አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
569 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ገረገራ


#ክፍል_አስራ_ስምንት


#በታደለ_አያሌው


...."“እስኪ…” አለች ዶክተር ከብዙ ዝምታ በኋላ፣ ወደ በሩ እያመለከተቻቸዉ። “እስኪ አድ አፍታ ላስቸግራችሁ፣ ዉጪ ጠብቁ ያለ ምንም ጥያቄ ሁሉም ምሰስ እያሉ ሲወጡ፣ በክፍሉ እኔና እሷ ብቻ ቀረንበት.

“ልጄን…” ስል ተቀበልኋት፣ ባልቻን የሸኙ ዓይኖቿ ወደኔ ሲመለሱልኝ፡
“ልጄ አታሳዪኝም?”

“ናፈቀችሽ አይደል?”

“ኧረ አልቻልሁም ሽዊት”

“ይገባኛል። አዉቃለሁ”

“ታዲያ አምጭልኛ”

“እያወቅሽዉ? እንደሱማ አይሆንም”

“እንዴት ናት ግን? እንደ ፈራነዉ ሆነ ወይስ እግዜር ተአምሩን አሳየሽ?” አልኋት፣ ፈራ ተባ እያልሁ።

“ኹለቱም”

የምትለዉን እንድትል ጠበቅኋት፡
“እንደ ፈራሁትም ነዉ፤ እግዚአብሔርም ተአምሩን አሳይቶኛል። ኹለቱንም”

አሁንም ጭጭ ብዬ አዳመጥኋት፡ ጠበቅኋት እያየኋት የግንባሯ ሰማይ ዳመነ፡ የዳመኑ ዓይኖቿም እንባ አዘሉ፡ ምንም ሳይቆይ ያዘለዘለ እንባዋ ቡልቅ እያለ ሲወርድ እኔም አልቻልሁም: የኔም ጉንጮች ቀዝቃዛ እንባ አለፈባቸዉ: ከመሬት ተነስቶ ብርድ አንሰፈሰፈኝ

“ቁርጤን ልስማዉ?” አልኋት፣ መጥፎ ነገር ብትነግረኝ ፍጥርቅ ብዬ ለመሞት እየተሰናዳሁ: ከመሞት በቀር ምን ምርጫ አለኝ? ምንም:: እሞታለሁ

“ግልጹል ንገርሽ: ወደ ኦፕራሲዮን ክፍሉ ስገባ፣ አንቺን ለማትረፍ
እንጂ ልጅሽ በሕይወት ትመጣለች ብዬ አልጠበቅሁም ነበር። በሆድ
ሳለች የልብ ምቷ ስናዳምጠዉ በጣም አስፈሪ ነበር። አንቺም ትናትና እንዳልሽኝ በሆድሽ ዉስጥ እየተንቀሳቀሰች አልነበረም: በዚያ ላይ ከመደበኛዉ የመወለጃ ጊዜ እጅግ ቀድማ ስለመጣች፣ ላንቺ ፈርቼልሽ ነበር: በግልጽ ልንግርሽ አይደል ዉብዬ? የልጅሽ በሕይወት መትረፍ፣ ያንቺም በጤና መገላገል የእግዚአብሔርን ሥራ በዓይኔ በብረቱ ያየሁበት
ተአምር ነዉ”
“እንግዲያዉ ምድነዉ የሚያስለቀሰሽ?”
ለመናገር ዳዳችና ተወችዉ፡፡

በጥያቄ የተጥለቀለቀ ፊቴን ስታይ ቆይታ፣ የነርሶቹን መጥሪያ ደወል ተጫነችዉ፡ ደወሉን ሳትለቀዉ ገና፣ ከቅድም ጀምራ በተለየ ሁኔታ ጠብ እርግፍ ስትልልኝ የነበረችዋ ነርስ ያለንበትን ክፍል ከፈት አድርጋ ገባች
“አቤት ዶክተር''
“እስኪ ባክሽ አንድ ነገር ላስቸግርሽ”
“ምን ልታዘዝ ዶክተር?''
“እስኪ ባክሽ ዉብርስት ወደ lCሀ ክፍል እንዉሰድና አንዳፍታ ልጇን
በዓይኗ እናሳያት”
“ኧረ?” አለች፣ ድንግጥ እያለች:
“አይዞሽ፤ አብሬሽ አለሁ: ኃላፊነቱን ራሴ እወስዳለሁ” ስትል
አደፋፈረቻት፣ ነፍሴን የያዘልኝ ግሉኮስ የተንጠለጠለበትን ዘንግ ራሷ ከፍ አድርጋ እያነሳችና መንገድ እየጀመረች:

ነርሷም ትንሽ እንደ ማቅማማት ስትል ከቆየች በኋላ መታዘዟን
አስበልጣ የተንጋለልኩበትን አልጋ
ማሽከርከር ጀመረች መኪና ማቆም ከሚያያስችለዉ የሕንጻዉ ሰፊ አሳንሰር ከነአልጋዬ ከጫኑኝ በኋላ ኹለት ፎቆች ወደ ላይ ወሰዱኝ፡ ከአሳንሠሩ ወርደን ትንሽ እንደ ሄድን፣ ጥልቀት ያለው እንክብካቤ ወደሚደረግበት (ICU) ክፍል ደረስን፡ እጅግ ሰፋ
ወዳለዉ አዳራሽ ከመግባቴ፣ የተለያየ ስምና መጠን ያላቸዉ ማሽኖች ተደርድረዉ አየሁ፡ በአብዛኛዎቹ ማሽኖች፣ በተለይም ያለ ዕድሜያቸው የተወለዱ ሕጻናት ተኝተዉባቸዋል፡ ያዉም በሆድ፣ አፍና አፍንጫቸ
ላይ በልዩ ልዩ ማስተላለፊያዎች ተተብትበዉ፡ በነዚህ ትብታቦች
አማካኝነት በዋናነት ምግብ እና አየር የሚያገኙ ሲሆን፣ ማሽኖች
የየራሳቸዉ ማሞቂያም ሆነ ማቀዝቀዣ የተሟላላቸዉ መሆናቸዉን በስማቸዉ አዉቃቸዋለሁ መሀል ለመሀል እየወሰዱኝ ሳለ፣ በግራም
በቀኝም በኩል ዓይኔ ዉስጥ የገቡትን ሕጻናት ሥራዬ ብዬ ተመለከትሁ ሁሉም እንደየአቅማቸዉ እግርና እጃቸዉን ያወራጫሉ።

ቱናትን ላያት ነዉ፡

ብዙ የተገመተላትን፣ የልጄን ዓይን በዓይኔ ላየዉ ነዉ፡፡ ልጄ ቱናት
ያለችበት ክፍል ዉስጥ መሆኔን ሳዉቅ፣ ይኼ ነዉ ብዬ መግለጽ
የማልችለዉ ሽብር ወረረኝ፡፡ ፍርሃቴም ናፍቆቴም ተደራርበዉ ልቤን ጫፍ ላይ አደረሱብኝ፡፡ ልትወጣ ምንም አልቀራትም፡፡

ፍርሃቴ ጫፉ ላይ ደርሷል፡

“ይቅርታ” አለች ዶክተር፣ ወደ ነርሷ ዘወር ብላ፡ ሲመስለኝ ቱናት
ያለችበት አጠገብ ደርሰናል በዓይኔ ባጣብራት ግን ላገኛት አልቻልሁም ጭንቅላቷ ከፍ ያለ ልጅ ፍለጋ ዓይኔን ባንከራትትም አላገኘኋትም፡ የዶክተሯ ጥቅሻ ገብቷት ነርሷ የያዘችዉን የአልጋዬን ብረት ለቀቀችና
ተመልሳ ወጣች:: ኹለት የክፍሉ ባለሙያዎች በክፍሉ ያሉ ቢሆንም፣በማሽኖች አጠገብ ግን አይደለም የቆሙት ዝም ብለዉ ብቻ እንደ ንቁ ወታደር፣ ወዲያ ወዲህ ይንጎራደዳሉ።

እኔም እሷም ወደ'ዚህ ክፍል ለመግባት፣ ቢያንስ የእነሱ ፈቃድ
እንደሚያስፈልግ እኔም ገምቻለሁ
በመሆኑም በየስማቸዉ ጠርታ ሰላም እያለቻቸዉ ወደ እነሱ ቀረበች: ምን እንደ ተባባሉ ባይሰማኝም፣ ብቻ የሆነ ነገር ብላ አሳምናቸዉ መጣች: በአንድ እጇ ግሉኮስ የተንጠለጠበትን የብረት ዘንግ፣ በሌላ እጇ ደግሞ አልጋዬን በትራስጌ በኩል እየገፋች ዉስጥ ለዉስጥ ተሂዶ ወደሚገኝ ሌላ ክፍል አደረሰችኝ፡: ጠጋ ብላ
ካነጋገረቻቸዉ ባለሙያዎች አንደኛዉ ቀደም ብሎ በመዳፉ አሻራ በሩን ከፈተልንና ገባን፡፡ እሱን በደረቅ ፈገግታም ጭምር እጅ ነስታ ከሸኘችዉ በኋላ፣ እስከ አሁን በጭራሽ አይቼባት የማላውቀዉን ፊቷን አሳየችኝ፡፡

ከተለዩትም የተለየ እክብካቤ ስለሚያስፈልጋት፣ ልጅሽ ያለችዉ
በዚህኛዉ ለይቶ ማቆያ ክፍል ነዉ: ልጅሽን የማየት መብት ቢኖርሽም፣ መንገዱ ግን አሁን የመጣንበት አይደለም: እንግዲህ ያለ ግርግር መምጣት የፈለግሁበት ምክንያት አንቺም የምታጭዉ አይመስለኝም”
ለጥያቄ አፌን እያሞጠሞጥሁ ሳለ፣ ቀልጠፍ ብላ ከአጠገባችን ያለዉን ማሽን ቁልፎች መነካካት ጀመረች ማሽኑ እጅግ ግዙፍ ሲሆን፣ ከላይ የተገለበጠ ሙኸዶ የሚመስል ክዳን አለዉ፡ ልክ መነካካት ስትጀምር፣
ቀድሞ ወደ ላይ ተስቦ የተከረፈደዉ ይኼዉ ክዳን ነዉ፡ በእርግጥ ክዳኑ ብርሃን አስተላላፊ ስለሆነ፣ ለቆመ ሰዉ እንደ ተከደነም ቢሆን ወደ ዉስጥ
ከማየት አይከለክልም፡ እኔ ግን እንደ ተንጋለልሁ ስለሆነ ተከፍቶልኝ እንኳን ልጄን ማየት አልቻልሁም እስከመጨረሻዉ ድረስ አልጋዬን ከወገብ በላይ አቃንታልኝ፣ ራሷ የመሸከም ያህል ደግፋ ቀና አደረገችኝ
እና ወደ ዉስጥ እንድመለከት አመቻቸልኝ፡

በሙሉ ዓይን ባይሆንም፣ አንገቴን ቀና አድርጋ አሳየችኝ አየኋት
ቱናትን አገኘኋት።እንደ ተፈራዉ ናት።

“ስንት ኪሎ ሆነች?” አልኋት፣ የጭንቅላቷን ግዝፈት እያስተዋልሁ፡አትሆንም እንጂ ኹለት ኪሎ እንኳን ብትሞላ ከግማሽ በላዩን የሚመዝነዉ ጭንቅላቷ እንደሚሆን ያስታዉቃል፡ ዓይኖቿ ወደ ዉስጥ
መቀበራቸዉ ሳያንስ ከተመለከቱም የሚመለከቱት ቁልቁል ብቻ ነዉ፡ እንቅስቃሴ የሚባል የላትም፡ የተኛ ሰዉ እንኳን ሲተነፍስ ሆዱ ላይ ብቅ ጥልቅ ይታይበታል፡ ልጄ ግን ጸጥ ብላለች፡ እኔን ልጄ!

“መቼስ እግዚአብሔር ምን ይሉታል?” አልሁ፣ ተአምሩን ለእኔም ያልገለጠልኝን አምላክ በመቀየም እና በማመስገን መካከል ሆኜ:

“ኧረ እንጃ። ከፊት ለፊትሽ ግን እንዲህ ነዉ የማይሉት ፈተና እንዳለ ልዋሽሽ አልፈልግም: ትእዛዝ ተቀባይ ነርቮች ብዙዎቹ በትክክል አይሠሩም: ስፓይናቢፊዳ እና ሀይድሮሴፋለስ ከጠበቅናቸዉም በላይ ሆነዉ
👍30
#ገረገራ


#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ


#በታደለ_አያሌው

...“እኮ ልትገድሏት?” አልኋት፣ በምን ተአምር ከአልጋዬ እንደ ተነሳሁ ሳይታወቀኝ፡ በቂጤ ቁጭ ብያለሁ

“ሽዊት? ለካ እስከዚህ ድረስ ጨካኝ ሆነሻል?”

“መቼም እኔን ታዉቂኛለሽ:: እኔ በሙያም በእምነትም ዓይን ስለማየዉ፣ እንደማልስማማበት ታዉቂያለሽ: ግን በእሱ እምነት ይኼ መግደል ሳይሆን ማዳን ነዉ”

“ቆይ ቆይ! ለምንድነዉ ይኼን ለኔ የምትነግሪኝ አሁን?”

“እኔ እንጃ: ምናልባት እንዲህ ያለ እምነት ያለዉ ሐኪም መኖሩንም
ማወቅ ከፈለግሽ ብዬ እደሆነ”

“አወቅሁ: ከዚያስ?”

“እመኚኝ ዉቤ፣ እኔም አልተስማማሁበትም…”

“በቃሽ!”

ንዴት አቅሌን አሳተኝ፡፡

ክፉና ደጉን የተጋራኋት የቀድሞ ጓደኛዬ አስጠላችኝ፡ ብዙ የተፈተንሁባትን ልጄን መግደል እንደ ማዳን የሚቆጥር ወዳጅ እንዳላት ከነገረችኝ በኋላ፣ ፈጽሞ ዓይኗን አያሳየኝ አልሁ: ዉዬ አድሬ ሳብሰለስለዉ እንዲያዉም፣ ሐሳቡ የወዳጇ ብቻ ሳይሆን የእሷም ጭምር መሆኑን ስለጠረጠርሁ ለሆስፒታሉ አስተዳደር ሳይቀር ከሰስኋት። እሷ የነገረችኝ ለብቻዬ ቢሆንም፣ እኔ ግን ያላዳረስሁባት ሰዉ የለም፡፡

ጨርሼ፣ እንደ ቀዉስ ሆኜ ሰነበትሁ።

ቱናትን ከተገላገልሁ ዛሬ ኹለት ወር ስለ ሞላኝ ቱናትን ይዤ
ከሆስፒታል የምወጣበት ቀን መሆኑን ሰምቻለሁ ዛሬ፣ በጥልቀት
እንክብካቤ ይደረግላት ከነበረችበት ክፍል ወጥታ በእቅፌ ትገባለች ጡቶቼን አጉርሻት በእናት ስስት እያየኋት፣ እስከማጠባት ጓጉቻለሁ።በዚ ላያ ላይ የሆስፒታል ቆይታዬም ጉሮሮዬ ላይ ደርሷል፡ ከዚህ በላይ
እንደ እስረኛ በአንዲት ጠባብ ክፍል ተከልክዬ ለመሰንበት ቀርቶ
ለአንዲትም አዳር የሚበቃ ትዕግሥት የለኝም፡ ሙጥጥ ብሎ አልቋል።

“በሉ ልጄን አምጡልኛ፣ ልዉጣበት” አልኋት ነርሷን፣ መጥሪያዉን ደዉዬ እንደ መጣችልኝ፡

“ሂሳብ ክፍል ያለዉን ነገር ጨረስሽ? ከጨረስሽ መዉጣት ትችያለሽ''

