#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
አማላጅ
ከራሳቸው ሃሳብ ጋር ሙግት ገጥመዋል ፡፡ እሽ ይሉኝ ይሆን ? ወይስ እንቢ ? እንደገና ደግሞ በአንዴማ እንቢም ፤ እሽም አይሉኝም ፡፡ እያሉ ሳይታወቃቸው ቄስ መልካሙ ቤት ደረሱ፡፡ ለመጣራት ወደ አጥሩ ተጠጉ ፡፡ እንደ አጋጣሚ ሆኖ ቄስ መልካሙን ግቢያቸው ውስጥ መፅኃፍ እያነበቡ ተመለከቷቸው ፡፡
መጣራታቸውን ትተው "ደህና አደራችሁ መልካሙ" ? አሉ፡፡ ቄስ አሻግሬ ፤
አቀርቅረው ከሚያነቡት መፅሃፍ ላይ አንገታቸውን ቀና አድርገው "እግዚአብሔር ይመስገን ሰላም አደሩ" ? አሉ ፡፡ ቄስ መልካሙ፡፡ ንስሃ አባታቸው ያለወትሯቸው በጥዋት በመምጣታቸው የመደናገጥ ምልክት እየታየባቸው ፡፡ ፀበል ሊረጩን ይሆን ? ሳንነግራቸውና ሳንዘጋጅ ፤ እነሱም ሳይነግሩን ፤ በሰላም ይሆን የመጡት? ከራሳቸው ሃሳብ ሳይወጡ የተናገሩት ነበር
"አንተን ፈልጌ ነበር የመጣሁት"፡፡ እደጅ ላግኝህ አሉ ቄስ አሻግሬ ፡፡ ለስለስ ባለ አነጋገር ፡፡
"ለምን እንደተፈለጉ ባያውቁም "ምነው ደህና አይደሉም እንዴ"?
አይ ደህና ነኝ ፡፡ ለጉዳይ ፈልጌህ ነበር አሉ
ከየት መጀመር እንዳለባቸው ግራ ቢገባቸውም "አቶ ለማ ልጅህን ለልጄ እንዲሰጡኝ አማላጅ ሂድልኝ ብሎኝ ነው የመጣሁት"፡፡ ብለው ሃሳባቸውን ሳያቋርጡ በመቀጠል አቶ ለማ ሽፈራው ጥሩ ሰው ናቸው፡፡ ዘራቸውም ቢሆንም ምንም አይወጣለትም ፡፡ ልጁም የተባረከ ፤ የተመሰገነ ፤ ጨዋ ፤ ድምፁም የማይሰማ ማለፊያ ገበሬ ነው" አሉ፡፡
ቄስ መልካሙ ያልጠበቁትና ያላሰቡት ነገር ሆነባቸው፡፡ ለጊዜው ምን ማለት እንዳለባቸው አብሰለሰሉ፡፡ የማይሆን ነገር ነው፡፡ አሁን እድላዊትን አግቢ ብላት ትምህርቷን ትታ የምታገባ አይመስለኝም፡፡ ከራሳቸው ሃሳብ ጋር እየተሟገቱ ከቆዩ በኋላ "እንግዲህ
ከቤተሰብና ዘመድ ጋር መክረን መልስ ብንሰጥ ይሻላል፡፡ አሁን እኔ ለብቻየ የምወስነው ነገር የለም" አሉ፡፡ ሆዳቸው እንደመባባት እያለም ቢሆን፡፡
"ታዲያ ቀነ ቀጠሮው ለመቼ ይሁን" ? አሉ፡፡ መቼም በአንዴ እሽ እንደማይባል የአገሩ ባህልና የተለመደ መሆኑን ስለሚያውቁ ፡ተመልሰው የሚመጡበትን ቀን በጉጉት ለመስማት እየጠበቁ ፡፡
"ዛሬ ቀኑ ሮዕብ አይደለም፡፡ የዛሬ አስራ አምስት ቀን ይመለሱ፡፡ እኛም እስከዛ ብንመካከርበት ይሻላል" በማለት መልስ ሰጧቸው፡፡
ይሁን መልካም ነው፡፡ ብለው የተሰጣቸውን ቀነ ቀጠሮ ተቀብለው ከቄስ መልካሙ ጋር ተሰነባብተው ወደ ቤታቸው ተመለሱ፡፡
ንሰሃ አባታቸውን ከሸኙ በኋላ ፤ ወደ ቤታቸው ገቡ፡፡ በመጨጊያቸው ላይ ተቀመጡ፡፡ አገጫቸውን በቀኝ እጃቸው ደገፍ አደረጉ፡፡ ትክዝ ባለ አንደበት ስለልጃቸው እድላዊት በውስጣቸው ማብሰልሰል ተያያዙት፡፡
ወ/ሮ አሰገደች ከማድቤት ወጥተው ወደ መኖሪያ ቤት እየሄዱ ባለቤታቸው ከወትሯቸው በተለየ ተክዘው ተመለከቷቸው፡፡ እርምጃቸውን ገታ አድርገው "ምነው ቄስ አሻግሬ አመጣጣቸው በደህና አይደለም እንዴ"? አሉ ፤ ለባለቤታቸው ፡፡
"አይ ደህና" ናቸው ፤ አሉ፡፡ ሃዘን ይሁን ትካዜ በተቀላቀለበት ንግግር፡፡
ወ/ሮ አሰገደች የንሰሃ አባታቸው ዛሬ በጥዋት አመጣጣቸው ለምን እንደሆነ ባያውቁም የባለቤታቸው መተከዝ አስጨንቋቸዋል፡፡ "በሰላምማ አልመሰለኝም" አሉ፡፡ ወደ ባለቤታቸው እየተጠጉ፡፡
"የመጡትስ በሰላም ቢሆንም አቶ ለማ ሽፈራው አማላጅ ልከዋቸው ነው የመጡት" አሉ፡፡ የባለቤታቸውን ሁኔታ እየተመለከቱ፡፡
"የምን አማላጅ ነው?" አሉ፡፡ ሆዳቸው እንደመርበትበት እያለ፡፡ የምን አማላጅነት እንደሆነ ለመስማት በመቸኮል፡፡
የአቶ ለማን ልጅ ታውቂዋለሽ ?"፡፡
"ትንሹን ነው ትልቁን?፡፡
"አይ! ትንሹን ይሁን ትልቁን አለየሁትም፡፡ አበበ የሚባለውን፡፡
ምን እንደሆነ ሳያውቁ "በሞትኩት ምን ነካው ያምስኪን ልጅ ከሰው ተጣላ" እንዴ ?፡፡
"እሱስ አልተጣላም፡፡ አቶ ለማ ሽፈራው እድላዊትን ለአበበ ስጡኝ ብሎ ነው፡፡ ቄስ አሻግሬን አማላጅ ተልከው የመጡት"፡፡
ወ/ሮ አሰገደች ለመስማት የጓጉትና ልባቸው ተንጠልጥሎ ሲጠብቁት የነበረው ምን እንደ ሆነ ባያውቁም ከባለቤታቸው የሰሙት ያልጠበቁትና ያላሰቡት ሆነባቸው፡፡ ለጊዜው መርዶ እንደ ተነገራቸው ያህል በዝምታ ተዋጡ፡፡ በሃሳባቸው ልጄን እማ አልሰጥም አስተምራለሁ፡፡ ትምህርቷን ሳትጨርስ አልድራትም፡፡ እሷም እሽ አትልም በዛ ላይ ጎበዝ ተማሪ እየተባለች አገር የመሰከረላት ነች ፡፡ የልጃቸውን ሃሳብ እያወጡና እያወረዱ ከሔዱበት የሃሳብ ሰመመን ሳይመለሱ..
እና "አሁን ምን ይሻላል ትያለሽ? አሉ ፤ ቄስ መልካሙ፡፡ ከነጎዱበት የሃሳብ ሰመመን መለስ ብለው "እኔ ምን እላለሁ አንተ ምን አልካቸው?፡፡
"እኔማ ለዛሬ አስራምስት ቀን ተመልሰው እንዲመጡ ቀጥሪያቸዋለሁ፡፡ እኛም መመካከርና የእድላዊትን ፈቃድ ማወቅ ስላለብን ብየ ነው፡፡ ቀኑን ያስረዘምኩት፡፡ ለመሆኑ የሚሳካ ይመስልሻል ?፡፡
"እኔ እድላዊት ለማግባት እሽ የምትል አይመስለኝም፡፡በዛ ላይ ለትምህርቷ ያላት ፍላጎት ጎበዝ ተማሪ እንደሆነች ማንም ያውቃታል፡፡ እንደ እኔ ሃሳብ ትምህርቷን ከጨረሰች በኋላ፤ ብታገባ ይሻላል፡፡ ትዳር ይደረሳል፡፡ የት እንዳትሔድ ነው፡፡ ብለው አሁን አንተ ምን ወሰንክ አሉ?፡፡
"ማድረግ ያለብንማ ሁለታችንም ተመካክረን መወሰን ነው፡፡ እንደ እኔ እድላዊት እሷ እንኳን ባትፈቅድም ማግባት አለባት፡፡ ለትዳር ደርሳለች፡፡ ትምህርቷም ይበቃታል፡፡ ከአሁን በኋላ፤ ከትምህርቷ ቀርታ የቤት ሙያ መልመድ አለባት" አሉ፡፡
እድላዊት እንደ እናቷ የጠይም ቆንጆ ሰለክለክ ያለች ፤ ቁመናዋ እና ጥርሶቿ ልክ እንደ አባቷ ከሩቅ የሚያማልል ነው፡፡ ታዲያ የጠይም መልከመልካሟን ቆንጆ እንድላዊትን የሚያያት ሁሉ ሳይጎመዣት
አያልፍም ነበር ፡፡
አበበ ለማ እድላዊትን ሊያገባት አማላጅ የላከው በአጋጣሚ ከወንድሟ ከተመስገን ጋር ወደ ትምህርት ቤት ስትሄድ ባያት ማግስት ነበር፡፡ለቤተሰቦቹ ነግሮ አማላጅ እንዲላክለት ያደረገው፡፡
ወ/ሮ አሰገደች እድላዊትን አልድርም ፤ አስተምራለሁ ፤ እያሉ በሃሳባቸውም ሲፎክሩ የነበሩት በባለቤታቸው ቁጣ ያዘለ ንግግር ተቀየሩ፡፡
አንተ ከወሰንህ ታዲያ ምን አደርጋለሁ፡፡ እኔም ማግባት አለባት ባይ ነኝ፡፡ ማግባቷ ለእኔም ትጠቅመኛለች፡፡ ብታመም እንኳን ጠያቂ ዘመድ በቅርብ የለኝ፡፡ የምታገባበት ቦታ ቅርብም በመሆኑ እየመጣች ትጠይቀኛለች፡፡ በፍራትም ቢሆን ከባለቤታቸው ሃሳብ ላለመውጣት የተናገሩት ነበር፡፡
ቄስ መልካሙ የባለቤታቸውን ሃሳብና የራሳቸውን ሃሳብ አንድ ላይ ካሰባሰቡ በኋላ፤ እድላዊትን አሁን የተባባልነውን ሁሉ ከትምህርቷ ስትመጣ ንገሪያትና ከትምህርት ቀርታ የቤት ውስጥ ስራ እንድትለምድ አድርጊያት አሉ፡፡ ቁርጥና ኮስተር ባለ ንግግር፡፡
"እሽ ነግሬያት እንድትቀር አደርጋለሁ ፡፡
እድላዊትና ተመስገን
የጥዋት ተማሪ ናቸው፡፡ ወደ ትምህርት ቤት እየሔዱ እድላዊት ከወትሮው በተለየ ምክንያቱ በምን እንደሆነ አላወቀችውም፡፡ ግራ ተጋብታለች ፤ ሰውነቷ ይርበተበታል፡፡ ወደ ፊት መሔዷን ተወት አድርጋ አንዳንዴ ቆም በማለት ራሷን ለማረጋጋት ትሞክራለች፡፡
ተመስገንም በእህቱ መለዋወጥና ዝምታ ግራ ገብቶታል፡፡ ከአሁን አሁን ትነግረኛለች ብሎ ቢያስብም እድላዊት ግን የሆነችውን ለራሷ አላወቀችም፡፡ ምን እንደሆነችም ልትነግረው አልቻለችም ነበር፡፡
"ምን ሆነሽ ነው አሞሻል እንዴ?፡፡
"አላመመኝም ውስጤን ግን ፍራት ፍራት ይለኛል፡፡
"ምነው በሰላም ?፡፡
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
አማላጅ
ከራሳቸው ሃሳብ ጋር ሙግት ገጥመዋል ፡፡ እሽ ይሉኝ ይሆን ? ወይስ እንቢ ? እንደገና ደግሞ በአንዴማ እንቢም ፤ እሽም አይሉኝም ፡፡ እያሉ ሳይታወቃቸው ቄስ መልካሙ ቤት ደረሱ፡፡ ለመጣራት ወደ አጥሩ ተጠጉ ፡፡ እንደ አጋጣሚ ሆኖ ቄስ መልካሙን ግቢያቸው ውስጥ መፅኃፍ እያነበቡ ተመለከቷቸው ፡፡
መጣራታቸውን ትተው "ደህና አደራችሁ መልካሙ" ? አሉ፡፡ ቄስ አሻግሬ ፤
አቀርቅረው ከሚያነቡት መፅሃፍ ላይ አንገታቸውን ቀና አድርገው "እግዚአብሔር ይመስገን ሰላም አደሩ" ? አሉ ፡፡ ቄስ መልካሙ፡፡ ንስሃ አባታቸው ያለወትሯቸው በጥዋት በመምጣታቸው የመደናገጥ ምልክት እየታየባቸው ፡፡ ፀበል ሊረጩን ይሆን ? ሳንነግራቸውና ሳንዘጋጅ ፤ እነሱም ሳይነግሩን ፤ በሰላም ይሆን የመጡት? ከራሳቸው ሃሳብ ሳይወጡ የተናገሩት ነበር
"አንተን ፈልጌ ነበር የመጣሁት"፡፡ እደጅ ላግኝህ አሉ ቄስ አሻግሬ ፡፡ ለስለስ ባለ አነጋገር ፡፡
"ለምን እንደተፈለጉ ባያውቁም "ምነው ደህና አይደሉም እንዴ"?
አይ ደህና ነኝ ፡፡ ለጉዳይ ፈልጌህ ነበር አሉ
ከየት መጀመር እንዳለባቸው ግራ ቢገባቸውም "አቶ ለማ ልጅህን ለልጄ እንዲሰጡኝ አማላጅ ሂድልኝ ብሎኝ ነው የመጣሁት"፡፡ ብለው ሃሳባቸውን ሳያቋርጡ በመቀጠል አቶ ለማ ሽፈራው ጥሩ ሰው ናቸው፡፡ ዘራቸውም ቢሆንም ምንም አይወጣለትም ፡፡ ልጁም የተባረከ ፤ የተመሰገነ ፤ ጨዋ ፤ ድምፁም የማይሰማ ማለፊያ ገበሬ ነው" አሉ፡፡
ቄስ መልካሙ ያልጠበቁትና ያላሰቡት ነገር ሆነባቸው፡፡ ለጊዜው ምን ማለት እንዳለባቸው አብሰለሰሉ፡፡ የማይሆን ነገር ነው፡፡ አሁን እድላዊትን አግቢ ብላት ትምህርቷን ትታ የምታገባ አይመስለኝም፡፡ ከራሳቸው ሃሳብ ጋር እየተሟገቱ ከቆዩ በኋላ "እንግዲህ
ከቤተሰብና ዘመድ ጋር መክረን መልስ ብንሰጥ ይሻላል፡፡ አሁን እኔ ለብቻየ የምወስነው ነገር የለም" አሉ፡፡ ሆዳቸው እንደመባባት እያለም ቢሆን፡፡
"ታዲያ ቀነ ቀጠሮው ለመቼ ይሁን" ? አሉ፡፡ መቼም በአንዴ እሽ እንደማይባል የአገሩ ባህልና የተለመደ መሆኑን ስለሚያውቁ ፡ተመልሰው የሚመጡበትን ቀን በጉጉት ለመስማት እየጠበቁ ፡፡
"ዛሬ ቀኑ ሮዕብ አይደለም፡፡ የዛሬ አስራ አምስት ቀን ይመለሱ፡፡ እኛም እስከዛ ብንመካከርበት ይሻላል" በማለት መልስ ሰጧቸው፡፡
ይሁን መልካም ነው፡፡ ብለው የተሰጣቸውን ቀነ ቀጠሮ ተቀብለው ከቄስ መልካሙ ጋር ተሰነባብተው ወደ ቤታቸው ተመለሱ፡፡
ንሰሃ አባታቸውን ከሸኙ በኋላ ፤ ወደ ቤታቸው ገቡ፡፡ በመጨጊያቸው ላይ ተቀመጡ፡፡ አገጫቸውን በቀኝ እጃቸው ደገፍ አደረጉ፡፡ ትክዝ ባለ አንደበት ስለልጃቸው እድላዊት በውስጣቸው ማብሰልሰል ተያያዙት፡፡
ወ/ሮ አሰገደች ከማድቤት ወጥተው ወደ መኖሪያ ቤት እየሄዱ ባለቤታቸው ከወትሯቸው በተለየ ተክዘው ተመለከቷቸው፡፡ እርምጃቸውን ገታ አድርገው "ምነው ቄስ አሻግሬ አመጣጣቸው በደህና አይደለም እንዴ"? አሉ ፤ ለባለቤታቸው ፡፡
"አይ ደህና" ናቸው ፤ አሉ፡፡ ሃዘን ይሁን ትካዜ በተቀላቀለበት ንግግር፡፡
ወ/ሮ አሰገደች የንሰሃ አባታቸው ዛሬ በጥዋት አመጣጣቸው ለምን እንደሆነ ባያውቁም የባለቤታቸው መተከዝ አስጨንቋቸዋል፡፡ "በሰላምማ አልመሰለኝም" አሉ፡፡ ወደ ባለቤታቸው እየተጠጉ፡፡
"የመጡትስ በሰላም ቢሆንም አቶ ለማ ሽፈራው አማላጅ ልከዋቸው ነው የመጡት" አሉ፡፡ የባለቤታቸውን ሁኔታ እየተመለከቱ፡፡
"የምን አማላጅ ነው?" አሉ፡፡ ሆዳቸው እንደመርበትበት እያለ፡፡ የምን አማላጅነት እንደሆነ ለመስማት በመቸኮል፡፡
የአቶ ለማን ልጅ ታውቂዋለሽ ?"፡፡
"ትንሹን ነው ትልቁን?፡፡
"አይ! ትንሹን ይሁን ትልቁን አለየሁትም፡፡ አበበ የሚባለውን፡፡
ምን እንደሆነ ሳያውቁ "በሞትኩት ምን ነካው ያምስኪን ልጅ ከሰው ተጣላ" እንዴ ?፡፡
"እሱስ አልተጣላም፡፡ አቶ ለማ ሽፈራው እድላዊትን ለአበበ ስጡኝ ብሎ ነው፡፡ ቄስ አሻግሬን አማላጅ ተልከው የመጡት"፡፡
ወ/ሮ አሰገደች ለመስማት የጓጉትና ልባቸው ተንጠልጥሎ ሲጠብቁት የነበረው ምን እንደ ሆነ ባያውቁም ከባለቤታቸው የሰሙት ያልጠበቁትና ያላሰቡት ሆነባቸው፡፡ ለጊዜው መርዶ እንደ ተነገራቸው ያህል በዝምታ ተዋጡ፡፡ በሃሳባቸው ልጄን እማ አልሰጥም አስተምራለሁ፡፡ ትምህርቷን ሳትጨርስ አልድራትም፡፡ እሷም እሽ አትልም በዛ ላይ ጎበዝ ተማሪ እየተባለች አገር የመሰከረላት ነች ፡፡ የልጃቸውን ሃሳብ እያወጡና እያወረዱ ከሔዱበት የሃሳብ ሰመመን ሳይመለሱ..
እና "አሁን ምን ይሻላል ትያለሽ? አሉ ፤ ቄስ መልካሙ፡፡ ከነጎዱበት የሃሳብ ሰመመን መለስ ብለው "እኔ ምን እላለሁ አንተ ምን አልካቸው?፡፡
"እኔማ ለዛሬ አስራምስት ቀን ተመልሰው እንዲመጡ ቀጥሪያቸዋለሁ፡፡ እኛም መመካከርና የእድላዊትን ፈቃድ ማወቅ ስላለብን ብየ ነው፡፡ ቀኑን ያስረዘምኩት፡፡ ለመሆኑ የሚሳካ ይመስልሻል ?፡፡
"እኔ እድላዊት ለማግባት እሽ የምትል አይመስለኝም፡፡በዛ ላይ ለትምህርቷ ያላት ፍላጎት ጎበዝ ተማሪ እንደሆነች ማንም ያውቃታል፡፡ እንደ እኔ ሃሳብ ትምህርቷን ከጨረሰች በኋላ፤ ብታገባ ይሻላል፡፡ ትዳር ይደረሳል፡፡ የት እንዳትሔድ ነው፡፡ ብለው አሁን አንተ ምን ወሰንክ አሉ?፡፡
"ማድረግ ያለብንማ ሁለታችንም ተመካክረን መወሰን ነው፡፡ እንደ እኔ እድላዊት እሷ እንኳን ባትፈቅድም ማግባት አለባት፡፡ ለትዳር ደርሳለች፡፡ ትምህርቷም ይበቃታል፡፡ ከአሁን በኋላ፤ ከትምህርቷ ቀርታ የቤት ሙያ መልመድ አለባት" አሉ፡፡
እድላዊት እንደ እናቷ የጠይም ቆንጆ ሰለክለክ ያለች ፤ ቁመናዋ እና ጥርሶቿ ልክ እንደ አባቷ ከሩቅ የሚያማልል ነው፡፡ ታዲያ የጠይም መልከመልካሟን ቆንጆ እንድላዊትን የሚያያት ሁሉ ሳይጎመዣት
አያልፍም ነበር ፡፡
አበበ ለማ እድላዊትን ሊያገባት አማላጅ የላከው በአጋጣሚ ከወንድሟ ከተመስገን ጋር ወደ ትምህርት ቤት ስትሄድ ባያት ማግስት ነበር፡፡ለቤተሰቦቹ ነግሮ አማላጅ እንዲላክለት ያደረገው፡፡
ወ/ሮ አሰገደች እድላዊትን አልድርም ፤ አስተምራለሁ ፤ እያሉ በሃሳባቸውም ሲፎክሩ የነበሩት በባለቤታቸው ቁጣ ያዘለ ንግግር ተቀየሩ፡፡
አንተ ከወሰንህ ታዲያ ምን አደርጋለሁ፡፡ እኔም ማግባት አለባት ባይ ነኝ፡፡ ማግባቷ ለእኔም ትጠቅመኛለች፡፡ ብታመም እንኳን ጠያቂ ዘመድ በቅርብ የለኝ፡፡ የምታገባበት ቦታ ቅርብም በመሆኑ እየመጣች ትጠይቀኛለች፡፡ በፍራትም ቢሆን ከባለቤታቸው ሃሳብ ላለመውጣት የተናገሩት ነበር፡፡
ቄስ መልካሙ የባለቤታቸውን ሃሳብና የራሳቸውን ሃሳብ አንድ ላይ ካሰባሰቡ በኋላ፤ እድላዊትን አሁን የተባባልነውን ሁሉ ከትምህርቷ ስትመጣ ንገሪያትና ከትምህርት ቀርታ የቤት ውስጥ ስራ እንድትለምድ አድርጊያት አሉ፡፡ ቁርጥና ኮስተር ባለ ንግግር፡፡
"እሽ ነግሬያት እንድትቀር አደርጋለሁ ፡፡
እድላዊትና ተመስገን
የጥዋት ተማሪ ናቸው፡፡ ወደ ትምህርት ቤት እየሔዱ እድላዊት ከወትሮው በተለየ ምክንያቱ በምን እንደሆነ አላወቀችውም፡፡ ግራ ተጋብታለች ፤ ሰውነቷ ይርበተበታል፡፡ ወደ ፊት መሔዷን ተወት አድርጋ አንዳንዴ ቆም በማለት ራሷን ለማረጋጋት ትሞክራለች፡፡
ተመስገንም በእህቱ መለዋወጥና ዝምታ ግራ ገብቶታል፡፡ ከአሁን አሁን ትነግረኛለች ብሎ ቢያስብም እድላዊት ግን የሆነችውን ለራሷ አላወቀችም፡፡ ምን እንደሆነችም ልትነግረው አልቻለችም ነበር፡፡
"ምን ሆነሽ ነው አሞሻል እንዴ?፡፡
"አላመመኝም ውስጤን ግን ፍራት ፍራት ይለኛል፡፡
"ምነው በሰላም ?፡፡
👍89❤12🥰1😱1🎉1
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ቄስ አሻግሬ
ሔደውልኝ ይሆን? ዛሬ ደግሞ ማርያም ናት፡፡ ቅዳሴ ይኖርባቸው ይሆን? ለነገሩ ቅዳሴ እንኳን ከሰዓት ነው፡፡ ቀኑ ዕሮብ አይደለም ምናልባት ጠዋት ሄደውልኝ ይሆናል፡፡ ለማንኛውም እኔም ማህበር ስላለኝ እዛው ቤተ ክርስቲያን አገኛቸዋለሁ፡፡ ከማህበር ስንወጣ እጠይቃቸዋለሁ፡፡ ብሎ ከሰው ጋር ባይይሆንም ከራሱ ሃሳብ ጋር የተናገረው ነበር፡፡ አቶ ለማ ሽፈራው፡፡
ከቅዳሴ የመውጫ ሰዓት ስለደረሰ ጋቢውን ለባብሶ ተነሳ፡፡ ወደ ጉራንባ ማርያም ቤተክርስቲያን ጉዞውን ቀጠለ፡፡
ቄስ አሻግሬ አማላጅነቱ ሙሉ በሙሉ ተሳክቷል ባይባልም በተወሰነ መልኩ ተስፋ የሚሰጥ መልስ በማግኘታቸው ተደስተዋል፡፡ ወደ ቤታቸው ከተመለሱ በኋላ ከሰዓት ቅዳሴ ስለነበረባቸው ብዙም ሳይቆዩ ተነስተው ወደ ጉራንባ ማርያም ቤተክርስቲያን ጉዞዋቸውን አቀኑ፡፡
አቶ ለማ ከቅዳሴ ሲወጡ ደረሰ፡፡ ቄስ አሻግሬን ለማናገር ከማህበር በኋላ ሊመሽ ስለሚችል ዛቲ እንደቀመሱ ማናገር እንዳለበት አሰበ፡፡ ከዛቲ እንደተበተኑ ካህናት ከቅዳሴ ወጥተው ወደ ተቀመጡበት ቦታ ሔደ፡፡
"ሰላም ዋሉ ቄስ አሻግሬ” ፡፡
"እግዚአብሔር ይመስገን ሰላም ዋልህ?፡፡ ለማ" ብለው አጠፌታ መልስ ሰጥተውት መስቀል አሳለሙት፡፡ "ዛሬ ማርያም መጥተህ ኖሯል፡፡ መሃበር አለህ ለካስ" አሉ፡፡
"አዎ፤ ማህበር አለኝ"፡፡ ብሎ በቀጥታ ለማናገር ወደ ፈለገው ጉዳይ ገባ፡፡ "እንዴው እዛ ጉዳይ ጋር ሔደውልኝ ነበር ?"፡፡
"አዎ፤ ሔጀ ነበር፡፡ ያው! መቼም በአንዴ እሽ እንደማይባል አንተም ታውቃለህ፡፡ ለማንኛውም ለዛሬ አስራ አምስት ቀን ቀጥረውኛል፡፡ ቁርጡ ያኔ ይታወቃል" ::
"ቀጠሮ መስጠታቸውም ጥሩ ተስፋ ነው፡፡ እና እርሶንም በጣም አመሰግናለሁ"፡፡ ብሎ የማህበር ሰዓት ስለደረሰባቸው ወደየ ማህበራቸው ገቡ፡፡
አቶ ለማ ከማህበሩ እንደወጣ ወደ ቤቱ እየሔደ ፤ እንዴው እሽ ባለኝ፡፡ ልጅቷ ጎበዝ ተማሪ እና ጨዋ እንደሆነች መቼም አገር ነው የሚያወራላት፡፡ ፀባይዋም ቢሆን ምንም አይወጣላትም ሲሉ ሰምቻለሁ፡፡ እንዴው በተሳካልኝ፡፡ ሰዎች ስለእድላዊት መልካምነት ሲያወሩ የሰማውን ሁሉ በሃሳቡ እየደጋገመ እና እያወራ ሳይታወቀው እቤቱ ደረሰ፡፡
"ምነው ዛሬ ደግሞ አመሸህ? ማህበሩ ቶሎ አላለቀም እንዴ?" አለ አበበ ላባቱ፡፡
"አዎ፤ ዛሬ ደግሞ ቶሎ ወደ ማህበር አልገቡም ነበር፡፡ ማህበረተኛውም የት እንደ ሄደ እንጃ ፤ጠላውም አላልቅ ብሎን እኔም ይመሽብኛል ብየነው ፤ ሳያልቅ ትቸው ነው የመጣሁት"፡፡
ከዛቲ መልስ ቄስ አሻግሬንም አግኝቻቸው ነበር፡፡ እቄስ መልካሙ ጋር እንደ ሔዱልኝ እና የድጋሜ ቀጠሮውም ለዛሬ አስራ አምስት ቀን እንደቀጠሯቸው ነገሩኝ" አለው፡፡
አበበ ለእድላዊት አማላጅ እንደላከለት ሲነግረው በጣም ወደር የሌለው ደስታ ተሰማው፡፡ ለማግባት የሚያስፈልገውን ነገር ማሟላት እንዳለበት በመወሰን የጀመረውን የቤት ስራ ለመጨረስ እየተጣደፈ ነው፡፡
እድላዊት ግን እሽ ትበለውም አትበለውም ባያውቅም ማድረግ የሚችለውን ሁሉ እያደረገ ባለበት ሰዓት በህሊናው አንድ ሃሳብ ያቃጭልበታል ?
