#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_ዘሪሁን_ገመቹ
ራሄል ከሁለት ረዳቷቾ ከሮቤልና ሎዛ ጋር ስብሰባ ላይ እያለች ነበር ስልኳ የጠራው…ንግግሯን ሳታቋርጥ ስልኩን አነሳችና አየችው፤ አባቷ አቶ ቸርነት ናቸው የደወሉላት ፡፡ስብሰባ ላይ ነኝ ብላ ልትዘጋባቸው አልፈለገችም…አባቷ በጣም አስፈላጊ ጉዳይ ባይሆን ኖሮ በዚህ ሰዓት አይደውሉላትም ነበር፡፡
‹‹አንዴ ይቅርታ… ይሄንን ስልክ ማንሳት አለብኝ››ብላ ከተቀመጠችበት ግዙፍ ተሸከርካሪ ወንበር ተነሳችና ቢሮውን ለቃ ወጣችና….ከዛ ስልኩን አነሳችው፡፡
‹‹ሄሎ አባዬ ..እንዴት ነህ?››
‹‹ሰላም ነኝ ልጄ››
ድምፃቸው ተጎተተባት‹‹ምነው አባዬ? ችግር አለ እንዴ?››
‹‹አይ ልጄ ሁሉ ነገር ሰላም ነው…እኔ እና እናትሽ አንድ ነገር ልናማክርሽ ነበር››
‹‹ምንድነው?››
‹‹ይሄውልሽ ልጄ ምን መሰለሽ..እኔና እናትሽ ጡረታ ወጥተን ቤት መዋል ከጀመርን በኃላ ህይወታችንን ታውቂያለሽ…ብቸኞች ነን..አንቺም አሻፈረኝ ብለሽ በራስሽ ቤት ነው የምትኖሪው…፡፡››
ራሄል በምትሰማው ነገር ፊቷን አጨማደደች….የገመተችው አብረሽን ኑሪ የሚለውን የዘወትር ጥያቄያቸውን ደግመው ሊያነሱባት ነበር የመሰላት፡፡
አባቷ ትንፋሽ ወሰዱና ንግግራቸውን ቀጠሉ‹‹እህት እንዲኖርሽ ፈልገን ነበር››
ደነገጠች‹‹እህት!!››
‹‹አዎ ቅር ማይልሽ ከሆነ እኔ እና እናትሽ እህት እንዲኖርሽ ፈልገናል…የመጨረሻ ውሳኔ ላይ ከመድረሳችን በፊት ያንቺን አስተያየት ማወቅ ስለፈለግን ነው የደወልንልሽ፡፡››
‹‹ብዥ አለባት…እናቴ በሰባ አመቷ አረገዘች እንዴ?››ስትል በውስጧ እራሷ ጠየቀች፡፡‹‹አባቴ የአብረሀምን አይነት የዋህነት ስላለው እግዜር በዚህ አድሜዋ የማዬን ማህፀን ቢከፍት አይገርመኝም››ስትል በራሷ ሀሳብ ሳቀችና ትኩረቷን ወደስልኩ መለሰች፡፡
‹‹አባዬ አልገባኝም..እንዴት ነው እህት ሊኖረኝ የሚችለው?››
አንድ የሁለት አመት ቆንጅዬ ሴት ልጅ በጉዲፈቻ ልንወስድ ነው….››
‹‹በጉዲፈቻ…በጣም ደስ ይላል….ጥሩ ውሳኔ ነው የወሰናችሁት..››
ሀሳባቸውን ለመደገፍ ጥቂት ማሰብ እንኳን አላስፈለጋትም…የሁለት አመት ጣፋጭ ልጅ እዛ ግዙፍ ቪላ ቤት ውስጥ ስትሯሯጥ…አንዴ አባቷ ላይ አንዴ ደግሞ እናቷ ላይ እየተንጠለጠች ስታስቃቸውና ሰታዝናናቸው፣እነሱም ሲያሞላቅቋት…እሷን መሀላቸው አድርገው ግራና ቀኝ እጇን ይዘው ወደቤተክርስቲያን ይዘዋት ሲሄዱ .... በአይነ ህሊናዋ ታያትና በደስታ ተፍለቀለቀች፡፡
‹‹ልጄ አሁን እሷን ልናይ ሆስፒታል ነው ያለነው ..ከቻልሽ ጋንዲ ነን …ብትመጪ ደስ ይለኛል፡፡››
መልሶ መደነጋገር ውስጥ ገባች‹‹ሆስፒታል…ምን ትሰራለች?››
‹‹ትንሽ አሟታል…ከቻልሽ ነይ፡፡››ደገሙላት፡፡
‹‹በቃ መጣው››……ስልኩን ዘጋችና ወደቢሮዋ ተመልሳ ለረዳቶቾ ወደስራ እንዲመለሱ ትዕዛዝ ሰጥታ ቦርሳውን አንጠልጥላ ወጣችና ቀጥታ ከፓርክ መኪናዋን በማንቀሳቀስ ስለአዲሷ እጩ እህቷ ምን እንደምትመስልና…ምኗን ታማ ሆስፒታል ልትገባ እንደቻለች እያብሰለሰለች ወደጋንዲ ሆስፒታል ነዳችው፡፡
ደርሳ ወደውስጥ ስትገባ ሰውነቷ መንቀጥቀጥ ጀመረ…ይሄ የተለመደ ስሜቷ ነው…ሆሲፒታል ሂጂ ከሚሏት ጦርነት ዝመቺ ብትባል ትመርጣለች…እንደምንም ግን ወደውስጥ ዘለቀች… አባቷን ደውላ አገኘችው…እጇን ይዞ እየመራ የተባለቸው ህፃን ወደተኛችበት ክፍል ይዟት ገባ፡፡ክፍሉ ውስጥ ከህፃኗ ጋር የገዛ እናቷ ብቻ ነች ያለችው፡፡ ከበራፉ አንድ እርምጃ ወደውስጥ ተራምዳ እንደቆመች ደንዝዛ ቀረች …ከዛ ማለፍ አልቻለችም፡፡
ፍፅም የሚባል ድንዛዜ ውስጥ ነው የገባችው…ልጅቷ ቢያንስ ከሶስት ማሽን ጋር በቱቦ ተያይዛለች…መልኳ ውብ ፀጉሯ ግንቧሯ ላይ ድፍት ያለ አጎጊ ብትሆንም ስልምልም ብላ እራሷን ስታ ተዘርራለች..እንደውም ነፍሷ ውስጧ እንዳለ እርግጠኛ መሆን አልቻለችም….
በቃ ውስጧ ግልብጥብጥ ነው ያለባት…ከአመታት በፊት ምትወደውና ልታገባው ስታልመው የነበረው እጮኛዋ ኪሩቤል እንዲህ እንደህፃኗ እራሱ ስቶና ዝርግትግት ብሎ በማሽን እገዛ ለመተንፈስ ሲያጣጥር የነበረው ትዝታ መጣባትና እራሷን ልትስት ተንገዳገደች..አጠገቧ ያለው አባቷ ፈጠን ብሎ ደገፋት…እናቷ በድንጋጤ ከተቀመጠችበት ተነሳችና ስሯ ደረሰች፡፡
‹‹ምነው ልጄ..አመመሽ እንዴ?››ሁለቱም ተቀባብለው ጠየቋት፡፡
‹‹አይ ደህና ነኝ …የመድሀኒት ሽታና የህክምና ማሽኖቹ ድምፅ ነው የረበሸኝ››
‹‹ቸሬ አንተ እኮ ነህ..እሷ ሆስፒታል እንዴት እንደምትጠላና እንደሚያማት እያወቅክ ነይ ያልካት፡፡››
‹‹እውነትሽን ነው አጥፍቻለው….በቃ ልጄ ነይ…ይሄን ያህል ካየሻት ይበቃሻል….ብለው እየጎተቱ ወደውጭ ወሰዷት…መኪናዋ ድረስ አደረሷት፡፡‹‹እርግጠኛ ነሽ ሰላም ነሽ…?መኪና መንዳት ትችያለሽ››
‹‹አታስብ አባዬ..ሰላም ነኝ..በቃ ተመለስ››
መኪና ውስጥ ገባታ ስትንቀሳቅስ አባትዬው ወደውስጥ ተመለሱ፡፡ቀጥታ ወደቤቷ ነው የሄደችው፡፡የልጅቷ ምስል ከአእምሮዋ ሊወጣ አልቻለም….ወላጆቾ ምን አስበው ያቺን በህይወት እና በሞት መካከል ባለች ቀጭን ክር ተንጠልጥላ ያለችን ልጅ በማደጎ ለመውሰድ እንዳሰቡ ሊገባት አልቻሉም…እንዴት አድርገው ሊንከባከቧት ነው…?ከለመዷትና ከወደዷት በኃላ ብትሞትባቸውስ…..?የሚወዱትን ሰው በሞት መነጠቅ እንዴት ልብን እንደሚሰብር እና ተስፋን እንደሚያከስም በራሷ ታውቀዋለች…እና በእሷ የደረሰ አይነት ሀዘን በዚህ እድሜያቸው በወላጆቾ እንዲድርስ አትፈልግም…፡፡
‹‹ግን ምን ማድረግ እችላለው?››ስትል እራሷን ጠየቀች፡፡እንዲሁ ስትብሰለሰል አደረች…ሳምንት ሙሉ አሰበችበት..አንድ ውሳኔ ወስና ለወላጆቾ ምንም ነገር ማለት ሳትችል…ወላጆቹ ህጋዊ የአሳዳጊነት ፕሮሰሱን ጨርሰው ልጅቷን ወደቤታቸው እንደወሰዱ ሰማች፡፡በቃ ከዛ በጊዜ ሂደት የሚሆነውን ጠብቃ ለመመልከት ወሰነችና ወደወላጇቾ ቤት ሄዳ አዲሷን እህቷን አየቻት…ምንም እንኳን ከዛ ሁሉ ማሽን ነፃ ሆና ብታያትም..አሁንም ግን በጣም ደካማ እና የሰለለ ሰውነት ያለት ሆና ነው ያገኘቻት፡፡ግን ደግሞ በዛው ልክ አሳዛኝና ተወዳጅ ልጅ መሆኗን መካድ አልቻለችም፡፡
============
ራሄል ከረዳቷ ጋር እያወራች ነው፡፡
‹‹ሮቤል ወ.ሮ ላምሮት ልገሳዋን ለእኛ ፋውንዴሽን እንድታደርግ አሁን በስልክ አናግሬታለው፡፡እሷን ማሳመን ከቻልኩ እና ውሳኔዋ ለእኛ ለመለገስ ከሆነ ለፋውንዴሽናችን ትልቅ ስኬት ነው››
ራሄል ወረቀቶቿን ወደ ቦርሳዋ አስገባች፣ አንድ አይኗ በእንጨት በተሸፈነው የቢሮዋ ግድግዳ ላይ በተሰቀለው ሰዓት ላይ ተሰክቶ ነበር።
‹‹ ለማውራት ጊዜ የለኝም። በሃያ ደቂቃ ውስጥ በወላጆቼ መኖሪያ ቤት በተዘጋጀው የምሳ ግብዣ ላይ መገኘት አለብኝ ››አለች፡፡
ረዳቷ ማንኛውንም አይነት ቅሬታ ከማንሳቱ በፊት አቋረጠችውና ‹‹ እንደገና ሴትዬዋ ከደወለች ብቻ አሳውቀኝ።››አለችው፡፡
ስልኳን ዘጋችና ሞባይሏን ቦርሳዋ ውስጥ ለትንሿ እህቷ ጸጋ ከገዛችው ትንሽ ስጦታ ጋር አስቀመጠችው፣ ፀጋ ወላጇቾ ሊያሳድጓት በቅርብ የተረከቧት እህቷ ነች፡፡ ራሄል ወደ መኪና ማቆሚያ ጋራዥ በፍጥነት በምትወርድበት ጊዜ የኖብል ፋውንዴሽን ቢሮዎችና ኮሪደሮች በፀጥታ ተውጠው ነበር።
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_ዘሪሁን_ገመቹ
ራሄል ከሁለት ረዳቷቾ ከሮቤልና ሎዛ ጋር ስብሰባ ላይ እያለች ነበር ስልኳ የጠራው…ንግግሯን ሳታቋርጥ ስልኩን አነሳችና አየችው፤ አባቷ አቶ ቸርነት ናቸው የደወሉላት ፡፡ስብሰባ ላይ ነኝ ብላ ልትዘጋባቸው አልፈለገችም…አባቷ በጣም አስፈላጊ ጉዳይ ባይሆን ኖሮ በዚህ ሰዓት አይደውሉላትም ነበር፡፡
‹‹አንዴ ይቅርታ… ይሄንን ስልክ ማንሳት አለብኝ››ብላ ከተቀመጠችበት ግዙፍ ተሸከርካሪ ወንበር ተነሳችና ቢሮውን ለቃ ወጣችና….ከዛ ስልኩን አነሳችው፡፡
‹‹ሄሎ አባዬ ..እንዴት ነህ?››
‹‹ሰላም ነኝ ልጄ››
ድምፃቸው ተጎተተባት‹‹ምነው አባዬ? ችግር አለ እንዴ?››
‹‹አይ ልጄ ሁሉ ነገር ሰላም ነው…እኔ እና እናትሽ አንድ ነገር ልናማክርሽ ነበር››
‹‹ምንድነው?››
‹‹ይሄውልሽ ልጄ ምን መሰለሽ..እኔና እናትሽ ጡረታ ወጥተን ቤት መዋል ከጀመርን በኃላ ህይወታችንን ታውቂያለሽ…ብቸኞች ነን..አንቺም አሻፈረኝ ብለሽ በራስሽ ቤት ነው የምትኖሪው…፡፡››
ራሄል በምትሰማው ነገር ፊቷን አጨማደደች….የገመተችው አብረሽን ኑሪ የሚለውን የዘወትር ጥያቄያቸውን ደግመው ሊያነሱባት ነበር የመሰላት፡፡
አባቷ ትንፋሽ ወሰዱና ንግግራቸውን ቀጠሉ‹‹እህት እንዲኖርሽ ፈልገን ነበር››
ደነገጠች‹‹እህት!!››
‹‹አዎ ቅር ማይልሽ ከሆነ እኔ እና እናትሽ እህት እንዲኖርሽ ፈልገናል…የመጨረሻ ውሳኔ ላይ ከመድረሳችን በፊት ያንቺን አስተያየት ማወቅ ስለፈለግን ነው የደወልንልሽ፡፡››
‹‹ብዥ አለባት…እናቴ በሰባ አመቷ አረገዘች እንዴ?››ስትል በውስጧ እራሷ ጠየቀች፡፡‹‹አባቴ የአብረሀምን አይነት የዋህነት ስላለው እግዜር በዚህ አድሜዋ የማዬን ማህፀን ቢከፍት አይገርመኝም››ስትል በራሷ ሀሳብ ሳቀችና ትኩረቷን ወደስልኩ መለሰች፡፡
‹‹አባዬ አልገባኝም..እንዴት ነው እህት ሊኖረኝ የሚችለው?››
አንድ የሁለት አመት ቆንጅዬ ሴት ልጅ በጉዲፈቻ ልንወስድ ነው….››
‹‹በጉዲፈቻ…በጣም ደስ ይላል….ጥሩ ውሳኔ ነው የወሰናችሁት..››
ሀሳባቸውን ለመደገፍ ጥቂት ማሰብ እንኳን አላስፈለጋትም…የሁለት አመት ጣፋጭ ልጅ እዛ ግዙፍ ቪላ ቤት ውስጥ ስትሯሯጥ…አንዴ አባቷ ላይ አንዴ ደግሞ እናቷ ላይ እየተንጠለጠች ስታስቃቸውና ሰታዝናናቸው፣እነሱም ሲያሞላቅቋት…እሷን መሀላቸው አድርገው ግራና ቀኝ እጇን ይዘው ወደቤተክርስቲያን ይዘዋት ሲሄዱ .... በአይነ ህሊናዋ ታያትና በደስታ ተፍለቀለቀች፡፡
‹‹ልጄ አሁን እሷን ልናይ ሆስፒታል ነው ያለነው ..ከቻልሽ ጋንዲ ነን …ብትመጪ ደስ ይለኛል፡፡››
መልሶ መደነጋገር ውስጥ ገባች‹‹ሆስፒታል…ምን ትሰራለች?››
‹‹ትንሽ አሟታል…ከቻልሽ ነይ፡፡››ደገሙላት፡፡
‹‹በቃ መጣው››……ስልኩን ዘጋችና ወደቢሮዋ ተመልሳ ለረዳቶቾ ወደስራ እንዲመለሱ ትዕዛዝ ሰጥታ ቦርሳውን አንጠልጥላ ወጣችና ቀጥታ ከፓርክ መኪናዋን በማንቀሳቀስ ስለአዲሷ እጩ እህቷ ምን እንደምትመስልና…ምኗን ታማ ሆስፒታል ልትገባ እንደቻለች እያብሰለሰለች ወደጋንዲ ሆስፒታል ነዳችው፡፡
ደርሳ ወደውስጥ ስትገባ ሰውነቷ መንቀጥቀጥ ጀመረ…ይሄ የተለመደ ስሜቷ ነው…ሆሲፒታል ሂጂ ከሚሏት ጦርነት ዝመቺ ብትባል ትመርጣለች…እንደምንም ግን ወደውስጥ ዘለቀች… አባቷን ደውላ አገኘችው…እጇን ይዞ እየመራ የተባለቸው ህፃን ወደተኛችበት ክፍል ይዟት ገባ፡፡ክፍሉ ውስጥ ከህፃኗ ጋር የገዛ እናቷ ብቻ ነች ያለችው፡፡ ከበራፉ አንድ እርምጃ ወደውስጥ ተራምዳ እንደቆመች ደንዝዛ ቀረች …ከዛ ማለፍ አልቻለችም፡፡
ፍፅም የሚባል ድንዛዜ ውስጥ ነው የገባችው…ልጅቷ ቢያንስ ከሶስት ማሽን ጋር በቱቦ ተያይዛለች…መልኳ ውብ ፀጉሯ ግንቧሯ ላይ ድፍት ያለ አጎጊ ብትሆንም ስልምልም ብላ እራሷን ስታ ተዘርራለች..እንደውም ነፍሷ ውስጧ እንዳለ እርግጠኛ መሆን አልቻለችም….
በቃ ውስጧ ግልብጥብጥ ነው ያለባት…ከአመታት በፊት ምትወደውና ልታገባው ስታልመው የነበረው እጮኛዋ ኪሩቤል እንዲህ እንደህፃኗ እራሱ ስቶና ዝርግትግት ብሎ በማሽን እገዛ ለመተንፈስ ሲያጣጥር የነበረው ትዝታ መጣባትና እራሷን ልትስት ተንገዳገደች..አጠገቧ ያለው አባቷ ፈጠን ብሎ ደገፋት…እናቷ በድንጋጤ ከተቀመጠችበት ተነሳችና ስሯ ደረሰች፡፡
‹‹ምነው ልጄ..አመመሽ እንዴ?››ሁለቱም ተቀባብለው ጠየቋት፡፡
‹‹አይ ደህና ነኝ …የመድሀኒት ሽታና የህክምና ማሽኖቹ ድምፅ ነው የረበሸኝ››
‹‹ቸሬ አንተ እኮ ነህ..እሷ ሆስፒታል እንዴት እንደምትጠላና እንደሚያማት እያወቅክ ነይ ያልካት፡፡››
‹‹እውነትሽን ነው አጥፍቻለው….በቃ ልጄ ነይ…ይሄን ያህል ካየሻት ይበቃሻል….ብለው እየጎተቱ ወደውጭ ወሰዷት…መኪናዋ ድረስ አደረሷት፡፡‹‹እርግጠኛ ነሽ ሰላም ነሽ…?መኪና መንዳት ትችያለሽ››
‹‹አታስብ አባዬ..ሰላም ነኝ..በቃ ተመለስ››
መኪና ውስጥ ገባታ ስትንቀሳቅስ አባትዬው ወደውስጥ ተመለሱ፡፡ቀጥታ ወደቤቷ ነው የሄደችው፡፡የልጅቷ ምስል ከአእምሮዋ ሊወጣ አልቻለም….ወላጆቾ ምን አስበው ያቺን በህይወት እና በሞት መካከል ባለች ቀጭን ክር ተንጠልጥላ ያለችን ልጅ በማደጎ ለመውሰድ እንዳሰቡ ሊገባት አልቻሉም…እንዴት አድርገው ሊንከባከቧት ነው…?ከለመዷትና ከወደዷት በኃላ ብትሞትባቸውስ…..?የሚወዱትን ሰው በሞት መነጠቅ እንዴት ልብን እንደሚሰብር እና ተስፋን እንደሚያከስም በራሷ ታውቀዋለች…እና በእሷ የደረሰ አይነት ሀዘን በዚህ እድሜያቸው በወላጆቾ እንዲድርስ አትፈልግም…፡፡
‹‹ግን ምን ማድረግ እችላለው?››ስትል እራሷን ጠየቀች፡፡እንዲሁ ስትብሰለሰል አደረች…ሳምንት ሙሉ አሰበችበት..አንድ ውሳኔ ወስና ለወላጆቾ ምንም ነገር ማለት ሳትችል…ወላጆቹ ህጋዊ የአሳዳጊነት ፕሮሰሱን ጨርሰው ልጅቷን ወደቤታቸው እንደወሰዱ ሰማች፡፡በቃ ከዛ በጊዜ ሂደት የሚሆነውን ጠብቃ ለመመልከት ወሰነችና ወደወላጇቾ ቤት ሄዳ አዲሷን እህቷን አየቻት…ምንም እንኳን ከዛ ሁሉ ማሽን ነፃ ሆና ብታያትም..አሁንም ግን በጣም ደካማ እና የሰለለ ሰውነት ያለት ሆና ነው ያገኘቻት፡፡ግን ደግሞ በዛው ልክ አሳዛኝና ተወዳጅ ልጅ መሆኗን መካድ አልቻለችም፡፡
============
ራሄል ከረዳቷ ጋር እያወራች ነው፡፡
‹‹ሮቤል ወ.ሮ ላምሮት ልገሳዋን ለእኛ ፋውንዴሽን እንድታደርግ አሁን በስልክ አናግሬታለው፡፡እሷን ማሳመን ከቻልኩ እና ውሳኔዋ ለእኛ ለመለገስ ከሆነ ለፋውንዴሽናችን ትልቅ ስኬት ነው››
ራሄል ወረቀቶቿን ወደ ቦርሳዋ አስገባች፣ አንድ አይኗ በእንጨት በተሸፈነው የቢሮዋ ግድግዳ ላይ በተሰቀለው ሰዓት ላይ ተሰክቶ ነበር።
‹‹ ለማውራት ጊዜ የለኝም። በሃያ ደቂቃ ውስጥ በወላጆቼ መኖሪያ ቤት በተዘጋጀው የምሳ ግብዣ ላይ መገኘት አለብኝ ››አለች፡፡
ረዳቷ ማንኛውንም አይነት ቅሬታ ከማንሳቱ በፊት አቋረጠችውና ‹‹ እንደገና ሴትዬዋ ከደወለች ብቻ አሳውቀኝ።››አለችው፡፡
ስልኳን ዘጋችና ሞባይሏን ቦርሳዋ ውስጥ ለትንሿ እህቷ ጸጋ ከገዛችው ትንሽ ስጦታ ጋር አስቀመጠችው፣ ፀጋ ወላጇቾ ሊያሳድጓት በቅርብ የተረከቧት እህቷ ነች፡፡ ራሄል ወደ መኪና ማቆሚያ ጋራዥ በፍጥነት በምትወርድበት ጊዜ የኖብል ፋውንዴሽን ቢሮዎችና ኮሪደሮች በፀጥታ ተውጠው ነበር።
❤108🔥3😱2
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ፀጋ አባቷ እቅፍ ላይ እንዳለች ፈገግ በማለት የራሄልን ትኩረት ለመያዝ ሞከረች፣ በዚህ ጊዜ እናቷ ጣልቃ ገብታ መናገር ጀመሩ ፡፡
‹‹ራሄል፣ ከዶክተር ኤሊያስን ጋር እንድትተዋወቂ እፈልጋለሁ። እሱ የፀጋ ሐኪም ነው…ዔሊ ይህች ልጃችን ራሄል ናት።››
ዶ/ሩ በስሱ ፈገግ በማለት ‹‹ሰለአንቺ ብዙ ሰምቼያለው ..አንድ ቀን እንደምንገናኝ አምን ነበር›› በማለት እጁን ወደ እሷ ዘረጋ
ጨዋነት ያልጎደለው ፈገግታ ፈገግ አለችለት እና የዘረጋውን እጅን ጨበጠች፡፡ወላጆቿ ከእሱ ጋር አማች ለመሆን እያሴሩ እና እሱንም እያደፋፈሩት እንደሆነ ታውቃለች…ቢሆንም የሱ ጥፋት አልነበረም።
‹‹የሞተር ሳይክሉ ሰው ነህ አይደል?››
‹‹አዎ… ነኝ›› አላት፡፡
እጁ ሞቃታማ፣ ጣቶቹ ረዣዥም ነበሩ፣ እና ሲነካት ለረጅም ጊዜ በእንቅልፍ የመወሰድ አይነት የግንዛቤ ብልጭታ በአእምሯዋ ተንፀባረቆ ነበር….ስሜቱን አልወደደችውም። ‹‹በዛ ፍጥነት ስታበር ገርሞኝ ነበር››አለችው፣ትንፋሽ ወሰደችና ‹‹ደግሞ ዶክተር መሆን እና …..››
‹‹እና ምን?›› ከአንደበቷ ቀልቦ ጠየቃት።
‹‹ከተሸከምከው ሃላፊነት አንፃር ሞተር ማሽከርከር….አንድ ነገር ቢደርስብህስ?››
‹‹ለጊዜው አቅሜ የሚፈቅደው ርካሹ እና ፈጣኑ መጓጓዣ ሞተር ነው. እና ደግሞ አስፈላጊውን ጥንቃቄ አደርጋለሁ.››ሲል መለሰላት፡፡
ቀዝቀዝ ባለ ድምፅ‹‹ሁሉም የሚያቀነቅናቸው ታዋቂ የመጨረሻ ቃላቶች ናቸው…ጥንቃቄ አደርጋለው..››አለች በንዴት፡፡
በመጠኑ ደፍረስ ባሉት አይኖቹ በትኩረት ተመለከታት…ከመተዋወቃቸው እየሰጠችው ያለው ጠንከር ያለ አስተያየት ግራ አጋብቷታል…
እናትዬው ፀጋን ከአቶ ቸርነት እቅፍ ወሰድና፡፡‹‹በሉ ወደምግብ ጠረጴዛው እንሄድ….ምሳ ዝግጁ ነው››ሲሉ አወጁ፡፡
ሁሉም ወደምግብ ጠረጴዛው ተከታትለው ሄዱ፡፡ራሄል፣ የተለመደውን ቦታዋ ላይ ተቀምጣለች፣ ዔሊያስ ከእሷ ፊት ለፊት ተቀምጠ።››
አቶ ቸርነት በቀኝ እጇቸው የሴት ልጇቸውን እጅ ግራ እጇቸው ደግሞ በዔሊያስ ትከሻ ላይ ዘረጉና። ‹‹ብዙውን ጊዜ ከምግብ በፊት እንፀልያለን››ሲሉ ለዔሊያስ ገለጹለት።
‹‹እኔ ደስተኛ ነኝ. በቤተሰቦቼ ቤትም ስርዓቱ እንዲሁ ነው.››ሲል መለሰ፡፡አባቷ እጇን ጨምቀው ነበር፣መጸለይ ሲጀምሩ አንገቷን ዝቅ አደረገች።አባቷ ከእግዚአብሔር ጋር ሲነጋገሩ ማዳመጥ ብትጀምርም ከጸሎቱ ጋር በልቧ መቀላቀል አልቻለችም። እሷ በሀይማኖት ስርዓት ውስጥ ተወልዳ ያደገች ቢሆንም፣ ባለፉት ጥቂት አመታት ውስጥ ከመስመር ወጥታለች። አምላክ በህይወቷ ጣልቃ እንዲገባ አትፈልግም ወይም ደግሞም እሱ ራሱም ለእሷ ደንታ እንደሌለው ታምናለች።ስለዚህ ለምን ትጨቀጭቀዋለች፡፡ ወላጆቿ በዚህ መሳኔዋ ደስተኛ እንዳልሆኑ በደንብ ታውቃለች ቢሆንም ግን ርቀታቸውን በመጠበቃቸው ታመሰግናቸዋለች። እና ምናልባት ወደቀልቧ እንድትመለስ ዘወትር ለእሷ በድብቅ ይፀልዩላት ይሆናል፡፡
ፀሎቱ ተገባዶ በ‹‹አሜን›› እንደተዘጋ እናትዬው ‹‹በሉ እራሳችሁን አስተናግዱ ››አለቻቸው፡፡ሁሉም ፊት ለፊቱ ባለው ሳህን ላይ ፊለፊታቸው ከተደረደሩት በርካታ የምግብ ዓይነቶች የሚፈልጉትን መጠን መውሰድ ጀመሩ፡፡ተ
‹‹ከቻልክ ክትፎውን አቀብለኝ››ስትል ራሄል ወደኤልያስ እያየች አጉተመተመች፣
እናትዬው የራሄልን አስተያየት ውድቅ በማድረግ እጆቿን እያወዛወዘ ‹‹እስኪ እንደአንበሳ ስጋ ማሳደድሽን አቁሚ።››በማለት ገሰፃት፡፡ ቀጠል አደረጉና ‹‹ለሚያገባሽ ሰው አዝንለታለው።››ሲሉ አከሉበት፡፡
‹‹ደህና፣ ደስ ሚለው ነገር ፍቅረኛ የለኝም ››አለች ራሄል፡፡
‹‹እነዚህማ የተለመዱ ቃላቷችሽ ናቸው››
እናቷ በራሄል ንግግር ተከፍተው ‹‹አንድ ቀን ያንን በብቸኝነት የቀዘቀዘ አፓርታማሽን እርግፍ አድርገሽ ጥለሽ እንደ ዶ/ር ኤሊያስ ቤት አይነት ግቢ ወዳለው ቤት ትቀይሪ ይሆናል።››ሲሉ ምኞታቸውን ተናገሩ፡፡
እናትዬው ወደ ዶ/ሩ ዘወር አሉን‹‹ቤትህን በማስተካከል ላይ እንዳለህ ሰምቼያለው?››
‹‹በእውነቱ ወንድሜ ቢንያም ነው እየተከታተለው ያለው። እሱ አናጺ ነው። ስለ ኩሽና አሰራር አንዳንድ ውሳኔዎችን እንድወስን እየጨቀጨቀኝ ነበር, ነገር ግን ዘመናዊ ይሁን ወይም ባህላዊ ጭብጥ ይኑረው የሚለውን ለመወሰን እርግጠኛ መሆን አልቻልኩም››
አቶ ቸርነት‹‹ራሄልን ይዘሀት ብትሄድ ልትረዳህ ትችል ይሆናል››የሚል ሀሳብ አቀረቡለት። ዔሊያስ የራሔልን መኮሳተር ችላ በማለት እንደ ተወደደ ልጅ ፊቱ እያበራ ነው።
አንቷም ‹‹አዎ የእኔ ልጅ …በኢንቴርዬር ዲዛይን ላይ በጣም ጎበዝ ነች።››ሲሉ የአባትዬውን ሀሳብ ደገፉ፡፡
ራሄል ስለእሷ የተሰጠ ያለው አስተያየት ከየት እንደመጣ አታውቅም። ወላጆቿ አፓርታማዋን በሚጎበኙበት ጊዜ በዕቃዎቾ፤በምንጣፎች እና በመኝታ ቤቷ ቀለም ..ብዙ ብዙ ኔጌቲቨ የሆነ አስተያየት ሲሰጧት እንደነበር ታስታውሳለች፡፡ እንደውም እናቷ ‹ጥቂት እንኳን ለስሜቷ ሳይጨነቁ ቤቷን መኖሪያ ቤት ሳይሆን ሙዚየም እንዳስመሰለችው ነግረዋት ነበር፡፡
‹‹የምፈልገውን በትክክል አውቃለሁ። ትልቁ ችግሬ ግን ውሳኔዎችን ለመወሰን ጊዜ ማግኘት አለመቻሌ ነው ›› ሲል ኤሊያስ መለሰ።
ራሄል የሆነውን ነገር የተረዳች መስላ‹‹እንድትጨርሰው የምትገፋፋህ ሴት የለችም?››ስትል ጠየቀችው፡፡
አባቷ ራሄልን በግንባራቸው ገፆት ፡፡
ዶ/ሩ ‹‹ለጊዜው አቋሜ ልክ እንደአንቺው ነው….ለሴት ዝግጁ አይደለሁም››ሲል መለሰ።
ራሄል ውይይቱ ወደ መሃል ከተማ የትራፊክ ፍሰት፣ የኑሮው ውድነትና ፣ እና የፖለቲካ ውዥንብር.እና የሰላም እጦት የመሳሰሉት ጉዳዬች ላይ ሲያተኩር እፎይ አለች፡፡
በመሀል ወደ ዶ/ሩ አትኩራ እየተመለከተች ‹‹በቅርቡ የኖብል ፋውንዴሽን አመታዊ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት አለ።በዝግጅቱ ላይ መገኘትህን ማረጋገጥ አለብህ››አለችው፡፡
‹አረ ችግር የለውም..አታስቢ እገኛለው››ሲል ቃል ገባላት፡፡
እናትዬው‹‹ቀኑ ደረሰ እንዴ..?እንግዲህ በስራ ጫና ድራሽሽ ሊጠፋ ነው››ሲሉ ስጋታቸውን ገለፁላት፡፡
ራሄል ‹‹እማዬ ደግሞ ….እኔ ብቻዬን የማደርገውን አስመሰልሺው ። አብዛኛውን ስራ የሚሰሩልኝ ትላልቅ ሰራተኞች አሉኝ እኮ››
‹‹ነገር ግን ለሰራተኞችሽ በቂ ውክልና አትሰጪም።ቅድስትን ለመተካት እነዚያን ሁለቱን ረዳቶች መቅጠርሽን ስሰማ ብዙ የስራ ጫናሽን ያቃልሉልሻል ብዬ አስቤ ነበር። ነገር ግን አሁን እንደማየው ከሆነ የበለጠ ስራ ነው ያበዛብሽ፡፡››
‹‹ሰራተኞቹ በጣም አዲስ ናቸው ። ፋይሎቹን ብቻ ሰጥቻቸው ሁሉንም ነገር በራሳቸው እንዲቋቋሙት መጠበቅ አልችልም።››
‹‹ዬኒቨርሲቲ ዲግሪ ያላቸውና …በደንብ የሰለጠኑ ናቸው እኮ።››
‹‹አዎ ትክክል ነሽ..ግን የፋውንዴሽኑን ስራ በተመለከተ ትንሽ ተጨማሪ ልምድ ያስፈልጋቸዋል፣ሁሉም ሰው ወደሆነ አዲስ ስራ ሲሄድ ለተወሰነ ጊዜ ከአሰራሩ ጋር እስኪለማመድ አዲስ ሆኖ መገኘት አይቀርም››ለእናቷ ሌላ የማስጠንቀቂያ እይታ ሰጠቻት። ይህን ጉዳይ ሙሉ በሙሉ በማያውቁት ሰው ፊት መወያየታቸውን አልወደደችውም ።
‹‹ውዴ እወድሻለሁ፣ ግን ደግሞ አውቅሻለሁ።››ሲሉ እናትዬው በአቋማቸው መፅናታቸውን አረጋገጡላት፡፡
የራሄልን ማስጠንቀቂያ ችላ በማለት ‹‹እና ሁሉንም ነገር መቆጣጠር እንደምትችይ ማሰብ ማቆም አለብሽ። አንዳንድ ነገሮችን ለእግዚአብሔርን መልቀቅ አለብሽ።››ሲሉ ንግግራቸውን ደመደሙ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ፀጋ አባቷ እቅፍ ላይ እንዳለች ፈገግ በማለት የራሄልን ትኩረት ለመያዝ ሞከረች፣ በዚህ ጊዜ እናቷ ጣልቃ ገብታ መናገር ጀመሩ ፡፡
‹‹ራሄል፣ ከዶክተር ኤሊያስን ጋር እንድትተዋወቂ እፈልጋለሁ። እሱ የፀጋ ሐኪም ነው…ዔሊ ይህች ልጃችን ራሄል ናት።››
ዶ/ሩ በስሱ ፈገግ በማለት ‹‹ሰለአንቺ ብዙ ሰምቼያለው ..አንድ ቀን እንደምንገናኝ አምን ነበር›› በማለት እጁን ወደ እሷ ዘረጋ
ጨዋነት ያልጎደለው ፈገግታ ፈገግ አለችለት እና የዘረጋውን እጅን ጨበጠች፡፡ወላጆቿ ከእሱ ጋር አማች ለመሆን እያሴሩ እና እሱንም እያደፋፈሩት እንደሆነ ታውቃለች…ቢሆንም የሱ ጥፋት አልነበረም።
‹‹የሞተር ሳይክሉ ሰው ነህ አይደል?››
‹‹አዎ… ነኝ›› አላት፡፡
እጁ ሞቃታማ፣ ጣቶቹ ረዣዥም ነበሩ፣ እና ሲነካት ለረጅም ጊዜ በእንቅልፍ የመወሰድ አይነት የግንዛቤ ብልጭታ በአእምሯዋ ተንፀባረቆ ነበር….ስሜቱን አልወደደችውም። ‹‹በዛ ፍጥነት ስታበር ገርሞኝ ነበር››አለችው፣ትንፋሽ ወሰደችና ‹‹ደግሞ ዶክተር መሆን እና …..››
‹‹እና ምን?›› ከአንደበቷ ቀልቦ ጠየቃት።
‹‹ከተሸከምከው ሃላፊነት አንፃር ሞተር ማሽከርከር….አንድ ነገር ቢደርስብህስ?››
‹‹ለጊዜው አቅሜ የሚፈቅደው ርካሹ እና ፈጣኑ መጓጓዣ ሞተር ነው. እና ደግሞ አስፈላጊውን ጥንቃቄ አደርጋለሁ.››ሲል መለሰላት፡፡
ቀዝቀዝ ባለ ድምፅ‹‹ሁሉም የሚያቀነቅናቸው ታዋቂ የመጨረሻ ቃላቶች ናቸው…ጥንቃቄ አደርጋለው..››አለች በንዴት፡፡
በመጠኑ ደፍረስ ባሉት አይኖቹ በትኩረት ተመለከታት…ከመተዋወቃቸው እየሰጠችው ያለው ጠንከር ያለ አስተያየት ግራ አጋብቷታል…
እናትዬው ፀጋን ከአቶ ቸርነት እቅፍ ወሰድና፡፡‹‹በሉ ወደምግብ ጠረጴዛው እንሄድ….ምሳ ዝግጁ ነው››ሲሉ አወጁ፡፡
ሁሉም ወደምግብ ጠረጴዛው ተከታትለው ሄዱ፡፡ራሄል፣ የተለመደውን ቦታዋ ላይ ተቀምጣለች፣ ዔሊያስ ከእሷ ፊት ለፊት ተቀምጠ።››
አቶ ቸርነት በቀኝ እጇቸው የሴት ልጇቸውን እጅ ግራ እጇቸው ደግሞ በዔሊያስ ትከሻ ላይ ዘረጉና። ‹‹ብዙውን ጊዜ ከምግብ በፊት እንፀልያለን››ሲሉ ለዔሊያስ ገለጹለት።
‹‹እኔ ደስተኛ ነኝ. በቤተሰቦቼ ቤትም ስርዓቱ እንዲሁ ነው.››ሲል መለሰ፡፡አባቷ እጇን ጨምቀው ነበር፣መጸለይ ሲጀምሩ አንገቷን ዝቅ አደረገች።አባቷ ከእግዚአብሔር ጋር ሲነጋገሩ ማዳመጥ ብትጀምርም ከጸሎቱ ጋር በልቧ መቀላቀል አልቻለችም። እሷ በሀይማኖት ስርዓት ውስጥ ተወልዳ ያደገች ቢሆንም፣ ባለፉት ጥቂት አመታት ውስጥ ከመስመር ወጥታለች። አምላክ በህይወቷ ጣልቃ እንዲገባ አትፈልግም ወይም ደግሞም እሱ ራሱም ለእሷ ደንታ እንደሌለው ታምናለች።ስለዚህ ለምን ትጨቀጭቀዋለች፡፡ ወላጆቿ በዚህ መሳኔዋ ደስተኛ እንዳልሆኑ በደንብ ታውቃለች ቢሆንም ግን ርቀታቸውን በመጠበቃቸው ታመሰግናቸዋለች። እና ምናልባት ወደቀልቧ እንድትመለስ ዘወትር ለእሷ በድብቅ ይፀልዩላት ይሆናል፡፡
ፀሎቱ ተገባዶ በ‹‹አሜን›› እንደተዘጋ እናትዬው ‹‹በሉ እራሳችሁን አስተናግዱ ››አለቻቸው፡፡ሁሉም ፊት ለፊቱ ባለው ሳህን ላይ ፊለፊታቸው ከተደረደሩት በርካታ የምግብ ዓይነቶች የሚፈልጉትን መጠን መውሰድ ጀመሩ፡፡ተ
‹‹ከቻልክ ክትፎውን አቀብለኝ››ስትል ራሄል ወደኤልያስ እያየች አጉተመተመች፣
እናትዬው የራሄልን አስተያየት ውድቅ በማድረግ እጆቿን እያወዛወዘ ‹‹እስኪ እንደአንበሳ ስጋ ማሳደድሽን አቁሚ።››በማለት ገሰፃት፡፡ ቀጠል አደረጉና ‹‹ለሚያገባሽ ሰው አዝንለታለው።››ሲሉ አከሉበት፡፡
‹‹ደህና፣ ደስ ሚለው ነገር ፍቅረኛ የለኝም ››አለች ራሄል፡፡
‹‹እነዚህማ የተለመዱ ቃላቷችሽ ናቸው››
እናቷ በራሄል ንግግር ተከፍተው ‹‹አንድ ቀን ያንን በብቸኝነት የቀዘቀዘ አፓርታማሽን እርግፍ አድርገሽ ጥለሽ እንደ ዶ/ር ኤሊያስ ቤት አይነት ግቢ ወዳለው ቤት ትቀይሪ ይሆናል።››ሲሉ ምኞታቸውን ተናገሩ፡፡
እናትዬው ወደ ዶ/ሩ ዘወር አሉን‹‹ቤትህን በማስተካከል ላይ እንዳለህ ሰምቼያለው?››
‹‹በእውነቱ ወንድሜ ቢንያም ነው እየተከታተለው ያለው። እሱ አናጺ ነው። ስለ ኩሽና አሰራር አንዳንድ ውሳኔዎችን እንድወስን እየጨቀጨቀኝ ነበር, ነገር ግን ዘመናዊ ይሁን ወይም ባህላዊ ጭብጥ ይኑረው የሚለውን ለመወሰን እርግጠኛ መሆን አልቻልኩም››
አቶ ቸርነት‹‹ራሄልን ይዘሀት ብትሄድ ልትረዳህ ትችል ይሆናል››የሚል ሀሳብ አቀረቡለት። ዔሊያስ የራሔልን መኮሳተር ችላ በማለት እንደ ተወደደ ልጅ ፊቱ እያበራ ነው።
አንቷም ‹‹አዎ የእኔ ልጅ …በኢንቴርዬር ዲዛይን ላይ በጣም ጎበዝ ነች።››ሲሉ የአባትዬውን ሀሳብ ደገፉ፡፡
ራሄል ስለእሷ የተሰጠ ያለው አስተያየት ከየት እንደመጣ አታውቅም። ወላጆቿ አፓርታማዋን በሚጎበኙበት ጊዜ በዕቃዎቾ፤በምንጣፎች እና በመኝታ ቤቷ ቀለም ..ብዙ ብዙ ኔጌቲቨ የሆነ አስተያየት ሲሰጧት እንደነበር ታስታውሳለች፡፡ እንደውም እናቷ ‹ጥቂት እንኳን ለስሜቷ ሳይጨነቁ ቤቷን መኖሪያ ቤት ሳይሆን ሙዚየም እንዳስመሰለችው ነግረዋት ነበር፡፡
‹‹የምፈልገውን በትክክል አውቃለሁ። ትልቁ ችግሬ ግን ውሳኔዎችን ለመወሰን ጊዜ ማግኘት አለመቻሌ ነው ›› ሲል ኤሊያስ መለሰ።
ራሄል የሆነውን ነገር የተረዳች መስላ‹‹እንድትጨርሰው የምትገፋፋህ ሴት የለችም?››ስትል ጠየቀችው፡፡
አባቷ ራሄልን በግንባራቸው ገፆት ፡፡
ዶ/ሩ ‹‹ለጊዜው አቋሜ ልክ እንደአንቺው ነው….ለሴት ዝግጁ አይደለሁም››ሲል መለሰ።
ራሄል ውይይቱ ወደ መሃል ከተማ የትራፊክ ፍሰት፣ የኑሮው ውድነትና ፣ እና የፖለቲካ ውዥንብር.እና የሰላም እጦት የመሳሰሉት ጉዳዬች ላይ ሲያተኩር እፎይ አለች፡፡
በመሀል ወደ ዶ/ሩ አትኩራ እየተመለከተች ‹‹በቅርቡ የኖብል ፋውንዴሽን አመታዊ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት አለ።በዝግጅቱ ላይ መገኘትህን ማረጋገጥ አለብህ››አለችው፡፡
‹አረ ችግር የለውም..አታስቢ እገኛለው››ሲል ቃል ገባላት፡፡
እናትዬው‹‹ቀኑ ደረሰ እንዴ..?እንግዲህ በስራ ጫና ድራሽሽ ሊጠፋ ነው››ሲሉ ስጋታቸውን ገለፁላት፡፡
ራሄል ‹‹እማዬ ደግሞ ….እኔ ብቻዬን የማደርገውን አስመሰልሺው ። አብዛኛውን ስራ የሚሰሩልኝ ትላልቅ ሰራተኞች አሉኝ እኮ››
‹‹ነገር ግን ለሰራተኞችሽ በቂ ውክልና አትሰጪም።ቅድስትን ለመተካት እነዚያን ሁለቱን ረዳቶች መቅጠርሽን ስሰማ ብዙ የስራ ጫናሽን ያቃልሉልሻል ብዬ አስቤ ነበር። ነገር ግን አሁን እንደማየው ከሆነ የበለጠ ስራ ነው ያበዛብሽ፡፡››
‹‹ሰራተኞቹ በጣም አዲስ ናቸው ። ፋይሎቹን ብቻ ሰጥቻቸው ሁሉንም ነገር በራሳቸው እንዲቋቋሙት መጠበቅ አልችልም።››
‹‹ዬኒቨርሲቲ ዲግሪ ያላቸውና …በደንብ የሰለጠኑ ናቸው እኮ።››
‹‹አዎ ትክክል ነሽ..ግን የፋውንዴሽኑን ስራ በተመለከተ ትንሽ ተጨማሪ ልምድ ያስፈልጋቸዋል፣ሁሉም ሰው ወደሆነ አዲስ ስራ ሲሄድ ለተወሰነ ጊዜ ከአሰራሩ ጋር እስኪለማመድ አዲስ ሆኖ መገኘት አይቀርም››ለእናቷ ሌላ የማስጠንቀቂያ እይታ ሰጠቻት። ይህን ጉዳይ ሙሉ በሙሉ በማያውቁት ሰው ፊት መወያየታቸውን አልወደደችውም ።
‹‹ውዴ እወድሻለሁ፣ ግን ደግሞ አውቅሻለሁ።››ሲሉ እናትዬው በአቋማቸው መፅናታቸውን አረጋገጡላት፡፡
የራሄልን ማስጠንቀቂያ ችላ በማለት ‹‹እና ሁሉንም ነገር መቆጣጠር እንደምትችይ ማሰብ ማቆም አለብሽ። አንዳንድ ነገሮችን ለእግዚአብሔርን መልቀቅ አለብሽ።››ሲሉ ንግግራቸውን ደመደሙ፡፡
❤59👍7
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ከወ.ሮ ላምሮት ጋር የተደረገው ስብሰባ በጣም ረጅም ጊዜ ወስዶ ነበር እና ውጤቱ በጣም ጥቂት የሚባል ነበር፡፡
ራሄል በጣም የደክማት ቢሆንም ቢሮዋ ገብታም ስራዋን ቀጥላለች፡፡
‹‹ጥሩ ነው…በብሮሹሮች ላይ ስህተቶችን አግኝቻለሁ.››
ሎዛ ወረቀቶቹን በመካከላቸው ባለው የእንጨት ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠች። ራሄል በተቀመጠችበት የቆዳ ሶፋ ላይ ወደ ኋላ ተደግፋ ከፊቷ ያለውን ብሮሹር ቃኘች። ‹‹ይህ ሰማያዊ ቀለም በጣም ደማቅ ነው….እና ይህ ቢጫው ደግሞ እንዲጠናከር እፈልጋለሁ። የቀረውን ደግሞ ደውዬ አሳውቃቸዋለሁ››
‹‹ለምን ያን እኔ ራሴ እንድከታተል አትፈቅጂልኝም?›› አለች ሎዛ
‹‹አመሰግናለሁ ሎዛ.. ግን ማየት የምፈልገውን በትክክል አውቃለሁ።››
ሎዛ ራሷን በይሁንታ ነቀነቀች፣ ራሄል ግን በእሷ ውሳኔ ደስተኛ እንዳልነበረች አይታለች።
‹‹ለአሁን እንዳደርግ የምትፈልጊው ሌላ ነገር አለ?››ሎዛ ጠየቀች።
‹‹ አይ ምንም የለም… በቃ እጅሽ ላይ ያሉ ስራዎች ላይ ትኩረት አድርጊ።››የሚል ትእዛዝ ሰጠቻት፡፡
ራሄል ወረቀቶቹን በጠረጴዛዋ ላይ አስቀመጠች እና ሎዛ ቢሮዋን ስትለቅ ወደ ሮቤል ዞረች።
‹‹ሮቤል አንተ የሆነ ነገር አንድታደርግልኝ እፈልጋለው››አለችው፡፡
ሮቤል ጎንበስ ብሎ ከቆዳው ቦርሳ ውስጥ አንድ ወረቀት አወጣና‹‹ጥቂት ስልክ ደዋውዬ ከምንጩ ያገኘሁት መረጃ ነው።›› በማለት ተጨማሪ ወረቀቶችን አቀበላት።
‹‹ከስብሰባው ጥቂት ቀደም ብሎ ከድርጅቱ ኃላፊ ጋር በግል ተወያይቼ ነበር።››
‹‹ጉልበቱን ከየት አመጣው?››ስትል አሞገሰችው፡፡ ራሄል ከወ.ሮ ላምሮት ጋር ከተገናኘ በኋላ ስላከናወናቸው ውይይቶችና ስለተለዋወጦቸው ቃላቶች በማሰብ ደክሞት ነበር።‹‹ይህ በጣም ጥሩ ነው፣ቀጣዩ እርምጃችን የበጎ አድራጎት ልገሳ ሁኔታቸውን ማረጋገጥ እና ከቻልን በእነሱ ላይ አንዳንድ ጥልቅ የጀርባ ስራዎችን መስራት ነው።››
‹‹እንደተፈጸመ ቁጠሪው.››ሲል ሮቤል ፈገግ አለ። በዚህ ጊዜ ስልኳ ጠራ…እናቷ መስመር ላይ ነበረች።‹‹እንደገና አመሰግናለሁ ሮቤል።በቅርብ ጊዜ ፋውንዴሽኑን እንደተቀላቀለ ሰው ምርጥ ስራ ሰርተሃል.›› ብላ ስልኩን አነሳች፡፡
ራሱን ነቀነቀና ዞር ብሎ ከቢሮ ወጣ።ራሄል ከኋላው ባለው ትልቅ የቆዳ ወንበር ላይ ለመቀመጥ በጠረጴዟ ዙሪያ ዞራ ሄደች።
‹‹ጤና ይስጥልኝ እናቴ››
‹‹ደህና ነኝ የእኔ ልጅ››
‹‹ እየሮጥኩ ያለሁት ባንቺ ጉዳይ እንደሆነ ከግምት ውስጥ በማስገባት ልትደሰቺ ይገባሻል።››ስትል ራሄል ወንበሯ ላይ በመቀመጥ ተሸከረከረች፡፡
‹‹ውዴ፣ ሁሌም በአንቺ ደስተኛ ነኝ ፡ ታውቃያለሽ?››
‹‹እማዬ አውቃለው…የቸኮሌት ኬኩ በጣም ጥሩ ነበር. ሮቤል እና ሎዛ አመስግኚልኝ ብለዋል.››
‹‹እንደተካፈላችሁት በማወቄ ደስተኛ ነኝ። ግን አንቺን አንድ ውለታ ልጠይቅሽ ነው። አያቶችሽ ከሁለት ሳምንታት በኋላ ወደ አድዋ ሄደን እንደንጠይቃቸው ይፈልጋሉ፣ ነገር ግን ፀጋን ይዘን ለመሄድ መድፈር አልቻልንም ።እስክንመለሰ እሷን ለመጠበቅ ፈቃደኛ ነሸ?››ስትል ጠየቀቻት፡፡ራሄል በድንጋጤ ስልኩ ሊያመልጣት ነበር..በመከራ ነው አጥብቃ የያዘችው።
‹‹ፈቃደኛ? ምናልባት…ቆይ እስኪ ፕሮግራሜን ልመልከት››አለችና የቀጠሮ ደብተሯን ለማየት ማስታወሻ ደብተሯን ከፈተች። በዛን ወቅት የማይሰረዝ ፕሮግራም ኖሯት ያንን እንደምክንያት ማቅረብ እንድትችል በውስጧ ፀለየች፡፡
የወሩ የመጨረሻ ቅዳሜና እሁድ…..ቢንጎ …የበጎ አድራጎት ፈንድ የመሰብሰብ ፕሮግራም አለባት። ‹‹ይቅርታ እማዬ ባልሻቸው ቀናት መሰረዝ የማልችላቸው ፕሮግራሞች አሉብኝ…በነዛ ቀናት አመታዊ የፋውንዴሽኑ ፈንድ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም አለብኝ ።››
‹‹ኦህ ውዴ፣ አያትሽ ቤት የሚውለው ቅዳሜና እሁድ ብቻ ነው።›› በለሆሳስ ተነፈሰች። እና ፀጋን ከማንም ጋር ልተዋት እችላለው? ….እንደምታውቂው እስካሁን በጣም ደካማ ነች።››
‹‹ለምን ስለችግርሽ ከዶክተር ዔሊያስ ጋር አታወሪበትም››ስትል ሀሳብ አቀረበች።
‹‹በእርግጥ ትክክል ብለሻል .. እሱ የግል ነርሲንግ ኤጀንሲን ወይም ተመሳሳይ ነገርን ሊመክረኝ ይችላል?››
ራሄል አሰበች፤ የጥፋተኝነት ስሜት ሊሰማት አይገባም። ወላጆቿ ይችን ልጅ ለማሳደግ መወሰናቸው የሷ ሀሳብ አልነበረም። እና ፀጋ ብቃት እንደሌላት እና አቅመ ቢስነት እንዲሰማት ያደረጋት የሷ ስህተት አልነበረም።
‹‹እሷን መንከባከብ ካልቻልሽ ችግር የለውም…›› እናቷ ቀጠለች‹‹እርግጠኛ ነኝ ዔሊ ፀጋን የት ልንወስደት እንደምንችል ያውቃል።››
‹‹እንደሚያውቅ እርግጠኛ ነኝ››ስትል ራሄል ተስማማች፣ እፎይታም ተሰማት።
‹እና ስለ ዶክተር ዔሊያስ ምን አሰብሽ? ››እናትዬው እንደቀልድ ሌላ ርዕስ ከፈተች፡፡
‹‹እሱ በጣም ደስ የሚል ሰው ነው…. ከፀጋ ጋር በጣም ጥሩ ግንኙነት አለው ››
ከእሷ ጋር ሊጣመር የሚችልበት ምንም እድል እንደማይኖር ለእናቷ ግልፅ ለማድረግ ጊዜው አሁን እንደሆነ ተሰማት ‹‹ግን እሱ የእኔ ምርጫ አይደለም ።››ስትል መለሰችላት፡፡
‹‹ምን አልሽ?››
‹‹እማዬ… እባክሽ አሁን ለማንም ቢሆን ጊዜ የለኝም… ታውቂያለሽ››
‹‹ባለፉት ስምንት አመታት ውስጥ ለማንም ጊዜ አልነበራሽም። ብዙ ማህበራዊ ህይወት የለሽም። የምታደርጊው አንድ ነገር ቢኖር ስራ መስራት ብቻ ነው።››
ራሄል ወንበሯን ትንሽ እያወዛወዘች ፊቷን ከሰከሰች። ‹‹ይህን ስራ እፈልገዋለሁ እናቴ…ለህይወቴ ትርጉም የሰጠኝ ስራዬ ነው››
‹‹ከጌታ ጋር ያለሽ ግንኙነትስ? ያ እንዴት አድርጎ ነው ስራሽን የሚጋፋው?››ወደ ማትፈልገው ሌላ ርዕስ ከተተቻት፡፡
‹‹‹እናቴ ሆይ፣ የእኔ ስራ የተቸገሩ ህፃናትንና አቅመ ደካሞችን መርዳት ነው። ኢየሱስ በዚህ ምድር እንድናደርግ የሚፈልገውን ተግባር ነው እያደረኩ ያለሁት።››ራሄል እናቷን የሚያስደስት ትክክለኛ ቃላቶችን ታውቃለች እና ያለ እፍረት ተጠቀመችባቸው፡፡
‹‹ያለ እምነት ሥራ የሞተ ነው ውዴ።›› እናቷ ወደ እምነቷ ሲመጣ…ጥልቅ የማሰብ ችሎታ ስላላት ሁሉንም የልጇን የማጭበርበሪያ ስልቶች ታውቃለች።
ራሄል በመጨረሻ ‹‹እኔ ማድረግ የምችለው ይህን ብቻ ነው እናቴ››አለች. ቀጠለችናም ‹‹ለወንድ ጓደኛ ጊዜ የለኝም እና ለአንድም ሰው ፍላጎት የለኝም። ስለዚህ እባካችሁ ከአሁን በኋላ የማልፈልገውን አይነት አስጨናቂ እራት ለማዘጋጀት አትሞክሩ።››ስትል ንግግሯን በመኮሳተር ደመደመች፡፡
የእናቷ ዝምታ እጅ የመስጠት ምልክት እንደሆነ ተስፋ አድርጋ ነበር።‹‹ደስተኛ ነኝ እማማ›› እናቷ ብርሃኑን እንድታይ ለማድረግ ቆርጣ ገፋችበት። ‹‹ዓላማ እና ትርጉም ያለው ንቁ ህይወት ነው እየኖርኩ ያለሁት ። ጓደኞች አሉኝ እናም በማህበረሰብ ውስጥ አስፈላጊ የሚባል ስራ አለኝ። እና አንቺ እና አባዬ እና ፀጋም አለችሁልኝ። ተጨማሪ አያስፈልገኝም።››
‹‹እሺ፣ ይቅርታ፣ አንቺና ዔሊ ትመጣጠናላችሁ ብዬ ስላሰብኩ ነው። እሱ ጥሩ እና ደግ ሰው ነው..ለዛ ነው ከእሱ መዛመድ የፈለኩት ።››
ራሄል ፊቱ ላይ ስለተመለከተችው ፈገግታ አሰበች‹ደህና፣ ለአንድ ሌላ ሴት ግሩም ባል እንደሚሆን እርግጠኛ ነኝ። ግን ያቺ ሴት እኔ አይደለሁም፣ እማማ።››
ወ.ሮ ትርሀስ ቃተቱ። ‹‹ካስከፋሁሽ ይቅርታ።››
‹‹አስቸጋሪ ሁኔታ ፈጠርሺብኝ እንጂ አላስከፋሺኝም።››
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ከወ.ሮ ላምሮት ጋር የተደረገው ስብሰባ በጣም ረጅም ጊዜ ወስዶ ነበር እና ውጤቱ በጣም ጥቂት የሚባል ነበር፡፡
ራሄል በጣም የደክማት ቢሆንም ቢሮዋ ገብታም ስራዋን ቀጥላለች፡፡
‹‹ጥሩ ነው…በብሮሹሮች ላይ ስህተቶችን አግኝቻለሁ.››
ሎዛ ወረቀቶቹን በመካከላቸው ባለው የእንጨት ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠች። ራሄል በተቀመጠችበት የቆዳ ሶፋ ላይ ወደ ኋላ ተደግፋ ከፊቷ ያለውን ብሮሹር ቃኘች። ‹‹ይህ ሰማያዊ ቀለም በጣም ደማቅ ነው….እና ይህ ቢጫው ደግሞ እንዲጠናከር እፈልጋለሁ። የቀረውን ደግሞ ደውዬ አሳውቃቸዋለሁ››
‹‹ለምን ያን እኔ ራሴ እንድከታተል አትፈቅጂልኝም?›› አለች ሎዛ
‹‹አመሰግናለሁ ሎዛ.. ግን ማየት የምፈልገውን በትክክል አውቃለሁ።››
ሎዛ ራሷን በይሁንታ ነቀነቀች፣ ራሄል ግን በእሷ ውሳኔ ደስተኛ እንዳልነበረች አይታለች።
‹‹ለአሁን እንዳደርግ የምትፈልጊው ሌላ ነገር አለ?››ሎዛ ጠየቀች።
‹‹ አይ ምንም የለም… በቃ እጅሽ ላይ ያሉ ስራዎች ላይ ትኩረት አድርጊ።››የሚል ትእዛዝ ሰጠቻት፡፡
ራሄል ወረቀቶቹን በጠረጴዛዋ ላይ አስቀመጠች እና ሎዛ ቢሮዋን ስትለቅ ወደ ሮቤል ዞረች።
‹‹ሮቤል አንተ የሆነ ነገር አንድታደርግልኝ እፈልጋለው››አለችው፡፡
ሮቤል ጎንበስ ብሎ ከቆዳው ቦርሳ ውስጥ አንድ ወረቀት አወጣና‹‹ጥቂት ስልክ ደዋውዬ ከምንጩ ያገኘሁት መረጃ ነው።›› በማለት ተጨማሪ ወረቀቶችን አቀበላት።
‹‹ከስብሰባው ጥቂት ቀደም ብሎ ከድርጅቱ ኃላፊ ጋር በግል ተወያይቼ ነበር።››
‹‹ጉልበቱን ከየት አመጣው?››ስትል አሞገሰችው፡፡ ራሄል ከወ.ሮ ላምሮት ጋር ከተገናኘ በኋላ ስላከናወናቸው ውይይቶችና ስለተለዋወጦቸው ቃላቶች በማሰብ ደክሞት ነበር።‹‹ይህ በጣም ጥሩ ነው፣ቀጣዩ እርምጃችን የበጎ አድራጎት ልገሳ ሁኔታቸውን ማረጋገጥ እና ከቻልን በእነሱ ላይ አንዳንድ ጥልቅ የጀርባ ስራዎችን መስራት ነው።››
‹‹እንደተፈጸመ ቁጠሪው.››ሲል ሮቤል ፈገግ አለ። በዚህ ጊዜ ስልኳ ጠራ…እናቷ መስመር ላይ ነበረች።‹‹እንደገና አመሰግናለሁ ሮቤል።በቅርብ ጊዜ ፋውንዴሽኑን እንደተቀላቀለ ሰው ምርጥ ስራ ሰርተሃል.›› ብላ ስልኩን አነሳች፡፡
ራሱን ነቀነቀና ዞር ብሎ ከቢሮ ወጣ።ራሄል ከኋላው ባለው ትልቅ የቆዳ ወንበር ላይ ለመቀመጥ በጠረጴዟ ዙሪያ ዞራ ሄደች።
‹‹ጤና ይስጥልኝ እናቴ››
‹‹ደህና ነኝ የእኔ ልጅ››
‹‹ እየሮጥኩ ያለሁት ባንቺ ጉዳይ እንደሆነ ከግምት ውስጥ በማስገባት ልትደሰቺ ይገባሻል።››ስትል ራሄል ወንበሯ ላይ በመቀመጥ ተሸከረከረች፡፡
‹‹ውዴ፣ ሁሌም በአንቺ ደስተኛ ነኝ ፡ ታውቃያለሽ?››
‹‹እማዬ አውቃለው…የቸኮሌት ኬኩ በጣም ጥሩ ነበር. ሮቤል እና ሎዛ አመስግኚልኝ ብለዋል.››
‹‹እንደተካፈላችሁት በማወቄ ደስተኛ ነኝ። ግን አንቺን አንድ ውለታ ልጠይቅሽ ነው። አያቶችሽ ከሁለት ሳምንታት በኋላ ወደ አድዋ ሄደን እንደንጠይቃቸው ይፈልጋሉ፣ ነገር ግን ፀጋን ይዘን ለመሄድ መድፈር አልቻልንም ።እስክንመለሰ እሷን ለመጠበቅ ፈቃደኛ ነሸ?››ስትል ጠየቀቻት፡፡ራሄል በድንጋጤ ስልኩ ሊያመልጣት ነበር..በመከራ ነው አጥብቃ የያዘችው።
‹‹ፈቃደኛ? ምናልባት…ቆይ እስኪ ፕሮግራሜን ልመልከት››አለችና የቀጠሮ ደብተሯን ለማየት ማስታወሻ ደብተሯን ከፈተች። በዛን ወቅት የማይሰረዝ ፕሮግራም ኖሯት ያንን እንደምክንያት ማቅረብ እንድትችል በውስጧ ፀለየች፡፡
የወሩ የመጨረሻ ቅዳሜና እሁድ…..ቢንጎ …የበጎ አድራጎት ፈንድ የመሰብሰብ ፕሮግራም አለባት። ‹‹ይቅርታ እማዬ ባልሻቸው ቀናት መሰረዝ የማልችላቸው ፕሮግራሞች አሉብኝ…በነዛ ቀናት አመታዊ የፋውንዴሽኑ ፈንድ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም አለብኝ ።››
‹‹ኦህ ውዴ፣ አያትሽ ቤት የሚውለው ቅዳሜና እሁድ ብቻ ነው።›› በለሆሳስ ተነፈሰች። እና ፀጋን ከማንም ጋር ልተዋት እችላለው? ….እንደምታውቂው እስካሁን በጣም ደካማ ነች።››
‹‹ለምን ስለችግርሽ ከዶክተር ዔሊያስ ጋር አታወሪበትም››ስትል ሀሳብ አቀረበች።
‹‹በእርግጥ ትክክል ብለሻል .. እሱ የግል ነርሲንግ ኤጀንሲን ወይም ተመሳሳይ ነገርን ሊመክረኝ ይችላል?››
ራሄል አሰበች፤ የጥፋተኝነት ስሜት ሊሰማት አይገባም። ወላጆቿ ይችን ልጅ ለማሳደግ መወሰናቸው የሷ ሀሳብ አልነበረም። እና ፀጋ ብቃት እንደሌላት እና አቅመ ቢስነት እንዲሰማት ያደረጋት የሷ ስህተት አልነበረም።
‹‹እሷን መንከባከብ ካልቻልሽ ችግር የለውም…›› እናቷ ቀጠለች‹‹እርግጠኛ ነኝ ዔሊ ፀጋን የት ልንወስደት እንደምንችል ያውቃል።››
‹‹እንደሚያውቅ እርግጠኛ ነኝ››ስትል ራሄል ተስማማች፣ እፎይታም ተሰማት።
‹እና ስለ ዶክተር ዔሊያስ ምን አሰብሽ? ››እናትዬው እንደቀልድ ሌላ ርዕስ ከፈተች፡፡
‹‹እሱ በጣም ደስ የሚል ሰው ነው…. ከፀጋ ጋር በጣም ጥሩ ግንኙነት አለው ››
ከእሷ ጋር ሊጣመር የሚችልበት ምንም እድል እንደማይኖር ለእናቷ ግልፅ ለማድረግ ጊዜው አሁን እንደሆነ ተሰማት ‹‹ግን እሱ የእኔ ምርጫ አይደለም ።››ስትል መለሰችላት፡፡
‹‹ምን አልሽ?››
‹‹እማዬ… እባክሽ አሁን ለማንም ቢሆን ጊዜ የለኝም… ታውቂያለሽ››
‹‹ባለፉት ስምንት አመታት ውስጥ ለማንም ጊዜ አልነበራሽም። ብዙ ማህበራዊ ህይወት የለሽም። የምታደርጊው አንድ ነገር ቢኖር ስራ መስራት ብቻ ነው።››
ራሄል ወንበሯን ትንሽ እያወዛወዘች ፊቷን ከሰከሰች። ‹‹ይህን ስራ እፈልገዋለሁ እናቴ…ለህይወቴ ትርጉም የሰጠኝ ስራዬ ነው››
‹‹ከጌታ ጋር ያለሽ ግንኙነትስ? ያ እንዴት አድርጎ ነው ስራሽን የሚጋፋው?››ወደ ማትፈልገው ሌላ ርዕስ ከተተቻት፡፡
‹‹‹እናቴ ሆይ፣ የእኔ ስራ የተቸገሩ ህፃናትንና አቅመ ደካሞችን መርዳት ነው። ኢየሱስ በዚህ ምድር እንድናደርግ የሚፈልገውን ተግባር ነው እያደረኩ ያለሁት።››ራሄል እናቷን የሚያስደስት ትክክለኛ ቃላቶችን ታውቃለች እና ያለ እፍረት ተጠቀመችባቸው፡፡
‹‹ያለ እምነት ሥራ የሞተ ነው ውዴ።›› እናቷ ወደ እምነቷ ሲመጣ…ጥልቅ የማሰብ ችሎታ ስላላት ሁሉንም የልጇን የማጭበርበሪያ ስልቶች ታውቃለች።
ራሄል በመጨረሻ ‹‹እኔ ማድረግ የምችለው ይህን ብቻ ነው እናቴ››አለች. ቀጠለችናም ‹‹ለወንድ ጓደኛ ጊዜ የለኝም እና ለአንድም ሰው ፍላጎት የለኝም። ስለዚህ እባካችሁ ከአሁን በኋላ የማልፈልገውን አይነት አስጨናቂ እራት ለማዘጋጀት አትሞክሩ።››ስትል ንግግሯን በመኮሳተር ደመደመች፡፡
የእናቷ ዝምታ እጅ የመስጠት ምልክት እንደሆነ ተስፋ አድርጋ ነበር።‹‹ደስተኛ ነኝ እማማ›› እናቷ ብርሃኑን እንድታይ ለማድረግ ቆርጣ ገፋችበት። ‹‹ዓላማ እና ትርጉም ያለው ንቁ ህይወት ነው እየኖርኩ ያለሁት ። ጓደኞች አሉኝ እናም በማህበረሰብ ውስጥ አስፈላጊ የሚባል ስራ አለኝ። እና አንቺ እና አባዬ እና ፀጋም አለችሁልኝ። ተጨማሪ አያስፈልገኝም።››
‹‹እሺ፣ ይቅርታ፣ አንቺና ዔሊ ትመጣጠናላችሁ ብዬ ስላሰብኩ ነው። እሱ ጥሩ እና ደግ ሰው ነው..ለዛ ነው ከእሱ መዛመድ የፈለኩት ።››
ራሄል ፊቱ ላይ ስለተመለከተችው ፈገግታ አሰበች‹ደህና፣ ለአንድ ሌላ ሴት ግሩም ባል እንደሚሆን እርግጠኛ ነኝ። ግን ያቺ ሴት እኔ አይደለሁም፣ እማማ።››
ወ.ሮ ትርሀስ ቃተቱ። ‹‹ካስከፋሁሽ ይቅርታ።››
‹‹አስቸጋሪ ሁኔታ ፈጠርሺብኝ እንጂ አላስከፋሺኝም።››
❤77👍6
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
እሁድ የእረፍት ቀን ስለሆነ ኤልያስ ከወንድሙና ከጓደኛው ጋር ካፌ ቁጭ ብለው ቁምነገሩንም ቀልዱንም ሲጫወቱ አረፈድና ሌላ የሚሄዱበት ቦታ ስለነበር ተያይዘው ወጡ፡፡ሶስቱም የቢኒያም መኪና ወዳቆመችበት ቦታ እየተለፉ እየሄዱ ሳለ ድንገት ኤልያስ ከወንድሙ ከቢኒያም ጉሽሚያ ለማምለጥ ወደኃላው ሲሸሽ ከአንድ ውብ ሴት ጋር ተላተመ ፡፡ሴትዬዋ በእጇ የያዘችው ወረቀቶቿ ከእጆቿ ተንሸራተው ወደቁ እና ቦርሳዋ ከተከሻዋ ተንሸራቶ ሊወድቅባት ነበር…እሷም ተነገዳግዳ ሚዛኗን ለመሳት ስትጥር ኤልያስ በፍጥነት ተስፈነጠረና ክንዷን ያዛት ። ተረጋግቶ ሲያያት አይኖቹን ማመን ነው ያቃተው ።፡ራሄል ነች፡፡ ሞባይል ስልኳ አንድ ጆሮዋ ላይ ተጣብቆል…ስልክ እያወራች እንደነበር ተገነዘበ፡፡
አቀርቅራ የተበተኑ ወረቀቷቾን እያየች‹‹ምንድነው…አይንህ አያይም እንዴ? አብደሃል?››ስትል ጮኸችበት ።ከዚያም ቀና ብሎ አያት።ሀዘን ያረበባቸው አይኖቿ እሱን ሲያዩት ፣ ንዴቷ በጥልቀት ወደ ውስጡ ዘልቆ ሲገባ ተሰማው። በልቡ ክልል ውስጥ የሆነ ቦታ ላይ የብርሃን ብልጭታ ፈነጠቀ።ድንገት ወደጎን ዞር ብላ እሱ መሆኑን ስታውቅ በንግግሯ አፈረች፡፡‹‹እባክህ ይቅርታ አድርግልኝ››ብላ አጉተመተመች፣ክንዷን ወደኋላ ጎተተች። አሁንም እንደያዛት ረስቶት ነበር። ፈጠን ብሎ ለቀቃት። ርቀቱን ጠብቆ በጉጉት እያዩ ወደነበሩት ወንድሙ እና ጓደኛው እየተመለከተ። ‹‹ይቅርታ አላየሁሽም….ከወንድሜ ቢኒ ጡጫ እራሴን ለማራቅ እየሞከርኩ ነበር.››አላት፡፡
‹‹ምንም አይደለም፣ እኔም ቀልቤ የማወራው ስልክ ላይ ስለነበር መጠንቀቅ አልቻልኩም ።›› በማለት ወረቀቶቿን ለማንሳት ጎንበስ አለች።
‹‹ቆይ እኔ ላንሳልሽ›› ብሎ እሱም ጎንበስ አለ… ሁለቱም በአንድነት እጇቸውን ወደወረቀቱ ሲሰዱ እርስ በርስ ተነካኩ ፡፡በመሀከላቸው የኤሌክትሪክ ንዝረት አይነት ቅፅበታዊ ብልጭታ ተፈጠረ፡፡
‹‹እባክህ አትጨነቅ›› የውስጥ ስሜቱን የሚቆሰቁስ አይነት እንደገና የሚያነቃቃ ፈጣን ፈገግታ ሰጠችው።
ወረቀቶቹን ሰብስበው ከተነሱ በኋላ‹‹ለመሆኑ እዚህ ሰፈር ምን እግር ጣለሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ለስራ ጉዳይ››ስትል አፏ ላይ የመጣላትን ምክንያት ሰጠችው፡፡
‹‹ በእረፍት ቀን ትሰሪያለሽ እንዴ?››
ራሄል ፊቷን አኮሳትራ‹‹ስራ እስካለኝ ድረስ ቀን ሳልመርጥ ነው የምሰራው..ታውቃለህ …ሥራዬ በጣም አስፈላጊ ነው።››ስትል መለሰችለት፡፡
‹‹ደህና፣ በቃ እንገናኛለን።››
‹‹ተስፋ አደርጋለው።›› አለችና መንገዷን ቀጠለች ፡፡
‹‹አሁንም አለሽ ራሄል?›› ከያዘችው የሞባይል ስልክ የአንድ ወንድ ድምፅ ተሰማ። እናም ራሄል እስከአሁን ስልኳ እንዳልተቆረጠ ስትረዳ ‹‹ ሮቤል በቃ ቆይቼ ደውልሀለው … መንገድ ላይ ያልሆነ ነገር አጋጥሞኝ ነው›› ብላ ስልኩን ዘጋችው፡፡
ከዛም እርምጃዋን ሳታቋርጥ ወደ ዔሊያስ ዞር ብላ ተመለከተች …በተገተረበት ቆሞ እያያት ነበር ..የሆነ ውርር የሚያደርግ ስሜት ተሰማት ፡፡መንገዱን አቋርጣ ወደካፌው ታጠፈችና ከእይታው ተሰወረች፡፡
ሁኔታውን በትኩረት ሲከታተሉ የቆዩት ቢንያም እና ጓደኛው ወደ እሱ ሮጠው ከጎኑ ቆመ
‹‹በቀጣዬቹ አመታት ውስጥ ያለህ የሕይወት እቅድ ውስጥ ሴት እንደሌለችበት ደጋግመህ ነግረኸኝ ነበር? ››አለው ቢኒያም፡፡
‹‹እና ታዲያ?››
‹‹እናማ ይህቺ ሴት ማን ነች?።››
ዔሊያስ ለወንድሙ ‹‹የህይወት እቅዴ ላይ ምንም ማስተካከያ አልተደረገበትም..ያንን ካወቅክ ይበቃል።››ብሎት ወደመኪናው ጉዞውን ቀጠለ፡፡
ወንድሙም ከኋላው ተከትሎት‹‹እቅድህን ማስተካከል ትችላለህ …በቅድሚያ ግን ብድርህን ክፈል፣ ሞተርህን ሽጥና ትክክለኛ መኪና ግዛ፣ ከዛ ኑሮህን የምትጋራ ሴት መፈለግ ትችላለህ››አለው
ዔሊያስ ሕይወት ሁል ጊዜ እንደማይተነበይ ከግል ተሞክሮ ያውቃል ። ዔሊ በስድስት ዓመቱ ወደ ማደጎ ቤት ለመግባት ተገዶ ነበር፡፡ በወቅቱ ጮርቃ ልጅ ነበር እና ስለ ተፈጥሮ ወላጆቹ የሚያውቀው ብቸኛው ነገር አባቱ ሉቃስ እናቱ ደግሞ ትእግስት እንደምትባል ብቻ ነው፡፡ስለ እነሱ ያለው የመጨረሻ ትዝታ ቤተሰቡ በአንድ ላይ ሆነው እየተጓዙ እያለ አባቱ መኪናውን መቆጣጠር ተስኖት ሲጯጯሁ ነበር፡፡አንድ አመት ሙሉ በህፃናት ማሳደጊያ ውስጥ ተጣለ፡፡በዛን ተመሳሳይ ወቅት ቢኒያምም የአንድ አመት ህፃን ሆኖ በወላጇቹ ተጥሎ እዛ ማደጎ ቤት ከእሱ ጋር ነበር፣ እንደእድል ሆኖ አሳዳጊዎቻቸው ለሁለቱም ልባቸው ራራና አንድ ላይ ወደቤታቸው ወስደው እንደገዛ ልጇቻቸው ተንከባክበው አሳደጓቸው..እነሱም እርስ በርስ የሚዋደዱና የሚደጋገፉ ወንድማማቾች ሆነው አደጉ፡፡ አሳዳጊ ወላጆቻቸው ሁለቱንም በፍፁም ፍቅር እና …በስርዓት አስተምረው ለዚህ ደረጃ አበቁዋቸው፡፡
ቀጥታ ጓደኖቾ ይጠብቋት ወደነበረው ካፌ ገባች፡፡በጠረጴዛ ዙሪያ እየተጨዋወቱ እና እየሳቁ ካሉት ከጓደኞቿ ጋር ተቀላቀለች፡፡
‹‹ደህና ናችሁ ፣ ውድ ጓደኞቼ››
እንዴት ነሽ ንግስቲቷ›› ሜሮን ነች ቀድማ ለሰላምታዋ መልስ የሰጠቻት፡፡ከዛ ያሬድና ሌንሳ ተከተሉ፡፡እነዚህ ሶስቱ የልጅነት የትምህርት ቤት ጓደኞቾ ናቸው፡፡ራሄል ልጅ ሆና ፈጣን እና ጎበዝ ተማሪ ነበረች እና በዚህ ምክንያት ሁለት ክፍል በመዝለሏ ትምህርት ቤት ከገባችባቸው ልጆች ትንሿ ነበረች። አንድ ቀን በክፍሏ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ልጃገረዶች በመጫወቻ ስፍራው ላይ ወደ ጥግ ወስደው ይሳለቁባት ጀመር። እንደአጋጣሚ ሶስቱ ጓደኛሞች በአካባቢው ሲያልፉ ሁኔታውን ተመለከቱ ..ዝም ብለው ሊያልፉ አልፈለጉም…ጣልቃ ገብተው ራሄልን በክንፋቸው ስር ከልለው ታደጓት። ከዛን በኃላ ቋሚ ጓደኞቾ ሆኑ..ይሄው እስከዛሬ በህይወት ውጣ ውረዶች ውስጥ፣ የእርሷ ምስጢረኞች አማካሪዎች እና ውድ ጓደኞቿ ሆነዋል።እና ከአራት አመት በፊት ሌንሳና ያሬድ የጓደኝነት ግንኙነታቸውን ወደፍቅር ቀይረው በመጋባት መንታ ልጆችን ለመውለድ ችለዋል፡፡
ያሬድ የራሄልን የተዘበራረቀ ሸሚዞን እና የተበታተነ ወረቀቷን ተመለከተና ‹‹ደህና ነሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹አዎ..ደህና ነኝ››
‹‹ቆይ ምን ሆንሽ?››ሜሮን ተቀበለችው፡፡
‹‹ከመኪናዬ ወርጄ ወደእዚህ ስመጣ ..፣ከአንድ ጓረምሳ ዶ/ር ጋር ተጋጨው ››
‹‹ምን…!ከጎረምሳ…?ወይስ ከዶክተር?››ሌንሳ ጠየቀቻት፡፡
‹‹ጓረምሳ የሆነ ዶ/ር ..ምነው ግልፅ አይለም እንዴ?››
‹‹እኔ ያልገባኝ..ጎረምሳ መሆኑን በእይታ አወቅሽ እንበል..ዶክተር መሆኑንስ?››ሜሮን ጠየቀች፡፡
‹‹ባክሽ የማውቀው ሰው ነው …የእህቴ የፀጋ ዶክተር ነው፡፡››ሸሚዙ እንደተከፈተ፣ እና ፀጉሩ በግንባሩ ላይ ተደፍቶ እንደነበረ ላለማሰብ ታገለች።
ሁሉም በአንድ ላይ አስካኩባት፡፡
‹‹ስሙ ማን ነበር?››ሌንሳ በማሾፍ ጠየቀች፡፡
ራሄል ግን ጥያቄዋን በቁም ነገር ወስዳ‹‹ዓሊ››ስትል መለሰች፡፡
‹‹ኤሊ ማለት?››ያሬድ በገረሜታ ጠየቀ፡፡
‹‹ማለቴ ኤልያስ….ዶ/ር ኤልያስ››
ሌላ የህብረት ሳቅ ተከተለ፡፡
‹‹ተመልከቷት ነገሩ ስር የሰደደ ይመስላል ። የዔሊን ስም ሲነሳ መልኳ በደቂቃ ተለወጠ›› ሜሮን ጮኸች።
‹‹እንዴት ነው ግን…?››ለሊሴ ጠየቀቻት፡፡
‹‹ እሱ ቆንጆ ነው ማለት ይቻላል...›› ቡድኑን ዞር ብላ ተመለከተች እና በራሷ ሳቀች።‹‹እንደ ያሬድ ወንዳ ወንድ ነው›› ስትል አከለችበት፡፡
ሁሉም ሳቃቸውን መቆጣጠር አልቻሉም፡፡
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
እሁድ የእረፍት ቀን ስለሆነ ኤልያስ ከወንድሙና ከጓደኛው ጋር ካፌ ቁጭ ብለው ቁምነገሩንም ቀልዱንም ሲጫወቱ አረፈድና ሌላ የሚሄዱበት ቦታ ስለነበር ተያይዘው ወጡ፡፡ሶስቱም የቢኒያም መኪና ወዳቆመችበት ቦታ እየተለፉ እየሄዱ ሳለ ድንገት ኤልያስ ከወንድሙ ከቢኒያም ጉሽሚያ ለማምለጥ ወደኃላው ሲሸሽ ከአንድ ውብ ሴት ጋር ተላተመ ፡፡ሴትዬዋ በእጇ የያዘችው ወረቀቶቿ ከእጆቿ ተንሸራተው ወደቁ እና ቦርሳዋ ከተከሻዋ ተንሸራቶ ሊወድቅባት ነበር…እሷም ተነገዳግዳ ሚዛኗን ለመሳት ስትጥር ኤልያስ በፍጥነት ተስፈነጠረና ክንዷን ያዛት ። ተረጋግቶ ሲያያት አይኖቹን ማመን ነው ያቃተው ።፡ራሄል ነች፡፡ ሞባይል ስልኳ አንድ ጆሮዋ ላይ ተጣብቆል…ስልክ እያወራች እንደነበር ተገነዘበ፡፡
አቀርቅራ የተበተኑ ወረቀቷቾን እያየች‹‹ምንድነው…አይንህ አያይም እንዴ? አብደሃል?››ስትል ጮኸችበት ።ከዚያም ቀና ብሎ አያት።ሀዘን ያረበባቸው አይኖቿ እሱን ሲያዩት ፣ ንዴቷ በጥልቀት ወደ ውስጡ ዘልቆ ሲገባ ተሰማው። በልቡ ክልል ውስጥ የሆነ ቦታ ላይ የብርሃን ብልጭታ ፈነጠቀ።ድንገት ወደጎን ዞር ብላ እሱ መሆኑን ስታውቅ በንግግሯ አፈረች፡፡‹‹እባክህ ይቅርታ አድርግልኝ››ብላ አጉተመተመች፣ክንዷን ወደኋላ ጎተተች። አሁንም እንደያዛት ረስቶት ነበር። ፈጠን ብሎ ለቀቃት። ርቀቱን ጠብቆ በጉጉት እያዩ ወደነበሩት ወንድሙ እና ጓደኛው እየተመለከተ። ‹‹ይቅርታ አላየሁሽም….ከወንድሜ ቢኒ ጡጫ እራሴን ለማራቅ እየሞከርኩ ነበር.››አላት፡፡
‹‹ምንም አይደለም፣ እኔም ቀልቤ የማወራው ስልክ ላይ ስለነበር መጠንቀቅ አልቻልኩም ።›› በማለት ወረቀቶቿን ለማንሳት ጎንበስ አለች።
‹‹ቆይ እኔ ላንሳልሽ›› ብሎ እሱም ጎንበስ አለ… ሁለቱም በአንድነት እጇቸውን ወደወረቀቱ ሲሰዱ እርስ በርስ ተነካኩ ፡፡በመሀከላቸው የኤሌክትሪክ ንዝረት አይነት ቅፅበታዊ ብልጭታ ተፈጠረ፡፡
‹‹እባክህ አትጨነቅ›› የውስጥ ስሜቱን የሚቆሰቁስ አይነት እንደገና የሚያነቃቃ ፈጣን ፈገግታ ሰጠችው።
ወረቀቶቹን ሰብስበው ከተነሱ በኋላ‹‹ለመሆኑ እዚህ ሰፈር ምን እግር ጣለሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ለስራ ጉዳይ››ስትል አፏ ላይ የመጣላትን ምክንያት ሰጠችው፡፡
‹‹ በእረፍት ቀን ትሰሪያለሽ እንዴ?››
ራሄል ፊቷን አኮሳትራ‹‹ስራ እስካለኝ ድረስ ቀን ሳልመርጥ ነው የምሰራው..ታውቃለህ …ሥራዬ በጣም አስፈላጊ ነው።››ስትል መለሰችለት፡፡
‹‹ደህና፣ በቃ እንገናኛለን።››
‹‹ተስፋ አደርጋለው።›› አለችና መንገዷን ቀጠለች ፡፡
‹‹አሁንም አለሽ ራሄል?›› ከያዘችው የሞባይል ስልክ የአንድ ወንድ ድምፅ ተሰማ። እናም ራሄል እስከአሁን ስልኳ እንዳልተቆረጠ ስትረዳ ‹‹ ሮቤል በቃ ቆይቼ ደውልሀለው … መንገድ ላይ ያልሆነ ነገር አጋጥሞኝ ነው›› ብላ ስልኩን ዘጋችው፡፡
ከዛም እርምጃዋን ሳታቋርጥ ወደ ዔሊያስ ዞር ብላ ተመለከተች …በተገተረበት ቆሞ እያያት ነበር ..የሆነ ውርር የሚያደርግ ስሜት ተሰማት ፡፡መንገዱን አቋርጣ ወደካፌው ታጠፈችና ከእይታው ተሰወረች፡፡
ሁኔታውን በትኩረት ሲከታተሉ የቆዩት ቢንያም እና ጓደኛው ወደ እሱ ሮጠው ከጎኑ ቆመ
‹‹በቀጣዬቹ አመታት ውስጥ ያለህ የሕይወት እቅድ ውስጥ ሴት እንደሌለችበት ደጋግመህ ነግረኸኝ ነበር? ››አለው ቢኒያም፡፡
‹‹እና ታዲያ?››
‹‹እናማ ይህቺ ሴት ማን ነች?።››
ዔሊያስ ለወንድሙ ‹‹የህይወት እቅዴ ላይ ምንም ማስተካከያ አልተደረገበትም..ያንን ካወቅክ ይበቃል።››ብሎት ወደመኪናው ጉዞውን ቀጠለ፡፡
ወንድሙም ከኋላው ተከትሎት‹‹እቅድህን ማስተካከል ትችላለህ …በቅድሚያ ግን ብድርህን ክፈል፣ ሞተርህን ሽጥና ትክክለኛ መኪና ግዛ፣ ከዛ ኑሮህን የምትጋራ ሴት መፈለግ ትችላለህ››አለው
ዔሊያስ ሕይወት ሁል ጊዜ እንደማይተነበይ ከግል ተሞክሮ ያውቃል ። ዔሊ በስድስት ዓመቱ ወደ ማደጎ ቤት ለመግባት ተገዶ ነበር፡፡ በወቅቱ ጮርቃ ልጅ ነበር እና ስለ ተፈጥሮ ወላጆቹ የሚያውቀው ብቸኛው ነገር አባቱ ሉቃስ እናቱ ደግሞ ትእግስት እንደምትባል ብቻ ነው፡፡ስለ እነሱ ያለው የመጨረሻ ትዝታ ቤተሰቡ በአንድ ላይ ሆነው እየተጓዙ እያለ አባቱ መኪናውን መቆጣጠር ተስኖት ሲጯጯሁ ነበር፡፡አንድ አመት ሙሉ በህፃናት ማሳደጊያ ውስጥ ተጣለ፡፡በዛን ተመሳሳይ ወቅት ቢኒያምም የአንድ አመት ህፃን ሆኖ በወላጇቹ ተጥሎ እዛ ማደጎ ቤት ከእሱ ጋር ነበር፣ እንደእድል ሆኖ አሳዳጊዎቻቸው ለሁለቱም ልባቸው ራራና አንድ ላይ ወደቤታቸው ወስደው እንደገዛ ልጇቻቸው ተንከባክበው አሳደጓቸው..እነሱም እርስ በርስ የሚዋደዱና የሚደጋገፉ ወንድማማቾች ሆነው አደጉ፡፡ አሳዳጊ ወላጆቻቸው ሁለቱንም በፍፁም ፍቅር እና …በስርዓት አስተምረው ለዚህ ደረጃ አበቁዋቸው፡፡
ቀጥታ ጓደኖቾ ይጠብቋት ወደነበረው ካፌ ገባች፡፡በጠረጴዛ ዙሪያ እየተጨዋወቱ እና እየሳቁ ካሉት ከጓደኞቿ ጋር ተቀላቀለች፡፡
‹‹ደህና ናችሁ ፣ ውድ ጓደኞቼ››
እንዴት ነሽ ንግስቲቷ›› ሜሮን ነች ቀድማ ለሰላምታዋ መልስ የሰጠቻት፡፡ከዛ ያሬድና ሌንሳ ተከተሉ፡፡እነዚህ ሶስቱ የልጅነት የትምህርት ቤት ጓደኞቾ ናቸው፡፡ራሄል ልጅ ሆና ፈጣን እና ጎበዝ ተማሪ ነበረች እና በዚህ ምክንያት ሁለት ክፍል በመዝለሏ ትምህርት ቤት ከገባችባቸው ልጆች ትንሿ ነበረች። አንድ ቀን በክፍሏ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ልጃገረዶች በመጫወቻ ስፍራው ላይ ወደ ጥግ ወስደው ይሳለቁባት ጀመር። እንደአጋጣሚ ሶስቱ ጓደኛሞች በአካባቢው ሲያልፉ ሁኔታውን ተመለከቱ ..ዝም ብለው ሊያልፉ አልፈለጉም…ጣልቃ ገብተው ራሄልን በክንፋቸው ስር ከልለው ታደጓት። ከዛን በኃላ ቋሚ ጓደኞቾ ሆኑ..ይሄው እስከዛሬ በህይወት ውጣ ውረዶች ውስጥ፣ የእርሷ ምስጢረኞች አማካሪዎች እና ውድ ጓደኞቿ ሆነዋል።እና ከአራት አመት በፊት ሌንሳና ያሬድ የጓደኝነት ግንኙነታቸውን ወደፍቅር ቀይረው በመጋባት መንታ ልጆችን ለመውለድ ችለዋል፡፡
ያሬድ የራሄልን የተዘበራረቀ ሸሚዞን እና የተበታተነ ወረቀቷን ተመለከተና ‹‹ደህና ነሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹አዎ..ደህና ነኝ››
‹‹ቆይ ምን ሆንሽ?››ሜሮን ተቀበለችው፡፡
‹‹ከመኪናዬ ወርጄ ወደእዚህ ስመጣ ..፣ከአንድ ጓረምሳ ዶ/ር ጋር ተጋጨው ››
‹‹ምን…!ከጎረምሳ…?ወይስ ከዶክተር?››ሌንሳ ጠየቀቻት፡፡
‹‹ጓረምሳ የሆነ ዶ/ር ..ምነው ግልፅ አይለም እንዴ?››
‹‹እኔ ያልገባኝ..ጎረምሳ መሆኑን በእይታ አወቅሽ እንበል..ዶክተር መሆኑንስ?››ሜሮን ጠየቀች፡፡
‹‹ባክሽ የማውቀው ሰው ነው …የእህቴ የፀጋ ዶክተር ነው፡፡››ሸሚዙ እንደተከፈተ፣ እና ፀጉሩ በግንባሩ ላይ ተደፍቶ እንደነበረ ላለማሰብ ታገለች።
ሁሉም በአንድ ላይ አስካኩባት፡፡
‹‹ስሙ ማን ነበር?››ሌንሳ በማሾፍ ጠየቀች፡፡
ራሄል ግን ጥያቄዋን በቁም ነገር ወስዳ‹‹ዓሊ››ስትል መለሰች፡፡
‹‹ኤሊ ማለት?››ያሬድ በገረሜታ ጠየቀ፡፡
‹‹ማለቴ ኤልያስ….ዶ/ር ኤልያስ››
ሌላ የህብረት ሳቅ ተከተለ፡፡
‹‹ተመልከቷት ነገሩ ስር የሰደደ ይመስላል ። የዔሊን ስም ሲነሳ መልኳ በደቂቃ ተለወጠ›› ሜሮን ጮኸች።
‹‹እንዴት ነው ግን…?››ለሊሴ ጠየቀቻት፡፡
‹‹ እሱ ቆንጆ ነው ማለት ይቻላል...›› ቡድኑን ዞር ብላ ተመለከተች እና በራሷ ሳቀች።‹‹እንደ ያሬድ ወንዳ ወንድ ነው›› ስትል አከለችበት፡፡
ሁሉም ሳቃቸውን መቆጣጠር አልቻሉም፡፡
❤63👍3
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
‹ከሃያ ደቂቃ በኋላ ቢሮዬ እንገናኝ።››
በእሺታ ራሷን ነቀነቀች፣ ከዚያም አልፋው ጥላው ሄደች፡፡
ከግማሽ ሰአት በኋላ ራሄል ቢሮው መጥታ ከጠረጴዛው ማዶ ተቀመጠች፣ በአንድ እጇ እስክሪብቶ፣ በሌላ እጇ ማስታወሻ ደብተር ይዛለች። ሁኔታዋ አስገረመው ፡፡
ዶ/ር ዔሊያስ መናገር ጀመረ ‹‹ፀጋ በቴክኒካል ተርሙ ሄሚፕሌጂያ ተብሎ የሚጠራ በሽታ ተጠቂ ነች፡፡በሌላ አነጋገር ሴሬብራል ፓልሲ ታማሚ ነች ማለት ነው፡፡ በሰውነቷ አንድ ጎን በግራ እጇ እና በግራ እግሯ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ አሳድሮባታል..አጥንቶቾ በጣም ደካማ ስለሆኑ እንደልብ ለመንቀሳቀስ ትቸገራለች…በተወሰነ መልኩ የመስማትና ቃላቶችን አቀላጥፎ የማውራት ችግርም አለባት።የእሷን ጤና ሁኔታ ለማሻሻል በሚደረገው ሂደት ውስጥ የሚሳተፉትን - ፊዚዬ ቴራፒስት ጨምሮ፣ ብዙ ባለሞያዎች አሉ.. እና እያንዳንዱን መቼ መቼ ማየት እንዳለባት አስረዳት፡፡
‹‹በተጨማሪም የጆሮ ኢንፌክሽንን እየተዋጋች ስለነበረ አንቲባዮቲክ ትወስዳለች።››ዔሊ የራሔልን እይታ በመሸሽ እስክሪብቶውን አንሥቶ መሞነጫጨር ጀመረ።
ራሄል ትዕግስት በማጣት‹‹ዶክተር ሌላ ልትነግረኝ የሚገባ ነገር እንዳለ ይሰማኛል››አለችው.
‹‹ትሁት ከጊዜ ወደ ጊዜ በንዴት በሽታ እየተሰቃየች ነው ። ስለዚህ ስሜቷን በጥንቃቄ መከታተል እና የሚያበሳጮትን ነገሮች ማስወገድ ያስፈልግሻል ማለት ነው ።ያው እንድትናደድ ከፈቀድሽላት የሚጥል በሽታ ስላለባት ነገሮች ይባባሳሉ… እንደ አለመታደል ሆኖ ይሄንን ጉዳይ በመድኃኒቷን ማስተካከል አልቻልንም።››
‹‹ትሁት ማለት?››ግራ በመጋባት ጠየቀችው
‹‹ይቅርታ..ፀጋ ወደእናንተ ቤት ከመምጣቷ በፊት ወላጅ እናቷ ትሁት ብላ ነበር ስም ያወጣችላት….ከዛ ነው አባትሽ ፀጋ ያለት፡፡እና እኔ ትሁት የሚለውን ስም ለረጅም ጊዜ ስለተጠቀምኩበት በቀላሉ ከአእምሮዬ ላወጣው አልቻልኩም…..››
‹‹አይ ችግር ለውም..ትሁትም ደስ የሚል ስም ነው››
‹‹አዎ…እና እንዳልኩሽ ፀጋ ማለት ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልጋት ልጅ ነች፣፣በተለይ መናደድ የለባትም….ምክንያቱም ከንዴቷ በኋላ የሚከሰተው የሚጥል በሽታ ሌሎች ብዙ የጤና ችግሯቾን ነው የሚያናጋባት››
በራሔል ፊት ላይ የፍርሃት ብልጭታ ሲያይ ተገረመ።
‹‹የሚጥል በሽታ ሊነሳባት መሆኑን እንዴት አውቃለሁ እና ምን ያህል መጥፎ ነው?››
‹‹ትለይወለሽ…እጆቿ ይንቀጥቀጣሉ… የዐይን ሽፋኖቿን ይርገበገባሉ እነዚህን እና የመሳሰሉት ምልክቶችን ታሳያለች፡፡የዛን ጊዜ አጓጉል ወድቃ እራሷን እንዳትጎዳ ጥንቃቄ መውሰድ ይገባሻል፡፡ ማንኛውም አሳሳቢ የጤና ችግር ሲያጋጥማት በአፋጣኝ ወደሆስፒታል ልትወስጂያት የግድ ነው፡፡ በመደበኝነት በሳምንት ሶስት ቀን ሆስፒታል የህክምና ክትትል አለት፡፡በመሀል አስፈላጊ ሲሆን ለእኔ በማንኛውም ሰዓት ልትደውይልኝ ትችያለሽ ፣ ወዲያውኑ ልመጣ እችላለሁ።..›› ዔሊያስ መጀመሪያ ያሰበው ለፀጋ ነው።‹ራሔል በዚህች ልጅ ላይ ያለውን ችግር በሙሉ ማወቅ አለባት› ሲል በውስጡ አሰበ፡፡
‹‹ፀጋን ከተወለደች ቀን ጀምሮ እየተንከባከባት ነበር…እናትዬው ተስፋ ቆርጣበት በሆስፒታል አልጋ ላይ ማሽን እንደተሰካካባት ጥላት ስትሰወርም አንደኛ እናትዬውን ከልጅነት ጀምሮ የሚያውቃት ጓደኛው ስለሆነች ሲሆን ሁለተኛም ከራሱ ህይወት ጋር አያይዞ ሲንከባከባትና እንደወላጅ ስለሚጨነቅላት ነው፡፡በመጨረሻም ከስድስት ወር የሆስፒታል ቆይታዋ በኃላ የራሄልን ወላጆችን በግሉ ፈልጎ በማግኘት በጉዲፈቻ እንዲወስዷት በማድረግ ሂደት ላይ የአንበሳውን ድርሻ የእሱ ነው፡፡ከዛም በኃላ በቃ በኃላፊነት የሚያሳድጓት እና የሚንከባከቧት ወላጆች አግኝታለች ብሎ አልተዋትም፤ በቆሚነት የእሷ ሀኪም በመሆን እነ አቶ ቸርነት ቤት ድረስ እየተመላለሰ ሁኔታዋን ይከታተላል፤ ታማለች ብለው ሲደውሉለት ያለምንም ማቅማማት ሞተሩን ተረክ አድርጎ በሮ ይሄድና ያያታል…እናም ይህቺ ልጅ ለእሱ እንደአንድ ታካሚው ብቻ አይደለችም…የህይወቱ አካል ነች….ስቃዮ ያመዋል…ለቅሶዋ ይሰማዋል….ፈገግታዋ ያስቀዋል….ለዛ ነው ራሄልን በትክክል እናቷ በምትንከባከባት መጠን ትንከባከባታለች ብሎ ሊያምን ያልቻለው፡፡
‹‹ራሄል ምን መሰለሽ ፀጋን እንዲህ ስታያት በአካላዊ እይታ ጥሩ ሁኔታ ላይ ያለች ሊመስልሽ ይችላል, ግን ውስብስብ በሆነ የህክምና ሂደት ውስጥ እያለፈች ነው፡፡ ሰውነቷ እየሰጠ ያለው መልስ በጣም ደካማ ነው. ለሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት በጤና እሷን ማቆየት ከቻልን ትልቅ ድል ነው…በህክምናው ሂደት ከባድ ችግር እያጋጠመን ነው ››
ራሔል በፍጥነት ማስታወሻ እየወሰደች ሲሆን በእጇ ላይ ትንሽ መንቀጥቀጥ አየ፡፡‹‹ስለ ምን ዓይነት የሕክምና ችግሮች ነው የምታወራው?››
‹‹በአእምሯዋ ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት ጀምሮል እና ተጨማሪ ኢንፌክሽኖች እና ሌሎች ችግሮችም እየተከሰቱባት ነው፡፡››
እሺ፣ ምናልባት ትንሽ አክብዶባት ሊሆን ይችላል ግን ማወቅ አለባት። የበለጠ መረጃ ባላት ቁጥር እሷ ማድረግ የምትችለው የተሻሉ ውሳኔዎች ትወስናለች፣ ።
‹‹ወላጆቼ ግን ፀጋ ያለባትን ይሄን ሁሉ የጤና ችግር ያውቃሉ?››
‹‹አዎ..እንደውም ለአንቺ በጥቅሉ ነው የነገርኩሽ እንሱ ግን እሷን ለማሳደግ ከመወሰናቸው በፊት እያንዳንዱን በዝርዝር አስረድቻቸዋለው…..ግን ለምን ጠየቅሺኝ?››
‹‹እኔ እንጃ…..በዚህ ሁሉ የጤና እክል ውስጥ ሆኖ ምን አልባትም የመሞቻ ቀኗን እየተጠባበቀች ያለች እና ክፉና ደጉን የማታውቅ ልጅ እንዴት ለማሳደግ እንደፈቀዱ ግራ ስለገባኝ ነው፡፡››
‹‹ትክክል ነሽ….እኔም ወላጆችሽን በጣም የማከብራቸውና ከልቤ ማደንቃቸው በዚህ ውሳኔያቸው ነው…እነሱ ያደረጉትን ማንም ሌላ ሰው ያደርገዋል ብዬ አላስብም..እነሱ ለእኔ የህይወት ዘመን ጀግናዎቼ ናቸው፡፡››አለና ካርዱን ከጠረጴዛው ላይ አንስቶ ሰጣት። ‹‹ይህ የሆስፒታሉ የድንገተኛ አደጋ ቁጥር፣የቤቴ ቁጥር እና የሞባይል ቁጥሬ ነው። በፈለግሺኝ ጊዜ ደዉይልኝ››ራሄል መረጃውን እንደያዘች ረጅም እና ዘገምተኛ ትንፋሽ ወደ ውስጣ ሳበች ከዛ ወደ ውጭ ተነፈሰች፡፡ ወረቀቱን እና ካርዱን በቦርሳዋ ውስጥ አስገባች።
‹‹ከመሄዴ በፊት ግን አንድ የመጨረሻ ጥያቄ ልጠይቅህ?››
‹‹የፈለግሽውን ጠይቂኝ››አላት በጉጉት፡፡
‹‹ፀጋን ቤተሰቦቼ እንዲያሳድጓት በግል የጠየቅካቸውና ያሳመንካቸው አንተ ነህ….ለሌሎችም ታካሚዎችህ እንደዛ ታደርጋለህ?››ስትል ያለሳበውን ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
‹‹እውነቱን ለመናገር የፀጋ እናት የልጅነት ጎደኛዬ ነች…አንድ ሰፈር ነው ያደግነው…ህይወት ባልሆነ መንገድ መርታ ያልሆነ ማጥ ውስጥ ጨመረቻት እንጂ እንዲህ እንደቀልድ ልጇን ጥላ የምትሰወር ልጅ አልነበረችም….እና ፀጋን ዝም ብዬ ችላ ብዬ ማደጎ ቤት ስትገባ ማየት አልቻልኩም…የምተማመንባቸው አሳዳጊዎች መፈለግ ጀምርኩ..መጀመሪያ የራሴ ወላጆች ነበር የመጡልኝ..ግን የጽጌረዳ ሰፈር እዛው ስለነበረ ትንሽ ልክ መስሎ አልተሰማኝም….ከዛ ምክንያት ነው ወላጆችሽን ያገኘሁት…እናም ደግሞ ሁሉንም ነገር በግልፅ ነግሬያቸዋለው….ምንም የማያውቁት ነገር የለም፡፡››
‹‹አባቷስ?››
‹‹ምን ያህል እውነት እንደሆነ አላውቅ…አባቷ እንደሞተ ነው የነገረችኝ… ሌላ ጥያቄ ይኖርሻል?››
‹‹ አይ የለኝም..አመሰግናለው…. ››አለች… ቆመች… እጁን ለመጨበጥ ከጠረጴዛው አሻግራ እጇን ዘረጋች፡፡
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
‹ከሃያ ደቂቃ በኋላ ቢሮዬ እንገናኝ።››
በእሺታ ራሷን ነቀነቀች፣ ከዚያም አልፋው ጥላው ሄደች፡፡
ከግማሽ ሰአት በኋላ ራሄል ቢሮው መጥታ ከጠረጴዛው ማዶ ተቀመጠች፣ በአንድ እጇ እስክሪብቶ፣ በሌላ እጇ ማስታወሻ ደብተር ይዛለች። ሁኔታዋ አስገረመው ፡፡
ዶ/ር ዔሊያስ መናገር ጀመረ ‹‹ፀጋ በቴክኒካል ተርሙ ሄሚፕሌጂያ ተብሎ የሚጠራ በሽታ ተጠቂ ነች፡፡በሌላ አነጋገር ሴሬብራል ፓልሲ ታማሚ ነች ማለት ነው፡፡ በሰውነቷ አንድ ጎን በግራ እጇ እና በግራ እግሯ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ አሳድሮባታል..አጥንቶቾ በጣም ደካማ ስለሆኑ እንደልብ ለመንቀሳቀስ ትቸገራለች…በተወሰነ መልኩ የመስማትና ቃላቶችን አቀላጥፎ የማውራት ችግርም አለባት።የእሷን ጤና ሁኔታ ለማሻሻል በሚደረገው ሂደት ውስጥ የሚሳተፉትን - ፊዚዬ ቴራፒስት ጨምሮ፣ ብዙ ባለሞያዎች አሉ.. እና እያንዳንዱን መቼ መቼ ማየት እንዳለባት አስረዳት፡፡
‹‹በተጨማሪም የጆሮ ኢንፌክሽንን እየተዋጋች ስለነበረ አንቲባዮቲክ ትወስዳለች።››ዔሊ የራሔልን እይታ በመሸሽ እስክሪብቶውን አንሥቶ መሞነጫጨር ጀመረ።
ራሄል ትዕግስት በማጣት‹‹ዶክተር ሌላ ልትነግረኝ የሚገባ ነገር እንዳለ ይሰማኛል››አለችው.
‹‹ትሁት ከጊዜ ወደ ጊዜ በንዴት በሽታ እየተሰቃየች ነው ። ስለዚህ ስሜቷን በጥንቃቄ መከታተል እና የሚያበሳጮትን ነገሮች ማስወገድ ያስፈልግሻል ማለት ነው ።ያው እንድትናደድ ከፈቀድሽላት የሚጥል በሽታ ስላለባት ነገሮች ይባባሳሉ… እንደ አለመታደል ሆኖ ይሄንን ጉዳይ በመድኃኒቷን ማስተካከል አልቻልንም።››
‹‹ትሁት ማለት?››ግራ በመጋባት ጠየቀችው
‹‹ይቅርታ..ፀጋ ወደእናንተ ቤት ከመምጣቷ በፊት ወላጅ እናቷ ትሁት ብላ ነበር ስም ያወጣችላት….ከዛ ነው አባትሽ ፀጋ ያለት፡፡እና እኔ ትሁት የሚለውን ስም ለረጅም ጊዜ ስለተጠቀምኩበት በቀላሉ ከአእምሮዬ ላወጣው አልቻልኩም…..››
‹‹አይ ችግር ለውም..ትሁትም ደስ የሚል ስም ነው››
‹‹አዎ…እና እንዳልኩሽ ፀጋ ማለት ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልጋት ልጅ ነች፣፣በተለይ መናደድ የለባትም….ምክንያቱም ከንዴቷ በኋላ የሚከሰተው የሚጥል በሽታ ሌሎች ብዙ የጤና ችግሯቾን ነው የሚያናጋባት››
በራሔል ፊት ላይ የፍርሃት ብልጭታ ሲያይ ተገረመ።
‹‹የሚጥል በሽታ ሊነሳባት መሆኑን እንዴት አውቃለሁ እና ምን ያህል መጥፎ ነው?››
‹‹ትለይወለሽ…እጆቿ ይንቀጥቀጣሉ… የዐይን ሽፋኖቿን ይርገበገባሉ እነዚህን እና የመሳሰሉት ምልክቶችን ታሳያለች፡፡የዛን ጊዜ አጓጉል ወድቃ እራሷን እንዳትጎዳ ጥንቃቄ መውሰድ ይገባሻል፡፡ ማንኛውም አሳሳቢ የጤና ችግር ሲያጋጥማት በአፋጣኝ ወደሆስፒታል ልትወስጂያት የግድ ነው፡፡ በመደበኝነት በሳምንት ሶስት ቀን ሆስፒታል የህክምና ክትትል አለት፡፡በመሀል አስፈላጊ ሲሆን ለእኔ በማንኛውም ሰዓት ልትደውይልኝ ትችያለሽ ፣ ወዲያውኑ ልመጣ እችላለሁ።..›› ዔሊያስ መጀመሪያ ያሰበው ለፀጋ ነው።‹ራሔል በዚህች ልጅ ላይ ያለውን ችግር በሙሉ ማወቅ አለባት› ሲል በውስጡ አሰበ፡፡
‹‹ፀጋን ከተወለደች ቀን ጀምሮ እየተንከባከባት ነበር…እናትዬው ተስፋ ቆርጣበት በሆስፒታል አልጋ ላይ ማሽን እንደተሰካካባት ጥላት ስትሰወርም አንደኛ እናትዬውን ከልጅነት ጀምሮ የሚያውቃት ጓደኛው ስለሆነች ሲሆን ሁለተኛም ከራሱ ህይወት ጋር አያይዞ ሲንከባከባትና እንደወላጅ ስለሚጨነቅላት ነው፡፡በመጨረሻም ከስድስት ወር የሆስፒታል ቆይታዋ በኃላ የራሄልን ወላጆችን በግሉ ፈልጎ በማግኘት በጉዲፈቻ እንዲወስዷት በማድረግ ሂደት ላይ የአንበሳውን ድርሻ የእሱ ነው፡፡ከዛም በኃላ በቃ በኃላፊነት የሚያሳድጓት እና የሚንከባከቧት ወላጆች አግኝታለች ብሎ አልተዋትም፤ በቆሚነት የእሷ ሀኪም በመሆን እነ አቶ ቸርነት ቤት ድረስ እየተመላለሰ ሁኔታዋን ይከታተላል፤ ታማለች ብለው ሲደውሉለት ያለምንም ማቅማማት ሞተሩን ተረክ አድርጎ በሮ ይሄድና ያያታል…እናም ይህቺ ልጅ ለእሱ እንደአንድ ታካሚው ብቻ አይደለችም…የህይወቱ አካል ነች….ስቃዮ ያመዋል…ለቅሶዋ ይሰማዋል….ፈገግታዋ ያስቀዋል….ለዛ ነው ራሄልን በትክክል እናቷ በምትንከባከባት መጠን ትንከባከባታለች ብሎ ሊያምን ያልቻለው፡፡
‹‹ራሄል ምን መሰለሽ ፀጋን እንዲህ ስታያት በአካላዊ እይታ ጥሩ ሁኔታ ላይ ያለች ሊመስልሽ ይችላል, ግን ውስብስብ በሆነ የህክምና ሂደት ውስጥ እያለፈች ነው፡፡ ሰውነቷ እየሰጠ ያለው መልስ በጣም ደካማ ነው. ለሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት በጤና እሷን ማቆየት ከቻልን ትልቅ ድል ነው…በህክምናው ሂደት ከባድ ችግር እያጋጠመን ነው ››
ራሔል በፍጥነት ማስታወሻ እየወሰደች ሲሆን በእጇ ላይ ትንሽ መንቀጥቀጥ አየ፡፡‹‹ስለ ምን ዓይነት የሕክምና ችግሮች ነው የምታወራው?››
‹‹በአእምሯዋ ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት ጀምሮል እና ተጨማሪ ኢንፌክሽኖች እና ሌሎች ችግሮችም እየተከሰቱባት ነው፡፡››
እሺ፣ ምናልባት ትንሽ አክብዶባት ሊሆን ይችላል ግን ማወቅ አለባት። የበለጠ መረጃ ባላት ቁጥር እሷ ማድረግ የምትችለው የተሻሉ ውሳኔዎች ትወስናለች፣ ።
‹‹ወላጆቼ ግን ፀጋ ያለባትን ይሄን ሁሉ የጤና ችግር ያውቃሉ?››
‹‹አዎ..እንደውም ለአንቺ በጥቅሉ ነው የነገርኩሽ እንሱ ግን እሷን ለማሳደግ ከመወሰናቸው በፊት እያንዳንዱን በዝርዝር አስረድቻቸዋለው…..ግን ለምን ጠየቅሺኝ?››
‹‹እኔ እንጃ…..በዚህ ሁሉ የጤና እክል ውስጥ ሆኖ ምን አልባትም የመሞቻ ቀኗን እየተጠባበቀች ያለች እና ክፉና ደጉን የማታውቅ ልጅ እንዴት ለማሳደግ እንደፈቀዱ ግራ ስለገባኝ ነው፡፡››
‹‹ትክክል ነሽ….እኔም ወላጆችሽን በጣም የማከብራቸውና ከልቤ ማደንቃቸው በዚህ ውሳኔያቸው ነው…እነሱ ያደረጉትን ማንም ሌላ ሰው ያደርገዋል ብዬ አላስብም..እነሱ ለእኔ የህይወት ዘመን ጀግናዎቼ ናቸው፡፡››አለና ካርዱን ከጠረጴዛው ላይ አንስቶ ሰጣት። ‹‹ይህ የሆስፒታሉ የድንገተኛ አደጋ ቁጥር፣የቤቴ ቁጥር እና የሞባይል ቁጥሬ ነው። በፈለግሺኝ ጊዜ ደዉይልኝ››ራሄል መረጃውን እንደያዘች ረጅም እና ዘገምተኛ ትንፋሽ ወደ ውስጣ ሳበች ከዛ ወደ ውጭ ተነፈሰች፡፡ ወረቀቱን እና ካርዱን በቦርሳዋ ውስጥ አስገባች።
‹‹ከመሄዴ በፊት ግን አንድ የመጨረሻ ጥያቄ ልጠይቅህ?››
‹‹የፈለግሽውን ጠይቂኝ››አላት በጉጉት፡፡
‹‹ፀጋን ቤተሰቦቼ እንዲያሳድጓት በግል የጠየቅካቸውና ያሳመንካቸው አንተ ነህ….ለሌሎችም ታካሚዎችህ እንደዛ ታደርጋለህ?››ስትል ያለሳበውን ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
‹‹እውነቱን ለመናገር የፀጋ እናት የልጅነት ጎደኛዬ ነች…አንድ ሰፈር ነው ያደግነው…ህይወት ባልሆነ መንገድ መርታ ያልሆነ ማጥ ውስጥ ጨመረቻት እንጂ እንዲህ እንደቀልድ ልጇን ጥላ የምትሰወር ልጅ አልነበረችም….እና ፀጋን ዝም ብዬ ችላ ብዬ ማደጎ ቤት ስትገባ ማየት አልቻልኩም…የምተማመንባቸው አሳዳጊዎች መፈለግ ጀምርኩ..መጀመሪያ የራሴ ወላጆች ነበር የመጡልኝ..ግን የጽጌረዳ ሰፈር እዛው ስለነበረ ትንሽ ልክ መስሎ አልተሰማኝም….ከዛ ምክንያት ነው ወላጆችሽን ያገኘሁት…እናም ደግሞ ሁሉንም ነገር በግልፅ ነግሬያቸዋለው….ምንም የማያውቁት ነገር የለም፡፡››
‹‹አባቷስ?››
‹‹ምን ያህል እውነት እንደሆነ አላውቅ…አባቷ እንደሞተ ነው የነገረችኝ… ሌላ ጥያቄ ይኖርሻል?››
‹‹ አይ የለኝም..አመሰግናለው…. ››አለች… ቆመች… እጁን ለመጨበጥ ከጠረጴዛው አሻግራ እጇን ዘረጋች፡፡
❤75👍3🥰1
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
ይህ ፋውንዴሽን አሁን የደረሰበት ደረጃ የደረሰው በዚህ መንገድ ነበር, አሰበች እንደ ሮቤል ያሉ ሰዎች የወላጆቿ ሀብት የፋውንዴሽኑን የጀርባ አጥንት እንደሆነ ነው የሚያስቡት፣ ገንዘብ በቀላሉ ወደ ሣጥን ውስጥ እንደሚገባ ያስባሉ ። ፣ ከቅርብ ረዳቶቿ ከሆኑ በጣም ጥቂት ሰዎች በስተቀር፣ በዚህ ስራ ውስጥ ግንኙነቶች ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። ግንኙነቶች፣ መተማመን እና ከፍተኛ የስራ ስሜት ወሳኝ ነገሮች ናቸው። ገንዘቡ ወደፋውንዴሽኑ ከሚገባት ፍጥነት ሚወጣበት ፍጥነት ይበልጣል።ራሄል የፋውንዴሽኑን አስተዳደር ስትረከብ፣ የሂሳብ መዝገቡ አሁን ባለበት ሁኔታ ጤናማ አልነበረም።
ወላጆቿ ጥሩ ልብ ያላቸው የሰው ልጅን ያለልዩነት ለመርዳትና ለማገዝ ከልብ የሚጥሩ ቀና ሰዎች ቢሆኑም የተሳሳቱ ሰዎችን አምነው ስለነበር ለከፍተኛ ምዝበራ ተጋልጠው ነበር።እና ራሄል ስራዋን ከወላጇቾ ሙሉ በሙሉ ከተረከበች በኃላ አጠቃላይ የፋውንዴሽኑን ተቋማዊ አቅም ለማሻሻል ጥቂት አመታትን እና አንዳንድ ከባድ ውሳኔዎችን እንድትወስድ አስገድዷታል፣ከዛ ቀስ በቀስ ፋውንዴሽኑን አሁን ያለበት አቋም ላይ እንዲገኝ ማድረግ ችላለች፡፡ የተቋቋሙ ያገኘውን ገቢ በጥንቃቄ ለተከበሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን እንደሙዳይ…ሜቅዶኒያ ላሉ ገንዘብን ለታለመለት አላማ ብቻ ለሚያውሉ ተቋማት ያከፋፍላል፡፡ቀዳዳቸውን ይደፍናል ጉድለታቸውን ይሞላል፡፡
‹‹ሮቤል፣ ስለዚህ ጉዳይ አሁን ማውራት አልችልም። አሁንም ከሎዛ ጋር መገናኘት እና ከዚያም ፀጋን ከመዋለ ሕጻናት መውሰድ አለብኝ።ከዛ ቀጥታ ወ.ሮ ላምሮትን ሄጄ አገኛታለው….ደውልላት እና ከአንድ ሰዓት በኋላ እቤቷ እንደምገኝ ንገራት፡፡››አለችው፡፡ ወይዘሮ ላምሮት ብዙ ጊዜዋን እየወሰደች ነበር፣ ሴትየዋን ወደ ሎዛ ለማስተላለፍ አልደፈረችም ፡፡ለዚህ ነው ቀጥታ እራሷ ልታገኛት የወሰነችው፡፡
ቦርሳዋን ይዛ ከቢሯዋ ወጣች፡፡
ከአስራ አራት ደቂቃ በኋላ ወደ መዋዕለ ሕጻናት ማእከሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ስትገባ ጎማ በጭቃ ውስጥ ገባ። ቦርሳዋን እና ቁልፏን ይዛ ከመኪናው ውስጥ ዘላ ወጣች፣ ጉልበቷን የበሩን ጠርዝ መታት..አቃሰተች እና ጎንበስ ብላ እያሻሸች መንገዷን ቀጠለች .. የሞባይል ስልኳ እየጠራ ቢሆንም ችላ ብላ የመዋዕለ ሕፃናት ማቆያውን የመስታወት በሮች ከፍታ ወደውስጥ ገባች ፡፡ለአባቷ የገባችው ቃል ኪዳን እና በኤሊያስ አይኖች ውስጥ ያነበበችው ጥርጣሬ ለፀጋ አስፈላጊውን ጊዜ መድቦ ተገቢውን እንክብካቤ ለማድረግ ቁርጠኛ እንድትሆን አድርጓታል። ከሁሉም በላይ ግን ፀጋ እህቷ ነበረች። እና ምንም አይነት አስቸጋሪ ቢሆንም በክፉ ቀን ቤተሰብ ለቤተሰብ መከታ መሆን እንዳለበት ታምናለች፡፡ ፀጋ ሰዓቱን በትኩረት በምትመለከተው የቀን ተንከባካቢ ሰራተኛ እቅፍ ውስጥ ሆና እየጠበቀቻት ነበር። አፏ እና ጠባብ አይኖቿ ስትመለከት ነገሮች ጥሩ እንዳልሄዱ ገመተች።
‹‹ሴት ልጃችሁን በፕሮግራማችን ስታስመዘግቡ ፖሊሲያችንን በግልፅ አሳውቀናችኋል።›› ሴትዬዋ በጠንካራ ንጭንጭ ተቀበለቻት፡፡
‹‹ይገባኛል... ›› አለች‹‹እና እህቴን በሰዓቱ ስላልወሰድኩ ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ››ስትል አከለችበት ፡፡
‹‹በጣም ዘግይተሻል››የሚለው ቃል አከለችበት ። ጎንበስ ብላ የፀጋን ዳይፐር ከቦርሳ አወጣች እና ከዚያም ወደ እህቷ ተጠጋች ።‹‹ቶሎ ልናገኝሽ ሞክረን ነበር።›› ወይዘሮ ባንቺ ወደ ፀጋ ተመለከተች እና ፊቷን አኮሰታተረች። ያን ጊዜ ነበር ራሄል የልጅቷን በእንባ የታጠበ ጉንጯች ያስተዋለች። ‹‹ፀጋ ጥሩ ቀን አላሳለፈችም። ነርሷ የሙቀት መጠንዋን ስትወስድ ከፍ ብሎ ነበር፣ በተቻለ ፍጥነት ሀኪም ቤት እንድትወስዷት ተናግራለች ።››
‹‹እንዴ አሁን?...ለማለት የፈለኩት ይህ ምን ያህል አጣዳፊ ነው? ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ልውሰዳት ወይስ ሁኔታዋን መከታተል አለብኝ?››ስትል ጠየቀች፡፡
ወይዘሮ ባንቺ ‹‹ወዲያውኑ ብትወስጂያት መልካም ይመስለኛል.. እህትሽ ካለባት የጤና ችግር አንፃር የበለጠ ንቁ መሆን ይገባታል።
‹‹ያንን አስቤ ነው ወደዚህ ያመጣኋት… በቃ ወስዳታለው›› የፀጋ የሰውነት ሙቀት በልብሷ አልፎ እየተሰማት ነው። ላለባት ቀጠሮ ሰዓቷን ለማየት አልደፈረችም። ሆስፒታሉ ከመዋዕለ ህጻናት ብዙም ባለመራቁ አመሰገነች፡፡
ከሃያ ደቂቃ በኋላ ወደ ሆስፒታሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ገባች እና በድንገተኛ ክፍል በሮች ቸኩላ ስታልፍ ትዝታዎቹ እየተጣደፉ መጡባት።በእቅፏ ወደተቀመመችው ፀጋ ተመለከተች እና አዲስ ፍርሃት መላ ሰውነቷን ተቆጣጠራት። ወደ መቀበያ ጠረጴዛው እየገሰገሰች ስትሄድ፣ ቀድሞውንስ ይሄን ጉዳይ እንዴት አድርጋት ልትወጣ እንዳሰበች ተገረመች። ላለፉት ስምንት አመታት በድንገት የሚደፈርስ ስሜት እና ከቁጥጥር ውጪ የሚወጣ ድንገተኛ ብስጭትን ስትዋጋ ነው የኖረችው። አሁን የአንዲት ቀጫጫ ነርስን ማይረብ ጥያቄዎችን በትዕግስት እየመለሰች ነው።እንደጨረሰች በውስጧ እየበቀሉ ያሉ አሮጌ እና አዲስ ፍራቻዎችን እየታገለች፣ ለሆስፒታሎች ልዩ የሆኑትን የተለመዱ ሽታዎች እያሸተተች በተጨናነቀው የመጠበቂያ ክፍል ውስጥ ተመልሳ ተቀመጠች።
ከድንጋጤዋ የተነሳ መላ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ነው ፡፡ለፀጋ ስትል ትኩረቷን ለመሰብሰብ መሞከር አለባት።ፀጋ እጆቿ ይንቀጠቀጣሉ፣ ከሰውነቷ የሚወጣው ሙቀት በየደቂቃው እየጨመረ ነው። ነርሶቹ በስራ ተጠምደዋል፡፡ችሎታ ያለው እና ኃላፊነት የሚሰማው ዶ ር ለማግኘት ዙሪያውን አማተረች። አንዳቸውም ወደ ራሔል ዞር ብለው አላዩትም።ሰዎች ወንበሮች ላይ ተቀምጠው ይንቆራጥጣሉ፣ አንዳንዶቹ ጎንበስ ብለው ያቃስታሉ፣ ሌሎች ደግሞ ደንዝዘው እያንጓላጅጁ ነው፡፡
እያንዳንዳቸው በራሳቸው መከራና ሀዘን ተይዘዋል..ስለ ራሄል እና በእቅፏ ውስጥ እየተቃጠለች ስላለችው ህፃን ደንታ አልነበራቸውም።ከዚያም ፀጋ እየደነዘዘች ሄደች፡፡ ድንጋጤ የራሄልን ጉሮሮ አነቃት። አምላክ ማንኛውንም ነገር እንደሚያደርግ ብታምን ኖሮ አሁን በዚህ አስጨናቂ ጊዜ ትጸልይ ነበር።እግዚአብሔር ግን ከዚህ በፊት ከልቧ በፀለየችበት ጊዜ ትኩረት አልሰጣትም ነበር እና አሁንም እሱ ላይ መንጠልጠል አልፈለገችም፡፡ ፀጋ ማቃሰቱን አቁማ እንደገና በመጠኑ ዘና ስትል እፎይታ ተሰማት። ራሄልን ቀና ብላ ተመለከተች፣ታናሽ እህቷ ለስላሳ ቡናማ አይኖቿን ራሄል ላይ አንከባለለችባት፡፡ ራሄል በምላሽ ልቧ ሲዘል ተሰማት። ከዚያም ራቅ ብላ ተመለከተች።
ፀጋ ለእሷ ግዴታዋ ነበርች ይህች ልጅ ቀስ በቀስ የፍቅር እሳት በልቧ ዙሪያ እንዲቀጣጠል እያደረገች ነው። እንደ ፀጋ ካለች ልጅ ጋር መጣበቅ ማለት ልቧን ለህመም እና ማጣት እምቅ ስቃይ መከፈት ማለት እንደሆነ ታውቃለች።እና ያንን በራሷ ላይ እንደገና ማድረግ ፈፅሞ አትፈልግም ነበር ፡፡ግን ደግሞ በምርጫዋ እያደረገችው ያለ ነገር አይደለም፡፡ከአሰልቺ ጥበቃ በኃላ ነርሷ መጥታ በመጋረጃ ወደተሸፈነው ክፍል ወሰዳቻቸው። ራሄል እህቷን አልጋው ላይ በጥንቃቄ አስቀመጠቻት።ነርሷ የጥያቄዎችን ፣ የአለርጂዎችን ፣ የመድኃኒቶችን ዝርዝር ጠየቀቻት። ራሄል የምትችለውን ያህል መለሰች።እንደጨረሰች ነርሷ ጆሮዋ ውስጥ ቴርሞሜትር ጨመረች ..በዛ ቅፅበት አንድ ዶክተር ኮሪደሩን ሰንጥቆ ወደ እነርሱ ሲመጣ ተመለከተች። ነጭ ጋወን አድረጎ ስቴቶስኮፕ አንገቱ ላይ አንጠልጥሏል ።ኤሊ ነበር።
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
ይህ ፋውንዴሽን አሁን የደረሰበት ደረጃ የደረሰው በዚህ መንገድ ነበር, አሰበች እንደ ሮቤል ያሉ ሰዎች የወላጆቿ ሀብት የፋውንዴሽኑን የጀርባ አጥንት እንደሆነ ነው የሚያስቡት፣ ገንዘብ በቀላሉ ወደ ሣጥን ውስጥ እንደሚገባ ያስባሉ ። ፣ ከቅርብ ረዳቶቿ ከሆኑ በጣም ጥቂት ሰዎች በስተቀር፣ በዚህ ስራ ውስጥ ግንኙነቶች ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። ግንኙነቶች፣ መተማመን እና ከፍተኛ የስራ ስሜት ወሳኝ ነገሮች ናቸው። ገንዘቡ ወደፋውንዴሽኑ ከሚገባት ፍጥነት ሚወጣበት ፍጥነት ይበልጣል።ራሄል የፋውንዴሽኑን አስተዳደር ስትረከብ፣ የሂሳብ መዝገቡ አሁን ባለበት ሁኔታ ጤናማ አልነበረም።
ወላጆቿ ጥሩ ልብ ያላቸው የሰው ልጅን ያለልዩነት ለመርዳትና ለማገዝ ከልብ የሚጥሩ ቀና ሰዎች ቢሆኑም የተሳሳቱ ሰዎችን አምነው ስለነበር ለከፍተኛ ምዝበራ ተጋልጠው ነበር።እና ራሄል ስራዋን ከወላጇቾ ሙሉ በሙሉ ከተረከበች በኃላ አጠቃላይ የፋውንዴሽኑን ተቋማዊ አቅም ለማሻሻል ጥቂት አመታትን እና አንዳንድ ከባድ ውሳኔዎችን እንድትወስድ አስገድዷታል፣ከዛ ቀስ በቀስ ፋውንዴሽኑን አሁን ያለበት አቋም ላይ እንዲገኝ ማድረግ ችላለች፡፡ የተቋቋሙ ያገኘውን ገቢ በጥንቃቄ ለተከበሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን እንደሙዳይ…ሜቅዶኒያ ላሉ ገንዘብን ለታለመለት አላማ ብቻ ለሚያውሉ ተቋማት ያከፋፍላል፡፡ቀዳዳቸውን ይደፍናል ጉድለታቸውን ይሞላል፡፡
‹‹ሮቤል፣ ስለዚህ ጉዳይ አሁን ማውራት አልችልም። አሁንም ከሎዛ ጋር መገናኘት እና ከዚያም ፀጋን ከመዋለ ሕጻናት መውሰድ አለብኝ።ከዛ ቀጥታ ወ.ሮ ላምሮትን ሄጄ አገኛታለው….ደውልላት እና ከአንድ ሰዓት በኋላ እቤቷ እንደምገኝ ንገራት፡፡››አለችው፡፡ ወይዘሮ ላምሮት ብዙ ጊዜዋን እየወሰደች ነበር፣ ሴትየዋን ወደ ሎዛ ለማስተላለፍ አልደፈረችም ፡፡ለዚህ ነው ቀጥታ እራሷ ልታገኛት የወሰነችው፡፡
ቦርሳዋን ይዛ ከቢሯዋ ወጣች፡፡
ከአስራ አራት ደቂቃ በኋላ ወደ መዋዕለ ሕጻናት ማእከሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ስትገባ ጎማ በጭቃ ውስጥ ገባ። ቦርሳዋን እና ቁልፏን ይዛ ከመኪናው ውስጥ ዘላ ወጣች፣ ጉልበቷን የበሩን ጠርዝ መታት..አቃሰተች እና ጎንበስ ብላ እያሻሸች መንገዷን ቀጠለች .. የሞባይል ስልኳ እየጠራ ቢሆንም ችላ ብላ የመዋዕለ ሕፃናት ማቆያውን የመስታወት በሮች ከፍታ ወደውስጥ ገባች ፡፡ለአባቷ የገባችው ቃል ኪዳን እና በኤሊያስ አይኖች ውስጥ ያነበበችው ጥርጣሬ ለፀጋ አስፈላጊውን ጊዜ መድቦ ተገቢውን እንክብካቤ ለማድረግ ቁርጠኛ እንድትሆን አድርጓታል። ከሁሉም በላይ ግን ፀጋ እህቷ ነበረች። እና ምንም አይነት አስቸጋሪ ቢሆንም በክፉ ቀን ቤተሰብ ለቤተሰብ መከታ መሆን እንዳለበት ታምናለች፡፡ ፀጋ ሰዓቱን በትኩረት በምትመለከተው የቀን ተንከባካቢ ሰራተኛ እቅፍ ውስጥ ሆና እየጠበቀቻት ነበር። አፏ እና ጠባብ አይኖቿ ስትመለከት ነገሮች ጥሩ እንዳልሄዱ ገመተች።
‹‹ሴት ልጃችሁን በፕሮግራማችን ስታስመዘግቡ ፖሊሲያችንን በግልፅ አሳውቀናችኋል።›› ሴትዬዋ በጠንካራ ንጭንጭ ተቀበለቻት፡፡
‹‹ይገባኛል... ›› አለች‹‹እና እህቴን በሰዓቱ ስላልወሰድኩ ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ››ስትል አከለችበት ፡፡
‹‹በጣም ዘግይተሻል››የሚለው ቃል አከለችበት ። ጎንበስ ብላ የፀጋን ዳይፐር ከቦርሳ አወጣች እና ከዚያም ወደ እህቷ ተጠጋች ።‹‹ቶሎ ልናገኝሽ ሞክረን ነበር።›› ወይዘሮ ባንቺ ወደ ፀጋ ተመለከተች እና ፊቷን አኮሰታተረች። ያን ጊዜ ነበር ራሄል የልጅቷን በእንባ የታጠበ ጉንጯች ያስተዋለች። ‹‹ፀጋ ጥሩ ቀን አላሳለፈችም። ነርሷ የሙቀት መጠንዋን ስትወስድ ከፍ ብሎ ነበር፣ በተቻለ ፍጥነት ሀኪም ቤት እንድትወስዷት ተናግራለች ።››
‹‹እንዴ አሁን?...ለማለት የፈለኩት ይህ ምን ያህል አጣዳፊ ነው? ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ልውሰዳት ወይስ ሁኔታዋን መከታተል አለብኝ?››ስትል ጠየቀች፡፡
ወይዘሮ ባንቺ ‹‹ወዲያውኑ ብትወስጂያት መልካም ይመስለኛል.. እህትሽ ካለባት የጤና ችግር አንፃር የበለጠ ንቁ መሆን ይገባታል።
‹‹ያንን አስቤ ነው ወደዚህ ያመጣኋት… በቃ ወስዳታለው›› የፀጋ የሰውነት ሙቀት በልብሷ አልፎ እየተሰማት ነው። ላለባት ቀጠሮ ሰዓቷን ለማየት አልደፈረችም። ሆስፒታሉ ከመዋዕለ ህጻናት ብዙም ባለመራቁ አመሰገነች፡፡
ከሃያ ደቂቃ በኋላ ወደ ሆስፒታሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ገባች እና በድንገተኛ ክፍል በሮች ቸኩላ ስታልፍ ትዝታዎቹ እየተጣደፉ መጡባት።በእቅፏ ወደተቀመመችው ፀጋ ተመለከተች እና አዲስ ፍርሃት መላ ሰውነቷን ተቆጣጠራት። ወደ መቀበያ ጠረጴዛው እየገሰገሰች ስትሄድ፣ ቀድሞውንስ ይሄን ጉዳይ እንዴት አድርጋት ልትወጣ እንዳሰበች ተገረመች። ላለፉት ስምንት አመታት በድንገት የሚደፈርስ ስሜት እና ከቁጥጥር ውጪ የሚወጣ ድንገተኛ ብስጭትን ስትዋጋ ነው የኖረችው። አሁን የአንዲት ቀጫጫ ነርስን ማይረብ ጥያቄዎችን በትዕግስት እየመለሰች ነው።እንደጨረሰች በውስጧ እየበቀሉ ያሉ አሮጌ እና አዲስ ፍራቻዎችን እየታገለች፣ ለሆስፒታሎች ልዩ የሆኑትን የተለመዱ ሽታዎች እያሸተተች በተጨናነቀው የመጠበቂያ ክፍል ውስጥ ተመልሳ ተቀመጠች።
ከድንጋጤዋ የተነሳ መላ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ነው ፡፡ለፀጋ ስትል ትኩረቷን ለመሰብሰብ መሞከር አለባት።ፀጋ እጆቿ ይንቀጠቀጣሉ፣ ከሰውነቷ የሚወጣው ሙቀት በየደቂቃው እየጨመረ ነው። ነርሶቹ በስራ ተጠምደዋል፡፡ችሎታ ያለው እና ኃላፊነት የሚሰማው ዶ ር ለማግኘት ዙሪያውን አማተረች። አንዳቸውም ወደ ራሔል ዞር ብለው አላዩትም።ሰዎች ወንበሮች ላይ ተቀምጠው ይንቆራጥጣሉ፣ አንዳንዶቹ ጎንበስ ብለው ያቃስታሉ፣ ሌሎች ደግሞ ደንዝዘው እያንጓላጅጁ ነው፡፡
እያንዳንዳቸው በራሳቸው መከራና ሀዘን ተይዘዋል..ስለ ራሄል እና በእቅፏ ውስጥ እየተቃጠለች ስላለችው ህፃን ደንታ አልነበራቸውም።ከዚያም ፀጋ እየደነዘዘች ሄደች፡፡ ድንጋጤ የራሄልን ጉሮሮ አነቃት። አምላክ ማንኛውንም ነገር እንደሚያደርግ ብታምን ኖሮ አሁን በዚህ አስጨናቂ ጊዜ ትጸልይ ነበር።እግዚአብሔር ግን ከዚህ በፊት ከልቧ በፀለየችበት ጊዜ ትኩረት አልሰጣትም ነበር እና አሁንም እሱ ላይ መንጠልጠል አልፈለገችም፡፡ ፀጋ ማቃሰቱን አቁማ እንደገና በመጠኑ ዘና ስትል እፎይታ ተሰማት። ራሄልን ቀና ብላ ተመለከተች፣ታናሽ እህቷ ለስላሳ ቡናማ አይኖቿን ራሄል ላይ አንከባለለችባት፡፡ ራሄል በምላሽ ልቧ ሲዘል ተሰማት። ከዚያም ራቅ ብላ ተመለከተች።
ፀጋ ለእሷ ግዴታዋ ነበርች ይህች ልጅ ቀስ በቀስ የፍቅር እሳት በልቧ ዙሪያ እንዲቀጣጠል እያደረገች ነው። እንደ ፀጋ ካለች ልጅ ጋር መጣበቅ ማለት ልቧን ለህመም እና ማጣት እምቅ ስቃይ መከፈት ማለት እንደሆነ ታውቃለች።እና ያንን በራሷ ላይ እንደገና ማድረግ ፈፅሞ አትፈልግም ነበር ፡፡ግን ደግሞ በምርጫዋ እያደረገችው ያለ ነገር አይደለም፡፡ከአሰልቺ ጥበቃ በኃላ ነርሷ መጥታ በመጋረጃ ወደተሸፈነው ክፍል ወሰዳቻቸው። ራሄል እህቷን አልጋው ላይ በጥንቃቄ አስቀመጠቻት።ነርሷ የጥያቄዎችን ፣ የአለርጂዎችን ፣ የመድኃኒቶችን ዝርዝር ጠየቀቻት። ራሄል የምትችለውን ያህል መለሰች።እንደጨረሰች ነርሷ ጆሮዋ ውስጥ ቴርሞሜትር ጨመረች ..በዛ ቅፅበት አንድ ዶክተር ኮሪደሩን ሰንጥቆ ወደ እነርሱ ሲመጣ ተመለከተች። ነጭ ጋወን አድረጎ ስቴቶስኮፕ አንገቱ ላይ አንጠልጥሏል ።ኤሊ ነበር።
❤55
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ራሄልም እህቷን ይዛ እቤት እንደገባች ጓደኛዋ ሜሮን ቤት እየጠበቀቻት ነው፡፡መጀመሪያ ቀጠሮውን ለመሰረዝ ፈልጋ ነበር…በኋላ ስታስበው ግን ሴትዬዋ ለስብሰባው ትኩረት እንዳልሰጠች አድርጋ ልትረዳት እንደምትችል ስላሰበች ለመሄድ ወሰነች፡፡ ከሆስፒታል እንደተነሳች ነበር ደውላ ቤት እንድትጠብቃት የጠየቀቻት፡፡፡‹‹ቀጠሮው በጣም ወሳኝ ስለሆነ ነው ያስቸገርኩሽ፡፡››
‹‹አረ ችግር የለውም..ያንቺ እህት ማለት እኮ የእኔ እህት ነች››አለች ሜሮን፡፡
‹‹እሱስ እውነት ነው››
‹‹አዎ ደግሞም አሪፍ የምስራች አለኝ…››
‹‹እባክሽ ንገሪኝ ቀኑን ሙሉ ስጨናነቅ ነው የዋልኩት…ፈገግ ማለት አምሮኛል››
‹‹አንድ እምቅ ችሎታ ያላት እና በነርሲንግ የሰለጠነች ሞግዚት አግኝቼልሻለው›› አለቻት….ከሁለት ቀን በፊት ለሁሉም ጓደኞቾ ስለፀጋ ነግራቸው የሰለጠነች ሞግዚት እንዲፈልጉላት አደራ ብላቸው ነበር፡፡
‹‹አንቺ እኮ ሕይወት አድን ነሽ›› አለችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ጉንጯን ሳመቻት፡፡
ወደቀጠሮ ቦታ ይዛ የምትሄደቸውን ወረቀቶች ወደ ቦርሳዋ አስገባች።
‹‹ሞግዚት ማግኘት ከቻልኩ የፀጋ ዶ/ር የሰጠውን መመሪያ በሙሉ በጥንቃቄ እንዲተገበር ማድረግ እችላለው። ውዴ ለአሁን ፀጋን ልትጠብቂልኝ ስለወሰንሽ ደስተኛ ነኝ። ነገሮች ሁሉ ሰላም እንደሚሆኑ አምናለው?››
‹‹ሄይ. ታውቂያለሽ እኔ በጣም ጥሩ ጓደኛሽ ነኝ.››
‹‹ብቃት ያለው ሞግዚት አግኝተሸልኝማ ያንን መካድ አልችልም… በጣም ጥሩ ጓደኛ መሆን ብቻ ሳይሆን ህይወት አድንም ነሽ።››
‹‹ጥሩ እንደዛ ከሆነ እስኪ በመጠኑ ዘና ለማለት ሞክሪ….››
ራሄል ከወ.ሮ ላምሮት ጋር ላላት ቀጠሮ የምትጠቀምባቸውን መረጀጃዎች የያዙ ወረቀቶች እየለየች ‹‹ዘና ማለት እንኳን የምችል አይመስለኝም…ደክሞኛል… በአእምሮዬ ውስጥ ብዙ ነገሮች አሉ,››ስትል መለሰችላት፡፡ቀጥላም‹‹‹‹በፋውንዴሽን ውስጥ ነገሮች በጥሩ መንገድ እየሄዱ አይደለም ፡፡ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ሁለት ለጋሾችን አጥቻለሁ አሁን የምሄድባትን ሴትዬ ከዋና ለጋሾቻችን የመጀመሪያዋ ነች….እሷን የግድ ማሳመን አለብኝ ››
‹‹ለምን ሎዛ እንድትሰራው አታደርጊም?››
ራሄል ነገሩን በማሰብ ትንሽ ቆም ብላ ራሷን በአሉታ ነቀነቀች።‹‹ይህን ከባድ ኃላፊነት በእሷ ትከሻ ላይ መጣል አልችልም››
‹‹ስለዚህ በራስሽ ላይ ትጥያለሽ ..እሱ ችግር የለውም ማለት ነው?››
‹‹ትከሻዬ ከሷ የበለጠ ልምድ ያለው ነው›› አለች ፡፡
‹‹ጓደኛዬ ጥቂት ስራዎችን ለሌላ ሰው ብታስተላልፊ አለም አትገለባበጥም።እና ደግሞ የህይወት ሸክማችንን የሚያቀልልን ክርስቶስ ነው….በእሱ መታመን ችግራቸንን ያቀልልናል፡፡››
‹‹እና ለምን ያቺን አሁን በስቃይ የምታለቅሰውን ትንሽ ልጅ እንዲህ አጎጉል አደረጋት? በኢየሱስ አላምንም ብላ ይሆን ?››በራሄል ንግግር ሜሮን በጣም ደነገጠች፣
‹‹ራሄል .. አንቺ እኮ ከዚህ የበለጠ አስተዋይ ነሽ ››ራሄል እጇን ወደ ላይ ዘረጋች።
‹‹አዝናለሁ ስለ ኃጢአት እና ክፋት ሁሉን ነገር አውቃለሁ እናም እግዚአብሔር ሁሉንም ነገር በቁጥጥሩ ስር እንደሆነም አምናለው, ስለዚህ ስብከት አንዳትጀምሪኝ››
ሜሮን የጓደኛዋን ትከሻው በፍቅር እየዳበሰች‹‹ታውቂያለሽ አይደል …?ማመን ስለማትፈልጊ ብቻ ነው. እንዲህ የምትይው…ግን እወቂ አሁንም በኢየሱስ ጥበቃ ውስጥ ነሽ …አዎ፣ በግንኙነቶች ውስጥ ህመም አለ…በሆነ ግንኙነት ተሰብረን ሊሆን ይችላል፣ ቢሆንም ልባችንን ሁሌ ለፍቅር ክፍት መሆን አለበት ››
‹‹ደህና፣ አሁን ለልብ ጉዳዬች ጊዜ የለኝም።ደግሞ እስከአሁን ለእኔ የሚሆን ሰው አላጋጠመኝም።›› መስታወት አወጣች እና ሜካፕ እና ፀጉሯን በፍጥነት አስተካከለች።
ሜሮን ‹‹ዶ/ሩ በጣም የሚስብ ይመስለኛል››ስትል አዲስ ድንገተኛ ርዕስ ከፈተች፡፡
ራሄል የጓደኛዋን ሹፈት ችላ በማለት ቦርሳዋን አነሳችና ትከሻዋ ላይ አንጠለጠለች ፡፡
‹‹እሱ ማራኪ ነው…እንዳልኩሽ ግን ለጊዜው ለማንም ጊዜ የለኝም ።››በማለት መለሰችላት፡፡
ራሄል ወደ በሩ ስትሄድ ሜሮን ‹‹መልካም ጊዜ ይሁንልሽ›› ብላ ጮኸች።
////
ራሄል ከሴትዬዋ ጋር እያካሄደች ያለውን ስብሰባ አንድ ሰዓት በላይ ብታሳልፍም..እስከአሁን ሙሉ በሙሉ ልታሳምናት አልቻለችም፡፡
‹‹ባለቤቴ በዚህ ገንዘብ በጣም ነው የሚያምነኝ… እናም ይህን በትክክለኛው መንገድ ማድረግ ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹ይገባኛል››አለች ራሄል። ነገር ግን የባለቤቷትን እምነትን ለመጠበቅ ምርጡ መንገድ ገንዘቡን ለትክክለኛው ዓላማ ብቻ ለሚጠቀም በጎ አድራጎት መስጠት ነው።››
ወ.ሮ ላምሮት ፈገግ አለችላት፡፡
ወ.ሮ ላምሮት ራሄልን በትኩረት አየቻትና ‹‹አባትሽን ትመስያለሽ›› አለቻት። ‹‹እሱ በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ የሚሰራ የእግዚአብሔር ፍቅር ሁልጊዜ ምሳሌ ነው.››ስትል አከለችበት፡፡
ራሄል መራራ ህመም ተሰማት። ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ ከአምላክ ጋር ብዙ ጊዜ አላጠፋችም። የወ.ሮዋ ቃላት አብዝታ ወደ ጸለየችበት፣ መጽሐፍ ቅዱሷን በሰፊው ታንብበት ወደ ነበረችበት ጊዜ አመጣት። ቤተክርስቲያን እና እምነት የመተንፈስ ያህል የእርሷ አካል ነበር። እምነቷን መልሶ ለማግኘት እና በአምላክ ላይ መታመን ለምን እንደሚያስፈልጓት አሰበች። ››
በወ.ሮ ላምሮት ፈገግ ብላ ሰዓቷን በጥበብ ተመለከተች። ለመውጣት ጊዜው ነበር፡፡
‹‹እኔ እንዳልኩት፣ እባኮት ይህን በትክክለኛው መንገድ ለማድረግ ትንሽ ጊዜ ስጡኝ..ያንን ብቻ ነው የምጠይቀው››አለች ራሄል፣
ወ.ሮ ላምሮት ከግዙፉ መኖሪያ ቤቷ ስትሸኛት ራሄል የመጨረሻ የማሳመኛ ንግግሯን ተናገረች‹‹እርግጠኛ ነኝ .. ባለቤቷት በዚህ ጉዳይ ላይ እንዲቸኩሉ አይፈልግም ››
ነገር ግን ከወ.ሮዋ ፊት ምንም ነገር ማንበብ አልቻለችም ፡፡ሴትዬዋን ለማሳመን የተቻላትን ሁሉ አድርጋለች..ግን ይሳካላት አይሳካላት መገመት ስላልቻለች በጣም ተበሳጨች ፣ መኪናውን አስነሳችና ወደቤቷ ነዳችው…መኪናዋን አቁማ ወደአፓርታማዋ ተጠጋች… የአሳንሰሩን ቁልፍ ተጫነች እና ገባች፤ውስጥ ያልጠበቀችውን ሰው አገኘች፡፡የቆዳ ጃኬት ለብሶ ነበር። የሞተር ሳይክል ሄልሜት በእጁ ይዟል።
‹‹ሰላም. እዚህ ምን እየሰራህ ነው?››ብላ ጠየቀችው፣ እስትንፋሶ ተቆራረጠባት፡፡
‹‹በቃ ጎራ ብዬ ከፀጋ ጋር እንዴት እየተለማመድሽ እንዳለሽ ለማየት አስቤ ነበር።››
‹‹ጥሩ አደረክ››አለችው
‹‹ወደ ውጭ ወጥተሽ ነበር?››
‹‹አዎ ጠቃሚ ስብሰባ ነበረኝ›
‹‹እንደ ሁሉም ስብሰባዎችሽ››አለ
‹‹አይዞህ አታስብ ጓደኛዬ በጣም ብቃት ያለት ሞግዚት ነች።እርግጠኛ ነኝ እሷ ከእኔ በተሻለ ከፀጋ ጋር ትግባባለች።››ሊፍት ሲቆም ወደ ኋላ ዞር አለላት።ራሄል ቀድማ ወጣች..ተከተላት፡፡ ኮሪደሩን እንደረገጡ የሚያለቅስ የህፃን ድምፅ በሁለቱም ጆሮ ገባ። የመጣው ከራሷ ቤት ነው።ሁለቱም ርምጃቸውን አፈጠኑና ተከታትለው ወደቤት ገቡ ፡፡ሜሮን የምትጮኸውን ፀጋን ተሸክማ እቤት ውስጥ ከወዲህ ወዲያ ትሽከረከራለች፣ የልጁቷ ክንዶች በሜሮን ጀርባ ላይ ተዝለፍልፋው ይታያሉ፡፡
ራሄል ቦርሳዋን ጥላ ወደ ጓደኛዋ ሮጣ ሄደች። ጸጋ ራሄልን እንዳየች ከሜሮን እቅፍ ውስጥ ተስፈንጥራ እጇን ዘረጋች። እንባዋ በጉንጮቾ እየተንከባለሉ በመርገፍ ላይ ናቸው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ራሄልም እህቷን ይዛ እቤት እንደገባች ጓደኛዋ ሜሮን ቤት እየጠበቀቻት ነው፡፡መጀመሪያ ቀጠሮውን ለመሰረዝ ፈልጋ ነበር…በኋላ ስታስበው ግን ሴትዬዋ ለስብሰባው ትኩረት እንዳልሰጠች አድርጋ ልትረዳት እንደምትችል ስላሰበች ለመሄድ ወሰነች፡፡ ከሆስፒታል እንደተነሳች ነበር ደውላ ቤት እንድትጠብቃት የጠየቀቻት፡፡፡‹‹ቀጠሮው በጣም ወሳኝ ስለሆነ ነው ያስቸገርኩሽ፡፡››
‹‹አረ ችግር የለውም..ያንቺ እህት ማለት እኮ የእኔ እህት ነች››አለች ሜሮን፡፡
‹‹እሱስ እውነት ነው››
‹‹አዎ ደግሞም አሪፍ የምስራች አለኝ…››
‹‹እባክሽ ንገሪኝ ቀኑን ሙሉ ስጨናነቅ ነው የዋልኩት…ፈገግ ማለት አምሮኛል››
‹‹አንድ እምቅ ችሎታ ያላት እና በነርሲንግ የሰለጠነች ሞግዚት አግኝቼልሻለው›› አለቻት….ከሁለት ቀን በፊት ለሁሉም ጓደኞቾ ስለፀጋ ነግራቸው የሰለጠነች ሞግዚት እንዲፈልጉላት አደራ ብላቸው ነበር፡፡
‹‹አንቺ እኮ ሕይወት አድን ነሽ›› አለችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ጉንጯን ሳመቻት፡፡
ወደቀጠሮ ቦታ ይዛ የምትሄደቸውን ወረቀቶች ወደ ቦርሳዋ አስገባች።
‹‹ሞግዚት ማግኘት ከቻልኩ የፀጋ ዶ/ር የሰጠውን መመሪያ በሙሉ በጥንቃቄ እንዲተገበር ማድረግ እችላለው። ውዴ ለአሁን ፀጋን ልትጠብቂልኝ ስለወሰንሽ ደስተኛ ነኝ። ነገሮች ሁሉ ሰላም እንደሚሆኑ አምናለው?››
‹‹ሄይ. ታውቂያለሽ እኔ በጣም ጥሩ ጓደኛሽ ነኝ.››
‹‹ብቃት ያለው ሞግዚት አግኝተሸልኝማ ያንን መካድ አልችልም… በጣም ጥሩ ጓደኛ መሆን ብቻ ሳይሆን ህይወት አድንም ነሽ።››
‹‹ጥሩ እንደዛ ከሆነ እስኪ በመጠኑ ዘና ለማለት ሞክሪ….››
ራሄል ከወ.ሮ ላምሮት ጋር ላላት ቀጠሮ የምትጠቀምባቸውን መረጀጃዎች የያዙ ወረቀቶች እየለየች ‹‹ዘና ማለት እንኳን የምችል አይመስለኝም…ደክሞኛል… በአእምሮዬ ውስጥ ብዙ ነገሮች አሉ,››ስትል መለሰችላት፡፡ቀጥላም‹‹‹‹በፋውንዴሽን ውስጥ ነገሮች በጥሩ መንገድ እየሄዱ አይደለም ፡፡ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ሁለት ለጋሾችን አጥቻለሁ አሁን የምሄድባትን ሴትዬ ከዋና ለጋሾቻችን የመጀመሪያዋ ነች….እሷን የግድ ማሳመን አለብኝ ››
‹‹ለምን ሎዛ እንድትሰራው አታደርጊም?››
ራሄል ነገሩን በማሰብ ትንሽ ቆም ብላ ራሷን በአሉታ ነቀነቀች።‹‹ይህን ከባድ ኃላፊነት በእሷ ትከሻ ላይ መጣል አልችልም››
‹‹ስለዚህ በራስሽ ላይ ትጥያለሽ ..እሱ ችግር የለውም ማለት ነው?››
‹‹ትከሻዬ ከሷ የበለጠ ልምድ ያለው ነው›› አለች ፡፡
‹‹ጓደኛዬ ጥቂት ስራዎችን ለሌላ ሰው ብታስተላልፊ አለም አትገለባበጥም።እና ደግሞ የህይወት ሸክማችንን የሚያቀልልን ክርስቶስ ነው….በእሱ መታመን ችግራቸንን ያቀልልናል፡፡››
‹‹እና ለምን ያቺን አሁን በስቃይ የምታለቅሰውን ትንሽ ልጅ እንዲህ አጎጉል አደረጋት? በኢየሱስ አላምንም ብላ ይሆን ?››በራሄል ንግግር ሜሮን በጣም ደነገጠች፣
‹‹ራሄል .. አንቺ እኮ ከዚህ የበለጠ አስተዋይ ነሽ ››ራሄል እጇን ወደ ላይ ዘረጋች።
‹‹አዝናለሁ ስለ ኃጢአት እና ክፋት ሁሉን ነገር አውቃለሁ እናም እግዚአብሔር ሁሉንም ነገር በቁጥጥሩ ስር እንደሆነም አምናለው, ስለዚህ ስብከት አንዳትጀምሪኝ››
ሜሮን የጓደኛዋን ትከሻው በፍቅር እየዳበሰች‹‹ታውቂያለሽ አይደል …?ማመን ስለማትፈልጊ ብቻ ነው. እንዲህ የምትይው…ግን እወቂ አሁንም በኢየሱስ ጥበቃ ውስጥ ነሽ …አዎ፣ በግንኙነቶች ውስጥ ህመም አለ…በሆነ ግንኙነት ተሰብረን ሊሆን ይችላል፣ ቢሆንም ልባችንን ሁሌ ለፍቅር ክፍት መሆን አለበት ››
‹‹ደህና፣ አሁን ለልብ ጉዳዬች ጊዜ የለኝም።ደግሞ እስከአሁን ለእኔ የሚሆን ሰው አላጋጠመኝም።›› መስታወት አወጣች እና ሜካፕ እና ፀጉሯን በፍጥነት አስተካከለች።
ሜሮን ‹‹ዶ/ሩ በጣም የሚስብ ይመስለኛል››ስትል አዲስ ድንገተኛ ርዕስ ከፈተች፡፡
ራሄል የጓደኛዋን ሹፈት ችላ በማለት ቦርሳዋን አነሳችና ትከሻዋ ላይ አንጠለጠለች ፡፡
‹‹እሱ ማራኪ ነው…እንዳልኩሽ ግን ለጊዜው ለማንም ጊዜ የለኝም ።››በማለት መለሰችላት፡፡
ራሄል ወደ በሩ ስትሄድ ሜሮን ‹‹መልካም ጊዜ ይሁንልሽ›› ብላ ጮኸች።
////
ራሄል ከሴትዬዋ ጋር እያካሄደች ያለውን ስብሰባ አንድ ሰዓት በላይ ብታሳልፍም..እስከአሁን ሙሉ በሙሉ ልታሳምናት አልቻለችም፡፡
‹‹ባለቤቴ በዚህ ገንዘብ በጣም ነው የሚያምነኝ… እናም ይህን በትክክለኛው መንገድ ማድረግ ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹ይገባኛል››አለች ራሄል። ነገር ግን የባለቤቷትን እምነትን ለመጠበቅ ምርጡ መንገድ ገንዘቡን ለትክክለኛው ዓላማ ብቻ ለሚጠቀም በጎ አድራጎት መስጠት ነው።››
ወ.ሮ ላምሮት ፈገግ አለችላት፡፡
ወ.ሮ ላምሮት ራሄልን በትኩረት አየቻትና ‹‹አባትሽን ትመስያለሽ›› አለቻት። ‹‹እሱ በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ የሚሰራ የእግዚአብሔር ፍቅር ሁልጊዜ ምሳሌ ነው.››ስትል አከለችበት፡፡
ራሄል መራራ ህመም ተሰማት። ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ ከአምላክ ጋር ብዙ ጊዜ አላጠፋችም። የወ.ሮዋ ቃላት አብዝታ ወደ ጸለየችበት፣ መጽሐፍ ቅዱሷን በሰፊው ታንብበት ወደ ነበረችበት ጊዜ አመጣት። ቤተክርስቲያን እና እምነት የመተንፈስ ያህል የእርሷ አካል ነበር። እምነቷን መልሶ ለማግኘት እና በአምላክ ላይ መታመን ለምን እንደሚያስፈልጓት አሰበች። ››
በወ.ሮ ላምሮት ፈገግ ብላ ሰዓቷን በጥበብ ተመለከተች። ለመውጣት ጊዜው ነበር፡፡
‹‹እኔ እንዳልኩት፣ እባኮት ይህን በትክክለኛው መንገድ ለማድረግ ትንሽ ጊዜ ስጡኝ..ያንን ብቻ ነው የምጠይቀው››አለች ራሄል፣
ወ.ሮ ላምሮት ከግዙፉ መኖሪያ ቤቷ ስትሸኛት ራሄል የመጨረሻ የማሳመኛ ንግግሯን ተናገረች‹‹እርግጠኛ ነኝ .. ባለቤቷት በዚህ ጉዳይ ላይ እንዲቸኩሉ አይፈልግም ››
ነገር ግን ከወ.ሮዋ ፊት ምንም ነገር ማንበብ አልቻለችም ፡፡ሴትዬዋን ለማሳመን የተቻላትን ሁሉ አድርጋለች..ግን ይሳካላት አይሳካላት መገመት ስላልቻለች በጣም ተበሳጨች ፣ መኪናውን አስነሳችና ወደቤቷ ነዳችው…መኪናዋን አቁማ ወደአፓርታማዋ ተጠጋች… የአሳንሰሩን ቁልፍ ተጫነች እና ገባች፤ውስጥ ያልጠበቀችውን ሰው አገኘች፡፡የቆዳ ጃኬት ለብሶ ነበር። የሞተር ሳይክል ሄልሜት በእጁ ይዟል።
‹‹ሰላም. እዚህ ምን እየሰራህ ነው?››ብላ ጠየቀችው፣ እስትንፋሶ ተቆራረጠባት፡፡
‹‹በቃ ጎራ ብዬ ከፀጋ ጋር እንዴት እየተለማመድሽ እንዳለሽ ለማየት አስቤ ነበር።››
‹‹ጥሩ አደረክ››አለችው
‹‹ወደ ውጭ ወጥተሽ ነበር?››
‹‹አዎ ጠቃሚ ስብሰባ ነበረኝ›
‹‹እንደ ሁሉም ስብሰባዎችሽ››አለ
‹‹አይዞህ አታስብ ጓደኛዬ በጣም ብቃት ያለት ሞግዚት ነች።እርግጠኛ ነኝ እሷ ከእኔ በተሻለ ከፀጋ ጋር ትግባባለች።››ሊፍት ሲቆም ወደ ኋላ ዞር አለላት።ራሄል ቀድማ ወጣች..ተከተላት፡፡ ኮሪደሩን እንደረገጡ የሚያለቅስ የህፃን ድምፅ በሁለቱም ጆሮ ገባ። የመጣው ከራሷ ቤት ነው።ሁለቱም ርምጃቸውን አፈጠኑና ተከታትለው ወደቤት ገቡ ፡፡ሜሮን የምትጮኸውን ፀጋን ተሸክማ እቤት ውስጥ ከወዲህ ወዲያ ትሽከረከራለች፣ የልጁቷ ክንዶች በሜሮን ጀርባ ላይ ተዝለፍልፋው ይታያሉ፡፡
ራሄል ቦርሳዋን ጥላ ወደ ጓደኛዋ ሮጣ ሄደች። ጸጋ ራሄልን እንዳየች ከሜሮን እቅፍ ውስጥ ተስፈንጥራ እጇን ዘረጋች። እንባዋ በጉንጮቾ እየተንከባለሉ በመርገፍ ላይ ናቸው፡፡
❤55👍3🥰1👏1😢1
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ወደ ሆስፒታሉ በሚወስደው መንገድ ላይ ሞተሩን እያስጎራ በመብረር ላይ ነው፡፡ ሀሳቡ ግን አሁንም ወደኋላ እየጎተተው ነው፡፡ በዚህ የሰንበት ማለዳ ወደእነራሄል ወላጆች ቤት የሄድኩት ራሄል ፀጋን እንዴት እያስተዳደረች እንደሆነ ለማየት ብቻ ነበር። ጉብኝቱ የህፃኗ ሐኪም በመሆኔ ያደረግኩት ነው።››ሲል ለራሱ ነገረው፡
አሁን፣ ፀጉሯን በትና እና የደበዘዘ ቲሸርት የለበሰች እንዲት ቆንጆ ሴት በአእምሮው ሰሌዳ ላይ ብልጭ ድርግም እያለች እየረበሸችው ነው፡፡ በባዶ እግሯ እና በሰማያዊ ጂንስዋ ምን ያህል ውብ እንደሆነች እያሰበ ነበር፣እሷ የምትኖርበትን ቤት እንዴት ግዙፍ እንደሆነ እና ወላጆቿ ምን ያህል ገንዘብ እንዳላቸው እያሰበ ነበር። እና የተከበረ የመኳንንት ዝርያ አለን ብለው የሚያስቡ ወላጇች እንዳሏት እያሰበ ነበር… እና ደግሞ እሱ ሰለወላጇቹ ምን ይሁኑ ምን የሚያውቀው ነገር እንደሌለም እያሰበ ነበር፡፡በዚህም ሆነ በዚያ ሀሳቡ በራሄል ዙሪያ ከመሽከርከር ሊያቅበው አልተቻለውም፡፡
ኤልያስ አሳዳጊ ወላጆቹ ስለስጋ ወላጇቹ ብዙ ጊዜ አይናገሩም ወይም የበለጠ እንዲያውቅ አያበረታቱትም። ወደፊት ፀጋም ልክ እንደእሱ ስለ እናቷ እና አባቷ ማወቅ እንደምትፈልግ ገመተ።ስለ ፀጋ ማሰቡ በትክክል ወደ ራሄል መለሰው።ሸሩባ የተሰራው ጥቁር ፀጉሯ ፊቷን እንዴት እንደአሳመረው እና ሀዘን ያጠላባቸው ጎላ ጎላ ያሉ አይኖቿ ከብለል ሲሉ እንዴት ልብን እንደሚያርዱ አሰበ። ሆስፒታል ደርሶ ሞተሩን ሲያቆም እንኳ ሀሳብን መግታት አልቻለም ነበር፡፡
///
ራሄል ትሁት ቁርስ ስትበላ ፊቷ ላይ የተዝረከረከውን በደረቅ ጨርቅ በጥንቃቄ ጠራረገችላት። እቃዎችን እያጣጠበች ሳለ ፀጋ ወደ በረንዳ በሮች ስትሄድ አየች። ሰራተኛዋ አለም ሁል ጊዜ መስኮቶቹን በሚያብረቀርቅ ንፅህና ነው የምትይዛቸው ፣ ዛሬ ግን እሷና ፀጋ ብቻቸውን ናቸው..ሰራተኛዋ የረፍት ቀኗ ስለሆነ ዘመድ ጥየቃ ሄዳለች።እቃ ማጠቧን እንዳጠናቀቀች..ትንሿን እህቷን ለማየት ወደበረንዳ ስትወጣ የጸጋ ትንሽዬ የእጅ ህትመቶች መስታወቱን ጠቅላላ አዳርሰውት ሌላ ቅርፅ ሰጥተውት አገኘች፡፡ መጀመሪያ መልሳ ለማፅዳት ስትሞከር ፀጋ ከኋላዋ እየተከተለች መልሳ ስታቆሽሽባት…በመናደድ ፋንታ ከት ብላ ሳቀችና ማፅዳቱን እርግፍ አድርጋ ተወችው፡፡
‹‹ከአንድ በላይ ልጅ ያላቸው ሰዎች እንዴት በህይወት መቆየት ቻሉ?››ስትል ገረሜታዋን ገለፀች ፡፡ከፀጋ ጋር በቀጣይ ምን ማድረግ እንደምትችል አሰበች.. ።ሰዓቱን ተመለከተች, ከዚያም ወደ እሷ ተመለሰች. ወላጆቿ ዘወትር እሁድ ወደ ቤተ ክርስቲያን እንደሚሄዱ ታውቃለች። ወጣት ሳለች ሁልጊዜ አብራቸው ትሄድ ነበር፣ ነገር ግን እጮኛዋ ኪሩቤል ከሞተ በኋላ ወደቤተክርስቲያን መሄዱን እርግፍ አድርጋ ተወችው፡፡ ይህ ድርጊቷ ወላጆቿን በጣም እንደሚያበሳጫቸው ታውቃለች፣ እነሱ ስለሚፈልጉ ብቻ ነገሮችን ማድረግ እንዳለባት አታምንም። እሷ የራሷን ሕይወት እየመራች ነበር፣ እና እግዚአብሔር የህይወቷ አካል አይደለም።
ፀጋን ስትመለከት ግን በድንገት ተጨማሪ ሀላፊነት እንዳለባት ተሰማት። በእርግጥ የሁለት ዓመት ልጅ ነበረች፣ … ስለግል እምነቷ ለራሷ ውሳኔ ማድረግ እንደምትችል ብታምንም ለዚህች ልጅም ተመሳሳይ ነገር ማድረጉ ትክክል ሆኖ አልተሰማትም።ወላጇቾ ቢኖሩ ይዘዋት እንደሚሄዱ እርግጠኛ ነች፡፡
‹ስለዚህ ወደ ፀጋ ጎንበስ አለችና‹‹የእኔ ቆንጅዬ እህት .. ወደ ቤተ ክርስቲያን መሄድ ትፈልጊያለሽ?›› ብላ ጠየቀቻት ፡፡
ህፃኗ በደስታ እየዘለለች‹‹ቤተክርስትያን እንሂድ፣ ቤተክርስትያን እንሂድ››አለች ፡፡ ራሄልም ልብሷን ቀያይራ ካለባበሰቻት በኋላ ወደቤተክርስቲያን ይዛት ሄደች፡፡
ራሄል የኮሌጅ ትምህርቷን እስካጠናቀቀች ድረስ ንቁ ተሳታፊ ነበረች።ሁሉ ነገር የተቀየረው እጮኛዋ ከሞት በኋላ ነው።እና አሁን የመቅደሱ ዙሪያ ስትመለከት፣ የልጅነትና የጉልምስና ትውስታዎች ሁሉ ተግተልትለው በአእምሯ ውስጥ ብልጭ ድርግም አሉባት። የዚህ ቤተክርስቲያን መዘምራን አባል ሆና ለረጅም አመት አገልግላለች ፤እዚህ መድረክ ላይ ወጥታ ስለጌታ የአዳኝነት ስራ ስትዘምር ትዝ ይላታል፡፡ ድምፆ ተስረቅራቂ የሚባል አይነት ስለነበር ብዙውን ጊዜ ድምጽ ማጉያውን ይዛ መዝምራኖችን የምትመራው እሷ ነበረች፡፡እጮኛዋ ኪሩቤልንም እዚሁ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው የተዋወቀችው፡፡እሱም ልክ እንደ እሷ የቤተክርስቲያን አገልጋይ ነበር…. ከዚያ ከመቀራረብና አብሮ ከመዋል ብዛት የፍቅር ስሜት በመሀከላቸው ተፈጠረ፡፡በቤተክርስቲያኒቷ ፊት ቃልኪዳን ተግባቡ …ሀይስኩል ጨረሱ ..ኮሌጅ ገቡ….እስከዛን ድረስ ሁለቱም በእምነታቸው የፀኑ ወጣቶች ነበሩ…ሁሉን ነገር ሀይማኖቱ በሚያዘው እና ቤተሰቦቻቸው በሚደሰቱበት አግባብ ለማድረግ ነበር እቅዳቸው…ሰርጋቸውን ባደጉበትና ባገለገሉበት ቤተክርስቲያን አደባባይ ላይ ለማድረግ ነበር ውጥናቸውና ጉጉታቸውም…ግን ምን ሆነ ህልማቸውን ሊኖሩ ወራት ሲቀራቸው..፣ኪሩቤል ድንገት ከእሷ ጋር ወደተቀጣጠረበት ቦታ ሞተር ሳይክሉን እያበረረ ሲመጣ እየተክለፈለፍ በፍጥነት ከሚያበር መኪና ጋር ተላትሞ በከፍተኛ ጉዳት ሆስፒታል ገባ…ይድንልኛል..መልሶ በእግሮቹ ቆሞ እንጋባላን ብላ ሆስፒታል ደረቅ ወንበር ላይ እየተኛች አንድ ወር ከግማሽ አካባቢ አስታመመችው…ግን አልተሳካም….የኪሩቤል ነፍስ ወደፈጣሪዋ ተጠርታ ሄደች..ከዛ ወዲህ ራሄል ሙሉ በሙሉ ሌላ ሰው ሆነች…ሆስፒታል አስጠላት…የመድሀኒት ሽታ ቀፈፋት…ቤተክርስቲያንና እምነት አንገሸገሻት..የታመመ ሰው ማየት አቃታት…ይሄው አሁን ለታናሽ እህቷ ስትል እዚህ ያደገችበት ቤተክርስቲያን ስትመጣ ቁስሏ ሁሉ ክፉኛ ተቀሰቀሰ፡፡ እና የሚቀስፍ አይነት ህመም ተሰማት፣ ከዚሁ ሁሉ በጣም የሚገርመው ግን ለአፍታ ያህል ኪሩቤል ምን እንደሚመስል እንኳ ማስታወስ አለመቻሏ ነው ። ከሞቱ በኋላ አብዛኛዎቹን የኪሩቤልን ምስሎች በወላጆቿ ቤት አስቀምጧቸው ነበር እና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አልተመለከቷቸውም። በጣም ተጎድታ ነበር። አሁን ምን እንደሚሰማት ግራ ተገባች።በመጨረሻም ጓዳኛዋ ሌንሳ ከወላጆቿ እና ከሁለት መንታ ልጇቾ ጋር ተቀምጣ አየች። ራሄል ከጎኗ ሾልካ ገባች።
‹‹ቤተክርስትያን መሄድ እርግፍ አድርገሽ የተውሽ መስሎኝ ነበር›› ስትል ወደጀ ጆሮዋ ቀርባ አንሾካሾከችላት፡፡
ሌንሳ ወደኋላ ዞረችና እያወራቻት ያለችው ራሄል መሆኗን ስታውቅ በመገረም ‹‹ራሄል እዚህ ምን እየሰራሽ ነው?›› ስትል ወደኋላ ተስባ አቀፈቻት፡፡
‹‹ፀጋን ማምጣት እንዳለብኝ ተሰማኝ››ስትል የመጣችበትን ምክንያት ነገረቻት፡፡
‹‹እሺ በምንም ምክንያት ይሁን በምንም እዚህ በመገኘትሽ ደስ ብሎኛል.››
የሌንሳ ወላጆችም በደስታ ሰላም አሏት፡፡
ዝግጅቱ እናዳለቀ ፀጋን እንዳቀፈች እነ ለሌንሳን ተከትላ ወደአውደ ምህረቱ ሄደች…ከረጅም ጊዜ በፊት የምታውቃቸውን በጣም ብዙ የድሮ ጎደኞቾንና ወዳጆቾን አገኘች፡፡ ብዙ ሰው ለምን እንደጠፋች እየጠየቃት በመምጣቷ እንደተደሰቱ ይነግሯት ነበር፡፡
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ወደ ሆስፒታሉ በሚወስደው መንገድ ላይ ሞተሩን እያስጎራ በመብረር ላይ ነው፡፡ ሀሳቡ ግን አሁንም ወደኋላ እየጎተተው ነው፡፡ በዚህ የሰንበት ማለዳ ወደእነራሄል ወላጆች ቤት የሄድኩት ራሄል ፀጋን እንዴት እያስተዳደረች እንደሆነ ለማየት ብቻ ነበር። ጉብኝቱ የህፃኗ ሐኪም በመሆኔ ያደረግኩት ነው።››ሲል ለራሱ ነገረው፡
አሁን፣ ፀጉሯን በትና እና የደበዘዘ ቲሸርት የለበሰች እንዲት ቆንጆ ሴት በአእምሮው ሰሌዳ ላይ ብልጭ ድርግም እያለች እየረበሸችው ነው፡፡ በባዶ እግሯ እና በሰማያዊ ጂንስዋ ምን ያህል ውብ እንደሆነች እያሰበ ነበር፣እሷ የምትኖርበትን ቤት እንዴት ግዙፍ እንደሆነ እና ወላጆቿ ምን ያህል ገንዘብ እንዳላቸው እያሰበ ነበር። እና የተከበረ የመኳንንት ዝርያ አለን ብለው የሚያስቡ ወላጇች እንዳሏት እያሰበ ነበር… እና ደግሞ እሱ ሰለወላጇቹ ምን ይሁኑ ምን የሚያውቀው ነገር እንደሌለም እያሰበ ነበር፡፡በዚህም ሆነ በዚያ ሀሳቡ በራሄል ዙሪያ ከመሽከርከር ሊያቅበው አልተቻለውም፡፡
ኤልያስ አሳዳጊ ወላጆቹ ስለስጋ ወላጇቹ ብዙ ጊዜ አይናገሩም ወይም የበለጠ እንዲያውቅ አያበረታቱትም። ወደፊት ፀጋም ልክ እንደእሱ ስለ እናቷ እና አባቷ ማወቅ እንደምትፈልግ ገመተ።ስለ ፀጋ ማሰቡ በትክክል ወደ ራሄል መለሰው።ሸሩባ የተሰራው ጥቁር ፀጉሯ ፊቷን እንዴት እንደአሳመረው እና ሀዘን ያጠላባቸው ጎላ ጎላ ያሉ አይኖቿ ከብለል ሲሉ እንዴት ልብን እንደሚያርዱ አሰበ። ሆስፒታል ደርሶ ሞተሩን ሲያቆም እንኳ ሀሳብን መግታት አልቻለም ነበር፡፡
///
ራሄል ትሁት ቁርስ ስትበላ ፊቷ ላይ የተዝረከረከውን በደረቅ ጨርቅ በጥንቃቄ ጠራረገችላት። እቃዎችን እያጣጠበች ሳለ ፀጋ ወደ በረንዳ በሮች ስትሄድ አየች። ሰራተኛዋ አለም ሁል ጊዜ መስኮቶቹን በሚያብረቀርቅ ንፅህና ነው የምትይዛቸው ፣ ዛሬ ግን እሷና ፀጋ ብቻቸውን ናቸው..ሰራተኛዋ የረፍት ቀኗ ስለሆነ ዘመድ ጥየቃ ሄዳለች።እቃ ማጠቧን እንዳጠናቀቀች..ትንሿን እህቷን ለማየት ወደበረንዳ ስትወጣ የጸጋ ትንሽዬ የእጅ ህትመቶች መስታወቱን ጠቅላላ አዳርሰውት ሌላ ቅርፅ ሰጥተውት አገኘች፡፡ መጀመሪያ መልሳ ለማፅዳት ስትሞከር ፀጋ ከኋላዋ እየተከተለች መልሳ ስታቆሽሽባት…በመናደድ ፋንታ ከት ብላ ሳቀችና ማፅዳቱን እርግፍ አድርጋ ተወችው፡፡
‹‹ከአንድ በላይ ልጅ ያላቸው ሰዎች እንዴት በህይወት መቆየት ቻሉ?››ስትል ገረሜታዋን ገለፀች ፡፡ከፀጋ ጋር በቀጣይ ምን ማድረግ እንደምትችል አሰበች.. ።ሰዓቱን ተመለከተች, ከዚያም ወደ እሷ ተመለሰች. ወላጆቿ ዘወትር እሁድ ወደ ቤተ ክርስቲያን እንደሚሄዱ ታውቃለች። ወጣት ሳለች ሁልጊዜ አብራቸው ትሄድ ነበር፣ ነገር ግን እጮኛዋ ኪሩቤል ከሞተ በኋላ ወደቤተክርስቲያን መሄዱን እርግፍ አድርጋ ተወችው፡፡ ይህ ድርጊቷ ወላጆቿን በጣም እንደሚያበሳጫቸው ታውቃለች፣ እነሱ ስለሚፈልጉ ብቻ ነገሮችን ማድረግ እንዳለባት አታምንም። እሷ የራሷን ሕይወት እየመራች ነበር፣ እና እግዚአብሔር የህይወቷ አካል አይደለም።
ፀጋን ስትመለከት ግን በድንገት ተጨማሪ ሀላፊነት እንዳለባት ተሰማት። በእርግጥ የሁለት ዓመት ልጅ ነበረች፣ … ስለግል እምነቷ ለራሷ ውሳኔ ማድረግ እንደምትችል ብታምንም ለዚህች ልጅም ተመሳሳይ ነገር ማድረጉ ትክክል ሆኖ አልተሰማትም።ወላጇቾ ቢኖሩ ይዘዋት እንደሚሄዱ እርግጠኛ ነች፡፡
‹ስለዚህ ወደ ፀጋ ጎንበስ አለችና‹‹የእኔ ቆንጅዬ እህት .. ወደ ቤተ ክርስቲያን መሄድ ትፈልጊያለሽ?›› ብላ ጠየቀቻት ፡፡
ህፃኗ በደስታ እየዘለለች‹‹ቤተክርስትያን እንሂድ፣ ቤተክርስትያን እንሂድ››አለች ፡፡ ራሄልም ልብሷን ቀያይራ ካለባበሰቻት በኋላ ወደቤተክርስቲያን ይዛት ሄደች፡፡
ራሄል የኮሌጅ ትምህርቷን እስካጠናቀቀች ድረስ ንቁ ተሳታፊ ነበረች።ሁሉ ነገር የተቀየረው እጮኛዋ ከሞት በኋላ ነው።እና አሁን የመቅደሱ ዙሪያ ስትመለከት፣ የልጅነትና የጉልምስና ትውስታዎች ሁሉ ተግተልትለው በአእምሯ ውስጥ ብልጭ ድርግም አሉባት። የዚህ ቤተክርስቲያን መዘምራን አባል ሆና ለረጅም አመት አገልግላለች ፤እዚህ መድረክ ላይ ወጥታ ስለጌታ የአዳኝነት ስራ ስትዘምር ትዝ ይላታል፡፡ ድምፆ ተስረቅራቂ የሚባል አይነት ስለነበር ብዙውን ጊዜ ድምጽ ማጉያውን ይዛ መዝምራኖችን የምትመራው እሷ ነበረች፡፡እጮኛዋ ኪሩቤልንም እዚሁ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው የተዋወቀችው፡፡እሱም ልክ እንደ እሷ የቤተክርስቲያን አገልጋይ ነበር…. ከዚያ ከመቀራረብና አብሮ ከመዋል ብዛት የፍቅር ስሜት በመሀከላቸው ተፈጠረ፡፡በቤተክርስቲያኒቷ ፊት ቃልኪዳን ተግባቡ …ሀይስኩል ጨረሱ ..ኮሌጅ ገቡ….እስከዛን ድረስ ሁለቱም በእምነታቸው የፀኑ ወጣቶች ነበሩ…ሁሉን ነገር ሀይማኖቱ በሚያዘው እና ቤተሰቦቻቸው በሚደሰቱበት አግባብ ለማድረግ ነበር እቅዳቸው…ሰርጋቸውን ባደጉበትና ባገለገሉበት ቤተክርስቲያን አደባባይ ላይ ለማድረግ ነበር ውጥናቸውና ጉጉታቸውም…ግን ምን ሆነ ህልማቸውን ሊኖሩ ወራት ሲቀራቸው..፣ኪሩቤል ድንገት ከእሷ ጋር ወደተቀጣጠረበት ቦታ ሞተር ሳይክሉን እያበረረ ሲመጣ እየተክለፈለፍ በፍጥነት ከሚያበር መኪና ጋር ተላትሞ በከፍተኛ ጉዳት ሆስፒታል ገባ…ይድንልኛል..መልሶ በእግሮቹ ቆሞ እንጋባላን ብላ ሆስፒታል ደረቅ ወንበር ላይ እየተኛች አንድ ወር ከግማሽ አካባቢ አስታመመችው…ግን አልተሳካም….የኪሩቤል ነፍስ ወደፈጣሪዋ ተጠርታ ሄደች..ከዛ ወዲህ ራሄል ሙሉ በሙሉ ሌላ ሰው ሆነች…ሆስፒታል አስጠላት…የመድሀኒት ሽታ ቀፈፋት…ቤተክርስቲያንና እምነት አንገሸገሻት..የታመመ ሰው ማየት አቃታት…ይሄው አሁን ለታናሽ እህቷ ስትል እዚህ ያደገችበት ቤተክርስቲያን ስትመጣ ቁስሏ ሁሉ ክፉኛ ተቀሰቀሰ፡፡ እና የሚቀስፍ አይነት ህመም ተሰማት፣ ከዚሁ ሁሉ በጣም የሚገርመው ግን ለአፍታ ያህል ኪሩቤል ምን እንደሚመስል እንኳ ማስታወስ አለመቻሏ ነው ። ከሞቱ በኋላ አብዛኛዎቹን የኪሩቤልን ምስሎች በወላጆቿ ቤት አስቀምጧቸው ነበር እና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አልተመለከቷቸውም። በጣም ተጎድታ ነበር። አሁን ምን እንደሚሰማት ግራ ተገባች።በመጨረሻም ጓዳኛዋ ሌንሳ ከወላጆቿ እና ከሁለት መንታ ልጇቾ ጋር ተቀምጣ አየች። ራሄል ከጎኗ ሾልካ ገባች።
‹‹ቤተክርስትያን መሄድ እርግፍ አድርገሽ የተውሽ መስሎኝ ነበር›› ስትል ወደጀ ጆሮዋ ቀርባ አንሾካሾከችላት፡፡
ሌንሳ ወደኋላ ዞረችና እያወራቻት ያለችው ራሄል መሆኗን ስታውቅ በመገረም ‹‹ራሄል እዚህ ምን እየሰራሽ ነው?›› ስትል ወደኋላ ተስባ አቀፈቻት፡፡
‹‹ፀጋን ማምጣት እንዳለብኝ ተሰማኝ››ስትል የመጣችበትን ምክንያት ነገረቻት፡፡
‹‹እሺ በምንም ምክንያት ይሁን በምንም እዚህ በመገኘትሽ ደስ ብሎኛል.››
የሌንሳ ወላጆችም በደስታ ሰላም አሏት፡፡
ዝግጅቱ እናዳለቀ ፀጋን እንዳቀፈች እነ ለሌንሳን ተከትላ ወደአውደ ምህረቱ ሄደች…ከረጅም ጊዜ በፊት የምታውቃቸውን በጣም ብዙ የድሮ ጎደኞቾንና ወዳጆቾን አገኘች፡፡ ብዙ ሰው ለምን እንደጠፋች እየጠየቃት በመምጣቷ እንደተደሰቱ ይነግሯት ነበር፡፡
❤39👍5👎1😁1
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ከሰዓት በኋላ ራሄል የፀጋን ጋሪ መኪናው ውስጥ አስገባች ። የዳይፐር ቦርሳውን ያዘች፣ሁሉንም ነገር እንዳላት ለማረጋገጥ ቦርሳውን ሁለቴ ፈትሸች፣ከዛ መኪናዋን ከወላጆቾ ጊቢ አንቀሳቀሰችና ነዳችው፡፡
ወደእንጦጦ ፓርኩ ነው የነዳችው፡፡ይህ ሀሳብ ድንገት ነው የመጣባት፡፡ እንደደረሰች መኪናዋን ፓርክ አደረገችና ..የጸጋን ጋሪ አወረደች…እሷን አነሳችና ጋሪው ላይ አስቀመጠቻት….አነስተኛ ሻንጣ አነሳችና በጀርባዋ አዘለች፡፡ከዛ ጋሪውን እየነዳች ወደፊት ቀጠለች… ስትራመድ የፓርኩ ፀጥታ፣የፀሀይ የሳሳ ሙቀት እና እርጥበት አዘል ንፋስ እና የዛፉ ቅጠሎች ሹክሹክታ በፅሞና እያዳመጠች ነው ።በርቀት ልጆችን ሲስቁ እና ሲሯሯጡ ይታያል። በቡድን የሚዝናኑ ሰዎች….ሳይክል የሚያበሩ ወጣቶች..ብዙ ብዙ ነገር እያየች ፀጋን ወደ ዳገቱ እየገፋች ወደፊ ቀጠለች ፡፡
‹‹ሄሎ፣ ሄሎ›› ፀጋን አላፊ አግዳሚው ሰላምታ እየሰጦት ያልፉ ጀመር...ራሄል መንገዱን በመከተል ደስተኛ ሆና በአእምሮዋ ብዙ ነገር እያሰላሰለች ቀጥላለች.. ዛሬ ጠዋት ከኬሩቤል ሞት በፊትም በውስጦ የነበሩትን አስደሳች የበረከት ስሜቶችን ቀስቅሶባታል ።
የሚገርመው፣ ቤተክርስቲያን ሆና የእግዚአብሔር ቃል ሲነገር መስማት፣ መዝሙር ሲዘመር አብራ መዘመር መቼም አደርገዋለው ብላ የምታስበው ጉዳይ አልነበረም ፡፡ ምናልባት ለእግዚአብሔር ሁለተኛ እድል ልትሰጥ ትፈልግ ይሆናል።
ራሄል ዳገቱን ጨርሳ ቁልቁለት እየወረደች ሳለ ድንገት ሳታስበው የፀጋ ጋሪ ከእጇ አሟልጮ አመለጣት …ጋሪው እህቷን ይዞ በራሱ ወደታች ተንደረደረ….ራሄል በድንጋጤ በድን ሆና ጮኸች… ጥቂት ሜትሮች ርቀት ላይ ባለው ሳሩ ውስጥ ምንም ጉዳት ሳይደርስባት ወደቀች ..ወደእሷ ስትንደረደር ቀድሟት አንድ ሰው ፀጋ ጋር ደርሶ ጋሪውና አቃንቶ አነሳና እሷን ከጋሪው አንስቶ አቀፋት…..‹‹ወይኔ በጌታ!!!›› አለች ራሄል…..ያስገረማት ፀጋ ሳትጎዳ መትረፏ ብቻ ሳይሆን ከሷ ቀድሞ የደረሰላት ደ/ር ኤልያስ ሆኖ መገኘቱ ነው፡፡‹‹ይሄ ሰውዬ ይከታተለኛል ማለት ነው…?እንደዛ ካልሆነማ እንደጠባቂ መልአክ በየሄድኩበት ሁሉ በድንገት አላገኘውም ነበር››ስትል አሰበች
በፈገግታ እንደተዋጠ‹‹አይዞሽ ..ምንም አልሆነችም››ሲል ሊያበረታታት ሞከረ፡፡
‹‹ቆይ እዚህ እንገናኝ ብዬ መልእክት ልኬልህ ነበር እንዴ ?።››ስትል ጠየቀችው
‹‹አዎ እንደዛ መሰለኝ..ምነው ስላገኘሺኝ ደበረሽ እንዴ?››
‹‹ለምን ይደብረኛል….ገርሞኝ እንጂ››
‹‹ላስገርምሽ ስለቻልኩ ደስ ብሎኛል››
ፀጋ እጆቿን እያጨበጨበች።‹‹ቤተክርስቲያን ሂድን››አለችው ፡፡
‹‹ቤተክርስቲያን?››ምን ለማለት እንደፈለገች አልገባውም፡፡
‹‹ወላጆቼ ሁል ጊዜ እሁድ እሁድ ቤተክርስቲያን ይዘዋት ይሄዱ ስለነበር ቅር እንዳይላት ብዬ ጥዋት ይዣት ሄድኩ…እሱን ልትነግርህ ፈልጋ ነው››ሥትል አብራራችለት ፡፡
‹‹እና እንዴት ነበር?››
‹‹በእውነቱ በጣም ጥሩ ነው.››
‹‹እሺ ..ወደሆነ ካፌ ሄደን አረፍ እንበል?የሆነ ነገር ልጋብዛችሁ?››አላት፡፡
‹‹አይ…. ለእኔ እና ለፀጋ መክሰስ አዘጋጅቼ ነበር… ቡና, ወተት እና ኩኪስ አለን.. ካፌ ከተማም ሰልችቶናል…የሆነ ለመብላት ጥሩና ጸጥ ያለ ምቹ ቦታ ፈልጌ ነበር.››
‹‹ከዚህ የአስር ደቂቃ የእግር መንገድ በአንዳንድ በዛፎች የተከበበ ወንበርና ጠረጴዛ ያለበት ቦታ አለ። ለፀጋም ቅርብ የሆነ የመጫወቻ ሜዳ አለ። ከፈለግሽ ላሳይሽ እችላለሁ።››
ራሄል የጠቀሰውን ቦታ ማግኘት ያን ያህል ከባድ እንደማይሆንባት ታውቃለች።አረ እንደውም የሚለው ቦታ በትክክል ትዝ ብሏታል፡፡ግን አብሯቸው እንዲሆን ፍላጎቷ ነው፡፡
‹‹ካላስቸገርንህ ደስ ይለኛል››አለችው፡፡
ችግር የለውም..ጥቂት ደቂቃ ስጡኝ ጓደኞቼን ተሰናብቼ ልምጣ አለና ወደኋላ ሄዶ አብረውት ከነበሩት ሶስት ጓደኞቹ ጋር በመሳሳቅ ጥቂት ቃላትን ከተለዋወጠ በኃላ ተመልሶ መጣና የፀጋን ጋሪ እየገፋ ወደተባለው ቦታ እየመራ ይወስዳቸው ጀመር፡፡
በአሁኑ ጊዜ ስለ ምንም ጥልቅ ነገር ማሰብ አልቻለም,ከእርሷ ጋር አብሮ ሄደ, ከዚህች ሴት አጠገብ ሲሆን ለራሱ ሐቀኛ እንዳይሆን ታደርገዋለች፡፡ብዙውን ጊዜ ከሴቶች ጋር መነጋገር ይከብደዋል ፣ ከፊቱ ላሉት የተወሰኑ አመታት ከሴት ራሱን ለማራቅ በተለይ ቆሚ የሆነ ግንኙነት ላለመመስረት ቁርጥ ያለ ውሰኔ ወስኖ ነበር።ለምን አሁን ራሄልን እንደሚያሳድዳት እርግጠኛ አይደለም። እሷ በተለምዶ የሚማረክባት አይነት ሴት አልነበረችም። ከመጀመርያው አንስቶ ለእሷ አሉታዊ አመለካከት ቢኖርም ፣ እሷ የሚያስደንቅ ጥንካሬ ባለቤት ሆና በሀሳቡ ውስጥ ተሰንቅራ መቆየት ችላለች ።
‹‹ስራ እንዴትነው..ማለቴ ፋውንዴሽኑ?››ሲል ጠየቃት
‹‹ጥሩ ነው…ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጥሬ ገንዘብ ፍሰት ላይ ችግር አጋጥሞናል.››
‹‹ ፋውንዴሽኑ ጥሩ ለጋሾች እንዳለው ከወላጆችሽ ተረድቼ ነበር እኮ።››
‹‹በአብዛኛዎቹ ጉዳዮች አዎ ትክክል ነው፣ ነገር ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ብዙ አዳዲስ በጎ አድራጎት ድርጅቶችን ገንዘብ እየጠየቁን ነው። እነዚህ ሁሉ መመርመር አለባቸው፣ ይህም ደግሞ ገንዘባቸውን ምን ላይ እንደዋለ ለማረጋገጥ ለሚፈልጉ ደንበኞችም የምናደርገው ነው። አጋጣሚ ሆኖ ደግሞ በሆነ እንግዳ ምክንያት ላለፉት ጥቂት ወራት የተወሰኑ ለጋሾችን አጥተናል።››ንግግሯን አቁማ የይቅርታ ፈገግታ ፈገግ አለችለት ።
‹‹ይቅርታ ስለ ፋውንዴሽኑ ሳወራ መጮህ እጀምራለሁ:››
‹‹አረ ችግር የለውም..አልጮኸሽም..ደግሞ ማወቅ ያለብሽ አንቺን ማዳመጥ ሁልጊዜ አስደሳች ነው።አንድ ሰው ስለ ሚወደው ነገር ሲናገር ሁል ጊዜ በጣም ስሜታዊ መሆኑ የሚጠበቅ ነው።››ሲላት ሳቀች።
‹‹ጓደኞቼ ከስራዬ ጋር እንደተጋባው አድርገው ያወራሉ። ፋውንዴሽኑ ለእኔ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። እዚያ መስራቴ ለእኔ ረድቶኛል ከጥልቅ ሀዘኔም እንዳገግም ያገዘኝ ስራዬ ነው ።››ቀና ብላ ተመለከተችው፣ ዓይኖቿ በብርታት እያበሩ ለሥራው ያላትን ቁርጠኝነት አጥርቶ ያሳይ ነበር።
የተባለበት ቦታ ደርሰው ቆሙ፡፡
‹‹በቂ ቡና እና ተጨማሪ ስኒ አለኝ። ከእኛ ጋር ትቆያለህ አይደል?›› ስትል ጠየቀችው… ።ለአፍታ እርግጠኛ ያልሆነች የትምህርት ቤት ልጅ ትመስላለች። ይህም ለዔሊ ግብዣዋን እንዲቀበል በቂ ማበረታቻ ሰጥቶታል።ራሄል ፌርሙሱን እና ኩባያዎቹን ስታወጣ ትሁት ከእሱ አፈንግጣ ወደ መጫወቻ ሜዳ ሄደች።
ተመቻችተው ተቀመጡና ጫወታ ጀመሩ
‹‹ ለምን ሆስፒታሎችን ትጠያለሽ?››ሲል ያልጠበቀችውን ጥያቄ ጠየቃት፡፡
ራሄል ራሷን ነቀነቀች፣ ለአፍታ ያህል መልስ እንደማትሰጠው አሰበ። በኋላ ግን ጉልበቷን ወደ አገጯ ሳብ አድርጋ እጆቿን አነባብራ ማውራት ጀመረች።‹‹ከስምንት አመት በፊት በሆስፒታል ውስጥ ለአንድ ወር ከግማሽ አሳልፌያለሁ….ኪሩቤልን እግዚአብሔር እንዳገባው የፈቀደልኝ የልቤ ሰው መስሎኝ ነበር…አደጋው በደረሰበት ጊዜ እንደሚድን በማመን አልጋ አጠገብ ተቀምጬ ነበር። ለስድስት ሳምንታት ያህል እግዚያብሄር እንዲያድልንኝ ያለማቆረጥ ጸለይኩ። የሆስፒታል የመተንፈሻ መሳሪያ ድምፅ እንዴት እንደሆነ ጠንቅቄ ያወቅኩት በዛን ጊዜ ነው፣ የልብ መቆጣጠሪያውንም እንደዛው። ጸሎቴ ግን ለውጥ አላመጣም…››ድምጿ በመጨረሻው ቃል ላይ ደምቆ ተሰማ፣ እና ዔሊ ታሪኩ ወዴት እንደሚሄድ ተረዳ። በእሷ ላይ ያለውን
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ከሰዓት በኋላ ራሄል የፀጋን ጋሪ መኪናው ውስጥ አስገባች ። የዳይፐር ቦርሳውን ያዘች፣ሁሉንም ነገር እንዳላት ለማረጋገጥ ቦርሳውን ሁለቴ ፈትሸች፣ከዛ መኪናዋን ከወላጆቾ ጊቢ አንቀሳቀሰችና ነዳችው፡፡
ወደእንጦጦ ፓርኩ ነው የነዳችው፡፡ይህ ሀሳብ ድንገት ነው የመጣባት፡፡ እንደደረሰች መኪናዋን ፓርክ አደረገችና ..የጸጋን ጋሪ አወረደች…እሷን አነሳችና ጋሪው ላይ አስቀመጠቻት….አነስተኛ ሻንጣ አነሳችና በጀርባዋ አዘለች፡፡ከዛ ጋሪውን እየነዳች ወደፊት ቀጠለች… ስትራመድ የፓርኩ ፀጥታ፣የፀሀይ የሳሳ ሙቀት እና እርጥበት አዘል ንፋስ እና የዛፉ ቅጠሎች ሹክሹክታ በፅሞና እያዳመጠች ነው ።በርቀት ልጆችን ሲስቁ እና ሲሯሯጡ ይታያል። በቡድን የሚዝናኑ ሰዎች….ሳይክል የሚያበሩ ወጣቶች..ብዙ ብዙ ነገር እያየች ፀጋን ወደ ዳገቱ እየገፋች ወደፊ ቀጠለች ፡፡
‹‹ሄሎ፣ ሄሎ›› ፀጋን አላፊ አግዳሚው ሰላምታ እየሰጦት ያልፉ ጀመር...ራሄል መንገዱን በመከተል ደስተኛ ሆና በአእምሮዋ ብዙ ነገር እያሰላሰለች ቀጥላለች.. ዛሬ ጠዋት ከኬሩቤል ሞት በፊትም በውስጦ የነበሩትን አስደሳች የበረከት ስሜቶችን ቀስቅሶባታል ።
የሚገርመው፣ ቤተክርስቲያን ሆና የእግዚአብሔር ቃል ሲነገር መስማት፣ መዝሙር ሲዘመር አብራ መዘመር መቼም አደርገዋለው ብላ የምታስበው ጉዳይ አልነበረም ፡፡ ምናልባት ለእግዚአብሔር ሁለተኛ እድል ልትሰጥ ትፈልግ ይሆናል።
ራሄል ዳገቱን ጨርሳ ቁልቁለት እየወረደች ሳለ ድንገት ሳታስበው የፀጋ ጋሪ ከእጇ አሟልጮ አመለጣት …ጋሪው እህቷን ይዞ በራሱ ወደታች ተንደረደረ….ራሄል በድንጋጤ በድን ሆና ጮኸች… ጥቂት ሜትሮች ርቀት ላይ ባለው ሳሩ ውስጥ ምንም ጉዳት ሳይደርስባት ወደቀች ..ወደእሷ ስትንደረደር ቀድሟት አንድ ሰው ፀጋ ጋር ደርሶ ጋሪውና አቃንቶ አነሳና እሷን ከጋሪው አንስቶ አቀፋት…..‹‹ወይኔ በጌታ!!!›› አለች ራሄል…..ያስገረማት ፀጋ ሳትጎዳ መትረፏ ብቻ ሳይሆን ከሷ ቀድሞ የደረሰላት ደ/ር ኤልያስ ሆኖ መገኘቱ ነው፡፡‹‹ይሄ ሰውዬ ይከታተለኛል ማለት ነው…?እንደዛ ካልሆነማ እንደጠባቂ መልአክ በየሄድኩበት ሁሉ በድንገት አላገኘውም ነበር››ስትል አሰበች
በፈገግታ እንደተዋጠ‹‹አይዞሽ ..ምንም አልሆነችም››ሲል ሊያበረታታት ሞከረ፡፡
‹‹ቆይ እዚህ እንገናኝ ብዬ መልእክት ልኬልህ ነበር እንዴ ?።››ስትል ጠየቀችው
‹‹አዎ እንደዛ መሰለኝ..ምነው ስላገኘሺኝ ደበረሽ እንዴ?››
‹‹ለምን ይደብረኛል….ገርሞኝ እንጂ››
‹‹ላስገርምሽ ስለቻልኩ ደስ ብሎኛል››
ፀጋ እጆቿን እያጨበጨበች።‹‹ቤተክርስቲያን ሂድን››አለችው ፡፡
‹‹ቤተክርስቲያን?››ምን ለማለት እንደፈለገች አልገባውም፡፡
‹‹ወላጆቼ ሁል ጊዜ እሁድ እሁድ ቤተክርስቲያን ይዘዋት ይሄዱ ስለነበር ቅር እንዳይላት ብዬ ጥዋት ይዣት ሄድኩ…እሱን ልትነግርህ ፈልጋ ነው››ሥትል አብራራችለት ፡፡
‹‹እና እንዴት ነበር?››
‹‹በእውነቱ በጣም ጥሩ ነው.››
‹‹እሺ ..ወደሆነ ካፌ ሄደን አረፍ እንበል?የሆነ ነገር ልጋብዛችሁ?››አላት፡፡
‹‹አይ…. ለእኔ እና ለፀጋ መክሰስ አዘጋጅቼ ነበር… ቡና, ወተት እና ኩኪስ አለን.. ካፌ ከተማም ሰልችቶናል…የሆነ ለመብላት ጥሩና ጸጥ ያለ ምቹ ቦታ ፈልጌ ነበር.››
‹‹ከዚህ የአስር ደቂቃ የእግር መንገድ በአንዳንድ በዛፎች የተከበበ ወንበርና ጠረጴዛ ያለበት ቦታ አለ። ለፀጋም ቅርብ የሆነ የመጫወቻ ሜዳ አለ። ከፈለግሽ ላሳይሽ እችላለሁ።››
ራሄል የጠቀሰውን ቦታ ማግኘት ያን ያህል ከባድ እንደማይሆንባት ታውቃለች።አረ እንደውም የሚለው ቦታ በትክክል ትዝ ብሏታል፡፡ግን አብሯቸው እንዲሆን ፍላጎቷ ነው፡፡
‹‹ካላስቸገርንህ ደስ ይለኛል››አለችው፡፡
ችግር የለውም..ጥቂት ደቂቃ ስጡኝ ጓደኞቼን ተሰናብቼ ልምጣ አለና ወደኋላ ሄዶ አብረውት ከነበሩት ሶስት ጓደኞቹ ጋር በመሳሳቅ ጥቂት ቃላትን ከተለዋወጠ በኃላ ተመልሶ መጣና የፀጋን ጋሪ እየገፋ ወደተባለው ቦታ እየመራ ይወስዳቸው ጀመር፡፡
በአሁኑ ጊዜ ስለ ምንም ጥልቅ ነገር ማሰብ አልቻለም,ከእርሷ ጋር አብሮ ሄደ, ከዚህች ሴት አጠገብ ሲሆን ለራሱ ሐቀኛ እንዳይሆን ታደርገዋለች፡፡ብዙውን ጊዜ ከሴቶች ጋር መነጋገር ይከብደዋል ፣ ከፊቱ ላሉት የተወሰኑ አመታት ከሴት ራሱን ለማራቅ በተለይ ቆሚ የሆነ ግንኙነት ላለመመስረት ቁርጥ ያለ ውሰኔ ወስኖ ነበር።ለምን አሁን ራሄልን እንደሚያሳድዳት እርግጠኛ አይደለም። እሷ በተለምዶ የሚማረክባት አይነት ሴት አልነበረችም። ከመጀመርያው አንስቶ ለእሷ አሉታዊ አመለካከት ቢኖርም ፣ እሷ የሚያስደንቅ ጥንካሬ ባለቤት ሆና በሀሳቡ ውስጥ ተሰንቅራ መቆየት ችላለች ።
‹‹ስራ እንዴትነው..ማለቴ ፋውንዴሽኑ?››ሲል ጠየቃት
‹‹ጥሩ ነው…ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጥሬ ገንዘብ ፍሰት ላይ ችግር አጋጥሞናል.››
‹‹ ፋውንዴሽኑ ጥሩ ለጋሾች እንዳለው ከወላጆችሽ ተረድቼ ነበር እኮ።››
‹‹በአብዛኛዎቹ ጉዳዮች አዎ ትክክል ነው፣ ነገር ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ብዙ አዳዲስ በጎ አድራጎት ድርጅቶችን ገንዘብ እየጠየቁን ነው። እነዚህ ሁሉ መመርመር አለባቸው፣ ይህም ደግሞ ገንዘባቸውን ምን ላይ እንደዋለ ለማረጋገጥ ለሚፈልጉ ደንበኞችም የምናደርገው ነው። አጋጣሚ ሆኖ ደግሞ በሆነ እንግዳ ምክንያት ላለፉት ጥቂት ወራት የተወሰኑ ለጋሾችን አጥተናል።››ንግግሯን አቁማ የይቅርታ ፈገግታ ፈገግ አለችለት ።
‹‹ይቅርታ ስለ ፋውንዴሽኑ ሳወራ መጮህ እጀምራለሁ:››
‹‹አረ ችግር የለውም..አልጮኸሽም..ደግሞ ማወቅ ያለብሽ አንቺን ማዳመጥ ሁልጊዜ አስደሳች ነው።አንድ ሰው ስለ ሚወደው ነገር ሲናገር ሁል ጊዜ በጣም ስሜታዊ መሆኑ የሚጠበቅ ነው።››ሲላት ሳቀች።
‹‹ጓደኞቼ ከስራዬ ጋር እንደተጋባው አድርገው ያወራሉ። ፋውንዴሽኑ ለእኔ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። እዚያ መስራቴ ለእኔ ረድቶኛል ከጥልቅ ሀዘኔም እንዳገግም ያገዘኝ ስራዬ ነው ።››ቀና ብላ ተመለከተችው፣ ዓይኖቿ በብርታት እያበሩ ለሥራው ያላትን ቁርጠኝነት አጥርቶ ያሳይ ነበር።
የተባለበት ቦታ ደርሰው ቆሙ፡፡
‹‹በቂ ቡና እና ተጨማሪ ስኒ አለኝ። ከእኛ ጋር ትቆያለህ አይደል?›› ስትል ጠየቀችው… ።ለአፍታ እርግጠኛ ያልሆነች የትምህርት ቤት ልጅ ትመስላለች። ይህም ለዔሊ ግብዣዋን እንዲቀበል በቂ ማበረታቻ ሰጥቶታል።ራሄል ፌርሙሱን እና ኩባያዎቹን ስታወጣ ትሁት ከእሱ አፈንግጣ ወደ መጫወቻ ሜዳ ሄደች።
ተመቻችተው ተቀመጡና ጫወታ ጀመሩ
‹‹ ለምን ሆስፒታሎችን ትጠያለሽ?››ሲል ያልጠበቀችውን ጥያቄ ጠየቃት፡፡
ራሄል ራሷን ነቀነቀች፣ ለአፍታ ያህል መልስ እንደማትሰጠው አሰበ። በኋላ ግን ጉልበቷን ወደ አገጯ ሳብ አድርጋ እጆቿን አነባብራ ማውራት ጀመረች።‹‹ከስምንት አመት በፊት በሆስፒታል ውስጥ ለአንድ ወር ከግማሽ አሳልፌያለሁ….ኪሩቤልን እግዚአብሔር እንዳገባው የፈቀደልኝ የልቤ ሰው መስሎኝ ነበር…አደጋው በደረሰበት ጊዜ እንደሚድን በማመን አልጋ አጠገብ ተቀምጬ ነበር። ለስድስት ሳምንታት ያህል እግዚያብሄር እንዲያድልንኝ ያለማቆረጥ ጸለይኩ። የሆስፒታል የመተንፈሻ መሳሪያ ድምፅ እንዴት እንደሆነ ጠንቅቄ ያወቅኩት በዛን ጊዜ ነው፣ የልብ መቆጣጠሪያውንም እንደዛው። ጸሎቴ ግን ለውጥ አላመጣም…››ድምጿ በመጨረሻው ቃል ላይ ደምቆ ተሰማ፣ እና ዔሊ ታሪኩ ወዴት እንደሚሄድ ተረዳ። በእሷ ላይ ያለውን
❤73👍5👏1
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
___
///
‹‹ነይ የኔ ማር፣ ዝም በይ፣ ላደርቅልሽ እፈልጋለሁ።››ራሄል ትሁትን ከመታጠቢያ ገንዳው ውስጥ አውጥታ በፎጣው ጠቀለለቻት።
ወደ ምትሄድበት የስብሰባ ቦታ ፀጋን መውሰድ እንዳለባት ወስናለች፡፡ ህጻኗን ዛሬ ከሰአት በኋላ ለረጅም ሰዓት እንቅልፍ እንድትተኛ አድርጋ ስለነበር ማታ ከሶስት ሰዓት በፊት እንደማትተኛ ታውቃለች። ልብስ ልታለብሳት እየተዘጋጀች ሳለ ሕፃኗ ከንፈሯ ላይ በጥፊ መታቻት። ትልቅ ሰው በጥፊ ያጠናገራት ነው የመሰላት‹‹አንቺ ትንሽ ድርዬ›› ብላ አጉተመተመች፡፡ ‹‹ምን ፈልገሽ ነው የምትደባደቢው?›› ጠየቀቻት፡፡
በዛው ቅፅበት የበሩ ደወል ጮኸ። ለመክፈት ፊቷን ስታዞር የራሄል እግር ይዛ ታገለቻት ሳትወድ በግዷ ጎንበስ ብላ አቀፈቻት፡፡ አሁንም በፎጣው ተጠቅልላለች። ራሄል በረዥሙ ኮሪዶር ላይ ወርዳ የራሷን ክፍል አልፋ ወደ መግቢያ በር ቀረበች። መጥሪያው ከእንደገና ጮኸ…
‹‹መጣሁ፣ መጣሁ››ስትል ራሄል አጉተመተመች፣ አሁንም በደረጃው ላይ ነች።ከታች ስትደርስ የእብነበረድ ወለሉ ቅዝቃዜ በባዶ እግሯ ዘልቆ ተሰማት ፡፡በሩን በዝግታ ከፈተችው።ዶ/ር ኤልያስ ነበረ፡፡
ወደ ውስጥ ስትጋብዘው ተንደርድራ ጉንጩ ላይ ተጣብቃ ልትስመው ፈልጋ ነበር…እንደምንም እራሷን ተቆጣጠረች፡፡
እሱ የፀጋ ሐኪም ብቻ ነው። እሱ የእህቷን ደህንነትን ሊቆጣጠር እናሊከታተል ብቻ ነው ወደቤታቸው የሚመላለሰው ። በማለት እራሷን ለማረጋጋት ጣረች፡፡ የዔሊ ሞቃታማ ሰማያዊ አይኖች ቀና ብላ ስትመለከት፣ውስጧ ተናወጠባት፡፡
‹‹ኤሊ ውሰደኝ…››ትሁት ጮኸች፣
ራሄል እህቷን ችላ ብላ ከኤልያስ ጋር ማውራቷን ቀጠለች፡፡‹‹አንዲት ብዙ ገንዘብ ለፋውንዴሽናችን የምትለግስ ሴት ማግኘት አለብኝ እና ምርጫ ስለሌለኝ ፀጋን ይዣት ልሄድ ነበር ያሰብኩት…ምን ትላለህ?››
‹‹ማታስቸግርሽ ከሆነ ምንም ችግር የለውም….››አላት
‹‹ እሱ የእኔም ስጋት ነው….ድፍረት ካልሆነብኝ ልትረዳኝ ትችላለህ?››
‹‹ለምን አይሆንም?እዚህ ሆኜ እንድጠብቅልሽ ነው የምትፈልጊው?››
‹‹ኮስተር አለችበት‹‹እሱም ይቻላል..ግን አብረኸን ብትሄድና እዛ ሴትዬዋ ጋር በምነጋርበት ሰዓት አንተ ፀጋን ታጫውትልኛለህ ብዬነበር ያሰብኩት…እኔም እንዲህ ሆና ይሆን ከሚል ስጋት ተገላግዬ በተረጋጋ መንፈስ ከሴትዬዋ ጋራ አወራለው››አለችው፡፡
ሳቀባት…….
በሳቁ ግራ ተጋባች‹‹ምነው ያልሆነ ነገር ተናገርኩ እንዴ?››
‹‹አይ…አሁን ኦርጂናል እናት እየሆንሽ እንደሆነ ስለታዘብኩ ነው…እዚህ ለእኔ እንኳን ቢሆን አምነሽ ጥለሻት ልትሄጂ አልፈቀድሽም…በእውነት ደስ ብሎኛል…አብሬችሁ እሄዳለው››
‹‹እሺ ይህችን ልጅ ላልብሳት እና እኔም ለብሼ መጣን ….አስር ደቂቃ ታገሰን››
‹‹ችግር የለም..ሂዱ›› ፈቀደላቸው…ሄለን ፀጋን እንዳቀፈች ወደመኝታ ቤት አመራች፡፡ፀጋን ካለበሰች በኃላ የራሷን ልብስ ቀየረችና መስታወት ፊት ስትቆም ቅድም ፀጋ የመታቻት ከንፈሯ ቀልቶ እና አብጦ ተመለከተች….፡፡
ወደፀጋ ዞራ ልንቦጯን ዘርግታ እያሳየቻት ‹‹ውይ አንቺ ልጅ ….እይው እስኪ ያደረግሺኝን››
ፀጋ እየተመለከተቻት ሳቀችባት፡፡ራሄል ከፍሬጅ ውስጥ በረዶ አወጣችና ያዘችበት፡፡ከዛ ቀይ ሊፒስቲክ አወጣችና በስሱ በመቀባት የቀላውን ከንፈሯን ከሌላው ክፍል ጋር አመሳሰለችው፡፡
ከዛ ዝግጅቷን እንዳጠናቀቀች ከተረዳች በኃላ ቦርሳዋን ይዛ በአንድ እጆ የፀጋን እጅ ጨብጣ ወደሳሎን ሄደች፡፡ተያይዘው ከቤት ወጡ፡፡
ራሄል ከንፈሯን አስጨነቀች፣ ጸጋና መሀከላቸው አድርገው ወደ ራሄል መኪና ሲያቀኑ ልክ በቅርብ የተጋቡ ባልና ሚስቶች ይመስሉ ነበር፡፡ፀጋን ከኋላ በስርዓቱ ቀበቶዋን አሰሩላትና እነሱ ገቢና ጎን ለጎን ተቀመጡ..መኪናውን የምታሽከረክረው ራሄል ነበረች፡፡
ለተወሰነ ደቂቃ በዝምታ ነበር የተጓዙት ያሉት፡፡በፋውንዴሽኑ ውስጥ ስላሏት ችግሮች ለአንድ ሰው መንገር ፈልጋ ነበር። የሮቤል ሚስጥራዊነት አሳስቧታል።ትናንት ማታ አነጋግራዋለች። ለምን ጥሪዋን እንዳልመለሰላት ስትጠይቀው ሞባይሉን ቤቱ ረስቶ እንደነበር ነው የነገራት።በበጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥ ያገኘኛቸውን መረጃዋች በማጠናከር ላይ ተጠምዷ ስለነበር ጊዜ አልነበረውም .. እሱ የሚፈልገው አንድ ነገር እንዳለ በግልፅ ነግሯታል….እሷም ልታምነው ፈለገች ነገር ግን አልቻለችም እና ዛሬ ከሰአት በኋላ በፋውንዴሽን ከኮምፒውተሯ ጋር ስትገናኝ፣ ሌላ ሰው የቢሮውን ኮምፒውተር ላይ እንደገባ አስተዋለች። መረጃዋን የሚበረብር ማን እንደሆነ ግራ ተጋብታለች፡፡
የአእምሮዋን ፍጭት ያነበበ ይመስል‹‹የምታናግሪው ሰው አለ?›› ስል ጠየቃት። ራሄል ወደ
‹‹ስለዚህ ነገር በተለምዶ ከአባቴ ጋር ነበር የምንነጋገረው፣ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ እንደምታውቀው በእናቴ ጉዳይ በጣም የተጠመደ ነው እና እሱን ማስቸገር አልፈልግም።››
‹‹የፋውንዴሽኑ ቦርድ እንዴት ነው? አይረዳዱሽም እንዴ?››
ራሄል አንገቷን በአሉታ ነቀነቀች። ‹‹አይ አሁን ያጋጠመን … ውስጣዊ ችግር ነው እነሱን ወደዚህ ጎትቼ ማስገባት አልፈልግም….እኔ በራሴ በምችለውን መንገድ መፍትሄ መፈለግ አለብኝ››
‹‹ሁሉንም ነገር በራስሽ ብቻ ማድረግ የለብሽም››ኤሊ ተቃወማት ።በዚህ ጊዜ የሚሄዱበት ቦታ ደርሰው መኪናዋን እያቆመች ነበር፡፡
ትንሽ ሳቅ ብላ‹‹በቅርብ ጊዜ ሁሉንም ነገር በራሴ የማደርገው ይመስላል››ስትል ቦርሳዋን አንጠልጥላ ከመኪናዋ ወረደች፡፡ራሄል ከመኪናው ጎን በመጣችበት ጊዜ ኤሊያስ ፀጋን ከታሰረችበት ቀበቶ እየፈታት ነበር። የዳይፐር ቦርሳውን ለራሔል ሰጣት እና በሩን ዘጋው። ራሄል ወደ ወ.ሮ ላምሮት መግቢያ ደረጃ ሲወጡ‹‹ልክ እንደ ትንሽ ቤተሰብ እንመስላለን››ስትል አሰበች።
መግቢያ በራፉ ላይ ደረሱና ደወሉን ተጫኑት፡፡ ‹‹ማግባት ምን አይነት ጣዕም ሊኖረው ይችላል?››እራሷን ጠየቀች፡፡ ጋብቻ ከኪሩቤል በኃላ ያልተጠቀመችበት ቃል ነበር።የስሙ ትዝታ የደስታ ስሜት እንዲሰማት አደረጋት፣ ከዚያም የታማኝነት መጉደል ውስጧን ሲያንቀጠቅጣት ተሰማት። እንዲህ ያሉ የቀን ህልሞችን እንድታልም ስውር ኃይል የነበረው ኪሩቤል ብቻ ነበረች። ከዚህ በፊት ወይም በኋላ ማንም ሌላ ሰው ያንን ስሜት ሊቀሰቅስባት አልቻለም ።
ራሄል ድጋሚ ደወሉን ልትደውል ስትል በሩ በራሱ ተከፈተ። ራሄል ወደ አንድ ትልቅ አዳራሽ መሳይ ሳሎን ውስጥ ገባች ወዲያው ጥርት ያለ ሰማያዊ ቀሚስ የለበሰች ሴት ተቀበለቻት።
‹‹ወ/ሮ ላምሮት ከኋላ ባለው አትክልት ስፍራ እየጠበቀችሽ ነው።››በማለት ዘወር ብላ ወደ ሌላ በር መራቻቸው፡፡ ወደ ዔሊ ተጠግታ በሹክሹክታ ‹‹ፀጋ ከስርህ እንድትርቅ አትፍቀድላት። ››ስትል ተናገረች፡፡ፈገግ አለላት….በፊት ፀጋን በተመለከተ እንዲህ አድርጊላት… ይሄንን ተጠንቀቂላት… እያለ የሚያጨናንቃት እሱ ነበር..አሁን ግን ይሄው በተቃራኒው ለእሱ መመሪያ እየሰጠችው ነው፡፡እያሳየች ባለችው ለውጥ በውስጡ እርካታ ተሰማው፡፡
ወ.ሮዋ ከተቀመጠችበት መድረክ መሳይ ውብ ቦታ ባሻገር በሁለት በኩል በጡብ ግድግዳ የተከበበ አበባ ሞልቶ ነበር። ወ.ሮ ላምሮት በትልቅ ዣንጥላ በተከለለ የመስታወት ጠረጴዛ ጎን ከተቀመጠችበት ልዩ ወንበር ተነስታ ‹‹ ጤና ይስጥልኝ ራሄል …በድጋሚ እንኳን ደህና መጣሽ ›› አለቻት ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
___
///
‹‹ነይ የኔ ማር፣ ዝም በይ፣ ላደርቅልሽ እፈልጋለሁ።››ራሄል ትሁትን ከመታጠቢያ ገንዳው ውስጥ አውጥታ በፎጣው ጠቀለለቻት።
ወደ ምትሄድበት የስብሰባ ቦታ ፀጋን መውሰድ እንዳለባት ወስናለች፡፡ ህጻኗን ዛሬ ከሰአት በኋላ ለረጅም ሰዓት እንቅልፍ እንድትተኛ አድርጋ ስለነበር ማታ ከሶስት ሰዓት በፊት እንደማትተኛ ታውቃለች። ልብስ ልታለብሳት እየተዘጋጀች ሳለ ሕፃኗ ከንፈሯ ላይ በጥፊ መታቻት። ትልቅ ሰው በጥፊ ያጠናገራት ነው የመሰላት‹‹አንቺ ትንሽ ድርዬ›› ብላ አጉተመተመች፡፡ ‹‹ምን ፈልገሽ ነው የምትደባደቢው?›› ጠየቀቻት፡፡
በዛው ቅፅበት የበሩ ደወል ጮኸ። ለመክፈት ፊቷን ስታዞር የራሄል እግር ይዛ ታገለቻት ሳትወድ በግዷ ጎንበስ ብላ አቀፈቻት፡፡ አሁንም በፎጣው ተጠቅልላለች። ራሄል በረዥሙ ኮሪዶር ላይ ወርዳ የራሷን ክፍል አልፋ ወደ መግቢያ በር ቀረበች። መጥሪያው ከእንደገና ጮኸ…
‹‹መጣሁ፣ መጣሁ››ስትል ራሄል አጉተመተመች፣ አሁንም በደረጃው ላይ ነች።ከታች ስትደርስ የእብነበረድ ወለሉ ቅዝቃዜ በባዶ እግሯ ዘልቆ ተሰማት ፡፡በሩን በዝግታ ከፈተችው።ዶ/ር ኤልያስ ነበረ፡፡
ወደ ውስጥ ስትጋብዘው ተንደርድራ ጉንጩ ላይ ተጣብቃ ልትስመው ፈልጋ ነበር…እንደምንም እራሷን ተቆጣጠረች፡፡
እሱ የፀጋ ሐኪም ብቻ ነው። እሱ የእህቷን ደህንነትን ሊቆጣጠር እናሊከታተል ብቻ ነው ወደቤታቸው የሚመላለሰው ። በማለት እራሷን ለማረጋጋት ጣረች፡፡ የዔሊ ሞቃታማ ሰማያዊ አይኖች ቀና ብላ ስትመለከት፣ውስጧ ተናወጠባት፡፡
‹‹ኤሊ ውሰደኝ…››ትሁት ጮኸች፣
ራሄል እህቷን ችላ ብላ ከኤልያስ ጋር ማውራቷን ቀጠለች፡፡‹‹አንዲት ብዙ ገንዘብ ለፋውንዴሽናችን የምትለግስ ሴት ማግኘት አለብኝ እና ምርጫ ስለሌለኝ ፀጋን ይዣት ልሄድ ነበር ያሰብኩት…ምን ትላለህ?››
‹‹ማታስቸግርሽ ከሆነ ምንም ችግር የለውም….››አላት
‹‹ እሱ የእኔም ስጋት ነው….ድፍረት ካልሆነብኝ ልትረዳኝ ትችላለህ?››
‹‹ለምን አይሆንም?እዚህ ሆኜ እንድጠብቅልሽ ነው የምትፈልጊው?››
‹‹ኮስተር አለችበት‹‹እሱም ይቻላል..ግን አብረኸን ብትሄድና እዛ ሴትዬዋ ጋር በምነጋርበት ሰዓት አንተ ፀጋን ታጫውትልኛለህ ብዬነበር ያሰብኩት…እኔም እንዲህ ሆና ይሆን ከሚል ስጋት ተገላግዬ በተረጋጋ መንፈስ ከሴትዬዋ ጋራ አወራለው››አለችው፡፡
ሳቀባት…….
በሳቁ ግራ ተጋባች‹‹ምነው ያልሆነ ነገር ተናገርኩ እንዴ?››
‹‹አይ…አሁን ኦርጂናል እናት እየሆንሽ እንደሆነ ስለታዘብኩ ነው…እዚህ ለእኔ እንኳን ቢሆን አምነሽ ጥለሻት ልትሄጂ አልፈቀድሽም…በእውነት ደስ ብሎኛል…አብሬችሁ እሄዳለው››
‹‹እሺ ይህችን ልጅ ላልብሳት እና እኔም ለብሼ መጣን ….አስር ደቂቃ ታገሰን››
‹‹ችግር የለም..ሂዱ›› ፈቀደላቸው…ሄለን ፀጋን እንዳቀፈች ወደመኝታ ቤት አመራች፡፡ፀጋን ካለበሰች በኃላ የራሷን ልብስ ቀየረችና መስታወት ፊት ስትቆም ቅድም ፀጋ የመታቻት ከንፈሯ ቀልቶ እና አብጦ ተመለከተች….፡፡
ወደፀጋ ዞራ ልንቦጯን ዘርግታ እያሳየቻት ‹‹ውይ አንቺ ልጅ ….እይው እስኪ ያደረግሺኝን››
ፀጋ እየተመለከተቻት ሳቀችባት፡፡ራሄል ከፍሬጅ ውስጥ በረዶ አወጣችና ያዘችበት፡፡ከዛ ቀይ ሊፒስቲክ አወጣችና በስሱ በመቀባት የቀላውን ከንፈሯን ከሌላው ክፍል ጋር አመሳሰለችው፡፡
ከዛ ዝግጅቷን እንዳጠናቀቀች ከተረዳች በኃላ ቦርሳዋን ይዛ በአንድ እጆ የፀጋን እጅ ጨብጣ ወደሳሎን ሄደች፡፡ተያይዘው ከቤት ወጡ፡፡
ራሄል ከንፈሯን አስጨነቀች፣ ጸጋና መሀከላቸው አድርገው ወደ ራሄል መኪና ሲያቀኑ ልክ በቅርብ የተጋቡ ባልና ሚስቶች ይመስሉ ነበር፡፡ፀጋን ከኋላ በስርዓቱ ቀበቶዋን አሰሩላትና እነሱ ገቢና ጎን ለጎን ተቀመጡ..መኪናውን የምታሽከረክረው ራሄል ነበረች፡፡
ለተወሰነ ደቂቃ በዝምታ ነበር የተጓዙት ያሉት፡፡በፋውንዴሽኑ ውስጥ ስላሏት ችግሮች ለአንድ ሰው መንገር ፈልጋ ነበር። የሮቤል ሚስጥራዊነት አሳስቧታል።ትናንት ማታ አነጋግራዋለች። ለምን ጥሪዋን እንዳልመለሰላት ስትጠይቀው ሞባይሉን ቤቱ ረስቶ እንደነበር ነው የነገራት።በበጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥ ያገኘኛቸውን መረጃዋች በማጠናከር ላይ ተጠምዷ ስለነበር ጊዜ አልነበረውም .. እሱ የሚፈልገው አንድ ነገር እንዳለ በግልፅ ነግሯታል….እሷም ልታምነው ፈለገች ነገር ግን አልቻለችም እና ዛሬ ከሰአት በኋላ በፋውንዴሽን ከኮምፒውተሯ ጋር ስትገናኝ፣ ሌላ ሰው የቢሮውን ኮምፒውተር ላይ እንደገባ አስተዋለች። መረጃዋን የሚበረብር ማን እንደሆነ ግራ ተጋብታለች፡፡
የአእምሮዋን ፍጭት ያነበበ ይመስል‹‹የምታናግሪው ሰው አለ?›› ስል ጠየቃት። ራሄል ወደ
‹‹ስለዚህ ነገር በተለምዶ ከአባቴ ጋር ነበር የምንነጋገረው፣ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ እንደምታውቀው በእናቴ ጉዳይ በጣም የተጠመደ ነው እና እሱን ማስቸገር አልፈልግም።››
‹‹የፋውንዴሽኑ ቦርድ እንዴት ነው? አይረዳዱሽም እንዴ?››
ራሄል አንገቷን በአሉታ ነቀነቀች። ‹‹አይ አሁን ያጋጠመን … ውስጣዊ ችግር ነው እነሱን ወደዚህ ጎትቼ ማስገባት አልፈልግም….እኔ በራሴ በምችለውን መንገድ መፍትሄ መፈለግ አለብኝ››
‹‹ሁሉንም ነገር በራስሽ ብቻ ማድረግ የለብሽም››ኤሊ ተቃወማት ።በዚህ ጊዜ የሚሄዱበት ቦታ ደርሰው መኪናዋን እያቆመች ነበር፡፡
ትንሽ ሳቅ ብላ‹‹በቅርብ ጊዜ ሁሉንም ነገር በራሴ የማደርገው ይመስላል››ስትል ቦርሳዋን አንጠልጥላ ከመኪናዋ ወረደች፡፡ራሄል ከመኪናው ጎን በመጣችበት ጊዜ ኤሊያስ ፀጋን ከታሰረችበት ቀበቶ እየፈታት ነበር። የዳይፐር ቦርሳውን ለራሔል ሰጣት እና በሩን ዘጋው። ራሄል ወደ ወ.ሮ ላምሮት መግቢያ ደረጃ ሲወጡ‹‹ልክ እንደ ትንሽ ቤተሰብ እንመስላለን››ስትል አሰበች።
መግቢያ በራፉ ላይ ደረሱና ደወሉን ተጫኑት፡፡ ‹‹ማግባት ምን አይነት ጣዕም ሊኖረው ይችላል?››እራሷን ጠየቀች፡፡ ጋብቻ ከኪሩቤል በኃላ ያልተጠቀመችበት ቃል ነበር።የስሙ ትዝታ የደስታ ስሜት እንዲሰማት አደረጋት፣ ከዚያም የታማኝነት መጉደል ውስጧን ሲያንቀጠቅጣት ተሰማት። እንዲህ ያሉ የቀን ህልሞችን እንድታልም ስውር ኃይል የነበረው ኪሩቤል ብቻ ነበረች። ከዚህ በፊት ወይም በኋላ ማንም ሌላ ሰው ያንን ስሜት ሊቀሰቅስባት አልቻለም ።
ራሄል ድጋሚ ደወሉን ልትደውል ስትል በሩ በራሱ ተከፈተ። ራሄል ወደ አንድ ትልቅ አዳራሽ መሳይ ሳሎን ውስጥ ገባች ወዲያው ጥርት ያለ ሰማያዊ ቀሚስ የለበሰች ሴት ተቀበለቻት።
‹‹ወ/ሮ ላምሮት ከኋላ ባለው አትክልት ስፍራ እየጠበቀችሽ ነው።››በማለት ዘወር ብላ ወደ ሌላ በር መራቻቸው፡፡ ወደ ዔሊ ተጠግታ በሹክሹክታ ‹‹ፀጋ ከስርህ እንድትርቅ አትፍቀድላት። ››ስትል ተናገረች፡፡ፈገግ አለላት….በፊት ፀጋን በተመለከተ እንዲህ አድርጊላት… ይሄንን ተጠንቀቂላት… እያለ የሚያጨናንቃት እሱ ነበር..አሁን ግን ይሄው በተቃራኒው ለእሱ መመሪያ እየሰጠችው ነው፡፡እያሳየች ባለችው ለውጥ በውስጡ እርካታ ተሰማው፡፡
ወ.ሮዋ ከተቀመጠችበት መድረክ መሳይ ውብ ቦታ ባሻገር በሁለት በኩል በጡብ ግድግዳ የተከበበ አበባ ሞልቶ ነበር። ወ.ሮ ላምሮት በትልቅ ዣንጥላ በተከለለ የመስታወት ጠረጴዛ ጎን ከተቀመጠችበት ልዩ ወንበር ተነስታ ‹‹ ጤና ይስጥልኝ ራሄል …በድጋሚ እንኳን ደህና መጣሽ ›› አለቻት ፡፡
❤60👍3😱2👏1