አትሮኖስ
286K subscribers
121 photos
3 videos
41 files
572 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


#ክፍል_ሀያ_አንድ


ስበሳጭ ጀርባዬን ይበላኛል...የበላኝን ቦታ ለማከክ እጄን በወገቤ አዙሬ አሽከረክራለሁ፤ ግን ደግሞ አልደርስበትም.. በትከሻዬ በኩል  አጠማዝዤ ሞክራለሁ፤ ትርፉ ድካም ነው። ከእከኬ ስቃይ እራሴን ለማስታገስ እገዛ መፈለጌ ያበሳጨኛል ደካማነቴንና ማድረግ የማልችላቸው ነገሮች ብዛት ያስጨንቀኛል...ጀርባዬን በላኝ እከኩልኝ ብዬ የሰው እገዛ ላለመጠየቅ ልብሴን አወልቅና ከሻካራ ግድግዳ ጋር እራሴን አፋትጋለሁ... ቢያቆስለኝም ያስተነፋሰኛል። ቢያንስ ገበናዬ ጠብቄያለሁ፡፡
አለመቻሌንም በሚስጥር በውስጤ አፍኜ ይዘዋለሁ፡፡አዎ አንዳንዴ ህይወት በዛ መጠን ትጨክንብኛለች በዛ መጠንም ታሰቃየኛለች፡፡
ዛሬ እርግጥ አልተበሳጨሁም ፤ግን ደግሞ በጣም ተጨንቄያለሁ፡፡ ጊዜው ጨለምለም ብሎል...አንድ ሰአት ከሩብ አካባቢ ነው›፡፡ ጀማሪ ማፊያ ይመስል ተጀባብኜ ወደሰፈር ተጠጋሁ...፡፡

እየተንቀጠቀጥኩ ነው ፡፡መቼስ ብርድ ብቻ አይመስለኝም እንደዚህ ውስጤ ገብቶ እያንቀጠቀጠኝ ያለው ።ኳስ እንጫወትበት የነበረው ሜዳ ባለአራት ፎቅ ህንፃ ተገማሽሮ ቆሞበታል። መቼስ ደፍረው ጠጠርና አሸዋ አምጥተው የሠፈሩ ሰው እያየ ሲሚንቶ አውርደው ፤ቀስበቀስ የገነቡት ሳይሆን ድንገት ከእለታት በአንድ ቀን ሁሉም የሰፈር ጎረምሳ ሆነ አሮጊት መተኛታቸውን አረጋግጠው ከሆነ ቦታ ጭነው መተው የተከተሉት ነው የሚመስለው። ወደቤታችን አየተቃረብኩ ስመጣ እግሬ እየተሳሰረ አስቸገረኝ፤ መራመድ ሁሉ አቃተኝ።
የውጩ ፍሬንች ዶር በአዲስ ከመቀየሩ ውጭ ቤታችን  ከውጭ ያለው እይታ በፊት እንዳነበረ ነው።አለፍ ብዬ ሄድኩና ኮርነር ጋር ስደርስ ጨለማን   ተገን አድርጌ ቆምኩ፡፡ ፊቴን ወደ በራፋችን አነጣጠርኩ

፡፡ ...ምንድነው የምጠብቀው..?.ማን እንዲወጣ ወይ ማን እንዲገባ ነው  ? ልጄን አሁን የማየት እድል አለኝ ይሆን?በዚህ ጨለማ ምን ልትሰራ ትወጣለች...?ምን አልባት አክስቴ...አዎ ምንአልባት እሷን ነው ላይ የምችለው...፡፡ባላናግራትም ላያት ምኞቴ ነው፡፡ ሶስት ሰአት ድረስ እዛው በቆምኩበት ደንዝዤለሁ… የጨው ሀውልት እንደሆነችው ልክ እንደ ሎጥ ሚስት  እኔም የበረዶ ሀውልት ከመሆኔ በፊት ወደ ሆቴሌ  ልመለስ ወስኜ እግሬን ሳንቀሳቅስ ስልኬ ተንጫረረ ።በደነዘዘ እጄ አወጣሁና አየሁት ..የደዋዪን ማንነት ሳይ ከሰውነቴ ላይ በረዶ የሠራው ቅዝቃዜ  በቅፅበት የረገፈ ይመስል ሙቀት ተሠማኝ ።ልጄ ነች።እንዴ አይታኝ ይሆን እንዴ? ዙሪያ ገባዬን ተገላምጬ  ተመለከትኩ።ምንም የለም፡፡ስልኩን አነሳሁት

"ሄሎ የእኔ ልዕልት"

"አባዬ እንዴት ነህ..?ምን እየሠራህ ነው?"

"ስለአንቺ እያሰብኩ"

"ታድዬ" ታድዬ አባባሏ  ልቤን ስንጥቅ አድርጎ  ቃላቱ በስንጥቁ እየተንጠባጠበ ወደውስጤ ሲዘልቅ ተሠማኝ።

"ምን  እየሠራሽ ነው...?ነገ ዝግጅት ስላለብሽ በጊዜ አትተኚም እንዴ?

"እነቴቴ እንደዛ ብለው አጠፋፍተው በጊዜ ተኙ።እኔ ግን ክፍሌ ከገባሁ ብኃላ ከመተኛቴ በፊት  መስኮቴን ከፍቼ ጨረቃን ሳያት አንተ ትዝ አልከኝ...እና ደወልኩልህ"

ቀና ብዬ ምትላትን ጨረቃ አያየኋት… ግማሽ ቅርፅ፤ግማሽ ውበት፡፡
"ልጄ እውነትሽን ነው ..ታምራለች"
"ማን ነች የምታምረው አባዬ"

"ያልሻት ጨረቃ ነቻ..አይኖቼን አንጋጥጬ እያየኋት ነው… ግማሽ ብትሆንም ልክ እንደአንቺ ታምራለች"

"አባዬ ዛሬ ከጎኔ ሆነህ እቅፍ አድርጌህ ብተኛ ደስ ይለኝ ነበር"

"እንግዲያው መስኮቱን ክፍት አድርጊና ለጥ በይ ..እኔ በርሬ እመጣና በመስኮት ክፍልሽ ገብቼ  እቅፍ አደርግሻለሁ..ግን ከተኛሽ በኃላ ነው የምመጣው"

"አባዬ ደስ የሚል ጫወታ ነው ...በቃ ሳልዘጋው ነው የምተኛው..ነገ ከዝግጅቱ በኃላ ደውልልሀለሁ.ወድሀለሁ።››

"እኔም ወድሻለሁ "ስልኩ ተዘጋ..

የእኔም ወደሆቴሌ የመመለስ አፒታይቴም አብሮ ተዘጋ፤

"ምን ላድርግ?"ከሀያ ደቂቃ በላይ ባለሁበት ቦታ ተገትሬ ማሰብ እንኳን አቅቶኝ ደንዝዤ ቆየሁ።ወደጓሮ ሄድኩ  ..፡፡.ካልተቀየረች አንድ ወደጊቢ  ዘሎ መግቢያ ምቹ  ቦታ ነበረች..አዎ አገኘኋት።ዙሪያ ገባውን ዞር ዞር ብዬ ሰው አለመኖሩ  አረጋገጥኩና እንደምንም ተንጠላጥዬ ዘልዬ ግቢውስጥ ገባሁ። ድሮ የሀይእስኩል ተማሪ እያለሁ በተለያየ ምክንያት ውጭ ሳመሽና በራፍ ሲዘጋብኝ በዚህ ዘዴ ነበር  ወደ ውስጥ የምገባው..፡፡ይሄው የዛን ጊዜው ልምድ ለዛሬ ረዳኝ።

የውጭ መብራት ስለጠፍ ግቢው በፀጥታና በጭለማ  ተውጧል።ኮቴዬን ሳላሰማ ቀስ ብዬ ወደልጄ ክፍል ማለት ወደእኔ የድሮ ክፍል አመራሁ...፡፡ወይ የእኔ ማር እንዳልኳት  መስኮቱን ከፍታ ነው የተኛችው። እንደምንም ተንጠላጠልኩና  መስኮቱ ላይ ወጣሁ ..ደግነቱ መስኮቱ አጠር ስለሚል በተለይ ከእኔ ቁመት አንፃር  አልተቸገርኩም፡፡  በቀላሉ ወደላይ ወጣሁና እግሬን አሽከርክሬ ወደውስጥ ገባሁ፡፡ ልጄን እንዳላስደነግጣት ተጠንቅቄ ወደማብሪያ ማጥፊያው አመራሁ..፡፡አብዛኛውን ዕድሜዬን የኖርኩበት ቤት መሆኑ ነገሮች የት የት እንደሆኑ በቀላሉ ለመለየት ረድቶኛል ።  መብራቱን አበራሁ።ልጄ እንዴት አድጋለች..ደግሞ አተኛኞ ልክ እንደናቷ ዝርግትግት ብላ ነው።በቅርቤ ያገኘኋት ኩርሲ መቀመጫ ወደአልጋዎ   አስጠጋሁና  ቁጭ አልኩ ...፡፡ጭንቅላቴን ሸፍኜበት የነበረውን  ኮፍያ ከላዬ ላይ ገፍፌ  ጣልኩት።አይኔ ላይ ሰክቼ የነበረውን መነፅር አወለቅኩና በአቅራቢዬ ያለ ትንሽ ጠረጰዛ ላይ አስቀመጥኩ። ሙሉ ትኩረቴን  ወደልጄ ሰበሰብኩ።እጆቼን በእርጋታ   ወደጭንቅላቷ ሰደድኩ .."ቀስ ብዬ ስዳብሳት  አይኖቾን ገለጠች...፡፡ደነገጥኩና እጄን ሰበሰብኩ...እሪ ብላ የምትጮህ መሠሎኝ ፈራሁ። ምን ላድርግ...?ፈጠን ብዬ  ዘልዬ   እንደአመጣጤ ልውጣ እንዴ?ብዙ ነገር አስቤ አንድንም ሳላደርግ

"አባዬ....ህልም አይደለም አይደል..?"አለችኝ፡፡

"አይደለም የእኔ ማር ...››በተኛችበት ጉንጮቾን ሞጨሞጭኳት...እሷም እጇቾን በአንገቴ ዙሪያ ጠመጠመችና ግንባሬን፤ጉንጬን ፤አገጬን ምንም የቀራት ቦታ የለም...ሙሉ በሙሉ ንቁ ሆና አልጋዎ መካከል ቁጭ አለች።

"አባዬ እኔ እኮ እመጣለሁ  ስትለኝ በህልሜ መስሎኝ ነው ቶሎ የተኛሁት።

"በጣም ስለናፈቅሺኝና ..ነገ  የደረጃ ተማሪ ሆነሽ ልትሸለሚ ስለሆነ እኔ  አባትሽ በጣም ኩራት ስለተሰማኝ  እንዴ ተደብቄም ቢሆን በዚህ ቀን ልጄን ካላየኋት  እኔ ምን አይነት አባት ነኝ ?ብዬ ነው በዚህ ለሊት ሹልክ ብዬ ክፍልሽ የተገኘሁት።

"አባቴ ውድድድ ነው የማደርግህ...አሁን አቅፍቅፍ ብለን እንተኛ"
"ግን አቴቴ ለሊት ልታይሽ ብትመጣስ?"

"አትመጣም ..ደግሞ እኮ ከውስጥ ተቀርቅሯል ..ብትመጣም ገና ስታንኳኳ ቶሎ ብለህ በመስኮት ትሄዳለህ"

"ምን አይነት ብልጥ ልጅ ነው ያለኝ"አልኩና ከላይ የለበስኩትን ጃኬት በማውለቅ ጠረጳዛ ላይ አኑሬ አልጋ ላይ ወጣሁ..ይሄ አልጋ የእኔና የእናትሽ እንደነበር ታውቂያለሽ?"

"አዎ …ለዛ እኮነው ክፍሌንም አልጋዬንም የምወደው"
👍564
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ


#ክፍል_ሀያ_ሁለት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

///

"አባዬ ምንድነው?


"በሹክሹክታ ጠየቀችኝ

"እኔ እንጃ ..የውጭ በራፍ እየተንኳኳ ነው" ብዬ የተኛሁበትን አልጋ ለቅቄ ወረድኩ፡

‹‹ምነው ልትሄድ ነው እንዴ?"

