ጥረት ገንዘብ ሲቸግረው…. ህክምናውን አግኝቶ መድሀኒት መግዣ ሲያጣ የሚሰማው ሀዘንና መሸማቀቅ .. በዛ ሰዓት ደግሞ አንተ ደርሰህ አይዞችሁ ስትላቸው የሚሰማቸው ደስታና እፎይታ …››ብዬ ላደንቀውም ላመሰግነውም ሞክራለው….
‹‹እኔ እኮ ምንም አላደረኩላቸውም..ደላላ በይኝ››ይለኛል
‹‹አልገባኝም››
‹‹ደላላ ማለት የሆነ ገዢን ከሻጭ አገናኝቶ ኮሚሽን የሚቀበል እና ባገኘው ኮሚሽን ደስተኛ የሚሆን ሰው አይደል…?እኔም ችግር ላይ ባሉ ሰዎች እና በእናትሽ መካከል አገናኝ ድልድይ በይኝ..ዋናዋ ተመስጋኝ ባለብሯ እናትሽ ነች፡፡ እኔ ከእሷ ብሩን እቀበላለው መጥቼ ልቤ በፈቀደው መንገድ እየመደብኩ አከፋፍላለው… የድለላዬን ዋጋ ሰዎቹ የማይገባኝን አይነት ሙገሳና ፤ መንግሰተ ሰማያት መሬት ለመግዛት የሚያስችለኝን አይነት ምርቃት ያሸክሙኛል..››ይለኛል
‹‹አይ አባ..እናቴ እኮ ብሩን ለሰዎቹ ብላ ሳይሆን አንተን ለማስደሰት ስትል ነው የምትሰጥህ…ለምሳሌ ይሄንን ብር ከጓደኞችህ ጋር ውስኪ ለመራጨት ብትጠቀምበትም እሷ ደንታዋ አይደለም…አረ ውሽማ ኖሮህ ለእሷም ብትሰጣት እንኳን ምንም የሚመስላት አይመስለኝም ….ደግሞ ማላውቅ እንዳይመስልህ››
‹‹ምኑን…? ››
‹‹ይሄንን ባህሪህን ከእናቴም ከመገናኘትህ በፊት ፤ ምንም ብር ባልነበረህም ጊዜ በዝርዝር ሳንቲሞች ደረቅ ዳቦ እየገዛህ በሽተኞችን እንደምትጠይቅ አዎቃለው..››
‹‹እሱስ ትክክል ነሽ›› ብሎ ትክዝ ይላል፡፡››
===
አባቴ ዝም ብሎ አይደለም የዚህ ባህሪ ባለቤት የሆነው…ታሪኩን እሱ ለእናቴ ነግሯት እሷ ደግሞ ለእኔ ነግራኛላች… እኔ ደግሞ አሁን አጠር አድርጌ ለእናንተ ልንገራችሁ…
አባቴ የአጄ ልጅ ነው፡፡አጄ በሻሸመኔ እና በአላባ መካከል የምትገኝ መለስተኛ ከተማ ነች ፡፡ለእናትና አባቱ አንድ ብቸኛ ልጅ ነበር.፡፡አባትዬው ህፃን ሳለ ነበር የሞቱት፡፡እናትዬው ግን አባት አልባ መሆኑን እንዳይሰማው ፊታቸው በማድያት እስኪሸፈን፤ ወገባቸው ያለእድሜያቸው እስኪጎብጥ እንደወንድ እያረሱ..እንደሴት እየፈተሉ ፤እንደገበሬ እያመረቱ ፤እደ ነጋዴ እየቸረቸሩ ምንም ሳይጎድልበት እስተማሩት ..እሱም ልፋታቸውን መሬት እንዲበተን አላደረገም… ጥሩ ውጤት አምጥቶ ዩኒቨርሲቲ ገባ፡፡ሁሉም ነገር መልካም ሆኖ ከቀጠለ ቡኃላ የመጨረሻ የመመረቂያው አመት ላይ ያልተጠበቀ ጨለማ ነገር ተፈጠረ….
ለእናቴ ደረስኩላት ብሎ ፈንጠዝያ ላይ ባለበት ጊዜ…..የአለምን ሁሉ ጥሩ ነገር በሚገባት መጠን ለአናቴ አደርግላታለው ብሎ በጉጉት በሚናጥበት ጊዜ ፡፤ እናቴን ስንድ እመቤት አድርጌ በምቾትና በድሎት እንድትኖር አደርጋታለው ብሎ ዝግጅት ላይ ባለበት ጊዜ በአስቸኳይ ድረስ ተብሎ ከዩኒቨርሲቲ ተጠራ…ሲደርስ እናቱ በሞትና በህይወት መካከል ስታጣጥር ነበር የደረሰው….ከዛ ያደረገው የአካባቢው ሰዎች ባዋጡት እና እናትዬውም እጅ ላይ በነበረች ጥቂት ገንዘብ ለተሻለ ህክምን ወደሻሸመኔ ሆስፒታል ይዞቸው መሄድ ነበር…በምርመራው የበሽታቸው አይነት ተለይቶ መድሀኒት ይታዘዝላቸዋል …ሶስት መድሀኒት 950 ብር…ያ ብር ከየት ይምጣ..…?አቅም ያላቸው የአባቱም ሆኑ የእናቱ ዘመዶች ጋር እየደወለም እራሱም በአካል እየሄደ እደጅ ቢጠና ከአስርና ከሃያ ብር በላይ ሊሰጠው የሚችል አዛኝ ልብ ያለው ሰው ማግኘት አልቻለም..ከዛ የመጨረሻ አማራጭ በሽተኛ እናቱን አስፓልት ዳር አስተኝቶ እናቴን አድኑልኝ እያለ ምድሀኒት መግዣ መለመን ነበር…ግን የተፈላገው ዘጠኝ መቶ ሃምሳ ብር ከማግኘቱ በፊት እዛው አስፓልት ላይ እናቱ ትሞትበታላች…ያ አባቴ ሙሉ በሙሉ የተቀየረበት ወቅት ነበር..ለገንዘብም ለህይወትም የነበረው ምልከታ ከስር መሰረቱ የተደረማመሰበት …ያ ወቅት አባቴ ዘመድ አልባ ብቸኛ ሰው እንደሆነ የተቀበለበት ጊዜ ነበር…
ትምህርቱን አጠናቆ ወደሀገሩ አልተመለሰም ….ዝም ብሎ ወደማያውቀው አዲስ አበባ ዲግሪውን
👍1
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_አስር
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
...‹‹ዛሬ የት እንሂድ…?›› አልኩት አባቴን ስምንት ሰዓት ከሩብ አካባቢ….
መኪና ውስጥ ገብተን እኔ እየነዳው ነው እያወራን ያለነው….
‹‹እኔ ምንም በውስጤ የለም…አረጀው መሰለኝ የመዝናኛ አይነቶች እየጠፉብኝ ነው፡፡››
‹‹የእኔ አባትማ እንዲህ በቀላሉ አያረጅም …ገና እኔና እናቴ ድል አድርገን ደግሰን ልጃገረድ ነው የምንድርህ››
‹‹አይ እብድ የሆንሽ ልጅ…በሚስት ላይ ሚስት ወንጀል እንደሆነ አታውቂም…››
‹‹አይ እናቴንማ ሚስቴ ብለህ መጥራቱን አቁም …አሁን መጨረሻ ውሳኔ ላይ ደርሼያለው…››
‹‹ምን አይነት ውሳኔ…?››
‹‹አሁን የጤናዋ ጉዳይ መስመር እስኪይዝ ነው እንጂ ወይ እንደገና ታግባህ ወይ ደግሞ በፍቃዷ ትልቀቅህና ልዳርህ››
ፈገግ አለና‹‹…አሁን ይሄን ምን አሳሰበሽ…?›
‹‹ለምን አላስብም አባ……? ደግሞ አሁን አይደለም …ሁሌ እኮ ነው ሚያንገበግበኝ…በዚህ ጉዳይ ላይ የሆነ ነገር ብትለኝ ደስ ይለኛል….››
‹‹ምን እንድልሽ ነው የምትፈልጊው……?››
‹‹እኔ እንጃ…እናቴን ለምን አልተውካትም……?መቼስ ለብሯ ስትል አብረሀት እንዳልቆየህ አውቃለሁ…አንተ በቁስ ፍቅር ልትሸነፍ ምትችል ሰው አይደለህም …››
‹‹ለምን ጥያቄውን ገልብጠሸ አልጠየቅሺኝም…?››
‹‹እንዴት ብዬ……?››
‹‹ለምን እናቴ አንተን ጥላህ አልሄደችም..…?ለምን እንደዛ ማድረግ ተሳናት……? ሀብታም ነች፤ቆንጆ ነች፤የተማረች እና ብልህ ነች ከንተ ጋር ለምን ኑሮዋን መቀጠል ፈለገች……?ለምን ከቤቷ አንተን አስወጥታ ሌላ የሚመጥናትን ባል አላገባችም ብለሽ አልጠየቅሺም….…?ለምን….…?››
‹‹ሚመጥናትን!! …?ጭራሽ አንተ ለእሷ መመጠን አቅቶህ…? አረ አታስቀኝ ....አንተ እኮ ሁሌ ባል ለመሆን ዝግጁ ነህ…አንተ እንከን አልባ ሰው ነህ…እሷ ነች ሀብት አሳዳጇ..እሷ ነች ቤቱን እርግፍ አድርጋ የአደባባይ ሴት የሆነችው…እሷ ነች…››
‹‹በይ ይብቃሽ ልጄ…ሁል ግዜ ስለምንወዳቸው ሰዎች ያለን ምልከታ ስለእነሱ እወነቱን እንዳናይ እያየንም እንኳን አምነን እንዳንቀበል ጥቁር መጋረጃ ይሆንብናል…ላንቺ አባትሽ ምንም ጉድፍ የለበትም…ያንቺን አባት የሚመስል ሰው በዚህ ምድር ላይ አልተፈጠረም…የዚህ ዓለም ቆነጃጅቶች ሁሉ አባትሽን ለማግኘት ቢደባደብና ቢቦጫጨቁ ተገቢ ነው…..አይደል..…?እንደዛ አይደል የምታስቢው..…?››
‹‹ምነው ባስብ ታዲያ ተሳሳትኩ……?.››
‹‹አዎ ተሳስተሸል..፡፡ባልና ሚስት በሆነ ነገር አልተስማሙም ማለት ጎጆቸውን ማፍረስ አለባቸው ማለት አይደለም…ደግሞ ልጄ አንድ ነገር ልነግርሽ እፈልጋለው.. ትዳርና ሀገር ውስብስብ ናቸው፡፡ትዳር ይዘሽ ልጆች ወልደሽ እና ንብረት አፍርተሸ ረጅም አመት ኖርሽ ማለት ሁሉ ነገር ገነታዊ ነው ማለት አይደለም…የሆነ ነገር ለማግኘት ሁሌ መክፈል ያለብሽ የሆነ መስዋዕትነት አለ…ባልሽ በምንም አይነት ሁኔታ መቶ ፐርሰንት አንቺ ወደምትወጂው ወይም አንቺ ወደምትጓዢበት የህይወት መንገድ ሊጓዝ አይችልም…እንደዛ እንዲያደርግ አደረግሽ ማለት ማነቱን አጠፋሺው ማለት ነው…ማንም ሰው ደግሞ የራሱን ማንነት እስከወዲያኛው ማጣት ስለማይፈልግ የሆነ ቀን ማንነቱን ለማስመለስ መንፈራገጡ አይቀርም ..ያ ደግሞ እቤት ወደመሰነጣጠቅ እና ወደማፍረሰ ያመራል…፡፡
አየሽ ባልና ሚስት ቃልኪዳናቸውን አክብረው እስከወዲያኛው ለመኖር አንድ ነገር ላይ ብቻ ነው እኩል መስማማት ሚገባቸው ‹‹ጎጆችን የጋራችን ነው… የጓጇችንን ህልውና ሁለታችንም እኩል እንፈልገዋለን… ለዛም ስንል ሁል ጊዜ በጋራ ሆነ በየግላችን የተቻለንን እንጥራለን..…››ይሄ ነው ወሳኙ ጉዳይ… ቃላቸውን ለማክበር ሲሉ ይከባበራሉ..ይሄንን ቃል ለማክበር ሲሉ ይደማመጣሉ፣ይሄንን እውን ለማድረግ ሲሉ ሁሌ ሳይሰለቻቸው ይቅር ይባባላሉ….ለጎጇቸው ህልውና ሲሉ ሰጥቶ በመቀበል ፤ተሸንፎም ጭምር በማሸነፍ እኩል ይጥራሉ….
እና ትዳር ቀላል ነገር አይደለም…ባልና ሚስት ተባብሎ እጅ ለእጅ በመያያዝ በየድግስ ቤቱ ከመሄድ በላይ ነው፣ባልና ሚስት መሆን አንድ መሶብ ከመብላት እና አንድ አልጋ ከመጋራትም በላይ ነው…
ይሄን ጌዜ ከተማውን ለቀን ቃሊቲ ኬላ ጋር ደርሰናል..…እየነዳው ያለውት ወደ ዱከም ነው..አባቴ ጥሬ ስጋ ይወዳል..ዱከም ደግሞ በጥሬ ስጋ የምታውቁት ነው…አባቴ ንግግሩን ቀጥሏል፡፡
ትዳር የሚባለው ተቋም ሀገር ከሚባለው የጋራ ቤት ጋር ይመሳሰላል…አንድ ሀገር ውስጥም በጋራ ለመኖር ሀገሬን እወዳለው ብቻ ማለት በቂ አይደለም..ለሀገሬ ስል ሌላው ወገኔ የማይፈልገውን ግማሽ ፍላጎቴን በውስጤ ማክሰምን ይጠይቃል…፡፡በሀገርሽ መጮኸ ሲያምርሽ መጮኸ ትችያለሽ….ጩኸትሽ ግን ህፃናቶች አስደንግጦ ችግር ላይ አለመጣሉን እርግጠኛ መሆንና ለሌላውም መጠንቀቅን ይጠይቃል…፡፡የጋራ በሆነ ሀገር ውስጥ ሙሉ ነፃነት ሚባል ነገር የለም…ያንቺ ነፃነት የእኔ ደህንነትን አደጋ ላይ የሚጥል ከሆነ ገደብ ይበጅለታል … ህግ የሚባል ገደብ…፡፡ስለዚህ በጋራ ሀገር ውስጥ የጋራ የሆነ ህግ ማክበር ስንችል ነው የጋራ የሆነች ሀገራችንን ህልውና ማስጠበቅ የምንችለው…ሀገራችን እንወዳለን ምንለው በትክክል የሚሰራው በዚህ መንገድ ብቻ ስንጓዝ ነው…ካለበለዚያ እንደፈለኩ ካልተንፈራገጥኩ ምል ከሆነ ስንፈራገጥ የሌላውን ሰው አፍንጫ ላጣምም ስለምችል ችግር መፍጠሬ አይቀርም ፤እራሴ አብኩቼ እራሴ ካልጋገርኩ አይጣፍጥም የምል ከሆነ አይደለም በጋራ ሀገር በጋራ ቤት ውስጥም ከቤተሰቦቼ ጋር መኖር አልችልም… …ሀገሩን የሚወድ ዲሞክራት ሰው እቤቱ ለተደገሰ ሰርግ የሚከፍተውን የሰርግ ዘፈን የጎራቤቱን የሀዘን ሙሾ አለመረበሹን ማረጋገጥ እና መጠንቀቅ እንዳለበት በደንብ ማወቅ አለበት….
ከየትኛው ሀሳብ ተነስተን ምን ውስጥ ገባን….አባቴ ሁሌ እንዴህ ነው….አንድ ነጠላ ስለቤተሰብ የተነሳችን ሀሳብ ለጥጦ ለጥጦ ሀገራዊና አለማቀፋዊ ጉዳይ ማድረግ የተካነበት ነው…...