ልክ ይኼን ብላኝ ስትጨርስና ባልቻ በሩን ከፍቶ ሲገባ አንድ ሆነ፡
ከሆስፒታሉ ያለብን ቀሪ ሂሳብ ቀድሞም ተነግሮን ስለነበር፣ ገንዘቡን ይዞልኝ መምጣቱ ነዉ፡ የሚከፈለዉን ከፍለን፣ የሚፈረመዉንም ሁሉ
ፈርመን ስናበቃ፣ ቱናት ኹለት ወር ሙሉ ጥልቅ እንክብካቤ ስታገኝበት ከነበረዉ ልዩ ክፍል በነጭ ፎጣ ተጠቅልላ መጣችልን፡፡ ያመጣችልንን
ነርስ ደህና አድርገን አመሰገንናት፡ ልጄን ተቀብዬ ላቅፋት እጄን ስዘረጋ ሁሉ፣ ቅር ብሏታል ነርሶች ግን ታድለዉ! ልበ ጥሩዋ ነርስ፣ ቱናትን የሰዉ ሰዉ ሳትል እንዴት እንደምትሳሳላት ሳይ እንደገና አመሰግንኋትአስከትላም ልናደርግላት የሚገባዉን ጥንቃቄ
አስረዳችን: ቱናት ራሷን ችላ ካካ ማድረግ ስለማትችል ትንሿን ጣታችንን እየተጠቀምን እንዴት ማጸዳዳት እንዳለብን አደራ አለችን በተጨማሪም ሌሎች ማስታወሻዎች በሥዕላዊ መንገድ የተገለጹበትን መጽሔት
ሰጠችንና፣ አስታቀፈችኝ፡፡
ልጄ ቱናትን ለመጀመሪያ አቀፍኋት፡

ከወለድኋት ከኹለት ረዣዥም ወራት በኋላ፣ ከቱናት ጋር ትንፋሽ
ለትንፋሽ ተገናኘን፡ ወደ ታች ተቀብሮ ግራና ቀኝ እንደ ነገሩ ከሚቃብዘዉ ዓይኗ እና ሲር ሲር ከሚለዉ የጭንቅ ትንፋሿ በቀር እንዲህ ነዉ የሚባል
እንቅስቃሴ የላትም፡ እግሯ አይላወስም፡ ጡቴን ዳብሳ ታገኘዋለች ብጠብቅም፣ አፏ ላይ አድርሼላት እንኳን ጎርሶ መጥባቱ አልሆንልሽ አላት፡ ዝም ብዬ ጭምጭም እያደረግሁ ሳምኋት
ትንፋሿን አሸተትሁት ደስ ይላል
“ወደ እመዋ ቤት አይደል?” አለኝ ባልቻ፣ መኪናዉ ዉስጥ እንደ ገባን የወንበሩን ቀበቶ በትካሻዉ ላይ እያዋለ፡፡ ቁልፉን ወደ ቀኝ ጠምዝዞ ሞተሩን አስነሳና፣ በፊተኛዉ መስታዎት ወደ ኋላ እያየኝ መልሴን
ተጠባበቀ

“አይ እኔ እንኳን ቤቴ ነበር መሄድ የፈለግሁት” አልሁት፣ ሲራክ ፯ ወደ ተከራየልኝ ምስጢራዊዋ የግሌ ቤት ለመሄድ በመምረጥ፡ “ለእመዋም ተጨማሪ ጫና ከምሆንባት፣ ፈተናዬ ራሴ ብወጣዉ ነበር የሚሻለኝ።
እሷን ለማሳመን የሚሆነዉን ምክንያት ግን ከየት ልዉለደዉ?”

“አለማፈርሽ!” አለ፣ ባልቻ “ሆ!”

“የአራስ ወጉ እዳይቀርብኝ ብለህ ነዉ?”

“ኧረ ተዪ አቺ! እናቷን አስቀምጣ ለብቻዬ ካልታረስሁ ያለችዋ
የመጀመሪያዋ እናት ልትሆኚነዉ እንዴ? ሆ! በይ ተይ፤ ዕድልሽንማ
አትቀልጅበት!''

“በል እሺ እንሂድ”

“ወደ እመዋ ቤት?”

“ይሁን”

ወደ እመዋ ቤት ሄድን፡፡ ልክ ከግቢዋ በር ስንደርስ በሕልሜም በዉኔም ያለልጠበቅሁት እልልታ መንደሩን አቀለጠዉ፡ መነሻዉን ለማወቅ ዞር ዞር ስል ያደገደጉ ቆንጆዎች እና ጎበዞች እርጥብ ጨፌ እየጎዘጎዙ ተቀበሉን፡፡ በአቀባበሉ እየተደነቅሁ ወደ ዉስጥ ብቅ ስል፣ የእመዋ ግቢ
ጭራሽ የጥምቀት አደባባይ መስሏል: ከግቢዉ ጫፍ እስከ ጫፍ የሚደርስ ዳስ ተጥሎበት፣ የንፋስ ማለፊያ እስኪጠፋ ድረስ በሰዉ ጢቅ ብሏል፡ ያልመጣ የአዲስ አበባ ሰዉ መኖሩን ሁሉ እንጃ፡፡ የእመዋ ጎረቤቶች፣ በቀጥታ እኔን የሚተዋወዉቁኝ፣ በባልቻ በኩል የሚያዉቁኝ፣
የእሸቴ ዘመዶች፣ በእህቶቼ በኩል የሚያዉቁኝ ሁሉም እዚህ አሉ፡
የንስሐ አባቴን ጨምሮ፣ በዛ ያሉ ካህናት ሁሉ ተገኝተዋል። ከሁሉም
ከሁሉም በላይ የገረመኝ ግን የተጣላኋት አዋላጅ ሐኪሜን፣ ሸዊትን እዚህ ማግኘቴ ነዉ፡ ተጣልቻት ንግግርም ከልክያት እንዳልነበር፣ ሚያሸንፍ ፈገግታዋ እንደዚህ ስታየኝ ግን አልቻልሁም: እኔም ፈገግ አልሁላት ወደ ዉስጥ በዘለቅሁ ቁጥር፣ ልክ ለንግሥ የወጣ ታቦት በአጠገባቸዉ የሚያልፍ ይመስል፣ጎንበስ ቀና እያሉ እልልታዉን አደበላለቁት “እንኳን ማርያም ማረችሽ” የሚል ምርቃት እንደ ጉድ ተዥጎደጎደ፡ እንደ ታቦትም፣ እንደ ሙሽራም፣ እንደ አራስም ነዉ የተከበርሁ፡ እመዋ በተለይ፣ አይቼባት የማላዉቀዉ ዓይነት ደስታ
ፈልቆባታል ልክ እንደ ልጅ አድርጓታል፡

ቱናትን ስታቅፋትማ ደስታ የሚያደርጋትን ነዉ ያሳጣት፡ ያዉም እኮ እንደ ተሸፋፈነች አቀፈቻት እንጂ ገና ገልጣ እንኳን አላየቻትም እንቅልፍ ወስዷት ስለነበር፣ ፀሐይም ላይ ላለመግለጥ ብላ እንደ
ተሸፋፈነች ከልቧ አጠገብ ደረቷ ላይ ልጥፍ አደረገቻት እና እኔን ወደ ዋናዉ ቤት ጎተተችኝ፡፡

ደስታ በደስታ ሆናለች ፍልቅልቅ ብላለች

“እመዋ”

“አቤት የኔ ልጅ”

“ምንድነዉ ጉዱ?”

“የምን ጉድ? ደስታ ነዉ ጂ! ሰርግሽም አይደል?''

“እ?” አልኋት፣ ከተናገረችዉ ያልስማሁት ቃል ያለ ይመስል
“ዓለሜን አሳየሽኝ ልጄ: ድሮዉንም ቢሆን ከአባትሽ ጋ እንጨቃጨቅ
የነበረዉ በአንቺ የሕይወት መንገድ የተነሳ አልነበር? እኔ ወትሮዉንም ዓለምሽን ማየት ነበር ምኞቴ: ይኼዉ ደራርበሽ አሳየሽኝ። ክብር አለበስሽኝ። ደግ አደረግሽ የኔ ልጅ! እልልልልል!”
ደስታዋ መረጋጋቷን ነጥቋታል: እያቻኮለች ወደ ዋናዉ ቤት አስከትላኝ ገብታ፣ ቱናትን ልታስተኛልኝ ክፍት ካሉት መኝታ ክፍሎች ያደረሳትን
መረጠች: እንዳደረሳት የመረጠችዉ ክፍል ግን የጃሪም መሆኑ የኔን ያህል ቀርቶ ምንም ያሰጋት አልመሰለኝም: በእርግጥ ይኼኛዉ ክፍል ለሳሎኑ ቅርብ በመሆኑ ቱናትን አስተኝቻት ብወጣ እንኳን ቶሎ ቶሎ እየመጣሁና እየሄድሁ በደህና መተኛቷን ለማየት ያመቸኛል: ችግሩ ግን
የጃሪም ክፍል ነዉ፡ ይኼን ጭንቄን ያላወቀችልኝ እመዋ፣ ዝም ብላ ቱናትን በጥንቃቄ አስተኛችልኝ፡ ከዚያ ቀዝቀዝ የምትልበት ትንሽ አፍታ
ከታገሰቻት በኋላ፣ ገለጥ አድርጋ አየቻት፡ እንደገና ሳመቻትና በንጹሕ
አዲስ ጋቢ ጥቅልል አድርጋ መልሳ አስተኛቻት፡፡ ቅሬታዬን እንኳን ለመግለጽ ፋታ ሳትሰጠኝ፣ ወዲያዉኑ እጄን ይዛ እንግዶች ወደ ሞሉት ዳስ ጎተተችኝ፡፡

“አንዴ? ልጄን ትቼ!?”

“ተኝታ የለ፤ ምንም አትሆንም”

“ብቻዋን?”
👍374👎1🔥1
#ገረገራ


#ክፍል_ሀያ


#በታደለ_አያሌው


ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ያለሁበት ክፍል ተንኳኳ።

“ጎሽ! ደረስሽልኝ ሸዊት?” አልሁ፣ እንባ ሲጠምቁ የቆዩ ዓይኖቼን በቱናት ጋቢ እያደራረቅሁ። ቱናት ደክሟት ይሁን እንጃ፣ ብቻ እየሰለለ መጥቶ የነበረዉ ለቅሶዋን ጨርሳ ትታዋለች: እንዲያዉም ያንን ሲር የሚል ትንፋሿን እንደገና መስማት ጀምሬያለሁ፡ ቢሆንም ግን
አላመንኋትም እነዚያ ቁልቁል ሰርገዉ እንደ ነገሩ ግራ ቀኝ የሚባክኑት
ዓይኖቿን ድንገት የምትከደንብኝ መሰለኝ፡፡ ይቺኑ ትንፋሿንም የማጣት መሰለኝ፡ ፍርሃት ፍርሃት ብሎኛል።

እሷን እሷን እያየሁ የጎድን ሄጄ፣ የበሩን ቁልፍ ጠምዝዤ ከፈትሁት

“አገኘሽ? አመጣሽልኝ?” አልሁ ቀና ብዬ እንኳን ሳላይ፣ መልሼ ጣቶቼን የቱናት ልብ ላይ እያስቀመጥሁ የልብ ምቷ አንጻራዊ መሻሻል እንዳለዉ ሳዉቅ፣ ተመስገን› ብዬ ሙሉ ቀልቤን ወደ ሸዊት ሳዞር
አጣኋት: እሷን በጠብቅሁበት ቦታ፣ ጃሪም ድፍርስ ዓይኑን ልጄ ላይ ተክሎ ቆሞበታል ለካ ለእሱ ነዉ በሩን የከፈትሁለት?

“የልጅሽ አባት…” አለኝ፣ ዓይኖቹን ከቱናት ላይ ሳይነቅል።

ደንግጫለሁ። ደረቅ ሊሾ ላይ እንደ ወደቀ ሸክላ ነዉ ድቅቅ ያልሁት።

እዚህ መሆኔን እንዴት አወቀ? ምን ቀረዉና መጣ ደግሞ? ምን ሊያደርገኝ? ልጄን ሊገድልብኝ? እንዲያዉም ፍርሃት ላይ ነበርሁ፣ ጨረሰኝ: በዓይኑ እና በቱናት መካከል ቆሜ አንዴ እሱን፣ አንዴ ደግሞ
ቱናትን በማየት ተወጠርሁ ከአሁን አሁን እጁን አነሳባት እያልሁ፣
ለመከላከል እንደ ምንም ጡንቻዎቼን አነቃቅቻለሁ።
“የልጅሽ አባት ግን ማነዉ? ማነዉ ያ ደብተራ ሰዉዬ፣ ባልቻ ነዉ ማን
የምትዪዉ ?»
መልስ አልሰጠሁትም አሁን እዉነት ባልቻ ጠፍቶት ነዉ "ያ" ብሎ የማያዉቀዉ የሚመስለዉ? ካላወቀም ሲራክ ፯ን እና ባልቻ የሲራክ፯ ዋና ኃላፊ መሆኑን አይወቅ እንጂ፣ ቢያንስ በአነጋጋሪ ድርሰቶቹ የተነሳ ባልቻን የማያዉቅ ሐበሻ የለም አለማድነቅ ሌላ፣ አለማወቅ ግን ሌላ ዉሸት፡

“ከእሱ ነዉ የወለድሻት ኣ? ብቻ ከማንም ዉለጃት፤ እሱ አይመለከተም ነበር ! ግ ን እሱ ሰዉዬ፣ ያለሁበት ድረስ ትናትና መጥቶ ሲመክረኝ ሲመክተኝ.” አለ፣ በማላገጥ በዙሪያዬ እየተንጎራደደብኝ፡ “ባይገርምሽ በንግግሩ ከመነካቴ የተነሳ፣ እራቴን እንኳ ን ሳልጠጣ ነዉ ያደርሁት
ብታይ። በጣም ነዉ የተሰማኝ"
ልጄን ለመከለል በእሱ እንቅስቃሴ ትይዩ እየተንቀሳቀስሁ፣ ስላቁን
አዳመጥሁለት “እናትሽ እናቴ አይደለችም, አልሁ እንጂ እናቴ አትወደኝም ያልሁት ይመስል፣ ‹እናትህ ትወድሃለች እያለ ሊሰብከኝ አማረዉ። ሱራሎ፣
እናትህ፣ አባትህ፣ ወደዚህ፣ ወደዚያ እያለ ሲዘበዝብብኝ አመሸ''
አለኝ፣ ስላቁን ለዘብ አድርጎ፡
“ትዝ አይልህም ግን?''
“ምኑ?”
“የሱራሎዉ ጊዜ ጎርፍ: ያ ጊዜ ረሳኸዉ? እመዋን ለማትረፍ ዘለህ የገባኸዉን? ሁላችንም የተሟሟትነዉ ? ''
ጀርባዉን ሰጥቶኝ ቆመ፡

“ረሳኸዉ?”

“አለማፈርሽ!” አለ የደም ሥሮቹ እየተገታተሩ። “አፍሽን ሞልተሽ
ሱራሎ ስትይ አለማፈርሽ! ቆይ ቀድሞ ነገር በምን ሆነና እናትሽ እናቴ አለመሆኗ ፣አንቺም እህቴ አለመሆሽ የተገለጠዉ? መቴ መሰለሽ? !! እ'
ከዚያ በኋላ እኮ ነዉ”

ዓይኖቼን በልጥጬ፣ አፍ አፉን አየሁ
“እንደዚያ ነፍሴን ለአደጋ ሰጥቼ ከዉሀ ሙላት ያተረፍኋት እናትሽ በቡናዉ እና በየእድሩ የምታወድሰዉ አንቺን ብቻ ሆነ። (ዉዷ ልጄ የምትለዉ፣ (መመኪያ የምትለዉ፣ (አተረፈችኝ የምትለዉ አንቺን ብቻ ነዉ። እኔስ? ሌሎቹስ? ጭራሽ በቦታዉ እንኳን የነበርን አታስመስይዉ
ነበር እኮ: አሁን ምን ተገኝቶ ነዉ ታዲያ፣ ሱራሎ ሱራሎ አልሽኝ በይ? እ!?”