ተመስገን
ሊነጋጋ ሲል የወሰደው እንቅልፍ ተጫጭኖት ቶሎ አልተነሳም፡፡ ለትምህርት ከሚነሳበት ሰዓት አርፍዶ ነው የተነሳው፡፡ የእድላዊት ባል ማግባት እና ከትምህርት መቅረት እውነት ሆኖ ቀረ ማለት ነው?፡፡ እውነት ባይሆንማ ኖሮ ሳትቀሰቅሰኝ ባልቀረች ነበር፡፡ ከራሱ ጋር እያወራ ከመኝታው ተነሳ፡፡ ሽንት ቤት ተፀዳድቶ ተመለሰ፡፡
እናቱን ከቤት ሲወጡ እበር ላይ አገኛቸው፡፡ እንደማይተዋወቅ ሰው የእግዚአብሔር ሰላምታ ሳይለዋወጡ ተላለፉ፡፡ የቤተሰቦቹ ድርጊት እና እርህራሔ የሌለው ውሳኔ ያስከፋው ተመስገን ለማነጋገር አይደለም የሚጨክን አንጀት እና አቅም ቢኖረው ቤተሰቦቹን በደበደባቸው ነበር፡፡
ወደ እድላዊት መኝታ ቤት አመራ፡፡ የቤቱ በር ከውስጥ የተዘጋ መስሎ ገርበብ ብሏል፡፡ እስካሁን ያልተነሳችው አሟት ቢሆን ነው፡፡ የቤቱን በር አንኳኳው፡፡ መልስ የሚሰጥ አላገኘም፡፡ ደጋግሞ በሩን ተመለከተ፡፡ ከነጋ የተከፈተ አይመስልም፡፡
ደግሞ ለማንኳኳት ሰውነቱን ከነከነው፡፡ ውስጡ ፍራት ፍራት ተሰማው፡፡ እጆቹም ተንቀጠቀጡ፡፡ የሚሆነው ሁሉ ጠፋበት፡፡ ከውስጥ አልተዘጋ ይሆን እንዴ? ተጠራጠረ፡፡ በሩን ማንኳኳቱን ትቶ የሞት ሞቱን ገፋው፡፡ መዝጊያው ከውስጥ ምንም የያዘው ነገር ባለመኖሩ ተከፈተ፡፡ በፍርሃት ወደ ውስጥ ገባ፡፡
ከአልጋ በስተቀር እድላዊት አይደለችም ፤ የእድላዊት ልብስ እንኳን አላገኘም ነበር፡፡ የህሊና ፀሎት እንደሚያደርስ ሰው ቆሞ የስልክ እንጨት መሰለ፡፡ ደቂቃዎች አልፈው ከወሰደው የድንጋጤ ሰመመን ባነነ፡፡ በቀጥታ ወደ እናት አባቱ ቤት ሄደ፡፡ እድላዊትን የት ሄደች ? ብሎ እናቱን ጠየቀ፡፡
ወ/ሮ አሰገደች የሚናገሩት ፣ የሚያነሱት ፣ የሚቧጥጡት አጡ፡፡ የት ሔደች? የለችም መኝታዋ ላይ ፤ እንደፎከረችው አደረገችው ማለት ነው፡፡ ወይ ጉዴ! እያሉ ከተመስገን መልስ ሳይጠብቁ ኡኡታቸውን አቀለጡት፡፡
የአካባቢው ሰውና ጎረቤቱ ምን ደረሰባቸው? ምን አጋጥሟቸው ይሆን?፡፡ እየተሯሯጡ ግቢው ሰው በሰው አጥለቀለቁት፡፡ታዲያ የሰው መዓት ቢሰበሰብ እና እሪ እየተባለ ቢጮህም እድላዊት ልትገኝ አልቻለችም፡፡ ኡኡታ
ሰምተው ከመጡት ሰዎች መካከል ወ/ሮ ስንዱ "የት ትሔዳለች ፤ ከዚህ በፊት ከቤት ወጥታ አታውቅም፡፡
ወደ ዘመዶቿ ሔዳ ይሆናል፡፡ ሰው ልኮ ማጠያየቅ ነው" አሉ፡፡
ወ/ሮ አሰገደችን ለማረጋጋት ቢሞክሩም ወ/ሮ አሰገደች ግን የሚረጋጉ አይደለም፤ ጨርቃቸውን ጥለው የሚያብዱ ነበር የሚመስሉት፡፡
ቄስ መልካሙ በድንጋጤ የተነሳ የሚጮኸውን ጩኸት የራሳቸው ችግር አይደለም፤ ለተመለከታቸው ሰው ከነጭራሹም ጩኸቱን የሰሙት አይመስልም ነበር፡፡
ጎረቤት የሆኑት አቶ ማን ችሎት ማን ያዝልሃል፡፡ ቄስ መልካሙን ለማነጋገር እና የተፈጠረውን ለመጠየቅ ቢሞክሩም ቄስ መልካሙ አይናቸውን ከማቁለጭለጭ ውጭ መልስ የሚባል ለመመለስ አይደለም ከነጭራሹም ለመናገር አቅቷቸው ነበር፡፡ ተመስገን ከእናት አባቱ የተሻለ ቢሆንም ሰው የሚጠይቀውን ጥያቄ ግን እሱም መመለስ አልቻለም፡፡
የተሰባሰቡት ሰዎች ሁሉ የሚያደርጉት ጠፋቸው፡፡ ከመካከላቸው አንድ ሰው መኮንን ሃይሌ የሚባል ተነሳ
"አሁን ሁላችንም አብሮ ማጃበሩን እና ማልቀሱ ዋጋ ያለው አይመስለኝም፡፡ እነሱን አረጋግተን መላ ብንፈልግ የሚሻል ይመስለኛል፡፡ ብሎ ሃሳብ ሰነዘረ፡፡ የተሰበሰበው ሰው በሃሳቡ ተስማምቶ ወሮ አሰገደችንና ባለቤታቸውን አረጋግተው እድላዊትን ፍለጋ በየ አቅጣጫው ሁሉም ሰው ተበታተነ፡፡
እድላዊት ግን በዘመዶቿ ቤት አይደለም በዱር በገደሉም ልትገኝ አልቻለችም፡፡ ከጠፋችበት ቀን አንስቶ አየናት፡፡ በዚህ አልፋለች የሚል አይደለም የበላት ጅብ እንኳን ሊጮህ አልቻለም፡፡
ቄስ መልካሙ በልጃቸው መጥፋት ጥልቅ ሃዘን ተሰማቸው፡፡ እድላዊት ትሙት ትኑር ሳያውቁ "አይ! አንተ ሰማይ እና ምድርን የፈጠርህ ጌታ እንደዚህ በቁሜ እንዳዋረደችኝ እና እንዳሰቃየችኝ በቁሟ የሚያዋርድ ይስጣት፡፡ የፈጠሯትን ልጅ አምርረው ረገሟት፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ቄስ አሻግሬ
ሔደውልኝ ይሆን? ዛሬ ደግሞ ማርያም ናት፡፡ ቅዳሴ ይኖርባቸው ይሆን? ለነገሩ ቅዳሴ እንኳን ከሰዓት ነው፡፡ ቀኑ ዕሮብ አይደለም ምናልባት ጠዋት ሄደውልኝ ይሆናል፡፡ ለማንኛውም እኔም ማህበር ስላለኝ እዛው ቤተ ክርስቲያን አገኛቸዋለሁ፡፡ ከማህበር ስንወጣ እጠይቃቸዋለሁ፡፡ ብሎ ከሰው ጋር ባይይሆንም ከራሱ ሃሳብ ጋር የተናገረው ነበር፡፡ አቶ ለማ ሽፈራው፡፡
ከቅዳሴ የመውጫ ሰዓት ስለደረሰ ጋቢውን ለባብሶ ተነሳ፡፡ ወደ ጉራንባ ማርያም ቤተክርስቲያን ጉዞውን ቀጠለ፡፡
ቄስ አሻግሬ አማላጅነቱ ሙሉ በሙሉ ተሳክቷል ባይባልም በተወሰነ መልኩ ተስፋ የሚሰጥ መልስ በማግኘታቸው ተደስተዋል፡፡ ወደ ቤታቸው ከተመለሱ በኋላ ከሰዓት ቅዳሴ ስለነበረባቸው ብዙም ሳይቆዩ ተነስተው ወደ ጉራንባ ማርያም ቤተክርስቲያን ጉዞዋቸውን አቀኑ፡፡
አቶ ለማ ከቅዳሴ ሲወጡ ደረሰ፡፡ ቄስ አሻግሬን ለማናገር ከማህበር በኋላ ሊመሽ ስለሚችል ዛቲ እንደቀመሱ ማናገር እንዳለበት አሰበ፡፡ ከዛቲ እንደተበተኑ ካህናት ከቅዳሴ ወጥተው ወደ ተቀመጡበት ቦታ ሔደ፡፡
"ሰላም ዋሉ ቄስ አሻግሬ” ፡፡
"እግዚአብሔር ይመስገን ሰላም ዋልህ?፡፡ ለማ" ብለው አጠፌታ መልስ ሰጥተውት መስቀል አሳለሙት፡፡ "ዛሬ ማርያም መጥተህ ኖሯል፡፡ መሃበር አለህ ለካስ" አሉ፡፡
"አዎ፤ ማህበር አለኝ"፡፡ ብሎ በቀጥታ ለማናገር ወደ ፈለገው ጉዳይ ገባ፡፡ "እንዴው እዛ ጉዳይ ጋር ሔደውልኝ ነበር ?"፡፡
"አዎ፤ ሔጀ ነበር፡፡ ያው! መቼም በአንዴ እሽ እንደማይባል አንተም ታውቃለህ፡፡ ለማንኛውም ለዛሬ አስራ አምስት ቀን ቀጥረውኛል፡፡ ቁርጡ ያኔ ይታወቃል" ::
"ቀጠሮ መስጠታቸውም ጥሩ ተስፋ ነው፡፡ እና እርሶንም በጣም አመሰግናለሁ"፡፡ ብሎ የማህበር ሰዓት ስለደረሰባቸው ወደየ ማህበራቸው ገቡ፡፡
አቶ ለማ ከማህበሩ እንደወጣ ወደ ቤቱ እየሔደ ፤ እንዴው እሽ ባለኝ፡፡ ልጅቷ ጎበዝ ተማሪ እና ጨዋ እንደሆነች መቼም አገር ነው የሚያወራላት፡፡ ፀባይዋም ቢሆን ምንም አይወጣላትም ሲሉ ሰምቻለሁ፡፡ እንዴው በተሳካልኝ፡፡ ሰዎች ስለእድላዊት መልካምነት ሲያወሩ የሰማውን ሁሉ በሃሳቡ እየደጋገመ እና እያወራ ሳይታወቀው እቤቱ ደረሰ፡፡
"ምነው ዛሬ ደግሞ አመሸህ? ማህበሩ ቶሎ አላለቀም እንዴ?" አለ አበበ ላባቱ፡፡
"አዎ፤ ዛሬ ደግሞ ቶሎ ወደ ማህበር አልገቡም ነበር፡፡ ማህበረተኛውም የት እንደ ሄደ እንጃ ፤ጠላውም አላልቅ ብሎን እኔም ይመሽብኛል ብየነው ፤ ሳያልቅ ትቸው ነው የመጣሁት"፡፡
ከዛቲ መልስ ቄስ አሻግሬንም አግኝቻቸው ነበር፡፡ እቄስ መልካሙ ጋር እንደ ሔዱልኝ እና የድጋሜ ቀጠሮውም ለዛሬ አስራ አምስት ቀን እንደቀጠሯቸው ነገሩኝ" አለው፡፡
አበበ ለእድላዊት አማላጅ እንደላከለት ሲነግረው በጣም ወደር የሌለው ደስታ ተሰማው፡፡ ለማግባት የሚያስፈልገውን ነገር ማሟላት እንዳለበት በመወሰን የጀመረውን የቤት ስራ ለመጨረስ እየተጣደፈ ነው፡፡
እድላዊት ግን እሽ ትበለውም አትበለውም ባያውቅም ማድረግ የሚችለውን ሁሉ እያደረገ ባለበት ሰዓት በህሊናው አንድ ሃሳብ ያቃጭልበታል ?
ተመስገን
ሊነጋጋ ሲል የወሰደው እንቅልፍ ተጫጭኖት ቶሎ አልተነሳም፡፡ ለትምህርት ከሚነሳበት ሰዓት አርፍዶ ነው የተነሳው፡፡ የእድላዊት ባል ማግባት እና ከትምህርት መቅረት እውነት ሆኖ ቀረ ማለት ነው?፡፡ እውነት ባይሆንማ ኖሮ ሳትቀሰቅሰኝ ባልቀረች ነበር፡፡ ከራሱ ጋር እያወራ ከመኝታው ተነሳ፡፡ ሽንት ቤት ተፀዳድቶ ተመለሰ፡፡
እናቱን ከቤት ሲወጡ እበር ላይ አገኛቸው፡፡ እንደማይተዋወቅ ሰው የእግዚአብሔር ሰላምታ ሳይለዋወጡ ተላለፉ፡፡ የቤተሰቦቹ ድርጊት እና እርህራሔ የሌለው ውሳኔ ያስከፋው ተመስገን ለማነጋገር አይደለም የሚጨክን አንጀት እና አቅም ቢኖረው ቤተሰቦቹን በደበደባቸው ነበር፡፡
ወደ እድላዊት መኝታ ቤት አመራ፡፡ የቤቱ በር ከውስጥ የተዘጋ መስሎ ገርበብ ብሏል፡፡ እስካሁን ያልተነሳችው አሟት ቢሆን ነው፡፡ የቤቱን በር አንኳኳው፡፡ መልስ የሚሰጥ አላገኘም፡፡ ደጋግሞ በሩን ተመለከተ፡፡ ከነጋ የተከፈተ አይመስልም፡፡
ደግሞ ለማንኳኳት ሰውነቱን ከነከነው፡፡ ውስጡ ፍራት ፍራት ተሰማው፡፡ እጆቹም ተንቀጠቀጡ፡፡ የሚሆነው ሁሉ ጠፋበት፡፡ ከውስጥ አልተዘጋ ይሆን እንዴ? ተጠራጠረ፡፡ በሩን ማንኳኳቱን ትቶ የሞት ሞቱን ገፋው፡፡ መዝጊያው ከውስጥ ምንም የያዘው ነገር ባለመኖሩ ተከፈተ፡፡ በፍርሃት ወደ ውስጥ ገባ፡፡
ከአልጋ በስተቀር እድላዊት አይደለችም ፤ የእድላዊት ልብስ እንኳን አላገኘም ነበር፡፡ የህሊና ፀሎት እንደሚያደርስ ሰው ቆሞ የስልክ እንጨት መሰለ፡፡ ደቂቃዎች አልፈው ከወሰደው የድንጋጤ ሰመመን ባነነ፡፡ በቀጥታ ወደ እናት አባቱ ቤት ሄደ፡፡ እድላዊትን የት ሄደች ? ብሎ እናቱን ጠየቀ፡፡
ወ/ሮ አሰገደች የሚናገሩት ፣ የሚያነሱት ፣ የሚቧጥጡት አጡ፡፡ የት ሔደች? የለችም መኝታዋ ላይ ፤ እንደፎከረችው አደረገችው ማለት ነው፡፡ ወይ ጉዴ! እያሉ ከተመስገን መልስ ሳይጠብቁ ኡኡታቸውን አቀለጡት፡፡
የአካባቢው ሰውና ጎረቤቱ ምን ደረሰባቸው? ምን አጋጥሟቸው ይሆን?፡፡ እየተሯሯጡ ግቢው ሰው በሰው አጥለቀለቁት፡፡ታዲያ የሰው መዓት ቢሰበሰብ እና እሪ እየተባለ ቢጮህም እድላዊት ልትገኝ አልቻለችም፡፡ ኡኡታ
ሰምተው ከመጡት ሰዎች መካከል ወ/ሮ ስንዱ "የት ትሔዳለች ፤ ከዚህ በፊት ከቤት ወጥታ አታውቅም፡፡
ወደ ዘመዶቿ ሔዳ ይሆናል፡፡ ሰው ልኮ ማጠያየቅ ነው" አሉ፡፡
ወ/ሮ አሰገደችን ለማረጋጋት ቢሞክሩም ወ/ሮ አሰገደች ግን የሚረጋጉ አይደለም፤ ጨርቃቸውን ጥለው የሚያብዱ ነበር የሚመስሉት፡፡
ቄስ መልካሙ በድንጋጤ የተነሳ የሚጮኸውን ጩኸት የራሳቸው ችግር አይደለም፤ ለተመለከታቸው ሰው ከነጭራሹም ጩኸቱን የሰሙት አይመስልም ነበር፡፡
ጎረቤት የሆኑት አቶ ማን ችሎት ማን ያዝልሃል፡፡ ቄስ መልካሙን ለማነጋገር እና የተፈጠረውን ለመጠየቅ ቢሞክሩም ቄስ መልካሙ አይናቸውን ከማቁለጭለጭ ውጭ መልስ የሚባል ለመመለስ አይደለም ከነጭራሹም ለመናገር አቅቷቸው ነበር፡፡ ተመስገን ከእናት አባቱ የተሻለ ቢሆንም ሰው የሚጠይቀውን ጥያቄ ግን እሱም መመለስ አልቻለም፡፡
የተሰባሰቡት ሰዎች ሁሉ የሚያደርጉት ጠፋቸው፡፡ ከመካከላቸው አንድ ሰው መኮንን ሃይሌ የሚባል ተነሳ
"አሁን ሁላችንም አብሮ ማጃበሩን እና ማልቀሱ ዋጋ ያለው አይመስለኝም፡፡ እነሱን አረጋግተን መላ ብንፈልግ የሚሻል ይመስለኛል፡፡ ብሎ ሃሳብ ሰነዘረ፡፡ የተሰበሰበው ሰው በሃሳቡ ተስማምቶ ወሮ አሰገደችንና ባለቤታቸውን አረጋግተው እድላዊትን ፍለጋ በየ አቅጣጫው ሁሉም ሰው ተበታተነ፡፡
እድላዊት ግን በዘመዶቿ ቤት አይደለም በዱር በገደሉም ልትገኝ አልቻለችም፡፡ ከጠፋችበት ቀን አንስቶ አየናት፡፡ በዚህ አልፋለች የሚል አይደለም የበላት ጅብ እንኳን ሊጮህ አልቻለም፡፡
ቄስ መልካሙ በልጃቸው መጥፋት ጥልቅ ሃዘን ተሰማቸው፡፡ እድላዊት ትሙት ትኑር ሳያውቁ "አይ! አንተ ሰማይ እና ምድርን የፈጠርህ ጌታ እንደዚህ በቁሜ እንዳዋረደችኝ እና እንዳሰቃየችኝ በቁሟ የሚያዋርድ ይስጣት፡፡ የፈጠሯትን ልጅ አምርረው ረገሟት፡፡
👍73❤6👏3
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እድላዊት
ከወሰዳት የንቅልፍ ሸለብታ ነቃች፡፡ መኝታዋን ሳታነጥፍ ለምን እንደተኛች ግራ ተጋባች፡፡ የሆነውን እና የተፈጠረውን ነገር ሁሉ ለማስታወስ አንድ በአንድ ወደ ኋላ ተመልሳ በሃሳብ ነጎደች፡፡
የተነሳችበት ሰዓት ሳይነጋ እኩለ ለሊት ላይ ነው፡፡ ወዴት እንደምትሔድ ጨነቃት፡፡ ልቧ ሸፍቶ ጥፊ እያለ አስቸግሯታል፡፡ ለመጥፋት ወሰነች፡፡
መተኛቷን ትታ ቁጭ አለች፡፡ ወዴት እንደምትጠፋ እና ወዴት እንደምትሔድ አሰበች፡፡ ምን ይገጥመኝ ይሆን ? እንደገና ደግሞ ሃሳቧ እየተቀያየረባት ከምጠፋ ታንቄ ብሞት አይሻልም ? ሰርጌን ለመብላት ሲያደገድጉ በአቋራጭ ተስካሬን ይበሉ ነበር፡፡
ሃሳቧን እየቀያየረች ስታወጣና ስታወረድ ቆየች፡፡ አልሸነፍም ፤ አልረታም ፤ ለሞት እጄን አልሰጥም ብሎ የመጥፋት መንገድን የመረጠው ልቧ ሳይመለስ ቀረ፡፡ ሲገፋፋት ቆየ፡፡ ልቧ የመጥፋት መንገድን ማሸነፍ አልቻለም፡፡
ከሔደችበት የሃሳብ ሰመመን ተመለሰች፡፡ ሌሊቱ እየነጋጋ ነው፡፡ የታጠበውንም ፣ ያልታጠበውንም ልብሷን በፌስታል ሸከፈች፡፡ ቤተሰቦቿ ሳይሰሟት መውጣት እንዳለባት ወሰነች፡፡
መጥፋትን የወሰነችው እድላዊት መነሻዋን እንጅ መድረሻዋን አታውቅም፡፡ ጓዟን ጠቅልላ የእናት አባቷን ቤት እና የተወለደችበትን ቀዬ ለቃ ለመሄድ ተነሳች፡፡በሮቹን ድምፅ ሳታሰማ እና የተከፈቱ ሳታስመስል ግቢውን ለቃ ጨለማ በተቀላቀለበት ሌሊት ጉዞዋን አሃዱ አለች፡፡
ትንሽ እንደተጓዘች ጨለማው እየለቀቀና እየነጋጋ ሄደ፡፡ እለቱ እሁድ በመሆኑ በሩቅ ርቀት ላይ ሰዎች ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሔዱ ተመለከተች፡፡ የምትጓዝበትን መንገድ ትታ ሰው ሳያያት ለመሔድ ፈለገች፡፡ አማራጭ መንገድ በጫካ ውስጥ መረጠች፡፡ የአካባቢው ሰው እንዳያያት የጫካውን መንገድ ይዛ መጓዝ የግድ ሆነባት፡፡
እድላዊት ከቤት ስትወጣ ከልብሷ በስተቀር የሚበላ ስንቅ አልያዘችም፡፡ በጉዞው አድካሚነትና አሰልችነት የተነሳ እራባት፡፡ ውሃም እየጠማት መጣ፡፡ ምግብ የበላችበትን ሰዓት አስታወሰች፡፡ ከትምህርት ቤት ከወንድሟ ጋር ስትመጣ የቀመሰች ነው፡፡ እራትም ሳትበላ ነበር ያደረችው፡፡
ድካሟ እየባሰባት መጣ፡፡ አረፍ ለማለት በምትጓዝበት ጫካ ውስጥ ወደ ሚገኝ አንድ ትልቅ ዛፍ ስር ተቀመጠች፡፡ ውሃ ጥሙ ግን እየባሰባት ሄደ፡፡ ካረፈችበት ዛፍ ስር ተነሳች፡፡እየተጓዘች በአይኖቿ መንደር እና ውሃ በአካባቢው እያፈላለገች ፣ እየቃኘች ስትሔድ ጫካ ከመሆኑ አንፃር ውሃና መንደር የሚባል በቅርብ ልታገኝ አልቻለችም፡፡ ታዲያ ማፈላለጓን አላቋረጠችም፡፡ ከምትሄድበት መንገድ ባሻገር ከብቶች ሲሔዱ ተመለከተች፡፡
ከብቶቹ ወደ ውሃ እንደሚሄዱ ገመተች፡፡ የያዘችውን መንገድ ለቃ ከብቶቹ የሚጓዙበትን መንገድ በመያዝ ተከተለች፡፡
እውነትም የገመተችው ትክክል በመሆኑ ከብቶቹ ውሃ ሲጠጡ አገኘቻቸው፡፡
እድላዊት የጠማትን ውሃ ለመጠጣት ከብቶቹ ከሚጠጡበት ከፍ ብላ ልትጠጣ ተቀመጠች፡፡ የሚያንጎራጉር እና የፉጨት ድምፅ ሰማች፡፡ውሃውን ሳትጠጣ የሚያንጎራጉረውን የሰው ድምፅ ከየት አቅጣጫ እንደሆነ ለመለየት በአይኖቿ አማተረች፡፡
የእንጉርጉሮው ድምፅ እየቀረባት መጣ፡፡ ፍራት ፍራት ተሰማት፡፡ የዛሬን አውጣኝ ከዚህ ጫካ እያለች ፈጣሪዋን እየተማፀነች ፤ እየተርበተበተች አብዝታ ለመነች፡፡
የሚያንጎራጉረው የእንጉርጉሮው ድምፅ ከብቶች የሚያጠጡ እረኞች ነበሩ፡፡
እድላዊት እረኞቹን ፈራች፡፡ የመውጫዋን እና የማምለጫ መንገዷን ፈለገች፡፡
ከብቶቹን ከሚያጠጡት ሁለት እረኞች መካከል አንዱ ከበደ የሚባለው እረኛ እያንጎራጎረ ወደ ወንዙ ቀና አለ፡፡ አንድ የተቀመጠ ሰው ተመለከተ፡፡
ለጓደኛው ደበበ ያየውን ሰው ያ ማነው ? እዛ ላይ የተቀመጠው? አለ፡፡ ደበበ ጓደኛው እንዳለው ወደ ላይ ቀና ብሎ አየ፡፡ ቁጭ ያለ ሰው ተመለከተ፡፡
"ውሃ የሚጠጣ ሰው ይሆናል" አለው ለጓደኛው፡፡
እድላዊት እረኞች በእጃቸው እየተጠቋቆሙ ሲመለከቷት የባሰ ፈራች፡፡ በድንጋጤ እንደጠማት ልትጠጣ በእጇ የጨለፈችውን ውሃ እንኳን ሳትጠጣ ተነሳች፡፡ ቁጭ ብላ ከእረኞቹ ማምለጫ ስታማትር ወደ አገኘችው መውጫ መንገድ ተነስታ ለማምለጥ ሞከረች፡፡
እረኞቹ እድላዊትን ወንዝ ላይ ተቀምጣ ሰው ከመሆኗ ውጪ ወንድ ይሁን ሴት ትሁን አላወቋትም ነበር፡፡
እድላዊት ውሃ ለመጠጣት ከተቀመጠችበት ተነስታ ስትሮጥ ተመልክተው ሴት መሆኗን ለይዋት ፤ ከብቶቻቸውን ማጠጣታቸውን ትተው በእድላዊት መልክና ውበት እየተገረሙ በአይናቸው ተከትለው ሸኟት፡፡
አይን ለአይን እየተያዩ፡፡ የማነች ቀሽት ባክህ! ስታምር ፤ ከየት ይሆን የምትመጣው?