አሁን ገላን ደርሰናል … የመኪናዋ ነዳጅ አስተማማኝ ስላልሆነ መኪናዬን ወደቀኝ ጠመዘዝኩና ወደ ነዳጅ ማደያ ገባው …. አስተካክዬ በማቆም ሞተሩን አጣፋውና ጋቢናውን ከፍቼ ከመኪናው ወረድኩ ..ነዳጁን እስኪሞላ ውሀ ስለጠማኝ ለመግዛት ወደሱፐር ማርኬት ነው ሄድኩት ….ምፈልገውን ገዝቼ ወደመኪናዬ ስመለስ ግማሽ መንገድ ላይ ከፊቴ ማን ገጭ ቢል ጥሩ መሰላችሁ ….?እስኪ ገምቱ …?አለቃዬ…አቤት የደነገጥኩት ድንጋጤ…በትምህርት ሰዓት ፎርፋ ሆቴል ቁጭ ብላ ስትዝናና አባቷ እይታ ውስጥ የገባች ልጃገረድ ነው የመሰልኩት…
‹‹ደግሞ እዚህ ምን ትሰሪያለሽ..…?››እጁን ለሰላምታ እየዘረጋልኝ
የዘረጋልኝን ከሶፍት የለሰለሰ የሴት የመሰለ እጁን እየጨበጥኩ..በዛውም ይሄ እጅ ገላዬ ላይ አርፎ ቢዳብሰኝ ምን ሊሰማኝ እደሚችል እየገመትኩ ‹‹ወደዱከም እየሄድን ..ነዳጅ እየሞላው ነው…›› ብዬ መለስኩለት ..በእጄ ወደመኪናችን እየጠቆምኩ
ግራ እንደማጋባትም እያለ‹‹ማለት…? ከማን ጋር……?››እንዴ!! እንደቦይ ፍሬንዴ እኮ ነው ኮስተር ብሎ እየጠየቀኝ ያለው
‹‹የትርፍ ጊዜ ስራ ከሚያሰሩኝ ከአለቃዬ ጋር …በእረፍት ቀናቸው መኪና ስላማይነዱ እኔነኝ ምሾፍርላቸው… ››ውሸቱን ከየት እንደመጣልኝ አላውቅም… ቀባጠርኩ…
‹‹አንቺ የእረፍት ቀንሽ አይደለ እንዴ……?ደግሞ መኪና መንዳት እደምትቺይ አልነገርሺኝም››
‹‹አልጠየቅከኝም እንጂ ብትጠይቀኝ እንገርህ ነበር……የእረፍት ቀንሽ ላልከው ደግሞ ደሀ እረፍት ቀን አያስፈልገውም..በዛ ላይ እንደምታየው ሰውዬዬ ጮማ ናቸው…አንተ ልታባርረኝ አይደል እሷቸው ናቸው
፡
፡
#ክፍል_አስር
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
...‹‹ዛሬ የት እንሂድ…?›› አልኩት አባቴን ስምንት ሰዓት ከሩብ አካባቢ….
መኪና ውስጥ ገብተን እኔ እየነዳው ነው እያወራን ያለነው….
‹‹እኔ ምንም በውስጤ የለም…አረጀው መሰለኝ የመዝናኛ አይነቶች እየጠፉብኝ ነው፡፡››
‹‹የእኔ አባትማ እንዲህ በቀላሉ አያረጅም …ገና እኔና እናቴ ድል አድርገን ደግሰን ልጃገረድ ነው የምንድርህ››
‹‹አይ እብድ የሆንሽ ልጅ…በሚስት ላይ ሚስት ወንጀል እንደሆነ አታውቂም…››
‹‹አይ እናቴንማ ሚስቴ ብለህ መጥራቱን አቁም …አሁን መጨረሻ ውሳኔ ላይ ደርሼያለው…››
‹‹ምን አይነት ውሳኔ…?››
‹‹አሁን የጤናዋ ጉዳይ መስመር እስኪይዝ ነው እንጂ ወይ እንደገና ታግባህ ወይ ደግሞ በፍቃዷ ትልቀቅህና ልዳርህ››
ፈገግ አለና‹‹…አሁን ይሄን ምን አሳሰበሽ…?›
‹‹ለምን አላስብም አባ……? ደግሞ አሁን አይደለም …ሁሌ እኮ ነው ሚያንገበግበኝ…በዚህ ጉዳይ ላይ የሆነ ነገር ብትለኝ ደስ ይለኛል….››
‹‹ምን እንድልሽ ነው የምትፈልጊው……?››
‹‹እኔ እንጃ…እናቴን ለምን አልተውካትም……?መቼስ ለብሯ ስትል አብረሀት እንዳልቆየህ አውቃለሁ…አንተ በቁስ ፍቅር ልትሸነፍ ምትችል ሰው አይደለህም …››
‹‹ለምን ጥያቄውን ገልብጠሸ አልጠየቅሺኝም…?››
‹‹እንዴት ብዬ……?››
‹‹ለምን እናቴ አንተን ጥላህ አልሄደችም..…?ለምን እንደዛ ማድረግ ተሳናት……? ሀብታም ነች፤ቆንጆ ነች፤የተማረች እና ብልህ ነች ከንተ ጋር ለምን ኑሮዋን መቀጠል ፈለገች……?ለምን ከቤቷ አንተን አስወጥታ ሌላ የሚመጥናትን ባል አላገባችም ብለሽ አልጠየቅሺም….…?ለምን….…?››
‹‹ሚመጥናትን!! …?ጭራሽ አንተ ለእሷ መመጠን አቅቶህ…? አረ አታስቀኝ ....አንተ እኮ ሁሌ ባል ለመሆን ዝግጁ ነህ…አንተ እንከን አልባ ሰው ነህ…እሷ ነች ሀብት አሳዳጇ..እሷ ነች ቤቱን እርግፍ አድርጋ የአደባባይ ሴት የሆነችው…እሷ ነች…››
‹‹በይ ይብቃሽ ልጄ…ሁል ግዜ ስለምንወዳቸው ሰዎች ያለን ምልከታ ስለእነሱ እወነቱን እንዳናይ እያየንም እንኳን አምነን እንዳንቀበል ጥቁር መጋረጃ ይሆንብናል…ላንቺ አባትሽ ምንም ጉድፍ የለበትም…ያንቺን አባት የሚመስል ሰው በዚህ ምድር ላይ አልተፈጠረም…የዚህ ዓለም ቆነጃጅቶች ሁሉ አባትሽን ለማግኘት ቢደባደብና ቢቦጫጨቁ ተገቢ ነው…..አይደል..…?እንደዛ አይደል የምታስቢው..…?››
‹‹ምነው ባስብ ታዲያ ተሳሳትኩ……?.››
‹‹አዎ ተሳስተሸል..፡፡ባልና ሚስት በሆነ ነገር አልተስማሙም ማለት ጎጆቸውን ማፍረስ አለባቸው ማለት አይደለም…ደግሞ ልጄ አንድ ነገር ልነግርሽ እፈልጋለው.. ትዳርና ሀገር ውስብስብ ናቸው፡፡ትዳር ይዘሽ ልጆች ወልደሽ እና ንብረት አፍርተሸ ረጅም አመት ኖርሽ ማለት ሁሉ ነገር ገነታዊ ነው ማለት አይደለም…የሆነ ነገር ለማግኘት ሁሌ መክፈል ያለብሽ የሆነ መስዋዕትነት አለ…ባልሽ በምንም አይነት ሁኔታ መቶ ፐርሰንት አንቺ ወደምትወጂው ወይም አንቺ ወደምትጓዢበት የህይወት መንገድ ሊጓዝ አይችልም…እንደዛ እንዲያደርግ አደረግሽ ማለት ማነቱን አጠፋሺው ማለት ነው…ማንም ሰው ደግሞ የራሱን ማንነት እስከወዲያኛው ማጣት ስለማይፈልግ የሆነ ቀን ማንነቱን ለማስመለስ መንፈራገጡ አይቀርም ..ያ ደግሞ እቤት ወደመሰነጣጠቅ እና ወደማፍረሰ ያመራል…፡፡
አየሽ ባልና ሚስት ቃልኪዳናቸውን አክብረው እስከወዲያኛው ለመኖር አንድ ነገር ላይ ብቻ ነው እኩል መስማማት ሚገባቸው ‹‹ጎጆችን የጋራችን ነው… የጓጇችንን ህልውና ሁለታችንም እኩል እንፈልገዋለን… ለዛም ስንል ሁል ጊዜ በጋራ ሆነ በየግላችን የተቻለንን እንጥራለን..…››ይሄ ነው ወሳኙ ጉዳይ… ቃላቸውን ለማክበር ሲሉ ይከባበራሉ..ይሄንን ቃል ለማክበር ሲሉ ይደማመጣሉ፣ይሄንን እውን ለማድረግ ሲሉ ሁሌ ሳይሰለቻቸው ይቅር ይባባላሉ….ለጎጇቸው ህልውና ሲሉ ሰጥቶ በመቀበል ፤ተሸንፎም ጭምር በማሸነፍ እኩል ይጥራሉ….
እና ትዳር ቀላል ነገር አይደለም…ባልና ሚስት ተባብሎ እጅ ለእጅ በመያያዝ በየድግስ ቤቱ ከመሄድ በላይ ነው፣ባልና ሚስት መሆን አንድ መሶብ ከመብላት እና አንድ አልጋ ከመጋራትም በላይ ነው…
ይሄን ጌዜ ከተማውን ለቀን ቃሊቲ ኬላ ጋር ደርሰናል..…እየነዳው ያለውት ወደ ዱከም ነው..አባቴ ጥሬ ስጋ ይወዳል..ዱከም ደግሞ በጥሬ ስጋ የምታውቁት ነው…አባቴ ንግግሩን ቀጥሏል፡፡
ትዳር የሚባለው ተቋም ሀገር ከሚባለው የጋራ ቤት ጋር ይመሳሰላል…አንድ ሀገር ውስጥም በጋራ ለመኖር ሀገሬን እወዳለው ብቻ ማለት በቂ አይደለም..ለሀገሬ ስል ሌላው ወገኔ የማይፈልገውን ግማሽ ፍላጎቴን በውስጤ ማክሰምን ይጠይቃል…፡፡በሀገርሽ መጮኸ ሲያምርሽ መጮኸ ትችያለሽ….ጩኸትሽ ግን ህፃናቶች አስደንግጦ ችግር ላይ አለመጣሉን እርግጠኛ መሆንና ለሌላውም መጠንቀቅን ይጠይቃል…፡፡የጋራ በሆነ ሀገር ውስጥ ሙሉ ነፃነት ሚባል ነገር የለም…ያንቺ ነፃነት የእኔ ደህንነትን አደጋ ላይ የሚጥል ከሆነ ገደብ ይበጅለታል … ህግ የሚባል ገደብ…፡፡ስለዚህ በጋራ ሀገር ውስጥ የጋራ የሆነ ህግ ማክበር ስንችል ነው የጋራ የሆነች ሀገራችንን ህልውና ማስጠበቅ የምንችለው…ሀገራችን እንወዳለን ምንለው በትክክል የሚሰራው በዚህ መንገድ ብቻ ስንጓዝ ነው…ካለበለዚያ እንደፈለኩ ካልተንፈራገጥኩ ምል ከሆነ ስንፈራገጥ የሌላውን ሰው አፍንጫ ላጣምም ስለምችል ችግር መፍጠሬ አይቀርም ፤እራሴ አብኩቼ እራሴ ካልጋገርኩ አይጣፍጥም የምል ከሆነ አይደለም በጋራ ሀገር በጋራ ቤት ውስጥም ከቤተሰቦቼ ጋር መኖር አልችልም… …ሀገሩን የሚወድ ዲሞክራት ሰው እቤቱ ለተደገሰ ሰርግ የሚከፍተውን የሰርግ ዘፈን የጎራቤቱን የሀዘን ሙሾ አለመረበሹን ማረጋገጥ እና መጠንቀቅ እንዳለበት በደንብ ማወቅ አለበት….
ከየትኛው ሀሳብ ተነስተን ምን ውስጥ ገባን….አባቴ ሁሌ እንዴህ ነው….አንድ ነጠላ ስለቤተሰብ የተነሳችን ሀሳብ ለጥጦ ለጥጦ ሀገራዊና አለማቀፋዊ ጉዳይ ማድረግ የተካነበት ነው…...
አሁን ገላን ደርሰናል … የመኪናዋ ነዳጅ አስተማማኝ ስላልሆነ መኪናዬን ወደቀኝ ጠመዘዝኩና ወደ ነዳጅ ማደያ ገባው …. አስተካክዬ በማቆም ሞተሩን አጣፋውና ጋቢናውን ከፍቼ ከመኪናው ወረድኩ ..ነዳጁን እስኪሞላ ውሀ ስለጠማኝ ለመግዛት ወደሱፐር ማርኬት ነው ሄድኩት ….ምፈልገውን ገዝቼ ወደመኪናዬ ስመለስ ግማሽ መንገድ ላይ ከፊቴ ማን ገጭ ቢል ጥሩ መሰላችሁ ….?እስኪ ገምቱ …?አለቃዬ…አቤት የደነገጥኩት ድንጋጤ…በትምህርት ሰዓት ፎርፋ ሆቴል ቁጭ ብላ ስትዝናና አባቷ እይታ ውስጥ የገባች ልጃገረድ ነው የመሰልኩት…
‹‹ደግሞ እዚህ ምን ትሰሪያለሽ..…?››እጁን ለሰላምታ እየዘረጋልኝ
የዘረጋልኝን ከሶፍት የለሰለሰ የሴት የመሰለ እጁን እየጨበጥኩ..በዛውም ይሄ እጅ ገላዬ ላይ አርፎ ቢዳብሰኝ ምን ሊሰማኝ እደሚችል እየገመትኩ ‹‹ወደዱከም እየሄድን ..ነዳጅ እየሞላው ነው…›› ብዬ መለስኩለት ..በእጄ ወደመኪናችን እየጠቆምኩ
ግራ እንደማጋባትም እያለ‹‹ማለት…? ከማን ጋር……?››እንዴ!! እንደቦይ ፍሬንዴ እኮ ነው ኮስተር ብሎ እየጠየቀኝ ያለው
‹‹የትርፍ ጊዜ ስራ ከሚያሰሩኝ ከአለቃዬ ጋር …በእረፍት ቀናቸው መኪና ስላማይነዱ እኔነኝ ምሾፍርላቸው… ››ውሸቱን ከየት እንደመጣልኝ አላውቅም… ቀባጠርኩ…
‹‹አንቺ የእረፍት ቀንሽ አይደለ እንዴ……?ደግሞ መኪና መንዳት እደምትቺይ አልነገርሺኝም››
‹‹አልጠየቅከኝም እንጂ ብትጠይቀኝ እንገርህ ነበር……የእረፍት ቀንሽ ላልከው ደግሞ ደሀ እረፍት ቀን አያስፈልገውም..በዛ ላይ እንደምታየው ሰውዬዬ ጮማ ናቸው…አንተ ልታባርረኝ አይደል እሷቸው ናቸው
👍1
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍስሀ
ምን ነካኝ..? የዓመታት ፍቅረኛዬን
ከወንድ ጋር ስትዳራ እጅ ከፍንጅ የያዝኳት አይነት ስሜት ነው የተሰማኝ…የሆነ ውስጥ አንጀትን የሚያላውስ አይነት የመረበሽ ስሜት…የሆነ ልብን ድክም የሚያደርግ አይነት የፍርሀት ስሜት…የሆነ ያሳደጋችኃት ለማዳ ወፍ ከእጃችሁ አምልጣ ሰማዩ ተንሳፋ አድማሱን ሰንጥቃ ስትበርባችሁ በዛው ትቀር ይሆን.? ብላችሁ ስትሰጉ የሚሰማችሁ አይነት የእጦት ስሜት …
ሱፐር ማርኬት ልገዛ የመጣውትን ዕቃ ስለጠፋኝ እንደፈዘዝኩ ዝም ብዬ ባዶዬን ነው ወደመኪናዬ የተመለስኩ…... መኪናዬ ውስጥ ገባውና ሞተሩን አስነስቼ የመኪናዋን አፍንጫ ወደ አዲስአባ መለስኩት……
‹‹እንዴ ምን እየሆንክ ነው.?››
‹‹ይቅርታ ለስራ ጉዳይ ስለተደወለልኝ መመለስ አለብን››
‹‹እርግጠኛ ነህ.?››አለቺኝ….