“ኧረ እኔ የተለየ አፍ ኖሮኝ አያዉቅም: ሱራሎ አስቤ አንተ ረስቹ
አላዉቅም: የሱራሎን ነገር ለሰዉ ስነግርም፣ በዚያ ጊዜ ወንድሞቼ እና
እህቶቼ የፈጸማችሁትን ሁሉ በጭራሽ ረስቼዉ አላዉቅም”

“ተዪ እንጂi” አለኝ፣ ቢያሳየኝ ቢያሳየኝ የማያልቅበትን የሽሙጥ ሳቁን
መልሶ እያመጣብኝ፡፡ “እሱን ተዪዉና፣ ባልቻ ተብዮሽ፣ ምን ብሎ እንደ
ጠየቀኝ ነገረሽ? ‹ቤተሰብህን ለምን ማፍረስ ፈለግU? ብሎኝ አረፈዋ!
እንዴት ነርቬን እንደ ነካኝi” አለኝ፣ ወዲያ ወዲህ መንጎራደዱን ትቶ ፍጭጭ ያለ ሳቅ እየሳቀብኝ፡ “ግን እኮ እዴት እኔ ማፍረስ እችላለሁ? ነዉ ወይስ መጀመሪያዉኑም፣ ቤተሰባችን የዉሸት ቤተሰብ ነበር?”

“የዉሸት?” አልሁት፣ አላስችል ቢለኝ በቆየሁ ቁጥር ለእሱ የነበረ ፍርሃት ለቀቅ እያደረገኝ መጥቷል። ልጄ ግን በረኀብ እንዳትሞትብኝ አሁንም እፈራላታለሁ

“እህስ!”

“እንዴት ነዉ የዉሸት?''

“ሌላዉ ይቅር እሺ። ግን… ኹለት ልጆች፣ መንታ ሳይሆኑ ግን ደግሞ ከአንድ እናት ተወልደዉ ዕድሜያቸዉ እኩል መሆኑ አይደንቅም ነዉ የምትዪኝ? ''

“እንዴት?” እንዴት አልሁኝ፣ እዉነትም አሁን አሁን ስናድግ እየተዉነዉ መጣን እንጂ፣ የእኔና የእሱ ልደት ይከበርልን የነበረዉ በአንድ ቀን መሆኑ ትዝ ብሎኝ፡፡

“ኅዳር 14 አይደል?”

“ልደታችን?”

“እ”

“አዎ” አልሁት፣ ምን እየጠቀለለብኝ እንደሆነ እንኳን ሳይገባኝ።

“እና ኹለታችንም ኅዳር 14 ተወልደን ነዉ የምትዪኝ?''

“ሌላ ምን ይሆናል?”

“መንታ ነን እንዴ ? ''

“አይ፣ እንደዚያ እንኳን አይመስለኝም”
“እሺ በተለያየ ዓመት ግን በአንድ ዓይነት ቀን ተወልደን ነዉ?”

“እንደሱም አይመስለኝም” አልሁት፣ በዕድሜ እንደማንበላለጥ
አስታዉሼ፡ የኹለታችንም ዕድሜ እኩል ከሆነ በተለያየ ዓመት ልንወለድ
አንችልም።

“አየሽ ጅልነታችሁን? ስትሸዉዱ እንኳን ብልሃቱን እታዉቁበትም: ኅዳር
14፣ አባትሽ አባቴን በመተት ገድሎ ርስቱን የቀማበት ቀን ነዉ። እንደዚህ
ነዉ የተሳለቃችሁብኝ! የእኔ የሐዘን ቀን ለእናንተ በዓል ነዉ! በእናቴ ቤት
ነዉ እናትሽ እንኳን እናት የመሰለችዉ!”

“ኧረ በማርያም! በማርያም ተዉ። እንዴት እዴት ነዉ የምታወራዉ?”

“ገብቶሻል። ግጥም አድርጎ ገብቶሻል”

“አንዴ” ሳቄን መያዝ አልቻልሁም: ለቀቅሁት። “ቆይ ምኑ ነዉ
የሚገባኝ? ''

እሱ ግን ብልጭ አለበት፡ እንደ ምንም ለመረጋጋት ወደ ግድግዳዉ ዞሮ
ከቆየ በኋላ፣ በዚያ ድፍርስ ዓይኑ መልሶ ጥብስቅ አድርጎ ያዘኝ፡፡ ያዉም
በኃይል እስከሚያመኝ ድረስ!
“ሲራክ ማነዉ?” አለኝ፣ ከዓይኑ ማምለጫ እየፈለግሁ ሳለ፡ እርፍ! ጭራሽ ሲራክ ፯ን ያዉቀዋል? መንግሥት እንኳን እስካሁን ያልደረሰበትን ሲራክ ፯ን ጃሪም ያዉቀወዋል? የብሔራዊ መረጃና ደኀንነት
አገልግሎት እኮ ማኅበራችንን በፖለቲካ ከመጠርጠር ባለፈ፣ እስከዚህ
አያዉቀዉም: ተአምር ነዉ!

“ሲራክ ምንድነዉ?” አለኝ፣ የባሰ ፍጥጥ ብሎ

“እ?”

“አቺና እናትሽ እዚያ ምን ትሠራላችሁ?”
ትንሽ ተንተባተብሁ፡ ሙልጭ አድርጌ መካድ ቢኖርብኝም፣ አልቻልሁም: አመነታሁ። ነገር ግን መላወሻ የሚባል አልሰጠኝም።

ስለዚህ የታየኝ አማራጭ እዉነቱን ማፍረጥረጥ ብቻ ነዉ፡ በእርግጥ
በሲራክ ፯ ሥነ ምግባር መሠረት፣ ቁጥር አንድ የሚባለዉ ወንጀል፣
አሁን እኔ ቀጥዬ የማደርገዉ ድርጊት ነዉ፡፡ እንደ ሕጋችንማ፣ ከቅርብ ኃላፊዬ ግልጽ ይሁንታ ካልተሰጠኝ በቀር፣ ማንም ቢያስፈራራኝም ሆነ
ቢያዉጣጣኝ፣ እንኳንስ በማኅበራችን ሥር ስላለዉ ሲራክ፯ ህልዉና ይቅርና፣ ስለ መጽሐፍ ቅዱሱ መጽሐፈ ሲራክ ቢሆንም ማዉራት አልችልም፡ ይኼ በማንኛዉም አባል የሚጠበቅ ሕግ ነዉ

አሁን ግን ይኼን ሕግ በመተላለፌ የጃሪምን ልብ የማለሰልሰዉ
ስለመሰለኝ፣ ልሽረዉ ነዉ፡
👍35👎1🔥1🥰1
#ገረገራ


#ክፍል_ሀያ_አንድ


#በታደለ_አያሌው


...ብችል ሀገር፣ ካልቻልሁ ግን ከተማ መለወጥ እንዳለብኝ ወስኜ ልጄን ጠቅልያለሁ ዓይኔን ጨፍኜ ስለ መጥፊያ አማራጮቼ ሳስብ ቆየሁና፣ ልጄን አቅፌ ቀና ስል በሰዉ ተከብቢያለሁ፡ እየቆየ ትንፋሽ እስከሚያጥረኝ ድረስ በዳስ የነበረዉ እድምተኛ ሁሉ እየመጣ ተኮደኮደ፡ ሁሉም
የቅድሙን የጃሪምን ሁኔታ ተመልክቷልና፣ አንድ አንድ እያለ መጥቶ መኝታ ክፍሉን እጭቅ ብሎበታል፡ የጃሪም መኝታ ክፍል ከሳሎኑ ጋር አንድ ግድግዳ የሚጋራ እና በሩም ሰፋ ያለ በመሆኑም ፣ ከዉስጥ የተረፈዉ
ሰዉ በዋናዉ ሳሎን ሆኖ ትከሻ ለትከሻ እየተጋፋ በበራፉ በኩል ቱናትን በዓይኑ ይወጋል። ያሽሟጥጣል፡ ከሩቅም ከቅርብም፣ ሹክሹክታ
ይሰማኛል፡

“እንዲህ ናት እዴ ለካ?” አለች አንደኛዋ በለሆሳስ፣ ግን ደግሞ
እንዲሰማኝ አድርጋ
“ጭንቅላቷ ደግሞ ምንድነዉ የሚ ያህለዉ?” ስትል ተቀበለቻት ሌላኛዋ፣ ገንፎ ያላመጠችበት ጥርሷን ለሳቅ እያገጠጠችዉ፡፡
“ገዳም ቅብጥርሴ ይላሉ እንዴ ቄሱ ደግሞ? ሆ! ሲጀመር ልክስክስነቷ መስሎኝ እዲንህ ያለ ልጅ ያስታቀፋት! መኝታዋን እንኳን በወጉ ለማድረግ ያላስቻላትን፣ እንዴት ብላ ነዉ ለገዳም ማዕረግ ትበቃለች ብለዉ የጠበቋት?”

“ጉድ እኮ ነዉ! ኧረ የሕጻኗን ዓይን ተመለከቺልኝ: እንዴት ነዉ ደግሞ
የምታቃስተዉ በናትሽ? አይ ይቺ ልጅማ አትተርፍም። ምናለች በዪኝ
ኋላ፤ የሳምንት ዕድሜ እንኳን አይኖራትም”

“የልጇ አባት ግን የትኛዉ ነዉ፤ ያ ከጎኗ ተቀምጦ የነበረዉ ጅላጅል ነዉ እዳትዪኝ ብቻ

ነዉ እንጂ እሸቴ ይባላል አሉ: ከሴተኛ አዳሪ ጭን አይጠፋም ሲሉ ሰምቻለሁ”

“ሂጅ ሂጅ ሂጅ… በስመ አብ!”

“ይቺን የመሰለች ልጅ ወስዶ እዚያ ምን እንደጣላት ላምን አልችልም
መቼም”

“አንቺ ደግሞ፣ሙሉ አድርጎ የፈጠረዉ ሰዉ አለ ብለሽ ነዉ? እንጂ እሷንም አታያትም? እኔ ነኝ የምትል ቆንጆ ደፍራ በዉብርስት አጠገብ ታልፋለች? ቆንጆ የሚለዉ ቃል እኮ አይበቃትም: ታዲያ ምን ዋጋ አለዉ? በአልጋ ሲለምኗት አፈር ሆና አረፈቺዋ! የቆንጆ ልክስክስ እሷን አየን”

“እግዚአብሔር ሲጣላ ደግሞ እንዴት እንደሚቀጣ አየሽልኝ አይደል?”

“አመንሽ? ባለፈዉ ለጃሪም እህቱ አይደለችም ስልሽ፣ እንዲያ
ስትሟገችኝ አልነበር? ይኼዉ ዛሬ ከራሱ አፍ ሰምተሽ እንኳን ለአፍ
እላፊሽ እፈሪ ተዋርደሻል''

“ኧረ እሱስ ደገቆኛል: እህቱ አይደለችም ማለት ነዉ በቃ?”
“እሷ ብቻ ናት ወንድሜ ስትለዉ የምትሰማዉ እንጂ፣ የእሷ እህትነት ከእሱ አፍ ተሰምቶ አይታወቅም ነዉ የሚባለዉ። እንዲያዉም ይኼ ግቢ
ከነቤቱ የእናት የአባቱ ነዉ አሉ እኮ: ከእነእናቷ አስወጣታለሁ እያለ ሲዝት የሰሙት ሰዎች ናቸዉ የነገሩኝ በእናትም በአባትም አይገናኙም አሉ

አሮጊቷ ራሱ በገዛ ርስቱ ላይ ተደላድላ ለመኖር ስትል እናት መሰለች እንጂ፣ የእናትነት ምልክቱ የላትም”

“ አንዴ... በየከተማዉ በየገጠሩ ሲንከራተቱ ኖረዉ ቅርብ ጊዜ
አደለም እንዴ ወደዚህ የመጡት?''

“እኮ! ድንገት ዱብ ብለዉ ነዉ አሉ አሁን ባለቤት የመሰሉት''

“እኔ አሁንም ላምን አልቻልሁም:: ጭራሽ አሮጊቷ የጃሪም እናት
አይደለችም ማለት ነዉ?''

“እየነገርሁሽ!”

“ይገርማል”

“የእሱ ይገርምሻል እንዴ አንቺ? ዝማምን ታዉቂያት የለ?''
“ዝማም ዝማም… ዝማም የዚችን እህት ማለትሽ ነዉ ወይስ ሌላ?”
“ወይ እህት እቴ: እኔማ ገና ትናንት አይደል እንዴ የምሰማዉ ?

“ምኑን? ”

“እህቷ አይደለችም''

“እርፍ! እሷም?”

“አይደለችም”

አንድ አንድ ብሎ እየገባ ቤቱን ጥቅጥቅ ብሎበት የነበረዉ እንግዳ ሁሉ፣ የቻለዉን ያህል ልጄን ተጠቋቁሞባት ሲበቃዉ፣ ቀስ በቀስ ስለ ወጣ በቤቱ
የቀረዉ ሰዉ ቀነሰ፡ ቀለል ማለቱን ተጠቅሜ ሐሜተኛ ሴቶቹን ዞሬ
በዓይኔ አጣበርኋቸዉ፡ ትኩር ብዬ ስመለከታቸዉ ልክ በድምፃቸዉ
እንደ ጠረጠርሁት እነዚያዉ ተናግሮ አናጋሪዎች ናቸዉ፡ ከአራት ወር በፊት፣ በታዕካ ነገሥት ገዳም ከእመዋ ጋር ቆይቼ ስወጣ መንገዴ ላይ ቆመዉ እህቱ ናት እህቱ አይደለችም እያሉ የተወራረዱብኝ ሴቶች ናቸዉ ምንም አላልኋቸዉም በዚያም ላይ፣ ልቤ ቆሟል ወዴት እንደምሄድ ባላዉቀዉም፣ ልጄን ይዤ ብን ብዬ ከመጥፋት ዉጪ ምንም ምርጫ አይታየኝም ጨክኛለሁ እንግዳዉ ከዳሱ እየተንጠባጠበ ወጥቶ ወጥቶ፣ ጥቂት ሰዎች ቀርተዉበታል፡ የመስኮቱን መጋረጃ በስሱ ገለጥ አድርጌ አሳልፌ ስቆጥር
እመዋ፣ ባልቻ፣ እሸቴ እና ጥቂት የቅርብ ዘመዶቻችን ብቻ ቅስማቸዉ ድቅቅ ብሎ ይታዩኛል፡ እርስ በእርስም አያወሩም: የደስታ ጫፍ እንቀምስበታለን ያሉት ቀን በብላሽ ቀርቶባቸዉ ከፍቷቸዋል፡ እኔ እርግጥ ወደምጠፋበት ለመጥፋት ከአሁን የተመቸ ጊዜ አላገኝም፡ ነገር ግን ጨቅላ ልጅ ይዤ በእግሬ ልሂድ ብል የት እደርሳለሁ? ያዉም ጨቅላዋ ቱናት ሆና፡ በዚያ ላይ፣ መጀመሪያ ወደ ምስጢራዊዋ ቤት ሄጄ
አንድ አንድ ነገሮችን መያዝ ይኖርብኛል ደግነቱ ዕድሜ ለሲራክ ፯ የብዙ ሀገራት ፓስፖርት በተለያየ ማንነት ወጥቶልኛል፡ ከሀገር መዉጣቴ ካልቀረ፣ ቢያንስ ፓስፖርቶቼን መያዝ አለብኝ ያለ ገንዘብም
የሚሆን ነገር የለም ዞሮ ዞሮ ወዲያ ወዲህ ማለቴ ላይቀር ነዉ።
እንደዚያ ከሆነ ደግሞ መኪናዬ የግድ ታስፈልገኛለች: አሁን የት
እንዳለች ግን አላዉቅም: ምክንያቱም ከነዳኋት ቆይቻለሁ፡ ሆስፒታል ከገባሁ ጀምሮ ታናሽ እህቴ እንድትጠቀምበት ፈቅጄላት እሷ ይዛት ስለሰነበተች፣ ምናልባትም ዳሱ ሲሠራ ቦታ እንዳታጣብብ ብላ፣ በጎረቤት
ግቢ ወይም የሆነ መንገድ ዳር አቁማት ይሆናል፡ በእርግጥ፣ የኔ ብቻ ሳይሆን የማንም መኪና በግቢዉ የለም።