"አይ ልነሳና ሁኔታውን እንይ"
"ምንድነው?
ማነው?"የእቴቴ ድምፅ ይሰማል
"ቀስ በይ.. ጫማ አላደረግሺም"እህቴ ነች
በዚህ ጊዜ ልጄ"አባዬ" አለችኝ በሹክሹክታ

"ወዬ ማሬ "በተመሳሳይ ቶን
"የውጩን በራፍ ሊከፍቱ ሲወጡ መስኮቱን ክፍት ሆኖ ያዩታል...ለምን ተከፈተ ብለው ወደእዚህ እንዳይመጡ ፈራሁ"
በበሳል አዕምሮዋ ተደምሜ ወደራሴ ሳብኩና ግንባሯን በመሳም ፈጠን ብዬ ወደ
መስኮቱ በመሄድ  ዘጋሁት.፡፡አውልቄ ጠረጰዛ ላይ አስቀምጬ የነበረውን ጃኬቴን ለበስኩ ፡፡ጫማዬን አጠለቅኩ..፡፡መነፅሬን ግንባሬ ላይ ሰካሁና ዝግጅ ሆኜ ወንበሩ ላይ በተጠንቀቅ ቁጭ አልኩ።
እቴቴና እህቴ በራፍ ከፍተው ሲወጡ ሰማን ...ልጄ ከመኝታዋ ወረደችና ወደእኔ መጣች፡፡ ስሬ ቆመች ፡፡በቀልጣፍ የአስተሳስብ ብቃቷ ታላቄ ብትሆንም ያው በእድሜ ልጄ ነችና አነሳሁና  ታፍዬ ላይ አስቀምጬ ወደ ውስጤ ጭምቅ አድርጌ አቀፍኳት ፡አንገቴ ስር ሽጉጥ አለች

..."ማን ነው?"
"እኔ ነኝ ክፈቱ"የሚል  የደበዘዘ አይነት  የቃላት ልውውጥ  ይሰማል"አሁን በዚህ ድንገተኛ ግርግር ምክንያት ሲኦል ከመግባት በላይ በምፈራት በአክስቴ ፊት እቆም ይሆን..?.አረ ፈጣሪ ምንም ሀጢያተኛና ዳተኛ ሰው ብሆንም ይሄን ያህልማ ጨክነህ አሳልፈህ አትሰጠኝም" ስል ፀለይኩ...ፀሎቴን ተከትሎ ‹‹ጉድ ጉድ …››እያለች አክስቴ ወደቤት ስትመለስ ሰማሁ
..‹‹.በቃ መርዶ ነው›››ስል አሰብኩ ..የታላቅ እህቴ ልጅ ምን ሆነው ይሆን?"ከአሁን አሁን ቤቱ በለቅሶ ይደበላለቃል ብዬ  መጠበቅ ጀመርኩ...አሁን ደግሞ ከእኔ  መጋለጥ በላይ ለቀናት ስታስበውና ስትዘጋጅበት የከረመችው የልጄ   ፕሮግራም መሰነካከሉን ሳስብ ልቤ ላይ ህመም ፈጠረብኝ።
"አባዬ ምንድነው? ጨነቀኝ?"
"አይዞሽ ልጄ.. አይዞሽ"እኔ እራሴም  ውስጤ በፍራቻ እየራደ ቢሆንም እሷን ግን ላበረታት ሞከርኩ፡፡
"በጊዜ አንድ ወይም ሁለት ሰዓት እኮ ነበር የምንገባው.. ሸኖን እንዳለፍን መኪናዋ ተበላሸችብን....መከራ አይተን ከሸኖ መካኒክ መቶ ነው ያስነሳት....››
በስመአብ እየቃዠሁ ነው እንዴ? ይሄንን ድምፅ አውቀዋለሁ፡፡
"እንደምትመጪ እኮ አልነገርሺንም...አዲስ አበባ ከገባሽ በኃላ እንኳን አትደውይም እንዴ..?›.
"በእኔ ቤትማ ሰርፐራይዝ ላደርጋችሁ ነበር....ግባ ….አዎ ሻንጣው እዛው ጋ ይሁን..ሌላው  መኪናው ላይ ይደር …ነገ ይወርዳል..ተቀመጥ ..አዎ ሶፋው ላይ ተቀመጥ››
"አባዬ. …እማዬ መጣች መሰለኝ"ልጄ ነች ጥርጣሬዋን በጆሮዬ ሹክ ያለችኝ
"አዎ መሰለኝ"
እቅፍ አድርጋ ሳም አደረገችኝ   ...እሷ ደስ ስላላት ደስ አለኝ...አረ በራሴም ደስ ብሎኛል ልቤ በውስጤ ስትንፈራፈር ሁሉ ይታወቀኛል።
አሁንም ጆሮዬ እዛኛው ክፍል ነው፡፡..."እማዬ ዛሬ እንኳን አታናግረኝም?"
"ተያት ... ደንግጣ ነው…እንኳን እሷ እኔ  እራሱ  በድንጋጤ ደርቄልሻለሁ"
"ታዲያ አሁን የት ሄደች ...?"
"ክፍሏ ገብታለች መሠለኝ"
"እሺ ልጄስ....?"
‹‹ተኝታለቻ..."
"ንፍቅ ብላኛለች ..በናትሽ ልቀስቅሳት"
"አይ ..ነገ ዝግጅቷ  ላይ ከምትንገላጀጅ ይቅርብሽ..እንደውም በጥዋት ስትነሳ ሰርፐራይዝ ታደርጊያታለሽ"
"ጥሩ ነው… እንደውም እንደዛ ይሻላል።"
ተንፈስ አልኩ...ወደእኛ አይመጡም ማለት ነው፡
"እማ አሁን እናትሽን ልታገኚያት ትፈልጊያለሽ?››ፈራ ተባ እያልኩ ታፋዬ ላይ የተቀመጠችውን ልጄን  ጠየቅኳት፡፡
"አይ አሁን ምፈልገው ከአንተ ጋር ተመልሶ መተኛት ነው..ከእሷ ጋር ነገ እተኛለሁ"
እቅፍ አደረኩና ወደአልጋው ይዤት ሄድኩ፤ ጫማዬን አወለቅኩና እቅፍ እንዳደረኳት ተኛሁ...ጆሮዬ ግን እዛው ሳሎን ነው ያለው፡፡
"የሚበላ ነገር ትፈልጋላችሁ ላሙቅ"እህቴ ነች እንግዶቹን የጠየቀችው
"አረ መንገድ ላይ ጂውስና ብስኩት ተጠቅመናል...አሁን መተኛት ነው የምንፈልገው...ለሀሰኖ የእንግዳ ክፍሉን ታሳይዋለሽ ..?እኔ ያው ካንቺ ጋር ነው ምተኛው?
"ምን ጥያቄ አለው...ወንድም ተነስ መኝታህን ላሳይህ››
‹እሺ›
የእግር ኮቴ .ከዛ ረዘም ያለ ዝምታ..ቀጥሎ ማንኳኳት ተሰማኝ
‹‹እቴቴ..እማ.እማዬ››
‹‹አረ አናግሪኝ..ውቅያኖስ አቆርጩ የመጣሁት እኮ አንድም አንቺ ስለናፈቅሺኝ ነው..በአመታት ርዝመት  እንኳን ይቅር አትይኝም››
‹‹እማ እንዳልተኛሽ አውቃለሁ›
‹‹እንዴ ምን እየሰራሽ ነው.››እህቴ ነች እንግዳውን አስተኝታ ስትመጣ ያየችው ነገር በመቃወም የተናገረችው፡
‹‹ብታናግረኘ እኮ ብዬ ነው››
‹‹ታገሺ….ነው ወይስ ዛሬውኑ ተመልሰሽ ሀጄ ነሽ››
‹‹ከገዛ እናት ጋር መዘጋጋት እንዴት እንደሚጨንቅ  እኮ ስለማታውቂ ነው..›
‹በይ በይ አሁን ወደመኝታችን እንሂድ››
ፀጥታ ሰፈነ…
…….በነጋታው

ከትምህርት ቤቱ ቅፅር ግቢ የፊት ለፊት  በራፍ ራቅ ብዬ በአንደኛው መንገድ ቆሜያለሁ።በተቻለኝ መጠን አለባበሴ በቀላሉ ማንነቴን ለመለየት የማያስችል እንዲሆን የተቻለኝን ጥንቃቄ አድርጌያለሁ።በአንድ እጄ ከጄኔራሏ የተዋስኩትን ካሜራ ይዣለሁ ሌላ እጄ ዝም ብሎ ከወዲህ ወዲያ እየተወናጨፈ ግራ መጋባቴን ለተመልካቹ እያሳበቀብኝ ነው። ተማሪዎች ለብቻቸውም ከወላጆቻቸው ጋርም በመሆን ወደውስጥ መግባት ከጀመሩ ደቂቃዎች አልፈዋል። እዛው ከቆምኩበት ሳልንቀሳቀስ ከፊት ለፊቴ ካለው መንገድ ሙሉ ቤተሠቤ ሲመጡ ተመለከትኩ።ፈጠን ብዬ ከመሀል መንገድ በመውጣት ደር ላይ የሚገኝ የት/ቤቱ ቢልቦርድን ተከልዬ እይታዬን ወደእነሱ አስተካከልኩ።

ቀድሞ በእይታዬ የገባችው  ደርባባዎ እመቤት አክስቴ ነች።ቅሬታ ያረበበት  የደግነት ተምሳሌት መሆኑ የሚያስታውቅ  የእናት ፊት ...ሮጠህ ሄደህ እግሯ ስር እዛ አቧራው ላይ በመንከባለል ይቅርታ ጠይቃት የሚል ስሜት ከጀርባዬ ወደ ፊት ሲገፈትረኝ ይታወቀኛል።እራሴን በመቆጣጠር ችሎታዬ ላይ ጥርጣሬ  ስለገባኝ የተከለልኩበትን የቢልባርድ ብረት ጨምድጄ ያዝኩ።ከመዋረዴ በፊት ትኩረቴን እንደምንም ከእቴቴ አንስቼ ወደ ልጄ አሸጋገርኩት።ልጄ ትንሽ ልዕልት መስላለች..ቦፍ ብሎ ሜዳውን የሞላ ነጭ ቀሚስ ከነጭ ጫማ ጋር ለብሳለች...ያ ክብ ፊቷ የደስታ ብርሀን እየረጨ ነው።በአጠቃላይ ድምቀትና ውበት የተዋሀደባት ሙሉ ጨረቃ መስላለች።አዎ ከአመታት የናፍቆት መቃተት በኃላ በአንድ ቀን እናትንና አባትን ማግኘት ከዚህ በላይም ቢያስፈነድቅ የሚገርም አይሆንም።የእኔ ልጅ የእኔ መላአክ እንኳንም ፈካሽልኝ።

ቀጥሎ እናትዬውን ነው ያየሁት፤ሩቾ ፍፅም ተቀይራ ሌላ ሰው መስላላለች ።በሳቋ ነው የለየኋት።ሙሉ ቆዳዋን አስገፍፋ በሌላ እንደተካች አይነት ነው የተሠማኝ።ደግሞ እንዲህ እረጅም ነበረች እንዴ?እርግጠኛ ነኝ ይሄንን እጄን እንደጥንቱ ፊቷ ላይ አሳርፌ ፊቷን ብዳብስ ይሸረካክታታል...ጉንጮቻ እኮ ተንጠልጥለዋል"ተአምርን በቀኝ እጆ ሌላ አነስ ያለ ወንድ ልጅ በግራ እጇ ይዛ ጠብ እርግፍ ትላለ…ወንድ ልጅ የማነው ልጅ?"

"ውይ ለካ ሁለት ልጆቾ ነው  ያሏት….አሁን እቺ ምኗ ነው የሁለት ልጅ እናት የሚመስለው፤  . .ይልቅስ እኔ  ነኝ በመጎሳቆሌ የተነሳ ግርጅፍጅፍ ብዬ የአራት ልጆች አባት የምመስለው።
👍602🤔2
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ


#ክፍል_ሀያ_ሶስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

////

መቼስ የሀገራችን የሚካሄድ ትንሽም ሆነ ትላልቅ ዝግጅቶች ተሳስተው እንኳን ከመዝረክረክ አያመልጡም።እና ይጀመራል ከተባለበት ሰዓት 40 ደቂቃ አርፈደው  ጀመሩ...ዝግጅቱ ከተጀመረ ከአንድ ሰአት በኃላ  የሽልማቱ ፕሮግራም ተጀመረ ። እንደአጋጣሚ ሽልማቱ ከታችኛው ክፍል ነው የተጀመረው...

‹‹ አማካይ ውጤት 97.5 በማምጣት ከሁለተኛ-ለ ክፍል እንዲሁም ከአጠቃላዩ  ሶስቱም  የሁለተኛ ክፍል ተማሪዎች አንደኛ በመውጣት ልዩ ተሸላሚያችን ተአምር እዬብ  ..››አካባቢው በጭብጨባ ተነጋ.. ቤተሰቦቼ  ሁሉም ከተቀመጡበት ተነስተው  አካባቢውን ቀወጡት..፡፡በስሜት ካሜራዬን ደቅኜ ወደፊት ተጠጋሁ .በተቻለኝ መጠን ልጄን በካሜራዬ ለማደን ሙከራዬን  ቀጠልኩ...፡፡የእኔ ልዕልት እየተንሳፈፈች ወደመድረክ
እየቀረበች ነው...፡፡

እናትዬውና አክስቶቾ ሰፌድ የሚያካክል  አይፓዳቸውን ቀስረው ከኃላ ተከተሏት...፡፡መድረክ  ላይ ወጥታ ከክብር እንግዳው ሽልማቷን ስትቀበል ስመለከት እንባዬን ከመርገፍ ላግደው አልቻልኩም...የራስ ልጅ  እንዲህ በክብር አደባባይ ላይ ብዙዎችን በአድናቆት ሲያስጨበጭብ ማየት ለአንድ ወላጅ ምን አይነት ልብን በደስታ የሚያጥለቀልቅ  መባረክ እንደሆነ እድሉ የገጠመው ወላጅ ብቻ ነው የሚያውቀው።

እኔም በጊዜው እዚህ መድረክ ላይ እስኪሰለቸኝ ድረስ በተደጋጋሚ በመውጣት ተሸልሜበታለሁ...በዛን ወቅት ግን  እቤተሠቧቼ አሁን እኔ የተሠማኝን አይነት ልዩ ስሜት እንደሚሰማቸው ገምቼ አላውቅም ነበር...፡፡ልጄ ሽልማቷን  በአየር ላይ እያወዛወዘች ህዝብን  አስጨበጨበች።ከዛ በእኔ አቅጣጫ ስትደርስ ሽልማቱን ባለበት አቆመችና ትኩር ብላ ወደእኔ ተመለከተች፤ እኔም በደስታ  እጄን እስኪያመኝ በአየር ላይ አወናጨፍኩት..ከዛ ለሌላ ተሸላሚ መድረኩን ለቃ ስትወርድ እኔም ፈጠን ብዬ በፊት ወደነበኩበት ቦታ ተመለስኩ…፡፡