‹‹ማነች እንደዛ ያለችህ.?›› እንዳትሉኝ…ፍቅረኛዬ ነች…ሳሮን ተስፋሁን ትባላለች፡፡አብረን ከሆን አንድ አመት አስቆጥረናል…የዛሬ አመት ለቫኬሽን ከውጭ የመጣው ጊዜ ነበር የተዋወቅነው…አንድ ወር እዚህ ስቆይ አብራኝ ነበረች..ከዛ ለትምህርቴ ወደውጭ ከተመለስኩ ቡኃላም በስልኩም በስካይፒውም ፍቅራችንን እንዲቀጥል ማድረግ ችለናል….አሁን ጨርሼ ከመጣው ቡኃላም እንደዛው…ዛሬ ወደ ደብረዘይት ለአዳር እየሄድን ነበር…. ዘና ብለን ለነገ ስራ በማለዳ ለመመለስ አቅደን ….ግን ይሄው ከቁጥጥር ውጭ በሆነ አደፍራሽ ስሜት ወደ አዲስአባ እየተመለስኩ ነው…..
‹‹እርግጠኛ ነህ ስትይ ….ምን ለማለት ነው.?››ጅራፍ ራሱ ገርፎ እራሱ ይጮኸል ይባላል ..ተቆጣሇት
‹‹የተደወለልህን ስልክ ታሰየኛለህ….?››
‹‹ማለት.? ››
‹‹ስከታተልህ ነበር …ምንም አይነት ስልክ ስታናግር አላየውም..ልጅቷ ማነች...?››
‹‹የቷ ልጅ.?››የምትለው ያልገባኘኝ መስዬ ጠየቅኳት
‹‹እንደዛ ያፈዘዘችህ ነቻ…ለዘመናት የጠፋችብህን ፍቅረኛህን በአጋጣሚ ያገኘህ ነው እኮ የምትመስለው….››
‹‹አትቀባጥሪ….››
‹‹አልተሳሳትኩም ማለት ነው….እንደው ወንዶች ሰትባሉ..››
‹‹በናትሽ አሁን ዝም ልትይልኝ ትቺያለሽ ..ምንም ነገር የመናገር ሙድ ላይ አይደለውም…››
‹‹እንግዲያውም አውርደኝ….››
‹‹የትነው ማወርድሽ.?››ገርሞኝ
‹‹እዚሁ አውርደኝ… ብቻዬን በትራንስፖርት ሄጄ አድሬ መጣለሁ…በስንት ዘዴ እና ውትወታ ቤተሰቤን አሳምኜ ያገኘውትን ከቤት ውጭ የማደር ዕድል ላባክነው አልፈልግም….››
‹‹እወነትሽን ባልሆነ.?››
‹‹እወነቴን ነው ..አውርደኝ አልኩህ እኮ…››አንቧረቀችብኝ
‹‹ሆድ ለባሰው ማጭድ አታውሰው ››ይላል የሀገሬ ሰው….ዳር ይዤ ፍሬኑን ጠርቅሜ ያዝኩና አቆምኩላት… ኮስሞቲኮቾን እና ቅያሬ ልብሶቾን ያጨቀችበትን ቦርሳዋን አንጠልጥላ ወረደች…ኪሴ ገባውና ለመዝናናት ይዥው የነበረ ከእሽጉ ያልተፈታ አምስት ሺ ብር እግሯ ስር ወረወርኩላትና መኪናዬን አስፈንጥሬ ተፈተለኩ……
ከዛ አዳሬን አትጠይቁኝ…ጥዋት አንድ ሰዓት ተኩል ቢሮ ነበርኩ..ስደርስ ፅዳቶች እንኳን ስራቸውን አላጠናቀቁም ነበር… አግኝቼ እስካናግራት ቸኩያለው አይገልፀውም…ደግሞ ሳይቸግረኝ ቅዳሜ ለት ከስራ መሰናበቷን የሚገልፅ የ30 ቀን ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ፈርሜ ነበር….እርግጥ ከሰዓት ሰራተኞች ከወጡ ቡኃላ ስለፈረምኩ ዛሬ ነው የሚደርሳት…ግን እንዴት አድርጌ ማስተካከል እችላለው.. .?መዝገብ ቤት የሚሰሩት አስተዳዳሪውም ጭምር ደብዳቤውን አይተውታል… በውሳኔው የሚዋልል አሐቃ ደግሞ ማንም አያከብረውም….እንደዛ እንዲያስቡኝ ፈፅሞ አልፈልግም….፡፡ ግን ደግሞ የሆነ ነገር ማድረግ አለብኝ…፡፡ብትከሰኝ ጥሩ ነው.. ግን እንዴት ጥሩ ሊሆን ይችላል...?አውቄ ልሸነፍላት ማለት ነው.? ….እሱም ሌላ ጣጣ አለው..‹ በክስ አሸንፍው ተመለሰች› መባሉ ሌላ ውድቀት ነው….አዳሜ ትንሽ በነካዋት ቁጥር ወደክስ እንድትበር መንገድ ማሳየት ነው….፡፡ይልቅ ይቅርታ እዲደረግላት ደብዳቤ ብታስገባ ጥሩ ነው…፡፡አዎ እንደዛ እድታደርግ በዘዴ አግባባታለው…ግን ሳስበው እሷ እንደዛ አታርግም …በፍጽም አንገቷን እንዲህ በቀላሉ የምትደፋ አይነት ልጅ አይደለችም ….
የባጥ የቆጡን ሳስብ 3 ሰዓት ሆነ ..ፀሀፊዬን ጠራዋትና ፌናንን እንድትጠራልኝ ነገርኳት…. ደወለችና….እንዳልገባች ነገረችኝ››
‹‹ምን ማለት ነው … 3 ሰዓት ድረስ አለመግባት….?››ፀሀፊዬ ላይ ነው የጮህኩት
‹‹እኔ እንጃ...?በሞባይሏ ልደውልላት››አለቺኝ እየተሸቆጠቆጠች…፡፡
‹‹አይ ተያት ..እሷን በተመለከተ የተፃፈ ደብዳቤ ከመዝገብ ቤት ታስመጪልኛለሽ.?››
‹‹ቆይ እኔ እራሴ ላምጣ ››ብላ ሄደች
ከሶስት ደቂቃ ቡኃላ ተመልሳ መጣችና ደብዳቤውን እየሰጠቺኝ ‹‹…ያመጣውት ቀሪው ነው ..ዋናውን ፈርማ ወስዳዋለች››አለቺኝ
‹‹ማን ነች የወሰደችው.?››..ሳላስበው ከመቀመጫዬ ተነሳው
‹‹ፌናን ነቻ››
‹‹ምን ጊዜ ወሰደች….? ቅዳሜ ከሰዓት ነበር እኮ የፈረምኩት …ለማንኛው አመሰግናለው..››ብዬ ፀሀፊዋን ሸኘዋትና አስተዳዳሪው ጋር ደወልኩ
‹ደህና አደርክ አቶ ፍሰሀ››
‹‹ሰላም ነኝ..ፌናንን ፈልጌያት ነበር››ቀጥታ ወደ ጉዳዬ ገባው….
‹‹አልገባችም ››
‹‹አልገባኝም ማለት.?››
‹‹ምትገባ አይመስለኝም …..ያው የተሰናበተችበትን ደብዳቤ ወስዳለች..››
‹‹ትውሰዳ..ዝም ብላ ደብዳቤ ተቀብላ መቅረት ትችላለች እንዴ...?ፎርማሊቲ ምናምን ሚባል ነገር የለም….?››
‹‹አይ ፍቃድ ሞልታለች..እንደዛ እንዲሆን መሰለኝ የተነጋገርነው››
‹‹ከምኔው እንዲህ ተዋክባ ሞላችው.?››
‹‹እኔም አልገባኝ አቶ ፍሰሀ …ደብዳቤውን ጥዋት ስገባ ጠረጳዛዬ ላይ ነው ያገኘውት››አሉኝ እየታዘብኝ መሆኑን በሚያሳብቅባቸው ቃና….
ስልኩን በንዴት ጆሮቸው ላይ ጠረቀምኩት ..እስቲ እሳቸው ምን አደረጉኝ…..
…..መልሼ የጠረጳዛውን መጥሪያ ተጫንኩ…ፀሀፊዬ መጣች…‹‹አቤት ፈለከኝ››
===
‹‹ደውይላት… ሞባይሏ ላይ ደውይላት …››ተመልሳ ሄደችና ሞባይሏን ይዛ መጥታ እያየዋት መሞከር ጀመረች… ትግስቴን በሚፈታተን ሁኔታ ደግማ ደጋግማ ሞከረች…‹‹ጥሪ አይቀበልም ነው ሚለው..ሁለቱም ሲሞ አይሰራም››
‹‹የቤት ወይም የጓደኛ ስልክ የላትም.?››
‹‹እኔ አላውቅም ..ወይ የሚያውቅ ሰው ካለ ልጠይቅልህ….?››ግራ ግብትብት ያላት ፀሀፊዬ መፍትሔ ያለችወን ሀሳብ አመጣች…››
‹‹አይ ተይው..አመሰግናለው…››ሸኘዋት
‹‹ምን እሆንኩ ነው ….?እዚህ ቢሮ ስራ ከጀማርኩ ሁለት ሳምንቴ ነው…፡፡በሁለት ሳምንት ብቻ የማውቃት ሴት እንዴት እንዲህ ውስጤን የማተረማመስ አቅም ኖራት….?ነው ወይስ ከእኔ ዕውቅና ውጭ ለዘማናት በውስጤ በስውር የኖረችበት የተፈጥሮ ምትሀታዊ ሚስጥር ይኖር ይሆን...?አይ እንደዛም አይሆንም አሁን እሷን መፈለግ ነው ወይስ በድያታለው ብዬ ስላሰብኩ መፀፀት የወለደው የጥፋተኝነት ስሜት ነው እንዲህ የሚያደርገኝ….?.በቃ አንዴ ላግኛትና አዋርቻት ይቅርታ ከጠየቅኳት ቡኃላ ይሄ ስሜት ይተወኛል…፡፡አዎ እርግጠኛ ነኝ ይተወኛል…››እራሴን ለማፅናናት ብዙ ጣርኩ…መልሼ የጠረጳዛዬን መጥሬያ አንጫረርኩ..የፈረደባት ፀሀፊዬ በፍጥነት መጣች
‹‹ፋይሎን ታመጪልኝ.?››››
‹‹የማንን.?››
‹‹ሌላ የማን ይሆናል .. .?የፌናንን ነዋ››
…‹‹እሺ›› ብላ ሹክክ ብላ ወጥታ ሄደች
‹‹ሰውዬው አረ ተረጋጋ….አሁን ይህቺ ምስኪን ምን አደረገችህ ….?›› እራሴን ለመገሰጽ ሞከርኩ…ይዛልኝ መጣችና አስረክባኝ ወደ ቦታዋ ተመለሰች …
‹‹ፋይሏን ገልጬ ማየት ጀመርኩ…ዝም ብሎ ስሜቴ ስለገፋፋኝ ወይንም ግራ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍስሀ
ምን ነካኝ..? የዓመታት ፍቅረኛዬን
ከወንድ ጋር ስትዳራ እጅ ከፍንጅ የያዝኳት አይነት ስሜት ነው የተሰማኝ…የሆነ ውስጥ አንጀትን የሚያላውስ አይነት የመረበሽ ስሜት…የሆነ ልብን ድክም የሚያደርግ አይነት የፍርሀት ስሜት…የሆነ ያሳደጋችኃት ለማዳ ወፍ ከእጃችሁ አምልጣ ሰማዩ ተንሳፋ አድማሱን ሰንጥቃ ስትበርባችሁ በዛው ትቀር ይሆን.? ብላችሁ ስትሰጉ የሚሰማችሁ አይነት የእጦት ስሜት …
ሱፐር ማርኬት ልገዛ የመጣውትን ዕቃ ስለጠፋኝ እንደፈዘዝኩ ዝም ብዬ ባዶዬን ነው ወደመኪናዬ የተመለስኩ…... መኪናዬ ውስጥ ገባውና ሞተሩን አስነስቼ የመኪናዋን አፍንጫ ወደ አዲስአባ መለስኩት……
‹‹እንዴ ምን እየሆንክ ነው.?››
‹‹ይቅርታ ለስራ ጉዳይ ስለተደወለልኝ መመለስ አለብን››
‹‹እርግጠኛ ነህ.?››አለቺኝ….
‹‹ማነች እንደዛ ያለችህ.?›› እንዳትሉኝ…ፍቅረኛዬ ነች…ሳሮን ተስፋሁን ትባላለች፡፡አብረን ከሆን አንድ አመት አስቆጥረናል…የዛሬ አመት ለቫኬሽን ከውጭ የመጣው ጊዜ ነበር የተዋወቅነው…አንድ ወር እዚህ ስቆይ አብራኝ ነበረች..ከዛ ለትምህርቴ ወደውጭ ከተመለስኩ ቡኃላም በስልኩም በስካይፒውም ፍቅራችንን እንዲቀጥል ማድረግ ችለናል….አሁን ጨርሼ ከመጣው ቡኃላም እንደዛው…ዛሬ ወደ ደብረዘይት ለአዳር እየሄድን ነበር…. ዘና ብለን ለነገ ስራ በማለዳ ለመመለስ አቅደን ….ግን ይሄው ከቁጥጥር ውጭ በሆነ አደፍራሽ ስሜት ወደ አዲስአባ እየተመለስኩ ነው…..
‹‹እርግጠኛ ነህ ስትይ ….ምን ለማለት ነው.?››ጅራፍ ራሱ ገርፎ እራሱ ይጮኸል ይባላል ..ተቆጣሇት
‹‹የተደወለልህን ስልክ ታሰየኛለህ….?››
‹‹ማለት.? ››
‹‹ስከታተልህ ነበር …ምንም አይነት ስልክ ስታናግር አላየውም..ልጅቷ ማነች...?››
‹‹የቷ ልጅ.?››የምትለው ያልገባኘኝ መስዬ ጠየቅኳት
‹‹እንደዛ ያፈዘዘችህ ነቻ…ለዘመናት የጠፋችብህን ፍቅረኛህን በአጋጣሚ ያገኘህ ነው እኮ የምትመስለው….››
‹‹አትቀባጥሪ….››
‹‹አልተሳሳትኩም ማለት ነው….እንደው ወንዶች ሰትባሉ..››
‹‹በናትሽ አሁን ዝም ልትይልኝ ትቺያለሽ ..ምንም ነገር የመናገር ሙድ ላይ አይደለውም…››
‹‹እንግዲያውም አውርደኝ….››
‹‹የትነው ማወርድሽ.?››ገርሞኝ
‹‹እዚሁ አውርደኝ… ብቻዬን በትራንስፖርት ሄጄ አድሬ መጣለሁ…በስንት ዘዴ እና ውትወታ ቤተሰቤን አሳምኜ ያገኘውትን ከቤት ውጭ የማደር ዕድል ላባክነው አልፈልግም….››
‹‹እወነትሽን ባልሆነ.?››
‹‹እወነቴን ነው ..አውርደኝ አልኩህ እኮ…››አንቧረቀችብኝ
‹‹ሆድ ለባሰው ማጭድ አታውሰው ››ይላል የሀገሬ ሰው….ዳር ይዤ ፍሬኑን ጠርቅሜ ያዝኩና አቆምኩላት… ኮስሞቲኮቾን እና ቅያሬ ልብሶቾን ያጨቀችበትን ቦርሳዋን አንጠልጥላ ወረደች…ኪሴ ገባውና ለመዝናናት ይዥው የነበረ ከእሽጉ ያልተፈታ አምስት ሺ ብር እግሯ ስር ወረወርኩላትና መኪናዬን አስፈንጥሬ ተፈተለኩ……
ከዛ አዳሬን አትጠይቁኝ…ጥዋት አንድ ሰዓት ተኩል ቢሮ ነበርኩ..ስደርስ ፅዳቶች እንኳን ስራቸውን አላጠናቀቁም ነበር… አግኝቼ እስካናግራት ቸኩያለው አይገልፀውም…ደግሞ ሳይቸግረኝ ቅዳሜ ለት ከስራ መሰናበቷን የሚገልፅ የ30 ቀን ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ፈርሜ ነበር….እርግጥ ከሰዓት ሰራተኞች ከወጡ ቡኃላ ስለፈረምኩ ዛሬ ነው የሚደርሳት…ግን እንዴት አድርጌ ማስተካከል እችላለው.. .?መዝገብ ቤት የሚሰሩት አስተዳዳሪውም ጭምር ደብዳቤውን አይተውታል… በውሳኔው የሚዋልል አሐቃ ደግሞ ማንም አያከብረውም….እንደዛ እንዲያስቡኝ ፈፅሞ አልፈልግም….፡፡ ግን ደግሞ የሆነ ነገር ማድረግ አለብኝ…፡፡ብትከሰኝ ጥሩ ነው.. ግን እንዴት ጥሩ ሊሆን ይችላል...?አውቄ ልሸነፍላት ማለት ነው.? ….እሱም ሌላ ጣጣ አለው..‹ በክስ አሸንፍው ተመለሰች› መባሉ ሌላ ውድቀት ነው….አዳሜ ትንሽ በነካዋት ቁጥር ወደክስ እንድትበር መንገድ ማሳየት ነው….፡፡ይልቅ ይቅርታ እዲደረግላት ደብዳቤ ብታስገባ ጥሩ ነው…፡፡አዎ እንደዛ እድታደርግ በዘዴ አግባባታለው…ግን ሳስበው እሷ እንደዛ አታርግም …በፍጽም አንገቷን እንዲህ በቀላሉ የምትደፋ አይነት ልጅ አይደለችም ….