የራሴን መኪና ማግኘቱ ቀላል አለመሆኑን እንዳወቅሁ፣ አልፎ አልፎ መኪና በማልይዘበት አጋጣሚ አገልግሎት የሚያደርግልኝን የታክሲ ደንበኛዬን ደዉዬ ጠራሁት። ወዲያዉኑ፣ ጥላዬን ጠብቄ በጀርባ በኩል
ወዳለችዋ ጠባብ የግቢያችን በር ሰተት አልሁ ሽሽት መሸነፍ መሆኑን ባዉቅም፣ ለልጄ ስል የትም ብሄድ አይገደኝም: ቢቻል ቢቻል ላሳክማት፣ ከሰዉ አፍ ላተርፋት ይገባል፡ ከዚህ በኋላ ማንም እንዲያይብኝ
አልፈልግም ማንም በልጄ ጤና እንዲሳለቅ አልፈቅድለትም።

እንዲያዉስ ገዳምሽ ናት ብለዉኝ የለ የንስሐ አባቴ? ታዲያ ወደ ገዳሜ መግባት አለብኛ! ልበል እንግዲህ ልጄ ዉስጥ ገብቼ ልመንኩስ፡፡
የሚጠበቅብኝን የአመክሮ ጊዜ እንደሆነ በሆስፒታል ቆይታዬ ተወጥቼዋለሁ

ምናልባት ቱናት፣ ከዝቋላ ወይ ከደብረ ሊባኖስ ገዳም የምትለየዉ የራሷ ትክለኛ ስለ ሌላት ብቻ ነዉ፡ ወፍጮም ሆነ እህል የሚገብርላት የለም
እንጂ፣ እሷም ሆነ ዝቋላ የእግዚአብሔር መኖሪያዎች እንደሆኑ ግን አልጠራጠርም ስለዚህ በከተማ የገደምኋትን ገዳም የሚቸግራት ነገር
እንዳይኖር ከፈለግሁ በከተማ ማገልገሉን እገደድበታለሁ
ከከተማም ደህና ሕክምና የምታገኝበት፣ ደህና ከተማ መምረጥ አለብኝ፡

አንዴ ከመነኮሱ በኋላ ደግሞ ዞሮ ማየት እንደ ሌለ አዉቃለሁ፡ አምሮቴ፣ ትዳሬ፣ ሥራዬ፣ ወዳጆቼ፣ ዘመዶቼ የሚሉትን ሁሉ መተዉ ቀዳሚዉ የገዳማዉያን ሕግ መሆኑን አዉቃለሁ ዞሮ አለማየት ፈታኝ ቢሆንም፣ የቀረዉ ይቀራል እንጂ ይኼኛዉን ሕግ ግን አልሽረዉም፡፡ በፍጹም!
👍272
#ገረገራ


#ክፍል_ሀያ_ሁለት


#በታደለ_አያሌው


...መቼም ባልቻን በግልፍተኛነት የሚያማዉ አይገኝም የጃሪምን ግልምጫ ከምንም ሳይቆጥር ፈገግ ብሎ አሳለፈዉና፣ ወደኔ መጥቶ አቀፈኝ፡ እሱን
እዚህ መሆኔን እንዴት አወቀ አይሉትም፡ እኔም በችኮላ ተንከረፈፍሁ እንጂ የትም ብሄድ ከሲራክ ፯ ማምለጥ እንደማልችል ማስተዋል ነበረብኝ፡ እንኳንስ እንደዚህ ተንዘላዝዬለት ይቅርና! የንዝህላልነቱ ንዝህላልነት ደግሞ በገዛ ስልኬ ለሸዊት ስልክ መደወሌ፡ በዚህ ስሕተቴ
እንኳንስ የሲራክ ፯ቱ ባልቻ፣ የተናቀ የመንደር ደመኛ እንኳን ሊያገኘኝ ይችላል።

ባልቻ ከመግባቱ አፍታ ሳይቆዩ እሸቴ እና ሸዊት ተከታትለዉ ገቡ።

“አንቺ?” ስል ተቀበልኋት፣ ከእሸቴ ኋላ መጥታ ለሰላምታ ስታቅፈኝ፡
“እንዲያዉ እስካሁን እያለቀሰችም ቢሆን ገና አሁን ነው የምትደርሽልኝ ማለት ነዉ?” አልኋት፣ ለቂሜ መወጫ ጠበቅ አድርጌ እያቀፍኋት።
የአሁኑ መተቃቀፋችን ትርጉሙ የትየለሌ ነዉ: አንድም በሆስፒታል
ቆይታዬ ዓይንሽን ለአፈር ብያት የነበረዉን ኩርፊያ ጨርሼ ረሳሁላት፣አንድም ለቱናት አምጭልኝ ያልኋትን ወተት ያዉም የሚሆናትን መጠጫ ጡጦ ጭምር ስላመጣችልኝ አመሰገንኋት፣ አንድም ነባሩ
ሰላምታችን እንደዚህ ነዉ፡ እንደገና እቅፍ አድርጌ ጨመቅኋት።

"እ?"

“ኧረ እኔስ ወዲያዉ ነበር የደረስሁት”

“አዎ” አለ ባልቻ፣ ክንዱን ትከሻዋ ላይ እየጫነ፡ “ወተቱን ብቻ ይዛ
ስትመጣ አግኝቻት፣ እኔ ነኝ ጡጦም ጨምራችሁ አምጡ ብዬ ከእሸቴ ጋ መልሼ የላክኋቸዉ። መቼም ምን ዶክተር ብትሆን፣ በዕድሜ ታናሼ ስለሆነች፣ በዚህ ቅር የምትሰኝብኝ አይመስለኝም”

“ኧረ በጭራሽ!” አለች፣ ወተቱን እና የጡጦ እቃዉን እያቀበለችኝ:
“ኧረ ስሚኝማ ዉቤ” አለች፣ የመደነቅ ፊቷን እየገለጠችልኝ፡፡
“ምን”
“ወንድምሽን እኮ ሊፍቱ ጋ አግኝቼዉ አሁን''

“ማንን?” አልኋት ለወጉ፣ ማንን ማለቷ እንደሆነ ባላጣዉም፡፡

“ጀሪምን ነዋ”

“እሺ”

“ምን እሺ ትይኛለሽ? ሰላምታ ከልክሎኝ ሄደ እኮ”

“ኧረ?” አልኋት፣ ከእሽጉ ዉሃ ከፍቼ ወደ ጡጦዋ እየቀነስሁ ዉሃዉ መቼ እንደ ተቀመጠልኝ ግን አላወቅሁም: ከአጠገቡ ሶፍት፣ ፎጣ እና ሌሎች አልባሌ ነገሮችም መኖራቸዉን ሳይ ማረፊያ ክፍሉን ከመያዜ
በፊትም ተቀምጠዉ እንደነበር ገባኝ፡፡

“አይገርምሽም? መቼስ ረስቶሽ ነዉ አትዪኝም ጃሪም እኔን ሊረሳ? ጉድ እኮ ነዉ! ያኔ እንዲያ …” ብላ፣ ተገርማ ቀረች፡፡ እየቆየ እንደገና በኃይል ከነከናት፡ ምክንያቷን አላጣሁትም፡ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ሳለን ለአንድ ዕረፍት እኛ ቤት በነበርንበት ጊዜ፣ ጃሪም ዓይን አብዝቶባት ነበር
እንዲያዉም ደጋግሞ ወድጃታለሁ እንዳለኝ አስታዉሳለሁ ስሜቱን በግልጽ ለእሷ እንደ ነገራት ግን አላውቅም፡ ከአሁኑ ሁኔታዋ
እንዳስተዋልሁት ከሆነ፣ መንገር ብቻም ሳይሆን እሞትልሻለሁ› ጭምር ሳይላት እንዳልቀረ ገመትሁ ያ ሁሉ ቀርቶ አሁን ግን እንደማያዉቃት ከሆነባት፣ ባይገርማት ነበር የሚገርመኝ፡ ያዉ፣ የእኔ ጓደኛ አይደለች?
በእሱ ቤት እኮ አሁን፣ የእኔ የሆነ እና እኔ የነካሁት ሁሉ ርኩስ
ሆኖበታል።

“አጀብ ነዉ አለ ጅብ? የሆነዉስ ይሁንና በምን ዝም አሰኘሻት?” አለች፣ ቱናትን ገለጥ እያደረገቻት፡ ከጀርባዋ አጥንት ላይ ላለዉ ቁስል ጥንቃቄ አድርጋላት፣ አቀፈቻት እና ልትቀመጥ ብትፈልግ መቀመጫ አጣች: ገና
ይኸኔ ነዉ የሆቴል ማረፊያ ክፍል ዉስጥ መሆኔ ራሱ ትዝ ያላት:
የጃሪምን ፊት መንሳት ማመን አቅቷት ዋናዉን ጥያቄዋን እንደ ረሳችዉ ልብ አደረገች፡፡

“ቆይ ቆይ፣ አንቺ ግን እዚህ ምን ትሠሪያለሽ? ከእመዋ ቤት ያዉም ያን ድግስ ጥለሽ? ያዉም ይቺን ጨቅላ ይዘሽ? ምን ልትሆኚ እዚህ መጣሽ በይ?”

ይኸዋ! እንደ ፈራሁት የማርያም መንገድ እንኳን ሳታስቀርልኝ ጥያቄዋን አመጣችዉ ያልሰማሁ መስዬ ዝም ልላት ፈልጌ ነበር፡ ነገር ግን እሷን ሽሽት ዓይኔን የጣልሁበት ባልቻም ከእሷ በላይ አፈጠጠብኝ፡፡ ለራሱ ጉዳይ
ቢሆን፣ ሽንቱ እንኳን የፈለገ ወጥሮ ቢይዘዉ የሲራክ ፯ ጉዳይ ፋታ
እንደማይሰጠዉ እያወቅሁ፣ ለእኔ ሲል ነዉ አትረፍርፎ የሚሰጠኝ። እኔ ግን እንደ ደመኛ ተደብቄዉ እዚህ ሲያገኘኝ ማዘን ይበቃዉ ይሆን? እንኳን ማኩረፍ ሌላም ቢያደርግ እዉነት አለዉ፡ ግን እሱ ነዉና ሰዉዬዉ፣ መተዉ ያዉቅበታል፡ ያም ቢሆን ግን ጥያቄዋን ተጋርቷታል።
እንድመልስላት ከእሷ እኩል እየተቁለጨለጨብኝ ሳለ እሸቴ በሩን ከፍቶ ገባ፡፡ መቼ እንደ ወጣ ግን አላየሁትም ነበር፡፡ ለካንስ እመዋ ደዉላለት፣ እሷን ለማነጋገር ወጥቶ ኖሯል።

“እመዋ ናት የደወለችልኝ። (ልምጣ ወይ እያለች ነዉ፣ ትምጣ እንዴ?" አለ፣ ሳይታወቀዉ በሸዊትና
በባልቻ ከተፋጠጥሁበት ጥያቄ
ሲያስመልጠኝ፡ ባልቻ ቅር እንዳለዉም ቢሆን ቸለል አለልኝ፡ ሸዊትም እንዲሁ ቱናትን እንዳቀፈቻት ከአልጋዉ ጫፍ ላይ ተቀምጣ ወተቱን ለማጥባት ሞከረች::

“እናንተ?” አለች፣ ወተቱን ልታጠጣት ሞክራ ሞክራ እንዳልሆነላት ስታዉቅ ተስፋ እየቆረጠች። “ቱናት የተለየ ልምምድ ሳያስፈልጋት
አይቀርም: ከተወለደች አንስቶ ኹለቱን ወር ሙሉ የከረመችዉ ግሉኮስ ተተክሎላት ስለነበር፣ ከጡትም ሆነ ከጡጦ ምግብ ስትሞክር ይኼ የመጀመሪያዋ ነዉ። ስለዚህ፣ እንደኔ እንደኔ አሁኑኑ ወደ ሆስፒታል ተመልሳ መግባት ያለባት ይመስለኛል” አለች፣ እኔ ደግሞ እንድሞክራት
እያቀበለችን፡ “ለጊዜዉ ጉሉኮሱም ቢሆን ማግኘት አለባት” አታዩትም
አተነፋፈሷንስ? የባሰ ሲር ሲር እያለ እኮ ነዉ። ለመሆኑ የቀጣይ
ሕክምናዋን ጉዳይ አማክራ ችሁበታል ወይ?”

“ማንን፣ ይኼዉ አንቺ አለሽል አይደል? አንቺዉ ምከሪን እጂ” አለ ባልቻ፣ እኔም እንደዚሁ ልላት ስል ቀድሞኝ፡፡

ይኼ ሙያዬ አይደለም: ስለዚህ እኔ በቅጡ ከምፈተፍት፣ ጉዳዩን ይሁነኝ ብለዉ የተማሩት
ባለሙያዎች ስላሉ ወደ እነሱ መሄድ ይኖርብናል”

«የት ናቸዉ እነሱ ታዲያ?”

“ምን እሱማ ባላውቃቸውስ በአብዛኛዉ ሆስፒታሎች አይጠፉም ነበር:: ግን የመሣሪያዎች ዉስንነት አለ: ለጊዜዉ ሕክምናዉ በኹለት
ሆስፒታሎች ብቻ እንደሚገኝ ነዉ የማዉቀዉ”

“በስመ አብ!” አለ ባልቻ፡ “ወረፋዉ አያድርስ ነዉ በይኛ''

“በጣም!”

ከመንግሥት ሆስፒታሎች መካከል ይኼን ሕመም ጉዳዬ ብሎ በብቸኝነት ሕክምና ወደሚሰጠዉ ዘዉዲቱ ሆስፒታል ሄድን፡፡ አቤት ወረፋዉ! ያሉት
አልጋዎች ዉስን ናቸዉ፤ ተመዝግቦ ተራዉን የሚጠባበቀዉ ግን የትየለሌ! እንዲያዉም የኋላ ኋላ እንደ ሰማነዉ ከሆነስ፣ በኢትዮጵያ በየዓመቱ ብቻ ከሃያ ሺ የሚበልጡ ሕጻናት የቱናት ዓይነት እክል ያጋጥማቸዋል አሉ፡ ቁጥሩን አሰብሁት ስንት የሚወራላቸዉ
ወረርሽኞችም እኮ ከዚህ የከፉ አይደሉም

የቱናንት ሁኔታ አጣዳፊ መሆኑን ልናስረዳ ብንልም፣ የሚሰማን
አላገኘንም: አብዛኛዉ እዚህ የመጣዉ ሰዉ ሁሉ ቱናት ካለችበት የሚተናነስ አለመሆኑን አምነን ተቀበልን፡፡ ሆኖም ሕክምናዉን በተመለከተ እስከሚወሰንልን ድረስ፣ ባይሆን በረኀብ እንዳትሞትብን በሚል ግሉኮስ ተፈቅዶልን አንድ ጥግ ላይ ተተከለላት:: በረንዳ ላይ:
መኝታ ክፍልማ የሚታሰብም አይደለም፡

“በቃ እናንተ ሂዱ እጂ” አልኋቸዉ፣ ለግማሽ ሰዓት ያህል እንደዚሁ
እንደ ቆየን፡፡ እሳቱ የማይበርድ ችግር እየተጠባበቃቸዉ ሳለ፣ የሦስቱም እዚህ መቀመጥ ከቱናት ሕክምና ባልተናነሰ አሳስቦኛል ሸዊትም ፋታ የለሽ ሐኪም ናት፣ ባልቻም ባልቻ ነዉ፣ እሸቴም ያዉ ነዉ፡፡ “ሂዱ አረ! ሂዱ” አልሁኝ፣ እንደማግባባትም እንደማጣደፍም እያደረግሁ::
“መጨረሻዉን ሳንሰማ?” አለ ባልቻ፣ ስልክ ስልኩን ሲያይ እንዳልነበር ሁሉ፡
👍381👎1🔥1
#ገረገራ


#ክፍል_ሀያ_ሦስት


#በታደለ_አያሌው


...በእኩል ሰሞን ኹለት ተቃራኒ የሚመስሉ ጥቅሶች ሰማሁ አንደኛዉ:-

“ተስፋ የሚባል ተሟጦ ተሟጦ፣ ጭልጥ ብሎ አልቋል:
እንጥፍጣፊዉ እንኳን በማንም እጅ ላይ የለም፡ አሁን ማንም
ላይ መንጠልጠል አንችልም:: የራሳችንን ተስፋ ግን ራሳችን
እንዳንፈጥር የሚከለክለን የለም!” ሲለኝ

ሌላኛዉ ደግሞ፡-
“እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን
ያድሳሉ፧ እንደ ንሥር በክንፍ ይወጣሉ፡ ይሮጣሉ፣አይታክቱም: ይኼዳሉ፣ አይደክሙም” ይላል

ኹለቱም ስለ ተስፋ ናቸዉ፡፡ ለኹለቱም ምንጭ ተጠቅሶልኛል ኹለቱንም የነገሩኝ ሰዎች ለእኔ ከማሰብ እንደ ነገሩኝ አዉቃለሁ የመጀመሪያዉን በቅጡ የማዉቃቸዉ ዘመናዊ የሥነ ልቡና ባለሙያ፣ ኹለተኛዉን ደግሞ
በቅጡ የሚያዉቁኝ የንስሐ አባቴ ናቸዉ የነገሩኝ፡ የመጀመሪያዉ
እምነቱንም ሥራዉንም ያንቺ ጉዳይ ነዉ ሲሉኝ፤ ኹለተኛዉ ደግሞ ማመኑ ያንቺ፣ ሥራዉ ግን የእግዚአብሔር ነዉ ብለዉኛል፡

ሕይወት ደግሞ የምርጫ ወንበር ናት አሉ᎓ ታዲያ እኔ የቱን ልምረጥ?
የቱን ነዉ መምረጥ ያለብኝ?