ዘመዶቾ ከበዋት ያውካካሉ እያንዳንዱ በየተራ አብረዋት ፎቶ ይነሳሉ…፡፡ቀናሁ… በጣም ቀናሁ…..እኔም ከመሀከላቸው መገኘት ነበረብኝ፡፡.ቁጭ አልኩና በሀሳብ ሰመጥኩ፡፡.አይኖቼ እንባ አግተዋል….፡፡ትንሽ ፊት ሚያሳየኝ ወይ ሚነካካኝ ነገር ባገኝ እዘረግፈዋለሁ….፡፡

አንድ ነገር ተከሻዬን ከኃላዬ ነካኝ…..ከሀሳብ ባነንኩና ዞር ስል ልጄ ነች…፡፡

‹‹አባዬ ተከተለኝ›› ብላ ብን ብላ ወደኃላ ሄደችና ከእኔ ጀርባ ባለ የመማሪያ  ክፍል ግድግዳ ኮርነር ተጠመዘዘች፡፡ፊቴን ወደ ፊትለፊት ላኩ ፡፡ወደዘመዶቼ፡፡ በራሳቸው ነገር ተጠምደው ያውካካሉ.፡፡ፈጠን አልኩና ተንቀሳቀስኩ፡፡ ልጄ ወደሄደችበት በፍጥት ሄድኩ ፡፡እንደተጠመዝኩ አገኘኋት፡፡ እጄን ያዘችና በፈጣን እርምጃ ወደፊት መጓዝ ጀመረች.፡፡ዝምብዬ ተጎተትኩላት…፡፡ምን ልታደርግ እንደሆነ አልገባኝም…፡፡ክፍሉን አለፈችና ሌላ ጠባብ መንገድ ውስጥ  ይዛኝ ገባች፡፡ጥቂት ተራመድንና  በፅድና በአትክልት የደመቀ የት/ቤቱ መናፈሻ ውስጥ ገባን፡፡ ምትፈልግበት ቦታ ከደረሰች በኃላ አዲስ እንዳገኘችኝ ነገር ተጠመጠመችብኝ፡፡

‹‹እንዳያዩን ብዬ እኮ ነው እዚህ ይዤህ የመጣሁት››

‹‹አይፈልጉሽም?››

‹‹ቶሎ እመለሳለሁ… ሽንት ቤት ብያቸው ነው የመጣሁት››

‹‹የእኔ ብልጥ በጣም ነው የኮራሁብሽ….፡፡.በጣም ነው ያስደሰሽኝ ….፡፡እንቺ ይህቺ ያዘጋጀውልሽ ትንሽ ስጦታ ነች›አልኩና  በሚያብረቀርቅ የስጦታ ወረቀት አምሮ የተጠቀለ እና በፔስታል ያለ ስጦታዬን ሰጣኋት..

‹‹አባዬ ምንድነው? ልክፈተው?››

‹አይ እቤት ብቻሽን ስትሆኚ ተከፍቺዋለሽ›

‹‹እሺ አበባዬ አመሰግናለሁ…በጣም አስደስተህኛል›ብላ ወደታች አስጎንብሳ ጉንጬን ሳመቺኝና

‹አባዬ ፎቶ እንነሳና ልሂዳ..›

‹‹እሺ …እሺ›› አልኩና የያዝኩትን ካሜራ በራሱ እንዲያነሳ አጀስት በማድረግ አንድ አምስት የሚሆኑ ፎቶዎች ተነሳን፡፡

‹‹አሁን ልሂድ አባዬ››

‹የእኔ ማር ሂጀ …አሁን እኔም ወደአዲስአባ ልመለስ…ማታ ብቻሽን ስትሆኚ ደውይልኝ››

‹‹እሺ አባዬ…ሌላ ጊዜም መጥተህ ታየኛለህ አይደል.?››

‹‹የእኔ ማር ከአሁን ወዲህ አንቺን ሳላይ ብዙ ጊዜ መቆየት ስለማልችል .አዎ መጥቼ አይሻለሁ›

አገላብጬ ሳምኳት.እሷም ሳመችኝና እንዳመጣጧ እየተሹለከለክች ብን ብላ ሄደች.፡፡እኔ እዛ መናፈሻ ውስጥ ለታሪክ ድምቀት የታነፀ በድን ሀውልት መስዬ ለረጅም ደቂቃዎች ቆምኩ፡፡ አሁን እንደቅድሙ የተንጠለጠለውን እንባዬን ገድቤ ማቆየት አልቻልኩም….ዝርግፍ ብሎ ሲንጠባጠብ እኔም ልክ እንደሌላ ሰው በትዝብት እያየሁት ነው፡፡ከዛ በኃላማ ወደዝግጅቱም አልተመለስኩም፡፡ ምን ላደርግ…?ሹልክ ብዬ ግቢውን ለቅቄ ወጣሁና ወደመናኸሪያ ነው ያመራሁት.፡፡ከዛ ቀጥታ ወደ አዲስአባዬ ፡፡

ይቀጥላል
👍998🥰6😁5🔥2👏2👎1
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ


#ክፍል_ሀያ_አራት

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

///
ከደብረብርሀን ከተመለስኩ በአራተኛው ቀን ይመስለኛል ማታ ከስራ ተመልሼ አልጋዬ ላይ ጋደም ብዬ ለመተኛት እየተገላበጥኩ ሳለ ልጄ ደወለች..አነሳሁና ስለእናቷ ስለቤተሰቡ ብዙ ብዙ ነገር ካወራን በኃላ

‹‹እናት…እናትሽ ከመጣች በኃላ እኮ ያቺን ነገር መላክ አቆምሽ››ስል ወቀስኳት

‹‹ምንድነው አባዬ?››

‹‹የእናትሽን ደብዳቤ ነዋ….ነው ወይስ ነጠቀችሽ?››

‹‹አይ አልነጠቀቺኝም እኔው ጋር ነው. ያለው...ግን እኮ አንድ ገፅ ብቻ ነች የቀረቺው..እሷን አሁን እልክልሀለሁ››

‹‹እሺ የእኔ ማር …እጠብቃለሁ..ደህና አደሪልኝ››

ከተሰናበትኳት ከ10 ደቂቃ በኃላ ቃሏን አክብራ የመጨረሻ ያለችውን ቅጠል በተለመደው መንገድ ላከችልኝ..እስኪ ከመተኛቴ በፊት የሪቾን የመጨረሻ ኑዛዜ አብረን እናንብባት፡፡
 
ሀምሌ 20/2008 ዓ.ም
ተስፋ መቁረጥ ብቻም ሳይሆን እግዚያብሄርን በጣም ነው የተቀየምኩት…. ወደ እዚህ ጉድ ከመግባት  እንዲታደገኝ እቤቱ ተመላልሼ አቧራ ላይ እየተንከባለልኩ ብዙ ቀን ተማፅኜዋለሁ…. በመሰናክሉም ተሰናክሎ ላለመውደቅ ያቅሜን ያህል ሞክሬያለሁ፡፡

የማላፈቅረውን ሰው በተክሊል እስከማግባት ድረስ ሄጄለሁ፣እኔ ይሄንን ሁሉ ስጥር እግዚያብሄር ምን ረዳኝ…..?እንደውም በተቃራኒው ላልተገባ ሀጥያት አሳልፎ ሰጠኝ……..ምንአልባት ጥንቱን ሲፈጥረኝ ለሲኦል አጭቶኝ ስለሆነ ይሆናል….ስለዚህ እጅ ሰጥቼያለሁ……በመንፈሳዊም ሆነ በስጋዊ ህይወቴ ያለኝ ተስፋ ፈርሶል፡፡አሁን ነፍሴ ሴይጣን ይንገስባት….. በተሰነካከለ ተስፋዬም  ዳቢሎስ ይደሰትበት ብዬ እራሴን ረገምኩ……
ከዛ በሃላ ብቸኛው ያስጨነቀኝ ጉዳይ የቤተሰቦቼ ሀዘን ነው…የእናቴ ቅስም መሰበር ነው…..እና እንደፈራሁትም በክስተቱ ቤተሰቦቼ የመጨረሻውን  ሀዘን አዘኑ ..እናትና አባቴ የ30 አመት ትዳራቸውን በተኑ……በወቅቱ ሁሉን  ነገር ጣጥዬ እራሴን ለማጥፍት  ወስኜ ነበር……ግን  ደግሞ ፈራሁ ..የፍራቻዬ ምክንያት ደግሞ የሚያስቅ ነው…‹‹ከሞትኩ በኃላ   እዬቤ ቢናፍቀኝስ…..?እውነት ይሄ ልክፍት ነው…፡፡አንድ የሁለት ልጆች እናት የሆነች  ባለ ጤነኛ አዕምሮ ሴት በሆነ ችግር እራሷን ለማጥፋት ስትነሳ ሊያሳስባት የሚገባው የመጀመሪያው ነገር ‹‹እኔ ከሞትኩ በኃላ ልጆቼ እንዴት ይሆናሉ?›› የሚለው ስጋት መሆን ነበረበት፡፡እኔ ግን ፈፅሞ እንደዛ አይት ሀሳብ አላስጨንቀኝም
…….ስላማያስጨንቀኝ ግን አፍራለሁ….እውነትም በጣም አፍራለሁ፡፡
በዛ መወዛገብ ውስጥ እያለሁ እዬብ የተአምር አባት እንደሆነ ሲያውቅ ማቄን ጨርቄን ሳይል እብስ ብሎ ጠፋ …ለአንድ ወር ፈለኩት እስከሀለማያ ሄጄ ፈለኩት…አውቆ የተኛ ቢቀሰቅሱት አይሰማም አይደል የሚባለው…ሊገኝ አልቻለም፡፡
በቃ ሁሉን ነገር ጣጥዬ በደስታ ሳይሆነ በሀዘን ተቆራምጄ..በተስፋ ሳይሆን  በተሰባበረ ልብ ወደአሜሪካ ለመጓዝ ወሰንኩ፡፡   ……አዎ እራሴን ማጥፋት ካልቻልኩ እራሴን መርሳት አለብኝ …እራስ ለመርሳት ደግሞ አሜሪካ ምቹ ቦታ ትመስለኛለች፡፡አዎ እዛ ሄጄ እራሴን በስራ እጠምዳለሁ ……ልክ ከአሜሪካ ሮቦቶች ማካከል እንደአንዱ እሆናለሁ ……በቃ ከሶስት ቀን በኃላ ሁሉን ነገር ጣጥዬ የፈረሰ ተስፋዬን እና የቆሰለ ልቤን ይዤ ወደአሜሪካ… እዛ እንደረስኩ ከምፈታው ባሌ ጋር እበራለሁ..

እዚህ ላይ ሪች ብዙ ነገር ሸፋፍና እና በጥቅሉ ጠቃቅሳ  አልፋቸዋለች…. ለዛውም ዋናውን አስኳል  ነገር ..እርግጠኛ ነኝ ሰለዛ ስታስብ  እእምሮዋ ከተገቢው በላይ እየተጨናነቀባት አስቸግሯት በምልሰት እያስታወሰች መፃፍ ከብዶት መሰለኝ እንደዛ ያደረገቺው፡፡
እኔና ሪች ለመጀመሪያ ጊዜ  ወደ ጻታዊ ግንኙነት ሰተት ብለን የገባናው ካገባች ከ10 ኛው ቀን በኃላ ነው፡:፡ሰርጉ አልፎ እኛ ቤትም መልስ ተጠርተው  ከተመለሱ በኃላ  እና ቤታቸው  ገብተው ኑሮን አህድ ብለው እንደጀመሩ መስፍኔ  አንድ ጎጃም ፍኖተሰላም ሚኖሩ አጎቱ ሞተው መርዶ ተነገረው፡፡
ከመሄዱ በፊት እኔን በአካል አግኝቶኝ በከፍተኛ አደራ ሪችን እንዳስተዳድራትና ቀንም ቢሆን ብቻዋን እንዳልተዋት በልመና ተማፀነኝ‹‹በሬ ከአራጁ ይውላል ይሎችኋል እንዲህ አይነቱን ነው››

…ለአስራአምስት ምናምን አመት  አንድ አልጋ ላይ አብረን ተኝተን ምንም ያላደረግን ሰዎች..ይሄው ከሰርጎ በኃላ አብረን በተኛን በመጀመሪያው ቀን እንዲህ  የሰማይ መስኮት ተከፍቶ የጥፋት ዘንዶ በላያችን ተጠመጠመ… ከሲኦል ድንገት የተረጨ ሚመስል የመርገምት እሳት ሁለታችንንም ለብልቦ አቃለጠን፡፡
.በመጀመሪያ ቀን ወሲብ ፈፅመን ነግቶ በማግስቱ ስንነሳ  ከመተፋፈራችን የተነሳ አይን ለአይን መተያየትም ሆነ ቃል አውጥተን ምንም  ነገር ማውራት አልቻልንም ነበር…፡፡ሁለታችንም ቀኑን ሙሉ በፀፀት ስንብሰለሰልና  እና ግራ በመጋባት  ደንዝዘን  ነበር የዋልነው…፡፡