የባጥ የቆጡን ሳስብ 3 ሰዓት ሆነ ..ፀሀፊዬን ጠራዋትና ፌናንን እንድትጠራልኝ ነገርኳት…. ደወለችና….እንዳልገባች ነገረችኝ››
‹‹ምን ማለት ነው … 3 ሰዓት ድረስ አለመግባት….?››ፀሀፊዬ ላይ ነው የጮህኩት
‹‹እኔ እንጃ...?በሞባይሏ ልደውልላት››አለቺኝ እየተሸቆጠቆጠች…፡፡
‹‹አይ ተያት ..እሷን በተመለከተ የተፃፈ ደብዳቤ ከመዝገብ ቤት ታስመጪልኛለሽ.?››
‹‹ቆይ እኔ እራሴ ላምጣ ››ብላ ሄደች
ከሶስት ደቂቃ ቡኃላ ተመልሳ መጣችና ደብዳቤውን እየሰጠቺኝ ‹‹…ያመጣውት ቀሪው ነው ..ዋናውን ፈርማ ወስዳዋለች››አለቺኝ
‹‹ማን ነች የወሰደችው.?››..ሳላስበው ከመቀመጫዬ ተነሳው
‹‹ፌናን ነቻ››
‹‹ምን ጊዜ ወሰደች….? ቅዳሜ ከሰዓት ነበር እኮ የፈረምኩት …ለማንኛው አመሰግናለው..››ብዬ ፀሀፊዋን ሸኘዋትና አስተዳዳሪው ጋር ደወልኩ
‹ደህና አደርክ አቶ ፍሰሀ››
‹‹ሰላም ነኝ..ፌናንን ፈልጌያት ነበር››ቀጥታ ወደ ጉዳዬ ገባው….
‹‹አልገባችም ››
‹‹አልገባኝም ማለት.?››
‹‹ምትገባ አይመስለኝም …..ያው የተሰናበተችበትን ደብዳቤ ወስዳለች..››
‹‹ትውሰዳ..ዝም ብላ ደብዳቤ ተቀብላ መቅረት ትችላለች እንዴ...?ፎርማሊቲ ምናምን ሚባል ነገር የለም….?››
‹‹አይ ፍቃድ ሞልታለች..እንደዛ እንዲሆን መሰለኝ የተነጋገርነው››
‹‹ከምኔው እንዲህ ተዋክባ ሞላችው.?››
‹‹እኔም አልገባኝ አቶ ፍሰሀ …ደብዳቤውን ጥዋት ስገባ ጠረጳዛዬ ላይ ነው ያገኘውት››አሉኝ እየታዘብኝ መሆኑን በሚያሳብቅባቸው ቃና….
ስልኩን በንዴት ጆሮቸው ላይ ጠረቀምኩት ..እስቲ እሳቸው ምን አደረጉኝ…..
…..መልሼ የጠረጳዛውን መጥሪያ ተጫንኩ…ፀሀፊዬ መጣች…‹‹አቤት ፈለከኝ››
===
‹‹ደውይላት… ሞባይሏ ላይ ደውይላት …››ተመልሳ ሄደችና ሞባይሏን ይዛ መጥታ እያየዋት መሞከር ጀመረች… ትግስቴን በሚፈታተን ሁኔታ ደግማ ደጋግማ ሞከረች…‹‹ጥሪ አይቀበልም ነው ሚለው..ሁለቱም ሲሞ አይሰራም››
‹‹የቤት ወይም የጓደኛ ስልክ የላትም.?››
‹‹እኔ አላውቅም ..ወይ የሚያውቅ ሰው ካለ ልጠይቅልህ….?››ግራ ግብትብት ያላት ፀሀፊዬ መፍትሔ ያለችወን ሀሳብ አመጣች…››
‹‹አይ ተይው..አመሰግናለው…››ሸኘዋት
‹‹ምን እሆንኩ ነው ….?እዚህ ቢሮ ስራ ከጀማርኩ ሁለት ሳምንቴ ነው…፡፡በሁለት ሳምንት ብቻ የማውቃት ሴት እንዴት እንዲህ ውስጤን የማተረማመስ አቅም ኖራት….?ነው ወይስ ከእኔ ዕውቅና ውጭ ለዘማናት በውስጤ በስውር የኖረችበት የተፈጥሮ ምትሀታዊ ሚስጥር ይኖር ይሆን...?አይ እንደዛም አይሆንም አሁን እሷን መፈለግ ነው ወይስ በድያታለው ብዬ ስላሰብኩ መፀፀት የወለደው የጥፋተኝነት ስሜት ነው እንዲህ የሚያደርገኝ….?.በቃ አንዴ ላግኛትና አዋርቻት ይቅርታ ከጠየቅኳት ቡኃላ ይሄ ስሜት ይተወኛል…፡፡አዎ እርግጠኛ ነኝ ይተወኛል…››እራሴን ለማፅናናት ብዙ ጣርኩ…መልሼ የጠረጳዛዬን መጥሬያ አንጫረርኩ..የፈረደባት ፀሀፊዬ በፍጥነት መጣች
‹‹ፋይሎን ታመጪልኝ.?››››
‹‹የማንን.?››
‹‹ሌላ የማን ይሆናል .. .?የፌናንን ነዋ››
…‹‹እሺ›› ብላ ሹክክ ብላ ወጥታ ሄደች
‹‹ሰውዬው አረ ተረጋጋ….አሁን ይህቺ ምስኪን ምን አደረገችህ ….?›› እራሴን ለመገሰጽ ሞከርኩ…ይዛልኝ መጣችና አስረክባኝ ወደ ቦታዋ ተመለሰች …
‹‹ፋይሏን ገልጬ ማየት ጀመርኩ…ዝም ብሎ ስሜቴ ስለገፋፋኝ ወይንም ግራ
😁2👍1👏1
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍስሀ
መፅሃፍ መደብሩ ቆሜያለሁ ነገረ ስራዋን በአትኩሮት እየተከታተልኩ ነው፡፡
ገዢው የሆነ መፃፍ ርዕስ ነገሯት
‹‹እንደዚህ የሚባል መጽሀፍ አለሽ.?››ጠየቃት
‹‹አለኝ ግን ለምን ፈለግከው?››
‹‹አልገባኝም?ልገዛሽ ነዋ.?››
‹‹እሱማ ልትገዛኝ ነው ?ለምን መጽሀፉን ልትገዛው ፈለክ ነው ጥያቄዬ?››
‹‹ለምንስ ብፈልገው አንቺ ምን ይመለከትሻል ?ካለሽ ሽጪልኝ ከሌለሽ የለኝም በይ››
‹‹ስኳር ወይ ሳሙና አይደለም የምትገዛው፤ መጽሀፍ ነው..፡፡መጽሀፍቶች ደግሞ ሳያነቡ የሚያነቡ ለመምሰል ታቅፈዋቸው የሚዞሩ ከንቱዎች እጅ እንዲገቡ አልፈልግም በተለይ እንደጠየቅከው ያለ መጽሀፍ……..፡፡ይሄውልህ እዛ አካባቢ በመደዳ መጽሀፍት ቤቶች አሉ ካላቸው ምክንያት ሳይጠይቁ ይሸጡልኸል….ደህና ሁን››ብላ አሰናበተችው፡፡
ሰውዬው በመገረም እያጉረመረመ ጥሏት ሄደ ..ዞር ስትል እኔን አየቺኝ
‹‹እንዴ አለቃ ምን እግር ጣለህ...?መፅሀፍ ልገዛሽ ነው እንዳትለኝ…?››አለች በመጠኑ ፈገግ ብላ
‹‹ለመሆኑ የትኛው የዋህ ነጋዴ ነው ለመክሰር አንቺን እዚህ ያቆመሽ….?››የእወነቴን ነበር የተናገርኩት
‹‹የሚተማመንብኝ››
‹‹እንዲ ደንበኛ እያበሳጨሽ እያባረርሽበት ነው የሚተማመንብሽ…››
ልትመልስልኝ አፎን ስታስተካክል አንድ ሽበት የወረራቸው ደስ የሚል ግርማ ሞገስ ያላቸው ግን ደግሞ ጎስቆል ያሉ አዛውንት ድምጽ በመሀከላችን ገባ ?››
‹‹ደህና ነሽ የእኔ አለም….?››
‹‹ደህና አደሩ..እንዴት ኖት? ጤናዎትስ?››እኔን ከማውቃት ተቃራኒ በሆነ እርብትብት ትህትና እየተፍለቀለቀች እና እየፈገገች በጋለ ሰላምታ ተቀበለቻቸው፡፡ሰው እንዴት እንዲህ ሁለት ገፃ ይኖረዋል?
‹‹….ሰላም ነኝ ልጄ…፡፡ይመስገነው፡፡››
‹‹አኔ እኮ ሲጠፉብኝ ያመሞት መስሎኝ ሰግቼ ነበር››
‹‹አይ ደህና ነኝ.ባለፈው ያስቀመጥሺልኝን መጽሀፍ ልጆቹ ሰጥተውኝ ወስጄ ነበር..እና መጻሀፎ ስለመሰጠቺኝ ከቤት መውጣት አልቻልኩም ለዛ ነው የጠፋሁብሽ››
‹‹ጨረሱት?››
‹‹ጨረሱት..ሁለት ጊዜ ነው ደግሜ ያነበብኩት…አሁንም አንዴ የምደግመው ይመስለኛል..››
‹‹ስለወደዱት ደስ ብሎኛል..አሁንም ያዘጋጀውሏት መጽሀፍ አለች›› ብላ ከተቆለሉት መጽሀፎቶች ጀርባ እጆን ሰደደችና አንድ ልባሱ አርጀት ያለ መጽሀፍት አውጥታ ሰጣቻቸው ፡፡በመንሰፍሰፍ ተቀበሏት እና ርዕሱን አገላብጠው ካነበብ ቡሃላ እሷን ወደ ራሳቸው ጎትተው ግንባሯን ከሳሟት ቡኃላ ‹‹ ስንትነው የእኔ ልጅ .?››ጠየቋት
‹‹ሁለት መቶ ሀምሳ ብር ነው የገዛውሎት››
ቀኝ የካፖርት ኪሳቸው ገቡ…የሆነ ባለአስር ብር ዝርዝር ብሮች አወጡ..የካፖርታቸውን ኪስ ከፈቱና ደረት ኪሳቸው ገቡ ሳንቲም ሳይቀር ያለቸውን ብር ከየኪሳቸው እያወጡ ባንኮኒው ላይ ዘረገፍት.በትኩረተ ስከታተላቸው ነበር…ቢቆጠር ከመቶ ምናንም ብር አይበልጥም ቢያንስ የጠየቀቻቸውን ግማሹን አይሸፍንም
‹‹ልጄ በዚህ ላይ አንቺ ሙይልኝ…››አሏት…የልመና ሳይሆን የትዕዛዝ ቃና ባለው የመተማመን ስሜት
‹‹.አይ ይሄ ልጅ የእርሶ አድናቂ ነው… ገና ሲመጡ አይቶት የሚወስዱትን መፃሀፍን እኔ ነኝ የምከፈለው.. አደራሽን እንዳተቀበያቸው ሲለኝ ነበር..አይደል ፍሰሀ?››አለቺኝ ወደእኔ ቀና ብላ አፍጥጣ እያየቺኝ
‹‹አዎ…እባኮት እልኩና ወደኪሴ ገብቼ ዋሌቴን በማውጣት በግምት አንድ ሺ ምናምን ብር ይመስለኛል አወጣውና ይሄው ብሩ የሚችለውን አይነት የሚፈልጉትን መጽሀፍ ስጭልኝ….››
<<አላልኮትም ››አለችና የእሳቸውን ብር ከባንኮኒው ሰብስባ ኪሳቸው መልሳ ጨመረችላቸውና…
‹‹ሌላ ምን ምን መፃሀፍ ነው የሚፈልጉት….?››
‹‹ያው የመጽሀፍ ምርጫዎቼን ታውቂ የለ.››
…ስድስት ወይም ሰባት የሚሆኑ መጻሀፎችን መረጠችና በፔስታል አድርጋ ሰጠቻቸው
ሰውዬው ከመሄዳቸው በፊት ወደእኔ ጠጋ አሉ..ብዙ ምርቃት እንደሚያዘንቡብኝ እየጠበቅኩ ነው…‹‹እነዚህን መፃሀፎች አንብቦ ለመጨረስ ሁለት ወር ያህል ይፈጅብኛል…ለቀጣዬቹ ሁለት ወራት እንድኖር የሚያስችል ምክንያት ሰጠተኸኛል ማለት ነው..ምክንያቱም እኔ በምንም አይነት ሁኔታ እጄ ላይ ያሉ መጽሀፎቸን አንብቤ ሳልጨርስ አልሞትምና.››አሉኝ ..ምን ለማለት እንደፈለጉ አልገባኝም..ይህቺ ልጅ ግራ አጋቢ የሆነችው ከእንደዚህ አይነት ግራ አጋቢ ብኩኖች ጋር እየኖረች ነው ስል በውስጤ አሰብኩ.. ሽማግሌው ወደፌናን ዞረው ‹‹የእኔ ትንሽ መላአክ ደህና ሰንብቺልኝ..››ብለው ፊታቸውን አዙረው የመጽሀፍ መደብሩን ለቀው ወጡ
‹‹ምትገርሚ እብድ ነሽ.ለማላውቃቸው ሰው መጽሀፍ ታስገዥኛለሽ…ደግሞ ባዋርድሽስ.?››
‹‹ምን ብለህ ነው የምታዋርደኝ.?››
<<መች አልኩሽ .?››ብልሽስ
‹‹አትልማ ..ለራስህ ያለህን ግምት በደንብ አውቃለው..››
<<እንዴት ነው ምታውቂው ….?በጣም ጉረኛ ነሽ…?ዘመድሽ መስለውኝ ነው..ደግሞ ደስ የሚሉ አዛውንት ናቸው.የሚያነብ ሰው እወዳለው ለዛ ነው…›› አልኩ ቀጥሎ በመሀከላችን ለሚፈጠረው ነገር ጥሩ ስሜት እንዲፈጠር ና ንግግራችን እንዳይከር እየፈራው
‹‹ ማን መሆናቸውን ታውቃለህ?››
‹‹እኔ እንጃ .በምን አውቃለው ፡፡ካለዛሬም አይቻቸው አላውቅም..እዚህ ቦታም ስገኝ የመጀመሪያ ቀኔ ነው››
እንግዲህ እንደዛ እንድታደርግ እድሉን ስላመቻቸውልህ አመስግነኝ…ምክንያቱም ለእሷቸው መፅሀፍ መግዛት ብዙ ሰዎች ቢፈልጉም እድሉን አያገኙምና›› ብላ ማንነታቸውን ነገረቺኝ… ነዘረኝ ከሰማዩ የሚከብድ ስም ያላቸው..ለኢትዬጵያ ብዙ የሰሩ ፤ ብዙ መጽሀፍ የጻፉ ታላቅ ደራሲ ናቸው..አፍሬ አፌን ያዝኩ.ማንነታቸውን ቀድሜ ባውቅ ኖሮ መፅሀፍ ልግዛሎት ብዬ ገንዘብ ከኪሴ ለማውጣት ድፍረት ሚኖረኝ አይመስለኝም
‹‹ስማቸው እና ኪሳቸው ምነው እንዲህ ተራራቀ.››ብዬ የገረመኝን ጥያቄ ጠየቅኳት
‹‹ስማቸውን እኮ በአዕምሮቸው እንጂ በኪሳቸው አይደለም ያገኙት…እሳቸው ለቁሳዊ ሀብት ብዙም ግድ የላቸውም ..ከሚጠቀሙት በላይ ገንዘብ ኪሳቸው እዲከርም አይፈልጉም..ግን አንዳንዴ እንደዛሬ ቀን የሚፈልጉት መፃሀፍ የሚገዙበት ብር ሲጎድላቸው ይበሳጫሉ..››ብላ ልታስረዳኝ ሞከረች፡፡
‹‹ሚገርም ፅናት ነው››አልኩኝ
‹‹ አዎ ነው..አንተ ግን ምን ፈልገህ እዚህ ድረስ መጣህ .?ነው እግረመንገድህን ስታልፍ ድንገት አይተኸኝ ነው?››አለችኝ ኮስተር ብላ..ሞባይሌን ከፈትኩና ሰዓቱን አየው..አምስት ሰዓት ከሩብ ይላል
‹‹ምሳ ልጋብዝሽ ነው አመጣጤ…ምሳ ስንት ሰዓት ነው መውጣት የሚፈቀድልሽ….?››
‹‹ምሳ ምሳ...?››
‹‹አዎ ምሳ..››
ስልኳን አወጣችና ደወለች…‹‹ቶሎ ና ልወጣ ነው…››ብላ መልሳ ዘጋችው…
‹‹የሚቀበለኝ ልጅ እስኪመጣ መኪና ውስጥ ጠብቀኝ ከአስር ደቂቃ ቡኃላ መጣለው››እንዲህ በቀላሉ እሺ ትለኛች ብዬ እልጠበቅኩም ነበር…ሀሳቧን እንዳትቀይር ‹‹እሺ አመሰግናለው›› ብዬ እንደህጻን በውስጤ እየቧረቅኩ በፍጥነት ወደ መኪናዬ ተመለስኩና መሪውን ከሹፌሬ ተቀብዬ እሱ በታክሲ ወደቢሮ እንዲመለስ ልኬው እሷን መጠበቅ ጀመርኩ…ስለእሷ እያሰብኩ…ስንት ሰው እንደሆነች እያሰላው...ከሳምንት በፊት እኛ ካምፓኒ ነበር የምትሰራው…ከዛ ሹፌር ሆና ስትሰራ አገኛዋት አሁን ደግሞ የመፃሀፍት መደብር ሻጭ..ህይወቷን እንዴት እዴት ነው ጢቢ ጢቢ እየተጫወተችበት ያለው.?መስመር የሚያሲዛት ቤተሰብ የላትም ማለት ነው….?እስቲ ትምጣና ለዚህ ሁሉ ጥያቄዎቼ መልስ ትሰጠኛለች….