እህቶቼ እና ወንድሞቼ እንደ ዋዛ ጀምረዉ፣ አንድ በአንድ ሸርተት እያሉ ጥለዉኝ ጥለዉኝ፣ አሁን አፉን ሞልቶ እህቴ ነሽ የሚለኝ ጠፍቷል።

እንዲያዉ ምናልባት ቆርጠዉ ያልቆረጡ ቢኖሩም እንኳን፣ ጨክነዉ እህታችን አይደለሽም አይሉኝ እንደሆነ እንጂ፣ እንደ ወትሮዉ ግን በእርግጠኝነት ‹እህታችን ነሽ አይሉኝም: እኔን ከመጥላታቸዉ የተነሳ
እህ ብላ የወለደቻቸዉን እመዋን ሳይቀር የዉብርስት እናት› እስከ ማለት ደርሰዋል የጃሪምስ እንዲያዉም አይወራም:

ይኼ ሁሉ ለሆነብኝ ለእኔ፣ ልጄ ባትኖርልኝ ኖሮ፣ ይኸኔ ሟች ነበርሁ። አፈር ገብቼ ነበር።

በስንት ዉጣ ዉረድ ቢሆንም፣ ልጄ ቱናት የመጀመሪያ ሕክምናዋን አግኝታልኛለች:: ጭንቅላቷ ላይ የሚመነጨዉ የዉሃ ክምችት እና ጥቅም
ላይ የሚዉለዉ ዉሃ
እንዲመጣጠን የሚያደርግ ቀዶ ሕክምና ተደርጎላታል በእርግጥ ሕክምናዉ እንኳንስ የእኔን የእናቷን አንጀት፣ ደመኛዬ ነሽ የሚለኝን ጃሪምን ሳይቀር አንሰፍስፋዋለች አሉ ያቺን ከደም የቀዘቀዘች እርጥብ ገላዋን ተቀዳ፣ ጀርባዋ ላይ ለነበረዉ የአጥንት ክፍተት
ጉዳቷ ሕክምና ተደርጎላታል፡ ይኼም አይብቃሽ ብሏት፣ ከላይ
ከጭንቅላቷ እና ዝቅ ብሎ ደግሞ ሆዷ ላይ ቀዳደዉ ነበር ማስተንፈሻ ቱቦዉን (shunt) የቀበሩላት።

አቤት መቻሏ!

እንደ'ኔ ፍራቻ ሳይሆን እንደ እሷ ብርቱነት፣ በትንሽ በትልቁ ሞተችብኝ እያልሁ ሥርበተበት ቱናት ናትና ልጅቷ፣ ሁሉንም ቻለችዉ፡ ችላ አሳለፈችዉ፡ እንደ ቱናት ቻይ አለ ወይ በምድር? እኔ አላዉቅም።

“አልሄድሽም እንዴ እመዋ?” አልሁ፣ ከልጄ ጋር ብቻ ዘግቼ
የተቀመጥሁበትን ክፍል በር ድንገት ያንኳኳችብኝ እመዋ መስላኝ ሌላ ሰዉ መሆኑን ያወቅሁት ድምፁን ስሰማ ነዉ፡፡

“ሰላም አደርሽ ዉብርስት?''

“እግዚአብሔር ይመስገን ማነዉ?” አልሁ፣ በሩን ለመክፈት
እያቅማማሁ አቅማምቼ አቅማምቼ ስከፍተዉ፣ አንድ ወጣት ከደጅ ቆሞ አገኘሁት ቁመናዉ ልጅ እግር ቢሆንም፣ አንተ ብሎ ማቅለሉ
አልመጣልኝም የእመዋን ቤት በረሃ፣ ልጄ ቱናትን ደግሞ ገዳም አድርጌ እሷ ዉስጥ ከመነንሁ ወዲህ፣ የመነኮሳቱ ባህል እና ሥርዓት እያደረብኝ መጥቷል፡ ማልዬለታለሁ አነጋገሬን፣ አመጋገቤን፣ ጸሎቴን፣ አጠቃላይ
ሥነ ሥርዓቴን እና ለዓለም ያለኝን ርቀት እንደ መነኮሳት ለማድረግ
ልምምድ ላይ ነኝ የማነባቸዉ መጻሕፍት ሁሉ የምንኩስናን ሕይወት የሚያወሱ እንዲሆኑ እመርጣለሁ፡ ከዚህ ሌላ፣ ማንኛዉም ወደ ዓለም የሚስብ ነገር ላይ ድርሽ ማለቱን ትቼዋለሁ፡ ፈታኙን የቱናትን የሕክምና
ጣጣ ጨርሼ እመዋ ቤት ባለኝ ክፍል ዉስጥ ጠቅልዬ ከገባሁ
ወዲህ የከተማዉን ግርግር አይቼዉ አላዉቅም፡ እንኳንስ በአካል በወሬም እንኳን፣ ስለ ከንቱዉ ዓለም የመስማት ፍላጎቴ ሞቷል፡ አላስችል ብሎኝ
ካስቀረኋት አንድ ክራሬ በቀር የቀድሞ ልብሶቼን፣ የቀድሞ ጌጣጌቶቼን የቀድሞ ሥራዬን ሁሉ እንዳለ እርግፍ አድርጌዋለሁ

“ምን ልርዳዎ የኔ ወንድም?” አልሁት፣ በደህና ትሕትና᎓

“ጋሽ ባልቻ ሊያናግሩሽ ይፈልጋሉ” አለኝ፣ ሞባይሉን ሊያቀብለኝ እጁን
ወደ'ኔ እየዘረጋ

“ባልቻ?”

“አዎ፤ መስመር ላይ ናቸዉ: እንኪ አናግሪያቸዉ” አለ፣ እንደገና የበለጠ ቀረብ ብሎኝ፡፡

“ሄ..ሎ” አልሁ፣ እያቅማማሁ ሞባይሉን ተቀብዬ ወደ ጆሮዬ አድርጌዉ፡

“ማንም አልቀደመኝም አይደል?” አለኝ ባልቻ፣ አብሮኝ ያደረ ይመስል ጨርሶ ሰላም እንኳን ሳይለኝ፡

“ምኑን?”

“እህ! ረስቼዋለሁ እንዳትዪኝ ብቻ”

“ምኑን?”

“አንቺ! ቀኑን ረስተሽዋል?”

“እህእ፣ የቱን ቀን?”

“የዛሬ ዓመት እኮ ነዉ ቱናት የተወለደችዉ። ልደቷ መሆኑ ረስተሽዉ ነዉ?”

ወይ መርሳት! እንኳንስ የተወለደችበትን ይቅርና፣ መቼ ሕክምና እንደ ገባች፣ መቼ እንደ ወጣች፣ ለመጀመሪያ ጊዜ መቼ ፈገግ እንዳለችልኝ፣ የትኛዉን ልብሷን መቼ እንዳስገዛሁላት ጭምር ከነዕለቱ እና ከነሰዓቱ
ልረሳዉ አልችልም: ያም ቢሆን ግን የልደት ቀኗ ላይ ትንሽ ተወዛግቤ ነበር፡ ያለ ቀኗ ከሆዴ የተወለደችበትን ዕለት ነዉ ልደቷ ብዬ የማከብርላት ወይስ ከዚያ በኋላ ለኹለት ወራት ያህል ቆይታ ከማቆያ ክፍል ወጥታ እቅፌ ዉስጥ የገባችበትን ዕለት የሚለዉ ግራ አጋብቶኝ
ነበር ባልቻ የሚለዉን ከወሰድሁ ግን፣ እዉነትም የቱናት ልደት ዛሬ
ዛሬ ከሆዴ ከወጣች አንድ ሙሉ ዓመት የደፈነችበት ዕለት ነዉ።

“ረስተሽዋል አይደል?”

“ኧረ በጭራሽ!”

“እኮ ይዘሻት ነያ”

“የት?”

“አጠገብሽ ያለዉ ልጅ መኪና ይዟል: እሸቴ ነበር ሊመጣልሽ የነበረዉ: ግን አንድ ድንገተኛ ተልእኮ ተሰጠዉ እና መምጣት አልቻለም አንቺ እስከምትደርሺ ግን እሱም ሥራዉን ይጨርሳል። ስለዚህ ቱናት ቆንጆ አድርገሽ አልብሻትና ይዘሻት ቶሎ ነይ”

“እህእ፤ መቀለድህ ነዉ እንዴ? ከመቼ ወዲህ ነዉ እንኳንስ ገዳሜ
ቱናትን ይዤ ይቅርና ለራሴስ ብሆን ከዚህ ወጥቼ የማዉቀዉ?”

“ይልቅ እንዳትቆዩ” ብሎ፣ ስልኩን ጆሮዬ ላይ ጠረቀመዉ፡ እንደ
ወትሮዉ ቢሆን እንኳንስ እያወራሁለት ሊዘጋብኝ ይቅርና፣ ቻዉ ተባብለን እንኳን ለመዝጋት እጁ እሺ አይለዉም: የአሁኑ ግን በእሱ የማላዉቀዉ እንግዳ ዐመል ሆነብኝ፡ ተዋክቦ ነዉ እንዳልል፣ ምንም የቸኮለ አይመስልም: መቼም ጊዜ ባይኖረዉ ኖሮ የቱናትን ልደት ካላከበርን
አይለኝም።

ከተቀየመም ይቀየመኝ እንጂ ቱናትን የትም ወስጄ አላንገላታትም ብዬ
ወሰንሁና ሞባይሉን ለሰጠኝ ልጅ ልመልስለት ዞር ስል አጣሁት ባልቻን
አናግሬ ስጨርስ እንደምከተለዉ እርግጠኛ በመሆን ከግቢ ዉጪ ወደ
መኪናዉ ተመልሷል፡ እየጠበቀኝ ስዘገይበት ጊዜ፣ ያቺን የሲራክ ፯ ኮድ
የሆነችዋን የመኪና ጥሩንባ አሰማኝ፡ ቢያንስ ሞባይሉን መመለስ
ስላለብኝ፣ ልጄ ለቅጽበት ብታጣኝ የማጣት መስሎኝ እንደ ፈራሁላት
ወደ መኪናዉ ሮጥሁ።

“ይቅርታ ወንድሜ፣ ባልቻ ዝም ብሎ ነዉ እዚህ ድረስ ያደከመዎ” አልሁት፣ በመነኩሴ የትሕትና ልምምዴ፡

ቱናት ገዳምሽ ናት ብለዉኝ የለ የንስሐ አባቴ? ታዲያ ገዳምን ወዳለበት
ሄደዉ ይሳለሙታል እንጂ፣ ራሱ ገዳም ተነቅሎ ካልመጣልኝ ይባላል እንዴ? በጭራሽ! ያዉም የገዳምን ክብር ከሚያዉቀዉ ከባልቻ ይኼ
ይጠበቃል? አዝናለሁ፣ ያለ ተፈጥሮዋ ወደ ጩኸት አዉጥቼ ገዳም አላስረብሻትም: አልሄድም፡ በእሷ የሚያድረዉን አምላክ ማመስገን የፈለገ ቢኖር እየመጣ ይሳለማት እንጂ፣ ገዳሜን ለመንቀል በጭራሽ አላደርገዉም

አልሞክረውም
👍29
#ገረገራ


#ክፍል_ሀያ_አራት


#በታደለ_አያሌው

“እንደምን አረፈድሽ የኔ እህት?” አለችኝ አንዲት ደርባባ ሴት፣ እንጀ አጋጣሚ በመንገዱ እያለፈች ሳለ እንደ ዋዛ መለስ ብላ እጅ ነስታኝ።

“እግ..እግዚአብሔር ይመስገ” አልሁኝ፣ እንደ መደናገር ብዬ፡ መልኳ እንግዳ አልሆነብኝም:

“ምነዉ በደህናሽ ነዉ፤ ልጅ ይዘሽ በመንገድ ዳር?”

“ደህና ነኝ” አለሁኝ፣ የሴትዮዋን መልክ አስታዋሽ ልቤ ላይ ብቅ ብሎ
ጥልቅ እያለብኝ፡፡ የት እንደማዉቃት ልጠይቅ አልጠይቅ ብዬ ከራሴ ጋር
ትንሽ ተከራከርሁ፡

“ቱናትስ እንዴት ናት?”

ይኸዋ! እሷ ጭራሽ ከእኔም አልፋ ከማንም ሸሽጌ የማኖራትን ገዳሜን
ሳይቀር ታዉቃለች፡ ኧረ ይቺ ሰዉ ማናት?

“አጠፋሽኝ መሰል”

“አይ ማጥፋት ሳይሆ” አልሁ፣ እሷ በዚህ መጠን አዉቃኝ እኔ አላወቅሁሽም ማለቱ ቢያሳፍረኝ፡

“ምነዉ እንኳን” አለችኝ፣ ጭንቀቴ ገብቷት ልትገላግለኝ፡ “ምነዉ
እንኳን ዘዉዲቱ ሆስፒታል ተዋዉቀን ?”

"አዎ!” አልሁ፣ ነፍሴን እያሳረፍኋት። “እዚያ ነዉ አይደል
የምንተዋወቀዉ ?»

መጣችልኝ፡ የቱናትን ሕክምና ለመጀመር ወደ ዘዉዲቱ ሆስፒታል የገባን ዕለት ማታዉን የተዋወቅናት ሴት ናት ከዳር ሀገር መጥታ፣ እዚያ ዘግናኝ ወለል ላይ ወረፋ ጥበቃ ወር ሙሉ ሕመምተኛ ልጇን ይዛ
መቀመጧን ነግራን እንደ ነበር ሁሉ አስታወስሁ፡ አስታወስኋት
የቀድሞዉ ባሌ መተት አስመትቶብኝ፣ ልጄ እንዲህ ሆኖብኝ ቀረ› ብላ ለእመዋ የነገረቻት ሴትዮ ናት።

እዴት ሆነልዎ ... ማነዉ ... እንዴት ሆነለሽ ልጅሽ?” አልኋት አንቱ
ማለት እና አንቺ በማለት መካከል እየዋለልሁ: አሁን አሁን
ምቸገርባቸዉ ነገሮች አንደኛዉ ይኼ ነዉ፡ በምለማመደዉ የምንኩስና ሕይወት ማንኛዉንም ሰዉ አንቱ ብዬ ማክበር እፈልጋለሁ ግን ደግሞ ቀደም ብዬ አንተ ወይ አንቺ እያልሁ የማዉቃቸዉ ሰዎች ግራ
እንዳይጋቡብኝም እሰጋለሁ።

“መቼም ወረፋዉ ደርሶሽ ይሆናል። ዳነልሽ፤ እንዴት ሆነ ልጅሽ?”
“ወረፋዉስ ደርሶኝ ነበር” አለች፣ በቅጽበት አንገቷን እየሰበረች ክፉ ነገር እንዳትነግረኝ እግዚአብሔርን በልቤ ለመንሁት፡ ልጇ እንደዳነላት ብቻ ነዉ መስማት የምፈልገዉ፡
“አልሆነም” አለችኝ፡፡

“እ?”

“አልዳነልኝም ወረፋዉ ደርሶት እንደ ነገ ተቀጥሮልኝ፣ እንደ ዛሬ
ማታዉን እቅፌ ላይ አረፈብኝ” አለችኝ፣ እንባዋን በሺህ መንታ
እያወረደች፡ የእኔም እንባ መቆሚያ አጣ፡ የልጁ ሁኔታ አሁንም ዓይኔ ላይ አለ፡ ምንም እንኳን ልጇን ገጥሞት የነበረዉ ከቱናት ቀለል ባለ ሁኔታ፣ ያልተመጣጠነ የጭንቅላት የዉሃ መጠን (hydrocephalus) ብቻ
ቢሆንም፣ ሁኔታዉ ግን አንጀት ይበላ ነበር፡፡ እሷም ይድንልኛል ብላ ያን ሁሉ መከራ አይታ በመቀርቷ አንጀቴን በላችዉ፡
“አልቅሼ ያልሞትሁትም አንዲት
ማጽናናት የሚያዉቁበት እናት
አባብለዉኝ ነዉ። አሁን እኮ እንዲያዉም እሳቸዉ ጸበል ጸዲቅ
ካልቀመስሽ ብለዉኝ ነዉ የልጄን ሬሳ ይዤ የወጣሁበትን ከተማ
ከመንፈቅ በኋላ ዳግመኛ የተመለስሁበት ያ ጊዜ እሳቸዉ ባይራዱኝ ኖሮ እኮ የልጄን ሬሳ እንኳን ጭኜ ወደ ሀገሬ መዉሰድ ባልቻልሁ ነበር።ዉለታቸዉ አለብኝ። በምን እከፍላቸዉ ይሆን ብለሽ?”

“እግዚአብሔር ዉለታ አዋቂ ነዉ። ግድየለም፣ እሱ በነፍስ ይክስልሻል”አልኋት፣ የተባሉት ሴትዮ ደግነት እያስቀናኝ፡

“ልመልስስ ብል በምን አቅሜ እቴ! እንዲያዉ የማትቸኩይ ከሆነ
እንዲያዉ ባስቸግርሽ፤ አብረን ሄደን ብናመሰግናቸዉ”

“አይ” አልሁ፣ እሺም እምቢ ማለትም እየከበደኝ፡

“እዚያች ዘንድ፣ ያዉና እኮ ቤታቸዉ: ያ በሰፊ ቆርቆሮ የታጠረዉው ግቢ ነዉ ቤታቸዉ መሆኑን ሰዎች የጠቆሙኝ። ነይ እንሂድ እስኪ እባክሽ”።

የእኔ አስፈላጊነት ባይገባኝም፣ እምቢ ማለት ግን አልቻልሁም፡ እሺ ብዬ ባለ ተሽከርካሪዉን የቱናትን አልጋ እያሽከረከርሁ ተከተልኋት። እሷም ጮራዋ የቱናት ዓይኖች ላይ መፈንጠቋን አይታ አላስቻላትም የራሷን ነጠላ ቀልጠፍ ብላ አውልቃ፣ ራስጌዋ ላይ አጠላችላት።

በነበርንበት የመንገዱ ጠርዝ ትንሽ ተራምደን መንገዱን አቋረጥነዉ።
ከዚያ በማቋረጫዉ ፊት ለፊት ባለዉ ቅያስ ትንሽ እንደ ሄድን በቆርቆሮዉ አጥር የታጠረዉን ግቢ በር አገኘነዉ: ቅድም ቆመንበት ከነበረዉ መንገድ
ዳር ሆኖ የታየዉ አጥር እዚህ ድረስ መስፋቱን አይቼ፣ ‹ምን ዓይነት ሴትዮ ቢሆኑ ነዉ? መቼም ሀብታም መሆን አለባቸዉ ልላት ወደ እሷ ስዞር ፊቷን በሳቅ ሞልታ ጠበቀችኝ፡

“ዝግጁ?” አለችኝ፣ በደስታ እየተፍለቀለቀች

“እኮ ሴትዮዋን ለማመስገን?” አልኋት፣ ድንገት ስለ ተሞላችዉ
የደስታዋ ምንጭ ምክንያት እየፈለግሁለት።

“እ" እንደዚያ ነዉ አዎ ግን ምንም ቢገጥምሽ እንዳትደነግጪ። ዝግጁ ነሽ አይደል ለዚያ?”

“ይቅርታ…”

“ይቅርታ አድርጊልኝ ዉብርስት: ትንሽ ዋሽቼሻለሁ: ዉለታ የዋሉልኝ
ሴትዮ የአንቺ እናት፣ እመዋ ናቸዉ። ይኼ በር ሲከፈትም የምናገኘዉ እመዋን እና የእሳቸዉ ዓይነት ዉለታ ዋዮችን ነዉ በእርግጥ ሌላ ያልጠበቅሽዉ ሰዉም ልታይ ትችያለሽ። ምንም ቢሆን ግን እንዳትደነግጪ” አለችኝ፣ እንደ ማቀፍ ጭምር እያደረገችኝ።

ተለዋዋጭ ሁኔታዋን ሳይ ትክክል አልመሰለችኝም፡ እንደዚያም ሆኖ ግን የሚጎዳ ነገር ዉስጥ እንደማትከተኝ በነፍሴ አምኛታለሁ ለምን እንደሆነ እንጃ ከቅድሙ ሹፌር ይልቅ እሷን በሙሉ ልቤ ነበረ ያመንኋት የልጄን ተሽከርካሪ አልጋ የሚገፉ እጆቼን ጠበቅ አድርጌ ይዤ፣ የሚሆነዉን ሁሉ
ለማየት ዓይኔን በሩ ላይ ተከልሁ። እኔን ያቀፈችበትም ሆነ በሩን
ለመክፈት የሚገፋዉ እጇ ይንቀጠቀጣል፡ ቀስ አድርጋ ከርፈድ አደረገችልኝ፡ አንድ የጠመጠሙ ቄስ ቀድመዉ ዓይኔ ዉስጥ ገቡ።

አሁንም ቀስ አድርጋ መግፋቷን ጨመር ስታደርግልኝ፣ ወዲያ ወዲህ የሚሉ የሰንበት ተማሪዎችን መለዮ የለበሱ ወጣቶች አየሁ ክፍተቱን
ሰፋ ባደረገችዉ ቁጥር፣ ዓይኔ ዉስጥ የሚገባዉም ሰዉ እየጨመረ እየጨመረ መጥቶ ጨርሳ ሙሉ በሙሉ ወለል አድርጋ ስትከፍተዉ፤አንድ ትልቅ ጉባዔ የሚሞላ ብዙ ሰዉ በግቢዉ ተጥለቅልቋል፡ በተለይም በአንደኛዉ ማዕዘን በኩል በድንኳን ዉስጥ ሰብሰብ ብሎ ወደ እኛ የሚመለከተዉን ሕዝብ ተመለከትሁት ነገሩ፣ ትክክለኛ ጉባዔ ነዉ።

“እንዴት እንዴት ነዉ ነገሩ?” አልኋት ወደ ሰዎቹ እንድንሄድ
የመጎተት ያህል ስትመራኝ። “ጭራሽ እመዋም አለችበት? ባልቻም፣ እሸቴም? ኧረ ምንድነዉ ጉዱ?” አልሁኝ፣ በቀረብን ቁጥር እንደ አዲስ እያላበኝ፡ ዓይኔን ከጫፍ እስከ ጫፍ አንከራተትሁት የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊን ጨምሮ፣ ሦስት ጳጳሳት ከጉባያተኛዉ የፊተኛዉ ረድፍ ላይ
ይታዩኛል፡ የጤና ሚኒስትሯን ጨምሮ አንዳንድ የማዉቃቸዉ
የመንግሥት ባለስልጣናትም መኖራቸዉን አስተዋልሁ: በርከት ያሉ ካህናት፣ የማኅበራችን ዋና ሊቀመንበር፣ ባልቻ፣ እሽቴ፣ እመዋ
ሌሎች የማኅበራችንም ሆነ የሲራክ ፯ አባላት ሁሉ አሉበት።

“እንኳን በደህና መጣችሁ” ሲሉ ተቀበሉን፣ ሁሉም: ያልቆመ
የማያጨበጭብ አለ ይሆን?

“ክቡራንና ክቡራት እንግዶቻችን፣ የጉባዔያችን መነሻ ምክንያቶቻችንም ተሟልተዉ ተገኝተዉልናል እንደ ቆማችሁ ማርያም ትቁምላችሁ እባካችሁ በየመቀመጫችሁ አረፍ አረፍ በሉልን” አለ የመርሐ ግብር
👍463
#ገረገራ


#ክፍል_ሀያ_አምስት


#በታደለ_አያሌው

...የጃሪም አወጣጥ በኃይል እየቆረቆረኝ ቢሆንም፣ ደስታዬ ግን ጢም እንዳለ ነዉ።

የመሠረት ድንጋዩ በጳጳሳቱ እና ሌሎች ታላላቅ ስዎች ተቀምጦ ከአበቃና የጉባዔዉ አጋፋሪ ‹ሂዱ በሰላም› ካለን ከብዙ ደቂቃዎች በኋላም ቢሆን፣ ችዬ መነሳት አልቻልሁም ነበር፡ ልጄ ቱናት የተኛችበትን አልጋ ወደ
ተቀመጠዉ የመሠረት ድንጋይ አስጠግቼ፣ በደስታ እንባዬን ሳወርድ ብዙ ቆየሁ፡ ሁኔታዬን ሁሉ እመዋ በሩቁ ስትመለከት ኖሯል መሰለኝ፣ ከእንግዳዉ ጋር መዉጣቷን ትታ ወደ'ኔ መጣች፡

“ደስ እለሽ ዉብዬዋ?” አለችኝ፣ ወደ እቅፏ እየሳበችኝ፡፡

“በጣም!” አልኋት፣ እንባዬን በቀሚሷ እያበስሁ

“እሰይ! እንኳ ንም ደስ አለሽ ልጄ”

“እንደ ዛሬዉም ደስ ብሎኝ አያዉቅ”

“እኔም” አለችኝ፣ ወደ አንገቷ ሥር ጠበቅ አድርጋ እየሳበችኝ ቀና ብዬ
ሳያት፣ እዉነትም ተጫጭኗት የነበረዉን እርጅና ሳይቀር ድል ነስታዉ ታየችኝ: ግንባሯ ላይ በተደረደሩ መስመሮች ሁሉ ደስታ ሲፈስ አየሁ በጣም ደስ ብሏታል። ይኼ ደስታዋ የኔንም ደስታ የትና የት አደረሰዉ።

“የቱናት እናት” አለ ባልቻ፣ እንግዳዉ ቀለል እስከሚልለት ድረስ ሲሸኝ ቆይቶ ወደ እኛ እየመጣ፡ የእሱም ፊት ከእኛ በሚስተካከል ደስታ ተጥለቅልቋል ቱናትን ከነአልጋዋ አቅፎ አነሳትና የመሠረት ድንጋዩ አናት ላይ ጉብ አደረጋት: “ይኼን ወደ መሰለ ሥፍራ ስጠራት እንዲያ
እንዳልተግደረደረች፣ ደስታ እንዴት እንደሚያደርጋት አየሽልኝ አይደል
ይቺን እናትሽ?” አላት፣ ቱናትን በስስት እየተመለከታት

የመሠረት ድንጋዩ ላይ ከነአልጋዋ ያደረግናትን ቱናትን ለረዥም ጊዜ
ከብበን ከቆየንና፣ ለዚሁ ደስታችንም ወሰን ልናበጅለት ከሞከርን በኋላ እኔና ባልቻ ቱናት የተኛችበትን አልጋ ከግራ እና ከቀኝ ይዘን ወደ ባልቻ
መኪና ተሳፈርን

“በሉ እንግዲህ” አለችን እመዋ፣ ከሀገር ርቀን የምንጓዝ ይመስል አቅፋ እየተሰናበተችን፡

“አብረሽን አትሄጅም ወይ እመዋ? ዉቤ እኮ ወደ ሲራክ እየተመለሰች
ያለችዉ ከዓመት በኋላ ነዉ። መቼም በዚህ አንድ ዓመት ዉስጥ
በማዕከላችን የተለዋወጠዉ ነገር ሁሉ እያየች እንደ ጀማሪ ጎብኚ
ይኼ ደግሞ ምንድነዉ እያለች በጥያቄ ማስቸገሯ አይቀርም: ብቻዬን እችላታለሁ ብለሽ ነዉ?” አለ ዓይኖቹን በእኔ፣ በእመዋ እና በቱናት ላይ እያንከባለለ፡፡

“ወደ ሲራክ ነዉ እንዴ የምንሄደዉ?”

“አዎ ምነዉ?” አሉኝ እኩል፣ ድንግጥ ብለዉ፡ ደግሞ ልትለመንብን ነዉ› ብለዉ ነዉ መሰለኝ፣ በቅጽበት አመዳቸዉ ቡንን አለ

“እሺ”

“እኮ! እንዳንቺም በሕጋችን የቀለደበት ሰዉ የለም: እንዲያዉ የቱናት እናት መሆንሽ አተረፈሽ እጂ፣ አንቺስ ደህና አድር ገዉ ቢቀጡሽ ሁሉ የምታጸድቂ ወንጀለኛ ነሽ” አለኝ፣ እንደ መሳቅም በእፎይታ እንደ
መተንፈስም ብሎ፡

“ታዲያ እኔ እምቢ ብዬ ነወይ? ልብ ካላችሁ መቅጣት ነበራ” አልሁት፣ የቱናትን ልብስ እያስተካከልሁ

“ይቀርልሽ መስሎሻል!”

“ቆይ ምን አጥፍቼ ነዉ ግን?”
ያልሰማኝ መስሎ ፊቱን አዞረብኝና፣ እመዋን እንደገና ተሰናበታት፡ እኔም እንደ'ሱ የመኪናዉን መስታዎት ዝቅ አድርጌ ልሰናበታት ስል፣ ሆነ ብሎ
መኪናዉን አንቀሳቀሰብኝ፡፡

“ አየሽልኝ አይደል ምቀኝነቱን እመዋ?” አልኋት፣ ልክ እንደ በባቡር ተጓዥ እጄን እያዉለበለብሁላት፡

እሷን ተለይተን መንገድ ከጀመርን በኋላ፣ ቅድም ያልሰማ መስሎ
ያለፈብኝን ጥያቄዬን እንደገና አነሳሁበት

“እ፣ በል ገረኛ”

“ምኑን?”

“ብቀጣበት የምትጸድቁበትን ጥፋቴን ነዋ”

ፍርጥም ብሎ ጥርሶቹን ገለጠልኝ፡

“እዉነት ጥፋትሽ ጠፍቶሽ ነዉ አንቺ? ሌላዉ ቢቀር፣ አንዲት የሲራክ አባል ብትወልድም እንኳን ፈቃዷ ምን ያህል እንደሆነ አጥተሽዉ ነዉ?”

“ወይ ጉድ… እኔስ አሁንም ወደ ሲራክ እየሄድሁ መሆኑ ደንቆኛል”

ቱናትን ከወለድሁ፣ በተለይም ኋላ በሕክምናዎቿ ጊዜ ያለፈችበትን አበሳ ካየሁ በኋላ፣ ወደ ሲራክ ፯ እመለሳለሁ አላልሁም ነበር፡ እንኳንስ እስከዚህ ድረስ፣ ገዳሜን ከገደምሁበት የእመዋ ቤት አንድም ርምጃ ንቅንቅ የምል አይመስለኝም ነበር፡ ዛሬ ግን ባልቻ ገና ‹እንሂድ› ሲለኝ፣
‹እሺ› ብዬ ከመከተል በቀር ምንም ያሳሰብኝ ነገር የለም፡

በዚህ ሁኔታ ከዋናዉ የማኅበራችን ሕንጻ ደርሰን፣ ጥብቁን እና ረዥሙን የሲራክ ፯ መንገድም አልፈን ከመጨረሻዉ በራፍ አጠገብ ስንደርስ ድንገት ቆመ፡፡ ጭራሽ እንደ መቅለስለስ ብሎ አየኝ፡፡ ይኼ አስተያየቱ
ነበር ቀድሞዉንም እኔን እና እሱን በሌላ ያስጠረጥረን የነበረዉ፡፡ ግራ ገብቶኝ አየሁት፡ በሩ ደግሞ ሲጠም፣ እኛ መሆናችንን አዉቆ በራሱ ጊዜ እንደ ቀድሞዉ ይከፈትልናል ብዬ ብጠባበቀዉም፣ ክርችም እንዳለ ቀረ፡

ምነዉ” አልሁት፣ ዓይን ቢያበዛብኝ፡ “ኧረ አባትዮ፣ እንዴት እንዴት እየሆንህ እንደሆነ ታዉቆሃል ግ?”

“እንዴት እንዴት ሆንሁ?”

“ለራስህ አይታወቀህም?''
መቅለስለሱን ተከትሎ፣ በዚያዉ ሐሳብ ገባዉና፣ ቁዝም ብሎ ቆየብኝ፡

“ምንድነዉ ጉዱ፣ የማትነግረኝ?”
“እንዳትቆጪኝ ፈራሁ እንጂ”

“እንዳትቆጪኝ?”ፈራሁ

“ለእሷ የምትሆኚዉን ሳይ፣ ትንሽ ፈራሁ”

“ማናት ደሞ እሷ?”

ልጅሽ፣ ቱናት” አለኝ፣ የቱናትን አልጋ የያዘ እጄን እያስለቀቀብኝ፡ እሱዐበአንደኛዉ ጎን፣ እኔ ደግሞ በሌላኛዉ ጎን ሆነን ነበር በየእጃችን የያዝናት አሁን ግን የመፈልቀቅ ያህል እጄን አስለቅቆ ለብቻዉ ወደ እቅፉ ወሰዳት አድራጎቱ ሊገባኝ ባይችልም፣ ባልቻ ነዉና ሰዉየዉ ልጄን አትንካብኝ ብዬ ልከላከለዉ አልቻልሁም፡ ትንፋሼን ዉጬ
መጨረሻዉን ጠበቅሁት፡፡ በእርግጥ፣ ደግሞ ሌላ የምሥራች
የተዘጋጀልኝም መስሎኝ ራሴን ለደስታ እያመቻቸሁ ነበር የለመደች ጦጣ አሉ!

“በቃ ዉቤ፤ በቃ ቱናትን ወስጄብሻለሁ” አለ፣ ስለ ራሱ ንግግር ራሱ ሐፍረት እየተሰማዉ፡፡

"እ" አልሁት፣ በግንባሬ፡ ብቻ ያንን የመሰለ ደስታ እንዳይከስምብኝ፡
ዓይኔን በልጥጬ በግርታ አየሁት፡

“አዎ”

“ኧረ አባትዮዉ ተዉ አታስቀኝ” ብዬ፣ እንደ ምንም ጥርሴን ለመግለጥ ሞከርሁ: ሳቄን የሚጋራኝ መስሎኝ ሳቅ ብርቃቸዉ የሆኑት ጥርሶቹ እስኪገለጡ ብጠብቅም፣ እሱ ግን ክርችም እንዳለ ነዉ አሁንም:

“እየቀለድህብኝማ አይደለም: ነዉ እንዴ?”

“በፍጹም! ከእሽቴ ጋርም ተመካክረበታል: ለማኅበራች
ሊቀመንበርም አወያይቼዋለሁ:: ያዉ እመዋንም ቢሆን ጫፍ ጫፏ
አጫዉቻታለሁ: ሁላችንም ጋ ያለዉ ሐሳብ ተመሳሳይ ነዉ''

“ቆይ ቆይ”

“ተዪ ዉቤ: በቃሽ: እዲያዉም ግልጹን ንገረኝ ካልሽኝ፣ ቱናት በዚህ መልኩ የምትጠቅሚያት አይመስለኝም” አለ፣ ቆምጨጭ ብሎ፡ ጭጭ ብዬ ከማዳመጥ በቀር የምሆነዉን እንጃልኝ፡፡

“ስለዚህ ቱናት እየወሰድሁብሽ ነዉ። ከእንግዲህ ቱናትን ለብቻሽ ቤት ዘግተሽባት የብቻሽ ማድረግሽ ይቀርና፣ የሁላችንም ልጅ አድር ገንእናሳድጋታለን። አንቺም ቱናት የምታገኛት እንደ ማናችም አልፎ አልፎ እና ከሥራ ዉጪ ይሆናል ማለት ነዉ። በማኅበራችን የሕጻናት መዋያ ዉስጥ እናስገባት እና እንደ ማንኛዉም ልጅ ጨዋታ እና ግበረ ሕጻናት እየፈጸመች ታድጋለች”

“እንደ ማንኛዉም ልጅ?”
👍27
#ገረገራ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#በታደለ_አያሌው


“እንዴት? ተለዉጫለሁ ማለት ነዉ በቃ?” እያልሁ፣ ከራሴ ጋር
ስተዛዘብ ቆየሁ።

እንዲያዉ ራሴንም ጭምር ስዋሸዉ የናፈቀኝ የለም አልሁ እንጂ፣ እንዴት ነዉ የማይኖረዉ? የጎዳናዉን ሰዉ ሁሉ የልቤ ሰዉ ማድረግ ይሆንልኝ የነበርሁት እኔ ዉብርስት፣የእናቴን ልጆች ከልቤ ችዬ ላስወጣ? አይሆንም፡ የናፈቀኝ የለም ያለ አፌን ይዤ እንኳንስ በባልቻ ፊት፣ በራሴ ኅሊናም ሚዛን ላይ ለመቆም ተሸማቀቅሁ።

አፈርሁ።

“ወዴት ነዉ ታዲያ?” አለኝ ባልቻ፣ ቱናት ያለችበትን አልጋ እየሳብሁ
ወደ መዉጫዉ ስራመድ አይቶኝ፡

“ወደ በረሃ”

“ወዴት?”

“ገዳሜን ወደ ገደምሁበት ወደ በረሃዬ። ወደ እመዋ ቤት!”

“ቅድም ምን ተባብለ'? ተይ እንጂ በማርያም: ይልቅ ቱናትን ይዘሽ
የማኅበራችን መዋእለ ሕጻናት እየጎበኛችሁት፣ ቅድም ያልሁሽን
አታስቢበትም?”

“እኔ የፈለገዉን ያህል ባስበዉ፣ የሚሆን የሚሆን መስሎ አልታኝም”

“ግድ የለሽም፣ እስከማታ ጊዜ አለሽ: ደጋግመሽ አስቢበት”

“እስኪ ይሁን። እሺ። መኪናህን አታዉሰኝም ታዲያ? ለማሰቡም ቢሆን እኮ የከረምሁባት በረሃዬ ትሻለኛለች: ወደ እመዋ ቤት መሄድ አለብኝ ትክ ብሎ ሲያየኝ ቆየና አንገቱን በይሁንታ ነቅንቆ፣ ቀድሞኝ ወደ በሩ አመራ፡ ዝም ብዬ ኖሯል እንጂ ቀደም ቀደም ያልሁት፣ ቀድሞ የነበሩኝ
የትለፍ ፈቃዶች ሁሉ መልሰዉ ካልታደሱልኝ በቀር ያለ'ሱ ወደ ሲራክ ፯ መግባትም ሆነ ከማዕከሉ መውጣት
አልችልም:: ስለሆነም
ጠመዝማዛዉን እና ባለ ብዙ በሩን ሲራክ ፯ አሳልፎኝ መኪናዉ
እስከቆመበት ድረስ ቱናትን ከነአልጋዋ አቅፎ አደረሰልኝ፡፡
“በይ እንግዲህ። ማታ፣ ልክ አንድ ሰዓት ሲሆን እደዉልልሻለሁ” አለኝ፣ የጠየቅሁትን የመኪናዉን ቁልፍና ያልጠየቅሁትን አንድ የእጅ ስልክ ጭምር አዉጥቶ እያቀበለኝ፡፡ እሺም፣ እምቢም፣ ቻዉም ሳልለዉ፣ ቱናትን ጭኜ የመኪናዉን ሞተር አስነሳሁ፡ እንደ ድሮዉ በችኮላ ሳይሆን፣ የመኪና መሪ ከነካሁ ቢያንስ መንፈቅ እንዳለፈኝ እና ከአጠገቤ
የጫንኋትም ሰዉ ገዳሜ ቱናት መሆኗን በማሰብ ወደ እመዋ ቤት
የሚወስደኝን ጎዳና በዝግታ አሽከረከርሁበት እንደ ደረስሁ፣ የግቢዉን በር ራሴዉ ለመክፈት ቀልጠፍ ብዬ ወረድሁ።
ስሞክረዉ ግን አልከፈትልሽ አለኝ፡፡ ለወትሮዉ ማናችንም የቤተሰቡ አባላት አድርሶን በመጣን ጊዜ እንዳንቸገር በሚል፣ ግቢያችን ተቆልፎብን
አያዉቅም: እንዲሁ በዉስጥ በኩል ይሸነጎርና፣ መሸንጎሪያዋን
የምንስብባት ደግሞ እኛ ብቻ የምናዉቃት አልባሌ ገመድ አለችልን፡አሁን ግን ይቺ ገመድ በሩን ልትከፍትልኝ አልቻለችም፡፡ እንዲያዉም እጄ ላይ ስለቀለለችብኝ፣ ሳብ ሳደርጋት ጭራሽ ምዝዝ ብላ ወጣች ገመዷ
ተበጥሳለች::

ቆይ፣ ገመዳችንን የበጠሰብን ማነዉ? ምንድነዉ?

“ኤጭ!” አልሁኝ፣ ንድድ ብሎኝ፡ በዚያ ላይ ልጄ ቱናት ምግብ
ከቀመሰች ቆይታለች፡፡ እንዲያዉም ለመንገድ ብዬ ይዤላት የነበረዉ
ምግብ ስለ ቀዘቀዘባት፣ እዚህ ደርሼ ትኩስ ምግብ እስከማጎርሳት ነበር
ችኮላዬ::
“ቆይ፤ ገመዳችንን ማነዉ የበጠሰብን?” አልሁኝ፣ እጄ ላይ ያለዉን የገመድ ቁራጭ ጨብጬ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ግራ ቢገባኝ፡

“እኔ” አለኝ፣ ከዉስጥ በኩል።

“አሃ፣አላችሁ እንዴ? በሉ ክፈቱልኝ' አልሁኝ በደፈናዉ፣ ማን
እንዳናገረኝ ስላላወቅሁት

“ምን ልትሆኚ?” አለኝ አሁን በድምፁ ለየሁት፡ ጃሪም ነዉ፡

“ክፈትልኝ”

“እንዳታስቢዉ!”

“ኧረ ባክህ አትቀልድብኝ። ለራሴ ልጄን ርቦብኛል። በል ክፈተዉ ይልቅ”

“አይ እግዲህ! በቋንቋሽ መሰለኝ ያናገርሁሽ!''

“ምን መሆንህ ነዉ፣ ክፈትልኝ እኮ ነዉ የምልህ”

“ሴትዮ! ምናለበት ባትፈታተኚኝ? ነገርሁሽ፤ ከዛሬ በኋላ እዚህ ግቢ ላይሽ አልፈልግም”

“እኔ ተናግሪያለሁ ጃሪም! ክፈተዉ ልጄን ርቧታል። አላበዛኸዉም እንዴ ?
ብለህ ብለህ ደግሞ ወደ እናቴ ቤት እንዳልገባ ልትከለክለኝም ያምርሃል ጭራሽ?” እልህ እየመጣ ጉሮሮዬን ተናነቀኝ፡፡

“ዉነት የእናትሽ ቤት እንግዲያዉስ እርምሽን አዉጪ። ሰማይ ዝቅ
ቢል ይቺን ግቢ ደግመሽ አትረግጫትም: በጭራሽ! ለአንቺም ሆነ ለእናትሽ፣ በቂ ጊዜ ሰጥቻችሁ ነበር: የማያልቅ መስሏችሁ ስትቀልዱበት
ያለቀባችሁ እንደሆነ፣ እኔ ጃሪም ምን እዳዬ? ከዚህ በቀር ምን
ላድርጋችሁ? የራሳችሁ ችግር ነዉ፣ ሥራችሁ ያዉጣችሁ: ከደጄ ግን ፈቀቅ! ያቺ ቆዳ እናትሽ መቼም ልብ የላትም፣ ያልኋትን ረስታ ድርሽ እንዳትልብኝ ብቻ!"
ይኼን ሁሉ ስንባባል፣ ጎረቤት እና አላፊ አግዳሚዉ ሁሉ በግላጭ
እየሰማና እያየኝ ነዉ አንዳንዱ ለእኔ አዛኝ መስሎ ጠጋ ይልና፣ ‹እንዲህ በይዉ› ብሎ ይመክረኛል የተረፈዉ ደግሞ ድምፁን ከፍ አድርጎ እንደ'ሱ ልክ ልኳን ንገራት ጃሪምን
ይመክረዋል አንዳንዱ እንዳትከፍትላት፣ ደግ አደረግህ!» ይለዋል እሱን፣ ሌላዉ ደግሞ ምን አለማመነሽ? ፈሪ ነሽ እንዴ? መኪና ይዘሽ የለ? ዝም ብለሽ ደርምሰሽዉ የማትገቢ! ይለኛል እኔን፡ አልደነቀኝም ምክራቸዉን ሰምቼ የእናቴን
አጥር ብደረምሰዉ እና ቢፈርስ፣ እኛ እንጂ እነሱ አይጎዱም፡

መካሪ እና ግርግሩ መብዛቱን ሳይ፣ ለመሸሽ መረጥሁ: ምስስ ብዬ ወደ መኪናዉ ገባሁና፣ ቆይቼ ብመለስ
አልፎለት እንደሚጠብቀኝ
በመተማመን፣ እሱን ትቼ እመዋን ፍለጋ ወደ ኋላ መንዳት ጀመርሁ።

እሺ ጎረቤት እና አልፎ ሂያጅስ የእኛን ነገር ያባብስብን ግድየለም፣ የቀሩት
እህትና ወንድሞቼን ድምፅ አለመስማቴ ግን ደነቀኝ፡፡ መቼም በግቢዉ
ዉስጥ ያለዉ ጃሪም ብቻዉን አይመስለኝም: ያም ብቻ ሳይሆን፣ እኔን
ከብቦ እኔንም ግፊ፣ እሱንም ግፋ ይል ከነበረዉ ሰዉ መሀል አንደኛዋ
እህቴ ጭጭ ብላ፣ ልክ እንደሌላዉ ሰዉ ስትታዘበን አይቻታለሁ የሆነዉ ሆኖ በቅቶኛል፡ እየተንገሸገሽሁ ከመንደራችን ራቅ እንዳልሁ፣ መኪናዉን ዳር አስይዤ
አቆምሁትና፣ አብሮ በሚዞረዉ አልጋዋ ላይ ከኋላዬ ያስተኛኋትን ልጄን
ዳበስኋት፡ ቱናትን፡ ትራፊ ምግብ አላበላትም ብዬ የመብያ ሰዓቷን
በጣም አሳልፌባታለሁ፡ አሁን ግን አማራጭ ስለ ሌለኝ፣ ቅድም
ቀማምሳለት የተረፈዉን ቀዝቃዛ ፍትፍትም ቢሆን ማብላት አለብኝ በተጨማሪም እንደ ልማዴ ዓይኔን ጨፍኜ እየተንሰፈሰፍሁ፣ ትንሿን ጣቴን በፊንጢጣዋ በኩል ሰድጄ ካካ ማስባል አለብኝ፡ ይኼንንም በየሦስት
ሰዓቱ ማድረግ ሲጠበቅብኝ፣ ዛሬ ግን አሳልፌባታለሁ በዚያም ላይ
ከጠዋት ጀምሬ ወዲያ ወዲህ ስላልኋት ነዉ መሰለኝ፣ እነዚያ ቁልቁል
የሰረጉ ዓይኖቿ ይበልጡኑ ቡዝዝ ብለዉ ታዩኝ፡

ቱናትን እንደ ነገሩ አቀማመስኋትና፣ ሌላ ሌላዋንም እንደሚሆን እንደሚሆን አድርጌላት ስጨርስ፣ ወደ ነበረችበት መልሼ አስተኛኋት። ከዚያ፣ እመዋን ፍለጋ ወደ ታዕካ ነገሥት ገዳም ማሽከርhር ጀመርሁ።
ምን እየተደረገ እንደሆነ እመዋን መጠየቅ አለብኝ፡፡ መቼም እሷ መልስ
አታጣልንም አሁኑኑ አግኝቻት እስከዛሬ እየናቅሁ ያለፍሁትን ጥያቄ
ሁሉ መጠየቅ አለብኝ፡ ምን እስኪፈጠር ነዉ ከዚህ በላይ? አይበቃም? ኧረ በቃ በቃኝ...

“እመዋን አይተዋታል አባ?” አልኋቸዉ ቄሰ ገበዙን፣ በሥዕል ቤት ኪዳነምሕረ እና ታዕካ ነገሥት በዓታ መካከል ባለዉ ሰፊ አደባባይ አግኝቻቸዉ፡

“እግዚአብሔር ይመስገን: ደህና ዉለዋል?” አሉኝ፣ መንገዳቸዉን ገታ አድርገዉ አቤት ትሕትና! እኔን እኮ ነዉ አንቱ ያሉኝ፡ መቼም ትሕትና ከገዳም ሌላ መኖሪያም የላት! ያልኋቸዉን ባይሰሙኝም፣ ሰላምታ እንዳቀረብሁላቸዉ ገምተዋል።

“እመዋን አይተዋት ይሆን?” ስል አቻኮልኋቸዉ አሁንም፣ ሰላምታቸዉ ጊዜ የሚወስድብኝ ስለመለሰኝ፡፡
👍22
#ገረገራ


#ክፍል_ሀያ_ሰባት


#በታደለ_አያሌው

...ለአንዳፍታም ቢሆን እንኳን ቱናትን መለየት ያሸብራል፡ መቼስ እንዲህ የሚያደርገኝ ልጅነቷ ወይም መላመዳችን ወይ ደግሞ ገዳሜ ስለሆነች ብቻ አይመስለኝም፡ ታዲያ ምንድነዉ?
ብቻ ክብድ ብሎኛል፡

ደረስሁ።

ከጨዋታ ይልቅ ለዝምታ የሚያመቸዉን በትላልቅ ሀገር በቀል ዛፎች የተሞላዉን ግቢ፣ በተለያየ ዕድሜ የሚገኙት ሕጻናት ይቦርቁበታል። አንዳንዶች ክብ ሠርተዉ፣ አንዳንዶች በመስመር ሆነዉ፣ ሌሎች ዝብርቅርቅ ብለዉ የልባቸዉን ይጫወቱበታል፡ አለፍ ብሎ ባለዉ ሜዳ ላይ ሰፊ ምንጣፍ ተነጥፎላቸዉ ጨቅላዎች ይንከባለላሉ ከእነሱ በወራት
ዕድሜ ከፍ ያሉት ደግሞ ራሳቸዉን ችለዉ ለመቆም ይዉተረተራሉ
የሕጻናቱ ተንከባካቢዎች እንደየምድባቸዉ የሚቆሙት ቆመዉ፣ ያቀፉት ደግሞ ተቀምጠዉ በየትዕይንቱ ይደሰታሉ።

መሥራትስ እንደ እነሱ ነዉ› አልሁኝ፣ በቅናት።

ሆኖም ሥጋቴ ሊያልፍልኝ አልቻለም: እንዲሁ ከመኪናዬ ወረድሁና ቱናትን ከአልጋዋ አንስቼ አቀፍኋትና፣ የግቢዉ አማካይ የሚሆን ሥፍራ ላይ ቆምሁ፡፡ በየትኛዉ ቢሮ የትኛዉን ሰዉ ማናገር እንዳለብኝ በዓይኖቼ
ወዲያ ወዲህ ስል አንዲት በልተት ያሉ ሴትዮ ቀረቡኝ፡

“እንኳን በደህና መጣችሁ” አሉ፣ ልብ በሚሞላ ፈገግታ እኔንም
ቱናትንም አይተዉ ይበልጥ እየቀረቡን፡፡

“እንኳን ደህና አገኘኋችሁ” አልሁ፣ አንገቴን ወደ ጉልበታቸዉ
በመስበር ለትሕትናቸዉ ጭምር አክብሮት እየሰጠሁት፡
እዉነትም እነ እመዋ ነገሮችን ጨራርሰዉልኝ ኖሮ፣ ማነሽ የሚለኝ ሰዉ ቀርቶ ቅጽ እንድሞላ እንኳን የጠየቀኝ ሰዉ የለም፡ ቀድሜ ያገኘኋቸዉ ሴትዮ ለቱናት የተመደበላትን ማደሪያ ክፍል፣ ክፍሉን የሚጋሯትን
ሕጻናት፣ ያለማስታጎል እንዲከታተላት የተመደበላትን ነርስ፣ የምግቦቿን ዝርዝር መርሐ ግብር፣ልብሶቿን እና ሌሎች ነገሮችን በዚያዉ በማይለዋወጥ ትሕትናቸዉ ከገለጹልኝ በኋላ፣ ሥጋት ወይም አስታያየት
ይኖረኝ እንደሆነ ጠየቁኝ፡፡

“እንግዲያዉ መዋእለ ሕጻናት ብቻ አይደለማ ይኼማ?” አልኋቸዉ:
“ትክክል። ያዉ እንደምታዉቂዉ” አሉ፣ ደጋገሜ አንቺ እንዲሉኝ
የለመንኋቸዉን እንደ ምንም ተስማምተዉልኝ፡ “ያዉ እንደምታዉቂዉ አብዛኛዉ የማኅበራች አገልጋዮች ሌት ከቀ ሥራ ላይ ናቸዉ። በዚህም
የተነሳ ለልጆቻቸዉ በቂ እክብካቤ ለማድረግ ይቸገራሉ። ይኼ የሕጻናት መዋያ ከተከፈተ ወዲህ ግን እንደየአገልግሎት ጸባያቸዉ፣ ሙሉ ኃላፊነቱን ለእኛ ለመተዉ የተፈቀደላቸዉ አገልጋዮች አሉ: ሥራቸዉ ፋታ የሚሰጣቸዉ ያሉ እንደሆነ ግን ኃላፊነት የም ወስድላቸዉ ወይ ቀኑን ወይ ማታዉን ብቻ ይሆናል ማለት ነዉ” አሉኝ፣ ቱናትን ባዘጋጁላት
አልጋዋ ላይ እያሳረፏት፡
“ታዲያ” አልሁኝ፣ ከሁሉም ቅድሚያ ለቱናት የሚበላ እንዲሰጡልኝ ለመጠየቅ እንደገና እየዳዳሁ የአንገት ሰላምታ በርቀት ሰጥተዉኝ ከነበሩት ሴቶች አንደኛዋ፣ የልቤን አዉቃልኝ ይሁን የቱናትን ቡዝዝ ማለት አይታ እንደሆነ እንጃ፣ ትኩስ የሥጋ ፍትፍት አመጣችላት። ደቀቅ
ያለዉን የሥጋ አመታሮ በቀይ እንጀራ ፈትፍታ አምጥታ ስታጎርሳት እኔ ምራቄን ብዉጥም፣ቱናት ግን እምቢ አለች: ለማጫወት ብትሞክራት ሁሉ ለማልቀስ ተነፋነፈች።

“ግድ የለም” አሉ፣ ባልቴቷ። “ግድየለም፤ እንግድነት ተሰምቷት ነዉ። ትንሽ ትፋሽ ትዉሰድና እኔ አጫዉቼ አበላታለሁ”

“አይ አልሁኝ፣ ሥጋቴን መደበቅ እያቃተኝ፡

“ግድ የለሽም”

“እንዲያዉ ዛሬ እምብዛም ሳትበላ ነዉ የዋለችዉ”

“ሐሳብ አይግባሽ፤ አጫዉቼ አበላታለሁ”

“እንግዲህ ምን እላለሁ፣ እግዚአብሔር ይስጥልኝ ከማለት በቀር አልኋቸዉ ኹለቱንም፣ ስለ በጎ አድራጎታቸዉ፡
"ተዪ ተዪ: እኛ ነን ማመስገን ያለብን: እንኳንም እግዚአብሔር ልዩ አድርጎ የሰጠሽ ልጅሽ እንድናገለግላት ዕድሉን ሰጠሸን”

“አይ… እንዲያዉ ወድጄ እንኳን አይደለም ያመጣኋት: ልጄ ከብዳኝ ወይ ደግሞ ከእሷ የሚበልጥብኝ ሥራ ኖሮብኝም አይደለም”

“ይገባኛል”

“የሆነዉ ሆኖ እንግዲህ ከኹለት ወይ ከሦስት ሰዓት በላይ
አላስቸግራችሁም”

“ማስቸገር? የለም የለም: ለእሷ ከምናደርግላት ይልቅ፣ እሷ ለእኛ
የምታደርግልን ይበልጥብናል። ከባሪዎቹ እኛዉ ነን''

“ይሁን” ብዬ፣ ወጣሁ።

ለቅሶዋን ከኋላዬ እየሰማሁ፣ እንደ ምንም ጨክኜ ወጣሁ ወደ ጦር ሜዳ እየኼድሁ እንደሆነ ነዉ የሚሰማኝ፡ ከወንድሞቼ እና
ከእህቶቼ፣ በተለይም ከጃሪም ጋር ፊት ለፊት እስከምገጥም ቸኩያለሁ።እሱም ቢሆን ሌላ ምንም ምርጫ አልተዉልኝም፡፡

‹ምን ይሉት ፍርጃ ነዉ ግን? ኧረ እንደ ዋዛ የት ነዉ የደረስነዉ
በማርያም? እያልሁ እንዲችዉ እንደ ተብሰለሰልሁ፣ በአዲስ አበባ
ዩኒቨርስቲ ዋናዉ ግቢ በኩል ባለዉ ቁልቁለት ወረድሁ።

ለነገሩ ለምን በእነሱ ብቻ እፈርዳለሁ? ጥፋቱ የራሴም ጭምር አይደል?እነሱ ሆኑብኝና ተለማመጥኋቸዉ፡ የእኔ በሕይወት መኖር በእነሱ ፈቃድ እስኪመስል ድረስ ግፊያቸዉን ሁሉ ቻልሁላቸዉ᎓ የጃሪም ወንድምነት
ቢቀርብኝ እሞት ይመስል፣ ያለ ጥፋቴ ጭምር ማረኝ ማረኝ አልሁት።

ቆይ፤ እዉነት ግን አልሞትም? ያለ ጃሪም ወንድምነት፣ ያለ እህቶቼ
እህትነት ምንድን ነኝ እኔ?

ወደ ማኅበራችን ሕንጻ የሚያደርሰኝን መንገድ እንደ ተያያዝሁት፣ የዛፍ እና የንብ ሽርክና በልቡናዬ ክችች አለብኝ፡፡
ሠራተኛዋ ንብ ለማኅበረ ንቧ የሚሆነዉን ምግብ ለመቅሰም አበባ ወዳለው ዛፍ ታርፋለች:: ከአበባዉ ላይ የምታገኘዉን ዕጩ ማር ከቀሰመች በኋላ ተጨማሪ ፍለጋ ወደ ሌላ ባለ አበባ ዛፍ ትሄዳለች: ነገር ግን ከዛፋ
በምትነሳበት ጊዜ፣ የአበባዉ ወንዴ ዘር በጸጉራም አካሏ ላይ ተሳፍሮ ይከተላታል። ወደ ቀጣዩ የአበባ ዛፍ በምታርፍ ጊዜም፣ ያ ከዚያኛዉ ዛፍ ያመጣችዉ ወንዴ ዘር፣ እዚህኛዉ ዘንድ ካለዉ የአበባዉ ሴቴ ዘር ጋር ይገናኛል፡ በዚህም ምክንያት፣ ንቧ ምግቧን ፍለጋ ከዛፍ ዛፍ ባረፈች
ቁጥር፣ የአበባ ዛፎች እንዲራቡ ታደርጋለች ማለት ነዉ ንብ ያለ አበባ ማለት እንግዲህ ያለ ምግብ፤ አበባም ያለ ንብ ማለት ደግሞ ያለ መራባት ስለሆነ ተከላክለዉ አያዉቁም:: እርስ በእርስ ቢከላከሉ፣ አንዳቸዉም መኖር እንደማይችሉ ኹለቱም ጠንቅቀዉ ያዉቁታል።

ስለዚህ ንብ እና አበባ አይለማመኑም:: አለመለማመን ብቻም ሳይሆን፣ ነፍሳቸዉ እስኪገባ ድረስ ይዋደዳሉ
እንደ እዉነቱ፣ እኔና ጃሪምም ሆንን ከሌሎች እህትና ወንድሞቻችንም
ጋር ግን፣ አበባና ንብ ብቻ አይደለንም፡፡ ወይ ንብ እና ንብ፣ ወይ አበባና አበባ ነን፡ ያዉም ወይ የአንድ እናት ንብ እናት አበቦች ነን፡፡ እንዲያዉ እሱም አጉል ሆኖ ቢፈርስ ግን፣ ቢያንስ ንቦች፣ ወይ ደግሞ የአንድ እንደ አበባና ንብ እንኳን መሆን እንዴት ያቅተናል?

የእኔም እጅ አለበት፡፡

አዎ፣ አለበት!

እኔ ያለ እነሱ መኖር እንደማልችል ብቻ እንጂ፣ እነሱም ያለ እኔ መኖር
እንደማይችሉ ነግሪያቸዉ አላዉቅም አበባ የንብን ጥቅም ባያዉቅ ኖሮ አያከብረዉም: የማያከብረዉን ደግሞ የሚወድ የለም፡ መናቅን እንጂ፣በእጄ ነሽ፣ ብለቅሽ ያልቅልሻል፣ ተሸከምሁሽ፣ በደልሽኝ ማለትን እንጂ
እንደ'ኔ ማለትን ያስተዋል፡፡ እህትነቴ እንዲተናነቃቸዉ፣ እነ ጃሪም እዚህ እንዲደርሱ የእኔም ሚና አለበት፡፡

“የት ናት?” አልሁት ባልቻን፣ ከራሴ ጋር እንዲህ እየተዋቀስሁ ወደ
ሲራክ ፯ ማዕከል ደርሼ ቢሮዉ ዉስጥ ያገኘሁት ከኹለት ሰዎች ጋር እየተነጋገረ ቢሆንም፣ ምንም ሳይመስለኝ፡
👍31👏2