የሚገርመው ግን መሽቶ መልሰን ስንተኛ መልሰን ተመሳሳዩን ከመፈፀም እራሳችንን መግታት አልቻልንም…፡፡በአጠቃላይ ጥቅምት ላይ የዩኒቨርሲቲ ትመህርት ተከፍቶ  ተመልሼ ወደ አለማይ እስከምሄድ ድረስ ከሰባት ወይም  ስምንት ቀን በላይ ፍቅር ሰርተናል፤እና ደግሞ በስድስተኛው ወር ሊጠይቁኝ ሀለማያ ድረስ ከመስፍኔ ጋር  መጥተው እራሱ እሱን   ለሆነ ሰዓት ሸውደን ለብቻችን የመንሆንበትን ሁኔታ በማመቻቸት  ፍቅር ሰርተናል፡፡ስሜቱ አስቀያሚ  ግን ደግሞ በጣም ጣፋጭ ነበር..በተለይ መስፍኔን ፊት ለፊት ማየት ልብን ይሰብራል.፡፡
የሚገርመው ደግሞ በጣም ብዙ ብዙ ቀናት እሷ መሀል ሆና ሶስታችንም በአንድ አልጋ ላይ አንዳችንን በግራ እጇ ሌላችንን በቀኝ እጇ  እያቀፈች ብዙ በጣም ብዙ የመሳቀቅ ለሊቶችን እንድናሳልፍ አድርጋናለች…አይ ወንዶች በፍቅር አይናችን ከተጋረደ እኮ በቃ በጣም የዋህና ገራሞች ነን፡፡ከዛ ያው እሷ  እንደነገረቻችሁ የአሜሪካው ጉዳይ መጣና ዲ.ኤን.ኤ ምርመራ ምናምን ተባለ ሁሉን ነገር አደፈራረሰው..ሀጥያታችንን ፀሀይ ላይ ተሰጣ…..ሁሉ ነገር እንደምታውቁት ሆነ፡፡

ይቀጥላል
👍82🥰53
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ


#ክፍል_ሀያ_አምስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

////
ከጄኔራሏ ጋር ከአስራ አምስት ቀን በኃላ መገናኘታችን ነው፡፡ በጣም ናቃኛለች፡፡እኔም ሰሞኑን በጣም በተወጣጠረ እና በተጨናነቀ ሁኔታ ላይ ስለነበርኩ ላገኛት አልቻልኩም ነበር…እሷም ለምን እንደሆነ አላውቅም ላግኝህ ብላኝ አታውቅም ፡፡

‹‹እንዴት ነች ልጅህ?››

‹‹ደህና ነች…በጣም ደህና ነች››

‹‹ደህና ነች ስትል ፊትህ ላይ ብርሀን ይረጫል …ታድለሀል፡፡››

‹‹አዎ ..ትክክል ነሽ ታድያለሁ….በተለይ በአካል ካገኘዋት በኃላ ነው በጣም መታደሌን ያወቅኩት፡፡››

‹‹እናትዬውስ…?›

‹‹አናትዬው ምን….?››

‹‹ማለቴ ካየሀት በኃላ አላገረሸብህም?››

‹‹አይ እንዴት ያገረሽብኛል…በሩቅ አየኋት እንጂ በቅርብ አለላወራኋት..በዛ ላይ እህቴ እኮ ነች..››

‹‹መጀመሪያም እኮ እህትህ  ነበረች››

‹‹መጀመሪያማ አለመብሰልና ልጅነት ነው…››

‹‹ብለህ ነው…?››

‹‹አዎ….››

‹‹ይሁንልህ…ለማንኛውም ልሄድ ነው››

‹አልገባኝም….ገና አሁን መምጣትሽ እኮ ነው›

ፈገግ አለችና‹‹ማለቴ ሰሞኑን  መንገድ ልሄድ ነው..››

ይበልጥ ደንግጬ

‹‹ወደየት…?››

‹‹ግብፅ››

‹‹ግብፅ..ለምን …..?››

‹‹አባይን ተከትዬ…››

‹‹አትቀልጂ››

‹‹እሺ ለስራ …››

‹‹የምን ስራ…እዚህ  ስራ ጀምራለው ብለሺኝ አልነበረ እንዴ…?አንተንም አግዝሀለው አላልሺኝም ነበር?››

‹‹አዎ ብዬህ ነበር..ግን…››

‹‹ግን ምን…;?

ያው እንደዛ ከተባባልን በኃላ አንተ ጋር ሆነ እኔ ጋ ብዙ የተቀያየሩ ነገሮች ተፈፅመዋል…..ደግሞ አሁን ያገኘሁትን የስራ እድል በቀላሉ ገሸሽ ላደርው አልፈልግም፡፡››

‹‹ለመሆኑ ምንድነው ስራው…?››

‹‹አንባሳደር ሆኜ ነው የተመደብኩት…››

‹‹ወታደር አምባሳደር……;››
‹‹አዎ፡፡ ምን ችግር አለው…?ብዙ ሰዎች ምታበሽቁኝ ወታደር ተኩሶ ከመግደል ውጭ ሌላ ዕውቀት ያለው አይመስላችሁም….ወታደር እኮ እንደሌላው ሰው ከሙሉ ጭንቅላት ጋር የተፈጠረ ነው፡፡ማንኛውንም ትምህርት ተምሮ የየትኛውም እውቀት ባለቤት የመሆን ብቃትም አቅሙም አለው..እኔም ወታደር ከመሆኔ በተጨማሪ ላይ በውጭ ግንኑነትና ፖለቲካል ሳይንስ ዲግሪ እንዳለኝ አትርሳ…፡፡››

‹‹አረ አታምርሪ እኔ እንደዛ ማለቴ አይደለም…››

‹‹ባክህ ነው…የንግግር ቃናህ እራሱ ይሻክራል፡፡››

‹‹እሺ እንደዛ እንዲሰማሽ ስላደረኩ ይቅርታ ,.እኔ ግን ባትርቂኝ ደስ ይለኝ ነበር..››

‹‹አይ የምን መራራቅ አመጣህ፡ ከአሁን በኃላ እኮ ልንለያይ የማንችል ዘመዳማቾች ሆነናል፡፡አንተ እኮ የጋሽ አያና ልጅ ነህ..ወንደሜ ማለት ነህ;››
የእውነት ተደንቄም ተበሳጭቼም‹‹ግን የእኔ  እጣ ፋንታ  ምን አይነት ነው?››አልኳት ‹‹ምነው ምን ሆነ? ››

‹‹እንዴት ምን ሆነ ትያለሽ..?ዘላለሜን የማፈቅረው እህቶቼን መሆኑ አይገርምም?››

‹‹የማፈቅረው….ከእኔ ፍቅር ይዞሀል እንዴ?››

‹‹እየቀለድሽ ነው….?ካገኘውሽ ከመጀመሪያዋ ቀን ጀምሮ አንቺን ከማፈቀር ውጭ ሌላ ምን ስራ አለኝ ብለሽ ነው››

ዝም አለች……..አንገቷን አቀረቀረችና ለደቂቃዎች በዝምታ ተውጣ አሰበች…እና እንደምንም ፈገግ ለማለት እየጣረች

‹‹ለማንኛውም ይሄንን ርዕስ ለጊዜው እንርሳው››አለችኝ፡፡

‹‹ለጊዜው ማለት?››

‹‹ለጊዜው ማለትማ …ጊዜ የራሱን መልስ አዘጋጅቶ በየልባችን ሹክ እስኪለን በነበረበት ተከድኖ ይቀመጥ ማለቴ ነው፡፡››

‹‹ይሻላል?›››

‹‹አዎ ይሻላል…ሳረሳው የፊታችን እሁድ እቤቴ ሽኝት ፕሮግራም አዘጋጅቼያለሁ.. ልክ 7 ሰዓት እንድትገኝ››

‹‹እኔ?››

‹‹አዎ አንተ..ዋናው የክብር እንግዳዬ ነህ››

‹‹አረ በፈጣሪ እኔ ፓለቲከኞችና ባለስልጣናት ያሉበት ቦታ መገኘት ይጨንቀኛል፡፡››

‹‹አይዞህ አታስብ…ግብዣው ላይ ሚገኙት ጓዶኞቼ እና ጥቂት ዘመዶቼ ናቸው፡፡ ተጋባዦቹ ከአሰር አይበልጡም፡፡››

‹‹እንደዛ ከሆነ እሺ…››
እጇን ወደ ቦርሳዋ ከተተችና ፖስታ ይዛ ወጣች…ከዛ ሰጠችኝ

‹‹ምንድነው?››

‹‹የጥሪ ካርድ››

‹‹በቃል ነገርሺኝ አይደል…አይበቃም፡፡››

‹‹አይ ለአንተ አይደለም››

‹‹እናስ?››

‹‹ ለአያትህ››

በጣም ደነገጥኩ..እስኪ ምን ሚያስደነግጥ ነገር አለ‹‹እየቀለድሽ ነው…?››

‹‹አንተ ምን  አስጨነቀህ..ብቻ የታሸገውን ፖስታ ሳትነካካ ወስደህ ስጣቸው…. መምጣትና አለመምጣቱን እሳቸው ይወስኑ››

‹‹ቀልደኛ ነሽ…እኔማ ምን
ቸገረኝ እሰጠቸዋለሁ…ውሳኔያቸውን ግን እኔው ልንገርሽ  አይመጡም… አታስቢው፡፡››

‹‹እሺ አንተ ብቻ ስጣቸው፡፡››
ተቀብዬ ኪሴ ከተትኩ
////
በተባለው እሁድ ቀን የልቤ ሰው የሆነችውን የጄኔራሏን የሽኝት በአል ላይ ለመታደም…ለዝግጅቱ የሚመጥን ሽክ ያለ አለባበስ ለብሼ አምሬና ተሸቀርቅሬ በእጄ ደግሞ ይመጥናታል ያልኩትን የማስታወሻ ስጦታና አንድ ጠርሙስ ውስኪ አንጠልጥዬ ልክ ከቀኑ ሰባት ሰዓት መኖሪያ ቤቷ በራፍ ላይ ተገኘሁ፡፡ወደውስጥ ለመግባት ግን ትንሽ አመነታሁ፡፡ውስጥ የማገኛቸውን የማላውቃቸው ሰዎች ጋር እንዴት ብዬ እንደምግባባቸውና እንዴት አይነት ጊዜ አብሬያቸው ላሳልፍ እንደምችል ሳስበው ጨነቀኝ…በተለይ እኛ ጄኔራል የቀድሞ ወዳጇ ተጠርተው ከሆነ ሙዴ ሁሉ ነው የሚከነተው…ለማንኛውም ምርጫ ስለሌለኝ እራሴን አበረታትቼ ወደግቢው ዘልቄ ገባሁ….በሩቅ በረንዳ ላይ አንድ ታዳጊ ልጅ ትታየኛለች…እየቀረብኩ ስመጣ የማየውን ማመን ነው ያቃተኝ ፡፡ልጅተቷ እኔን ሳታይ ተመልሳ ወደውስጥ ሮጣ ገባች ፡፡
በዛች ቅፅበት ምንም ነገር ማሰብ አልቻልኩም።ልክ ልጅቷ እንደወፍ በራ የምታመልጠኝ ይመስል በሩጫ ተከተልኳት……ታአምር ታምሬ እያልኩ ተንደርድሬ ወደቤት ገባሁ።አንድ እግሬን እቤት ውስጥ አንድ እግሬን በረንዳ ላይ አድርጌ ከነሀስ እንደተሠራ ሀውልት ተገትሬ ቆምኩ።ውስጥ ሳሎኑ ሙሉ ነው። የሚገርመው ደግሞ ሁሉንም ሰዎች አውቃቸዋለሁ… በቀጣይ ምን ማድረግ እንዳለብኝ እንዲህ ግራ ገብቶኝ አያውቅም።ወደኃላ ተመልሼ ሮጬ ማምለጥ ወደፊት ሄጄ ሁኔታዎችን መጋፈጥ.."ሁለቱንም ለማድረግ አእምሮዬን መጠቀም ሰውነቴንም ማዘዝ አልቻልኩም።

ጄኔራሏ  ከሌላኛው ክፍል ወጣችና ቀጥታ ወደእኔ መጣች "እንዴ ግባ እንጂ"
ስሬ ደርሳ ክንዴን ቀጨም አድርጋ ያዘቺኝ እና ጎትታ ከተቸነከርኩበት አነቃነቀችኝ።ከውስጥ አፍጥጠው ከሚያዩኝ ሰዎች መካከል አንድ አዛውንት ወደእኔ መንቀሳቀስ ጀመሩ..ማን እንደሆኑ መገመት አትችሉም፤አያቴ ናቸው።ከሶስት አመት በኃላ እንዴት ክፍላቸውን ለቀው እዚህ ሊገኙ ቻሉ?የጥሪውን ካርድ በሰጠዋቸሁ ቀን ፈፅሞ እንዳላስበው በማያሻማ ቋንቋ ነግረውኝ እኔም አምኜያቸው ነበር….እና ታዲያ እንዴት ሀሳባቸውን ቀየሩ?ይሄ ነገር ህልም  ይሆን እንዴ ?
‹‹ና በል አክስትህን ይቅርታ ጠይቅ።›አያቴ ናቸው የተናገሩት፡

ካለሁበት ድንዛዜ ድንገት ባንኜ በአየር ላይ እንደመንሳፈፍ ተንደርድሬ አክስቴ እግር ስር ድፍት አልኩ… እሷም ፈጥና ልታነሳኝ ትከሻዬን ለመያዝ ብትሞክርም እንደምንም አመለጥኳትና እግሯ ስር ተደፍቼ በእንባ እየታጠብኩ ‹‹እቴትዬ በፈጣሪ ይቅር በይኝ..አሳፍሬሻለሁ.››የመጣልኝን ቀባጠርኩ፡፡

ይቀጥላል
👍1067👏1
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///

እኔ ይቅርታዬን ሳልጨርስ ምስርም ካለችበት ተንደርድራ መጥታ ልክ እኔ እንዳደረኩት እቴቴ እግር ስር ድፍት አለች።አንዳንድ እግር ተከፍፋልን ።እቤቱ ለቅሶ በለቅሶ ተደበላለቀ።ተረባርበው ሁለታችንንም ከተደፋንበት አነሱን ..እንደተነሳን በግራና ቀኝ ትከሻዋን ተከፋፍለን ተጠመጠምንባት፡፡ ተአምርን ጨምሮ ሌሎቹም እየመጡ ተቀላቀሉን። መላቀሱና መሳሳሙ አልቆ ስርአት ይዘን ለመቀመጥ ምን አልባት ከ20 ደቂቃ በላይ ሳይፈጅ አልቀረም።የዛ ሁሉ አመት ስቃይ….የዛ ሁሉ ጊዜ ቁጭትና ፀፀት ….የዛ ሁሉ ለሊትና ቀን የልብ ድማትና የጨጓራ ቁስለት እንዲህ በአስር ደቂቃ የይቅርታ ቃላቶች እና መላቀሶች መሻሩእና መጠገኑ የሚገርም ነው፡፡ይቅርታ የሚባል ነገር ባይኖር የሰው ልጅ ጠቅላላ ህይወቱ ምን መልከ ይኖረው ነበር ?ብዬ አሰበብኩና ዝግንን አለኝ ፡፡ብቻ ቀስ በቀስ መረጋጋቱ ሲመጣ ወደ ጫወታና መሳሳቅ ገባን።

"አያቴ ግን እንዴት..?"እኔ ነኝ ለመጀመሪያ ጊዜ አያቴን ፊት ለፊት በአካል ከእነአዛውንት ውበቱና ግርማ ሞገሱ በማየቴ እየተደመምኩ የጠየቅኩት፡፡

"እንዴት ምን..?"

"ዛሬ እንዴት ወጡ..አታስበው አልመጣም ብለውኝ ነበርኮ"

‹ሀሳቤን ቀየርኮ…ይሄ ተአምራዊ ቀን እንዲያመልጠኝ ፈፅሞ አልፈለኩም..ስለልጅህ ስለአክስትህ በአጠቃላይ ስለመላው ቤተሠብ ለሁለት አመት በእየለቱ ስታወራልኝ ስለከረምክ ለእኔም ልክ እንደቤተሠቤ ነበር የሚናፍቁኝ.ጄኔራል ሁኔታውንና የተቀደሰ ሀሳቧን አብራርታ ስትነግረኝ በእንቢታዬ መግፋት አልቻለልኩም።"

‹‹እሱሰ እውነቷትን ነው አያቴ. ግን ይሄ በጣም የሚገደርም ውሳኔ ነው ?መቼስ ጋሼ ይሄንን ቢያይ ተገርሞም አያባራም…››

ከዛ ብዙ ብዙ ጫወታ ተጫወትን..ምሳ ቀረበ የሚጣጡ መጠጦች እንደየምራጫችን ታደሉን …በሳቅና ጫወታ ያወራረድን በደስታ ተመገብን፡፡
እስከ10 ሰዓት ስንጫወት ቆየንና ከሳምንት በኃላ ወይ እኔ ሄጄ ልጠይቃቸው ወይ ደግሞ ሁሉም ተሰብስበው እኔ ቤት ሊመጡ ተነጋገርንና እንዳመጣጣቸው ሸኘናቸው….በመጨረሻ እኔና ጄኔራሎ ብቻ ቀረን፡፡ከዛ የተደመምኩባቸውን ጥያቄዎች ተራ በተራ አቀርብላት ጀመር፡፡

"ግን እንዴት?"
"እንዴት ማለት?"
"እነ አክስቴን እንዴት አገኘሽ ?እንዴት አሳመንሻቸው?"

"ቀላል ነበር..የአንተን ማንነት ካወቅኩ በኃላ የወላጆችህን ቤት የተከራዪት ሰዎች ጋር ሄድኩና ያክስትህን ስልክ ተቀበልኩ …ከዛ ወደ ደብረብርሀን ሄድኩ።"
"ደብረ ብርሀን ድረስ?"
"ደብረብርሀን እኮ እዚሁ አዲስ አበባ አፍንጫ ስር ነች።"
"እሺ ይሁን .ከዛስ..?"
"ከዛማ ደረስኩና ደወልኩላት… የሞች እህቷ የድሮ ወዳጅ እንደሆንኩ ነግሬ የቤቷን አድራሻ ጠየቅኩ ።በቀላሉ ነገረችኝ፡፡ቀጥታ እቤት ሄጄ አዋዝቼ ስላንተ ነገርኳት።"

"በፈጣሪ ምን አለች ..?አልተበሳጨችም?"በከፍተኛ ጉጉት ጠየቅኳት

"ወይ መበሳጨት ..እዬብ በህይወት አለ ስላት እህተሽ ከመቃብር ወጣች ያልኳት ነው የመሠላት ..ለአንድ ሰዓት ስታለቅስ፤ ስትስመኘ፤ስትመርቀኝ ምኑን ልንገርህ..እውነት መሆኑን አላመነችም እህትቶችህ..በተለይ በተለይ እማ!!ያው ይገባሀል..አሁንም የፍቅር ስቃይ ፊቷ ላይ አለ…አሁንም በናፍቆት እየቃተተች ነው..አሁንም በማይድነው አጉል በሽታ ተለክፋ ትንፍሽ እንዳጠራት መሆኑን ሁኔታዎን ለደቂቃ አይቶ መረዳት ይቻላል።››

"ልጅህ ደግሞ።"
"ልጄ ምን?"
"አደገኛ አክተር ይወጣታል ..ልክ ስለአንተ ለመጀመሪያ ቀን እንደሰማ ሰው አብራ ስታዳንቅ ሳይ እኔ እራሴ ይሄ ልጅ ዋሽቶኛል እንዴ?በእርግጥስ የእውነት አግኝቶት ያውቃል? ብዬ እራሴን ለመጠየቅ ተገደድኩ"
"አዎ ቆቅ የሆነች ልጅ ነች ያለቺኝ"
"እስማማለሁ"
"እሺ አያቴንስ እንዴት አሳምነሽ አመጣሻቸው?"
ቀላል አልነበረም፣የጥሪ ካርዱን ባንተ በኩል ል እንዳልተስማሙ ከነገርከኝ ቡኃላ ያንተን አለመኖር እየጠበቅኩ ከሶስት ቀን በላይ መመላለስ ነበረብኝ..ቢያለፋኝም ተሳክቶልኛል።በዚህ አጋጣሚ ልንገርህ ..መቼም መቼም አያትህን እንዳታስቀይማቸው።የእውነትም እንደልጃቸው ነው የሚያዪህ።በጣም ነው የሚወድህ"
"አውቃለሁ..እኔም አያቴ ስላቸው ለማስመሰል አይደለም...የእውነት ከልቤ እንደዛ ስለሚሰማኝ ነው።
"ታድለህ"
እንዴት ታድለህ ልትይ ቻልሽ?"
"ብዙ ሰዎች ብዙ ደክመው ብዙ ጥረው የማይሳካላቸውን የሠው መውደድ አንተ በቀላሉ አለህ..አክስትህ..እህቶችህ.ልጅህ..አያትህ ..እኔ..ሁላችንም አምርረን እንወድሀለን "
"የእውነት ..?አንቺም አምርረሽ ትወጂኛለሽ?"
"ከዝርዝሩ ውስጥ የእኔ ነው አጠራጣሪው?"
"አይ እንደዛ ማለቴ አይደለም ..እንዲሁ አለ አይደል ..ለማረጋገጥ ነው የጠየቅኩት"
‹‹አይዞህ አትጠራጠር ..አንተ በጣም ውድድድ የማደርግህ ፤ታናሽ ወንድሜ ነህ?"
"በለው....አየሽ እድሌን?"
"እንዴት?"
"አሁን እኔ እህት የናፈቀኝ ይመስልሻል..?"
"አሁን እኳ ምርጫ የለህም ..የልጅህ እናት አሁንም እንደተራበችህ ነው..እርግጠኛ ነኝ አንተን ሳትይዝ ወደአሜሪካዋ አትመለስም።"
"ይዛኝ ሄዳስ?"
"እሱን እንግዲህ ጊዜ የሚመልሰው አስቸጋሪ ጥያቄ ይሆናል።››

"እሺ እንዳልሽ አሁን ትንሽ ጉዳይ ስላለችብኝ ልሂድ… ነገ እመጣና እዚሁ አድሬ እሸኝሻለሁ..ይቻላል አይደል?"
"በጣም ደስ ይለኛል።ጉንጯን ስሜ ተሠናብቼ ወጣሁ።››

ይቀጥላል
👍808😢2🔥1🤔1
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበር


#ክፍል_ሀያ_ሰባት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////

በስራ ጉዳይ ወዲህና ወዲያ ስሯሯጥ ቆይቼ ከምሽተ 3 ሰዓት ካለፈ በኃለ ነው ወደ ቤት የገባሁት፡፡ያው የተለመደ የወንደላጤ ቤቴን አየከፈትኩ ሳለ ስልኬ ተንጣረረ...በአንድ እጄ እየከፈትኩ በሌለው እጄ ከኪሴ አወጣሁና አየሁት፡፡ ልጄ ነች፡አነሳሁትና

‹‹ሄሎ የእኔ ጣፋጭ››

‹‹ያንተ ጣፋጭ አይደለሁም..ማለት እናቷ ነኝ››

‹‹ውይ እሪች ይቅርታ …ተአምር መስላኝ ነው››

‹‹አውቃለሁ..አንተ አልተሳሳትክም እኮ የደወልኩት በእሷ ስልክ ነው…አባትና ልጅ ግን የምትገርሙ ሴረኞች ናችሁ››

‹‹እንዴት ማለት››በራፉን ከፍቼ ወደውስጥ ከገባሀ በኃላ አልጋዬ ጠርዝ ላይ ቁጭ ብዬ ወሬዬን ቀጠልኩ፡፡

‹‹ምን እንዴት አለው…ሁሉን ነገር ሰማሁ….በሚስጥር መገናኘትና መደዋወል ከጀመራችሁ መከራረማችሁን….አረ ጭካኔያችሁ…. ከአንተ  ደግሞ የእሷ አይገረምም፡፡››

‹‹እንዴት?››

‹‹ሰው እንዴት ከገዛ እናቱና አያቱ እንዲህ አይነት ሚስጥር ሰውሮ መቆየት ይችላል….ለዛውም በዚህ እድሜዋ››

‹‹ያው የአባት ጉዳይ ሲሆን ይችላል.ልጄን ደግሞ ታውቂያታለሽ… ልክ እንደአባቷ እስማርት ነች፡፡››

‹‹ይሀቺ ጉራ አሁንም አለቀቀችህም››

‹‹ምነው ተሳሳትኩ አንዴ?››

‹‹አላልኩም….ለማንኛውም በጣም እንዳስደመማችሁኝም እንዳስቀናችሁኝም መናገር እፈልጋለሁ…ለመሆኑ አንተስ እንዴት ነህ…?››

‹‹ይመስገነው… ህይወት እንደጢባ ጢቢ አንቀርቅባ አንቀርቀባ ገና  አሁን በቅርብ ቀን ነው  እያረጋጋቺኝ ያለው››

‹‹በጣም አዝናለሁ››

‹‹ለምኑ?››

‹‹ከእኔ ጋር የሆነው ነገር ባይሆን ኖሮ አንተ አንዱንም ችግር አታይም ነበር…››

‹‹ተይ ተይ ..ችግሩር ያየሁት እኮ ሀገሪቱ ተምሬ በተመረቅኩት ሞያ ስራ ልትሰጠኝ ስላልቻለች ነው››

‹‹ያ እውነት እንዳልሆነ ሁለታችንም እናውቃለን››

‹‹እንዴት ማለት?››

‹‹አንተ ስራ አጣሁ የሚለውን እንደሽፋን ተጠቅመህ እራስህን እየቀጣህ ነበር...ቤተሰቦቼ ላይ ከሰራሁት መጥፎ  ስራ አንፃር የተሻለ ህይወት ፈፅሞ አይገባኝም ብለህ በመወሰን ነው በዝቅተኛ ህይወት ውስጥ እራስህን ዘፍቀህ በችግር በመዳከር እራስህን ስትቀጣ የኖረከው…እንጂ ሌላውን ተው አዲስአባ ወላጆችህ ትተውልህ የሞቱት ቤት እንዳለ ታውቃለህ….ባንክ ውስጥም ቢያንስ ከግማሽሚሊዬን ብር በላይ ትተው መሞታቸውን ከቤት ኪራይ እየተሰበሰበ ለዘመናት የተጠራቀመው ብር  እንዳለ ታውቃለህ… ይሄ ሁሉ ሀብት ያለው ሰው በጤናው የፓርኪንግ ሰራተኝነት እና የሆቴል አስተናጋጅ ሆኖ የወጣትነት ህይወቱን አይገፋም…ለዛውም ባለዲግሪ ሆኖ..