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍስሀ
መፅሃፍ መደብሩ ቆሜያለሁ ነገረ ስራዋን በአትኩሮት እየተከታተልኩ ነው፡፡
ገዢው የሆነ መፃፍ ርዕስ ነገሯት
‹‹እንደዚህ የሚባል መጽሀፍ አለሽ.?››ጠየቃት
‹‹አለኝ ግን ለምን ፈለግከው?››
‹‹አልገባኝም?ልገዛሽ ነዋ.?››
‹‹እሱማ ልትገዛኝ ነው ?ለምን መጽሀፉን ልትገዛው ፈለክ ነው ጥያቄዬ?››
‹‹ለምንስ ብፈልገው አንቺ ምን ይመለከትሻል ?ካለሽ ሽጪልኝ ከሌለሽ የለኝም በይ››
‹‹ስኳር ወይ ሳሙና አይደለም የምትገዛው፤ መጽሀፍ ነው..፡፡መጽሀፍቶች ደግሞ ሳያነቡ የሚያነቡ ለመምሰል ታቅፈዋቸው የሚዞሩ ከንቱዎች እጅ እንዲገቡ አልፈልግም በተለይ እንደጠየቅከው ያለ መጽሀፍ……..፡፡ይሄውልህ እዛ አካባቢ በመደዳ መጽሀፍት ቤቶች አሉ ካላቸው ምክንያት ሳይጠይቁ ይሸጡልኸል….ደህና ሁን››ብላ አሰናበተችው፡፡
ሰውዬው በመገረም እያጉረመረመ ጥሏት ሄደ ..ዞር ስትል እኔን አየቺኝ
‹‹እንዴ አለቃ ምን እግር ጣለህ...?መፅሀፍ ልገዛሽ ነው እንዳትለኝ…?››አለች በመጠኑ ፈገግ ብላ
‹‹ለመሆኑ የትኛው የዋህ ነጋዴ ነው ለመክሰር አንቺን እዚህ ያቆመሽ….?››የእወነቴን ነበር የተናገርኩት
‹‹የሚተማመንብኝ››
‹‹እንዲ ደንበኛ እያበሳጨሽ እያባረርሽበት ነው የሚተማመንብሽ…››
ልትመልስልኝ አፎን ስታስተካክል አንድ ሽበት የወረራቸው ደስ የሚል ግርማ ሞገስ ያላቸው ግን ደግሞ ጎስቆል ያሉ አዛውንት ድምጽ በመሀከላችን ገባ ?››
‹‹ደህና ነሽ የእኔ አለም….?››
‹‹ደህና አደሩ..እንዴት ኖት? ጤናዎትስ?››እኔን ከማውቃት ተቃራኒ በሆነ እርብትብት ትህትና እየተፍለቀለቀች እና እየፈገገች በጋለ ሰላምታ ተቀበለቻቸው፡፡ሰው እንዴት እንዲህ ሁለት ገፃ ይኖረዋል?
‹‹….ሰላም ነኝ ልጄ…፡፡ይመስገነው፡፡››
‹‹አኔ እኮ ሲጠፉብኝ ያመሞት መስሎኝ ሰግቼ ነበር››
‹‹አይ ደህና ነኝ.ባለፈው ያስቀመጥሺልኝን መጽሀፍ ልጆቹ ሰጥተውኝ ወስጄ ነበር..እና መጻሀፎ ስለመሰጠቺኝ ከቤት መውጣት አልቻልኩም ለዛ ነው የጠፋሁብሽ››
‹‹ጨረሱት?››
‹‹ጨረሱት..ሁለት ጊዜ ነው ደግሜ ያነበብኩት…አሁንም አንዴ የምደግመው ይመስለኛል..››
‹‹ስለወደዱት ደስ ብሎኛል..አሁንም ያዘጋጀውሏት መጽሀፍ አለች›› ብላ ከተቆለሉት መጽሀፎቶች ጀርባ እጆን ሰደደችና አንድ ልባሱ አርጀት ያለ መጽሀፍት አውጥታ ሰጣቻቸው ፡፡በመንሰፍሰፍ ተቀበሏት እና ርዕሱን አገላብጠው ካነበብ ቡሃላ እሷን ወደ ራሳቸው ጎትተው ግንባሯን ከሳሟት ቡኃላ ‹‹ ስንትነው የእኔ ልጅ .?››ጠየቋት
‹‹ሁለት መቶ ሀምሳ ብር ነው የገዛውሎት››
ቀኝ የካፖርት ኪሳቸው ገቡ…የሆነ ባለአስር ብር ዝርዝር ብሮች አወጡ..የካፖርታቸውን ኪስ ከፈቱና ደረት ኪሳቸው ገቡ ሳንቲም ሳይቀር ያለቸውን ብር ከየኪሳቸው እያወጡ ባንኮኒው ላይ ዘረገፍት.በትኩረተ ስከታተላቸው ነበር…ቢቆጠር ከመቶ ምናንም ብር አይበልጥም ቢያንስ የጠየቀቻቸውን ግማሹን አይሸፍንም
‹‹ልጄ በዚህ ላይ አንቺ ሙይልኝ…››አሏት…የልመና ሳይሆን የትዕዛዝ ቃና ባለው የመተማመን ስሜት
‹‹.አይ ይሄ ልጅ የእርሶ አድናቂ ነው… ገና ሲመጡ አይቶት የሚወስዱትን መፃሀፍን እኔ ነኝ የምከፈለው.. አደራሽን እንዳተቀበያቸው ሲለኝ ነበር..አይደል ፍሰሀ?››አለቺኝ ወደእኔ ቀና ብላ አፍጥጣ እያየቺኝ
‹‹አዎ…እባኮት እልኩና ወደኪሴ ገብቼ ዋሌቴን በማውጣት በግምት አንድ ሺ ምናምን ብር ይመስለኛል አወጣውና ይሄው ብሩ የሚችለውን አይነት የሚፈልጉትን መጽሀፍ ስጭልኝ….››
<<አላልኮትም ››አለችና የእሳቸውን ብር ከባንኮኒው ሰብስባ ኪሳቸው መልሳ ጨመረችላቸውና…
‹‹ሌላ ምን ምን መፃሀፍ ነው የሚፈልጉት….?››
‹‹ያው የመጽሀፍ ምርጫዎቼን ታውቂ የለ.››
…ስድስት ወይም ሰባት የሚሆኑ መጻሀፎችን መረጠችና በፔስታል አድርጋ ሰጠቻቸው
ሰውዬው ከመሄዳቸው በፊት ወደእኔ ጠጋ አሉ..ብዙ ምርቃት እንደሚያዘንቡብኝ እየጠበቅኩ ነው…‹‹እነዚህን መፃሀፎች አንብቦ ለመጨረስ ሁለት ወር ያህል ይፈጅብኛል…ለቀጣዬቹ ሁለት ወራት እንድኖር የሚያስችል ምክንያት ሰጠተኸኛል ማለት ነው..ምክንያቱም እኔ በምንም አይነት ሁኔታ እጄ ላይ ያሉ መጽሀፎቸን አንብቤ ሳልጨርስ አልሞትምና.››አሉኝ ..ምን ለማለት እንደፈለጉ አልገባኝም..ይህቺ ልጅ ግራ አጋቢ የሆነችው ከእንደዚህ አይነት ግራ አጋቢ ብኩኖች ጋር እየኖረች ነው ስል በውስጤ አሰብኩ.. ሽማግሌው ወደፌናን ዞረው ‹‹የእኔ ትንሽ መላአክ ደህና ሰንብቺልኝ..››ብለው ፊታቸውን አዙረው የመጽሀፍ መደብሩን ለቀው ወጡ
‹‹ምትገርሚ እብድ ነሽ.ለማላውቃቸው ሰው መጽሀፍ ታስገዥኛለሽ…ደግሞ ባዋርድሽስ.?››
‹‹ምን ብለህ ነው የምታዋርደኝ.?››
<<መች አልኩሽ .?››ብልሽስ
‹‹አትልማ ..ለራስህ ያለህን ግምት በደንብ አውቃለው..››
<<እንዴት ነው ምታውቂው ….?በጣም ጉረኛ ነሽ…?ዘመድሽ መስለውኝ ነው..ደግሞ ደስ የሚሉ አዛውንት ናቸው.የሚያነብ ሰው እወዳለው ለዛ ነው…›› አልኩ ቀጥሎ በመሀከላችን ለሚፈጠረው ነገር ጥሩ ስሜት እንዲፈጠር ና ንግግራችን እንዳይከር እየፈራው
‹‹ ማን መሆናቸውን ታውቃለህ?››
‹‹እኔ እንጃ .በምን አውቃለው ፡፡ካለዛሬም አይቻቸው አላውቅም..እዚህ ቦታም ስገኝ የመጀመሪያ ቀኔ ነው››
እንግዲህ እንደዛ እንድታደርግ እድሉን ስላመቻቸውልህ አመስግነኝ…ምክንያቱም ለእሷቸው መፅሀፍ መግዛት ብዙ ሰዎች ቢፈልጉም እድሉን አያገኙምና›› ብላ ማንነታቸውን ነገረቺኝ… ነዘረኝ ከሰማዩ የሚከብድ ስም ያላቸው..ለኢትዬጵያ ብዙ የሰሩ ፤ ብዙ መጽሀፍ የጻፉ ታላቅ ደራሲ ናቸው..አፍሬ አፌን ያዝኩ.ማንነታቸውን ቀድሜ ባውቅ ኖሮ መፅሀፍ ልግዛሎት ብዬ ገንዘብ ከኪሴ ለማውጣት ድፍረት ሚኖረኝ አይመስለኝም
‹‹ስማቸው እና ኪሳቸው ምነው እንዲህ ተራራቀ.››ብዬ የገረመኝን ጥያቄ ጠየቅኳት
‹‹ስማቸውን እኮ በአዕምሮቸው እንጂ በኪሳቸው አይደለም ያገኙት…እሳቸው ለቁሳዊ ሀብት ብዙም ግድ የላቸውም ..ከሚጠቀሙት በላይ ገንዘብ ኪሳቸው እዲከርም አይፈልጉም..ግን አንዳንዴ እንደዛሬ ቀን የሚፈልጉት መፃሀፍ የሚገዙበት ብር ሲጎድላቸው ይበሳጫሉ..››ብላ ልታስረዳኝ ሞከረች፡፡
‹‹ሚገርም ፅናት ነው››አልኩኝ
‹‹ አዎ ነው..አንተ ግን ምን ፈልገህ እዚህ ድረስ መጣህ .?ነው እግረመንገድህን ስታልፍ ድንገት አይተኸኝ ነው?››አለችኝ ኮስተር ብላ..ሞባይሌን ከፈትኩና ሰዓቱን አየው..አምስት ሰዓት ከሩብ ይላል
‹‹ምሳ ልጋብዝሽ ነው አመጣጤ…ምሳ ስንት ሰዓት ነው መውጣት የሚፈቀድልሽ….?››
‹‹ምሳ ምሳ...?››
‹‹አዎ ምሳ..››
ስልኳን አወጣችና ደወለች…‹‹ቶሎ ና ልወጣ ነው…››ብላ መልሳ ዘጋችው…
‹‹የሚቀበለኝ ልጅ እስኪመጣ መኪና ውስጥ ጠብቀኝ ከአስር ደቂቃ ቡኃላ መጣለው››እንዲህ በቀላሉ እሺ ትለኛች ብዬ እልጠበቅኩም ነበር…ሀሳቧን እንዳትቀይር ‹‹እሺ አመሰግናለው›› ብዬ እንደህጻን በውስጤ እየቧረቅኩ በፍጥነት ወደ መኪናዬ ተመለስኩና መሪውን ከሹፌሬ ተቀብዬ እሱ በታክሲ ወደቢሮ እንዲመለስ ልኬው እሷን መጠበቅ ጀመርኩ…ስለእሷ እያሰብኩ…ስንት ሰው እንደሆነች እያሰላው...ከሳምንት በፊት እኛ ካምፓኒ ነበር የምትሰራው…ከዛ ሹፌር ሆና ስትሰራ አገኛዋት አሁን ደግሞ የመፃሀፍት መደብር ሻጭ..ህይወቷን እንዴት እዴት ነው ጢቢ ጢቢ እየተጫወተችበት ያለው.?መስመር የሚያሲዛት ቤተሰብ የላትም ማለት ነው….?እስቲ ትምጣና ለዚህ ሁሉ ጥያቄዎቼ መልስ ትሰጠኛለች….