እውነትም ቀሽት ናት፡፡ ደግሞ እየፈራች ነው ፣ የምትሔደው፡፡ ምን ያገላምጣታል;
እረኞቹ እድላዊት ስትርበተበት አይተዋት ፤ ብቻዋንና የተከተላት ሰው አለመኖሩን ነቅተውባታል፡፡ይች ቀሽት ሳታመልጠን እንከተላት ተባባሉ፡፡ መጀመሪያ በአይናቸው ሸኝተዋት ቢመለሱም ልባቸው ግን ተከትሏት ነበር፡፡ እየተጣደፉ
እንዳታመልጣቸው በሔደችበት መንገድ ተከተሏት፡፡ እድላዊት የልቧ ትርታ ጨመረ፡፡ ሰውነቷ ሁሉ እየተንቀጠቀጠ፡፡ ትንፋሿ ቁርጥ ቁርጥ አለ፡፡ ይከተሉኝ ይሆን ብላ ተጠራጠረች፡፡ እንዴው አምላኬ
የዛሬን አውጣኝ፡፡ ከዚህ ከጨለማ፡፡ እያለች እንዳይደርሱባት በደከመ አቅሟ ለመሮጥ ሞከረች፡፡ ለእሷ የሮጠች መሰላት፡፡ ዳገቱ ግን ሊገፋላት አልቻለም፡፡ መልሶ ወደ መጣችበች ይገፈትራት ነበር፡፡ በአይኖቿ ወደ ኋላ፤ እየተመለሰች ብትገላመጥም የጠረጠረችው እና የፈራችው አልቀረም ፡፡ ባልጠበቀችው አቅጣጫ ሁለቱም እረኞች ከላይ እንደመጣ የመብረቅ ነበልባል ሆነው ደረሱባት፡፡
እድላዊት መሬት ተከፍታ ብትውጣት እንዴት በተደሰተች ነገር፡፡ ግን መሬት ተከፍታ ልትውጣት አልቻለችም፡፡ በድንጋጤ ሰውነቷ ተርበተበተ፡፡ ላብ በላብ ሆነች፡፡ እረኞቹ ግን የሚተዋትና የሚያዝኑላት አይመስሉም፡፡
ገና ሳይዟት ከነ ነብሷ የሚውጧት ነበር የሚመስሉት፡፡ አንበሳ አፍ ውስጥ እንደገባ ስጋ እንደሆነች ታወቃት፡፡
እረኞቹ ከመንገድ ላይ እጆቿን ይዘው ወደ ጫካ ጎተቷት፡፡ ማምለጥ አልቻለችም፡፡ ነብስ ዝም ብላ ከስጋ እስከ ምትለይ መፈራገጧን አተውም እና እድላዊትም እየጮኸች ባላት አቅም እየተፈራገጠች ጩኸቷን አባረቀችው፡፡
ዘመድና ወገን እንደሌላት መሬት ለመሬት ነብሱ እንደወጣ የአህያ እሬሳ ጎተቷት፡፡ ያ የሚያምረው ለግላጋና ማራኪ ውበቷ በደምና በአቧራ ተለወሰ፡፡
ከሴት ልጅ እንዳልተፈጠሩ እናትና ሴት እህት እንደሌለው ሰው ጭካኔ በተሞላበት አረመኔያዊ ድርጊት ለወሷት፡፡ መንገዱን አስለቅቀው ጫካው ውስጥም አስገቧት፡፡
እግዚአብሔር የእድላዊትን ስቃይና መከራዋን አይቶ ፤ የመማፀኒያ ልመናዋን ሰምቶ ፤ መላክተኛውን የሚካኤል አምሳያ ላከላት፡፡
አደን እንኳን ወጥቶ አያውቅም፡፡ አቶ አርምዴ የሚባል ሚንሻ፡፡ እድላዊት በአረመኔዎቹ እረኞች ተይዛ በምጮህበት በረሃ አካባቢ ነበር፡፡ አንድ አሳቻ ቦታ ተቀምጦ የሚያድነውን አውሬ እየፈለገ፡፡ በጫካው ውስጥ የሴት ልጅ ጩኸት ሰማ፡፡ ተነስቶ ወደ ጩኸቱ እሮጠ፡፡ ሁለት ልጆች እድላዊትን መሬት ለመሬት እየጎተቷት ደረሰ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እድላዊት
ከወሰዳት የንቅልፍ ሸለብታ ነቃች፡፡ መኝታዋን ሳታነጥፍ ለምን እንደተኛች ግራ ተጋባች፡፡ የሆነውን እና የተፈጠረውን ነገር ሁሉ ለማስታወስ አንድ በአንድ ወደ ኋላ ተመልሳ በሃሳብ ነጎደች፡፡
የተነሳችበት ሰዓት ሳይነጋ እኩለ ለሊት ላይ ነው፡፡ ወዴት እንደምትሔድ ጨነቃት፡፡ ልቧ ሸፍቶ ጥፊ እያለ አስቸግሯታል፡፡ ለመጥፋት ወሰነች፡፡
መተኛቷን ትታ ቁጭ አለች፡፡ ወዴት እንደምትጠፋ እና ወዴት እንደምትሔድ አሰበች፡፡ ምን ይገጥመኝ ይሆን ? እንደገና ደግሞ ሃሳቧ እየተቀያየረባት ከምጠፋ ታንቄ ብሞት አይሻልም ? ሰርጌን ለመብላት ሲያደገድጉ በአቋራጭ ተስካሬን ይበሉ ነበር፡፡
ሃሳቧን እየቀያየረች ስታወጣና ስታወረድ ቆየች፡፡ አልሸነፍም ፤ አልረታም ፤ ለሞት እጄን አልሰጥም ብሎ የመጥፋት መንገድን የመረጠው ልቧ ሳይመለስ ቀረ፡፡ ሲገፋፋት ቆየ፡፡ ልቧ የመጥፋት መንገድን ማሸነፍ አልቻለም፡፡
ከሔደችበት የሃሳብ ሰመመን ተመለሰች፡፡ ሌሊቱ እየነጋጋ ነው፡፡ የታጠበውንም ፣ ያልታጠበውንም ልብሷን በፌስታል ሸከፈች፡፡ ቤተሰቦቿ ሳይሰሟት መውጣት እንዳለባት ወሰነች፡፡
መጥፋትን የወሰነችው እድላዊት መነሻዋን እንጅ መድረሻዋን አታውቅም፡፡ ጓዟን ጠቅልላ የእናት አባቷን ቤት እና የተወለደችበትን ቀዬ ለቃ ለመሄድ ተነሳች፡፡በሮቹን ድምፅ ሳታሰማ እና የተከፈቱ ሳታስመስል ግቢውን ለቃ ጨለማ በተቀላቀለበት ሌሊት ጉዞዋን አሃዱ አለች፡፡
ትንሽ እንደተጓዘች ጨለማው እየለቀቀና እየነጋጋ ሄደ፡፡ እለቱ እሁድ በመሆኑ በሩቅ ርቀት ላይ ሰዎች ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሔዱ ተመለከተች፡፡ የምትጓዝበትን መንገድ ትታ ሰው ሳያያት ለመሔድ ፈለገች፡፡ አማራጭ መንገድ በጫካ ውስጥ መረጠች፡፡ የአካባቢው ሰው እንዳያያት የጫካውን መንገድ ይዛ መጓዝ የግድ ሆነባት፡፡
እድላዊት ከቤት ስትወጣ ከልብሷ በስተቀር የሚበላ ስንቅ አልያዘችም፡፡ በጉዞው አድካሚነትና አሰልችነት የተነሳ እራባት፡፡ ውሃም እየጠማት መጣ፡፡ ምግብ የበላችበትን ሰዓት አስታወሰች፡፡ ከትምህርት ቤት ከወንድሟ ጋር ስትመጣ የቀመሰች ነው፡፡ እራትም ሳትበላ ነበር ያደረችው፡፡
ድካሟ እየባሰባት መጣ፡፡ አረፍ ለማለት በምትጓዝበት ጫካ ውስጥ ወደ ሚገኝ አንድ ትልቅ ዛፍ ስር ተቀመጠች፡፡ ውሃ ጥሙ ግን እየባሰባት ሄደ፡፡ ካረፈችበት ዛፍ ስር ተነሳች፡፡እየተጓዘች በአይኖቿ መንደር እና ውሃ በአካባቢው እያፈላለገች ፣ እየቃኘች ስትሔድ ጫካ ከመሆኑ አንፃር ውሃና መንደር የሚባል በቅርብ ልታገኝ አልቻለችም፡፡ ታዲያ ማፈላለጓን አላቋረጠችም፡፡ ከምትሄድበት መንገድ ባሻገር ከብቶች ሲሔዱ ተመለከተች፡፡
ከብቶቹ ወደ ውሃ እንደሚሄዱ ገመተች፡፡ የያዘችውን መንገድ ለቃ ከብቶቹ የሚጓዙበትን መንገድ በመያዝ ተከተለች፡፡
እውነትም የገመተችው ትክክል በመሆኑ ከብቶቹ ውሃ ሲጠጡ አገኘቻቸው፡፡
እድላዊት የጠማትን ውሃ ለመጠጣት ከብቶቹ ከሚጠጡበት ከፍ ብላ ልትጠጣ ተቀመጠች፡፡ የሚያንጎራጉር እና የፉጨት ድምፅ ሰማች፡፡ውሃውን ሳትጠጣ የሚያንጎራጉረውን የሰው ድምፅ ከየት አቅጣጫ እንደሆነ ለመለየት በአይኖቿ አማተረች፡፡
የእንጉርጉሮው ድምፅ እየቀረባት መጣ፡፡ ፍራት ፍራት ተሰማት፡፡ የዛሬን አውጣኝ ከዚህ ጫካ እያለች ፈጣሪዋን እየተማፀነች ፤ እየተርበተበተች አብዝታ ለመነች፡፡
የሚያንጎራጉረው የእንጉርጉሮው ድምፅ ከብቶች የሚያጠጡ እረኞች ነበሩ፡፡
እድላዊት እረኞቹን ፈራች፡፡ የመውጫዋን እና የማምለጫ መንገዷን ፈለገች፡፡
ከብቶቹን ከሚያጠጡት ሁለት እረኞች መካከል አንዱ ከበደ የሚባለው እረኛ እያንጎራጎረ ወደ ወንዙ ቀና አለ፡፡ አንድ የተቀመጠ ሰው ተመለከተ፡፡
ለጓደኛው ደበበ ያየውን ሰው ያ ማነው ? እዛ ላይ የተቀመጠው? አለ፡፡ ደበበ ጓደኛው እንዳለው ወደ ላይ ቀና ብሎ አየ፡፡ ቁጭ ያለ ሰው ተመለከተ፡፡
"ውሃ የሚጠጣ ሰው ይሆናል" አለው ለጓደኛው፡፡
እድላዊት እረኞች በእጃቸው እየተጠቋቆሙ ሲመለከቷት የባሰ ፈራች፡፡ በድንጋጤ እንደጠማት ልትጠጣ በእጇ የጨለፈችውን ውሃ እንኳን ሳትጠጣ ተነሳች፡፡ ቁጭ ብላ ከእረኞቹ ማምለጫ ስታማትር ወደ አገኘችው መውጫ መንገድ ተነስታ ለማምለጥ ሞከረች፡፡
እረኞቹ እድላዊትን ወንዝ ላይ ተቀምጣ ሰው ከመሆኗ ውጪ ወንድ ይሁን ሴት ትሁን አላወቋትም ነበር፡፡
እድላዊት ውሃ ለመጠጣት ከተቀመጠችበት ተነስታ ስትሮጥ ተመልክተው ሴት መሆኗን ለይዋት ፤ ከብቶቻቸውን ማጠጣታቸውን ትተው በእድላዊት መልክና ውበት እየተገረሙ በአይናቸው ተከትለው ሸኟት፡፡
አይን ለአይን እየተያዩ፡፡ የማነች ቀሽት ባክህ! ስታምር ፤ ከየት ይሆን የምትመጣው?
እውነትም ቀሽት ናት፡፡ ደግሞ እየፈራች ነው ፣ የምትሔደው፡፡ ምን ያገላምጣታል;
እረኞቹ እድላዊት ስትርበተበት አይተዋት ፤ ብቻዋንና የተከተላት ሰው አለመኖሩን ነቅተውባታል፡፡ይች ቀሽት ሳታመልጠን እንከተላት ተባባሉ፡፡ መጀመሪያ በአይናቸው ሸኝተዋት ቢመለሱም ልባቸው ግን ተከትሏት ነበር፡፡ እየተጣደፉ
እንዳታመልጣቸው በሔደችበት መንገድ ተከተሏት፡፡ እድላዊት የልቧ ትርታ ጨመረ፡፡ ሰውነቷ ሁሉ እየተንቀጠቀጠ፡፡ ትንፋሿ ቁርጥ ቁርጥ አለ፡፡ ይከተሉኝ ይሆን ብላ ተጠራጠረች፡፡ እንዴው አምላኬ
የዛሬን አውጣኝ፡፡ ከዚህ ከጨለማ፡፡ እያለች እንዳይደርሱባት በደከመ አቅሟ ለመሮጥ ሞከረች፡፡ ለእሷ የሮጠች መሰላት፡፡ ዳገቱ ግን ሊገፋላት አልቻለም፡፡ መልሶ ወደ መጣችበች ይገፈትራት ነበር፡፡ በአይኖቿ ወደ ኋላ፤ እየተመለሰች ብትገላመጥም የጠረጠረችው እና የፈራችው አልቀረም ፡፡ ባልጠበቀችው አቅጣጫ ሁለቱም እረኞች ከላይ እንደመጣ የመብረቅ ነበልባል ሆነው ደረሱባት፡፡
እድላዊት መሬት ተከፍታ ብትውጣት እንዴት በተደሰተች ነገር፡፡ ግን መሬት ተከፍታ ልትውጣት አልቻለችም፡፡ በድንጋጤ ሰውነቷ ተርበተበተ፡፡ ላብ በላብ ሆነች፡፡ እረኞቹ ግን የሚተዋትና የሚያዝኑላት አይመስሉም፡፡
ገና ሳይዟት ከነ ነብሷ የሚውጧት ነበር የሚመስሉት፡፡ አንበሳ አፍ ውስጥ እንደገባ ስጋ እንደሆነች ታወቃት፡፡
እረኞቹ ከመንገድ ላይ እጆቿን ይዘው ወደ ጫካ ጎተቷት፡፡ ማምለጥ አልቻለችም፡፡ ነብስ ዝም ብላ ከስጋ እስከ ምትለይ መፈራገጧን አተውም እና እድላዊትም እየጮኸች ባላት አቅም እየተፈራገጠች ጩኸቷን አባረቀችው፡፡
ዘመድና ወገን እንደሌላት መሬት ለመሬት ነብሱ እንደወጣ የአህያ እሬሳ ጎተቷት፡፡ ያ የሚያምረው ለግላጋና ማራኪ ውበቷ በደምና በአቧራ ተለወሰ፡፡
ከሴት ልጅ እንዳልተፈጠሩ እናትና ሴት እህት እንደሌለው ሰው ጭካኔ በተሞላበት አረመኔያዊ ድርጊት ለወሷት፡፡ መንገዱን አስለቅቀው ጫካው ውስጥም አስገቧት፡፡
እግዚአብሔር የእድላዊትን ስቃይና መከራዋን አይቶ ፤ የመማፀኒያ ልመናዋን ሰምቶ ፤ መላክተኛውን የሚካኤል አምሳያ ላከላት፡፡
አደን እንኳን ወጥቶ አያውቅም፡፡ አቶ አርምዴ የሚባል ሚንሻ፡፡ እድላዊት በአረመኔዎቹ እረኞች ተይዛ በምጮህበት በረሃ አካባቢ ነበር፡፡ አንድ አሳቻ ቦታ ተቀምጦ የሚያድነውን አውሬ እየፈለገ፡፡ በጫካው ውስጥ የሴት ልጅ ጩኸት ሰማ፡፡ ተነስቶ ወደ ጩኸቱ እሮጠ፡፡ ሁለት ልጆች እድላዊትን መሬት ለመሬት እየጎተቷት ደረሰ፡፡
👍86❤7🔥1👏1
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ተመስገን
ከጠፋች በኋላ፤ ብቻ ሳይሆን ከእድላዊት ጋርም ከትምህርት ቤት መጥተው ምሳቸውን ከበሉበት ቀን አንስቶ ወደ ትምህርት ቤት ለመሄድ አይደለም አስቦትም አያውቅም፡፡
ወደ ትምህርት ቤትም አልሄደም፡፡ ትዳር የሚባል ሳያስብ እናት አባቱን እየረዳ የግብርና ስራውን ሌት ከቀን እየተጋ መዋሉን ተያይዞታል፡፡
ከሚወዳት እህቱ እድላዊት ውጪ የቅርብ ጓደኛዬ የሚለው ሴትም ይሁን ወንድ ለግዜው አልነበረውም፡፡ አንድ ቀን በስራ ምክንያት ከሰፈሩ ልጅ ያሬድ ጋር ይገናኛል፡፡ ታዲያ ተመስገንና ያሬድ ከዚህ በፊት ከእግዚአብሔር ሰላምታ በስተቀር የጠበቀ ግንኙነት አልነበራቸውም፡፡
ያሬድ ተመስገንንም ይሁን ቤተሰቦቹን በደንብ ጠንቅቆ ያውቃቸዋል፡፡ በጥሩ ቤተሰብ ያደገና ከቤተሰቦቹ ጋር የሚኖር ገና ታዳጊ ወጣት ሆኖ በራሱ ፈቃድ
ትምህርቱን አቋርጦ ወደ ግብርናው ከተሰማራ ሰንበትበት ብሏል፡፡
ከተመስገን ጋር ግንኙነታቸው ከእግዚአብሔር ሰላምታ አልፎ ወደ መቀራረብ ደረሰ ፤ አልፎ አልፎም ስራ በመተጋገዝ መረዳዳት ጀምረዋል፡፡
ተመስገን እንደ እህቱ የሚሆንለት ባያገኝም ለእሱ የሚሆንና የሚያበረታታው የቅርብ ጓደኛ በማግኘቱ ደስተኛ አድርጎታል፡፡
ከእለታት አንድ ቀን እነያሬድ ቤት የሽንብራ ቆሎ እየፈጩ ፤ ከስንዴው ጠላ ጎንጨት እያሉ የወደፊት ምኞታቸውና አላማቸውን ይጫወታሉ፡፡
"ለወደፊት ምን ለመስራት አስበሃል?" ብሎ ጠየቀው ተመስገን፡፡
"እኔ ለቀጣይ ያስብኩት አሁን የጀመርኩትን ቤት ስጨርስ ቤተሰቦቼ ትምህርትህን ከተወህ ማግባት አለብህ እያሉኝ ስለሆነ ለማግባት አቅጃለሁ፡፡ ብሎት አንተስ ምን አስበሃል? አለው ያሬድ፡፡
ተመስገን የወደፊት ምኞትና እቅዱ ከጓደኛው ያሬድ የተለየና ተቃራኒ ነው፡፡ "እኔ እንኳን እህቴን እስከማገኝ ድረስ ትዳር የመያዝ ሃሳብና ፍላጎት የለኝም"፡፡
ቤተሰቦቸን እየረዳሁ ለራሴም ትንሽ እያጠራቀምኩ ለመኖር ነው የማስበው አለ፡፡
ያሬድ የተመስገንን እቅድ ሲሰማ እህቱን በፊትም እደሚወዳት ስለሚያቅ ለምን አታገባም ብሎም አልጠይቀውም..፡፡
አርምዴ
ባለቤታቸው ከሞተ በኋላ፤ ሌላ ባል አላገቡም፡፡ ወደ ውጭ ወጥተው ጎንበስ ቀና ብለው መስራት አይችሉም፡፡
ልጃቸው ሰርቶ የሚሰጣቸውን እህል አብስለው ለመብላት ያልተቸገሩ የስልሳ ዓመት የእድሜ ባለፀጋ ናቸው፡፡ የአርምዴ እናት ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
ቀኑ እንደመምሸት ብሎ ለዓይን ያዝ አድርጓል፡፡ ኩራዝ ለመለኮስ ከምድጃቸው እሳት ለማቀጣጠል ይታገላሉ፡፡
አይናቸው ተርገበገበባቸው፡፡ ዛሬ ደግሞ በምሽት ምን ሊያሳየኝ ነው ፡፡ አይኔ የሚርገበገበው እያሉ የውጭ በር ተንኳኳ
እሳት ማቀጣጠሉን ተወት አርገው ወደ ውጭ ወጡ፡፡ ልጃቸው አርምዴ እድላዊትን አዝሎ ገባ፡፡ ደነገጡ፡፡
"ውይ! በሞትኩት ልጄ ምን ሆና ነው? ብለው ጠየቁት፡፡
እረኞች ጫካ ውስጥ መሬት ለመሬት ጎትተዋት ነው፡፡
"እና በጣም ጎድተዋታል" ?
"አዎ! ይዣትም ስመጣ ለማናገር ብሞክርም ማናገር አልቻለችም"፡፡
"ታዲያ ከየት እንደመጣችም አልነገረችህም"?
"አልነገረችኝም ፡፡ ጩኸት ሰምቼ እየሮጥሁ ሲሄድ ጥለዋት ተበታተኑ፡፡ እሷም ተጎድታ ስለነበር አላናገረችኝም፡፡ እንዴው እግዚአብሔር ድረስላት ሲለኝ ነው እንጂ ዛሬ አደን የሔድኩት ይገሏት ነበር፡፡
"አሁን ምን እንስጣት? ነው ትንሽ ትተኛ? ድካሟ እስከ ሚያልፍላት አሉ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
ወደ አስተኛት ፍራሽ ላይ ተጠጋ፡፡ እድላዊት አይኖቿን አንከራተተች፡፡ ግራና ቀኝ ተቁለጨለጨች፡፡
አርምዴ የእድላዊትን አይኖች መንከራተትና በእንባ መሞላት አየ፡፡ እሱም ከየት መጣ ሳይባል አይኖቹ በእንባ ተሞሉ፡፡
እድላዊት አርምዴን የምትመለከተው ውሃ ስጠኝ ለማለት ነበር፡፡ ግን መናገር አቅቷታል፡፡
አቶ አርምዴ ውሃ መፈለጓን የተረዳት አይመስልም፡፡ አንጀቱ እንደነብሰጡር ተላወሰ፡፡ እንባ እየተናነቀው "ምን ልስጥሽ " አላት፡፡
እድላዊት መናገር አልቻለችም፡፡ በእጇ ውሃ እንደ ጠማት አመለከተችው፡፡
አቶ አርምዴ በምልክት የገለፀችውን ሳያደናግረው ተረዳት፡፡ ውሃ ቀድቶ ሰጣት፡፡
ውሃው ወደ ውስጥ መግባቱን ትቶ ግራና ቀኝ በአፏ ወደ ውጭ ፈሰሰ፡፡
እድላዊት በውሃ ጥም የተነሳ ቶንሲሏ ወርዷል፡፡ አቶ አርምዴ የባሰ ተጨነቀ
"ውይ በሞትኩት ልጄን ውሃ አልወርድላት አለ ? ቶንሲሏ ወርዶ ይሆናል አሉ፤ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
"እና ምን ይሻላል? መድሃኒት በቅርብ አይገኝም? አለ ፤ አቶ አርምዴ፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ የሃበሻ መድሃኒት ሊያቀምሷት መድሃኒቱን እንዲያመጣላቸው ልጃቸውን እንዳይልኩት መድሃኒቱ ሲቆረጥ ስሙ መጠራት የለበትም፡፡ እራሳቸው ለመቁረጥ ቆይ እስቲ መጣሁ ብለው ወደ ጓሮ ሄዱ፡፡
ለቶንሲል መድሃኒት የሚሆነውን ሰባት የጌሾ ቀንበጥ ቆርጠው አመጡ፡፡ ለእድላዊት እንድታኝከው ሰጧት፡፡
እድላዊት መናገር ቢያቅታትም መስማት ትችላለች፡፡ የተሰጠችውን የቶንሲል መድሃኒት አኝኪው ስለተባለች ብቻ
እየመረራት ቢሆንም ጨክና አኘከችው፡፡
በውሃ ጥም ምራቋ ደርቋል፡፡ ከንፈሮቿም ኩበት መስለዋል፡፡ ምላሷ ብቻ ብቅ ጥልቅ ይላል፡፡ ነብሷ ልትወጣ ደረሰች፡፡ ሰውነቷ በላብ ተዘፈቀ፡፡ ልቧ ተጨነቀች፡፡ በጀመረችው የምልክት ቋንቋ ውሃ ስጡኝ ብላ በእጇ አመለከተች፡፡
አቶ አርምዴ የእድላዊት ነገር አሁንም ግራ ገባው፡፡ ከሸንበቆ ላይ ቀጭን ሸንበቆ ተከርክሞ እድላዊት በሸንበቆው አማካኝነት ውሃ እንድትቀምስ ተደረገ፡፡
ለእድላዊት እንጀራ እንዳይሰጧት ችላ አትበላም፡፡ ምን እንደሚሰጧት ጨነቃቸው፡፡ የእድላዊት ነገር አንጀታቸውን በላው፡፡
በደከመ አቅማቸውም ቢሆን ትንሽ ገንፎ አገንፍተው እንድትቀምስ አደረጉ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
እድላዊት የተሰራላትን ገንፎ ለመድሃኒት ያህል ቀመሰች፡፡ ወ/ሮ በሰልፏ ለቶንሲሏ ሌላ መዳኒት ዝንጅብል እንድታኝክበት ሰጧት፡፡
"ለቶንሲል ጥሩ ነው፡፡ ለነገ በደንብ ይሻልሻል፡፡ አይዞሽ እያሉ ልጃቸው ያሰረላትን ጨርቅ ከቁስሏ ላይ ፈቱላት፡፡ ለብ ባለ ውሃ አጠቡላት፡፡ ያበጠውን እግርና እጇንም በቅባት አሹላት፡፡ የተላላጠውን ቁስሏንም በነጠላ ጨርቅ ተኩሰው መኝታ ላይ ጋደም እንድትል አደረጉ፡፡
አቶ አርምዴ የሚደረግላትን ካደረገ በኋላ ወደ ቤቱ ሄደ፡፡ አድሮ በነጋታው ጥዋት እድላዊት እንዴት እንዳደረች ለመጠየቅ ከመኝታው ተነስቶ ሲመጣ እናቱ የቤቱን በር ከፍተው ሲወጡ ደረሰ፡፡
የእግዚአብሔር ሰላምታ ተለዋውጠው "ደግሞ ማታ እመለሳለሁ ብለህ ሳትመጣ ቀረህ በሰላም ነው ያልተመለስከው? አሉት ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
"ለመምጣት አስቤ ነበር፡፡ ግን ቤቱንና ከብቶቹን ትቼ እንዳልመጣ አውሬ እንኳን ቢገባ የሚሰማ ስላልነበረ ቀረሁ"፡፡ እንዴት አደረች ልጅቷ?ተሸሏት አላደረችም? አለ፡፡
የእድላዊት ስቃይና መከራ ከአንጀቱ ገብቶ ሳይወጣ አንጀቱ እያለቀሰላት እህል እንኳን አልወርድ ብሎት ለአደን ሲሄድ በቀመሰው ቁራሽ እንጀራ ነበር፡፡ እራት ሳይቀምስ ያደረው፡፡
ከአሁን አሁን ያማት ይሆን ? እያሉ ሌሊቱን ሙሉ እንቅልፍ ሳይወስዳቸው አይደለም በዓይናቸው ሳይዞር ነበር ያደሩት ወ/ሮ በሰልፏም፡፡
"ሰላም አድራለች፡፡ ብቻ ሌሊቱን ሲያቃዧት ነው ያደረው፡፡ አሟት ይሆን ብየ ሌሊት ተነስቼ ሳያት ከቅዠት በስተቀር ምንም አላየሁባትም፡፡ ከነጋም አልቀሰቀስኳትም፡፡ ቅዝቃዜ ስላለ ትንሽ ትተኛ ብየ ነው፡፡ እስኪ አሁን አንተ ከመጣህ ቀስቅሳትና እንዴት እንዳደረች ጠይቃት አሉ፡፡ ቤታቸውን ለመጥረግ የቤት መጥረጊያ ቅጠል ለማምጣት ወደ ውጭ እየወጡ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ተመስገን
ከጠፋች በኋላ፤ ብቻ ሳይሆን ከእድላዊት ጋርም ከትምህርት ቤት መጥተው ምሳቸውን ከበሉበት ቀን አንስቶ ወደ ትምህርት ቤት ለመሄድ አይደለም አስቦትም አያውቅም፡፡
ወደ ትምህርት ቤትም አልሄደም፡፡ ትዳር የሚባል ሳያስብ እናት አባቱን እየረዳ የግብርና ስራውን ሌት ከቀን እየተጋ መዋሉን ተያይዞታል፡፡
ከሚወዳት እህቱ እድላዊት ውጪ የቅርብ ጓደኛዬ የሚለው ሴትም ይሁን ወንድ ለግዜው አልነበረውም፡፡ አንድ ቀን በስራ ምክንያት ከሰፈሩ ልጅ ያሬድ ጋር ይገናኛል፡፡ ታዲያ ተመስገንና ያሬድ ከዚህ በፊት ከእግዚአብሔር ሰላምታ በስተቀር የጠበቀ ግንኙነት አልነበራቸውም፡፡
ያሬድ ተመስገንንም ይሁን ቤተሰቦቹን በደንብ ጠንቅቆ ያውቃቸዋል፡፡ በጥሩ ቤተሰብ ያደገና ከቤተሰቦቹ ጋር የሚኖር ገና ታዳጊ ወጣት ሆኖ በራሱ ፈቃድ
ትምህርቱን አቋርጦ ወደ ግብርናው ከተሰማራ ሰንበትበት ብሏል፡፡
ከተመስገን ጋር ግንኙነታቸው ከእግዚአብሔር ሰላምታ አልፎ ወደ መቀራረብ ደረሰ ፤ አልፎ አልፎም ስራ በመተጋገዝ መረዳዳት ጀምረዋል፡፡
ተመስገን እንደ እህቱ የሚሆንለት ባያገኝም ለእሱ የሚሆንና የሚያበረታታው የቅርብ ጓደኛ በማግኘቱ ደስተኛ አድርጎታል፡፡
ከእለታት አንድ ቀን እነያሬድ ቤት የሽንብራ ቆሎ እየፈጩ ፤ ከስንዴው ጠላ ጎንጨት እያሉ የወደፊት ምኞታቸውና አላማቸውን ይጫወታሉ፡፡
"ለወደፊት ምን ለመስራት አስበሃል?" ብሎ ጠየቀው ተመስገን፡፡
"እኔ ለቀጣይ ያስብኩት አሁን የጀመርኩትን ቤት ስጨርስ ቤተሰቦቼ ትምህርትህን ከተወህ ማግባት አለብህ እያሉኝ ስለሆነ ለማግባት አቅጃለሁ፡፡ ብሎት አንተስ ምን አስበሃል? አለው ያሬድ፡፡
ተመስገን የወደፊት ምኞትና እቅዱ ከጓደኛው ያሬድ የተለየና ተቃራኒ ነው፡፡ "እኔ እንኳን እህቴን እስከማገኝ ድረስ ትዳር የመያዝ ሃሳብና ፍላጎት የለኝም"፡፡
ቤተሰቦቸን እየረዳሁ ለራሴም ትንሽ እያጠራቀምኩ ለመኖር ነው የማስበው አለ፡፡
ያሬድ የተመስገንን እቅድ ሲሰማ እህቱን በፊትም እደሚወዳት ስለሚያቅ ለምን አታገባም ብሎም አልጠይቀውም..፡፡
አርምዴ
ባለቤታቸው ከሞተ በኋላ፤ ሌላ ባል አላገቡም፡፡ ወደ ውጭ ወጥተው ጎንበስ ቀና ብለው መስራት አይችሉም፡፡
ልጃቸው ሰርቶ የሚሰጣቸውን እህል አብስለው ለመብላት ያልተቸገሩ የስልሳ ዓመት የእድሜ ባለፀጋ ናቸው፡፡ የአርምዴ እናት ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
ቀኑ እንደመምሸት ብሎ ለዓይን ያዝ አድርጓል፡፡ ኩራዝ ለመለኮስ ከምድጃቸው እሳት ለማቀጣጠል ይታገላሉ፡፡
አይናቸው ተርገበገበባቸው፡፡ ዛሬ ደግሞ በምሽት ምን ሊያሳየኝ ነው ፡፡ አይኔ የሚርገበገበው እያሉ የውጭ በር ተንኳኳ
እሳት ማቀጣጠሉን ተወት አርገው ወደ ውጭ ወጡ፡፡ ልጃቸው አርምዴ እድላዊትን አዝሎ ገባ፡፡ ደነገጡ፡፡
"ውይ! በሞትኩት ልጄ ምን ሆና ነው? ብለው ጠየቁት፡፡
እረኞች ጫካ ውስጥ መሬት ለመሬት ጎትተዋት ነው፡፡
"እና በጣም ጎድተዋታል" ?