‹‹ትክክል ልትሆኚ ትቺያለሽ…..እኔ ግን በዚህ መንገድ አይቼው አላውቅም…እኔ ያምትይውን ብር ሆነ ቤት መጠቀም ያልቸልኩት ሳልፈልግ ቀርቼ ሳይሆን እሱን ለመጠቀም የእቴቴን አይን ማየት ስላልፈለኩ ነው፡፡››

‹‹ተው ተው..ትንሽ ካሰብክበት እኮ የእቴቴን አይን ሳታይ የሚገባህን ንብረትህን እጅህ ማስገባት ትችል ነገር››

‹‹ተይ ተይ .እንደምታስቢው ቀላል አልነበረም››

‹‹አውቃለሁ… ግን ያደረከው ያልኩትን ነው እራስህን መቅጣት.እኔም አኮ ስላደረኩት ነው እንደዛ የምልህ…..?››

‹‹እንዴት?››

‹‹ያው እደምታየኝ አምሮብኛል ሰውነቴ አብረቀርቆል..ግን አሜሪካ ያሳለፍኳቸውን ስድስት አመቶች እንደምታስበው  እንዳይመስልህ.. ከጥዋት እስከ ሊሊት ከሶስት በላይ ስራ እሰራለሁ..ብዙ ብዙ ገንዘብ አገኛለሁ..የማያስፈልገኝን ገንዘብ ለማግኘት ማለት ነው እንደዛ እለፋ የነበረው..  ማንንም አላገኝም ..የትም ሄጄ መዝናናት አልፈልግም….የሳምንት እረፍቴ ከስድስት ሰዓት አይበልጥም ነበር…ማን መሆኔን እራሱ ዘንግቼ በድኔ ልክ እንደሮቦት ሆኜ ነበር የምንቀሳቀሰው…አሁን በቅርብ ጊዜ ግን ይህ ጉዳይ እንዴት ነው..?ለምድነው እንደዚህ የምለፋው..?የምሰበስበው ገንዘብ ለማን ብዬ ነው….?ብዬ ሳስብ  በጣም ግራ ተጋባሁ እና ባለሞያ ጋር ሄድኩ.. ባለሞያውም የህይወት ታሪኬን ካስለፈለፉኝ በኃላ በስተመጨረሻ የደረሰበት መደምደሚያ የምሰራው ስራ ሁሉ እራስን መቅጣት እንደሆነ እና  ከዚህ ወጥመድ የመውጫው መንገድ ግን ይሄ እንዳልሆነ መከረኝ….ለዛ ነው ካለእቅዴ ድንገት ወደሀገሬ ፈጥኜ የመጣሁት..መድሀኒቱ እዚህ ስለሆነ…››

‹‹አልገባኝም›አልኳት

የእውነትም ስላልገባኝ፡፡
‹‹አየህ ያባለሞሞው ውሳኔዬ በጣም ትክክል ነበረ..ይሄው ወደ ሀገሬ ከተመለስኩ በኃላ ካስብኩት በጣም በፈጠነ ጊዜ መድሀኒቱን አግኝቼ እየታከምኩ ነው…አንተን ማግኘትና ያለህበትን ሁኔታ መረዳት ችያለሁ….ይህ ማለት በእየለቱ የት ወድቆ ይሆን በሚል እምሮዬን ሲበላኝ የነበረው ነገር አሁን ድኖልኛል….ሌላው የእቴቴን ይቅርታ ማግኘት ችያለሁ…ያ ደግሞ ምን ያህል የአእምሮ ሰላም እንደሚሰጥ በራስህ ታውቀዋለህ…በነገራችን ላይ አባዬንም ይቅርታ ጠይቄዋለሁ.. አሁን የቀረኝ ትንሽ ነገር ነው…አንተን እና አባዬን ማገናኘት..››

‹‹አንተን እና አባዬን…?››ደንግጬ

‹‹አዎ ምነው ያንን ማድረግ አትፈልግም እንዴ?››

‹‹አረ በጣም ፈልጋለሁ..ግን እንዴት ብዬ አይኑን አያለሁ ?››

‹‹ልክ የማዬን አይን እንዳየህ..ደግሞ እኔ አፍጥጬ ሄጄ እሱን ማናገር ከቻልኩ አንተስ እንዴት ያቅትሀል?፡፡:ከዛ ከእማዬ ጋር መልሰን እናጋባቸዋለን…አንድ ላይ ሆነን ወላጀቻችንን ሆነ እህቶቻችንን አንክሳቸዋለን… በእኛ ምክንያት የቆሰለው ልባቸው ፈፅሞ እንዲድን የተቻለንን እናደርጋለን..ከዛ የእኛም ቁስል ቀስ እያለ ሙሉ በሙሉ ይድናል…ምን ይታወቃል የፈረሰ ተስፋችን መልሶ ይገነባ ይሆናል…እርግጠኛ ነኝ በመጨረሻ እራሳችንንም ይቅር እንላለን፡፡

‹‹አሜሪካ ተመልሰሽ እትሄጂም ማለት ነው?››

‹‹ሄዳለሁ.. ግን ለመኖር አይደለም…ሁኔታዎችን አመቻችቼ አንደኛዬን ጠቅልዬ እመጣለሁ..››

‹‹የእውነትሽን ነው?››
‹‹ምነው ደነገጥክ…እዛ ብኖር ይሻላል እንዴ?››

‹‹አረ እንደዛ ስለወሰንሽ በጣም ደስተኛ ነኝ››

‹‹በጣም ደስተኛ ለምን እንደሆንክ ማወቅ እችላለሁ?››

‹‹እንዴ ትቀልጂያለሽ እንዴ…አንድ ቀን ታአምርን ወደአሜሪካ ልውሰድሽ ብትላት ምንድነው የማደርገው? በሚል ስጋት እንዴት እየተሰቃየሁ እንደነበር ግምቱ የለሽም››

‹‹ይገርማል?››

‹‹ምኑ?››

‹‹መልስህ ያልገመትኩት ነው..ለልጅህ ባለህ ፍቅር ቅናት አደረብኝ››

‹‹እሷ እኮ የከሰመ ህይወቴን መልሳ ያለመለመችልኝ  ካሳዬ ነች. .ለእሷ ስል ህይወቴን እሰጣለሁ..››

‹‹በነገራችን ላይ አዲስአበባ ሪል እስቴት ገዝቼያለሁ..ስለዚህ ልክ ጉዳዬን ጨርሼ ከአሜሪካ እንደተመለስኩ ሁለችንም አንድ ላይ እንኖራለን ማለት ነው..››

‹‹አንድ ላይ ስትይ….?ማለት….?እንዴት…?››

የፈራሁት ነገር ዞሮ ሊመጣ ነው ብዬ በማሰብ ተርበበተበትኩ.

‹‹አይዞህ አትደንግጥ…ይሄውልህ እዬቤ እኔ አሁንም በጣም አፈቅርሀለሁ…እሱን ስሜቴን ካንተም ሆነ ከማንም መደበቅ አልችልም፡፡ደግሞም .አንተን ማፍቀር መቼም አላቆምም…ግን ደግሞ ከዚህ በፊት የሰራነውን ስህተት መቼም ደግመን እንድንሰራ አልፈልግምም፤ አልፈቅድምም….፡፡ይሄንን ደግሞ በቀደም እማዬ ሁለት  ጡቶቾን እስይዛ 
ነው ያስማለችኝ..ስለማልኩ ብቻ ሳይሆን የመጀመሪያውም ስህታችን ያስከፈለንን መከራ አይቼ ዳግመኛ ተመሳሳዩን ስህተት ለመፈፀም ጥንካሬው የለኝም፡፡.ቢያንስ ለእናቴ ስል….ለእህቶቼ ስል..ለአንተ ስል…፡፡ስለዚህ ምንም ስጋት አይግባህ
👍798🔥1🥰1😁1
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ+ነበረ


#ክፍል_ሀያ_ስምንት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////

ትንፋሽ ወሰድኩና ከመተኛቴ በፊት  ከአያቴ ጋር ለማውራት አፌን ከፈትኩ…አያቴ እንዳልተኙ በመብራቱ አለመጥፋት እና በዕቃ መንኳኳት ማወቅ ችያለሁ፡፡

‹‹አያቴ ጉዴን እየሰሙ ነው አይደል?››
መልስ የለም

‹‹አያቴ ይሰሙኛል?››
መልስ የለም

‹‹እንዴ..ያን የተለመደ ዝምታቸውን ጀመሩ ማለት ነው..?አሁን በዚህ ከእሳቸው ጋር ማውራት በፈለኩ ቀን ዝም ይላሉ..››ብዬ ተሰፋ በመቁረጥ ልተኛ ልብሴን ማውለቅ ስጀምር በጆሮዬ ደምፅ ሰማሁ፣፣

‹ምንድነው… አያቴ ሙዚቃ…?››ወደግድግዳው ተጠጋሁና ጆሮዬን ቀስሬ አዳመጥኩ….ውይ እለተ ምፅአት ደርሶል መሰለኝ…ከአያቴ ቤት የሲሊንዲዮን ዘፈን እየተሰማ ነው…፡፡

‹‹አያቴ እኔ አላምንም…ሰሞኑን በጣም እያስደመሙኝ ነው..ከቤት ለመውጣት መወሰኖት ሳያንስ ጭራሽ የፈረንጅ ሙዚቃ….በአንዴ ግን እንዲህ አይነት ለውጥ አይከብድም.?

አሁንም ፀጥታ ነው….

‹‹አያቴ ምንም የማያናግሩኝ ከሆነ በፊት ለፊት በራፍ ዞሬ መምጣቴ ነው..››

‹‹በፊት ለፊት በራፍ… ተው ይቅርብህ..አታድርገው››

‹‹ምን ?››የባሰ አለ ጆሮዬን ማመን አልቻልኩም

‹‹ሰምተሀል››
አዎ በደንብ ሰምቼያለሁ… አያቴ ቤት ሴት….አረ አይደረግም…እያናገረችኝ ያለችው ሴት ነች..ወጣት ሴት፡፡

‹‹አያቴ የሉም እንዴ?››
‹‹አያትህ የለም››ለስላሳ ለጋ የሴት ድምፅ መልስ ሰጠኝ፡፡
‹‹ይቅርታ ማን ልበል….?››ግራ በመጋባት ተሞልቼ ጠየቅኩ፡፡

‹በዚህ ውድቅት ለሊት ከአዲስ ሰው ጋር መተዋወቅ አይክብድም..?ይቅርታ ጥዋት እንተዋወቃለን… ባይሆን አሁን የአያትህን መልዕክት ተቀበለኝ..››

ከአያቴ ጋር እቃ ወደምንቀባበልበት ስንጥቅ አመራሁ...ለግላጋ ጠይም የእጅ እጣት ብጣሽ ወረቀት አቀበለኝ.. .ተቀበልኳት እና ወደአልጋው ተመለስኩ… ገለጥኩና ማንበብ ጀመርኩ፡፡

ልጄ ሳልነግርህ ይህን በማድረጌ ይቅርታ..ለአንድ ወር ወደገዳም ሄጄያለሁ…ትንሽ በፅሞና ከእግዚያብሄር ጋር ማውራት አምሮኛል…ልክ የዛሬ ወር ተመልሼ እመጣለሁ...እስከዛ የምወዳት የልጅ ልጄ ማራናታ ካንተ ጋር  እንድትቆይልኝ እፈልጋለሁ፡፡ያው ከሰሎሞን ሚስት ማለት ከእንጀራ እናቷ  ጋር አምርራ ስለማትስማማ እነሱ ጋር መቀመጥ አትችልም…እኔ ወደገዳም መሄዱን ቀድሜ የያዝኩት ቀጠሮ ነው…  ከእግዚያሄር ጋር የያዝኩትን ቀጠሮ ማስተጓጎል አልችልኩም…እሷ ደግሞ ድንገት መጣችብኝ….ግን ያው አንተ ልጄን ከእራሴ በላይ ስለማምንህ ልክ እንደእኔ አረገህ  ከእኔም በላይ እንደምትጠብቃትና እንደምትንከበከባት ቅንጣት ጥርጣሬ አይገባኝም…ቀንም ስራም ሆነ ሌላ ቦታ ስትሄድ ይዘሀት ሂድ…ማታም ጥለሀት ውጭ እንዳታድር..ነግሬሀለው አንተ ወሽካታ..ደግሞ ለእሷም እንዳታስቸግርህ ነግሬያታለሁ...አደራ አንተ ቀልማዳ እናንተ ሁለታችሁ በአለም ላይ እጅግ የምወዳችሁ የልጅ ልጆቼ ናችሁና ተመልሼ እስክመጣ በመደጋገፉ ጊዜችሁን በጥሩ ሁኔታ አሳልፉ.፡፡

ያንተው አያት ሙሉአለም ነኝ፡፡

‹‹እህት ይቅርታ ማራናታ ይሄ ምንድነው..?አያቴ ምንድነው የሰሩት?››

‹‹ያው አያትህ የሰራው እንዳነበብከው ነው›

‹‹እያሾፍሽ ነው እንዴ?››
‹አንተ እንዴት ነው የምታናግረኝ እንግዳህ እኮ ነኝ…ከደበረህ ነገ ጥዋት ተነስቼ ወደ ሀገሬ እበራለሁ..››

‹‹አረ በፈጣሪ ..ነገሩ ዱብ እዳ ሆኖብኝ እንጂ እንደዛ ማለቴ አይደለም...አሁን እራት በልተሻል..?››

‹‹አዎ በልቼያለሁ››
‹‹ሌላ የምትፈልጊው ነገር አለ….?››

‹‹አዎ አንድ ጠርሙስ ቢራ ባገኝ ደስ ይለኝ ነበር..››

‹‹እሺ አሁን አመጣልሻለሁ.››.ከአልጋዬ ተነሳሁና ጫማዬን ማድረግ ጀመርኩ

‹‹ምነው አለህ እንዴ?››ጠየቀችኘ
‹‹አይ የለኝም ግን አታስቢ አሁን ገዝቼ መጠለሁ. ምንድነው ሚመችሽ ማለት ጊርጊስ፤ በደሌ፤ሀረር ..››
‹‹አራት ሰዓት  እኮ አልፏል..የእውነት አሁን በዚህ ሰዓት ሄደህ ልትገዛልኝ ነው?›

‹‹አራት ሰዓት አይደለም ስድስት ሰዓትስ ቢሆን ምን ችግር አለው…የአያቴ አደራ እኮ  ነሽ…››

‹‹በል ስቀልድ ነው..አሁን አልፈልግም ነገ ትጋብዘኛለህ››

‹‹እውነተሽን ነው…?››
‹‹.አዎ አሁን ስለደከመኝ እንቅልፌ መጥቷል …ቻው ደህና እደር..››

‹‹ደህና እደሪ …ለሊት በማንኛውም ሰዓት የምትፈልጊው ምንም ነገር ቢኖር ንገሪኝ..››

‹‹ለሊት ምንም ነገር ብፈልግ?››ሳቅ ባፈነው ድምፅ

‹‹አዎ ምንም ነገር ብትፈልጊ..››

‹‹እሺ ነግርሀለሁ.. .አሁን ደህና እደር››

‹‹ደህና እደሪ›› ብዬ ሳደርግ የነበረውን ጫማ መልሼ አወለቅኩና ወደ አልጋዬ  ወጣሁ...ከልጅቷ ጋር በግድግዳ ወዲህ ማዶና ወዲያ ማዶ ሆነን የተነጋገርናቸውን ነገሮች መልሼ ሳስብ...ልጅቷ ልክ እንደ አያቴ ተንኮለኛ ቢጤ ነች መሰለኝ ስል አሰብኩና ፈገግ አልኩ…

ስለእዚህች ልጅ አያቴ ለብዙ ቀን አውርተውኛል..በየ15 ቀኑም ደብደቤ እየጻፉ እየሰጡኝ ለረጂም ጊዜ ፖሰታ ቤት ወስጄ የማስገባላቸው አኔ ስለሆንኩ ስለእሷ በመጠኑ አውቃለሁ..…ለምሳሌ የድሬደዋ ልጅ መሆኗን..ከእናቷ ጋር እንደምትኖርና… ጋሽ ሰለሞን የአሁኗን ሚስቱን ከማግባቱ በፊት እናትዬውን አግብቶ እሷን ከወለደ በኃላ እንደተፋቱ ከዛ እናትዬው ልጆን ይዛ ቤተሰቦቾ ጋር ድሬደዋ እንደገባች አውቃለሁ…አያቴም ከቤት አልወጣም ብለው እራሳቸውን ኳራንቲን ከማስገባቸው በፊት ቢያንስ በስድስት ወር አንዴ እየሄዱ እንደሚጠይቋት እሷም አልፎ አልፎ እየመጣች ትጠይቃቸው እንደነበረ መረጃው አለኝ ….ከልጃቸው ከጋሽ ሰለሞን በላይ ከእሷ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዳላቸውም አውቃለሁ....ሌላው በ1987 ዓ.ምህረት እንደተወለደች ነግረውኛል…ያ ማለት ይህቺ የሚቀጥለው ክፍል ውስጥ ያለች ወጣት አሁን 25 ዓመቷ ነው፡ በትምህርቷ በአካውንቲንግ ዲግሪ አላት…የእናቷ ቤተሰቦች ሀብታም ነጋዴዎች ስለሆኑ የራሷ ቡቲክ ከፍተውላት እየሰራች እንደሆነም አውቃለሁ...በቃ ስለእሷ የማውቀው ይሄንን ያህል ብቻ ነው ፡፡በተረፈ ቀጭን ትሁን ወፍራም..ቀይ ትሁን ጥቁር..ረጀም ትሁን አጭር ….ትሁት ትሁን መሰሪ ምንም አላውቅም….ምንም ፡፡ ግን ምንም ትሁን ምንም ለአንድ ወር የእኔ ኃላፊት ነች.. ፡፡ ያንን ኃላፊነት ደግሞ ያለምንም ማቅማማት በፍጽም ትዕግስት እና ብቃት እወጣለሁ...ምክንያቱም ያዘዙኝ አያቴ ናቸው..አሁን ልተኛ….ነገ ምን አልባት ረጅም ቀን ሊሆን ይችላል፡፡

ይቀጥላል
👍5944🔥4😁3👎1
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበር


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

ጥዋት የበረፍ መንኳኳት ነው ከእንቅልፌ ያባነነኘ…በርግጌ ተነሳሁና አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጥኩ…አሁንም በራፉ ይንኳኳል ግን የውጭ በራፍ ሳይሆን ከአያቴ ጋር የምንወሰነበት ተከፍቶ ያማያውቀው የውስጡ በራፍ ነው የሚንኳኳው…‹‹ውይ ልጅቷን ረስቼያት… በፈጣሪ ምን አይነት ዝፍዝፍ ሰው ነኝ? .እስከ አሁን እንግዳ እያለብኝ እንዲህ ነገር አለሙን ችላ ብዬ እተኛለሁ…?ይሄኔ እኮ እርቧት ይሆናል….?››

‹‹ማራናታ… ደህና አደርሽ?.››

‹‹አዎ ደህና አድሬያለሁ….ልግባ…ልብስህን ለብሰሀል?፡፡››ግራ አጋቢ ጥያቄ ጠየቀቺኝ፡፡

‹‹ውይ እሱ በራፍ የታሸገ ነው …ቆይ በፊት ለፊት ዞሬ መጣሁ..››

‹‹አይ እሽጉን ትናንት አያቴ አስነስቶት ነው የሄደው››…ከሚል ድምፅ ጋር የበር መንሳጠጥ ተሰማና ወለል ብሎ ተከፈተ..ውይ የተሰማኝ ስሜት…. በቅዱሳን መላዕክቱ የገነት በር ሲከፈት ፊት ለፊት በአይኖቼ እያየሁ  ያለሁ   ነው የመሰለኝ...እና ከበሩ መከፈትም በላይ በተከፈተው በራፍ አንገቷን አስቀድማ በማስገግ ብቅ ብላ ወደእኔ ግዛት የገባቸው ልጅ…  በፈጣሪ ሰይጣን አይደል እንዴ የምትመስለው፣ሰይጣን ክብሩን ከመገፈፉ በፊት…ለነገሩ ክብሩን ከተገፈፈም በኃላም ውበቱን አልተነጠቀም…

‹‹አንቺ ይገርማል..አያቴን አይደል እንዴ የምትመስይው?››ሳላስበው አድናቆት ከአንደበቴ አፈትልኮ ወጣ
‹‹ሽማግሌ ፊት ነው ያለሽ እያልከኝ ነው?››

‹‹ይቅርታ …ማለቴ በጣም ቆንጆ ነሽ ለማለት ፈልጌ ነው….››አዎ እውነቴን ነው …ልጅቷ ልክ አያቴን ነው የምትመስለው…ልቅም ያለች የጥቁር   ልጥልጥ  ውብ ነች…፡፡ልክ እንዳየኋት ልቤ ቢጫ ወባ እንደነደፈው ሰው ነው በደቂቃ ውስጥ ፍርፍር ስትል የተሰማኝ፡፡
‹‹ለማንኛወም ቁርስ መብላት ከፈለክ ና ቀርቧል….››ብላኝ በራፉን ክፍት ጥላ ተመልሳ ወደውስጥ ገባች፡፡እንግዳ ሲያፍር ባለቤት ይጋብዛል አሉ….ሲሆን ሲሆን ለሊት ተነስቶ ቁርስ በመስራት እሷን መቀስቀስ የነበረብኝ እኔ ነበርኩ..ዳሩ አጅሪቷ በየት አሲይዛ …በሁሉ ነገር ጥድፍ ጥድፍ ትላለች፡፡በፈጣሪ በዚህ አይነት አጀማመር ይህቺን አንድ ወር እንዴት ነው ተቋቁሜ የምዘልቀው…? አያቴ ምን ነካቸው..?ይሄንንማ አውቀው ሆነ ብለው እኔን ለመፈተን ያደረጉት ነገር ነው፡፡ወይ እዳዬ ለዘመናት ከዳከርኩበት እና ፍዳዬን ካየሁበት የፍቅር ታሪክ ገና ትናንትና መደምደማሚያ አበጅቼለት ተገላገልኩ ስል….

‹‹እዬቤ...››ጥሪው ከተዘፈዘፍኩበት ሀሳብ መዞ  አነቃኝ

‹‹አቤት››

‹‹ቁርሱ ቀዘቀዘ እኮ….በዛ ላይ እርቦኛል››

ተንደርድሬ ተነሳሁና ፊቴን ተለቃልቄ ልብሴንም ሳልቀይር በለበስኩት ቢጃማ ተንንርድሬ ሚቀጥለው ክፍል ገባሁ…..እንግዲህ ይታያችሁ እዚህ ቤት መኖር ከጀምርኩ ሶስተኛ አመቴ ውስጥ ብሆንም አሁን ያለሁበትን ክፍል ስረግጥና የውስጥ ገፅታውን ሳይ ዛሬ የመጀመሪያ ቀኔ ነው፡ክፍሉ በስርአት ቦታቸውን ይዘው በተቀመጡ የቤት እቃዎች የተሞላ ነው፡፡ ቢያንስ ሶስት ቦታ በመፅሀፎች የተሞሉ መደርደሪያዎች ይታያሉ…አልጋው በስርኣት ተነጥፏል፡፡  አልጋውን ተጠግቶ ያለው መካከለኛ መጠን ያለው ጠረጴዛ በምግብ ተሞልቷል…

‹‹ምን ይገትርሀል አልጋ ጠርዝ ላይ ቁጭ በል ››አለችኝ

የእሷን  ግብዣ ችላ አልኩና ግድግዳ ተደግፎ ያተቀመጠ አንድ ደረቅ ወንበር በማንሳት ወደምግብ ጠረጴዛው አስጠግቼ በመቀመጥ አንዴ የቤቱን ዙሪያ መልሼ ደግሞ እሷን ከስር አስከላይ መቃኘት ጀመርኩ… አቀራርባ ስትጨርስ ፊት ለፊቴ አልጋ ጠርዝ ላይ ቁጭ በማለት እሷም ለመብላት ዝግጁ ሆና እጇን ወደምግቡ እየሰደደች‹‹..በል ብላ››.አለችኝ..

‹‹ይሄን ሁሉ ምን ጊዜ ሰራሺው?››የገረመኝን ጥያቄ ጠየቅኳት.፡፡

‹‹እቤትህ ሰዓት የለም እንዴ..?ሶስት ሰዓት ሊሆን እኮ ነው››አመሏ ከመልኳ ተቃራኒ ነው..እስከአሁን እንዳየሆት ለየትኛውም ጥያቄ ቀና መልስ መስጠት አይሆንላትም…

‹‹ይቅርታ .እንቅልፍ ጣለኝ››

‹‹አያቴ ጠንካራ ሰራተኛ ነው እያለ ሲፎክርብህ የነበረው እንዲህ እየተኛህ ነው እንዴ?››

‹‹አጋጣሚ ሆኖ ነው..›› የጠቀለልኩትን ምግብ እየጎረስኩ መለስኩላት፡

‹‹እሺ ቢሾፍቱ ዛሬ ትወስደኛለህ ?››አዲስ ርዕስ ከፈተች

‹‹ለምን…?መሄድ ትፈልጊያለሽ?››
‹‹አይ የስራህ ቦታ እዛ አይደለ? ስራ ከሄድክ አብሬህ ለመሄድ ብዬ ነው››
‹‹እ ….እንደዛ ነው….ዛሬ ሳይሆን ነገ ነው የምሄደው ….ነገ አብረን እንሄዳለን….ዛሬ የሆነ ጓደኛዬን ከአገር ውጭ ስለምትሄድ እሷን እንሸኛለን››

‹‹እ… .ጄኔራሏን?››

‹‹ምን….?በምን አወቅሽ…?››.ደንግጬ

‹‹ይሄውልህ ስለአንተ የማላውቀው እንዲህ ቆንጆ መሆንህን ብቻ ነበር… አሁን ደግሞ እሱኑም አወቅኩ››ብለኝ እርፍ
‹‹እንዴት…?አሀ ይሄን ሁሉ የነገሩሽ አያቴ ናቸው?››

‹‹አዎ  አያትህ…በነገራችን ላይ አያቴ በየደብዳቤው ስለአንተ ሲዘበዝብልኝ በጣም እበሳጭበት ነበር››

‹‹ለምን? ቀንተሸ?››

‹‹አዎ ብቀና ይፈረድብኛል..?እኔ በአያቴ ቀልድ አላቅም...እና ብቸኛ የልጅ ልጁ ሆኜ መቀጠል ነበር ምፈልገው..››

‹‹እና አሁንስ?››ስል ጠየቅኳት በመገረም፡፡

‹‹አሁንማ አንደኛ አባቴ ከዛች የተረገመች ሚስቱ ሌላ ልጅ ስለወለደ ብቸኛ የልጅ ልጁ መሆኔ ማክተሙን አምኜ ተቀበልኩ ….ሁለተኛ እኔም ሳላስበው ታሪክህን ቀስ በቀስ ሲያስጠናኝ የእውነትም አያቴ አያትህ ይመስለኝ ጀመር…››

ተበሳጨሁ… ልጎርስ አፌ ላይ ያደረስኩትን ምግብ መልሼ ትሪው ላይ በትኜ ተነሳሁና‹‹ምን ለማለት ፈልገሽ ነው..?››አፈጠጥኩባት

‹‹አቦ ምን ለማለት ፈልገሽ ነው ማለት ምን ማለት ነው?››እሷስ መች የዋዛ ሆነችና በተቀመጠችበት መልሳ አፈጠጠችብኝ፡፡

‹‹አያቴ ስል ለማሾፍ ወይም ለፉገራ ይመስልሻል…?የእውነት አንቺ ከእኔ በላይ እራስሽን ባለመብት አድርገሽ መጎረርሽ ነው..?››ወረድኩባት
‹‹ባለመብቱንማ በተግባር አየነው እኮ…. እኔ እኮ አይደለሁም የአንድ ሚሊዬን ብር ቼክ የተፃፈልኝ…አሁን እንብር እንብር አትበል ቁጭ በልና ቁርስህን ጨርስ .ደግሞ አያቴን የነጠቅከኝ ሳያንስ ስድብ ትመርቅልኛለህ….አረ አይነፋም…››

በንግግሯ ተሸነፍኩና ተመልሼ ቁጭ አልኩ…ገና በመጀመሪያው ቀን ይሄን ያህል ከተጮጮህን ዋል አደር ስንል..ወይኔ ጉዴ…ጨነቀኝ፡፡

አንድ ክፍል ቀረው
👍17915😁11🥰4👎3🔥2
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበር


#ክፍል_ሰላሳ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

////

ከቁርስ ቡኃላ ልብስ ቀያየርንና ተያይዘን ወጣን….የተወሰኑ ጉዳዬች ስለነበረኝ እዚህም እዛም እሷን አንጠልጥዬ ስራራጥ ሰባት ሰዓት ሆነ…. ቁርስ ሰዓት ላይ ያቆምነውን ወሬ ሆቴል ገብተን ምግብ አዘን ምሳችንን እየበላን ቀጠልነው፡፡ የሚገርመው ደግሞ ወሬውን ድንገት የጀመረችው እሷ ነች….
‹‹አሜሪካዊቷ እስከመጨረሻው ቀይ አሻረችህ አይደል?››
‹‹ማ…?ለእኔ….?አልገባኝም››
‹‹ባክህ ማታ በስልክ ስታወሩ ሰምቼያለሁ››
‹‹አንቺ የሰው ሚስጥር ጆሮን ግድግዳ ላይ ለጥፎ ማዳመጥ ነውር አይደል እንዴ?››
‹‹እናንተ የመሀል ሀገር ሰዎች ደግሞ ኮተታ ኮተቱንም ሚስጥር ታደርጉታላችሁ..ግን የእውነት ሁለታችሁም አንጀቴን ነው የበላችሁት››
‹‹እንዴት?››
‹‹በቃ ፎንቃ ክፍኛ ነው የጠለፋችሁ….ታድላችሁ?››
‹‹እንዴ በዚህ ፍቅር ምክንያት ምን ያህል መከራ እንደተቀበልን ብታውቂ እንደዚህ አፍሽን ሞልተሸ ታድላችሁ አትይም ነበር….››

‹‹እንደእኔ በምቾትና በእንክብካቤ ዝም ብሎ አይነት ኑሮ ከመኖር በፎንቃ ተጠልፎ ስቅይትይት ማለት አይሻልም…?ምናለ በእሷ ቦታ እኔ በሆንኩ››
‹‹ጭረሽ….አንቺ ልጄ ቀልደኛ ነሽ ..››
‹‹እውነቴን እኮ ነው..››
ስልኬ ጠራ…የምጎርሰውን ጋብ አደረኩና አነሳሁት…. ጄኔራሏ ነች
‹‹እሺ ዜና..እንዴት ነሽ?››
‹‹አለሁልህ..››
‹‹ዝግጅትስ?››
‹‹ያው ሁሉን ነገር አጠናቅቄ አንተን መምጣት እየጠበቅኩ ነው››
‹‹የት ነሽ?››
‹‹እቤት ነኝ…››
‹‹ያው እንግዳ አለብኝ…እና ማታ ስመጣ ከእንግዳ ጋር ብመጠ ቅር ይልሻል?፡፡
‹‹አረ ፍፅም….ስራ ከሌላችሁ ለምን አሁን አትመጡም..››
‹‹አሁን?››
‹‹ምነው ስራ አለብህ እንዴ?››
‹‹አይ የለብኝም….ግን እንግዳ ያልኩሽ..››
‹‹አውቃለሁ ስለአያትህ የልጅ ልጅ ነው አይደለ የምታወራኝ…በቃ እጠብቃችኋለው… ይዘሀት ና..የእኔም እንግዳ እኮ ነች..ደግሞም ቆንጆ ነች አሉ…እንዴት ነው እውነት ነው እንዴ?›
‹‹አረ ተይኝ..ለማንኛውም እንመጣለን ቸው››ስልኩ ተዘጋ
ጭው አለብኝ..በዙሪያዬ ምን እየተካሄደ ነው…?እኔ መምጣቷን ሳላውቅ ማታ እቤት ስገባ ስላየኋት ጥቁር እንግደ ጄኔራሏ ቀድማ ታውቃለች…፡፡እንዴት..?እኔ ከነጋ ጀምሮ አሁን እንዴት ነው የማደርገው? እንግዳዋን እንዴት እሷ ጋር ይዤት ሄዳለሁ…?ጥያትስ አንዴት ሄዳው…?ምን ብዬስ መጥቼ እቤትሽ አድሬ እሸኝሻለሁ ካልኩ በኃላ እቀራለሁ …››እያልኩ ስብሰለሰል ቆይቼ ይሄው እሷ ሁለታችንንም በእንግድነት እሷ ቤት ሄደን እንደምናድርና አብረን እንደምንሸኛት ትናንትናውኑ ታውቅ ነበር
‹‹ምነው ፊትህን አጨማደድከው?››
‹‹አይ ነገሮች ግራ አጋብተውኝ ነው…ቅድም የነገርኩሽ ጎደኛዬ ጋር አብረን አንሄዳለን…››
‹‹ጄኔራሏ ጋ››
‹‹አዎ ጄኔራሏ ጋ››
‹‹ታፈቅራታለህ አይደል.?››
‹‹ማለት…?››
‹‹አትደንግጥ..ታድለሀል..ፍቅር በፍቅር የሆንክ ሰው ነህ…እኔንስ አንድ ቀን ምታፈቅረኝ ይመስልሀል?››
‹‹ምን አልሽ?››
‹‹አረ አትደንግጥ…ለፈገግታ ነው…ምነው ይሄን ያህል ፍቅር አንገሽግሾሀል እንዴ..?››
ወይ ጉድ ይህቺ ልጅ በቅርቡ እጄ ላይ ምትፈነዳ አደገኛ ፈንጅ ነች‹…አቶ እዬብ ፈተናህ ገና አላለቀም….ወይ አያቴ ከችግሮችህ ሁሉ ቀስ በቀስ ተላቀቅ ብለው መክረውኝ እንድወጣም አግዘውኝ ከብዙ ጥረት በኃላ አብዛኛው ተሳክቶልኝ ነፃ ልወጣ የድል ሪባኑን ልበጥስ መቀሱን እያስተካከለልኩ እያለሁ እራሳቸው ወደተመሳሳይ ችግር የሚጎተት ሌላ ፈተና ያስታቅፉኛል..?ምሳ ጨርሰን ሂሳብ ከፍለን በራይድ ወደ ጄኔራሏ ቤት እየሄድን ሳለ
‹‹እዬቤ በርጫ ገዝተን ብንሄድ ጄኔራሎ ይደብራታል?››ስትል ቀለል አድርጋ ጠየቀቺኝ፡፡
‹‹ትቅሚያለሽ እንዴ?››
‹‹ምነው ?መቃም እንዲህ ያስደነግጣል እንዴ?››
‹‹አይ…ስላልመሰለኝ ነው….ችግር የለውም ስንቃረብ እንገዛለን.››
ወዲያው ስልኬ ጠራ….ወይ ልጄ ደወለች አልኩና አነሳሁት
‹‹የእኔ ማር… የእኔ ጣፋጭ እንዴት ነሽ?››
‹አለሁ አባዬ….እሁድ እንደምንመጣ ታውቀለህ አይደል?››
‹‹አዎ አውቃለሁ…እናትሽ ነግራኛለች.እናም በናፍቆት እየጠበቅኩሽ ነው››
‹‹እሺ እሱን ልንግርህ ነው የደወልኩት…››
‹‹ስለደወልሽ ደስ ብሎኛል››
‹‹የት ነህ አባዬ መኪና ውስጥ ነህ እንዴ..ድምፅ ይሰማኛል››
‹‹አዎ የእኔ ልጅ ….ታክሲ ውስጥ ነኝ….አያቴን ታውቂያቸዋለሽ አይደል?
‹‹አዎ አውቃቸዋለህ… ከእሷቸው ጋር ነህ?››
‹‹አይ ከእሳቸው ጋር ሳይሆን ከልጃቸው ጋር የሆነ ቦታ እየሄድን ነው…ማራናታ ትባላለች ፡፡ስትመጪ ከእሷ ጋር አስተዋውቅሻለሁ››
‹‹እሺ አባዬ ሰላም በልልኝ››
‹‹ቸው እሺ ልጄ›ሥልኩ ተዘጋ
ጊዜ ሳታባክን ጥዝጠዛዋን ቀጠለች‹‹ከልጅህ እያስተዋወቅከኝ ነው እንዴ?››
‹‹አዎ እሁድ ቤተሰቦቼ ሁሉ ይመጣሉ ….ልጄም ትመጣለኝ …አብራን ስታየን ማን ነች ብላ ስትጠይቀኝ በቀላሉ አስረዳታለሁ ማለት ነው፡፡››
‹‹ለእሷ ብቻ ነው..ወይስ ለቤተሰብህ ሁሉ ነው የምታስተዋቀውቀኝ ?››
‹‹አሁን ይህ ምን የሚሉት ጥያቄ ነው፡፡አዎ…የአያቴ የልጅ ልጅ ነሽ….እቤተሰቤ ነሽ ማለት ነው፡ስለዚህ ከሁሉም ጋር አስተዋውሻለሁ››
‹‹እንደዛ ስላልክ ደስ ብሎኛል…..አክስትህ ግን የአያቴ ልጅ ነች ብለህ ብታስተዋውቀኝ ብዙም ደስ አይላትም››
‹‹ለምን…?አክስቴ ምን እንደምትፈልግ በምን ተውቂያለሽ….?አክስቴ እኮ ከአያቴ ጋ ተዋውቀዋል…አያቴ ማለት ለእኔ ምን እንደሆነ እና ምን እዳደረገልኝ በዝርዝር ነግሬታለሁ፤ በዛም የተነሳ በጣም የምታከብረው ሰው ነው……እንደውም አንቺ የእሱ የልጅ ልጅ በመሆንሽ በደስታ ነው የምትተዋወቅሽ››
‹‹አውቃለሁ ግን ፍቅረኛህ ብሆንና ይህቺ ፍቅረኛዬ ነች ብለህ ብታስተዋውቀኝ እንዴት ፍፅማዊ ደስታ እንደምትደሰት ይታየኛል››
‹‹እንዴት እንደዛ ልትይ ቻልሽ?አክስቴን እኮ በደንብ ምታውቂያት ነው ያስመሰለሺው››
‹‹እኔን ከስጋት ትገላግለኛለች ብላ ተስፋ ታደርግ ነበር .እሷ እኮ አሁንም እነዚህ ልጆች መልሰው ይሳሳቱ ይሆን ብላ እንቅልፍ ተኝታ አታድርም…ታዲያ አንተ እኔን የመሰለች ፍቅረኛ አግኝተህ ወስደህ ብታስተዋውቃት… ታየኝ፡፡እንዲሁ ስለምታሳዝነኝ እንደዛ ብለህ ብታስተዋውቀኝ አይከፋኝም….ምን ችግር አለው? አያታችን ከሄደበት እስኪመለስ የእቃቃ ፍቅረኛ ፍቅረኛ እንጫወትና ከእዛ ተጣልተን ተለያየን ብለን እናውጃለን…እስከዛ ሴትዬህም ወደአሜሪካዋ ተመልሳ ስለምትሄድ ችግር አይኖረውም..
‹‹ውይ ምን አይነት ጉድ ነሽ.?ሳትቅሚ እንደዚህ የለፈለፍሽ ከምርቃና ቡኃላ እንዴት ልትሆኚ ነው?››
‹‹አይዞህ ሀሳብ አይግባህ…ከመረቅንኩ ስሬ ኒዩክልር ብታፈነዳ እንኳን ከአንደበቴ ቃል አይወጣም….››
‹‹እንደዛ ከሆነማ ጫቱን አሁኑን ልግዛልሽ ‹‹.ሹፌር ምቹ ቦታ ስታገኝ ታቋምልኝ….?እቃ ገዛለሁ››

ተፈፀመ
👍149🤔52👎10👏6😱52😢2