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍2
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሦስት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
...ሆቴል ፍለጋ ብዙም አራቅንም ..እዛው ዞር ብለን ዋቤ ሸበሌ ነበር የገባነው…እንደተቀመጥን ነው የምንበላውን በማዘዝ ወደጭቅጭቃችን የገባነው…እኔን ፍለጋ ይሄን ያህል መንገድ ይጓዛል ብዬ አልገመትኩም ነበር…እርግጥ ነገሮችን በፍጥነት እንዲህ እንዲሆኑ አድርጌ ስልኬንም፤ አድራሻዬንም አጠፋፍቼ ከመስሪያ ቤቴ የጠፋውት አውቄ ነው …ለእሱ የማሰቢያ እና የመረጋጊያ ጊዜ እንዲያገኝ በማሰብ ….እንጂማ ስራዬን እሱ ስላለ መልቀቄ አይደለም..እንደዛማ አይታሰብም…ሰው በገዛ ግዛቱ ውስጥ በታነፀ ቤተመንግስት ሊነግስበት ያሰበውን ወንበር ሌላ ተቀናቃኝ ልቀቅ ስላለው በቀላሉ ይለቃል…አይ በፍፁም ይሄ የነገስታት ባህሪ አይደለም..እሱ በንግስናው ኃይል ተማምኖ ወግጂልኝ ቢለኝ እኔ በቀላሉ ምኞቱን ላሳካለት አልችልም..ምክንያቱም እኔም ከእሱ እኩል ኃይል ያለኝ ንግስት ስለሆንኩ…
‹‹እኔን ፍለጋ እንዲህ መባከንህ አስደስቶኛል››አልኩት
‹‹ጉረኛ አትሁኚ… ስለአንቺ አንዳንድ ነገር ሳጣራ ከበፊትም ጀመሮ በካምፓኒው አንቺን በተመለከተ ያለው ነገር ትክክል ስላልመሰለኝ ያንን ለማስተካከል ነው..የአንድ አዲስ መሪ ስራ የወደፊት የካምፓኒውን አካሄድ ማስተካከል ብቻ ሳይሆን ወደኃላም ተመልሶ በባለፍት መሪዎች አላግባብ የተሰሩ ስራዎች ካሉ ለእነዛ እርማት እንዲደረግ ማሰድረግም ጭምር ነው…
‹‹ስለመሪነት ጥሩ ግንዛቤ እያገኘህ ነው››
‹‹አዎ…አስተዳደግሽ፤ የቤተሰቦችሽ ሁኔታ እና የህይወት ገጠመኞችሽ የፈጠሩብሽ ተፅዕኖ እንዳለ ሆኖ ካምፓኒያችንም ላንቺ የሰጠው ቦታ ለህይወትሽ መበላሸት አንድ አስዋፅኦ እንዳበረከተ ተሰምቶኛል..እኔም ነገሩን በደነብ ሳላጣራ በእሳቱ ላይ ቤንዚል ጨመርኩበት››አለኝ እጆቹን እያፍተለተለ…አይገርማችሁም አንዳንድ ሰው ወደ ህይታችሁ ድንገት ከመንገድ ጎራ ብሎ ይገባና ገና በሁለት እግሩ እንኳን ተስተካክሎ ሳይቆም አፍርሼ ልስራችሁ ይላል፡፡
‹‹ያው ቸኩሎ መፍረድ የአንተ ብቻ ሳይሆን…የእኛ ኢትዬጵያውያን ዋና ችግር ነው.. ለወሬ ያለን ፍቅር ለራሳችን ካለን ፍቅር በብዙ እጥፍ ይበልጣል፡፡እንደህዝብ ብቻ ሳይሆን በከፍተኛ ደረጃ ተምረዋል በሚባሉት የህብረተሰብ ደረጃ ጨምር የ<critical thinking >ልምምድ የለንም… የሆነ ውሳኔ ላይ ከመድረሳችን በፊት የሰማነውን ወሬ ‹‹ለምን?›› ‹‹እንዴት?›› ‹‹የት?›› ‹‹ መቼ?›› ብለን በመጠየቅ የነገሩን ብልት በታትነን የማየት የምናደርገው ጥረት ለዜሮ የቀረበ ነው፡፡የሰማነውን ወሬ ወይም መረጃ በዚህ መጠን መመርመር ደግሞ የመረጃዎችን ጥራት ለመጨመር..እርግጠኝነቱን አስተማማኝ ለማድረግ እና እወነተኝነቱን በአስተማማኝ መንገድ ለማረጋገጥ ወሳኝ መንገዶች ናቸው፡፡ እኛ ግን እንደዛ አናደርግም…በዛም ምክንያት ውሳኔያችን ቡዙ ግዜ የጥድፊያና በስህተት የተሞላ ነው››አልኩት… ከገባው ብዬ
‹‹አዎ ትክክል ነሽ››አለኝ ኮራና ጀነን ብሎ
‹‹አየህ አሁንም ተሳሳትክ..ትክክል መሆኔን እንዴት በዚህ ቅፅበት ልታረጋግጥ ቻልክ….?››
ግራ ገባውና ‹‹ማለቴ….››ብሎ ሊያብራራልኝ ሲሞክር መልሼ ጣልቃ ገባውና
‹‹ግዴለም ብታስረዳኝም አታሳምነኝም..ይልቅ ህይወቴ እንደተበላሸ ስትናገር ነበር…እስቲ እንዴት እንዲያ ልታስብ እንደቻልክ አስረዳኝ..….?››
‹‹ይሄ ምን ማስረዳት ያስፈልገዋል…በዛ ነጥብ ዲግሪ ተመርቀሽ በትንሽ ደሞዝ በፀሀፊነት እየሰራሽ ነው..በቀደም አያትሽ ከሚሆን ሰው ጋር አግኝቼሻለው…ዛሬ ደግሞ ተራ የሽያጭ ሰራተኛ ሆነሽ መጽሀፍ ስትቸረችሪ ነው ያገኘውሽ…ህይወትሽ እርጋታ የሌለው ምስቅልቅሉ የወጣ ነው….ከዚህ በላይ የህይወት መበለሻሸት ከየት ይመጣል››በቃ በእሱ ቤት የእኔን ህይወት ብጥርጥር አድርጎ አጥንቶ ጨርሶል..
‹‹እውነት ግን ምንድነው ….?››ጠየቅኩት
ግራ ተጋባ‹‹….ምን አልሺኝ….?››
‹‹እውነት ምንድነው..….?››ፍጥጥ ብዬ ጥያቄዬን ደገምኩለት
‹‹ምን አይነት ጥያቄ ነው….….?እውነት ሀቅ ነው…በትክክል የተተገበረ ወይም የተነገረ ክንውን ነው..በቃ ይሄው ነው፡፡››
‹‹እሱ ብቻማ አይደለም…እውነት እረቂቅ ነው..እውነት ጥልቅ ነው…የሰማህው ነገር ሁሉ እውነት ሊሆን አይችልም..ለምን ይመስልሀል እኔ እና አንተ አንድ አይነት ነገር ከአንድ ሰው በእኩል ሰዓት ብንሰማ የምንረዳበት መንገድ አንድ አይነት ሊሆን አይችልም…ምክንያም ሁለታችንም በየራሳችን አዕምሮ ተጠቅመን ነው ተርጉመን ነገሩን ለመገንዘብ የምንጥረው…..ስንተረጉም ደግሞ የበፊት የህይወት ልምዳችን..የምንከተለው የሀይማኖት አይዲኦሎጂ፤ ከተወለድንበት አካባቢ ማህበረሰብ የቀሰምነው ባህል፤ የራሳችን ፍላጎት…..እነዚህና ሌሎችም በአተረጋጎማችን ላይ የየራሳቸውን ስውር ተፅዕኖ ያሳድራብናል…… የሰማነው እውነት በግማሽ ይበረዛል ማለት ነው…ያየነውም እንደዛ..፡፡ሌላ ምሳሌ ልስጥህ የአንድ ወጣት ልጃገረድ ፎቶን ሶስት ወጣት ወንዶች ቢያዩት እና ከሳዕታት ቡኃላ ምን እንዳዩ ቢጠየቁ..አንድ የተቀሰረ አስጎሚዥ ጡቶች ያላት ወጣት ይልሀል…ሌላው የሚያምረ መቀመጫ ያላት ሞዴል መሆን የምትችል ወጣት ይልሀል…ሌላው ደግሞ የሚያምር ቁንጅና ያላት ግን ልቧ በሀዘን የተሰበረ፤የእኔ ያለችውን ነገር በመጠበቅ በናፍቆ እየተሰቃየች መሆኖን አይኖቾ ውስጥ ያጋቱት እናባዋ የሚመሰክሩ ፤ ግን ደግሞ ያልሸነፍ ባይነት እና የራስን ስሜት የመቆጣጠር ጥረት በፊቷ ላይ የሚነበብባት፤ከዕድሜዋ በላይ የምታውቅ ወጣት ነች ይላል፡፡አየህ ሶስቱንም አስተያየት ሰጪዎች አንድ አይነት ስዕል ከአንድ አይነት እርቀት ላይ አይተው የተረዱት ነገር የተለያየ ነው፡፡እውነቱ የማናኛቸው ነው…….?አየህ እውነት እንደሽንኩርት ነው ሚባለው ለዛ ነው…በላጥከው ቁጥር ሌላ አዲስ ነገር..አሁንም ስትልጠው ሌላ ሚስጥር…..አንዳንዴማ ማብቂያ ሁሉ ላይኖረው ይችላል….ጲላጦስ እኮ እኔ ማውቀው አለማወቄን ነው ያለውም አንድም ለዛ ነው….ያወቀ የመሰለው ሁሉ እሱ ገና ጀማሪ ተማሪ ነው….
‹‹ወይ አንቺ ልጅ…እያወራን የነበረውን ቁም ነገር እኮ አወሳስበሽ ድራሹን አጠፋሽው….››
‹‹አይ አሁን ያወራውት ነው ትክክለኛው ቁም ነገር….አየህ የእኔ ህይወት ብልሽትሽት ማለቱን ለመወሰን በአንድ ሰምንት ውስጥ ያየሀቸው ወይም የሰማሀቸው ቅንጭብጫቢ ታሪኮች ላንተ በቂዎች መሆናቸው አስገራሚ ነው››
‹‹እኛ ካምፓኒ በፀሀፊነት እንደምትሰሪ ማንም ተናገረው ማንም እውነት ነው…..በቢዝነስ ማነጅመንት ዲግሪ እንዳለሽም አንቺ እራስሽ አትክጂም…ሹገር ዳዲሽንም በአይኔ ነው ያየውት››
በዚህ ጊዜ ምግቡ ቀርቦልን እየበላን ነበር እያወራን ያለነው..ሁሉን ነገር ጨርሶ ሳያውቅ እንደአወቀ የሚያወራው ነገር ብሽቅ አደረገኝ ‹‹ሌላውን ተወው ….ሹገር ዳዲዬ መሆኑን በምን አረጋገጥክ…….?››
‹‹አይቼሻለው አልኩሽ እኮ..አንቺም አረጋግጠሽልኛል…››
‹‹ዋሽቼህ ቢሆንስ…….?››
‹‹በምን ምክንያት ትወሺኛለሽ ….?››
‹‹ላስቀናህ ፈልጌ››
ሳቁን ለቀቀው…
‹‹ምን ያስቅሀል….?››
‹‹ለምን ብዬ ቀናለው…አፈቅሬሽ ነበር እንዴ….?››
‹‹እኔ እንጃ… ሰው አንድ ሰውን ላይ ካለምክንያት ትኩረት ካደረገና ምክንያት እየፈለገ ጥዋትና ቀን የሚነጫነጭበት ከሆነ ያው በእኔ ግምት ፍቅር ነው ብዬ ነው የማስበው፡፡››
‹‹እንደ ህይወትሽ ለራስሽ ያለሽ ግምት የተዘበራረቀ ነው…አንዳዴ መሬት የሚወረድ ሌላ ጊዜ ደግሞ ሰማይ ላይ ልንጠልጠል የሚል…›› አለኝ …በመበሳጨትና ስሜቱን ለመቆጣጠር በሚጥር የስሜት መደበላለቅ
‹‹እሺ ተሳስቼ ይሆናል..ለምን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሦስት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
...ሆቴል ፍለጋ ብዙም አራቅንም ..እዛው ዞር ብለን ዋቤ ሸበሌ ነበር የገባነው…እንደተቀመጥን ነው የምንበላውን በማዘዝ ወደጭቅጭቃችን የገባነው…እኔን ፍለጋ ይሄን ያህል መንገድ ይጓዛል ብዬ አልገመትኩም ነበር…እርግጥ ነገሮችን በፍጥነት እንዲህ እንዲሆኑ አድርጌ ስልኬንም፤ አድራሻዬንም አጠፋፍቼ ከመስሪያ ቤቴ የጠፋውት አውቄ ነው …ለእሱ የማሰቢያ እና የመረጋጊያ ጊዜ እንዲያገኝ በማሰብ ….እንጂማ ስራዬን እሱ ስላለ መልቀቄ አይደለም..እንደዛማ አይታሰብም…ሰው በገዛ ግዛቱ ውስጥ በታነፀ ቤተመንግስት ሊነግስበት ያሰበውን ወንበር ሌላ ተቀናቃኝ ልቀቅ ስላለው በቀላሉ ይለቃል…አይ በፍፁም ይሄ የነገስታት ባህሪ አይደለም..እሱ በንግስናው ኃይል ተማምኖ ወግጂልኝ ቢለኝ እኔ በቀላሉ ምኞቱን ላሳካለት አልችልም..ምክንያቱም እኔም ከእሱ እኩል ኃይል ያለኝ ንግስት ስለሆንኩ…
‹‹እኔን ፍለጋ እንዲህ መባከንህ አስደስቶኛል››አልኩት
‹‹ጉረኛ አትሁኚ… ስለአንቺ አንዳንድ ነገር ሳጣራ ከበፊትም ጀመሮ በካምፓኒው አንቺን በተመለከተ ያለው ነገር ትክክል ስላልመሰለኝ ያንን ለማስተካከል ነው..የአንድ አዲስ መሪ ስራ የወደፊት የካምፓኒውን አካሄድ ማስተካከል ብቻ ሳይሆን ወደኃላም ተመልሶ በባለፍት መሪዎች አላግባብ የተሰሩ ስራዎች ካሉ ለእነዛ እርማት እንዲደረግ ማሰድረግም ጭምር ነው…
‹‹ስለመሪነት ጥሩ ግንዛቤ እያገኘህ ነው››
‹‹አዎ…አስተዳደግሽ፤ የቤተሰቦችሽ ሁኔታ እና የህይወት ገጠመኞችሽ የፈጠሩብሽ ተፅዕኖ እንዳለ ሆኖ ካምፓኒያችንም ላንቺ የሰጠው ቦታ ለህይወትሽ መበላሸት አንድ አስዋፅኦ እንዳበረከተ ተሰምቶኛል..እኔም ነገሩን በደነብ ሳላጣራ በእሳቱ ላይ ቤንዚል ጨመርኩበት››አለኝ እጆቹን እያፍተለተለ…አይገርማችሁም አንዳንድ ሰው ወደ ህይታችሁ ድንገት ከመንገድ ጎራ ብሎ ይገባና ገና በሁለት እግሩ እንኳን ተስተካክሎ ሳይቆም አፍርሼ ልስራችሁ ይላል፡፡
‹‹ያው ቸኩሎ መፍረድ የአንተ ብቻ ሳይሆን…የእኛ ኢትዬጵያውያን ዋና ችግር ነው.. ለወሬ ያለን ፍቅር ለራሳችን ካለን ፍቅር በብዙ እጥፍ ይበልጣል፡፡እንደህዝብ ብቻ ሳይሆን በከፍተኛ ደረጃ ተምረዋል በሚባሉት የህብረተሰብ ደረጃ ጨምር የ<critical thinking >ልምምድ የለንም… የሆነ ውሳኔ ላይ ከመድረሳችን በፊት የሰማነውን ወሬ ‹‹ለምን?›› ‹‹እንዴት?›› ‹‹የት?›› ‹‹ መቼ?›› ብለን በመጠየቅ የነገሩን ብልት በታትነን የማየት የምናደርገው ጥረት ለዜሮ የቀረበ ነው፡፡የሰማነውን ወሬ ወይም መረጃ በዚህ መጠን መመርመር ደግሞ የመረጃዎችን ጥራት ለመጨመር..እርግጠኝነቱን አስተማማኝ ለማድረግ እና እወነተኝነቱን በአስተማማኝ መንገድ ለማረጋገጥ ወሳኝ መንገዶች ናቸው፡፡ እኛ ግን እንደዛ አናደርግም…በዛም ምክንያት ውሳኔያችን ቡዙ ግዜ የጥድፊያና በስህተት የተሞላ ነው››አልኩት… ከገባው ብዬ
‹‹አዎ ትክክል ነሽ››አለኝ ኮራና ጀነን ብሎ
‹‹አየህ አሁንም ተሳሳትክ..ትክክል መሆኔን እንዴት በዚህ ቅፅበት ልታረጋግጥ ቻልክ….?››
ግራ ገባውና ‹‹ማለቴ….››ብሎ ሊያብራራልኝ ሲሞክር መልሼ ጣልቃ ገባውና
‹‹ግዴለም ብታስረዳኝም አታሳምነኝም..ይልቅ ህይወቴ እንደተበላሸ ስትናገር ነበር…እስቲ እንዴት እንዲያ ልታስብ እንደቻልክ አስረዳኝ..….?››
‹‹ይሄ ምን ማስረዳት ያስፈልገዋል…በዛ ነጥብ ዲግሪ ተመርቀሽ በትንሽ ደሞዝ በፀሀፊነት እየሰራሽ ነው..በቀደም አያትሽ ከሚሆን ሰው ጋር አግኝቼሻለው…ዛሬ ደግሞ ተራ የሽያጭ ሰራተኛ ሆነሽ መጽሀፍ ስትቸረችሪ ነው ያገኘውሽ…ህይወትሽ እርጋታ የሌለው ምስቅልቅሉ የወጣ ነው….ከዚህ በላይ የህይወት መበለሻሸት ከየት ይመጣል››በቃ በእሱ ቤት የእኔን ህይወት ብጥርጥር አድርጎ አጥንቶ ጨርሶል..