"አዎ! ይዣትም ስመጣ ለማናገር ብሞክርም ማናገር አልቻለችም"፡፡
"ታዲያ ከየት እንደመጣችም አልነገረችህም"?
"አልነገረችኝም ፡፡ ጩኸት ሰምቼ እየሮጥሁ ሲሄድ ጥለዋት ተበታተኑ፡፡ እሷም ተጎድታ ስለነበር አላናገረችኝም፡፡ እንዴው እግዚአብሔር ድረስላት ሲለኝ ነው እንጂ ዛሬ አደን የሔድኩት ይገሏት ነበር፡፡
"አሁን ምን እንስጣት? ነው ትንሽ ትተኛ? ድካሟ እስከ ሚያልፍላት አሉ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
ወደ አስተኛት ፍራሽ ላይ ተጠጋ፡፡ እድላዊት አይኖቿን አንከራተተች፡፡ ግራና ቀኝ ተቁለጨለጨች፡፡
አርምዴ የእድላዊትን አይኖች መንከራተትና በእንባ መሞላት አየ፡፡ እሱም ከየት መጣ ሳይባል አይኖቹ በእንባ ተሞሉ፡፡
እድላዊት አርምዴን የምትመለከተው ውሃ ስጠኝ ለማለት ነበር፡፡ ግን መናገር አቅቷታል፡፡
አቶ አርምዴ ውሃ መፈለጓን የተረዳት አይመስልም፡፡ አንጀቱ እንደነብሰጡር ተላወሰ፡፡ እንባ እየተናነቀው "ምን ልስጥሽ " አላት፡፡
እድላዊት መናገር አልቻለችም፡፡ በእጇ ውሃ እንደ ጠማት አመለከተችው፡፡
አቶ አርምዴ በምልክት የገለፀችውን ሳያደናግረው ተረዳት፡፡ ውሃ ቀድቶ ሰጣት፡፡
ውሃው ወደ ውስጥ መግባቱን ትቶ ግራና ቀኝ በአፏ ወደ ውጭ ፈሰሰ፡፡
እድላዊት በውሃ ጥም የተነሳ ቶንሲሏ ወርዷል፡፡ አቶ አርምዴ የባሰ ተጨነቀ
"ውይ በሞትኩት ልጄን ውሃ አልወርድላት አለ ? ቶንሲሏ ወርዶ ይሆናል አሉ፤ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
"እና ምን ይሻላል? መድሃኒት በቅርብ አይገኝም? አለ ፤ አቶ አርምዴ፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ የሃበሻ መድሃኒት ሊያቀምሷት መድሃኒቱን እንዲያመጣላቸው ልጃቸውን እንዳይልኩት መድሃኒቱ ሲቆረጥ ስሙ መጠራት የለበትም፡፡ እራሳቸው ለመቁረጥ ቆይ እስቲ መጣሁ ብለው ወደ ጓሮ ሄዱ፡፡
ለቶንሲል መድሃኒት የሚሆነውን ሰባት የጌሾ ቀንበጥ ቆርጠው አመጡ፡፡ ለእድላዊት እንድታኝከው ሰጧት፡፡
እድላዊት መናገር ቢያቅታትም መስማት ትችላለች፡፡ የተሰጠችውን የቶንሲል መድሃኒት አኝኪው ስለተባለች ብቻ
እየመረራት ቢሆንም ጨክና አኘከችው፡፡
በውሃ ጥም ምራቋ ደርቋል፡፡ ከንፈሮቿም ኩበት መስለዋል፡፡ ምላሷ ብቻ ብቅ ጥልቅ ይላል፡፡ ነብሷ ልትወጣ ደረሰች፡፡ ሰውነቷ በላብ ተዘፈቀ፡፡ ልቧ ተጨነቀች፡፡ በጀመረችው የምልክት ቋንቋ ውሃ ስጡኝ ብላ በእጇ አመለከተች፡፡
አቶ አርምዴ የእድላዊት ነገር አሁንም ግራ ገባው፡፡ ከሸንበቆ ላይ ቀጭን ሸንበቆ ተከርክሞ እድላዊት በሸንበቆው አማካኝነት ውሃ እንድትቀምስ ተደረገ፡፡
ለእድላዊት እንጀራ እንዳይሰጧት ችላ አትበላም፡፡ ምን እንደሚሰጧት ጨነቃቸው፡፡ የእድላዊት ነገር አንጀታቸውን በላው፡፡
በደከመ አቅማቸውም ቢሆን ትንሽ ገንፎ አገንፍተው እንድትቀምስ አደረጉ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
እድላዊት የተሰራላትን ገንፎ ለመድሃኒት ያህል ቀመሰች፡፡ ወ/ሮ በሰልፏ ለቶንሲሏ ሌላ መዳኒት ዝንጅብል እንድታኝክበት ሰጧት፡፡
"ለቶንሲል ጥሩ ነው፡፡ ለነገ በደንብ ይሻልሻል፡፡ አይዞሽ እያሉ ልጃቸው ያሰረላትን ጨርቅ ከቁስሏ ላይ ፈቱላት፡፡ ለብ ባለ ውሃ አጠቡላት፡፡ ያበጠውን እግርና እጇንም በቅባት አሹላት፡፡ የተላላጠውን ቁስሏንም በነጠላ ጨርቅ ተኩሰው መኝታ ላይ ጋደም እንድትል አደረጉ፡፡
አቶ አርምዴ የሚደረግላትን ካደረገ በኋላ ወደ ቤቱ ሄደ፡፡ አድሮ በነጋታው ጥዋት እድላዊት እንዴት እንዳደረች ለመጠየቅ ከመኝታው ተነስቶ ሲመጣ እናቱ የቤቱን በር ከፍተው ሲወጡ ደረሰ፡፡
የእግዚአብሔር ሰላምታ ተለዋውጠው "ደግሞ ማታ እመለሳለሁ ብለህ ሳትመጣ ቀረህ በሰላም ነው ያልተመለስከው? አሉት ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
"ለመምጣት አስቤ ነበር፡፡ ግን ቤቱንና ከብቶቹን ትቼ እንዳልመጣ አውሬ እንኳን ቢገባ የሚሰማ ስላልነበረ ቀረሁ"፡፡ እንዴት አደረች ልጅቷ?ተሸሏት አላደረችም? አለ፡፡
የእድላዊት ስቃይና መከራ ከአንጀቱ ገብቶ ሳይወጣ አንጀቱ እያለቀሰላት እህል እንኳን አልወርድ ብሎት ለአደን ሲሄድ በቀመሰው ቁራሽ እንጀራ ነበር፡፡ እራት ሳይቀምስ ያደረው፡፡
ከአሁን አሁን ያማት ይሆን ? እያሉ ሌሊቱን ሙሉ እንቅልፍ ሳይወስዳቸው አይደለም በዓይናቸው ሳይዞር ነበር ያደሩት ወ/ሮ በሰልፏም፡፡
"ሰላም አድራለች፡፡ ብቻ ሌሊቱን ሲያቃዧት ነው ያደረው፡፡ አሟት ይሆን ብየ ሌሊት ተነስቼ ሳያት ከቅዠት በስተቀር ምንም አላየሁባትም፡፡ ከነጋም አልቀሰቀስኳትም፡፡ ቅዝቃዜ ስላለ ትንሽ ትተኛ ብየ ነው፡፡ እስኪ አሁን አንተ ከመጣህ ቀስቅሳትና እንዴት እንዳደረች ጠይቃት አሉ፡፡ ቤታቸውን ለመጥረግ የቤት መጥረጊያ ቅጠል ለማምጣት ወደ ውጭ እየወጡ፡፡
👍88❤13🥰3👎1
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
#ያሬድ
ሁሉም ተሳካለት፡፡ ከዚያው አካባቢ አበበች የምትባል ልጅ አገባ፡፡ ኑሮውን ለማሻሻል ከግብርና ስራው በተጨማሪ የንግድ ስራ ለመስራት አቀደ፡፡ ለባለቤቱ ማማከር እንዳለበት ወሰነ፡፡
አንድ ቀን ከባለቤቱ ጋር እራት እየበሉ ነው፡፡ "እንዴው ይሔ የግብርና ስራ ከእጅ ወደ አፍ ብቻ ሆነ፡፡ በትርፍ ሰዓቴ እንኳን ንግድ ብሞክር ፤ ሳይሻል አይቀርም" አላት ያሬድ ለባለቤቱ አበበች፡፡ በእጁ የተቀለለውን እንጀራ እየጎረሰ፡፡
"ሃሳብህ ጥሩ ነው፡፡ ግን ምን ዓይነት ንግድ ነው የምነግደው? አለች አበበች፡፡
ጥያቄን በጥያቄ እንዲሉ መልሶ "ቡና ይሻላል ወይስ አልባሳት?'' አላት፡፡
ሁለቱም አማራጮች ጥሩ ናቸው፡፡ ግን ከየት አምጥተህ ነው የምትነግደው ?፡፡
ያሬድ ተጨማሪ የንግድ ስራ ለመስራት እንጅ ከየት አምቶ እና ምን እንደሚነግድ እንኳን በደንብ አላሰበበትም፡፡
አልባሳት በቅርብ ባይገኝም ወደ ድሬደዋ በመሔድ ማግኘት እንደሚቻል ግን ያውቃል፡፡
"ድሬደዋ በውሎ ገባ መድረስ ይቻላል እንዴ"? አለችው፡፡
ያሬድ ድሬደዋ ሔዶባት አያውቅም፡፡ "ሰዎች ሲያወሩ ሰምቻለሁ፡፡ ውሎ ገባ አይደረስም፡፡ መኪና ከተገኘ ሁለት ቀን ቢወስድ ነው"፡፡
ያሬድ ከባለቤቱ ተስማምቶ ፤ ማምጫ ገንዘብ ለሰው አበድሮት የነበረውን ሰበሰበ፡፡ ከቤትም ትንሽ ስንዴ ሸጦ ለመነገጃ የሚሆን ገንዘብ አጠራቀመ፡፡
ታዲያ ወደ ድሬደዋ ሲሔድ ቤቱን ፣ ከብቶቹንና ባለቤቱን ብቻዋን ጥሏት እንዳይሄድ ስጋት አደረበት፡፡
ተመስገን ለቤተሰቦቹ ውሃ ሊቀዳ አህያ ላይ ጀሪካን እየጫነ ነው፡፡
"ደህና አደርህ ተመስገን" አለ፡፡ ቤቱን እና ከብቶቹን እስከሚመለስ እንዲያይለት ሊጠይቀው በጥዋት የመጣው
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደርህ ያሬድ" አለ፡፡ ጀርካን መጫኑን ተወት አድርጎ ወደ ያሬድ እየተጠጋ፡፡ የእጅ ሰላምታ ሰጥቶት ወደ ቤት ግባ አለው ተመስገን፡
"አልገባም ይሁን" ብሎ "አንተጋር ነበር የመጣሁት" አለ
"ምነው በሰላም" ?
"አይ! በሰላም ነው፡፡ አንድ ነገር ላስቸግርህ ብየ ነው የመጣሁት"፡፡
"ምን ችግር አለው የምችል ከሆነ"፡፡
"አይ! ቀላል ነው"፡፡ እኔ ወደ ድሬደዋ ለመሄድ ስለፈለግሁ ቤቴን እንድትከታተልልኝ ፈልጌ ነበር፡፡
"ምነው በሰላም ነው፡፡ ወደ ድሬደዋ የምትሄደው ?
"ለራሴ ጉዳይ ነው፡፡ ትንሽ አልባሳት ለመነገድ ስላሰብኩ ለማምጣት ነው የምሔደው ፡፡
"አይ! ደህና ነው፡፡ እከታተልልሃለሁ ግን ለምን አብረን ብቻህን እዛ ድረስ ከምትሄድ ለኔም ታስተዋውቀኝ ነበር አለ ተመስገን፡፡
"ሐሳብህ ጥሩ ነው፡፡ ግን እኔም ገና አዲስ ስለሆንኩ መጀመሪያ ልየውና የሚያዋጣ ከሆነ አብረን እንሔዳልን እስከዛ ገንዘብ አጠራቅም፡፡ ብሎት ተሰነባብተው ተለያያዩ።
እድላዊት
ሲሻለኝ ውለታቸውን በጉልበቴም ቢሆን አግዠ እከፍላቸዋለሁ ብላ አሰበች፡፡ ግን ያሰበችው ቶሎ አልሆነም፡፡
ከህመሟ ሳይሻላት እየባሰባትና እየጠናባት ሄደ፡፡ ሁለት ወር ከ18 ቀን የአልጋ ቁራኛ ሆና አሳለፈች፡፡ ምነው እዛው ጫካ ሞቼ በቀረሁ ኖሮ፡፡ እንደዚህ የአልጋ ቁራኛ ሆኘ ሰው ከማስቸገር ምን አለ ፈጣሪየ መከራና ስቃየን ከምታበዛብኝ ብትገላግለኝ?፡፡ ፈጣሪዋን እየተማፀነች እና እያማረረች ውላ በተራው ጨለማውን ተገን አድርጎ ሌሊቱ ይተካል፡፡
እድላዊት ሌሊትም ሆነ ቀን የምትተኛበት የእንቅልፍ ሰዓት በሃሳብና በጭንቀት ሳይታወቃት ቀን መሽቶ ይነጋል፡፡ በብርድልብስ ውስጥ ተሸፍና የምታለቅሰው እንባ ቢጠራቀም ዘመዶቿንና ቤተሰቦቿን ይቀብርላት ነበር፡፡
አንዳንዴ ሲጨንቃት የተሻላት ይመስላታል፡፡ ለመሄድ አስባ ትነሳለች፡፡ አሁን ልሂድ በቃ ተሸሎኛል፡፡ እናንተንም
አስቸገርኳችሁ፡፡ ተነስታ ለመሄድ ስታስብ አቅም ያንሳታል ፤ እራሷን ያዞራታል፡፡ ተመልሳ መቀመጥ አትችልም፡፡
የእድላዊት ቶሎ አለመዳንና የአልጋ ቁራኛ መሆኗ አሳስቧቸዋል ፤ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡ ምነው ፈጣሪዬ ይህችን አንድ ፍሬ ህፃን የአልጋ ቁራኛ ከምታደርግብኝ ለኔ ብሰጠኝ፡፡ እያሉ ፈጣሪያቸውን እየተማፀኑ ውለው ማደራቸው ሳያንሳቸው እድላዊት ደግሞ በሽታዋን ሳታስብ አስቸገርኳችሁ ስትላቸው የባሰ ያስጨንቃቸዋል፡፡
እባክሽን ልጄ ተለመኝኝ ; እባክሽ ስለፈጠረሽ አምላክ ; በደንብ ሲሻልሽ ትሔጃለሽ፡፡ ልጄ እባክሽ ለኔ ምንም አታስቢ፡፡ አንቺ ብቻ ዳኝልኝ፡፡ ለሁሉም ይደረሳል፡፡ ብለው ምንም እንዳታስብና እንዳትጨነቅ ይማፀኗታል ፡፡
እድላዊት በትንሹም ቢሆን እየተሸላት መጣ፡፡ መጀመሪያ ውለታቸውን ከፍየ እሄዳለሁ ብላ ያሰበችውን አረሳችም፡፡
ገና በደንብ ሳይሻላት ለመርዳት ተቻኮለች፡፡ ቡና ሲያፈሉ እኔ አፈላለሁ እያለች ወ/ሮ በሰልፏን ታስቸግራቸውም ጀመር፡፡ ቆይ በደንብ አልተሻለሽም፡፡ በደንብ ሲሻልሽ ታፈያለሽ፡፡ ቢከለክሏትም እሽ አትላቸውም ነበር፡፡
እድላዊት በቤቱ ውስጥ ያለውን ስራ በመስራት መርዳትና ማገዝ ጀመረች፡፡ ትንሽ ሲሻለኝ እሄዳለሁ ያለችውን ሰረዘች፡፡ ውለታቸውን በደንብ ለመክፈል ህሊናዋ አስገደዳት፡፡
የተባረከች ልጅ የእግዚአብሔር ቸርነት ያደረባት፡፡ የትንሽ አዋቂ በማለት ያመሰግኗትም ነበር ፤ ወሮ በሰልፏ፡፡
ከባለቤታቸው አንድ ወንድ ልጅና ሁለት ሴት ልጆችን ወልደዋል፡፡ያለመታደል ሆኖ ግን ሁለቱን ሴት ልጆቻቸውን በአንድ ወቅት በተከሰተው የኩፍኝ ወረርሽኝ በሞት ተነጥቀዋል፡፡
የሴትን ልጅ ጥቅም በደንብ ያወቁት በእድላዊት እንጅ በልጆቻቸውም አልነበረም፡፡ እርጅናቸው ገፋ ባይባልም በባለቤታቸውና በልጆቻቸው ሞት በመከራ ላይ መከራ አሳልፈዋል፡፡ አቅማቸው እየደከመ ፤ ጤንነታቸው ከቀን ቀን እየባሰባቸው ሄደ፡፡ የጤና ማጣታቸው ታዲያ አልጋ እንዲይዙ አስገድዷቸዋል፡፡
እድላዊት ከቤተሰቦቿ የተፈጠረችበትን ቀን ስታስታውስ አምርራ ትረግማለች፡፡ ቤተሰቦቿ እንደ ወ/ሮ በሰልፏ ቅን ፤ የሰውን ሃሳብ የሚረዱ ቢሆኑ ኖሮ ዛሬ ትምህርቷን ጨርሳ እሩቅ የመድረስ ፤ አላማዋና ተስፋዋ በተሳካላት ነበር፡፡
አንዴ ለመከራ የታደለች አድርጎ የፈጠራት እድላዊት፡፡ ከአልጋ ቁራኛ ተነስታ ውለታቸውን በጥቂቱም ቢሆን በጉልበቷ ከፍላ ለመሔድ ተነሳች፡፡ ግን አልተሳካላትም፡፡ ያስታመሟት ወሮ በሰልፏ ተረኛ የአልጋ ቁራኛ ሆኑባት፡፡
ጥላቸው እንዳትሄድ በእጃቸው በልታ ፣ ጠጥታ ያደረጉላት ውለታ ፤ መቼም የማይረሳ ሆነባት፡፡ ብትሔድ እንኳን የማይቀናትና የማይሳካላት መስሎ ታያት፡፡ ከስራቸው ሆና ለማስታመም ተገደደች፡፡
ወላጅ እናቷን እንደምጠራው እማዬ ምን ላምጣሎት ? ምን ላድርግሎት ? ምን ይሻላል ? እያለች አቅሟ የፈቀደውን ሁሉ እያደረገች አስታመቻቸው፡፡
ታዲያ ስትወጣና ስትገባ አይን አይናቸውን ስትመለከት ህመማቸው ፤ ህመሟ ይሆንባታል፡፡ ሁለት ወር ከ18 ቀን የአልጋ ቁራኛ እያለች
ያደረጉላት ሁሉ በሃሳቧ ይመጣ፡፡
አይኖቿ በእንባ ይሞላሉ፡፡ ስታለቅስ እንዳያዩዋት ወደ ውጭ ወጥታ ልውጣ ልውጣ እያለ በሃይል የሚያስቸግራትን ፤ የእንባ ጎርፍ ፊቷንና አይኖቿ እስከሚቀሉ ድረስ ታዘንበዋለች፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ የራሳቸው በሽታና ስቃይ ሳያንሳቸው በእድላዊት ማሰብና መጨነቅ አንጀታቸው አልችል አለ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
#ያሬድ
ሁሉም ተሳካለት፡፡ ከዚያው አካባቢ አበበች የምትባል ልጅ አገባ፡፡ ኑሮውን ለማሻሻል ከግብርና ስራው በተጨማሪ የንግድ ስራ ለመስራት አቀደ፡፡ ለባለቤቱ ማማከር እንዳለበት ወሰነ፡፡
አንድ ቀን ከባለቤቱ ጋር እራት እየበሉ ነው፡፡ "እንዴው ይሔ የግብርና ስራ ከእጅ ወደ አፍ ብቻ ሆነ፡፡ በትርፍ ሰዓቴ እንኳን ንግድ ብሞክር ፤ ሳይሻል አይቀርም" አላት ያሬድ ለባለቤቱ አበበች፡፡ በእጁ የተቀለለውን እንጀራ እየጎረሰ፡፡
"ሃሳብህ ጥሩ ነው፡፡ ግን ምን ዓይነት ንግድ ነው የምነግደው? አለች አበበች፡፡
ጥያቄን በጥያቄ እንዲሉ መልሶ "ቡና ይሻላል ወይስ አልባሳት?'' አላት፡፡
ሁለቱም አማራጮች ጥሩ ናቸው፡፡ ግን ከየት አምጥተህ ነው የምትነግደው ?፡፡
ያሬድ ተጨማሪ የንግድ ስራ ለመስራት እንጅ ከየት አምቶ እና ምን እንደሚነግድ እንኳን በደንብ አላሰበበትም፡፡
አልባሳት በቅርብ ባይገኝም ወደ ድሬደዋ በመሔድ ማግኘት እንደሚቻል ግን ያውቃል፡፡
"ድሬደዋ በውሎ ገባ መድረስ ይቻላል እንዴ"? አለችው፡፡
ያሬድ ድሬደዋ ሔዶባት አያውቅም፡፡ "ሰዎች ሲያወሩ ሰምቻለሁ፡፡ ውሎ ገባ አይደረስም፡፡ መኪና ከተገኘ ሁለት ቀን ቢወስድ ነው"፡፡
ያሬድ ከባለቤቱ ተስማምቶ ፤ ማምጫ ገንዘብ ለሰው አበድሮት የነበረውን ሰበሰበ፡፡ ከቤትም ትንሽ ስንዴ ሸጦ ለመነገጃ የሚሆን ገንዘብ አጠራቀመ፡፡
ታዲያ ወደ ድሬደዋ ሲሔድ ቤቱን ፣ ከብቶቹንና ባለቤቱን ብቻዋን ጥሏት እንዳይሄድ ስጋት አደረበት፡፡
ተመስገን ለቤተሰቦቹ ውሃ ሊቀዳ አህያ ላይ ጀሪካን እየጫነ ነው፡፡
"ደህና አደርህ ተመስገን" አለ፡፡ ቤቱን እና ከብቶቹን እስከሚመለስ እንዲያይለት ሊጠይቀው በጥዋት የመጣው
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደርህ ያሬድ" አለ፡፡ ጀርካን መጫኑን ተወት አድርጎ ወደ ያሬድ እየተጠጋ፡፡ የእጅ ሰላምታ ሰጥቶት ወደ ቤት ግባ አለው ተመስገን፡
"አልገባም ይሁን" ብሎ "አንተጋር ነበር የመጣሁት" አለ
"ምነው በሰላም" ?
"አይ! በሰላም ነው፡፡ አንድ ነገር ላስቸግርህ ብየ ነው የመጣሁት"፡፡
"ምን ችግር አለው የምችል ከሆነ"፡፡
"አይ! ቀላል ነው"፡፡ እኔ ወደ ድሬደዋ ለመሄድ ስለፈለግሁ ቤቴን እንድትከታተልልኝ ፈልጌ ነበር፡፡
"ምነው በሰላም ነው፡፡ ወደ ድሬደዋ የምትሄደው ?
"ለራሴ ጉዳይ ነው፡፡ ትንሽ አልባሳት ለመነገድ ስላሰብኩ ለማምጣት ነው የምሔደው ፡፡
"አይ! ደህና ነው፡፡ እከታተልልሃለሁ ግን ለምን አብረን ብቻህን እዛ ድረስ ከምትሄድ ለኔም ታስተዋውቀኝ ነበር አለ ተመስገን፡፡
"ሐሳብህ ጥሩ ነው፡፡ ግን እኔም ገና አዲስ ስለሆንኩ መጀመሪያ ልየውና የሚያዋጣ ከሆነ አብረን እንሔዳልን እስከዛ ገንዘብ አጠራቅም፡፡ ብሎት ተሰነባብተው ተለያያዩ።
እድላዊት
ሲሻለኝ ውለታቸውን በጉልበቴም ቢሆን አግዠ እከፍላቸዋለሁ ብላ አሰበች፡፡ ግን ያሰበችው ቶሎ አልሆነም፡፡
ከህመሟ ሳይሻላት እየባሰባትና እየጠናባት ሄደ፡፡ ሁለት ወር ከ18 ቀን የአልጋ ቁራኛ ሆና አሳለፈች፡፡ ምነው እዛው ጫካ ሞቼ በቀረሁ ኖሮ፡፡ እንደዚህ የአልጋ ቁራኛ ሆኘ ሰው ከማስቸገር ምን አለ ፈጣሪየ መከራና ስቃየን ከምታበዛብኝ ብትገላግለኝ?፡፡ ፈጣሪዋን እየተማፀነች እና እያማረረች ውላ በተራው ጨለማውን ተገን አድርጎ ሌሊቱ ይተካል፡፡
እድላዊት ሌሊትም ሆነ ቀን የምትተኛበት የእንቅልፍ ሰዓት በሃሳብና በጭንቀት ሳይታወቃት ቀን መሽቶ ይነጋል፡፡ በብርድልብስ ውስጥ ተሸፍና የምታለቅሰው እንባ ቢጠራቀም ዘመዶቿንና ቤተሰቦቿን ይቀብርላት ነበር፡፡
አንዳንዴ ሲጨንቃት የተሻላት ይመስላታል፡፡ ለመሄድ አስባ ትነሳለች፡፡ አሁን ልሂድ በቃ ተሸሎኛል፡፡ እናንተንም
አስቸገርኳችሁ፡፡ ተነስታ ለመሄድ ስታስብ አቅም ያንሳታል ፤ እራሷን ያዞራታል፡፡ ተመልሳ መቀመጥ አትችልም፡፡
የእድላዊት ቶሎ አለመዳንና የአልጋ ቁራኛ መሆኗ አሳስቧቸዋል ፤ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡ ምነው ፈጣሪዬ ይህችን አንድ ፍሬ ህፃን የአልጋ ቁራኛ ከምታደርግብኝ ለኔ ብሰጠኝ፡፡ እያሉ ፈጣሪያቸውን እየተማፀኑ ውለው ማደራቸው ሳያንሳቸው እድላዊት ደግሞ በሽታዋን ሳታስብ አስቸገርኳችሁ ስትላቸው የባሰ ያስጨንቃቸዋል፡፡
እባክሽን ልጄ ተለመኝኝ ; እባክሽ ስለፈጠረሽ አምላክ ; በደንብ ሲሻልሽ ትሔጃለሽ፡፡ ልጄ እባክሽ ለኔ ምንም አታስቢ፡፡ አንቺ ብቻ ዳኝልኝ፡፡ ለሁሉም ይደረሳል፡፡ ብለው ምንም እንዳታስብና እንዳትጨነቅ ይማፀኗታል ፡፡
እድላዊት በትንሹም ቢሆን እየተሸላት መጣ፡፡ መጀመሪያ ውለታቸውን ከፍየ እሄዳለሁ ብላ ያሰበችውን አረሳችም፡፡
ገና በደንብ ሳይሻላት ለመርዳት ተቻኮለች፡፡ ቡና ሲያፈሉ እኔ አፈላለሁ እያለች ወ/ሮ በሰልፏን ታስቸግራቸውም ጀመር፡፡ ቆይ በደንብ አልተሻለሽም፡፡ በደንብ ሲሻልሽ ታፈያለሽ፡፡ ቢከለክሏትም እሽ አትላቸውም ነበር፡፡
እድላዊት በቤቱ ውስጥ ያለውን ስራ በመስራት መርዳትና ማገዝ ጀመረች፡፡ ትንሽ ሲሻለኝ እሄዳለሁ ያለችውን ሰረዘች፡፡ ውለታቸውን በደንብ ለመክፈል ህሊናዋ አስገደዳት፡፡
የተባረከች ልጅ የእግዚአብሔር ቸርነት ያደረባት፡፡ የትንሽ አዋቂ በማለት ያመሰግኗትም ነበር ፤ ወሮ በሰልፏ፡፡
ከባለቤታቸው አንድ ወንድ ልጅና ሁለት ሴት ልጆችን ወልደዋል፡፡ያለመታደል ሆኖ ግን ሁለቱን ሴት ልጆቻቸውን በአንድ ወቅት በተከሰተው የኩፍኝ ወረርሽኝ በሞት ተነጥቀዋል፡፡
የሴትን ልጅ ጥቅም በደንብ ያወቁት በእድላዊት እንጅ በልጆቻቸውም አልነበረም፡፡ እርጅናቸው ገፋ ባይባልም በባለቤታቸውና በልጆቻቸው ሞት በመከራ ላይ መከራ አሳልፈዋል፡፡ አቅማቸው እየደከመ ፤ ጤንነታቸው ከቀን ቀን እየባሰባቸው ሄደ፡፡ የጤና ማጣታቸው ታዲያ አልጋ እንዲይዙ አስገድዷቸዋል፡፡
እድላዊት ከቤተሰቦቿ የተፈጠረችበትን ቀን ስታስታውስ አምርራ ትረግማለች፡፡ ቤተሰቦቿ እንደ ወ/ሮ በሰልፏ ቅን ፤ የሰውን ሃሳብ የሚረዱ ቢሆኑ ኖሮ ዛሬ ትምህርቷን ጨርሳ እሩቅ የመድረስ ፤ አላማዋና ተስፋዋ በተሳካላት ነበር፡፡
አንዴ ለመከራ የታደለች አድርጎ የፈጠራት እድላዊት፡፡ ከአልጋ ቁራኛ ተነስታ ውለታቸውን በጥቂቱም ቢሆን በጉልበቷ ከፍላ ለመሔድ ተነሳች፡፡ ግን አልተሳካላትም፡፡ ያስታመሟት ወሮ በሰልፏ ተረኛ የአልጋ ቁራኛ ሆኑባት፡፡
ጥላቸው እንዳትሄድ በእጃቸው በልታ ፣ ጠጥታ ያደረጉላት ውለታ ፤ መቼም የማይረሳ ሆነባት፡፡ ብትሔድ እንኳን የማይቀናትና የማይሳካላት መስሎ ታያት፡፡ ከስራቸው ሆና ለማስታመም ተገደደች፡፡
ወላጅ እናቷን እንደምጠራው እማዬ ምን ላምጣሎት ? ምን ላድርግሎት ? ምን ይሻላል ? እያለች አቅሟ የፈቀደውን ሁሉ እያደረገች አስታመቻቸው፡፡
ታዲያ ስትወጣና ስትገባ አይን አይናቸውን ስትመለከት ህመማቸው ፤ ህመሟ ይሆንባታል፡፡ ሁለት ወር ከ18 ቀን የአልጋ ቁራኛ እያለች
ያደረጉላት ሁሉ በሃሳቧ ይመጣ፡፡
አይኖቿ በእንባ ይሞላሉ፡፡ ስታለቅስ እንዳያዩዋት ወደ ውጭ ወጥታ ልውጣ ልውጣ እያለ በሃይል የሚያስቸግራትን ፤ የእንባ ጎርፍ ፊቷንና አይኖቿ እስከሚቀሉ ድረስ ታዘንበዋለች፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ የራሳቸው በሽታና ስቃይ ሳያንሳቸው በእድላዊት ማሰብና መጨነቅ አንጀታቸው አልችል አለ፡፡
👍74❤7😁2🔥1
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ደላላው
ያዋጣኝ ይሆን ? ወይስ ያከስረኝ ? ይሆን ? ተጠራጠረ ፤ የአልባሳት ንግዱ ግን ውጤታማ አድርጎታል፡፡ እየተመላለሰ መነገዱን ቀጥሏል፡፡
የባልጪ መኪና ቶሎ ያሬድ ወደ ድሬድዋ ሊሄድ ረፍዶበት ተቻኩሏል፡፡ መኪናው ግን ሳይሞላ መውጣት አልቻም፡፡ አዳማ አርፍዶ ደረሰ፡፡ ወደ ድሬደዋ በጥዋት የሚወጣው መኪና አምልጦታል፡፡
ተናደደ ፣ ተበሳጨ፡፡ ምነው ዛሬ ባልመጣሁ ኖሯል፡፡ እንደሚረፍድብኝ እያወቅሁ፡፡ ከባልጪ መመለስ ሲኖርብኝ፡፡ ወደ አዳማ መንከርፈፍ ምን ይሉታል? ራሱን እየወቀሰ ከአሰላ መውጫ መነሃሪያ ወጥቶ በስተቀኝ በኩል ወደ ምትገኝ አንድ ሻይ ቤት አመራ፡፡
አንድን ጠቆር ያለ ወጣት ነው፡፡ ቁመተ አጭር ዳክየ፡፡ የተከረከመ ጉቶ ይመስላል፡፡ ፀጉሩ በአቧራ የተለወሰ ፣ የተንጨበረረ ፣ ቁጥርጥር ፀጉራም፡፡
ከመነሃሪያ ውጭ ቆሞ አላፊ አግዳሚውን ድሬ ፣ ድሬ አንድ ሰው የቀረው እያለ ይለፈልፋል፡፡
ቀኝ እግሩን አንስቶ ግራ እግሩን አልደገመም፡፡ ድሬ አንድ ሰው የሚል ድምፅ ሰማ፡፡ ወደ ፊት መራመዱን ትቶ ወደ ኋላ ተመለሰ፡፡ ብስጭትና ንዴቱ ለቀቀው፡፡ እየተጣደፈ ድሬ ፣ ድሬ አንድ ሰው እያለ ወደ ሚለፈልፈው ደላላ ተጠጋ፡፡ እኔ አለሁ ድሬ አለ፡፡
"ኧረ! ድሬ ነህ ና ተከተለኝ፡፡ አሁን ልንወጣ ነው"፡፡ ብሎት ወደ መኪናው ወሰደው፡፡ ሂሳብ ክፈልና እዚህኛው መኪና ግባ አለው፡፡
ለመሳፈሪያ ብሎ ለይቶ ካስቀመጠው የሱሪ ኪሱ አውጥቶ ከፈለ፡፡ ደረሰኝ ግን አልተቀበለም፡፡ ደላላው ገንዘቡን ተቀብሎት ታጠፈ፡፡
ያሬድ ግባ ወደ ተባለበት አውቶቢስ ገባ፡፡ እውነትም አንድ ሰው ብቻ ነበር የቀረው፡፡ አንድ ተሳፋሪ ቀርቷት የነበረች ወንበር ላይ ተቀመጠ፡፡
እረዳቱ የአውቶቢሱን በር ዘጋ፡፡ ሹፌሩ መኪናውን አስነሳ፡፡ ጉዞው ከአዳማ ወደ ድሬደዋ ተጀመረ፡፡
"ምዕመናን ሂሳብ ወጣ! ወጣ! አድርጉ አለ እረዳቱ፡፡ እየተቀበለ ያሬድ ጋር ደረሰ፡፡
"ለእኔ ደረሰኝ ብቻ ስጠኝ ገንዘቡን ከፍያለሁ አለ ያሬድ፡፡
"ለማነው የከፈልከው አለ እረዳቱ?፡፡
"ሊያሳፍረኝ ይዞኝ ለመጣው ሰውየ ፡፡
"አባት የከፈሉት ሂሳብ ለእኔ አልደረሰኝም፡፡ አሁን ለእኔ ይክፈሉኝ አለ፡፡ ትህትና በተሞላበት ንግግር፡፡
"አልከፍልም" አለ ያሬድ፡፡
"እባክዎት ይክፈሉኝ" አባት ቢልም ፤ ምንም ቢል ያሬድ ሊሰማ አልቻለም፡፡ ክፈል ፣ ጭቅጭቅና ንትርኩ ተባባሰ፡፡ ሹፌር መኪናውን መንዳቱን አቆመ፡፡ በረዳቱና በያሬድ መሃል ጣልቃ ገባ
"ለምንድ ነው የማከፍለው? በነፃ ተሳፍረህ የምትሄደው የአባትህ ፈረስ አደረግከው አለ ሹፌሩ፡፡ በፊቱ ላይ የደም ስሮቹ ተወጣጠሩ፡፡
"የአባቴ ፈረስ ባይሆንም ገንዘብ ከፍየ ነው የተሳፈርኩት፡፡ ያጭበረበራችሁኝ እናንተ ናችሁ፡፡ በማስፈራራት ደግማችሁ ልታስከፍሉኝ ነው? አልከፍልም፡፡ ወደ ህግ እንሄዳለን እንጅ አለ ያሬድ፡፡
ከመኪናው ውስጥ ጎትተው አወጡት፡፡ ሊደበድቡት ተጋበዙ፡፡ ተሳፋሪዎቹ ገላገሏቸው፡፡ ክርክሩና ንትርኩ አላቋረጠም፡፡
አቶ ላንቻ ባልቻ የሚባሉ ከያሬድ ጋር አንድ ወንበር ላይ አብረው ተቀምጠዋል፡፡ ጭቅጭቁ አበሳጭቷቸዋል፡፡ ቶሎ ለመድረስ ያሰቡበት ቦታ እየረፈደባቸው ነው፡፡
"ለረዳቱ በቃ! ተወው እኔ እከፍለዋለሁ፡፡ ንትርኩን ተውና ቶሎ ቶሎ ንዳ፡፡ እውነት ይሄ ሰውዬ ሳይከፍልም የተከራከረ አይመስለኝም፡፡ የአዳማ ሞጭላፋ ጩልሌዎች ጨልፈውት ይሆናል፡፡ እንኳን የክፍለ ሃገር ሰው አግኝተው አይደለም ወፍ ከሰማይ ያወርዳሉ፡፡ ይዞት የመጣው ደላላ የሻይ ሲጠይቀው የመሳፈሪያውን ሂሳብ ተቀብሎት ላፍ ብሎ ይሆናል፡፡ ብለው የሚያጨቃጭቀውን የያሬድን ሂሳብ ከደረት ሸሚዝ ኪሳቸው አውጥተው ከፈሉለት፡፡
"አጭበርብረውኝ ነው፡፡ እንጅ እኔ እኮ ገንዘቡን ከፍያቸዋለሁ አባት አለ፡፡ እንደ መፀፀት ብሎ፡፡
"ያጭበረበሩህ ባለ መኪናዎቹ አይደሉም፡፡ ዱርዬዎች ናቸው፡፡ አንተም መኪና ውስጥ ሳትገባ መክፈል አልነበረብህም፡፡ ወይም ስትከፍል ደረሰኝ መቀበል ነበረብህ::
"እኔ መቼ አወኩ፡፡ እንደዚህ መሆኑን የት አውቄ፡፡ የእነሱ አጋዥ መስሎኝ ነው፡፡ የከፈልኩት፡፡ መቼ ሰባራ ሳንቲም አቀምሰው ነበር፡፡ ብሎ ስህተቱ የራሱ መሆኑን አውቆ የከፈሉለትን ገንዘብ ሊከፍል ከኪሱ አወጣ፡፡
አባት አመሰግናለሁ ገንዘቡን እንኩ አለ፡፡ በፊቱ ላይ የይቅርታ ምልክት እያሳየ፡፡
ገንዘቡን ለመቀበል አልፈለጉም፡፡ ተወው ችግር የለውም፡፡ አንተም ተወስዶብህ ነው፡፡ እንጅ አውቀህ አይደለም፡፡ አሁን ያወጣኸውን ገንዘብ መልሰህ ወደ ኪስህ አስገባ እኔ አልቀበልም አሉ አቶ ላንቻ፡፡
አቶ ላንቻ ከድሬደዋ አዳማ እየተመላለሱ የሚነግዱ የታወቁ ቱጃር አልባሳ ነጋዴ ናቸው፡፡ ጨዋታቸው እየሞቀ ሄደ፡፡ አቶ ላንቻ ከተደገፉበት ወንበር ቀና አሉ፡፡
"ስምህን ማን አልከኝ"? አሉት፡፡ መጀመሪያ ነግሯቸው በጭዋታ የተነሳ ዘንግተውት ይሁን ተመስሎባቸው ደግመው መጠየቃቸው፡፡
"ያሬድ እባላለሁ አለ፡፡ ፊቱን ወደ አቶ ላንቻ መለስ አድርጎ፡፡
"አሁን ወዴት ነው የምትሄደው"? ፡፡
"ወደ ድሬ የምሄደው"፡፡
"እዛው ነዋሪ ነህ ወይስ ለስራ ነው የምትሄደው?፡፡
"አይ! ለስራ ነው፡፡ ነገ እመለሳለሁ፡፡ እቤት ከመቀመጥ ብዬ ትንሽ ሳልባጅ ቢጤ ጀምሬ ነበር፡፡ ሞልቶ ለማይሞላ ነገር ስንት ገዛኸው ዘጠኝ ፤ ስንት ሸጥከው ዘጠኝ ፤ ትርፉስ ምንድነው? ዘጥ ዘጥ እንደሚባለው የበሰለውን ከማጥፋት ውጭ ድካም ነው፡፡ ውጤት የለውም አላቸው፡፡ ንግግሩ የሚያስቅ ስለነበር ፈገግ አደረጋቸው፡፡
አቶ ላንቻ አለመተዋወቅ እንጅ አልባሳት ከሆነ የምትነግደው እኔ አዳማ ድረስ አመጣልህ ነበር አሉ፡፡
"አልባሳት ይነግዳሉ እንዴ? አለ ያሬድ፡፡
"አዎ፤ ነጋዴ ነኝ፡፡ አሁንም አራግፌ እየተመለስኩ ነው፡፡
"ጥሩ አጋጣሚ ነው፡፡ እንዴው የሰው መተዋወቂያው መንገዱ ብዙ ነው አለ ያሬድ፡፡ ያገናኛቸው አጋጣሚ እያስገረመው፡፡
"ድሬ ደንበኛ አለህ የምትረከብበት"? ፡፡
"ደንበኛ እንኳን የለኝም፡፡ የጀመርኩት ቅርብ ጊዜ ስለሆነ ደንበኛ አላበጀሁም፡፡ ከአሸዋ ሜዳ ነው የምገዛው ፡፡
የዛሬ መገናኘታችን ጥሩ አጋጣሚ ነው፡፡ አሁን እየደረስን ስለሆነ መነሃርያ ሳንገባ ወርደን አረፍ ብለን እንነጋገራለን" አሉ ፤ አቶ ላንቻ፡፡
ከመኪና ወርደው ወደ አንድ ሪስቶራንት አመሩ፡፡ አረፍ ብለው የሚጠጣ ለስላሳ አዘዙ፡፡ በመኪና ላይ የጀመሩትን ጭውውታቸውን እንደቀጠሉ ናቸው፡፡
"አዳማ ውስጥ የራስዎ ቡቲክ አሎት እንዴ? አለ ያሬድ፡፡
"የራሴ እንኳን ቡቲክ የለኝም፡፡ አዳማ መነሃሪያ አካባቢ ቢያድግልኝ የሚባል የጅምላ አከፋፋይ ሱቅ አጠገብ የተከራየሁት ቡቲክ አለኝ፡፡ እዛ ነው የምሸጠው፡፡ ቦታውን ነገ አብረን ስንሄድ አሳይሃለሁ፡፡ አሁን እንሂድና እዚህ ድሬ ውስጥ ያለኝን ቡቲክ ላሳይህ፡፡ የሚያስፈልግህንም ገዝተህ እኔ በምጭንበት መኪና ጭነህ ነገ አብረን አንሄዳለን፡፡
ያሬድ ያገናኘውን አጋጣሚ እየመረቀ እንዴው ምን ዓይነት ደግ ሰው ነው፡፡ ያጋጠመኝ የእግዚአብሔር ሰው ናቸው፡፡ እያለ "አይደህና ነው፡፡ ለእኔም እዚህ ድረስ ከምለፋ ጥሩና መልካም ነው፡፡ እንዴው ውለታዎን ለመክፈል ያብቃኝ" አለ፡፡ ቀለስለስ እያለ፡፡
"አይ! ምንም ማለት አይደለም፡፡ የራሴም ስራ ነው፡፡ አሁን ከአንተ የምጠብቀው ታማኝ ሆኖ መገኘት ብቻ ነው"፡፡ ብለውት ሊያሳድሩት ወደ ቤታቸው ወሰዱት፡፡
በነጋታው በጥዋት ተነሱ፡፡ በተነጋገሩት መሰረት የሚያስፈልገውን ልብሶች ገዝቶ አብረው ወደ አዳማ ተጓዙ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ደላላው
ያዋጣኝ ይሆን ? ወይስ ያከስረኝ ? ይሆን ? ተጠራጠረ ፤ የአልባሳት ንግዱ ግን ውጤታማ አድርጎታል፡፡ እየተመላለሰ መነገዱን ቀጥሏል፡፡
የባልጪ መኪና ቶሎ ያሬድ ወደ ድሬድዋ ሊሄድ ረፍዶበት ተቻኩሏል፡፡ መኪናው ግን ሳይሞላ መውጣት አልቻም፡፡ አዳማ አርፍዶ ደረሰ፡፡ ወደ ድሬደዋ በጥዋት የሚወጣው መኪና አምልጦታል፡፡
ተናደደ ፣ ተበሳጨ፡፡ ምነው ዛሬ ባልመጣሁ ኖሯል፡፡ እንደሚረፍድብኝ እያወቅሁ፡፡ ከባልጪ መመለስ ሲኖርብኝ፡፡ ወደ አዳማ መንከርፈፍ ምን ይሉታል? ራሱን እየወቀሰ ከአሰላ መውጫ መነሃሪያ ወጥቶ በስተቀኝ በኩል ወደ ምትገኝ አንድ ሻይ ቤት አመራ፡፡
አንድን ጠቆር ያለ ወጣት ነው፡፡ ቁመተ አጭር ዳክየ፡፡ የተከረከመ ጉቶ ይመስላል፡፡ ፀጉሩ በአቧራ የተለወሰ ፣ የተንጨበረረ ፣ ቁጥርጥር ፀጉራም፡፡
ከመነሃሪያ ውጭ ቆሞ አላፊ አግዳሚውን ድሬ ፣ ድሬ አንድ ሰው የቀረው እያለ ይለፈልፋል፡፡
ቀኝ እግሩን አንስቶ ግራ እግሩን አልደገመም፡፡ ድሬ አንድ ሰው የሚል ድምፅ ሰማ፡፡ ወደ ፊት መራመዱን ትቶ ወደ ኋላ ተመለሰ፡፡ ብስጭትና ንዴቱ ለቀቀው፡፡ እየተጣደፈ ድሬ ፣ ድሬ አንድ ሰው እያለ ወደ ሚለፈልፈው ደላላ ተጠጋ፡፡ እኔ አለሁ ድሬ አለ፡፡
"ኧረ! ድሬ ነህ ና ተከተለኝ፡፡ አሁን ልንወጣ ነው"፡፡ ብሎት ወደ መኪናው ወሰደው፡፡ ሂሳብ ክፈልና እዚህኛው መኪና ግባ አለው፡፡
ለመሳፈሪያ ብሎ ለይቶ ካስቀመጠው የሱሪ ኪሱ አውጥቶ ከፈለ፡፡ ደረሰኝ ግን አልተቀበለም፡፡ ደላላው ገንዘቡን ተቀብሎት ታጠፈ፡፡
ያሬድ ግባ ወደ ተባለበት አውቶቢስ ገባ፡፡ እውነትም አንድ ሰው ብቻ ነበር የቀረው፡፡ አንድ ተሳፋሪ ቀርቷት የነበረች ወንበር ላይ ተቀመጠ፡፡
እረዳቱ የአውቶቢሱን በር ዘጋ፡፡ ሹፌሩ መኪናውን አስነሳ፡፡ ጉዞው ከአዳማ ወደ ድሬደዋ ተጀመረ፡፡
"ምዕመናን ሂሳብ ወጣ! ወጣ! አድርጉ አለ እረዳቱ፡፡ እየተቀበለ ያሬድ ጋር ደረሰ፡፡
"ለእኔ ደረሰኝ ብቻ ስጠኝ ገንዘቡን ከፍያለሁ አለ ያሬድ፡፡
"ለማነው የከፈልከው አለ እረዳቱ?፡፡
"ሊያሳፍረኝ ይዞኝ ለመጣው ሰውየ ፡፡
"አባት የከፈሉት ሂሳብ ለእኔ አልደረሰኝም፡፡ አሁን ለእኔ ይክፈሉኝ አለ፡፡ ትህትና በተሞላበት ንግግር፡፡
"አልከፍልም" አለ ያሬድ፡፡
"እባክዎት ይክፈሉኝ" አባት ቢልም ፤ ምንም ቢል ያሬድ ሊሰማ አልቻለም፡፡ ክፈል ፣ ጭቅጭቅና ንትርኩ ተባባሰ፡፡ ሹፌር መኪናውን መንዳቱን አቆመ፡፡ በረዳቱና በያሬድ መሃል ጣልቃ ገባ
"ለምንድ ነው የማከፍለው? በነፃ ተሳፍረህ የምትሄደው የአባትህ ፈረስ አደረግከው አለ ሹፌሩ፡፡ በፊቱ ላይ የደም ስሮቹ ተወጣጠሩ፡፡
"የአባቴ ፈረስ ባይሆንም ገንዘብ ከፍየ ነው የተሳፈርኩት፡፡ ያጭበረበራችሁኝ እናንተ ናችሁ፡፡ በማስፈራራት ደግማችሁ ልታስከፍሉኝ ነው? አልከፍልም፡፡ ወደ ህግ እንሄዳለን እንጅ አለ ያሬድ፡፡
ከመኪናው ውስጥ ጎትተው አወጡት፡፡ ሊደበድቡት ተጋበዙ፡፡ ተሳፋሪዎቹ ገላገሏቸው፡፡ ክርክሩና ንትርኩ አላቋረጠም፡፡
አቶ ላንቻ ባልቻ የሚባሉ ከያሬድ ጋር አንድ ወንበር ላይ አብረው ተቀምጠዋል፡፡ ጭቅጭቁ አበሳጭቷቸዋል፡፡ ቶሎ ለመድረስ ያሰቡበት ቦታ እየረፈደባቸው ነው፡፡
"ለረዳቱ በቃ! ተወው እኔ እከፍለዋለሁ፡፡ ንትርኩን ተውና ቶሎ ቶሎ ንዳ፡፡ እውነት ይሄ ሰውዬ ሳይከፍልም የተከራከረ አይመስለኝም፡፡ የአዳማ ሞጭላፋ ጩልሌዎች ጨልፈውት ይሆናል፡፡ እንኳን የክፍለ ሃገር ሰው አግኝተው አይደለም ወፍ ከሰማይ ያወርዳሉ፡፡ ይዞት የመጣው ደላላ የሻይ ሲጠይቀው የመሳፈሪያውን ሂሳብ ተቀብሎት ላፍ ብሎ ይሆናል፡፡ ብለው የሚያጨቃጭቀውን የያሬድን ሂሳብ ከደረት ሸሚዝ ኪሳቸው አውጥተው ከፈሉለት፡፡
"አጭበርብረውኝ ነው፡፡ እንጅ እኔ እኮ ገንዘቡን ከፍያቸዋለሁ አባት አለ፡፡ እንደ መፀፀት ብሎ፡፡
"ያጭበረበሩህ ባለ መኪናዎቹ አይደሉም፡፡ ዱርዬዎች ናቸው፡፡ አንተም መኪና ውስጥ ሳትገባ መክፈል አልነበረብህም፡፡ ወይም ስትከፍል ደረሰኝ መቀበል ነበረብህ::
"እኔ መቼ አወኩ፡፡ እንደዚህ መሆኑን የት አውቄ፡፡ የእነሱ አጋዥ መስሎኝ ነው፡፡ የከፈልኩት፡፡ መቼ ሰባራ ሳንቲም አቀምሰው ነበር፡፡ ብሎ ስህተቱ የራሱ መሆኑን አውቆ የከፈሉለትን ገንዘብ ሊከፍል ከኪሱ አወጣ፡፡
አባት አመሰግናለሁ ገንዘቡን እንኩ አለ፡፡ በፊቱ ላይ የይቅርታ ምልክት እያሳየ፡፡
ገንዘቡን ለመቀበል አልፈለጉም፡፡ ተወው ችግር የለውም፡፡ አንተም ተወስዶብህ ነው፡፡ እንጅ አውቀህ አይደለም፡፡ አሁን ያወጣኸውን ገንዘብ መልሰህ ወደ ኪስህ አስገባ እኔ አልቀበልም አሉ አቶ ላንቻ፡፡
አቶ ላንቻ ከድሬደዋ አዳማ እየተመላለሱ የሚነግዱ የታወቁ ቱጃር አልባሳ ነጋዴ ናቸው፡፡ ጨዋታቸው እየሞቀ ሄደ፡፡ አቶ ላንቻ ከተደገፉበት ወንበር ቀና አሉ፡፡
"ስምህን ማን አልከኝ"? አሉት፡፡ መጀመሪያ ነግሯቸው በጭዋታ የተነሳ ዘንግተውት ይሁን ተመስሎባቸው ደግመው መጠየቃቸው፡፡
"ያሬድ እባላለሁ አለ፡፡ ፊቱን ወደ አቶ ላንቻ መለስ አድርጎ፡፡
"አሁን ወዴት ነው የምትሄደው"? ፡፡
"ወደ ድሬ የምሄደው"፡፡
"እዛው ነዋሪ ነህ ወይስ ለስራ ነው የምትሄደው?፡፡
"አይ! ለስራ ነው፡፡ ነገ እመለሳለሁ፡፡ እቤት ከመቀመጥ ብዬ ትንሽ ሳልባጅ ቢጤ ጀምሬ ነበር፡፡ ሞልቶ ለማይሞላ ነገር ስንት ገዛኸው ዘጠኝ ፤ ስንት ሸጥከው ዘጠኝ ፤ ትርፉስ ምንድነው? ዘጥ ዘጥ እንደሚባለው የበሰለውን ከማጥፋት ውጭ ድካም ነው፡፡ ውጤት የለውም አላቸው፡፡ ንግግሩ የሚያስቅ ስለነበር ፈገግ አደረጋቸው፡፡
አቶ ላንቻ አለመተዋወቅ እንጅ አልባሳት ከሆነ የምትነግደው እኔ አዳማ ድረስ አመጣልህ ነበር አሉ፡፡
"አልባሳት ይነግዳሉ እንዴ? አለ ያሬድ፡፡
"አዎ፤ ነጋዴ ነኝ፡፡ አሁንም አራግፌ እየተመለስኩ ነው፡፡
"ጥሩ አጋጣሚ ነው፡፡ እንዴው የሰው መተዋወቂያው መንገዱ ብዙ ነው አለ ያሬድ፡፡ ያገናኛቸው አጋጣሚ እያስገረመው፡፡
"ድሬ ደንበኛ አለህ የምትረከብበት"? ፡፡
"ደንበኛ እንኳን የለኝም፡፡ የጀመርኩት ቅርብ ጊዜ ስለሆነ ደንበኛ አላበጀሁም፡፡ ከአሸዋ ሜዳ ነው የምገዛው ፡፡
የዛሬ መገናኘታችን ጥሩ አጋጣሚ ነው፡፡ አሁን እየደረስን ስለሆነ መነሃርያ ሳንገባ ወርደን አረፍ ብለን እንነጋገራለን" አሉ ፤ አቶ ላንቻ፡፡
ከመኪና ወርደው ወደ አንድ ሪስቶራንት አመሩ፡፡ አረፍ ብለው የሚጠጣ ለስላሳ አዘዙ፡፡ በመኪና ላይ የጀመሩትን ጭውውታቸውን እንደቀጠሉ ናቸው፡፡
"አዳማ ውስጥ የራስዎ ቡቲክ አሎት እንዴ? አለ ያሬድ፡፡
"የራሴ እንኳን ቡቲክ የለኝም፡፡ አዳማ መነሃሪያ አካባቢ ቢያድግልኝ የሚባል የጅምላ አከፋፋይ ሱቅ አጠገብ የተከራየሁት ቡቲክ አለኝ፡፡ እዛ ነው የምሸጠው፡፡ ቦታውን ነገ አብረን ስንሄድ አሳይሃለሁ፡፡ አሁን እንሂድና እዚህ ድሬ ውስጥ ያለኝን ቡቲክ ላሳይህ፡፡ የሚያስፈልግህንም ገዝተህ እኔ በምጭንበት መኪና ጭነህ ነገ አብረን አንሄዳለን፡፡
ያሬድ ያገናኘውን አጋጣሚ እየመረቀ እንዴው ምን ዓይነት ደግ ሰው ነው፡፡ ያጋጠመኝ የእግዚአብሔር ሰው ናቸው፡፡ እያለ "አይደህና ነው፡፡ ለእኔም እዚህ ድረስ ከምለፋ ጥሩና መልካም ነው፡፡ እንዴው ውለታዎን ለመክፈል ያብቃኝ" አለ፡፡ ቀለስለስ እያለ፡፡
"አይ! ምንም ማለት አይደለም፡፡ የራሴም ስራ ነው፡፡ አሁን ከአንተ የምጠብቀው ታማኝ ሆኖ መገኘት ብቻ ነው"፡፡ ብለውት ሊያሳድሩት ወደ ቤታቸው ወሰዱት፡፡
በነጋታው በጥዋት ተነሱ፡፡ በተነጋገሩት መሰረት የሚያስፈልገውን ልብሶች ገዝቶ አብረው ወደ አዳማ ተጓዙ፡፡
👍64❤12😁1
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እድላዊት
"የባሰ አለና አገርህን አትልቅ" እንደሚባለው እድላዊት ከወ/ ሮ በሰልፏ ሞት ጋር የተቃጠረች ይመስላል፡፡
ሳይሞቱ ቀድሜ ልውጣ ማለቷ በአካል ባትነሳም በመንፈስ ተነስታ ጉዞዋን ማሰቧ ፤ አፈር ሳታለብሽኝ ፤ ጥለሽኝ ልትሄጅ ነው? ያሏት፡፡ ወ/ሮ በሰልፏ ፤ ከህሊና የማይወጣ ጥያቄ አሳደረባት፡፡
እድላዊት ግን አፈር ሳታለብሳቸው አልሄደችም ነበር፡፡ አንዴ ያደላትን የስቃይና የመከራ ፅዋ ተቀብላ የወ/ሮ በሰልፏን ተስካር አወጣች፡፡ ሁሉን ነገር ምላድ ምላድ አሰያዘች፡፡ ልብሶቿን አጣጥባ ተነሳች፡፡
"አሁን ባዶሽን አትሄጅም"፡፡ ስንቅ አሰናድተሽ ነገ እሸኝሻለሁ ብሎ አስቀራት፡፡ እሸ ብላ ቀረች፡፡
ስንቅ ለማሰናዳት አልፈለገችም፡፡ ግን ደግሞ ፀበል አለመሔዷን እንዲነቃባት አትፈልግም፡፡ ትንሽ ዳቦ ቆሎ መሳይ አዘጋጀች፡፡ በነጋታው ጠዋት ከአቶ አርምዴ ጋር ተነሳች፡፡
አንዳንዴ እየተነጋገሩ ፤ አንዳንዴ የመለያየታቸው ነገር እያሳሰባቸው ፤ ለየብቻቸው ፣ በየራሳቸው ሃሳብ እየነጎዱ ሳይታወቃቸው ሸንኮራ ዮሐንስ ደረሱ፡፡
የሸንኮራ ዮሃንስ ፀበል ከመዲናችን አዲስ አበባ በ144 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ሚያዝያ 15/1654 ዓ/ም ገደማ ፀበሉ ለአባ ካሳ እንደተገለፀላቸው ይነገራል፡፡
ይህ ፀበል አይነ ስውር የሚያበራ ፤ ለምፅን የሚያነፃ ፤ ኤች አይቪን የሚፈውስ ፤ የአጥንት ካንሰርን ነቅሎ የሚጥል ፤ በአጠቃላይ ሰው ሰራሽ ይሁን ተፈጥሯዊ በሽታዎችን የሚፈውስ ለመሆኑ ብዙዎች ድነዋል፡፡ ተፈውሰዋል ፣ ምስክርነታቸውንም ተናግረዋል ፡፡
"የት አካባቢ ይሻልሻል"? አላት፡፡ ቤት ሊያሲዛት ፈልጎ ፤ አቶ አርምዴ፡፡
እድላዊት ሸንኮራን አልፋ ለመሄድ እንጅ ቤት ለመያዝ አልፈለገችም፡፡
"አሁን ቤት አልይዝም ወደ ፀበሉ ልሂድና ስመለስ እይዛለሁ፡፡አይታወቅም ወይም የማቀው ሰው ላገኝ እችላለሁ፡፡ ለእኔ ምንም አታስብ ፤ በቃ አንተም ተመለስ፡፡ ስራህን ትተህ ነው የመጣኸው፡፡ ላደርክልኝ ውለታና እገዛ እግዚአብሔር ሁሉንም እሱ ይክፈልልኝ አመሰግናለሁ" አለች፡፡ የሃዘን ስሜት በውስጧ እየተሰማት፡፡
አይ! እድል እኔ ምን አላደረግሁልሽም፡፡ ትንሽ ስንዴ ነገር ሸጥ እንኳን አድርጌ ፤ እንዳላዘጋጅልሽ ለመሄድ ቸኮልሽ፡፡
ለስምንት ዓመት አብራው የኖረችው የሟች እህቶቹ ምትክ እድላዊት ልትለየው በመወሰኗ ፤ የወንድ አንጀቱ እንደወላድ ተላወሰ፡፡ በአይኖቹ እንባው ግጥም አለበት፡፡
እድላዊት ከሞት አፋፍ ላይ ያተረፋትን አርምዴን መለየት አቃታት፡፡ ሆድ ባሳት፤ አለቀሰች፡፡ አርምዴ ያወራውን የሰማች አትመስልም፡፡
በፊቱ ላይ የወረደውን እንባ ጠራረገ፡፡ እድል ይበቃል አስካሁን ስታለቅሽ የኖርሽው፡፡ በትንሹም ፣ በትልቁም ማልቀስ ጥሩ አይደለም፡፡ የባሰ ሊያስከትል ይችላል፡፡ ለማፅናናት ሞከረ፡፡
እዚህ ከቆየሽ ተመልሸ አይሻለሁ፡፡ ሰባት መቶ ብር ለአንድ ነገር ይሆንሻል ብሎ ሰጣት፡፡ እግዚአብሔር ከአንች ጋር ይሁን፡፡ ብሏት ተሰነባብተው አቋርጦት ወደ ነበረው ስራው ተመለሰ፡፡
ከተሰነባበቱ በኋላ፤ አቶ አርምዴ ከአካባቢው ዞር እስከሚልላት ድረስ ፀበልተኛ መሰለች፡፡ ከአካባቢው እስኪሰወር ጠብቃ ወደ ሸንኮራ ባልጭ የሚወስደውን የፈረስ ጋሪ ተሳፈረች፡፡
ሰው እያባረረ የሚከተላት መሰላት፡፡ ከፈረስ ጋሪ እንደወረደች ከባልጭ ሞጆ የሚያደርሳትን ያዘች፡፡
እድላዊት አሁንም መነሻዋን እንጅ መድረሻዋን አታውቅም፡፡ ሞጆ መነሃሪያ ደረሰች፡፡ ከተሳፈረችበት ባስ ወርዳ ልብስ የያዘችበትን ፌስታል አንጠልጥላ ስራ ፈላጊዎች ወደ ሚቀመጡበት አካባቢ አመራች፡፡
አዳማ ናዝሬት አዳማ ….እያለ ይለፈልፋል፡፡ ጆሯዋ ጥልቅ አለ፡፡ ሃሳቧን ሰርዛ አዳማ ናዝሬት የሚለውን ሚኒባስ ተሳፍራ ጉዞዋን ወደ አዳማ ናዝሬት አደረገች፡፡
እረዳቱ ውረዱ አለ፡፡ መነሃሪያ ደርሰው፡፡ እድላዊት ሞጆና አዳማ የሚራራቁ መስሏት ውረዱ ሲባል አላመነችም ነበር፡፡
ከሞጆ እስሯ ተቀምጦ የመጣ አንድ መልከ መልካም ፍሪዛም ወጣት ሲወርድ ለመጠየቅ እየፈራች አንተ አንተ…..ብላ ሳትጨርስ ሳይሰማት ጥሏት ወረደ፡፡
እድላዊት ያላት አማራጭ ወርዳ መጠየቅ ሆነ፡፡ ፌስታሏን አንጠልጥላ ወረደች፡፡
የአዳማ መነሃሪያ ደላሎች እንደተገለበጠ የንብ ቀፎ ከበቧት፡፡ እያዋከቡ አንዱ ደላላ የትነሽ ? ድሬ ከሆንሽ አንድ ሰው የቀረው ነው፡፡ አሁን ልንወጣ ነው ነይ፡፡ ያንጠለጠለችውን ፌስታል የመዝረፍ ያህል ነጥቋት ሄደ፡፡
ሁለተኛው ደላላ ደግሞ የት ነሽ ? አሰላ ከሆንሽ ባይሞላም አሁን ይወጣል፡፡ ነይ እያለ እጇን እየጎተተ ወደ አሰላ በሚሄደው አውቶቢስ ውስጥ አስገባት፡፡ የአውቶቢሱን በር ዘግቶባት ወረደ፡፡
እድላዊት ወዲያና ወዲህ ሲያዋክቧት ቀልቧ ተገፏል፡፡ አፏን በፕላስተር የታሸገች መስላለች፡፡ ይህ ሁሉ ትእሪት ሲካሄድ የምትሄድበትን አልተናገረችም ነበር፡፡
"አንች እዚህ ምን ትሰሪያለሽ ? ያልሞላ መኪና ውስጥ እቃሽ እኮ ተጭኗል፡፡ አሁን ልንወጣ ነው ነይ፡፡
የዘጋባትን በር ከፍቶ ይዟት ሄደ፡፡ ፌስታሏን ወስዶ የጫነባት ደላላ፡፡ እኔ ነኝ ፣ እኔ ነኝ የምጭነው፡፡ ግብግብ ተፈጠረ፡፡ ከአሰላው ደላላ ጋር፡፡
የድሬው አሸንፎ መኪናው ውስጥ ጎትቶ አስገባት፡፡ ገና መቀመጫ ሳይሰጣት የአውቶቢሱን በር ዘግቶ ተንቀሳቀሰ፡፡ እድላዊት እኔ አልሔድም ፣ እቃየን ስጠኝ፡፡ አውርደኝ ብትልም የሚሰማት አላገኘችም፡፡
"ሂጅ እዛጋ ክፍት ወንበር አለ፡፡ ተቀመጭ" አላት እረዳቱ፡፡
ግራ የገባት ከርታታዋ እድላዊት ተቀመጭ ከተባለችበት ወንበር ላይ ተቀመጠች፡፡ ከአንገቷ አቀርቅራ መኪናው ወንበር ላይ ተደገፈች፡፡ ለተሳፋሪ እንቅልፍ የወሰዳት መሰለች፡፡ የመውደቂያዋ ቦታ አሳስቧታል፡፡ ተጨንቃለች ፣ ሆዷ ተርፏ ተርፏ ይላል፡፡
አይኖቿ እንባ አቅረዋል፡፡ ምነው አምላኬ የት ልታደርሰኝ ነው?፡፡ መድረሻየን አላውቀውም፡፡
አንተን አምኘ ነው፡፡ እንግዴህ እንደፍቃድህ አድርገኝ እያለች ፈጣሪዋን እያለቀሰች ተማፀነችው፡፡
የራሳቸውን ሃሳብ እያወጡ እያወረዱ ስለስራ ያስባሉ፡፡ ከስሯ የተቀመጡት ወ/ሮ ዘነቡ፡፡ እድላዊት ለምን አቀርቅራ እንደምታለቅስ ግራ ገብቷቸዋል፡፡
"ምነው ልጄ ምን ሆነሽ ነው የምታለቅሽው ? አሏት፡፡
"አይ! ምንም አልሆንኩም፡፡ አይኔን አሞኝ ነው አለች፡፡ ለራሷ ማልቀሷ ቢታወቃትም ፤ ስታለቅስ ግን ሰው የሰማት አልመሰላትም ነበር፡፡
"እና ማልቀሱ ጥሩ እኮ አይደለም፡፡ የባሰ ያምሻል አሉ፡፡ የእውነት አይኗን የታመመች መስሏቸው፡፡
ወ/ሮ ዘነቡ እድላዊትን በአለባበሷና በአነጋግሯ የገጠር ልጅ ለመሆኗ አልተጠራጠሩም ነበር፡፡
"እና አሁን የት ነው የምትሄጅው? አሏት ወ/ሮ ዘነቡ፡፡
እድላዊት የምትሄድበትን ቦታ አታውቅም፡፡ መጠጊያና ማረፊያ ለማግኘት ግን ሁሉንም አፍረጥርጣ መናገር የግድ ሆነባት፡፡
"የምሄድበትና መውደቂያዬን ባውቅማ ምን ያስለቅሰኝ ነበር፡፡ ያለማወቄ ነው እንጅ አለች፡፡ እንባዋ ሳያቋርጥ ግራና ቀኝ ጉልበቶቿ ላይ እየተንጠባጠበ፡፡
ከቤተሰቦቿ ጠፍታ መሆን አለበት ብለው ጠርጥረዋል ወ/ሮ ዘነቡ፡፡ ደግመው "ከየት ነው የመጣሽው? ታዲያ አሏት፡፡
"ከሸንኮራ ጅማ ነው የመጣሁት፡፡ ቤተሰቦቼን በህፃንነቴ ሞተውብኛል፡፡ ከዘመዶቼ ጋር አልስማማ ብዬ ጠፍቼ ነው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እድላዊት
"የባሰ አለና አገርህን አትልቅ" እንደሚባለው እድላዊት ከወ/ ሮ በሰልፏ ሞት ጋር የተቃጠረች ይመስላል፡፡
ሳይሞቱ ቀድሜ ልውጣ ማለቷ በአካል ባትነሳም በመንፈስ ተነስታ ጉዞዋን ማሰቧ ፤ አፈር ሳታለብሽኝ ፤ ጥለሽኝ ልትሄጅ ነው? ያሏት፡፡ ወ/ሮ በሰልፏ ፤ ከህሊና የማይወጣ ጥያቄ አሳደረባት፡፡
እድላዊት ግን አፈር ሳታለብሳቸው አልሄደችም ነበር፡፡ አንዴ ያደላትን የስቃይና የመከራ ፅዋ ተቀብላ የወ/ሮ በሰልፏን ተስካር አወጣች፡፡ ሁሉን ነገር ምላድ ምላድ አሰያዘች፡፡ ልብሶቿን አጣጥባ ተነሳች፡፡
"አሁን ባዶሽን አትሄጅም"፡፡ ስንቅ አሰናድተሽ ነገ እሸኝሻለሁ ብሎ አስቀራት፡፡ እሸ ብላ ቀረች፡፡
ስንቅ ለማሰናዳት አልፈለገችም፡፡ ግን ደግሞ ፀበል አለመሔዷን እንዲነቃባት አትፈልግም፡፡ ትንሽ ዳቦ ቆሎ መሳይ አዘጋጀች፡፡ በነጋታው ጠዋት ከአቶ አርምዴ ጋር ተነሳች፡፡
አንዳንዴ እየተነጋገሩ ፤ አንዳንዴ የመለያየታቸው ነገር እያሳሰባቸው ፤ ለየብቻቸው ፣ በየራሳቸው ሃሳብ እየነጎዱ ሳይታወቃቸው ሸንኮራ ዮሐንስ ደረሱ፡፡
የሸንኮራ ዮሃንስ ፀበል ከመዲናችን አዲስ አበባ በ144 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ሚያዝያ 15/1654 ዓ/ም ገደማ ፀበሉ ለአባ ካሳ እንደተገለፀላቸው ይነገራል፡፡
ይህ ፀበል አይነ ስውር የሚያበራ ፤ ለምፅን የሚያነፃ ፤ ኤች አይቪን የሚፈውስ ፤ የአጥንት ካንሰርን ነቅሎ የሚጥል ፤ በአጠቃላይ ሰው ሰራሽ ይሁን ተፈጥሯዊ በሽታዎችን የሚፈውስ ለመሆኑ ብዙዎች ድነዋል፡፡ ተፈውሰዋል ፣ ምስክርነታቸውንም ተናግረዋል ፡፡
"የት አካባቢ ይሻልሻል"? አላት፡፡ ቤት ሊያሲዛት ፈልጎ ፤ አቶ አርምዴ፡፡
እድላዊት ሸንኮራን አልፋ ለመሄድ እንጅ ቤት ለመያዝ አልፈለገችም፡፡
"አሁን ቤት አልይዝም ወደ ፀበሉ ልሂድና ስመለስ እይዛለሁ፡፡አይታወቅም ወይም የማቀው ሰው ላገኝ እችላለሁ፡፡ ለእኔ ምንም አታስብ ፤ በቃ አንተም ተመለስ፡፡ ስራህን ትተህ ነው የመጣኸው፡፡ ላደርክልኝ ውለታና እገዛ እግዚአብሔር ሁሉንም እሱ ይክፈልልኝ አመሰግናለሁ" አለች፡፡ የሃዘን ስሜት በውስጧ እየተሰማት፡፡
አይ! እድል እኔ ምን አላደረግሁልሽም፡፡ ትንሽ ስንዴ ነገር ሸጥ እንኳን አድርጌ ፤ እንዳላዘጋጅልሽ ለመሄድ ቸኮልሽ፡፡
ለስምንት ዓመት አብራው የኖረችው የሟች እህቶቹ ምትክ እድላዊት ልትለየው በመወሰኗ ፤ የወንድ አንጀቱ እንደወላድ ተላወሰ፡፡ በአይኖቹ እንባው ግጥም አለበት፡፡
እድላዊት ከሞት አፋፍ ላይ ያተረፋትን አርምዴን መለየት አቃታት፡፡ ሆድ ባሳት፤ አለቀሰች፡፡ አርምዴ ያወራውን የሰማች አትመስልም፡፡
በፊቱ ላይ የወረደውን እንባ ጠራረገ፡፡ እድል ይበቃል አስካሁን ስታለቅሽ የኖርሽው፡፡ በትንሹም ፣ በትልቁም ማልቀስ ጥሩ አይደለም፡፡ የባሰ ሊያስከትል ይችላል፡፡ ለማፅናናት ሞከረ፡፡
እዚህ ከቆየሽ ተመልሸ አይሻለሁ፡፡ ሰባት መቶ ብር ለአንድ ነገር ይሆንሻል ብሎ ሰጣት፡፡ እግዚአብሔር ከአንች ጋር ይሁን፡፡ ብሏት ተሰነባብተው አቋርጦት ወደ ነበረው ስራው ተመለሰ፡፡
ከተሰነባበቱ በኋላ፤ አቶ አርምዴ ከአካባቢው ዞር እስከሚልላት ድረስ ፀበልተኛ መሰለች፡፡ ከአካባቢው እስኪሰወር ጠብቃ ወደ ሸንኮራ ባልጭ የሚወስደውን የፈረስ ጋሪ ተሳፈረች፡፡
ሰው እያባረረ የሚከተላት መሰላት፡፡ ከፈረስ ጋሪ እንደወረደች ከባልጭ ሞጆ የሚያደርሳትን ያዘች፡፡
እድላዊት አሁንም መነሻዋን እንጅ መድረሻዋን አታውቅም፡፡ ሞጆ መነሃሪያ ደረሰች፡፡ ከተሳፈረችበት ባስ ወርዳ ልብስ የያዘችበትን ፌስታል አንጠልጥላ ስራ ፈላጊዎች ወደ ሚቀመጡበት አካባቢ አመራች፡፡
አዳማ ናዝሬት አዳማ ….እያለ ይለፈልፋል፡፡ ጆሯዋ ጥልቅ አለ፡፡ ሃሳቧን ሰርዛ አዳማ ናዝሬት የሚለውን ሚኒባስ ተሳፍራ ጉዞዋን ወደ አዳማ ናዝሬት አደረገች፡፡
እረዳቱ ውረዱ አለ፡፡ መነሃሪያ ደርሰው፡፡ እድላዊት ሞጆና አዳማ የሚራራቁ መስሏት ውረዱ ሲባል አላመነችም ነበር፡፡
ከሞጆ እስሯ ተቀምጦ የመጣ አንድ መልከ መልካም ፍሪዛም ወጣት ሲወርድ ለመጠየቅ እየፈራች አንተ አንተ…..ብላ ሳትጨርስ ሳይሰማት ጥሏት ወረደ፡፡
እድላዊት ያላት አማራጭ ወርዳ መጠየቅ ሆነ፡፡ ፌስታሏን አንጠልጥላ ወረደች፡፡
የአዳማ መነሃሪያ ደላሎች እንደተገለበጠ የንብ ቀፎ ከበቧት፡፡ እያዋከቡ አንዱ ደላላ የትነሽ ? ድሬ ከሆንሽ አንድ ሰው የቀረው ነው፡፡ አሁን ልንወጣ ነው ነይ፡፡ ያንጠለጠለችውን ፌስታል የመዝረፍ ያህል ነጥቋት ሄደ፡፡
ሁለተኛው ደላላ ደግሞ የት ነሽ ? አሰላ ከሆንሽ ባይሞላም አሁን ይወጣል፡፡ ነይ እያለ እጇን እየጎተተ ወደ አሰላ በሚሄደው አውቶቢስ ውስጥ አስገባት፡፡ የአውቶቢሱን በር ዘግቶባት ወረደ፡፡
እድላዊት ወዲያና ወዲህ ሲያዋክቧት ቀልቧ ተገፏል፡፡ አፏን በፕላስተር የታሸገች መስላለች፡፡ ይህ ሁሉ ትእሪት ሲካሄድ የምትሄድበትን አልተናገረችም ነበር፡፡
"አንች እዚህ ምን ትሰሪያለሽ ? ያልሞላ መኪና ውስጥ እቃሽ እኮ ተጭኗል፡፡ አሁን ልንወጣ ነው ነይ፡፡
የዘጋባትን በር ከፍቶ ይዟት ሄደ፡፡ ፌስታሏን ወስዶ የጫነባት ደላላ፡፡ እኔ ነኝ ፣ እኔ ነኝ የምጭነው፡፡ ግብግብ ተፈጠረ፡፡ ከአሰላው ደላላ ጋር፡፡
የድሬው አሸንፎ መኪናው ውስጥ ጎትቶ አስገባት፡፡ ገና መቀመጫ ሳይሰጣት የአውቶቢሱን በር ዘግቶ ተንቀሳቀሰ፡፡ እድላዊት እኔ አልሔድም ፣ እቃየን ስጠኝ፡፡ አውርደኝ ብትልም የሚሰማት አላገኘችም፡፡
"ሂጅ እዛጋ ክፍት ወንበር አለ፡፡ ተቀመጭ" አላት እረዳቱ፡፡
ግራ የገባት ከርታታዋ እድላዊት ተቀመጭ ከተባለችበት ወንበር ላይ ተቀመጠች፡፡ ከአንገቷ አቀርቅራ መኪናው ወንበር ላይ ተደገፈች፡፡ ለተሳፋሪ እንቅልፍ የወሰዳት መሰለች፡፡ የመውደቂያዋ ቦታ አሳስቧታል፡፡ ተጨንቃለች ፣ ሆዷ ተርፏ ተርፏ ይላል፡፡
አይኖቿ እንባ አቅረዋል፡፡ ምነው አምላኬ የት ልታደርሰኝ ነው?፡፡ መድረሻየን አላውቀውም፡፡
አንተን አምኘ ነው፡፡ እንግዴህ እንደፍቃድህ አድርገኝ እያለች ፈጣሪዋን እያለቀሰች ተማፀነችው፡፡
የራሳቸውን ሃሳብ እያወጡ እያወረዱ ስለስራ ያስባሉ፡፡ ከስሯ የተቀመጡት ወ/ሮ ዘነቡ፡፡ እድላዊት ለምን አቀርቅራ እንደምታለቅስ ግራ ገብቷቸዋል፡፡
"ምነው ልጄ ምን ሆነሽ ነው የምታለቅሽው ? አሏት፡፡
"አይ! ምንም አልሆንኩም፡፡ አይኔን አሞኝ ነው አለች፡፡ ለራሷ ማልቀሷ ቢታወቃትም ፤ ስታለቅስ ግን ሰው የሰማት አልመሰላትም ነበር፡፡
"እና ማልቀሱ ጥሩ እኮ አይደለም፡፡ የባሰ ያምሻል አሉ፡፡ የእውነት አይኗን የታመመች መስሏቸው፡፡
ወ/ሮ ዘነቡ እድላዊትን በአለባበሷና በአነጋግሯ የገጠር ልጅ ለመሆኗ አልተጠራጠሩም ነበር፡፡
"እና አሁን የት ነው የምትሄጅው? አሏት ወ/ሮ ዘነቡ፡፡
እድላዊት የምትሄድበትን ቦታ አታውቅም፡፡ መጠጊያና ማረፊያ ለማግኘት ግን ሁሉንም አፍረጥርጣ መናገር የግድ ሆነባት፡፡
"የምሄድበትና መውደቂያዬን ባውቅማ ምን ያስለቅሰኝ ነበር፡፡ ያለማወቄ ነው እንጅ አለች፡፡ እንባዋ ሳያቋርጥ ግራና ቀኝ ጉልበቶቿ ላይ እየተንጠባጠበ፡፡
ከቤተሰቦቿ ጠፍታ መሆን አለበት ብለው ጠርጥረዋል ወ/ሮ ዘነቡ፡፡ ደግመው "ከየት ነው የመጣሽው? ታዲያ አሏት፡፡
"ከሸንኮራ ጅማ ነው የመጣሁት፡፡ ቤተሰቦቼን በህፃንነቴ ሞተውብኛል፡፡ ከዘመዶቼ ጋር አልስማማ ብዬ ጠፍቼ ነው፡፡
👍56❤12
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እጅግ በጣም ይቅርታ ስልኬ ስለጠፋ እረጅም ጊዜ ታሪኩን ሳለቅ ቀረሁ ወደኋላ መለስ ብለቹ ታሪኩን በማስታወስ ቀጥሉ እንደእግዚአብሔር ፍቃድ ከነገ ጀምሮ ሁለት ክፍል እለቃለሁ እንዲሁም ነገ ማታ ሁለት ሰአት ላይ ሌላ አዲስ ታሪክ እንጀምራለን የተከፋችሁብኝ አሁንም በድጋሚ ይቅርታ እጠይቃለሁ🙏
ያሬድ
ከገበያ መጥቶ ደክሞታል፡፡ ገና ሳይመሽ ከመኝታው ላይ ጋደም እንደማለት ብሏል፡፡
"ተመስገንን አብረን እንሄዳለን ብለኸው ነበር እንዴ"? አለች ፤ ባለቤቱ አበበች፡፡
"አዎ ፤ ብዬው ነበር፡፡ ገንዘብ እንዳዘጋጀ ነገረሽ እንዴ"?
"ትላንት አንተን ፈልጎ መጥቶ ነበር፡፡ ሳያገኝህ ሲቀር ለእኔ አጫውቶኛል፡፡ እንሂድ እስከምትለው ነው የሚጠብቀው" ፡፡
"ታዲያ ምን ችግር አለ፡፡ የመነገድ ፍላጎት ካለው አሁን ደግሞ ውሎ ገባ ስለሆነ የምንመጣው ቀን እንኳን ቢመሽም ሁለት መሆኑ አይከፋም፡፡ ከነገ ወዲያ ይዠው እሄዳለሁ"፡፡
ገና በደንብ አልነጋም፡፡ ያሬድም ከመኝታው አልተነሳም፡፡ አበበች አለ ፡፡ ሳይደጋግም በአንዴ የሚሰማ መስሎት፡፡ ነገር ግን የሚሰማው አላገኘም፡፡ አቤት የሚለው አጣ፡፡ ደግሞ ተጣራ፡፡ ያሬድ…..ያሬድ አለ፡፡ አቤት አለች አበበች፡፡ ብቅበይ አለ፡፡ በጥዋት ወደ ያሬድ ጋር የመጣው ተመስገን፡፡
ማነው በጥዋት ብቅበይ የሚለው ብላ ብቅ አለች፡፡
"ደህና አደርሽ አበበች ? አለ" ተመስገን፡፡
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደርህ ተመስገን፡፡ አትገባም እንዴ ከብርድ ላይ ፡፡
"ይሁን አልገባም፡፡ ያሬድ የለም እንዴ ? ፡፡
"አለ ፤ ከመኝታውም አልተነሳም፡፡ ምነው ደህና አይደለህም እንዴ ?
"ኧረ ደህናነኝ፡፡ ለዛ ላጫወትኩሽ ጉዳይ ነበር የመጣሁት ፡፡
"አይ! እሱንማ ከሆነ እኔም ማታ አጫውቸዋለሁ፡፡ ለመነገድ ፍላጎት ካለው ይዠው እሄዳለሁ ብሏል፡፡ ለማንኛውም ግባና አነጋግረው ፡፡
ተመስገን የመጣበትን ጉዳይ እንደተሳካለት አሰበ፡፡ ያሬድን ለማነጋገር ወደ ቤት ገባ፡፡
"ደህና አደርህ ያሬድ? ፣ ደሞ ዛሬ በጥዋት አልተነሳህም፡፡ እንቅልፍ ነው ወይስ ድካም ነው?፡፡ ያስተኛህ ፡፡
"ሰላም አደርህ ተመስገን፡፡ ምን የትናንት ገበያ ውልቅልቅ አድርጎኛል፡፡ አሁን በደንብ ነግቷል ማለት ነው እንዴ? አለ፡፡ ከተኛበት መኝታ ተነስቶ እየተንጠራራ፡፡
"ስድስት ሰዓት ሆኖ ነግቷል ትላለህ እንዴ ፤ ለነገሩ ከተማ ለከተማ ስትመላለስ የከተማ ሰው ሆነሃል፡፡ እነኝህ ከተመኞች ሰዓት አስረው ቢይዙም ፤ የሚቆጥሩ መሆናቸውን እንጃ ፤ በየሰዓቱ ነው የሚበሉ
አለ፡፡ ተመስገን እንደማሾፍ ብሎ፡፡
"አይ! ተመስገን እነሱማ በሰዓት የማይበሉበት ጊዜ ስለሌላቸው ነው፡፡ ያለመቁጠር አይደለም፡፡ እንዲያውም እኛ ነን አንዴ ቁርስሠ ፣ አንዴ ምሳ ሰዓት ፣ ደረሰ እያልን ሰዓት የሚቃወመን ይመስል በቀን ሶስቴ ሳይበቃን አራተኛ መክሰስ እያልን የምንመገበው፡
"አይ! መልካም ነው" ብሎ "ለባለፈው ጉዳይ ነበር የመጣሁት" አለ ተመስገን ፡፡
"አበበች ማታ በጨዋታ አንስተን ነግራኛለች፡፡ እና ለመነገድ ፈልገሃል ማለት ነው?፡፡
"የመነገድ ፍላጎት እንኳን ብዙም የለኝም፡፡ እንዴው የዛችን የእህቴ ነገር አንጄቴ አልቆርጥ ብሎኝ ነው፡፡ መቼም እቤት ከመቀመጥ አካባቢንና አገርን ማወቅ አይከፋም፡፡ የእግዚአብሔር ስራም አይታወቅም፡፡ በዛውም እናገኛት ይሆናል"፡፡
"ጥሩ ነው ለማንኛውም ሃሳብህ አይከፋም፡፡ ነገ አብረን ማለድ ብለህ በጥዋት ና፡፡ ውሎ ገባ ስለምንመለስ እንዳይረፍድብን"፡፡
"እሽ በጥዋት እመጣለሁ፡፡ ብሎት ተሰነባብተው ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡
"በነጋታው በጥዋት ቡና ፈልቶ ተመስገን እየተጠበቀ ነው፡፡ ግን ቶሎ ሊመጣ አልቻለም፡፡ በቃ ቀርቶ ነው ብላ አበበች ቁርስ ልታቀርብ ስትል ተመስገን መጣ፡፡ ሰላምታ ተለዋውጠው ተቀመጠ፡፡
"ምነው አረፈድህ" አለው ያሬድ
"ምን ሌሊቱን እንቅልፍ ሳይወሰደኝ አድሮ ሊነጋጋ አካባቢ ሸለብ አላደረገኝ መሰለህ ፡፡
"አይ! አንተ ሌሊቱን ሙሉ በሃሳብ ስትሄድ አድረህ ነዋ፡፡ ጥዋት በመነሻህ ሰዓት እንቅልፍ የጣለህ፡፡ በል አሁን የቡና ቁርሱን ያዝና ቡናውን ጠጥተን ቶሎ እንውጣ፡፡ የባልጪ መኪና ሳያመልጠን እንድረስበት፡፡ አንዴ ካመለጠን መመለስ ካልሆነ ሌላ መኪና አናገኝም፡፡
ባለቤቱን በይ እንግዴህ ከብት ሳይበዛ ከብቶቹን ውሃ አጠጫቸው ብሏት ተነስተው ከተመስገን ጋር ጉዞዋቸውን ወደ አዳማ ቀጠሉ፡፡
መኪና እንዳያመልጣቸው እየተጣደፉ ነው፡፡ ከመንገድ ላይ አንድ ጥቁር ሰው ከፊት ለፊታቸው ገጠማቸው፡፡
"ዛሬ ላይቀናን ነው መሰለኝ አለ ተመስገን፡፡ ውስጡ እንደመረበሽ እያለበት፡፡
"ምነው ምን አየህ አለው? ያሬድ፡፡
"ተመስገን የፍጥነት እርምጃውን ገታ አድርጎ ፤ መንገድ ስትሄድ አንድ ሰው ከገጠመህ የምትሄድበት አይቀናህም፡፡ አባቴ ሲናገር ሰምቻለሁ፡፡ አሁንም እኛ አንድ ሰው ሰለገጠመን ብዬ ነው፡፡
ባያምንበትም ግን ሆዱ እንደመፍራት ብሏል፡፡ "ተው! እባክ ይህ የአንዳንድ ሰው አባባል ነው፡፡ አንተ ደግሞ ያባትህን አትከተል እግዚአብሔር እንደፈቀደ ያድርገን እንግዴህ አለ፡፡ በፍራቻ ንግግርም ቢሆን፡፡
"እሱማ እግዚአብሔር ነው የሚያውቀው፡፡ እንዴው የሚባለውንና ነው እንጅ ያልኩህ፡፡
ያሬድ ነገሩን ተወት አድርጎ ፤ አሁን ቶሎ ቶሎ ራመድ ራመድ በል፡፡ ያ አቶ ላንቻ ብቻ ሳይቀድመን እንድንደርስበት፡፡
"የማነው አቶ ላንቻ? አለ ተመስገን፡፡
"ለእኔ ከድሬ አዳማ ድረስ አልባሳ የሚያመጡልኝ ናቸው፡፡ መቼም ብታያቸው የተባረኩ እና ደግ ሰው ናቸው፡፡
አሁንም ከሳቸው ተረክበን ነው፡፡ የምንመለሰው ከቀናን"፡፡
"እኔ እኮ ውሎ ገባ ስትመጣ በአየር መምጣት ጀመረ እንዴ ብየ ነበር፡፡ ለካስ አንተ አዳማ ድረስ የሚያመጣልህ ደንበኛ አግኝተህ ኖሯል፡፡እየከነፍህ የምትመጣው"፡፡
"መኪናው ሞልቶ አንድ ሰው ብቻ ቀርቶት ይጠባበቃል፡፡ እየተጣደፉ ደረሱ፡፡ ግን እረዳቱ ከአንድ ሰው ውጭ አልጭንም አላቸው፡፡ ጫነን አልጭንም ፤ ሲከራከሩ አንድ ረፍዶበት የነበር ሰው ረዳቱንም ሳይጠይቅ አልፎ መኪናው ውስጥ ገባ፡፡ ያሬድ ቢለምንም ፣ ቢማፀንም ሳያሳፍራቸው ጥሏቸው ሄደ፡፡
አላልኩህም፡፡ አንድ ሰው ጥሩ አይደለም ብየህ ነበር አለው ተመስገን፡፡
ጸያሬድ ተመስገን ያለውን የሰማው አይመስልም፡፡ ልቡ ያለው አቶ ላንቻ ጋር ነው፡፡ አንድ የጭነት መኪና ወደ አዳማ ልትወጣ ከመንገድ ላይ ቆማለች፡፡
"ይችን መኪና እንጠይቃት እስቲ ፤ ትጭነን እንደ ሆነ አለ ተመስገን፡፡
"እህል ጭና እያየሃት እንዴት እሽ ብለው ይጭኑናል፡፡ ያጠፋነው እኛ ነን፡፡ በጥዋት መምጣት ሲገባን አርፍደን፡፡ አሁን ያለን አማራጭ ወደ ቤት መመለስ ነው፡፡ ነገ ተመልሰን እንመጣለን፡፡ እንደው
የሚያነድደኝ እምነት ማጉደሌ ነው፡፡ መቼም መኪና አጥቶ ቀረ አይሉኝም፡፡ ሆነ ብሎ ነው እንጅ የሚሉኝ፡፡ እህል ወደ ጫነችው አይሱዚ ተጠጉ፡፡
ፈራ ተባ እያለ ማነህ ወንድም ወደ አዳማ እንደሆነ የምትሄደው መኪና ጥሎን ስለሄደ ነው፡፡ እባክህ ተባበረን ብሎ ሹፌሩን ጠየቀው ያሬድ፡፡
የመኪናው ሹፌር አላመነታም፡፡ "ስንት ናችሁ"? አለ፡፡
"ሁለት ነን አለ፤ ያሬድ፡፡
"ሁለት ሰው ከሆነ አልጭንም"፡፡ አንድ ሰው ከሆነ ጋቢና ግባ አለ፡፡ ባጭር ቃል ሹፌሩ፡፡
"እባክህን ወንድም ተባበረን ስለማንነጣጠል ነው፡፡ የምንሔደውም የታመመ ሰው ለማምጣት ነው፡፡
እንደምንም ተቸገርልን፡፡ ከላይም ቢሆን ተጭነን እንሄዳለን እያለ ሹፌሩን ተማፀነው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እጅግ በጣም ይቅርታ ስልኬ ስለጠፋ እረጅም ጊዜ ታሪኩን ሳለቅ ቀረሁ ወደኋላ መለስ ብለቹ ታሪኩን በማስታወስ ቀጥሉ እንደእግዚአብሔር ፍቃድ ከነገ ጀምሮ ሁለት ክፍል እለቃለሁ እንዲሁም ነገ ማታ ሁለት ሰአት ላይ ሌላ አዲስ ታሪክ እንጀምራለን የተከፋችሁብኝ አሁንም በድጋሚ ይቅርታ እጠይቃለሁ🙏
ያሬድ
ከገበያ መጥቶ ደክሞታል፡፡ ገና ሳይመሽ ከመኝታው ላይ ጋደም እንደማለት ብሏል፡፡
"ተመስገንን አብረን እንሄዳለን ብለኸው ነበር እንዴ"? አለች ፤ ባለቤቱ አበበች፡፡
"አዎ ፤ ብዬው ነበር፡፡ ገንዘብ እንዳዘጋጀ ነገረሽ እንዴ"?
"ትላንት አንተን ፈልጎ መጥቶ ነበር፡፡ ሳያገኝህ ሲቀር ለእኔ አጫውቶኛል፡፡ እንሂድ እስከምትለው ነው የሚጠብቀው" ፡፡
"ታዲያ ምን ችግር አለ፡፡ የመነገድ ፍላጎት ካለው አሁን ደግሞ ውሎ ገባ ስለሆነ የምንመጣው ቀን እንኳን ቢመሽም ሁለት መሆኑ አይከፋም፡፡ ከነገ ወዲያ ይዠው እሄዳለሁ"፡፡
ገና በደንብ አልነጋም፡፡ ያሬድም ከመኝታው አልተነሳም፡፡ አበበች አለ ፡፡ ሳይደጋግም በአንዴ የሚሰማ መስሎት፡፡ ነገር ግን የሚሰማው አላገኘም፡፡ አቤት የሚለው አጣ፡፡ ደግሞ ተጣራ፡፡ ያሬድ…..ያሬድ አለ፡፡ አቤት አለች አበበች፡፡ ብቅበይ አለ፡፡ በጥዋት ወደ ያሬድ ጋር የመጣው ተመስገን፡፡
ማነው በጥዋት ብቅበይ የሚለው ብላ ብቅ አለች፡፡
"ደህና አደርሽ አበበች ? አለ" ተመስገን፡፡
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደርህ ተመስገን፡፡ አትገባም እንዴ ከብርድ ላይ ፡፡
"ይሁን አልገባም፡፡ ያሬድ የለም እንዴ ? ፡፡
"አለ ፤ ከመኝታውም አልተነሳም፡፡ ምነው ደህና አይደለህም እንዴ ?
"ኧረ ደህናነኝ፡፡ ለዛ ላጫወትኩሽ ጉዳይ ነበር የመጣሁት ፡፡
"አይ! እሱንማ ከሆነ እኔም ማታ አጫውቸዋለሁ፡፡ ለመነገድ ፍላጎት ካለው ይዠው እሄዳለሁ ብሏል፡፡ ለማንኛውም ግባና አነጋግረው ፡፡
ተመስገን የመጣበትን ጉዳይ እንደተሳካለት አሰበ፡፡ ያሬድን ለማነጋገር ወደ ቤት ገባ፡፡
"ደህና አደርህ ያሬድ? ፣ ደሞ ዛሬ በጥዋት አልተነሳህም፡፡ እንቅልፍ ነው ወይስ ድካም ነው?፡፡ ያስተኛህ ፡፡
"ሰላም አደርህ ተመስገን፡፡ ምን የትናንት ገበያ ውልቅልቅ አድርጎኛል፡፡ አሁን በደንብ ነግቷል ማለት ነው እንዴ? አለ፡፡ ከተኛበት መኝታ ተነስቶ እየተንጠራራ፡፡
"ስድስት ሰዓት ሆኖ ነግቷል ትላለህ እንዴ ፤ ለነገሩ ከተማ ለከተማ ስትመላለስ የከተማ ሰው ሆነሃል፡፡ እነኝህ ከተመኞች ሰዓት አስረው ቢይዙም ፤ የሚቆጥሩ መሆናቸውን እንጃ ፤ በየሰዓቱ ነው የሚበሉ
አለ፡፡ ተመስገን እንደማሾፍ ብሎ፡፡
"አይ! ተመስገን እነሱማ በሰዓት የማይበሉበት ጊዜ ስለሌላቸው ነው፡፡ ያለመቁጠር አይደለም፡፡ እንዲያውም እኛ ነን አንዴ ቁርስሠ ፣ አንዴ ምሳ ሰዓት ፣ ደረሰ እያልን ሰዓት የሚቃወመን ይመስል በቀን ሶስቴ ሳይበቃን አራተኛ መክሰስ እያልን የምንመገበው፡
"አይ! መልካም ነው" ብሎ "ለባለፈው ጉዳይ ነበር የመጣሁት" አለ ተመስገን ፡፡
"አበበች ማታ በጨዋታ አንስተን ነግራኛለች፡፡ እና ለመነገድ ፈልገሃል ማለት ነው?፡፡
"የመነገድ ፍላጎት እንኳን ብዙም የለኝም፡፡ እንዴው የዛችን የእህቴ ነገር አንጄቴ አልቆርጥ ብሎኝ ነው፡፡ መቼም እቤት ከመቀመጥ አካባቢንና አገርን ማወቅ አይከፋም፡፡ የእግዚአብሔር ስራም አይታወቅም፡፡ በዛውም እናገኛት ይሆናል"፡፡
"ጥሩ ነው ለማንኛውም ሃሳብህ አይከፋም፡፡ ነገ አብረን ማለድ ብለህ በጥዋት ና፡፡ ውሎ ገባ ስለምንመለስ እንዳይረፍድብን"፡፡
"እሽ በጥዋት እመጣለሁ፡፡ ብሎት ተሰነባብተው ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡
"በነጋታው በጥዋት ቡና ፈልቶ ተመስገን እየተጠበቀ ነው፡፡ ግን ቶሎ ሊመጣ አልቻለም፡፡ በቃ ቀርቶ ነው ብላ አበበች ቁርስ ልታቀርብ ስትል ተመስገን መጣ፡፡ ሰላምታ ተለዋውጠው ተቀመጠ፡፡
"ምነው አረፈድህ" አለው ያሬድ
"ምን ሌሊቱን እንቅልፍ ሳይወሰደኝ አድሮ ሊነጋጋ አካባቢ ሸለብ አላደረገኝ መሰለህ ፡፡
"አይ! አንተ ሌሊቱን ሙሉ በሃሳብ ስትሄድ አድረህ ነዋ፡፡ ጥዋት በመነሻህ ሰዓት እንቅልፍ የጣለህ፡፡ በል አሁን የቡና ቁርሱን ያዝና ቡናውን ጠጥተን ቶሎ እንውጣ፡፡ የባልጪ መኪና ሳያመልጠን እንድረስበት፡፡ አንዴ ካመለጠን መመለስ ካልሆነ ሌላ መኪና አናገኝም፡፡
ባለቤቱን በይ እንግዴህ ከብት ሳይበዛ ከብቶቹን ውሃ አጠጫቸው ብሏት ተነስተው ከተመስገን ጋር ጉዞዋቸውን ወደ አዳማ ቀጠሉ፡፡
መኪና እንዳያመልጣቸው እየተጣደፉ ነው፡፡ ከመንገድ ላይ አንድ ጥቁር ሰው ከፊት ለፊታቸው ገጠማቸው፡፡
"ዛሬ ላይቀናን ነው መሰለኝ አለ ተመስገን፡፡ ውስጡ እንደመረበሽ እያለበት፡፡
"ምነው ምን አየህ አለው? ያሬድ፡፡
"ተመስገን የፍጥነት እርምጃውን ገታ አድርጎ ፤ መንገድ ስትሄድ አንድ ሰው ከገጠመህ የምትሄድበት አይቀናህም፡፡ አባቴ ሲናገር ሰምቻለሁ፡፡ አሁንም እኛ አንድ ሰው ሰለገጠመን ብዬ ነው፡፡
ባያምንበትም ግን ሆዱ እንደመፍራት ብሏል፡፡ "ተው! እባክ ይህ የአንዳንድ ሰው አባባል ነው፡፡ አንተ ደግሞ ያባትህን አትከተል እግዚአብሔር እንደፈቀደ ያድርገን እንግዴህ አለ፡፡ በፍራቻ ንግግርም ቢሆን፡፡
"እሱማ እግዚአብሔር ነው የሚያውቀው፡፡ እንዴው የሚባለውንና ነው እንጅ ያልኩህ፡፡
ያሬድ ነገሩን ተወት አድርጎ ፤ አሁን ቶሎ ቶሎ ራመድ ራመድ በል፡፡ ያ አቶ ላንቻ ብቻ ሳይቀድመን እንድንደርስበት፡፡
"የማነው አቶ ላንቻ? አለ ተመስገን፡፡
"ለእኔ ከድሬ አዳማ ድረስ አልባሳ የሚያመጡልኝ ናቸው፡፡ መቼም ብታያቸው የተባረኩ እና ደግ ሰው ናቸው፡፡
አሁንም ከሳቸው ተረክበን ነው፡፡ የምንመለሰው ከቀናን"፡፡
"እኔ እኮ ውሎ ገባ ስትመጣ በአየር መምጣት ጀመረ እንዴ ብየ ነበር፡፡ ለካስ አንተ አዳማ ድረስ የሚያመጣልህ ደንበኛ አግኝተህ ኖሯል፡፡እየከነፍህ የምትመጣው"፡፡
"መኪናው ሞልቶ አንድ ሰው ብቻ ቀርቶት ይጠባበቃል፡፡ እየተጣደፉ ደረሱ፡፡ ግን እረዳቱ ከአንድ ሰው ውጭ አልጭንም አላቸው፡፡ ጫነን አልጭንም ፤ ሲከራከሩ አንድ ረፍዶበት የነበር ሰው ረዳቱንም ሳይጠይቅ አልፎ መኪናው ውስጥ ገባ፡፡ ያሬድ ቢለምንም ፣ ቢማፀንም ሳያሳፍራቸው ጥሏቸው ሄደ፡፡
አላልኩህም፡፡ አንድ ሰው ጥሩ አይደለም ብየህ ነበር አለው ተመስገን፡፡
ጸያሬድ ተመስገን ያለውን የሰማው አይመስልም፡፡ ልቡ ያለው አቶ ላንቻ ጋር ነው፡፡ አንድ የጭነት መኪና ወደ አዳማ ልትወጣ ከመንገድ ላይ ቆማለች፡፡
"ይችን መኪና እንጠይቃት እስቲ ፤ ትጭነን እንደ ሆነ አለ ተመስገን፡፡
"እህል ጭና እያየሃት እንዴት እሽ ብለው ይጭኑናል፡፡ ያጠፋነው እኛ ነን፡፡ በጥዋት መምጣት ሲገባን አርፍደን፡፡ አሁን ያለን አማራጭ ወደ ቤት መመለስ ነው፡፡ ነገ ተመልሰን እንመጣለን፡፡ እንደው
የሚያነድደኝ እምነት ማጉደሌ ነው፡፡ መቼም መኪና አጥቶ ቀረ አይሉኝም፡፡ ሆነ ብሎ ነው እንጅ የሚሉኝ፡፡ እህል ወደ ጫነችው አይሱዚ ተጠጉ፡፡
ፈራ ተባ እያለ ማነህ ወንድም ወደ አዳማ እንደሆነ የምትሄደው መኪና ጥሎን ስለሄደ ነው፡፡ እባክህ ተባበረን ብሎ ሹፌሩን ጠየቀው ያሬድ፡፡
የመኪናው ሹፌር አላመነታም፡፡ "ስንት ናችሁ"? አለ፡፡
"ሁለት ነን አለ፤ ያሬድ፡፡
"ሁለት ሰው ከሆነ አልጭንም"፡፡ አንድ ሰው ከሆነ ጋቢና ግባ አለ፡፡ ባጭር ቃል ሹፌሩ፡፡
"እባክህን ወንድም ተባበረን ስለማንነጣጠል ነው፡፡ የምንሔደውም የታመመ ሰው ለማምጣት ነው፡፡
እንደምንም ተቸገርልን፡፡ ከላይም ቢሆን ተጭነን እንሄዳለን እያለ ሹፌሩን ተማፀነው፡፡
👍85❤11👎2🥰1
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ቀነ ጎደሎ
ጨለማ በተቀላቀለበት ሌሊት ተነሱ፡፡ ወደ አዳማ ለመሄድ ተቻኩለዋል፡፡ ከቡቲካቸው አልባሳት እና ሌሎች እቃዎችንም ጫኑ፡፡ እንዳይረፍድባቸው ሹፌሩን ፍጥነት ጨምሮ እንዲነዳ አዘዙት፡፡ ከወትሮው በተለየ መልኩ ደብሯቸዋል፡፡ ሰውነታቸውን ከብዷቸዋል፡፡ ፊታቸውን ጨፍጓቸዋል፡፡ አፋቸውን እሬት እሬት ብሏቸዋል፡፡ ደጋግመው አፋቸውን በባዶው አላመጡት፡፡ ለውጥ ግን አላመጣላቸውም
ለሹፌሩ "ዛሬ ደግሞ ምን እንደሆንኩ እንጃ አፌን እሬት እሬት እያለኝ ነው" አሉት፡፡
"ምነው ቁርስ አልበሉም እንዴ?" ደግሞ ደስተኛ አይመስሉም፡፡ ደህና አይደሉም"? አለ፡፡ ሹፌራቸው ሰለሞን፡፡
"ኧረ ! ደህናነኝ፡፡ ብቻ ውስጤ እርብሽብሽ ብሏል፡፡ ሌሊትም ደግሞ ሲያቃዥኝ ነው ያደረው፡፡ ጥዋትም ቁርስ ወደ አፌ ስል አልዋጥ አለኝ፡፡ ምን እንደሆንኩ ለራሴም ሊገባኝ አልቻለም አሉ ፤ አቶ ላንቻ፡፡
"አስበውት ያላሳኩት ነገር አለ እንዴ"?
"አስቤ ያላሳካሁት ነገር እንኳን ያለ አይመስለኝም፡፡ ምንአልባት ዛሬ ማርፈዴ ብቻ ነው ትንሽ ያበሳጨኝ፡፡ ለምን እንደረፈደብኝም ሳላውቅ ከሩቅ የሚመጣ ደንበኛ ነበረኝ ያሬድ የሚባል፡፡ እንዴው ጠብቆኝ ሲያጣኝ ባልተመለሰ ብቻ እንጅ ቢያድግልኝ እንኳን ከሱቅ የትም ስለማይሄድ አምሽተንም ብንደርስ እናገኘዋለን፡፡ ለማንኛውም ነዳጅ ሰጠት አድርገህ ቶሎ ቶሎ ንዳው ፡፡
"እሽ አሁንም እኮ ፈጥነናል፡፡ ግን እኔም እኮ እጄ ሁሉ ተሳሰረብኝ" አለ ሰለሞን፡፡
ዘ
"ምነው አንተ ደግሞ ምን ሆነህ ነው ? ስትጨፍር እና ስትጠጣ አድረህ ፤ ምን አልባት እንቅልፍ መጥቶብህ እንዳይሆን"?
"እንኳን ስጠጣ ፣ ስጨፍር ላድር ፤ የጨብስም አጥቼ የዘጠኝ ብር አህያ መስየ ነው፡፡ ያደርኩት ፡፡
.አቶ ላንቻ የሰለሞን ፈሊጣዊ ንግግር አሳቃቸው፡፡ የዘጠኝ ብር አህያ ማለት ደግሞ ምን ማለት ነው? መቼም የዛሬ ልጆች የማታመጡት ጉድ የለም ፡፡
በመስኮት አይናቸውን ወርወር አደረጉ፡፡ ከበስተቀኝ በኩል የጋኔል ቁራጭ የሚመስል ጥቁር ውሻ ሊያቋርጣቸው ይሮጣል፡፡ ሰለሞን አፍጥነው ፣ አፍጥነው መኪናውን ፤ ይሔ ውሻ ሳያቋርጠን ፤ እንቅደመው አሉ፡፡ ሆዳቸው ተርፏ ተርፏ እያለ፡፡
ማርሽ ቀየረም ፤ ነዳጅ እረገጠም ፤ ውሻውን ግን ሊቀድመው አልቻለም፡፡ ውሻው አቋርጧቸው አለፈ፡፡
"ጭራሽ መንዳትም አቃተህ ፤ ውሻ መቅደም ያቅትህ አሉ፡፡ በፊታቸው ላይ የደም ስራቸው በንዴት እየተወጣጠረ፡፡
"መኪናው ሰርቪስ ከገባ ቆይቷል፡፡ ፍጥነት ጨምሬ ስነዳ እንዳይቆም ስለፈራሁ ነው፡፡ እንጅ ውሻ መቅደም አቅቶኝ አይደለም" ፡፡
የባሰ በጭንቀት ላይ ጭንቀት ሆነባቸው፡፡ መኪናው ከመንገድ ላይ እንዳይቆም ስጋቻ አደረባቸው፡፡ብቻ እንዳያዋርደን የባሰ ለማርፈዱ ሲቆጨን ከመንገድ ላይ ቆሞ፡፡ "የቆጡን አወርድ ብላ የብብቷን ጣለች" እንደ ሚባለው ከሁለት አጉል እንዳንሆን፡፡ እያሉ ከአፋቸው ተናግረው ሳይጨርሱ መኪናው ማዞሪያ ላይ መሪው አልዞር አለ፡፡ መስመር ሳተ፡፡ ሰለሞን ላብ በላብ ሆነ፡፡ ጎትቶ የማስገባት ያህል መልሶ ወደ መስመር አሰገባው፡፡
አቶ ላንቻ ከአሁን አሁን ተገለበጠ እያሉ ሰለሞን መሪው ሲያዞር ያገዙት ይመስል አንገታቸውን አብረው ያዞሩ ነበር፡፡
ከመስመር ሲገባ ትንሽ ትንፏሻቸው መለስ አለ፡፡ በል አሁን ቀስ ብለህ ንዳ የትም ጫካ እንዳታስቀረኝ አሉ ፤ እየፈሩም ቢሆን፡፡
"አሁን እግዚአብሔር ነው ያተረፈን ፡፡ ተገልብጦብኝ ነበር፡፡ እንጃ ብቻ ዛሬ በሰላም የምንገባ አልመስለኝም፡፡ ሆዴ ሁሉ በጣም ፈርቷል ፡፡
በስ መዓብ በል፡፡ ደግሞ ታሟርታለህ እንዴ ? አንዳንዴ ማሟረት ጥሩ አደለም፡፡ አፍ ሊከተል ይችላል አሉ ፤ አቶ ላንቻ፡፡
"አሁን ደግሞ ጭሱ መሽተት ጀምሯል፡፡
"እስኪ አቁመህ ውረድና እየው፡፡ የጭስ መውጫው ታፍኖ ይሆናል፡፡
ሰለሞን ወርዶ አየው፡፡ መኪናው ከመሽተት ውጭ የሚታይ ነገር አላገኘም፡፡ ተመልሶ ከሁለተኛ ማርሽ ወደ ሶስተኛ ማርሽ ቀይሮ ነዳ፡፡
የባሰ የመኪናው ድምፅ ተቀይሮ የመኪና ድምፅ መሆኑ ቀርቶ እንደ ወፍጮ መንኮራኮር ጀመረ፡፡ በስጋቻ አይኖቹ ተርገበገቡ፡፡ ቀኑ ወደ ጨለማ ተቀየረበት፡፡ አንዳንዴ የመኪና መብራት ያበራል፡፡
የመኪና መብራት የምታበራው መንገዱ አልታይ አለህ"? እንዴ አሉ ፤ አቶ ላንቻ፡፡
አንዳንዴ ጨለማ እየመሰለኝ ነው እኮ፡፡ አሁንማ እጄ ሁሉ እየተንቀጠቀጠብኝ ነው፡፡ እስኪ ከእኔ ይሻሉ እንደሆን ይሞክሩት ፡፡
"እኔ ከአንተ እሻላለሁ ብለህ ነው፡፡ ምን አይነት ቀነ ጎደሎ ነው ፤ የገጠመን ዛሬ፡፡ እያሉ የሰለሞን ቦታ ቀይረው መኪናውን ለመንዳት መሪውን ጨበጡ፡፡ የባሰ እጃቸው ተሳሰረ፡፡ ግራና ቀኝ ዋዥቁ፡፡
"ፍሬን ይያዙ ፣ ፍሬን ይያዙ ፣ መስመር ስቷል፡፡ እያለ ጮኸ ሰለሞን፡፡ መኪናው ግን አልቆመም፡፡ እስከ አሁን ታግሸ አገለገልኳችሁ፡፡ የዚህ አለም ኑሮ ይበቃኛል፡፡ ብሎ አራት እግሩን ወደ ላይ ሰቅሎ ከመስመር በታች ወርዶ ተከረበተ፡፡
የፈሩት አልቀረም፡፡ ሰለሞን በደረሰው አደጋ ወዲያውኑ ህይወቱ ሲያልፍ አቶ ላንቻ ከባድ የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸው ህይወታቸው ቢተርፍም ወደ ህክምና ሲሄዱ ጭንቅላታቸው በጣም ተጎድቶ ስለነበር ህክምናም ሳይደርሱ ህይወታቸው በመንገድ ላይ አለፈ፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ZOO አዲሱ ፕሮጀክት... 19 ቀን ብቻ ቀርቶታል ቢያንስ ገባ ብላችሁ እዩት አጭር ግዜ ነው የቀረው..ይመቻቹ
ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ቀነ ጎደሎ
ጨለማ በተቀላቀለበት ሌሊት ተነሱ፡፡ ወደ አዳማ ለመሄድ ተቻኩለዋል፡፡ ከቡቲካቸው አልባሳት እና ሌሎች እቃዎችንም ጫኑ፡፡ እንዳይረፍድባቸው ሹፌሩን ፍጥነት ጨምሮ እንዲነዳ አዘዙት፡፡ ከወትሮው በተለየ መልኩ ደብሯቸዋል፡፡ ሰውነታቸውን ከብዷቸዋል፡፡ ፊታቸውን ጨፍጓቸዋል፡፡ አፋቸውን እሬት እሬት ብሏቸዋል፡፡ ደጋግመው አፋቸውን በባዶው አላመጡት፡፡ ለውጥ ግን አላመጣላቸውም
ለሹፌሩ "ዛሬ ደግሞ ምን እንደሆንኩ እንጃ አፌን እሬት እሬት እያለኝ ነው" አሉት፡፡
"ምነው ቁርስ አልበሉም እንዴ?" ደግሞ ደስተኛ አይመስሉም፡፡ ደህና አይደሉም"? አለ፡፡ ሹፌራቸው ሰለሞን፡፡
"ኧረ ! ደህናነኝ፡፡ ብቻ ውስጤ እርብሽብሽ ብሏል፡፡ ሌሊትም ደግሞ ሲያቃዥኝ ነው ያደረው፡፡ ጥዋትም ቁርስ ወደ አፌ ስል አልዋጥ አለኝ፡፡ ምን እንደሆንኩ ለራሴም ሊገባኝ አልቻለም አሉ ፤ አቶ ላንቻ፡፡
"አስበውት ያላሳኩት ነገር አለ እንዴ"?
"አስቤ ያላሳካሁት ነገር እንኳን ያለ አይመስለኝም፡፡ ምንአልባት ዛሬ ማርፈዴ ብቻ ነው ትንሽ ያበሳጨኝ፡፡ ለምን እንደረፈደብኝም ሳላውቅ ከሩቅ የሚመጣ ደንበኛ ነበረኝ ያሬድ የሚባል፡፡ እንዴው ጠብቆኝ ሲያጣኝ ባልተመለሰ ብቻ እንጅ ቢያድግልኝ እንኳን ከሱቅ የትም ስለማይሄድ አምሽተንም ብንደርስ እናገኘዋለን፡፡ ለማንኛውም ነዳጅ ሰጠት አድርገህ ቶሎ ቶሎ ንዳው ፡፡
"እሽ አሁንም እኮ ፈጥነናል፡፡ ግን እኔም እኮ እጄ ሁሉ ተሳሰረብኝ" አለ ሰለሞን፡፡
ዘ
"ምነው አንተ ደግሞ ምን ሆነህ ነው ? ስትጨፍር እና ስትጠጣ አድረህ ፤ ምን አልባት እንቅልፍ መጥቶብህ እንዳይሆን"?
"እንኳን ስጠጣ ፣ ስጨፍር ላድር ፤ የጨብስም አጥቼ የዘጠኝ ብር አህያ መስየ ነው፡፡ ያደርኩት ፡፡
.አቶ ላንቻ የሰለሞን ፈሊጣዊ ንግግር አሳቃቸው፡፡ የዘጠኝ ብር አህያ ማለት ደግሞ ምን ማለት ነው? መቼም የዛሬ ልጆች የማታመጡት ጉድ የለም ፡፡
በመስኮት አይናቸውን ወርወር አደረጉ፡፡ ከበስተቀኝ በኩል የጋኔል ቁራጭ የሚመስል ጥቁር ውሻ ሊያቋርጣቸው ይሮጣል፡፡ ሰለሞን አፍጥነው ፣ አፍጥነው መኪናውን ፤ ይሔ ውሻ ሳያቋርጠን ፤ እንቅደመው አሉ፡፡ ሆዳቸው ተርፏ ተርፏ እያለ፡፡
ማርሽ ቀየረም ፤ ነዳጅ እረገጠም ፤ ውሻውን ግን ሊቀድመው አልቻለም፡፡ ውሻው አቋርጧቸው አለፈ፡፡
"ጭራሽ መንዳትም አቃተህ ፤ ውሻ መቅደም ያቅትህ አሉ፡፡ በፊታቸው ላይ የደም ስራቸው በንዴት እየተወጣጠረ፡፡
"መኪናው ሰርቪስ ከገባ ቆይቷል፡፡ ፍጥነት ጨምሬ ስነዳ እንዳይቆም ስለፈራሁ ነው፡፡ እንጅ ውሻ መቅደም አቅቶኝ አይደለም" ፡፡
የባሰ በጭንቀት ላይ ጭንቀት ሆነባቸው፡፡ መኪናው ከመንገድ ላይ እንዳይቆም ስጋቻ አደረባቸው፡፡ብቻ እንዳያዋርደን የባሰ ለማርፈዱ ሲቆጨን ከመንገድ ላይ ቆሞ፡፡ "የቆጡን አወርድ ብላ የብብቷን ጣለች" እንደ ሚባለው ከሁለት አጉል እንዳንሆን፡፡ እያሉ ከአፋቸው ተናግረው ሳይጨርሱ መኪናው ማዞሪያ ላይ መሪው አልዞር አለ፡፡ መስመር ሳተ፡፡ ሰለሞን ላብ በላብ ሆነ፡፡ ጎትቶ የማስገባት ያህል መልሶ ወደ መስመር አሰገባው፡፡
አቶ ላንቻ ከአሁን አሁን ተገለበጠ እያሉ ሰለሞን መሪው ሲያዞር ያገዙት ይመስል አንገታቸውን አብረው ያዞሩ ነበር፡፡
ከመስመር ሲገባ ትንሽ ትንፏሻቸው መለስ አለ፡፡ በል አሁን ቀስ ብለህ ንዳ የትም ጫካ እንዳታስቀረኝ አሉ ፤ እየፈሩም ቢሆን፡፡
"አሁን እግዚአብሔር ነው ያተረፈን ፡፡ ተገልብጦብኝ ነበር፡፡ እንጃ ብቻ ዛሬ በሰላም የምንገባ አልመስለኝም፡፡ ሆዴ ሁሉ በጣም ፈርቷል ፡፡
በስ መዓብ በል፡፡ ደግሞ ታሟርታለህ እንዴ ? አንዳንዴ ማሟረት ጥሩ አደለም፡፡ አፍ ሊከተል ይችላል አሉ ፤ አቶ ላንቻ፡፡
"አሁን ደግሞ ጭሱ መሽተት ጀምሯል፡፡
"እስኪ አቁመህ ውረድና እየው፡፡ የጭስ መውጫው ታፍኖ ይሆናል፡፡
ሰለሞን ወርዶ አየው፡፡ መኪናው ከመሽተት ውጭ የሚታይ ነገር አላገኘም፡፡ ተመልሶ ከሁለተኛ ማርሽ ወደ ሶስተኛ ማርሽ ቀይሮ ነዳ፡፡
የባሰ የመኪናው ድምፅ ተቀይሮ የመኪና ድምፅ መሆኑ ቀርቶ እንደ ወፍጮ መንኮራኮር ጀመረ፡፡ በስጋቻ አይኖቹ ተርገበገቡ፡፡ ቀኑ ወደ ጨለማ ተቀየረበት፡፡ አንዳንዴ የመኪና መብራት ያበራል፡፡
የመኪና መብራት የምታበራው መንገዱ አልታይ አለህ"? እንዴ አሉ ፤ አቶ ላንቻ፡፡
አንዳንዴ ጨለማ እየመሰለኝ ነው እኮ፡፡ አሁንማ እጄ ሁሉ እየተንቀጠቀጠብኝ ነው፡፡ እስኪ ከእኔ ይሻሉ እንደሆን ይሞክሩት ፡፡
"እኔ ከአንተ እሻላለሁ ብለህ ነው፡፡ ምን አይነት ቀነ ጎደሎ ነው ፤ የገጠመን ዛሬ፡፡ እያሉ የሰለሞን ቦታ ቀይረው መኪናውን ለመንዳት መሪውን ጨበጡ፡፡ የባሰ እጃቸው ተሳሰረ፡፡ ግራና ቀኝ ዋዥቁ፡፡
"ፍሬን ይያዙ ፣ ፍሬን ይያዙ ፣ መስመር ስቷል፡፡ እያለ ጮኸ ሰለሞን፡፡ መኪናው ግን አልቆመም፡፡ እስከ አሁን ታግሸ አገለገልኳችሁ፡፡ የዚህ አለም ኑሮ ይበቃኛል፡፡ ብሎ አራት እግሩን ወደ ላይ ሰቅሎ ከመስመር በታች ወርዶ ተከረበተ፡፡
የፈሩት አልቀረም፡፡ ሰለሞን በደረሰው አደጋ ወዲያውኑ ህይወቱ ሲያልፍ አቶ ላንቻ ከባድ የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸው ህይወታቸው ቢተርፍም ወደ ህክምና ሲሄዱ ጭንቅላታቸው በጣም ተጎድቶ ስለነበር ህክምናም ሳይደርሱ ህይወታቸው በመንገድ ላይ አለፈ፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ZOO አዲሱ ፕሮጀክት... 19 ቀን ብቻ ቀርቶታል ቢያንስ ገባ ብላችሁ እዩት አጭር ግዜ ነው የቀረው..ይመቻቹ
ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
YouTube
አትሮኖስ_ Tube
Share your videos with friends, family, and the world
👍63😢18❤4👎1
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
አንድ አይጠጣም
የወጣት ሰውነቱ ፣ ለግላጋ ቁመናው ፣ ተቀያይሯል፡፡ ከአሁን በፊት ያልነበረውን ፂም አውጥቷል፡፡ ታዲያ በጉንጮቹ ላይ ግራና ቀኝ የወረደው አሪዝ መሳይ ፂሙ ጳጳስ አስመስሎታል፡፡ እንኳን ለማያቀው ለሚያውቀውም ሰው ተመስገንን መለየት ያስቸግር ነበር፡፡
ምግብ አዝዘው እየበሉ ነው፡፡ መብላቱን ተወት አድርጎ በሆቴሉ ዲም ላይት ይገረማል፡፡
"ከተሜ ማለት እንደ ዚህ ነው እንዴ"? አለ ተመስን፡፡
የተለየ ነገር አየህ"? አለው ያሬድ፡፡
"እኛም አገር ነጫጭ ሰው አስተናጋጅ ሆኖ ሳይ ነው"፡፡
"ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ………...ትገርማለህ የአገርህን ሰው እንኳን መለየት አቃተህ፡፡ እነዚህ እኮ የእኛ አገር ሰዎች ናቸው፡፡ ቅባት ስለተቀባቡ ነው፡፡ ነጭ የመሰሉህ ብሎት ለምግብ ማወራረጃ ቢራ ለማዘዝ ከተቀመጠበት ወንበር ላይ አንገቱን ዞር አደረገ፡፡ ከአንድ መልከ መልካም ህንዳዊ ከምትመስል ቆንጆ ሴት ልጅ ጋር አይኖቹ ተጋጨ፡፡
"ማነሽ እህት ቢራ ታዘዥን" አላት፡፡
"እኔ እኮ ቢራ ጠጥቼ አላውቅም፡፡ ያሰክረኛል ፣ አልጠጣም፡፡ ለራስህ እዘዝ ፤ ለእኔ ጠጅ የለመድሁት ይሻለኛል፡፡ አለ ፤ ተመስገን፡፡
"አይ! ተመስገን ትገርማለህ ፤ እኔ እኮ ብዙ የምታቅ ትመስለኝ ነበር፡፡ ለካስ ምንም አታውቅም፡፡ ጠጅ እኮ እንደዚህ ያለ ሆቴል ውስጥ አይሸጥም፡፡ አለማወቅህ ነው እንጅ ከጠጁ ቢራው ነው የሚሻለው፡፡ ባይሆን አንድ ጠጥተህ ትተወዋለህ፡፡ ብሎት ቢራ እንዲጠጣ አሳመነው፡፡
"ምን አይነት ቢራ ልታዘዛችሁ አለች፡፡ የተጠራችው መልከ መልካም የህንድ ቆንጆ የምትመስል አስተናጋጅ፡፡
"በእናንተ አገር መጀመሪያ ሰላምታ አይፈቀድም እንዴ"? አላት ያሬድ፡፡
"ኧረ ! ይባላል፡፡ እሽ ይቅርታ ብላ የእጅ ሰላምታ ሰጠቻቸው፡፡ ለዛ ያለው ፈገግታዋ በታከለበት፡፡
"ስምሽ ማን ይባላል"? አላት ያሬድ፡፡ እጁን ከእጇ ሳያላቅቅ፡፡
"የሽሃረግ እባላለሁ" ፡፡
"እሽ አመሰግናለሁ ብሏት የራሱን ስም ሳይነግራት ሁለት ሐረር ቢራ አምጭልን አላት፡፡
የሽሃረግ አስተናጋጅ አይደለችም፡፡ አስተናጋጅዋ ወደ ሱቅ ወታለች፡፡ እስከ ምትመለስ ግን ወደ ሆቴሉ የሚገቡትን ተስተናጋጆች ታስተናግዳለች፡፡
ታዲያ የሆቴሉ አረንጓዴ ፣ ቢጫ ፣ ቀይና ሐምራዊ የተቀላቀለ በሚመስለው ዲም ላይት ውስጥ ሽር ሽር እያለች ስታስተናግድ አትኩሮ ለተመለከታት ፤ የቀሚስ አለባበሷ ፤ ኢትዮጵያዊነቷን ያለቀቀ ሆኖ በሰው እጅ የተሰራ ሳይሆን ከለግላጋ ሰውነቷ ጋር አምላክ አብሮ የፈጠረው ይመስል ነበር፡፡
ተመስገን የሽሃረግ እጁን ከጨበጠችው በኋላ፤ ከባንኮኒው ስትወጣና ስትገባ አብሯት በአይኖቹ ይመላለሳል፡፡
"ሊያመኝ ነው መሰለኝ"? ፡፡
"ጠጣበት ይለቅሃል፡፡ ዘና በል ደግሞ እንደ ልጅ አገረድ አትሽኮርመም"፡፡ "ምነው ደግሞ አይንህን በልጅቷ ላይ የምታንጃብበው"? አለው ያሬድ፡፡
"ኧረ ! አላንጃበብኩም፡፡ ግን ጓደኛዋ የወንድ ሱሪ ነው ያጠለቀችው፡፡ እሷ ደግሞ እንዴው ሳያት አለባበሷ አገረኛውን አለቀቀም፡፡ ታምራለች" ፡፡
"የቤት ልጅ ሆና ይሆናል፡፡ አለ ፤ ያሬድ፡፡
ያሬድ የአልባሳት ንግድ ከጀመረ ብቻ ሳይሆን በፊትም ከእናት አባቱ ቤት እያለ ስለከተማ ሴቶች አንዳንድ ነገሮችን ያውቃል፡፡ ለከተማ አዲስ አይደለም፡፡
ተመስገን አንድ ቢራ ያሰክረኛል ብሎ እየፈራ ቢጠጣውም አንድ ቢራ ግን አላሰከረውም፡፡ ለመድገም ፈልጓል፡፡
"ለካ ቢራ እንደዚህ ይጣፍጣል እንዴ"? አለ፡፡ ከጠርሙሱ ውስጥ የቀረውን እየጨለጠ፡፡
ቢራ እንግዴህ አንድ አይጠጣም፡፡ ከሰከርክም ከአሁን በኋላ ፤ ስለማንቀሳቀስ መቼም መኝታችን ድረስ ገብተን መተኛት አያቅተንም፡፡ ብሎት ቢራ ሊደግሙ የሽሃረግን ጠራት፡፡
የሽሃረግ ደግሞ አስተናጋጇን መቅደስን ጠርታ እዛጋ እየጠሩሽ ነው፡፡ ታዘዣቸው አለች፡፡
መቅደስ "ቢራ ይደገም"? አለች፡፡
ድገሚን ሳይላት "የሽሃረግ አታስተናግድም እንዴ"? አላት ያሬድ፡፡
"እሷ ብዙም አታስተናግድም፡፡ ሂሳብ ነው የምትቀበለው፡፡ የማስተናግደው እኔ ነኝ ፡፡
"እሽ ሁለት ሐረር ድገሚን" ፡፡
ተመስገን የጥላሁን ገሰሰ "ያቺ ቆንጆ ጥርሰ በረዶናት ፤ ውብ አይናማ ናት፡፡ የሚለውን ቀዝቀዝ ያለ ዜማ ልቡን ወሰድ አድርጎታል፡፡ አይኖቹን በየሽሃረግ ላይ ማንከራተቱን አላቋረጠም፡
ድገሚን ሳይላት "የሽሃረግ አታስተናግድም እንዴ"? አላት ያሬድ፡፡
"አሁን ከቅድሙ ድብርቱ ለቀቅ አላደረገህም ?
ካለቀቀህ ቢራውን ደጋግምበት፡፡ አልያም ሐገረኛ ሙዚቃ አስከፍተን እንጨፍራለን" አለ ፤ ያሬድ፡፡ የያዘውን ቢራ ጎንጨት እያደረገ፡፡ አንዳንድ ቢራ አልበቃቸውም፡፡ አራት አራቱን ቆነደዱት፡፡ ተመስገን ሞቅ እያለው መጣ፡፡
ያሬድ አገረኛ ሙዚቃ የለም እንዴ? አለ ፤ ለመቅደስ፡፡
"ልቀይርላችሁ"? ፡፡
"አዎ፤ በዚያውም ቢራ ይዘሽልን ነይ" ፡፡
አገረኛው ሙዚቃ ተከፈተ፡፡ ተነስተው ግን አልጨፈሩም፡፡ በተቀመጡበት አንገታቸውን ያወዛውዛሉ፡፡ የጠጣው ሐረር ቢራ መንፈሱን ሰረቅ አድርጎታል፡፡"ያች ኮረዳ ዝምብላ ታየኛለች" አለ ተመስገን፡፡ የራሱ አትኩሮ ማየት ሳይታወቀው፡፡
"የቷ ኮረዳ"? ፡፡
"ያቺ እዛ ውስጥ ተቀምጣ አንገቷን ብቻ የምትታየው፡፡ ስሟ ማን ነበር ያለችው"?
"የሽሃረግን ነው የምትለው"?፡፡
"አዎ፤ ትክክል ነህ፡፡ ቅድም እኮ ስትጠራት ሰምቼ አሁን አፌ ላይ ጠፍቶብኝ ነው፡፡
"የፈለግሃት ትመስላለህ፡፡ ለማንኛውም የሽሃረግን ለማግኘት መቅደስን መጥራት አለብን፡፡ በእጁ አጨብጭቦ መቅደስን ጠራት፡፡
"ልድገማችሁ" ብላ ጠየቀች መቅደስ፡፡ ቢራ ፈልገው መስሏት፡፡
"ቢራ እንኳን አልጨረስንም፡፡ ለየሽሃረግ አንድ ቢራ
ስጫት" አለ ፤ ያሬድ፡፡
ቢራ ጠጥታ አታውቅም፡፡ ለስላሳ ከሆነ ነው እንጅ ፡፡
"እሽ ፤ ስጫት" ፡:
መቅደስ የታዘዘችውን ለስላሳ ከፊሪጅ አውጥታ ሰጠቻት፡፡
ማነው ያዘዘሽ ; አለቻት የሽሃረግ?፡፡
"እዛጋ የተቀመጡት ሁለት ሰዎች ናቸው የጋበዙሽ፡፡ ብላ እነ ያሬድን በእጇ አመለከተቻት፡፡ ደግሞ ስምሽን ያውቁታል፡፡ ከአሁን በፊት ትተዋወቃላችሁ እንዴ?
"ኧረ ! ካለ ዛሬ አላየኋቸውም፡፡ ቅድም ነው ሱቅ ሄደሽ ሳስተናግዳቸው ስምሽ ማነው ሲሉኝ የነገርኳቸው" አለች፡፡ በዲም ላይቱ ፈገግታ ተመስገንን በስርቆት እየተመለከተች፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
አንድ አይጠጣም
የወጣት ሰውነቱ ፣ ለግላጋ ቁመናው ፣ ተቀያይሯል፡፡ ከአሁን በፊት ያልነበረውን ፂም አውጥቷል፡፡ ታዲያ በጉንጮቹ ላይ ግራና ቀኝ የወረደው አሪዝ መሳይ ፂሙ ጳጳስ አስመስሎታል፡፡ እንኳን ለማያቀው ለሚያውቀውም ሰው ተመስገንን መለየት ያስቸግር ነበር፡፡
ምግብ አዝዘው እየበሉ ነው፡፡ መብላቱን ተወት አድርጎ በሆቴሉ ዲም ላይት ይገረማል፡፡
"ከተሜ ማለት እንደ ዚህ ነው እንዴ"? አለ ተመስን፡፡
የተለየ ነገር አየህ"? አለው ያሬድ፡፡
"እኛም አገር ነጫጭ ሰው አስተናጋጅ ሆኖ ሳይ ነው"፡፡
"ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ………...ትገርማለህ የአገርህን ሰው እንኳን መለየት አቃተህ፡፡ እነዚህ እኮ የእኛ አገር ሰዎች ናቸው፡፡ ቅባት ስለተቀባቡ ነው፡፡ ነጭ የመሰሉህ ብሎት ለምግብ ማወራረጃ ቢራ ለማዘዝ ከተቀመጠበት ወንበር ላይ አንገቱን ዞር አደረገ፡፡ ከአንድ መልከ መልካም ህንዳዊ ከምትመስል ቆንጆ ሴት ልጅ ጋር አይኖቹ ተጋጨ፡፡
"ማነሽ እህት ቢራ ታዘዥን" አላት፡፡
"እኔ እኮ ቢራ ጠጥቼ አላውቅም፡፡ ያሰክረኛል ፣ አልጠጣም፡፡ ለራስህ እዘዝ ፤ ለእኔ ጠጅ የለመድሁት ይሻለኛል፡፡ አለ ፤ ተመስገን፡፡
"አይ! ተመስገን ትገርማለህ ፤ እኔ እኮ ብዙ የምታቅ ትመስለኝ ነበር፡፡ ለካስ ምንም አታውቅም፡፡ ጠጅ እኮ እንደዚህ ያለ ሆቴል ውስጥ አይሸጥም፡፡ አለማወቅህ ነው እንጅ ከጠጁ ቢራው ነው የሚሻለው፡፡ ባይሆን አንድ ጠጥተህ ትተወዋለህ፡፡ ብሎት ቢራ እንዲጠጣ አሳመነው፡፡
"ምን አይነት ቢራ ልታዘዛችሁ አለች፡፡ የተጠራችው መልከ መልካም የህንድ ቆንጆ የምትመስል አስተናጋጅ፡፡
"በእናንተ አገር መጀመሪያ ሰላምታ አይፈቀድም እንዴ"? አላት ያሬድ፡፡
"ኧረ ! ይባላል፡፡ እሽ ይቅርታ ብላ የእጅ ሰላምታ ሰጠቻቸው፡፡ ለዛ ያለው ፈገግታዋ በታከለበት፡፡
"ስምሽ ማን ይባላል"? አላት ያሬድ፡፡ እጁን ከእጇ ሳያላቅቅ፡፡
"የሽሃረግ እባላለሁ" ፡፡
"እሽ አመሰግናለሁ ብሏት የራሱን ስም ሳይነግራት ሁለት ሐረር ቢራ አምጭልን አላት፡፡
የሽሃረግ አስተናጋጅ አይደለችም፡፡ አስተናጋጅዋ ወደ ሱቅ ወታለች፡፡ እስከ ምትመለስ ግን ወደ ሆቴሉ የሚገቡትን ተስተናጋጆች ታስተናግዳለች፡፡
ታዲያ የሆቴሉ አረንጓዴ ፣ ቢጫ ፣ ቀይና ሐምራዊ የተቀላቀለ በሚመስለው ዲም ላይት ውስጥ ሽር ሽር እያለች ስታስተናግድ አትኩሮ ለተመለከታት ፤ የቀሚስ አለባበሷ ፤ ኢትዮጵያዊነቷን ያለቀቀ ሆኖ በሰው እጅ የተሰራ ሳይሆን ከለግላጋ ሰውነቷ ጋር አምላክ አብሮ የፈጠረው ይመስል ነበር፡፡
ተመስገን የሽሃረግ እጁን ከጨበጠችው በኋላ፤ ከባንኮኒው ስትወጣና ስትገባ አብሯት በአይኖቹ ይመላለሳል፡፡
"ሊያመኝ ነው መሰለኝ"? ፡፡
"ጠጣበት ይለቅሃል፡፡ ዘና በል ደግሞ እንደ ልጅ አገረድ አትሽኮርመም"፡፡ "ምነው ደግሞ አይንህን በልጅቷ ላይ የምታንጃብበው"? አለው ያሬድ፡፡
"ኧረ ! አላንጃበብኩም፡፡ ግን ጓደኛዋ የወንድ ሱሪ ነው ያጠለቀችው፡፡ እሷ ደግሞ እንዴው ሳያት አለባበሷ አገረኛውን አለቀቀም፡፡ ታምራለች" ፡፡
"የቤት ልጅ ሆና ይሆናል፡፡ አለ ፤ ያሬድ፡፡
ያሬድ የአልባሳት ንግድ ከጀመረ ብቻ ሳይሆን በፊትም ከእናት አባቱ ቤት እያለ ስለከተማ ሴቶች አንዳንድ ነገሮችን ያውቃል፡፡ ለከተማ አዲስ አይደለም፡፡
ተመስገን አንድ ቢራ ያሰክረኛል ብሎ እየፈራ ቢጠጣውም አንድ ቢራ ግን አላሰከረውም፡፡ ለመድገም ፈልጓል፡፡
"ለካ ቢራ እንደዚህ ይጣፍጣል እንዴ"? አለ፡፡ ከጠርሙሱ ውስጥ የቀረውን እየጨለጠ፡፡
ቢራ እንግዴህ አንድ አይጠጣም፡፡ ከሰከርክም ከአሁን በኋላ ፤ ስለማንቀሳቀስ መቼም መኝታችን ድረስ ገብተን መተኛት አያቅተንም፡፡ ብሎት ቢራ ሊደግሙ የሽሃረግን ጠራት፡፡
የሽሃረግ ደግሞ አስተናጋጇን መቅደስን ጠርታ እዛጋ እየጠሩሽ ነው፡፡ ታዘዣቸው አለች፡፡
መቅደስ "ቢራ ይደገም"? አለች፡፡
ድገሚን ሳይላት "የሽሃረግ አታስተናግድም እንዴ"? አላት ያሬድ፡፡
"እሷ ብዙም አታስተናግድም፡፡ ሂሳብ ነው የምትቀበለው፡፡ የማስተናግደው እኔ ነኝ ፡፡
"እሽ ሁለት ሐረር ድገሚን" ፡፡
ተመስገን የጥላሁን ገሰሰ "ያቺ ቆንጆ ጥርሰ በረዶናት ፤ ውብ አይናማ ናት፡፡ የሚለውን ቀዝቀዝ ያለ ዜማ ልቡን ወሰድ አድርጎታል፡፡ አይኖቹን በየሽሃረግ ላይ ማንከራተቱን አላቋረጠም፡
ድገሚን ሳይላት "የሽሃረግ አታስተናግድም እንዴ"? አላት ያሬድ፡፡
"አሁን ከቅድሙ ድብርቱ ለቀቅ አላደረገህም ?
ካለቀቀህ ቢራውን ደጋግምበት፡፡ አልያም ሐገረኛ ሙዚቃ አስከፍተን እንጨፍራለን" አለ ፤ ያሬድ፡፡ የያዘውን ቢራ ጎንጨት እያደረገ፡፡ አንዳንድ ቢራ አልበቃቸውም፡፡ አራት አራቱን ቆነደዱት፡፡ ተመስገን ሞቅ እያለው መጣ፡፡
ያሬድ አገረኛ ሙዚቃ የለም እንዴ? አለ ፤ ለመቅደስ፡፡
"ልቀይርላችሁ"? ፡፡
"አዎ፤ በዚያውም ቢራ ይዘሽልን ነይ" ፡፡
አገረኛው ሙዚቃ ተከፈተ፡፡ ተነስተው ግን አልጨፈሩም፡፡ በተቀመጡበት አንገታቸውን ያወዛውዛሉ፡፡ የጠጣው ሐረር ቢራ መንፈሱን ሰረቅ አድርጎታል፡፡"ያች ኮረዳ ዝምብላ ታየኛለች" አለ ተመስገን፡፡ የራሱ አትኩሮ ማየት ሳይታወቀው፡፡
"የቷ ኮረዳ"? ፡፡
"ያቺ እዛ ውስጥ ተቀምጣ አንገቷን ብቻ የምትታየው፡፡ ስሟ ማን ነበር ያለችው"?
"የሽሃረግን ነው የምትለው"?፡፡
"አዎ፤ ትክክል ነህ፡፡ ቅድም እኮ ስትጠራት ሰምቼ አሁን አፌ ላይ ጠፍቶብኝ ነው፡፡
"የፈለግሃት ትመስላለህ፡፡ ለማንኛውም የሽሃረግን ለማግኘት መቅደስን መጥራት አለብን፡፡ በእጁ አጨብጭቦ መቅደስን ጠራት፡፡
"ልድገማችሁ" ብላ ጠየቀች መቅደስ፡፡ ቢራ ፈልገው መስሏት፡፡
"ቢራ እንኳን አልጨረስንም፡፡ ለየሽሃረግ አንድ ቢራ
ስጫት" አለ ፤ ያሬድ፡፡
ቢራ ጠጥታ አታውቅም፡፡ ለስላሳ ከሆነ ነው እንጅ ፡፡
"እሽ ፤ ስጫት" ፡:
መቅደስ የታዘዘችውን ለስላሳ ከፊሪጅ አውጥታ ሰጠቻት፡፡
ማነው ያዘዘሽ ; አለቻት የሽሃረግ?፡፡
"እዛጋ የተቀመጡት ሁለት ሰዎች ናቸው የጋበዙሽ፡፡ ብላ እነ ያሬድን በእጇ አመለከተቻት፡፡ ደግሞ ስምሽን ያውቁታል፡፡ ከአሁን በፊት ትተዋወቃላችሁ እንዴ?
"ኧረ ! ካለ ዛሬ አላየኋቸውም፡፡ ቅድም ነው ሱቅ ሄደሽ ሳስተናግዳቸው ስምሽ ማነው ሲሉኝ የነገርኳቸው" አለች፡፡ በዲም ላይቱ ፈገግታ ተመስገንን በስርቆት እየተመለከተች፡፡
👍47❤9