‹‹እውነት ግን ምንድነው ….?››ጠየቅኩት
ግራ ተጋባ‹‹….ምን አልሺኝ….?››
‹‹እውነት ምንድነው..….?››ፍጥጥ ብዬ ጥያቄዬን ደገምኩለት
‹‹ምን አይነት ጥያቄ ነው….….?እውነት ሀቅ ነው…በትክክል የተተገበረ ወይም የተነገረ ክንውን ነው..በቃ ይሄው ነው፡፡››
‹‹እሱ ብቻማ አይደለም…እውነት እረቂቅ ነው..እውነት ጥልቅ ነው…የሰማህው ነገር ሁሉ እውነት ሊሆን አይችልም..ለምን ይመስልሀል እኔ እና አንተ አንድ አይነት ነገር ከአንድ ሰው በእኩል ሰዓት ብንሰማ የምንረዳበት መንገድ አንድ አይነት ሊሆን አይችልም…ምክንያም ሁለታችንም በየራሳችን አዕምሮ ተጠቅመን ነው ተርጉመን ነገሩን ለመገንዘብ የምንጥረው…..ስንተረጉም ደግሞ የበፊት የህይወት ልምዳችን..የምንከተለው የሀይማኖት አይዲኦሎጂ፤ ከተወለድንበት አካባቢ ማህበረሰብ የቀሰምነው ባህል፤ የራሳችን ፍላጎት…..እነዚህና ሌሎችም በአተረጋጎማችን ላይ የየራሳቸውን ስውር ተፅዕኖ ያሳድራብናል…… የሰማነው እውነት በግማሽ ይበረዛል ማለት ነው…ያየነውም እንደዛ..፡፡ሌላ ምሳሌ ልስጥህ የአንድ ወጣት ልጃገረድ ፎቶን ሶስት ወጣት ወንዶች ቢያዩት እና ከሳዕታት ቡኃላ ምን እንዳዩ ቢጠየቁ..አንድ የተቀሰረ አስጎሚዥ ጡቶች ያላት ወጣት ይልሀል…ሌላው የሚያምረ መቀመጫ ያላት ሞዴል መሆን የምትችል ወጣት ይልሀል…ሌላው ደግሞ የሚያምር ቁንጅና ያላት ግን ልቧ በሀዘን የተሰበረ፤የእኔ ያለችውን ነገር በመጠበቅ በናፍቆ እየተሰቃየች መሆኖን አይኖቾ ውስጥ ያጋቱት እናባዋ የሚመሰክሩ ፤ ግን ደግሞ ያልሸነፍ ባይነት እና የራስን ስሜት የመቆጣጠር ጥረት በፊቷ ላይ የሚነበብባት፤ከዕድሜዋ በላይ የምታውቅ ወጣት ነች ይላል፡፡አየህ ሶስቱንም አስተያየት ሰጪዎች አንድ አይነት ስዕል ከአንድ አይነት እርቀት ላይ አይተው የተረዱት ነገር የተለያየ ነው፡፡እውነቱ የማናኛቸው ነው…….?አየህ እውነት እንደሽንኩርት ነው ሚባለው ለዛ ነው…በላጥከው ቁጥር ሌላ አዲስ ነገር..አሁንም ስትልጠው ሌላ ሚስጥር…..አንዳንዴማ ማብቂያ ሁሉ ላይኖረው ይችላል….ጲላጦስ እኮ እኔ ማውቀው አለማወቄን ነው ያለውም አንድም ለዛ ነው….ያወቀ የመሰለው ሁሉ እሱ ገና ጀማሪ ተማሪ ነው….
‹‹ወይ አንቺ ልጅ…እያወራን የነበረውን ቁም ነገር እኮ አወሳስበሽ ድራሹን አጠፋሽው….››
‹‹አይ አሁን ያወራውት ነው ትክክለኛው ቁም ነገር….አየህ የእኔ ህይወት ብልሽትሽት ማለቱን ለመወሰን በአንድ ሰምንት ውስጥ ያየሀቸው ወይም የሰማሀቸው ቅንጭብጫቢ ታሪኮች ላንተ በቂዎች መሆናቸው አስገራሚ ነው››
‹‹እኛ ካምፓኒ በፀሀፊነት እንደምትሰሪ ማንም ተናገረው ማንም እውነት ነው…..በቢዝነስ ማነጅመንት ዲግሪ እንዳለሽም አንቺ እራስሽ አትክጂም…ሹገር ዳዲሽንም በአይኔ ነው ያየውት››
በዚህ ጊዜ ምግቡ ቀርቦልን እየበላን ነበር እያወራን ያለነው..ሁሉን ነገር ጨርሶ ሳያውቅ እንደአወቀ የሚያወራው ነገር ብሽቅ አደረገኝ ‹‹ሌላውን ተወው ….ሹገር ዳዲዬ መሆኑን በምን አረጋገጥክ…….?››
‹‹አይቼሻለው አልኩሽ እኮ..አንቺም አረጋግጠሽልኛል…››
‹‹ዋሽቼህ ቢሆንስ…….?››
‹‹በምን ምክንያት ትወሺኛለሽ ….?››
‹‹ላስቀናህ ፈልጌ››
ሳቁን ለቀቀው…
‹‹ምን ያስቅሀል….?››
‹‹ለምን ብዬ ቀናለው…አፈቅሬሽ ነበር እንዴ….?››
‹‹እኔ እንጃ… ሰው አንድ ሰውን ላይ ካለምክንያት ትኩረት ካደረገና ምክንያት እየፈለገ ጥዋትና ቀን የሚነጫነጭበት ከሆነ ያው በእኔ ግምት ፍቅር ነው ብዬ ነው የማስበው፡፡››
‹‹እንደ ህይወትሽ ለራስሽ ያለሽ ግምት የተዘበራረቀ ነው…አንዳዴ መሬት የሚወረድ ሌላ ጊዜ ደግሞ ሰማይ ላይ ልንጠልጠል የሚል…›› አለኝ …በመበሳጨትና ስሜቱን ለመቆጣጠር በሚጥር የስሜት መደበላለቅ
‹‹እሺ ተሳስቼ ይሆናል..ለምን
👍1
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
‹‹ሁለተኛው ቢሮ በሰራተኛ አስተዳደር አንድ ኤክስፐርት ለመቅጠር ይፈልጋሉ…እዛ ቦታ እንድታመለክቺ ልመክርሽ ነው…››
‹‹እንዴ!!! በስነምግባር ጉድላት ከስራው የተባረረ ሰው እኮ መልሶ መዋዳደር እንደማይችል ይታወቃል..ለዛውም ከበፊቱ ከፋ ባለ የስራ መደብ….?››
‹‹ግድ የለሽም በማነጅመንት እናየዋለን…ያ ውሰኔ የእኔ የግሌ ነበር..እንደውም ባንቺ መባረር ማናጅመንቱ ብዙም ምቾት አልተሰማቸውም..ስለዚህ አንቺን ለመመለስ ብዙም አያንገራንግሩም..››
‹‹አንተስ.?››አልኩት በብልጣ ብልጥነቱ ተደምሜ..
‹‹እኔ ድምፀ-ተአቅቦ አደርጋለው….በእነሱ ድምጽ መልሰሽ በሚገባሽ ቦታ ትቀጠሪያለሽ..ህይወትሽ ይስተካከላል….ግን ቅድመ ሁኔታ አለው››
‹‹ምን ?የፍቅር ጥያቄ እንዳይሆን››
‹‹ቢሆንስ?››አለኝ ፊቱን ጨምድዶ
‹‹አይ እንቢ ስለማልልህ ይቅርብህ ልልህ ነው››
በግርምት አፍጥጦ ለደቂቃዎች አየኝና ‹‹እያስፈራራሺኝ ነው…….?››
ማስፈራራት አይደለም.. ለእኔ ፍቅር ማለት መላላስ እና መወሳሰብ አይደለም…ሁሌ አድቬንቸር ነው…ሁሌ ሚተረመመስ ነገር ፈልጋለው…››
‹‹ግን .ጤነኛ አዕምሮ ነው ያለሽ...?እንዴት ሰው የሚተረማመስ ነገር ያስደስተዋል.?››
‹‹አየህ የተረማመሰውን ነገር በጥበብ ሳስተካክል የሚሰማኝ የአሸናፊነት እና የውጤታማነት ደስታ ነው የፍቅር እርካታዬ…ሁል ጊዜ በፍቅር ውስጥ ጌም እንዲኖር እፈልጋለው…ላሸንፍም ልሸነፍም እችላለው..ዋናው ሁል ጊዜ ምጫወተውን ማጣት የለብኝም …ጥሩ ቁማርተኛ ካልሆንክ ከአኔ ጋር በፍቅር መዝለቅ አትችልም እና ይቅርብህ ብዬ ልመክርህ ነው፡፡››
‹‹ምን ጉድ ነሽ በፈጣሪ…እኔ ቅድመ ሁኔታ ያልኩት አንድ ከዛ ከሹገር ዳዲሽ ጋር ያለሽን ፍቅርም ሆነ የስራ ግንኙነት ታቆሚያለሽ ልልሽ ነው..ሌላው እዚህ መፃሀፍት መደብርም ያለሽን ስራ እንደዛው….
‹‹ያስቃል..››አልኩት..እውነትም ገርሞኝ
‹‹ምኑ ገረመሽ?››
‹‹በዚህ ምድር ላይ ሶስት አይነት ሰዎች አሉ .. givers , takers , matcher ይባላሉ፡፡ < givers > ምንም ነገር ሲሰጡህ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ነው…ሲያፈቅሩህ የእነሱን ማፍቀር ብቻ እንጂ የእነሱን መፈቀር አለመፈቅር አያስጨንቃቸውም..ሲለግሱህም ከአንተ በመልሱ ምንም የሚጠብቁት ነገር የለም…እንደዚህ አይነት ሰዎች የአለም በጣም ደሀ ሰዎች ሊሆኑ ይችላሉ ግን ሰማያዊ ስብዕና ያላቸው ናቸው… በተቃራኒውም የአለም በጣም ሀብታሞቹና ባለትልቅ ገቢ ባለቢቶችም እንዚሁ < givers > የሚባሉ ሰዎች ናቸው..ምክንያቱም ለአበባ ያደረጉት በእጥፍ ከሰለሞን ይደረግላቸዋል…ይሄ የተፈጥሮ ህግ ነዋ፡፡‹‹ለማታውቀው ወገንህ አንድ ስትሰጥ ከማታቀው ዘጠኝ ተጭምሮ አስር ሆኖ ይመለሰልሀል…›› የሚለው ዋና መመሪያቸው ነው..እነእየሱስ ፤ ነብዩ ሙሀመድ፤እነማዘር ትሬዛ..እነአበበች ጎበና እነሲስተር ዘቢደር፤ማህተመጋንዲ፤ማንዴላ ወዘተ …እነዚህ ዝም ብለው በነፃ ሲሰጡ በመኖራቸው ሀብታምነትን ብቻ ሳይሆን በታሪክ ማህደር ዘላለማዊነትንም የተጎናፀፈ ናቸው….
ሌላው‹‹ takers› የሚባሉት ናቸው …ከሌላው መቀበልን ብቻ ነው ዓላማ አድርገው የሚንቀሳቀሱት..ሁሌ ማትረፍን ብቻ ነው የሚያስቡት…ለእነሱ ዋናው ውጤት ነው …ምን ያህል አተርፋለው እንጂ በእኔ ማትረፍ ውስጥ እነማን ይጎዳሉ… ?የማን ቤት ይፈርሳል..?የማን ነፍስ ይነጠቃል ?አያስጨንቃቸውም..፡፡የአለም ሙሰኞች፤ ኮንትሮባንዲስቶች፤ቅጥረኛ ነፍስ ገዳዬች… ሀሺሽ ነጋዴዎች እዚህ ግሩፕ ውስጥ ይጠቃለላሉ..
ሶስተኛዎቹ ‹matcher› የሚባሉት ናቸው፡፡በሰጡት ልክ መቀበልን ይፈልጋሉ….ሁል ጊዜ በህይወት ሚዛን እየጠበቁ መጓዝ ዓላማቸው ነው…ዲፕሎማቶች ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ናቸው…‹በሰጥቶ መቀበል መርህ› የሚጓዙ ናቸው… በዚህ ህግ ስትሰጥ በተሻለ መጠን እንደምትቀበል እርግጠኛ መሆን አለብህ››.እከክልኝ ልከክልህ…መመሪያቸው ነው፡፡
‹‹እና እኔ ከሶስቱ የትኛው ነኝ.?››አለኝ
‹‹እራስህን ፈልገዋ….አሁን ይብቃን እንሂድ….››
‹‹ስላልኩሽ ነገር እኮ ምንም አላልሺኝም...?››
‹‹እየሄድን መኪና ውስጥ ነገርሀለው….››
‹‹እሺ ››ብሎ ሂሳብ ሊከፍል አስተናጋጁን ደረሰኝ ሲጠይቀው..እንደተከፈለ ነገረው…
‹‹ማን ነው የከፈለው...?››አይን አይኔን እያየ ባለማመን ጠየቀኝ..የእኔም ጥያቄ ስለነበረ ልመልስለት አልቻልኩም
‹‹እዛ ጥግ ተቀምጦ የነበረው ሰውዬ ጥቁር ሱፍ ለብሶ የነበረው ..›› አስተናጋጁ አብራራልን
‹‹ማነው አውቀሺዋል….?››
‹‹አዎ፡፡ ተነስ እንሄድ በቃ…የእኔ ሰው ነው››አልኩት…
የአይኖቹ ቀለማት ሲቀየሩ ታወቀኝ
‹‹ምንድነው እንዲህ አይነት ነገር… ሰው በሰው ነገር እንዲህ ጥልቅ ሲል ሲያበሳጨኝ ..ከፈለገ ሌላ ቀን አይጋብዝሽም.?…››ይሄንን እጃችንን ታጥበን ከሆቴሉ እየወጣን በነበረበት ጊዜ ነው የሚነጫነጭብኝ..
‹‹ ምንድነው የደበረህ ….?ይክፈል…እንደውም ጥሩ ነው››
‹‹ለምን ይከፍላል .?አሁን አራት መቶ የማትሞላ ብር ከፈለ አልከፈለ ለእኔ ምኑ ነው ጥሩ…ጉረኛ በይው…››
ሁሉን ነገር ከማሸነፍና ከመሸነፍ ጋር የሚያገናኝ ምን አይነት ሰው ነው… .?አሁን አበሳጨኝ ‹‹እውነትህን ነው….እንደውም ብሩን ስጠኝ ልመልስለት…››አልኩት
ፈገግ አለ..‹‹የት ታገኚዋለሽ ወጥቷል እኮ››
‹‹አይ ያ ፊት ለፊት ያለው ብቲክ የእሱ ነው.. ስጠኝና አፍንጫው ላይ ወርውሬለት ልምጣ..ነገ ይሄንን እንደውለታ ቆጥሮ ሊለፋደድብኝ ይችላል››
ጥርስ በጥርስ ሆነ‹‹ ..በደስታ ብሩን አውጥቶ ሰጠኝ..‹‹ጠብቀኝ ››አልኩና አስፓልት ጠርዝ ላይ አቁሜው በዝብራ ተሸገርኩና ሁለት ልጆች ታቅፋ ለምትለምን ለማኝ እጆ ላይ አስጨበጥኮት ሴትዬዋ መብረቅ እንደመታት አይነት በድንጋጤ ፈዛ ለመጮህም ዳድቶት ስትርበተበት ፊቴን አዞርኩና መልሼ አስፓልቱን ተሸግሬ ወደእሱ ስሄድ እያጨበጨበ ጠበቀኝ …ሁኔታው የብሽቀት ነው…‹‹ጀግና ነሽ… ሸወድሽኝ ማለት ነው››አለኝ ለንቦጩን ጥሎ
‹‹አይ አልሸወድኩህም..አሁን ጋብዘኸኛል ማለት ነው….ስለዚህ ዘና ማለት ትችላለህ›› አልኩት
‹‹ግን ታውቂያለሽ አይደል …በጣም እብድ ልጅ ነሽ…የምትገርሚ እብድ…ነይ በይ ላድርስሽ..››
‹‹አይ.. አንተ በዚሁ ሄድ እኔ በዚች ጋ አቋራጬ መንገድ አለች …በዛ ሄዳለው.››
‹‹አረ ችግር የለም አደርስሻለው..››
‹‹ለራሴው ነው..በዚህ አቋራጭ አምስት ደቂቃ ነው የሚፈጅብኝ..አንተ ግን ገና መብራት ጠብቀህ አደባባይ ዞረህ 30 ደቂቃም አይበቃ..››
‹‹ይሁን ግን መልሱን አልነገርሺኝም እኮ...?››
‹‹እ እረሳውት ነገ 12 ሰዓት አይደል መነሻው ..እመጣለው..አንተም ባትለኝ ያ ፕሮግራም እንዲያመልጠኝ አልፈልግም››
‹‹ጥሩ ነው ስራውን ደግሞ ካዛ ስንመለስ ሰኞ ታመለክቺያለሽ..››
‹‹አይ አላመለክትም ቅዳሜ ወይም እሁድ እዛ ዝግጅቱ ላይ ሁሉም ሰራተኞች ባሉበት እኔን በተመለከተ በተሳሳተ መረጃ በማባረርህ ስህተት መስራትህን ተናግረህ ይቅርታ ትጠይቀኛለህ..ከዛ ሞራሌን በመንካትህ ለመካስ ይሄ ያልከኸውን አዲስ ቦታ በእድገት እንደሰጠኸኝ ለሁሉም ታበስራለህ….አንተ ራስህ እንደዛ ታደርጋለህ…እንደዛ ሲሆን ነው ሁሉ ነገር ተፈታ የሚባለው ከዛ እንዳልከው ስለሹገር ዳዲዬ እና ሰለ መፃሀፍ መደብሩ እናወራለን በል ቻው ››እልኩና ምንም እንዲናገር ዕድሉን ሳልሰጠው ፈዞ በደነዘዘበት ጥዬው ሄድኩ
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
‹‹ሁለተኛው ቢሮ በሰራተኛ አስተዳደር አንድ ኤክስፐርት ለመቅጠር ይፈልጋሉ…እዛ ቦታ እንድታመለክቺ ልመክርሽ ነው…››
‹‹እንዴ!!! በስነምግባር ጉድላት ከስራው የተባረረ ሰው እኮ መልሶ መዋዳደር እንደማይችል ይታወቃል..ለዛውም ከበፊቱ ከፋ ባለ የስራ መደብ….?››
‹‹ግድ የለሽም በማነጅመንት እናየዋለን…ያ ውሰኔ የእኔ የግሌ ነበር..እንደውም ባንቺ መባረር ማናጅመንቱ ብዙም ምቾት አልተሰማቸውም..ስለዚህ አንቺን ለመመለስ ብዙም አያንገራንግሩም..››
‹‹አንተስ.?››አልኩት በብልጣ ብልጥነቱ ተደምሜ..
‹‹እኔ ድምፀ-ተአቅቦ አደርጋለው….በእነሱ ድምጽ መልሰሽ በሚገባሽ ቦታ ትቀጠሪያለሽ..ህይወትሽ ይስተካከላል….ግን ቅድመ ሁኔታ አለው››
‹‹ምን ?የፍቅር ጥያቄ እንዳይሆን››
‹‹ቢሆንስ?››አለኝ ፊቱን ጨምድዶ
‹‹አይ እንቢ ስለማልልህ ይቅርብህ ልልህ ነው››
በግርምት አፍጥጦ ለደቂቃዎች አየኝና ‹‹እያስፈራራሺኝ ነው…….?››
ማስፈራራት አይደለም.. ለእኔ ፍቅር ማለት መላላስ እና መወሳሰብ አይደለም…ሁሌ አድቬንቸር ነው…ሁሌ ሚተረመመስ ነገር ፈልጋለው…››
‹‹ግን .ጤነኛ አዕምሮ ነው ያለሽ...?እንዴት ሰው የሚተረማመስ ነገር ያስደስተዋል.?››
‹‹አየህ የተረማመሰውን ነገር በጥበብ ሳስተካክል የሚሰማኝ የአሸናፊነት እና የውጤታማነት ደስታ ነው የፍቅር እርካታዬ…ሁል ጊዜ በፍቅር ውስጥ ጌም እንዲኖር እፈልጋለው…ላሸንፍም ልሸነፍም እችላለው..ዋናው ሁል ጊዜ ምጫወተውን ማጣት የለብኝም …ጥሩ ቁማርተኛ ካልሆንክ ከአኔ ጋር በፍቅር መዝለቅ አትችልም እና ይቅርብህ ብዬ ልመክርህ ነው፡፡››
‹‹ምን ጉድ ነሽ በፈጣሪ…እኔ ቅድመ ሁኔታ ያልኩት አንድ ከዛ ከሹገር ዳዲሽ ጋር ያለሽን ፍቅርም ሆነ የስራ ግንኙነት ታቆሚያለሽ ልልሽ ነው..ሌላው እዚህ መፃሀፍት መደብርም ያለሽን ስራ እንደዛው….
‹‹ያስቃል..››አልኩት..እውነትም ገርሞኝ
‹‹ምኑ ገረመሽ?››
‹‹በዚህ ምድር ላይ ሶስት አይነት ሰዎች አሉ .. givers , takers , matcher ይባላሉ፡፡ < givers > ምንም ነገር ሲሰጡህ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ነው…ሲያፈቅሩህ የእነሱን ማፍቀር ብቻ እንጂ የእነሱን መፈቀር አለመፈቅር አያስጨንቃቸውም..ሲለግሱህም ከአንተ በመልሱ ምንም የሚጠብቁት ነገር የለም…እንደዚህ አይነት ሰዎች የአለም በጣም ደሀ ሰዎች ሊሆኑ ይችላሉ ግን ሰማያዊ ስብዕና ያላቸው ናቸው… በተቃራኒውም የአለም በጣም ሀብታሞቹና ባለትልቅ ገቢ ባለቢቶችም እንዚሁ < givers > የሚባሉ ሰዎች ናቸው..ምክንያቱም ለአበባ ያደረጉት በእጥፍ ከሰለሞን ይደረግላቸዋል…ይሄ የተፈጥሮ ህግ ነዋ፡፡‹‹ለማታውቀው ወገንህ አንድ ስትሰጥ ከማታቀው ዘጠኝ ተጭምሮ አስር ሆኖ ይመለሰልሀል…›› የሚለው ዋና መመሪያቸው ነው..እነእየሱስ ፤ ነብዩ ሙሀመድ፤እነማዘር ትሬዛ..እነአበበች ጎበና እነሲስተር ዘቢደር፤ማህተመጋንዲ፤ማንዴላ ወዘተ …እነዚህ ዝም ብለው በነፃ ሲሰጡ በመኖራቸው ሀብታምነትን ብቻ ሳይሆን በታሪክ ማህደር ዘላለማዊነትንም የተጎናፀፈ ናቸው….
ሌላው‹‹ takers› የሚባሉት ናቸው …ከሌላው መቀበልን ብቻ ነው ዓላማ አድርገው የሚንቀሳቀሱት..ሁሌ ማትረፍን ብቻ ነው የሚያስቡት…ለእነሱ ዋናው ውጤት ነው …ምን ያህል አተርፋለው እንጂ በእኔ ማትረፍ ውስጥ እነማን ይጎዳሉ… ?የማን ቤት ይፈርሳል..?የማን ነፍስ ይነጠቃል ?አያስጨንቃቸውም..፡፡የአለም ሙሰኞች፤ ኮንትሮባንዲስቶች፤ቅጥረኛ ነፍስ ገዳዬች… ሀሺሽ ነጋዴዎች እዚህ ግሩፕ ውስጥ ይጠቃለላሉ..
ሶስተኛዎቹ ‹matcher› የሚባሉት ናቸው፡፡በሰጡት ልክ መቀበልን ይፈልጋሉ….ሁል ጊዜ በህይወት ሚዛን እየጠበቁ መጓዝ ዓላማቸው ነው…ዲፕሎማቶች ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ናቸው…‹በሰጥቶ መቀበል መርህ› የሚጓዙ ናቸው… በዚህ ህግ ስትሰጥ በተሻለ መጠን እንደምትቀበል እርግጠኛ መሆን አለብህ››.እከክልኝ ልከክልህ…መመሪያቸው ነው፡፡
‹‹እና እኔ ከሶስቱ የትኛው ነኝ.?››አለኝ
‹‹እራስህን ፈልገዋ….አሁን ይብቃን እንሂድ….››
‹‹ስላልኩሽ ነገር እኮ ምንም አላልሺኝም...?››
‹‹እየሄድን መኪና ውስጥ ነገርሀለው….››
‹‹እሺ ››ብሎ ሂሳብ ሊከፍል አስተናጋጁን ደረሰኝ ሲጠይቀው..እንደተከፈለ ነገረው…
‹‹ማን ነው የከፈለው...?››አይን አይኔን እያየ ባለማመን ጠየቀኝ..የእኔም ጥያቄ ስለነበረ ልመልስለት አልቻልኩም
‹‹እዛ ጥግ ተቀምጦ የነበረው ሰውዬ ጥቁር ሱፍ ለብሶ የነበረው ..›› አስተናጋጁ አብራራልን
‹‹ማነው አውቀሺዋል….?››
‹‹አዎ፡፡ ተነስ እንሄድ በቃ…የእኔ ሰው ነው››አልኩት…
የአይኖቹ ቀለማት ሲቀየሩ ታወቀኝ
‹‹ምንድነው እንዲህ አይነት ነገር… ሰው በሰው ነገር እንዲህ ጥልቅ ሲል ሲያበሳጨኝ ..ከፈለገ ሌላ ቀን አይጋብዝሽም.?…››ይሄንን እጃችንን ታጥበን ከሆቴሉ እየወጣን በነበረበት ጊዜ ነው የሚነጫነጭብኝ..
‹‹ ምንድነው የደበረህ ….?ይክፈል…እንደውም ጥሩ ነው››
‹‹ለምን ይከፍላል .?አሁን አራት መቶ የማትሞላ ብር ከፈለ አልከፈለ ለእኔ ምኑ ነው ጥሩ…ጉረኛ በይው…››
ሁሉን ነገር ከማሸነፍና ከመሸነፍ ጋር የሚያገናኝ ምን አይነት ሰው ነው… .?አሁን አበሳጨኝ ‹‹እውነትህን ነው….እንደውም ብሩን ስጠኝ ልመልስለት…››አልኩት
ፈገግ አለ..‹‹የት ታገኚዋለሽ ወጥቷል እኮ››
‹‹አይ ያ ፊት ለፊት ያለው ብቲክ የእሱ ነው.. ስጠኝና አፍንጫው ላይ ወርውሬለት ልምጣ..ነገ ይሄንን እንደውለታ ቆጥሮ ሊለፋደድብኝ ይችላል››
ጥርስ በጥርስ ሆነ‹‹ ..በደስታ ብሩን አውጥቶ ሰጠኝ..‹‹ጠብቀኝ ››አልኩና አስፓልት ጠርዝ ላይ አቁሜው በዝብራ ተሸገርኩና ሁለት ልጆች ታቅፋ ለምትለምን ለማኝ እጆ ላይ አስጨበጥኮት ሴትዬዋ መብረቅ እንደመታት አይነት በድንጋጤ ፈዛ ለመጮህም ዳድቶት ስትርበተበት ፊቴን አዞርኩና መልሼ አስፓልቱን ተሸግሬ ወደእሱ ስሄድ እያጨበጨበ ጠበቀኝ …ሁኔታው የብሽቀት ነው…‹‹ጀግና ነሽ… ሸወድሽኝ ማለት ነው››አለኝ ለንቦጩን ጥሎ
‹‹አይ አልሸወድኩህም..አሁን ጋብዘኸኛል ማለት ነው….ስለዚህ ዘና ማለት ትችላለህ›› አልኩት
‹‹ግን ታውቂያለሽ አይደል …በጣም እብድ ልጅ ነሽ…የምትገርሚ እብድ…ነይ በይ ላድርስሽ..››
‹‹አይ.. አንተ በዚሁ ሄድ እኔ በዚች ጋ አቋራጬ መንገድ አለች …በዛ ሄዳለው.››
‹‹አረ ችግር የለም አደርስሻለው..››
‹‹ለራሴው ነው..በዚህ አቋራጭ አምስት ደቂቃ ነው የሚፈጅብኝ..አንተ ግን ገና መብራት ጠብቀህ አደባባይ ዞረህ 30 ደቂቃም አይበቃ..››
‹‹ይሁን ግን መልሱን አልነገርሺኝም እኮ...?››
‹‹እ እረሳውት ነገ 12 ሰዓት አይደል መነሻው ..እመጣለው..አንተም ባትለኝ ያ ፕሮግራም እንዲያመልጠኝ አልፈልግም››
‹‹ጥሩ ነው ስራውን ደግሞ ካዛ ስንመለስ ሰኞ ታመለክቺያለሽ..››
‹‹አይ አላመለክትም ቅዳሜ ወይም እሁድ እዛ ዝግጅቱ ላይ ሁሉም ሰራተኞች ባሉበት እኔን በተመለከተ በተሳሳተ መረጃ በማባረርህ ስህተት መስራትህን ተናግረህ ይቅርታ ትጠይቀኛለህ..ከዛ ሞራሌን በመንካትህ ለመካስ ይሄ ያልከኸውን አዲስ ቦታ በእድገት እንደሰጠኸኝ ለሁሉም ታበስራለህ….አንተ ራስህ እንደዛ ታደርጋለህ…እንደዛ ሲሆን ነው ሁሉ ነገር ተፈታ የሚባለው ከዛ እንዳልከው ስለሹገር ዳዲዬ እና ሰለ መፃሀፍ መደብሩ እናወራለን በል ቻው ››እልኩና ምንም እንዲናገር ዕድሉን ሳልሰጠው ፈዞ በደነዘዘበት ጥዬው ሄድኩ
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍2