አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
569 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አስራ_አራት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው


“ኑ ወደ ማዕድ ቤት ትንሽ ምግብ ያስፈልጋችኋል።” አለ ሴራሊዮናዊው የዩኒሴፍ ሰራተኛ፡፡ ተከተልነው።

በማዕድ ቤቱ ውስጥ አግድም ወንበርአ ላይ ከሌሎች ልጆች ጋር ተቀመጥን። ሩዝ በጎድጓዳ ስሃን ቀረበልን፡፡ እሱን ያለምንም
ፋታ መብላት ጀመርን። አል ሃጂ ከየት ናችሁ ብሎ እስከሚጠይቅ ድረስ ምንም አላወራንም: አል ሃጂ ሲጠይቃቸው
ደስተኛ አልነበሩም:: ማነህ አንተ? ያንተን ጥያቄ ልንመልስ ነው የመጣነው?” ሲል አል ሃጂ ተነስቶ ገፈተረው። ልጁ ተነስቶ
ሊደባደብ ሲል አንድ ሰው ተዉ ልጆች!” አለ።

ቦምብ አውጥቼ ይሄ የመጨረሻችሁ እንዲሆን ነው የምትፈልጉት ወይስ ጥያቄውን ትመልሳላችሁ?” አልኩ፡፡

ከኬኖ ወረዳ ነው የመጣነው”
“አልማዝ ከሚገኝበት አካባቢ?” አለ አል ሃጂ።
“ከጦሩ ጋር ነው ወይስ ለአማጺዎች ነው የተዋጋችሁት?”
ምኔ አማጺ ይመስላል? ለጦሩ ወግኜ ነው የተዋጋሁት።
አማጺዎች መንደሬን አቃጥለው ወላጆቼን ገለዋል፤ አንተ ግን እነሱን ትመስላለህ።”

በአንድ ወገን ነዋ የተዋጋነው” አለ አል ሃጂ። ተቀመጥን።ቦምቡን እንደያዝኩት ነበር። ፊቴን ወደ ማዕድ ቤቱ ያመጣን
ሰውየ አዙሬ “ መቶ አለቃ ለምን ለእነዚህ ያልታጠቁ ሴታ ሴት ሰዎች አሳልፈው እንደሰጡን ታውቃለህ?” ብየ ጠየቅኩት።
በፍርሃት ርዶ፣ በላብ ተጠምቆ ሊመልስ ሲል አንዱ ልጅ “ እሱ ያልታጠቀ ነው ሌሎች ልጆችን እንጠይቃቸው”አለ። ማቡ ይባል ነበር በኋላ ጓደኛሞች ሁነናል፡፡ ተነስተን ቤት ደጃፍ ላይ ወደ ተቀመጡት ታዳጊዎች ሄድን፡፡

“ጓዶች አዛጋችሁ ለምን ለእነዚህ ሰዎች እንደሰጡዋችሁ ታውቃላችሁ?” ብሎ አል ሃጂ ጠየቀ። ዝም አሉ፡፡ “ኣትሰሙም
እንዴ?

“ማንም እንዲያስቸግረን አንፈልግም” አለ በሸካራ ድምጸ።በዛ ላይ ላልታጠቀ ተራ ሰው ጥያቄ መልስ መስጠት አንፈል
ግም።”

“ተራ ሰው ሲቪል አይደለንም! አለ ማቡ በቁጣ።” ተራ ያልታጠቀ ሰው ካለ እናንተ ናችሁ። መለዮ እንኳን ያልለበሳ
ችሁ። ምን አይነት ወታደር ነው መለዮ ማይለብሰው ባካችሁ?!”

“ለአማጺዎች ነው የተዋጋ ነው፤ ጦሩ ጠላታችን ነው።ለነጻነት ነው የተዋጋነው! ጦሩ ቤተሰቤን ገድሏል መንደሬንም
አፍርሷል፡፡የጦሩን አባላት ባገኘሁት አጋጣሚ ሁሉ እገላለሁ”ብሎ ተነሳ።

“አማጺዎች” ብሎ ማቡ ጮኸ። ሰንጢዎቻችን አውጥተን ተፋጠጥን፡፡ እንደገና ጦርነት! ፈረንጆቹ ቦታ ስለቀየርን ከጦር ቀጠና ስለተገለልን ብቻ ደህና የምንሆን መስሏቸዋል።አዕምሮችን የተበረዘ አደገኛ ነፍሰ ገዳይ መሆናችንን አላወቁም! አሁን በቀላሉ እንደማናገግም ይገባቸዋል።

ቦምብ ወረወርኩ ግን ዘገየ፡፡ ድብድቡ ቀጠለ አንዳንዶቻችን ሰንጢ ይዘን ሌሎች በባዶ እጅ መታገል ጀመርን። አንዱን እግሩን ወጋሁት ሌላው እኔን ሊወጋ ሲል አል ሃጂ ቀድሞ ከጀርባ ወጋው፡፡ የጮኸ ወይም ያለቀስ የለም ሁላችንም ለምደነዋል በዛ ላይ አደገኛ ዕፅ ወስደን ነበር፡፡ ፖሊሶቹ “አቁሙ አቁሙ” እያሉ
ወደ እኛ መጡ፡፡ከአገላገሉን በኋላ የወደቀውን ሊያነሱ ሲጎነበሱ ገፍትረን ጥለን መሳሪያቸውን ቀማን። ማቡ ተኩሶ የተወሰኑትን ገደለ ሌሎችን ደግሞ አቆሰለ፡፡ አማጺዎች ከእኛ ወገን ሁለት
ታዳጊዎችን ገደሉ፡፡ ፖሊስ ወደ ሰማይ ቢተኩስም መታገል አላቆምንም:: ስለዚህ በጉልበት ለያዩን መሳሪያ ድቅነው
አቆሙን። አምቡላንስ እየጮኸ መጥቶ የተጎዱትን ወሰደ።ስድስት ታዳጊዎች ሲሞቱ ሁለት ፖሊሶችን ጨምሮ ብዙዎች
ቆሰሉ።

በማቡ ጀብድ ተገረምን፤ማዕድ ቤት ተመልሰን ስለእሱ ነበር የምናወራው። አንዱን ልጅ አይኑን መትቶት ልጁ ቡጢ ሊመልስ ቢፈልግም ማቡን ማየት አልቻለም። ድብድብ ረብሻው ለእኛ
ጨዋታ ነበር። ከማዕድ ቤት አውጥተው ወሰዱን። የጦር መኪና እየጠበቀን ነበር፡፡ “ወደ ጦርነቱ ሊመልሱን መሆን አለበት::” አለ አል ሃጂ። ዝም ብለን ብሔራዊ መዝሙሩን መዘመር ጀመርን::ወደ ጦርነቱ አልመለሱንም ነገር ግን ቤኒን ቤት ወደ ሚባል ሌላ የማገገሚያ ማዕከል ነበር የወስዱን፡፡ ለምን ወደ እዚህ ቦታ
እንደመጣን አሁንም አላወቅኩም፡፡ G3 ሽጉጤ፣ የጦርነት ፊልም እና የምወስደው ክኒን ትዝ ይለኛል። ከሁሉም በላይ መቶ
አለቃ “ከአሁን በኋላ ያገኘነውን አማጺ እንገላለን፧ ምህረት ምርኮኛ የሚባል ነገር የለም”የሚለው ንግግር ወደ አዕምሮየ
ይመላለስ ነበር።

ባልታጠቀ በሲቪል መታዘዝ ያበሳጫል፡፡ ድምጻቸውን መስማት እንኳ አልፈልግም:: ለቁርስ እንኳ ሲጠሩን ሳጥን ያገኘሁትን ነገር በቡጢ እመታለሁ። ከመመገብ ውጭ የታዘዝነውን አንፈፅምም ነበር።
እንቢተኛ ነበርን! ቁርስ ሻይ እና ዳቦ፣ ምሳ እና እራት ደግሞ ሩዝ እና ሾርባ እንበላ ነበር። መሳሪያችን እና አደገኛ ዕፅ ከእኛ
ጋር ስላልነበር ደስተኞች አልነበርንም።

ተደጋጋሚ የጤና ምርመራ እና የምክር አገልግሎት በነርሶቹ እና ሌሎች ሰራተኞች ይደረግልን ነበር፡፡ አንወደውም ነበር፡፡ ገና
ሲጀምሩ ያገኘነውን እቃ እንወረውራለን እንደበድባቸዋለን።ከምግብ በኋላ ያለምንም ምክንያት እንደባደብ ነበር። ሰራተኞቹ ምንም ብናደርግ እነሱን እንኳ ብንደበድባቸው አያዝኑብንም።
“የእናንተ ጥፋት አይደለም እንደዚህ ልታደርጉ የቻላችሁት”ብለው ፈገግታ ያሳዩናል።በእኛ ተስፋ ላለመቁረጥ የተስማሙ ይመስላሉ።

የራስ ምታት ማይግሬን እንደገና ተንስቶ ያሰቃየኝ ጀምሯል። አንጥረኛ በመዶሻ ራሴን የሚቀጠቅጥ ይመስለኛል።
አንዳንድ ቀን ራሴን መቆጣጠር ከብዶኝ መሬት ላይ እንከባለላሁ:: አል ሃጂ ደግሞ የቤቱን ምሰሶ በመደብደብ ሆስፒታል ገብቶ ነበር፡፡ ቆይቼ እኔም ራሴን ስቼ ሆስፒታል ገባሁ:: ሰውነቴን ሙሉ ያመኝ ነበር፤ ጉሮሮየ ደርቆ የማጥወልወል ስሜት ይሰማኝ ነበር። ነርሷ ፈገግታ እያሳየች ወደ እኔ አልጋ መጥታ መርፌ ወጋችኝ። አካሌ ተዳክሞ ተኛሁ።
በሚቀጥለው ቀን ከሆስፒታል ወጣሁ። ነርሷ ውሃ በደንብ ጠጣ አለች::

አንዳንዴ ከማጥወልወል ስሜት እና ድንገት እራስን ስቶ ከመውደቅ ባለፈ ከሁለት ወር በኋላ በአብዛኛው እየተሻለን
መጣ፡ የጦርነቱ መጥፎ ትዝታዎች ትርፍ ጊዜ ስለነበረን ወደ አዕምሮዋችን እየመጣ ያስጨንቀን ነበር። ይሄን ለማስረሳት ይመስላል ትምህርት ትጀምራላችሁ ተብለን የትምህርት
መሳሪያዎች ተሰጠን። ደብተር፣ እስክርቢቶ እና እርሳስ ከተሰጠን በኋላ ከሰኞ እስከ አርብ ከአራት ስዓት እስከ አስራ ሁለት ስዓት ትምህርቱ እንደሚሰጥ ተነገረን።ወዲያው ግን የተሰጠንን የትምህርት መሳሪያዎች አቃጠልን።
እንደገና ተሰጠን። እንደገና አቃጠልነው፡፡

አንድ ቀን ቀትር ላይ የማገገሚያው ሰራተኛች የተወሰነ የትምህርት መሳሪያዎች ደጃፍ አስቀምጠው ሂዱ። ማቡ የትምህርት መሳሪያዎችን አየና ለምን አንሸጠውም የሚል ሃሳብ
አመጣ። “ማን ይገዛናል? ሰዎች ይፈሩናል? አለ አንድ ታዳጊ ልጅ፡፡ “የሚረከበን ነጋዴ እንፈልጋለን” አለ ማቡ። በፕላስቲክ ቦርሳ ተሸክመን ቅርብ ወደ ሚገኝ ገቢያ ወስደን ለአከፋፋይ
ሸጥነው:: “ብዙ ገንዘብ ነው ያገኘነው” አለ ማቡ። ምሳ እንዳያመልጠን ወደ ማዕከሉ ቶሎ ተመልሰን። ከምሳ በኋላ ማቡ ድርሻችንን አከፋፈለ። ግማሾቹ ኮካ ኮላ፣ ከረሜላ እና ሌሎች ነገሮች ሲገዙ ማቡ፣ አል ሃጂ እና እኔ ደግሞ ለሽርሽር ወደ ፍሪ ታውን ለመሄድ አቀድን።

ጥዋት ቶሎ ቶሎ በላይ በላይ ቁርሳችንን ከበላን በኋላ አንድ በ አንድ ሾልከን ከመመገቢያ አዳራሹ ወጣን። ከውጭ ከተገናኘን በኋላ አውቶብስ መጠበቅ ጀመርን።

“ከተማውን ታውቁታላችሁ? ከዚህ በፊት ወደ ከተማው

ሂዳችሁ ታውቃላችሁ?”
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አስራ_አምስት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው

...ቅጠሎቹ አረንጓዴ ሲሆኑ ግንዱ ግን በጣም አርጅቷል። “ይሄን ስንነግራቸው ማንም አያምነንም” አለ አል ሃጂ።

የእራት ስዓት እየደረሰ ስለነበር ወደ ማዕከል መመለስ ነበረብን፡፡ ያን ምሽት ጓደኞቻችን ስለ ረጃጂም ህንጻዎች :
መኪናዎች እና ገበያው ነገርናቸው፡፡ ሁሉም ደስ ብሏቸው ማየት ፈለጉ። ማዕከሉም ይሄን በመረዳት በሳምንት አንድ ቀን የሽርሽር ፕሮግራም ተያዘልን፡፡

ቀስ በቀስ ወደ ትምህርት ተመለስን። ቀለል ያለ የትምህርት ስርዓት ነበር፡፡ ለሂሳብ መደመር፣ማባዛት እና ማካፈል ስንማር እንግሊዝኛ ደግሞ ምንባብ ማንበብ፣ ቃላቶችን ትርጉም ማወቅ
እና የእጅ ጽሁፍ እንማራለን። ብዙም አንከታተልም ; ትኩረታችን በትንሽ ነገር ይሰረቃል። በእርሳስ እንወጋጋላን
እንደባደባለን። “የናንተ ጥፋት አይደለም
ወደፊት ትስተካከላላችሁ' ይለናል መምህሩ።

ከምሳ በኋላ የጠረጴዛ ቴንስ ወይም እግር ኳስ እንጫወት ነበር። ለሊት ግን አስጨናቂ ነበር። በቅዥት እንባንናለን፣ በላብ እንጠመቃለን፣ ጩኸት እና ግድግዳ መደብደብ ነበር። ሰራተኞቹ
ይህን ስለሚያውቁ ጥበቃ ያደርጉልን ነበር።

የሴራሊዮን ዝናባማ ወቅት ከግንቦት እስከ ጥቅምት ሲሆን ሐምሌ፣ ነሐሴ እና መስከረም ደግሞ ከባድ ዝናብ ይኖራል።
ዝናቡ አንዳንዴ የጦርነቱን መጥፎ ትዝታዎች ይቀሰቅስብኛል።
የሰለጠንኩበት ቦታ እና የሞሪባ ሞት ትዝ ይለኛል። ሞሪባ በተኩስ እሩምታ ሲገደል መቅበር ቀርቶ ማልቀስ እንኳ አልቻልንም። አንድ ዛፍ ላይ አስጠግተነው በአፉ ደም እየደፈቀ ትተነው ሄድን።

ሲነጋ ሰራተኛዋ ብርድ ልብሱን መልሳ እያለበሰችኝ “ያንተ ጥፋት አይደለም በፍጹም! አይዞህ ትረሳዋለህ ይሻልሃል”
ትለኛለች፡፡

አንድ ቀን ረፋድ ላይ ቴንስ ስንጫወት የግቢው ሰራተኞች በሙሉ ይመለከቱን ነበር። አንድ ሰው ከኋላ ትከሻዬ ላይ ሲነካኝ ተሰማኝ ። ነርሷ ነበረች ። ነጭ ደምብ ልብስ እና ነጭ ኮፍያ ለብሳለች። ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር ፊት ለ ፊት ሳያት። ነጭ ጥርሷ ከጥቁር እና አንጸባራቂ ቆዳዋ ጋር ተጣምሮ ልዩ ውበት
ሰጥቷታል። ስትስቅ ደግሞ የበለጠ ውበቷ ይፈካል። ረዥም ናት፤ ትልልቅ አይኖች አሏት፡፡ ጠርሙስ ኮካ ኮላ ሰጥታኝ በሚያስፈልግህ ጊዜ ና እና እየኝ” ብላ ፈገግታ ሰጥታኝ ሄደች::
ከአል ሃጂ ጋር ጨዋታውን ትተን ወደ ውጭ ወጣን እና ኮካውን መጠጣት ጀመርን። “ወዳሃለች” እያለ አል ሃጂ ሊቀልድብኝ ሞከረ። ምንም አላልኩም::

እህ ትወዳታለህ እንዴ?” ብሎ ጠየቀኝ፡፡
“ እኔ አላውቅም:: ትልቅ ናት በዛ ላይ ነርሳችን ናት” አልኩ።
ማለት ሴቶችን ትፈራለህ?” አለ
“አንተ እንደምታስበው ወዳኝ አይመስለኝም” ብየ አል ሃጂን
ተመለከትኩት። የምለውን ነገር እያዳመጠ ይስቃል።

ኮካውን ጠጥተን እንደጨረስን አል ሃጂ ሄደ እኔ ግን ወደ ሆስፒታል ለመሄድ ወሰንኩ፡፡ በሩ ስደርስ ነርሷ ስልክ እያወራች አየኋት። እንድገባ እና እንድቀመጥ በእጇ ምልክት አሳየችኝ።
ወዲያው ስልኳን አቁማ ፈገግታ እያሳየችኝ ወንበሯን ወደ እኔ
አቀረበች፡፡ ስለ ጦርነቱ ጥያቄ ልትጠይቀኝ እንደሆነ ገመትኩ።
እሷ ግን በተረጋጋ መንፈስ “ ስምህ ማነው” ብላ ጠየቀችኝ፡፡ገረመኝ! ስሜን እንደምታውቀው እርግጠኛ ነበርኩ። “ስሜን ታውቂዋለሽ” ብየ በቁጣ መለስኩ።
“ ምን አልባት ላውቀው እችላለሁ ግን ስምህን እንድትነግረኝ እፈልጋለሁ?” አለች አይኗን እያፈጠጠች::

እሺ እሺ እስማይል” አልኩ፡፡

“ጥሩ ስም” አለች እራሷን እየነቀነቀች፡፡ “ የእኔ ስም አስቴር ነው። ጓደኛሞች እንሁን።”

“እርግጠኛ ነሽ ከእኔ ጋር ጓደኛ መሆን ትፈልጊያለሽ” አልኳት::ለተወሰነ ጊዜ ካሰበች በኋላ “እርግጠኛ ላልሆን እችላለሁ” አለች።

ምን ማለት እንዳለብኝ ስላላወቅኩ እና ማንንም ስለማመን ለተወሰነ ጊዜ ዝም አልኩ። እንዴት መትረፍ እና እራሴን
መንከባከብ እንዳለብኝ ብቻ ነው ነበር የተማርኩት። እንደ መቶ አለቃ ጃባቲ ያሉ ያመንኳቸው የታዘዝኳቸው ሰዎች እንኳ
ሰዎችን በተለይ አዋቂዎችን እንድጠራጠር አድርገውኛል::
የሰዎችን ሃሳብ መጠራጠር ከጀመርኩ ቆይቻለሁ። ሰዎች ጓደኛ የሚሆኑት አንዱ ሌላው ላይ ጥቅም ለማግኘት ነው ብየ አስብ ነበር፡፡ ስለዚህ ለነርሷ ምንም መልስ አልሰጠኋትም።

“ያንተ ነርስ ነኝ በቃ ይሄ ነው። ከእኔ ጋር ጓደኛ መሆን ከፈለክ ልትጠይቀኝ እና ላምንህ ይገባል” አለች። ተመሳሳይ ሃሳብ
ስለነበረን ፈገግ አልኩ። ፈገግታህ ያምራል” አለች። አፍሬ ቁጥብ ሆንኩ።
“ከከተማ እንዳመጣልህ የምትፈልገው ነገር አለ?” ብላ ጠየቀችኝ፡፡ መልስ አልሰጠሁም::

“ለዛሬ ይበቃናል” አለች፡፡

ከተወሰነ ቀን በኋላ ነርሷ ስጦታ ሰጠችኝ። የተጠቀለለ ነገር ነበር ምን ይሆን እያልኩ መክፈት ጀመርኩ። ልክ እንዳየሁት በደስታ ተነስቼ አቀፍኳት። “ጓደኛ ካልሆን ለምን ይሄን ማዳመጫ እና ካሴት አመጣሽልኝ? ራፕ ሙዚቃ እንደምወድ እንዴት አወቅሽ?”

“እባክህ ተቀመጥ” አለች። የጆሮ ማዳመጫውን አደረኩ
D.M.C የዲ.ኤም.ሲ ሙዚቃ ነበር የምሰማው “It's like that and that the Way it is...” እንደዛ ነው እንደነገሩ” ራሴን ማንቀሳቀስ ጀመርኩ።አስቴር የጆሮ ማዳመጫውን ከጆሮዬ አውጥታ “አንተ ሙዚቃ ስታዳምጥ እኔ ልመረምርህ ነው”
አለች። ተስማማሁ። ምላሴን ፣ አይኔን አየች ከዛ እግሬን ስታይ ጠባሳ ነበረኝ። “ይሄ ጠባሳ እንዴት ወጣብህ?”

“በጥይት ተመትቼ ቆስየ ነው” እላለሁ በቀላሉ።

ፊቷ በሃዘን ተሞላ “ምን እንደሆንክ ምን እንደሚሰማህ ከነገርከኝ መድሃኒት ላዝልህ እችላለሁ” አለች። ሁሉንም
ነገርኳት፡፡ እንዴት በጥይት እንደተመታሁ፣
ስንት ጊዜ እንደተመታሁ እና ከዛ ምን እንዳደረኩ ነገርኳት። ልነግራት ግን
ፈልጌ አልነበረም፡፡ አስቃቂውን የጦርነቱን ክስተት ስነግራት መጠየቅ ታቆማለች ብዬ እንጂ። እሷ ግን በጥንቃቄ ታዳምጣለች። የትናንቱን ታሪኬን ማስታወስ ስጀምር አንገቴን ደፋሁ።

በበጋ ወቅት ስለነበረው ጦርነት ነገርኳት። ምግብ እና ጥይት ያጠረን አስቸጋሪ ወቅት ነበር። ሌላ መንደር ማጥቃት ነበረብን።ከትንሽ ስለላ በኋላ የሶስት ቀን ጉዞ ወደ ሚጠይቅ አንድ ሰፈር ሄድን። እቅዳችን ምግብ እና ጥይት ይዞ መምጣት ሳይሆን የምናጠቃውን ሰፈር ወደ ዋና ማዕከል መቀየር ነበር። ያለን
መሳሪያ እና ምግብ ይዘን ወጣን። ቦታው ደርሰን ለደፈጣ ውጊያ ስንዘጋጅ መንደሩ ባዶ መሆኑን ተገነዘብን። ከስዓት በኋላ
አምስት ታጣቂዎች መጥተው ባልዲ ይዘው ወደ ወንዙ ወረዱ..ገና መጠርጠር ስንጀምር ከኋላ ተኩስ ተከፈተብን። ለሊቱን ሙሉ ተታኮስን፡፡ አምስት ሰዎች ሞቱብን፣ የተረፍነውንም ተከተሉን። መቶ አለቃ ጠንክሮ ከመዋጋት ሌላ አማራጭ
እንደለለን ነገረን። ሌላ መንደር ለመሄድ በቂ ምግብ ወይም ጥይት የለንም፡፡ይሄን ጦርነት ካላሸነፍን ጫካው ውስጥ
መንከራተት ከዛም ማለቃችን ነው:: ስለዚህ ወደ ማጥቃት ገብተን መጀመሪያ ከሞቱት መሳሪያ አገኘን እና ተበተን::
በሁለተኛው ዙር እንደገና ተሰባስበን ማጥቃት ጀመርን::በመጨረሻ ከጠላቶቻችን በላይ ሐይል አግኝተን መበተን ቻልን:: የተኩስ እሩምታው በረደ፡፡ መንደሩ በእኛ ቁጥጥር ውስጥ ሆነ::
በድንገት ጥይቶችን በምሰበስብበት ወቅት የጥይት ዝናብ ወረደብን።

ሶስት ጊዜ እግሬ ላይ ተመትቼ ራሴን ስቼ ወደቅኩ። ሁለቱ ጥይቶች ገብተው ወጥተዋል አንዱ ግን እግሬ ውስጥ ቀረ::
በሚቀጥለው ቀን ስነቃ እግሮቼ ላይ ምስማር የተተከለ ይመስላል።
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አስራ_ስድስት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው


ይሄን ነግሬያት ከሆስፒታሉ ለመውጣት ተነሳሁ። አስቴር ግን “በኮንናውት ሆስፒታል ሙሉ ምርመራ እንድታደርግ
ሁኔታዎችን አመቻቻለሁ።” ብላ ላፍታ ዝም ብላ ከቆየች በኋላ ሙዚቃ ማዳመጫው ከእኔ ጋር ይቆይ ሌሎች እንዲቀኑብህ
እና እንዲሰርቁህ አያስፈልግም፡፡ በፈለከው ቀን መጥተህ ማዳመጥ ትችላለህ። ሁሌም እኔ ከዚህ ነኝ” አለች። ሙዚቃ ማዳመጫውን ወርውሬ ወጣሁ።

አንድ ቀን ከስዓት አስቴር ከስራ እረፍት ብትሆንም ከሁለት ሌላ ሰዎችጋር በነጭ ቶዮታ መጣች። አንዱ ሰው ሹፌር ሲሆን
ሌላው ግን የ ጦርነት ጋር የተገናኙ ህጻናት ወይም Children Associated with War የመስክ ሰራተኛ ነበር። ድርጅቱ ከ ዩኒሴፍ እና ሌሎች መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር የሚሰራ የካቶሊክ ድርጅት ነበር።

“ ወደ ሆስፒታል ሂደን ከተመረመርክ በኋላ ከተማ ሽርሽር ትሄዳለህ።” አስቴር በደስታ ምን ትላለህ ብላ ጠየቀችኝ፡፡

“እሺ” ብየ ተስማማሁ። ደስ ብሎኛል።”ጓደኛየ አል ሃጂ መምጣት ይችላል?” ብየ ጠየቅኩ።

“ይችላል” ስትል እንደምጠይቃት የጠበቀች ይመስላል።ወደ ፍሪ ታውን መንቀሳቀስ ስንጀምር የመስክ ሰራተኛው
“ ስሜ ለስሊ ይባላል፤ ስላገኘሁህ ደስ ብሎኛል” ብሎ ተዋወቅን።ወደ መሐል ከተማው ስንደርስ አስቴር እጆቿን እየጠቆመች ፖስታ ቤት፣ ሱቆችን፣ የተባባሩት መንግስታት ድርጂት
ህንጻዎችን እና የጥጥ ዛፉን አሳየችኝ። በከተማው ሁሌም እደነቃለሁ። በስራ የተጠመዱ ሰዎች ሲጣደፉ ሲወጡ ሲወርዱ የነጋዴዎች የግዙኝ ጩኧት ደግሞ ልዩ ድምፅ ይሰጣል።

ዶክተሩ የቆሰለ ወይም በጥይት የተወጋ ሰውነቴን እየነካ እና እየጨበጠ “የሚሰማህ ነገር አለ” እያለ ደጋግሞ ይጠይቀኝ ነበር፡፡መናደድ ስጀምር ጨርሰሃል አለኝ፡፡ ልብሴን ለብሼ አስቴር ፣
ለስሊ እና አል ሃጂ ወደ ሚገኙበት መቆያ ክፍል ሄድኩ::ተያይዘን ወደ ገበያው ሄድን። አስቴር ለ አል ሃጂ የስፖርት
ማሊያ ስትገዛለት ለስሊ ደግሞ ለእኔ የ ቦብ ማርሌን ኤክሶዶስ (ስደት) የሚለውን አልበም ገዛልኝ፡፡ አል ሃጂ ማሊያውን
ወዲያው ለበሰው:: ማሊያው የሃገሪቱን ብሔራዊ ሰንደቃላማ ማለትም አረንጓዴ፣ ነጭ እና ሰማያዊ ቀለማቶችን ይዟል።
አስቴር ለሁላችንም ኮካ ኮላ ገዛችልን። ለስለ እኔ እና ሌሎች ልጆችን ለማገዝ እንደተመደበ እና ዋና ስራው እኛ ከማገገሚያው በኋላ ለሚኖረን ህይወት ነገሮችን ማመቻቸት ነው።

በሚቀጥለው ቀን ወደ ከተማ ተመልሰን እኔ ሆስፒታል ሄድኩ። አስቴር ራሴን እያሻሸች “ መልካም ዜና ነው። ውጤትህ
መጥቷል። ዶክተሩ ለክፉ የሚሰጥ ህመም እንደሌለብህ አረጋግጧል። ለበለጠ እርግጠኝነት የተወሰኑ መድሃኒቶችን ትወስድ እና ዳግም ምርመራ ይደረግልሃል” አለች። ምንም
አላልኩም ! እሷ ግን ካሴት እና ማዳመጫውን ሰጠችኝ። አስቴርን እየለመድኳት ስመጣ ስለ ብዙ ነገር ማውራት ጀመርን፡፡በተለይ ግን ስለ ሙዚቃ ቦብ ማርሌ እና ራን ዲ.
ኤም.ሲ፡፡ ለስሊ በሳምንት ሁለት ጊዜ ይመጣ ነበር። ስለ ራስ ተፈሪያኒዝም ማውራት ይወዳል። እኔም #የኢትዮጵያ ታሪክ ደስ ይለኛል በተለይ ንግስት ሳባ እና ንጉስ ሰለሞን የተገናኙበት ታሪክ
ይገርመኛል። የተጓዙት ረዥሙ ጉዞ ፣ የመረጡት ቦታ እና ለመድረስ ያሳዩት ፅናት ሁሌም ይገርመኛል። ከህይወቴ ጋርም ለማገናኘት እጥራለሁ፡፡ የእኔ የህይወት ሩጫ እንደ እነሱ ትርጉም ያለው እና ደስታ የሞላበት እንዲሆን እመኛለሁ።

አንድ ምሽት አስቴር ቤቷ ወሰዳ እራት ጋበዘችኝ፡፡ ከእራት በኋላ ወደ ከተማ ወጥተን መናፈስ ጀመርን። ራውዶን መንገድ ጫፍ ወዳለ የባህር ዳርቻ ሄድን። ጨረቃ በድምቀት ወጥታ ነበር እና ደርቻው ላይ ሁነን መመልከት ጀመርን፡
ልጅ እያለሁ በጨረቃ ውስጥ የተለያየ ቅርፆችን እንመለከት እንደነበር ለ
አስቴር ነገርኳት። ገረማት። ጨረቃዋን እያየን የያዘችው ቅርፅ ምን እንደሆነ መገመት ጀመርን።

ልጅ እያለሁ አያቴ አስተውሎ ለሚያይ እና ለሚያዳምጥ ሰው ሰማይ ይናገራል ትል ነበር፡፡ በሰማይ ሁሌም የጥያቄዎቻችን
መልስ እና የነገሮች ምክንያት ይገለፃል። የእያንዳንዱ ስቃይ፣ ጉዳት፣ ደስታ እና ግራ መጋባት መንስዔ ይነገራል፡፡” ያ ለሊት ሰማዩ እንዲያወራኝ ፈለኩ።

ከአምስት ወር የቤኒን ማገገሚያ ቆይታ በኋላ አንድ ቀን ዓለት ድንጋይ ላይ ተክዤ ተቀምጬ እያለሁ አስቴር አየችኝ። ምንም
ሳትናገር መጥታ ከጎኔ ተቀመጠች። በሰለለ ድምፅ “ ከዚህ በኋላ የምኖርለት ምክንያት ያለ አልመስለኝ እያለ ነው” አልኩ።” ቤተሰብ የለኝም። እኔ ብቻ ነው የቀረሁት። የልጅነት ታሪኬን እንኳ የሚናገር የለም::”

አስቴር እጆቹዋን ወደ እኔ ልካ ጎትታ አስጠጋችኝ እና አቅፋ
“እኔን እንደ ቤተሰብህ አስበኝ፤ እንደ እህት ” አለች:: ግን እህት እኮ የለኝም”
አሁን አለህ፡፡ የአዲስ ህይወት ገፀ በረከት ነው። የተለያዩ የቤተሰብ አባላትን ማፍራት ትችላለህ።” ብላ አየችኝ፡፡

“እሺ! እህቴ መሆን ትችያለሽ ለጊዜው።”

“ይሁን ስለዚህ ነገ ጊዚያዊ እህትህን ለማየት ትመጣለህ አይደል።”

“እሺ!”

በሚቀጥለው ቀን አስቴር ወደ ማዕከሉ የሚመጡ ጎብኚዎች እንዳሉ ነገረችኝ። ሰራተኞቹ የተሰጥዎ ውድድር እንድናደርግ ጠየቁን፡፡ የምንችለውን ማንኛውንም አይነት ነገር እንድናቀርብ
ነበር የተፈለገው።

ሬጌ ሙዚቃህን ለምን አትዘፍንም” ብላ አስቴር ሃሳብ አቀረበች።

• የሼክስፒርን ቃለ ተውኔትን ባቀርብስ”

“እሺ ትንሽ ሙዚቃ ብትጨምር ጥሩ ይመስለኛል” አለች

እጆችዋን ትከሻየ ላይ አደርጋ። ወድጃታለሁ ግን መውደዱን አላሳያትም:: ስታቅፈኝ ቀስ ብየ ከእቅፏ እወጣለሁ፡፡ ስትሄድ ግን አያታለሁ። ከትምህርት በኋላ ሩጬ እሷን ላይ እሄዳለሁ።ጓደኞቼ ማቡ እና አል ሃጂ “ የሴት ጓደኛህ መጣች እስማኤል” እያሉ ይቀልድብኛል፡፡

ጎብኚዎቹ ከ አውሮፓ ኮሚሽን፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና ሌሎች መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጂቶች የተውጣጡ ናቸው። ሙሉ ልብስ ከነከራባቱ ለብሰዋል። እርስበርሳቸው
ስላምታ ከተለዋወጡ በኋላ ማዕከሉን እየዞሩ ቃኙ። በኋላ ለተሰጥኦ ውድድሩ በሚገባ ወደ ተዘጋጀው ወደ ምግብ አዳራሽ ገቡ። የማዕከሉ ዳሬክተር አቶ ካማራ የመክፈቻ ንግግር ካደረጉ
በኋላ ውድድሩ ቀጠለ። ተረቶች፣ አስፈሪ ታሪኮች እና የባህል ጭፈራዎች ቀረቡ። እኔ ከጁሊየስ ቄሳር የተወሰነ ቃለ ተውኔት
ካቀረብኩ በኋላ አንድ የሂፕ ሆፕ ሙዚቃ ተጫወትኩ።ሙዚቃው ስለ አንድ ታዳጊ ወታደር ትንሳኤ ሲሆን በአስቴር
የሞራል ድጋፍ እራሴ የፃፍኩት ነው::

ከውድድሩ በኋላ በማዕከሉ ታዋቂ ሆንኩ። የማዕከሉ ዳሬክተር አቶ ካማራ ቢሯቸው ጠርተው “ አንተ እና ጓደኞችህ የእውነት ጎብኚዎችን አስደምማችኋል። አሁን ታዳጊዎች ማገግም እንደሚችሉ አውቀዋል።” አሉ። ወደፊት እንደገና የማቅረብ እድሉ እንዳለኝ ሳውቅ በጣም ደስ አለኝ፡፡ አቶ ካማራ ደግሞ ከእኔ
በላይ በከፍተኛ ስሜት ላይ ነበሩ።

የማዕከሉ ቃል አቀባይ ብትሆን ምን ይመስልሃል?” ብለው ጠየቁኝ፡፡
“ምን! ምንድን ነው ምሰራው ወይም የምናገረውስ?”አልኩ።

“ በመጀመሪያ ስለ ታዳጊ ወታደሮች ዝግጅት በሚኖርበት ጊዜ የምታነበውን ነገር እንፅፍልሃለን። ስራውን ከለመድከው በኋላ ፀ የምታቀርበውን ንግግር እራስህ ልታዘጋጅ ትችላለህ” አሉኝ::
ሳምንት ሳይቆይ በታዳጊ ወታደርነት እና እንዴት መቆም አለበት በሚሉ ሃሳቦች ላይ ንግግር አደረኩ። “ማገገም እንችላለን ብየ እራሴን ምሳሌ በማድረግ ህፃናት ከችግሩ መውጣት
👍3😁1
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አስራ_ሰባት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው


“ደህና ነህ?” ብየ ጠየቅኩት::

ደህና ነኝ ብሎ ራሱን እያሻሸ ይቅርታ ይሄን ነገር እንደገና ስላነሳሁት እንደሚያስከፋህ ይገባኛል ግን እውነቱን መናገር አለብኝ” አለ። ክፍሉን እየዞረ የቅርብ ቤተሰቦችህን ማግኘት አልቻልንም። ስለዚህ አሳዳጊ ቤተሰብ ልንፈልግልህ ነው።
እንደሚስማማህ ተስፋ አለኝ፡፡ ሌላ ሃሳብ አለህ?”

“አዎ!” ብየ አባቴ ከጦርነቱ በፊት በዚህ ከተማ የሚኖር አንድ አጎት እንዳለኝ ይነግረኝ እንደነበር ነገርኩት።

ስሙ ማን ነው?”

“ቶሚ ይባላል እና አባቴ አናፂ እንደሆነ ነግሮኝ ነበር” ብየ መለስኩ።

“ምንም ቃል አልገባልህም፤ ግን የቻልኩትን እሞክራለሁ።በቅርብ እንገናኛለን” ብሎ ዝም ካለ በኋላ ትከሻየን እየነካካ “ ጥሩ እየሰራህ እንደሆነ ሰምቻለሁ። በርታ”አለኝ። ለስሊ በሰጠሁት ትንሽ መረጃ አጎቴን ከትልቅ ከተማ መሐል ያገኘዋል ብየ ተስፋ
አልታጣኩበትም ነበር። ለስሊ ከሄደ በኋላ ወደ አስቴር ሄድኩ።ለአስቴር ከ ለስሊ ጋር ስለበረን ቆይታ እና አጎቴን ያገኘዋል ብየ
እንደማልጠብቅ ነገርኳት። “ አይታወቅም! ሊያገኘው ይችላል” ” አለች::

አንድ ቀን ቅዳሜ ከስዓት ይመስለኛል ከአስቴር እና መሐመድ ጋር እየተጫወትኩ እያለ ለስሊ እየሳቀ መጣ። ጉድፈቻ የሚወስደኝ ቤት አግንቶልኛል፤ ልቀላቀል ነው ብየ ገመትኩ። ከማህበረሰቡ ጋር “መቀላቀል” ይሉታል ታዳጊ ወታደር የነበሩ ልጆችን ከ ዘመዶቻቸው ወይም ከአሳዳጊዎች ጋር ሲያገናኙ።

“ምንድን ነው መልካሙ ዜና?”ለስሊ ዜናውን ለመስማት ፤ጉጉቴን ፊቴን ላይ እያነበበ ወደ በሩ ተመልሶ በሩን ከፈተው።
አንድ ረጂም ሰውየ ገባ፡፡ ከአባቴ ትንሽ ጠቆር ያለ ፈገግታው ግን ደመቅ ያለ ሰው ነበር።

“አጎትህ ነው አለ ለስሊ በኩራት።

' እንዴት ነህ ልጄ እስማየል? አለ ሰውየው:: ጎንበስ ብሎ በረጅም እጆቹ ጠበቅ አርጎ አቀፈኝ፡፡ ምን አልባት እያስመስለ ቢሆንስ ብየ አሰብኩ። ለቆኝ አለቀሰ። ሲያለቅስ እውነትም ዘመዴ
እንደሆነ አመንኩ፡፡ ምክንያቱም የእውነት ነበር ያነባው፤ በሃገራችን ባህል ወንዶች እምብዛም አያለቅሱም::

“ይህን ሁሉ ጊዜ መጥቼ ስላላየሁህ ይቅርታ አድርግልኝ:: ከዝች ቀን በፊት መጥቼ አይቼህ ቢሆን ንሮ እንዴት ደስ ይለኝ ነበር። አሁን ያለፈው አልፏል። ዛሬ መጀመር እንችላለን። ስለ አጣሃቸው ቤተሰቦችህ በጣም አዝኛለሁ መፅናናተትን እመኝልሃለሁ። በርታ። ለስሊ ሁሉንም ነግሮኛል።” ለስሊን በአክብሮት አይን እየተመለከተ ቀጠለ “ ከዚህ ጨርሰህ ስትወጣ ከእኔ ጋር መጥተህ መኖር ትችላለህ። ልጄ ነህ! ብዙ የለኝም ግን የምታድርበት ቦታ፣ምግብ እና ፍቅር እስጥሃለሁ።” አለ።

ተነስቼ አጎቴን አቀፍኩት፤ እሱም አቅፎ ግንባሬን ሳመኝ፡፡ትንሽ ዝም ብለን ከቆየን በኋላ “ብዙ መቆየት አልችልም ከከተማ
ውጭ የጀመርኩት ስራ አለ። ለጊዜው ቅዳሜ እና እሁድ እየመጣሁ እጠይቅሃለሁ። አንተም ስትችል አንድ ቀን መጥተህ ቤቴን ታያልኛለህ:: ልጆቼን እና ባለቤቴን ቤተሰቦችህን ትተዋወቃለህ” አለ፡፡

“ጋሼ ከዚህ በኋላ ስለዚህ ልጅ ደህንነት እነግርዎታለን” አለ ለስሊ።

አመሰግናለሁ” አለ አጎቴ።

አጎቴ ስንሸኘው አባትህን ነው የምትመስለው ፤አስተዳደጋችንን አስታወስከኝ። እንደ አባትህ አስቸጋሪ
እንደማትሆን ግን ተስፋ አለኝ” አለ እየሳቀ። እኔም ሳቅኩ።

ስንመለስ አስቴር የቦብ ማርሌን ሙዚቃ ከፈተች እና አብረን ማዜም ጀመርን። “Three Little Birds” ሶስት ትናንሽ ወፎች “Dont Woy about a thing” ስለ ምንም ነገር አትጨነቅ
"Cause every little thing gonna be all right...."
ምክንያቱም ሁሉም መልካም ይሆናል

አጎቴን ስለማግኘቴ ለ አል ሃጂ እና ማቡ ልነግራቸው ፈለኩ ግን እነሱ ቤተሰብ ስላላገኙ ተሰማኝ።

አጎቴ ቃሉን ጠብቆ ቅዳሜ እና እሁድ እየመጣ ይጠይቀኝ ጀመር። ስጦታ ያመጣልኛል፣ ስለ አስተዳደጉ ይነግረኛል ስለ አባቴም ይጠይቀኝ ነበር። አንዴ አባቴ ስለነገረኝ አንድ የልጅነት ትውስታቸው ነገርኩት። አባቴ እና አጎቴ ውሃ ለመቅዳት ወደ ወንዝ ሲወርዱ ድንገት የንብ ቀፎ ያንቀሳቅሱ እና ንቦቹ ይከተሏቸዋል። አባቴ አጭር ስለነበር አብዛኛው ንብ ከአጎቴ ራስ
ላይ ነበር፡፡ ሩጠው ወንዝ ውስጥ ቢገቡም ጠብቆ ሊለቃቸው አልቻለም:: ስለዚህ ከውሃው ወጥተው ወደ መንደር ሲሮጡ ንቦቹን ወደ ሰፈር ይዘዋቸው መጡ።

“አዎ አስታውሳለሁ፡፡ ሁሉም ሰው ንቦቹን ወደ መንደር ይዘናቸው ስለመጣን አዝኖብን ነበር። መሮጥ የማችሉትን
ሽማግሌ ሰዎች እና ትንንሽ ህፃናትን ንቡ ነድፏቸው ነበር።አባትህ እና እኔ ግን በር ዘግተን አልጋ ስር ተደብቀን በሰዉ
እንስቅ ነበር” ብሎ ሲስቅ አብሬው ሳቅኩ፡፡

አንድ ቀን አጎቴ ቤተሰቦቹን ሊያስተዋውቀኝ ወደ ቤቱ ወሰደኝ::
ፍንትው ያለ ፀሐያማ ቅዳሜ ነበር። ኒው ኢንግላንድ ቬል New England Vile ውስጥ ነው የሚኖረው፡ውብ ከተማ ነበር። ቤቱግን መብራት ሆነ የቦንቧ ውሃ የለም። ወደ ደጁ ስንጠጋ የአጎቴ
ባለቤት ወጣች:: ፊቷ ያበራ ነበር፡፡ አጥብቃ አቀፈችኝ፡፡ ለቀቀችኝ እና ካየችኝ በኋላ ጉንጨን ቆንጥጣ “ እንኳን ደህና መጣህ ልጅ አለች:: አጠር ያለች ጥቁር ፣ ክብ ፊት እና አይኖቿ ጎላ ጎላ ያሉ ሴትዮ ነበረች። አባቴ የራሱ ልጆች አልነበሩትም ግን የቤተሰብ ልጆችን እንደራሱ አድርጎ ያሳድግ ነበር፡፡ አራት ነበሩ፦ አሌ
ትልቁ ሲሆን፣ ማቲልዳ፣ ኮና እና ሶሞ ይከተላሉ፡፡ የሚሰሩትን ስራ አቁመው መጥተው ሰላም አሉኝ፡፡ “ሌላ ወንድም ማግኘት ደስ ይላል” አለ አሌ እያቀፈኝ፡፡ ከተዋወቅን በኋላ ከአክስቴ እና ከአጎቴ በስተቀር ሁሉም ወደ ስራቸው ሄዱ። አክስቴ የምግብ አይነት እያመጣች ትደረድራለች፦ ሩዝ፣ አሳ፣ ሾርባ፣ አትክልት
ሌሎች ምግቦች። ሆዴ እስከሚነፋ ድረስ ብዙ በላሁ። ከምግብ በኋላ አጎቴ የአናፂ መሳሪያዎችን እና መስሪያ ቦታውን
አስጎበኘኝ፡፡

“ አናፂ መሆን የምትፈልግ ከሆነ ረዳቴ ልትሆን ትችላለህ። ግን እንደ አባትህ ትምህርት ቤት መግባት የምትፈልግ
ይመስለኛል” ሲል ፈገግ አልኩ። አሌ ተመልሶ መጣና አጎቴን ከእኔ ከእሱ ጋር ኳስ እንዲጫወት ፍቃድ ጠየቀ፡፡ አጎቴም እሱ ከፈለገ እሽ አለ፡፡ እኔ እና አሌ ተያይዘን ብሮክፊልድስ Brookfields ወደ ሚባል አካባቢ ሄድን።

“ወደ እኛ ስለመጣህ ደስ ብሎኛል:: የእኔን ክፍል መጋራት እንችላለን” አለኝ፡፡ በእድሜ ከእኔ ይበልጠኛል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱንም አጠናቋል። ደስተኛ ፣ ስርዓት ያለው እና ተናጋሪ ነው። ጨዋታው ከመጀመሩ በፊት አንዲት ቆንጆ ልጅ ወደ እኛ እጇን ታውለበልባለች። ማናት ብየ ከ መጠየቄ በፊት አሌ የአጎታችን ልጅ ናት ከመንገዱ ማዶ ከጉድ ፈቻ አሳዳጊዎቿ ጋር ነው የምትኖረው፡፡ አሚናታ ትባላለች ትተዋወቃላችሁ” አለኝ፡፡አሚናት የአባቴ ሁለተኛ ወንድም ልጅ ነች።
ኳስ ጨዋታውን እየተመለከትን የእኔ ልብ ግን የነበረው ይኖራል ብየ አስቤው የማላውቀው ቤተሰብ መገኘት ላይ ነበረ።
ደስተኛ ነበርኩ። ስንመለስ አጎቴ ወደ ማዕከሉ ሊመልሰኝ እየጠበቀኝ ነበር። እጄን ይዞ አውቶብስ ጣቢያው እስከምንደርስ ድረስ ምንም አላልኩም:: አውቶብስ ጣቢያው ስንደርስ ሌላ ጊዜ
በእራስህ ልትጎበኘን ከፈለክ ብሎ ገንዘብ ሰጠኝ፡፡

ከሁለት ሳምንት በፊት ለስሊ ወደ ማህበረሰቡ እንደምቀላቀል ነግሮኝ ነበር፡፡ ከአጎቴ ጋር ነው የምኖረው ሁለቱ
ሳምንቶች ቤኒን ቤት ካሳለፍኩት
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አስራ_ስምንት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው

....ብዙ የጦርነት ታሪክ እያዳመጡ መኖር
ይከብዳል። እኔ የራሴ አንድ አስቸጋሪ፣ አስጨናቂ እና በየ ጊዜው የሚጎዳ ታሪክ አለኝ፡፡ ለምንድን ነው ግን እሷ ይህን የምትሰሪው? ለምንድን ነው ግን እነሱ ይሄን የሚሰሩት? በየፊናችን የሄድን ይመስለኛል። ለመጨረሻ ጊዜ ያየኋት ጊዜ ነው። እወዳታለሁ ግን አልነገርኳትም::

አጎቴ በእጆቹ አንስቶ መኪና ውስጥ አስገባኝ፡፡ “ እንደ አለቃ (ሊቀ መንበር) ነው የምቀበልህ። አለቅነትህ ዛሬ ይጀምራል” አለኝ። አራቱ የአጎቶቼ ልጆች አሌ እና ሶስቱ ሴቶች ማቲልዳ፣
ኮና እና ሶሞ ተራ በተራ እያቀፉ ሳሙኝ። ፊታቸው በፈገግታ በራ። “እርቦሃል አይደል፤ እንኳን ደህና መጣህ በማለት ቆንጆ ዶሮ ወጥ ሰርቼለሁ” አክስቴ፡፡ እውነትም ቆንጆ ነበር። ታፋጭ!
እጄን እየላስኩ ነበር፡፡ ከምግብ በኋላ ምኝታ ቤቱን አሌ አሳየኝ።መሬት ላይ ነበረ ምተኛው። ምንጣፍ፣ አንሶላ እና ብርድ ልብስ የት እንዳለ አሳየኝ፡፡ ወደ ደጃፍ ስወጣ አጎቴ ከተማውን ታውቀዋለህ?” ብሎ ጠየቀኝ፡፡ “ብዙም አለመድኩትም” አልኩ።

“አሌ ያስጎበኝሃል። ካልሆነ ደግሞ በራስህ እየጠፋህ እየተገኘህ ልታጠናው ትችላለህ። ከተማው ለማውቅ ጥሩ ነው::”

ከአጎቴ ጋር መኖር ከጀመርኩ ከአንድ ወይም ሁለት ቀናት በኋላ አሌ ሸሚዝ፣ ቀበቶ እና ከሙሉ ልብስ ጋር የሚለበስ ጫማ ሰጠኝ:: “ ጨዋ መሆን ከፈለክ እንደ ጨዋ ልበስ” ብሎ ሳቀና ቀጠለ፡፡ “ሚስጥር ነው:: ዛሬ ማታ ጭፈራ ቤት ልወስድህ እፈልጋለሁ:: ትንሽ ዘና ትላለህ:: አጎቴ ወደ ምኝታ ከሄደ በኋላ
እንወጣለን::”

ማታ ከቤት ሾልከን ወደ መጠጥ ቤት ሄድን። ከአሌ ጋር ስንሄድ ትምህርት ቤት እያለሁ የሄድኩባቸው የጭፈራ ምሽቶች
ትዝ አሉኝ፡፡ ረጂም ጊዜ ነው ግን የጭፈራ ምሽቶቹ ስያሜዎችን አይረሱኝም፡፡ Back to School” ወደ ትምህርት ቤት
እንመለስ፣ “Pens down” ብዕራችንን እንጣል፣ “Bob Marley Night የቦብ ማርሌ ምሽት እና ሌሎችም ነበሩ። አውራ ዶሮ እስከሚጮህ ድረስ እንጨፍር ነበር። ያኔ በጣም ደስተኛ ነበርኩ።

“ደርሰናል” አለ አሌ። ብዙ ወጣቶች ወደ ጭፈራ ቤቱ ለመግባት ሰልፍ ይዘው ነበር፡፡ ወንዶቹ በደንብ የተተኮስ ሱሪ
እና ሸሚዝ ለብሰዋል፡፡ ሴቶቹ ደግሞ ቆንጆ አበባ ቀሚስ ከረጂም ተረከዝ ጫማ ለብሰው ከአንዳንድ ወንዶች በላይ ረዝመው ይታዩ ነበር። ከንፈሮቻቸውን ደማቅ ቀለም ተቀብተዋል። አሌ ደስተኛ
ሁኖ ከሰልፉ ፊት ካሉት ሰዎች ጋር ያወራ ነበር። ስንገባ ሙዚቃ እስከአንቃሩ ተከፍቶ ነበር። አሌን ተከትየ ጠረጴዛ አግንተን አንድ ከፍ ያለ ወንበር ላይ ተቀመጥን።

“ ወደ ዳንስ መድረኩ ልሄድ ነው” ብሎ ተነሳ፡፡ ብዙም ሳይቆይ በህዝቡ መሐል ተሰወረ። ለደቂቃዎች ሳስብ ከዛ ብቻየን ስደንስ ከቆየሁ በኋላ ድንገት አንድ በጣም ጥቁር ሴት አንስታ ወደ ዳንስ
መድረኩ መራችኝ። አብረን ከምቱ ጋር መደነስ ጀመርን።በሙዚቃው መሐል አንድ ከእኔ ተለቅ ያለ ልጅ ጎትቶ ወሰዳት።

“ አማላይ ነህ አየሁህ እኮ” አለ አሌ ከአጠገቤ ቁሞ። እየሳቀ ነበር። እኔ ምንም አላረኩም:: ከእኔ ጋር መደነስ ፈልጋ ነው።አልኩ

እውነት ምንም ሳትል ሴቶች ወደ አንተ ይመጣሉ” ብሎ ቀለደ፡፡ ለሊቱን ሙሉ ደነሰን አጎቴ ከመንቃቱ በፊት ተመለስን።

ከተወሰኑ ምሽቶች በኋላ ብቻየን ወደ መጠጥ ቤቱ ሂጂ ልጂቱን አገኘኋት። ስሟ ዘይናብ እንደሆነ ነገረችኝ፡፡

“ባለፈው ስለሆነው ነገር ይቅርታ አድርግልኝ” አለች።ወንድሜ ወደ ቤት መሄድ ፈልጎ ነው እና ከእሱ ጋር መሄድ
ነበረብኝ፡፡ ካልሆነ ወላጆቼ ይጨነቃሉ።”

ልክ እንደ እኔ እሷም ብቻዋን ነበረች።

ለሶስት ሳምንታት ያህል አብረን ከቆየን በኋላ ብዙ ጥያቄ መጠየቅ ጀመረች፡፡ ከየት እንደመጣሁ? ክፍለ ሃገር ማደግ
እንዴት እንደሆነ? ክፍለ ሃገር ብዙ የፍሪ ታውን ሰው የሚጠቀምበት ቃል ሲሆን ገጠሬነትን ከኋላ ቀርነት እና ስርዓት
ማጣት ጋር አያይዞ ይገልፃል። ምንም ልነግራት አልፈለኩም ስለዚህ ተወችኝ። በቃ ከ ፍሪታውን ሴቶች ጋር የነበረኝ የፍቅር ታሪክ ይሄው ነው። ስለ እኔ ማወቅ ይፈልጋሉ እኔ ደግሞ ታሪኬን ለመንገር ዝግጁ አልነበርኩም። ምንም አይደል። ብቻየን መሆኔን ወድጀዋለሁ።

ለስሊ ሊያየኝ መጣ፡፡ እንዴት እንደሆንኩ እና ምን እየሰራሁ እንደሆነ ጠየቀኝ፡፡ ከትንሽ የራስ ምታት በስተቀር ደህና
እንደሆንኩ ነገርኩት። ማስታወሻ ደብተር ነገር አውጥቶ ፃፈ። “አንድ ስራ አለ ላንተ: በጣም አስፈላጊ ነው::”

ሁሌም የመልካም ዜና አብሳሪ ነህ” አልኩት።

“ ጠቃሚ ነው:: ሁለት ልጆችን ወደ ተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኒው ዮርክ አሜሪካ በመላክ የህፃናት ህይወት
በሴራሊዮን ምን እንደሚመስል ለማስረዳት ታስቧል። ስለዚህ
ቃለ መጠይቅ እየተደረገ ነው:: አቶ ካማራ አንተ ቃለ መጠይቅ እንድታደርግ ጠቁመው ነበር። ከፈለክ ይሄ አድራሻው ነው።አለና ሲፅፍበት የነበረውን ወረቀት ከማስታወሻው ገንጥሎ ሰጠኝ፡፡ “አብሬህ እንድሄድ ከፈለክ ቢሮ ና። ለቃለ መጠይቁ

የሚመጥን ልብስ ለብሰህ ና እሺ” ብሎ ሄደ::

የቃለ መጠይቁ ቀን ሲደርስ ግን እንደነገሩ የ አዘቦት ልብስ ለበስኩ። ስኒከርስ ፣ ጂንስ ሱሪ እና ረጅም እጅጌ ቲ ሸርት ለብሼ ሄድኩ። ለማንም የት እንደምሄድ አልተናገርኩም። ለአሌ
ልነግረው አሰብኩ ግን መናገር ከጀመርኩ ስለ ራሴ ከሚያውቀው አጎቴም ከነገረው በላይ ልነግረው ስለምችል ብየ ፈርቼ
ተውኩት።

ጠያቂው አትኩሮ ተመለከትኝ እና ቀስ ብሎ በእንግሊዝኛ

“ስምህ ማነው” ብሎ ጠየቀኝ።

“እስማየል” አልኩ።

ለምን አንተ ወደ ተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሂዶ በዚህ ሃገር ስላሉ ህፃናት ችግሮች ለመናገር ትክክለኛው ሰው ነኝ ብለህ ታስባለህ?”

“ከክፍለ ሃገር ነው የመጣሁት:: በጦርነቱ የተጎዳ ብቻ ሳይሆን በጦርነቱ የተሳተፍኩ እና በህፃናት ማገገሚ ያለፍኩ ነኝ፡፡ በቃለ
መጠየቁ ከተሳተፉት የከተማ ልጆች በላይ የተሻለ ግንዛቤ አለኝ፡፡ እኔ አልፌበታለሁ። እነሱ ግን እዛ ሄደው ምን ሊሉ ይችላሉ? ከዜና የበለጠ ምንም የሚያውቁት ነገር የለም::” ፈገግ ብሎ
የሚያየኝ ጠያቂ ትንሽ አበሳጭቶኛል።

“ሌላስ ምን ትላለህ?” ብሎ ጠየቀኝ፡፡

“ምንም! ለምንድን ነው ምትስቅብኝ?” ብየ መልሼ ጠየቁኩት::

“አሁን መሄድ ትችላለህ” አለ ሰውየው አሁንም እየሳቀ።

ተነስቼ ወጣሁ። በኋላየ በሩ እንደተከፈተ ትቼው ወደ አሳንሰሩ ሄጄ ቆምኩ አልተከፈተም። ለቃለ መጠየቁ የመጡት
ልጆች ሳቁብኝ። ትንሽ ቆይቶ አንድ ሰው መጣና ግድግዳው ላይ ቁልፍ ተጭኖ ከፈተልኝ፡፡ ቁጥር ተጫነልኝ እና እጁን
በማውለብለብ ተሰናበተኝ፡፡ አሳንሰሩ መንቀሳቀስ ሲጀምር የምይዘው አጣሁ ወዲያው ግን ከወለል ደረስኩ። ከህንጻው
ወጥቼ ቅርጹን መመርመር ጀመርኩ። ለመሐመድ አግኝቼ ልነግረው ጓጓሁ።

ቀስ ብየ የሚያልፉትን መኪናዎች እያየሁ መጓዝ ጀመርኩ፡፡ብዙ መኪናዎች፣ የጦር መኪና እና የሃገሪቱን ባንዴራ እላያቸው
ላይ ያደረጉ መርሰዲስ መኪኖች ተከታትለዉ በፍጥነት አለፉ።ቤት ስደርስ በብዙ መኪኖች ታጂቦ የሚልፈው የተከበረ ሰው ማነው ብየ አሌን ጠየቁኩት። ቲጃን ከባህን ይባላል። አዲሱ ፕሬዝደንት ነው አለኝ፡፡ የሴራ ሊዮን ህዝቦች ፓርቲ የሚባለው ፓርቲው ግንቦት 1996 ምርጫ አሸንፎ ሃገሪቱን ከ ሰምንት
ወራት በፊት ጀምሮ እየመራ እንደሆነ ነገረኝ።

አንድ ጥዋት አቶ ካማራ ወደ አጎቴ ቤት መጣ። ከቀናቶች በፊት
👍2
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው


አክስቴን ተሰናብቼ መኪና ውስጥ ዘልዬ ገባሁ እና የይለፍ ወረቀት (ፓስፖርት) ለማግኘት በረርን፡፡ የከተማው ሰው ሁሉ
ፓስፖርት አውጥቶ ከሃገር ለመኮብለል የወሰነ ይመስላል። ብዙ ሰው ነበር። አቶ ካማራ ግን ቀጠሮ ስላስያዘ ገብተን ፎቶ፣
አስፈላጊ መረጃዎችን አስገባን እና ክፍያ ፈፅምን። ፓስፖርቱ ከአራት ቀን በኋላ እንደሚደርስ ለአቶ ካማራ ነገሩት።

“የመጀመሪያው ደረጃ ተጠናቋል፤ አሁን ቪዛ ማግኘት አለብን።” አለ አቶ ካማራ ከዛም ከፓስፖርት ቢሮ ወጣን፡፡

ማታ ቤት ስመለስ አጎቴ ቤት ነበር ሰላምታ ስሰጠው ፈገግ ብሎ
“ምን እየተካሄደ እንደሆነ ልትነግረኝ ትችላለህ” አለ። በዝርዝር ኒው ዮርክ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሂጄ ስለ ጦርነቱ እና በህፃናት ላይ ስለ ሚያደርሰው ተፅዕኖ ንግግር ላደርግ
እንደሆነ ነገርኩት። አጎቴ ብዙም አላመነም። “ሰዎች ብዙ ጊዜ
እንደዚህ አይነት ተስፋ እየስጡ ሌሎችን ያታልላሉ። ልጄ ተጠንቀቅ! ተስፋህን ሙሉ በሙሉ በእሱ ላይ ብቻ እንዳትጥል!”
አለኝ::

ጥዋት ወደ ስራ ከመሄዱ በፊት “የአሜሪካው ጉዞ ዘግጅት እንዴት ነው?!”ብሎ ይቀልዳል።
አቶ ካማራ ገበያ ይዞኝ ሄደና የልብስ ሻንጣ እና የተለያዩ አይነቶች ልብሶች፦ ረጂም እጅጌ ሸሚዝ፣ ጨርቅ ሱሪ እና ባህላዊ ልብሶች ገዛልኝ፡፡ ለአጎቴ አሳየሁት ግን ትሄዳለህ ብሎ ሊያምን
አልቻለም:: “ትንሽ ቀየር ብትል፤ ቢያምርብህ ብለው ነው” ብሎ
ይቀልድብኛል።

አንዳንዴ አጎቴ እና እኔ ከስራ በኋላ ዘወር ዘወር እንላለን። እንደት እንደሆንኩ
ይጠይቀኛል። ደህና እንደሆንኩ
እነግረዋለሁ። ረጂም እጆቹን ትክሻዬ ላይ ያደርግ እና ወደ እሱ ያስጠጋኛል። አንዳንድ ነገሮችን ልነግረው ፈልጌ ቃላቶችን እንዳጣሁ የሚውቅ ይመስለኛል፡፡ እንደዛ ነው ሚሰማኝ፡፡ ከአጎቴ ልጆች ጋር ወደ ጫካ ሂደን እንጨት ስንለቅም አዕምሮዬ ባለፈው
ያየሁት እና የተሰራው በማስታወስ ይዋዥ ቃል።

ሰኞ ጥዋት ዶ/ር ታምባ የተባለ ሰው በአሜሪካን ኢምባሲ እንዳገኘው ተነግሮኛል። ወደ ኢምባሲው ሲሄድ የከተማው ቀስ በቀስ መንቃት ይሰማኝ ነበር። በከተማው ሙሉ የሚሰማው
ማህል ከተማ ያለው የመስጊድ የጸሎት ጥሪ፣ የአዟሪዎች የግዙኝ ተማፅኖ፣ የመኪና ረዳቶች ጥሪ “ሉምሌ፣ሉምሌ” ወይም ኮንጎ ሰፈር። በጣም በጥዋቱ ብደርስም ብዙ ሰዎች ኢምባሲ በር ላይ
ተሰልፈዋል። ፊታቸው የተቆጣ ሰው ይመስላል። ፍርድ ትሞታለህ ወይም ትኖራለህ የሚል ፍርድ የሚጠብቁ ነው
ሚመስሉት፡፡ ምን እንደማደርግ አላውቅም ነበር። ዝም በዬ ሰልፉን ጠብቄ ተሰለፍኩ። ከአንድ ስዓት በኋላ ዶ/ር ታምባ ከአንድ ልጅ ጋር መጣ እና እንድከተለው ጠየቀኝ። ልጁም ቀድሞ
ወታደር እራሱን አስተዋወቀ “ቤህ እባላለሁ። አብረን ስለምንሄድ ደስ ብሎኛል” ብሎ እጄን ጨበጠ። የአጎቴ መልስ ትዝ አለኝ ልጄ ተጠንቀቅ! ተስፋህን ሙሉ በሙሉ በእሱ ላይ ብቻ እንዳትጥል”

ከሚያማምሩ መቀመጫዎች ላይ ተቀመጥን ቃለ መጠየቁን መጠባበቅ ጀመርን፡፡ አንድ ነጭ ሴትዮ በግልፅ መስታውት ጀርባ ቁማ በድምፅ ማጉያ “
ለምን አላማ ነበር ወደ አሜሪካ የምትጓዘው?” ብላ ጠየቀች፡፡

የእኛ ተራ ሲደርስ ከመስታውቱ ጀርባ ያለችው ሴትዮ ፓስፖርታችንን ይዛ ነበር፡፡ ወደ እኔ አላየችም ይልቅ የፓስፖርቴን ገጾች ትገልጥ ነበር። መስኮቱ ለምን እንደዚህ የሰው ንክኪ እንዳይኖር ታስቦ እንደተሰራ ገረሞኝ እመለከት ነበር።

“በድምፅ ማጉያ ተናገር” አለች እና “ለምን አላማ ነበር ወደ አሜሪካ የምትጓዘው?” ብላ ጥያቄዋን ጀመረች::
“በህፃናት ላይ ስለ ሚያደርሰው ተፅዕኖ” ብየ ገለጸኩ::
“ጉባኤው የት ነበር?”
“ተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኒው ዮርክ ከተማ
“ወደ ትውልድ ሃገርህ ለመመለስህ ዋስትናህ ምንድን ነው?እያሰብኩ ነበር “ንብረት አለህ፣ መመለስህን ሊያረጋግጥ
የሚችል የባንክ ተቀማጪስ አለህ?”
ተናደድኩ። በዚህ ሃገር ስላለው የህዝብ ኑሮ የምታውቂው ነገር አለ? ብዬ ልጠይቃት አስብኩ። ቀና ብላ ብታየኝ ኖሮ ይሄን ጥያቄ አትጠይቅም ነበር። በእኔ እድሜ ያለ ማንኛውም የሃገሬው ሰው የባንክ ሂሳብ መኖር አይደለም እስከ ጪራሹ ህልሙም የለውም:: ዶ/ር ታምባ በጦርነት የተጎዱ ህጻናት ተራድኦ
ድርጅት ሊቀ መንበር እንደሆነ እና አብሮን እንደሚሄድ፣ጉባኤው ሲያልቅ ወደ ሴራሊዮን እንደሚመልሰን አስረዳት።
ሴትዮዋ የመጨረሻ ጥያቄ ጠየቀች: “ አሜሪካ የሚኖር የምታውቀው ሰው አለ?”

“ማንም የለም። ከዚህ ሃገር ወጥቼ አላውቅም እንዳውም በዚህ ከተማ እንኳ የመጀመሪያየ ነው” አልኩ። ፓስፖርቴን
ዘግታ ነጥላ አስቀመጠችው።

ውጭ ዶ/ር ታምባ ቪዛ እንዳገኘን እና ፓስፖርታችንን ነገ እንደሚወስድ ነገረን፡፡ በመጨረሻ መንገደኛ መምስል ጀመርኩ፡፡
በቀኝ እጄ ሻንጣየን ይዣለሁ ፤ ቡናማ ባህላዊ ሱሪ እና ሽሚዝ ለብሼ ነበር። ከአሌ ክፍል ስወጣ አጎቴ ደጃፍ ላይ ተቀምጦ ነበር።

“ወደ አየር መንገድ እየሄድኩ ነው” አልኩ ፈገግ ብዬ፡ አጎቴ እንደሚቀልድብኝ አውቅ ነበር፡፡አዎ! አሜሪካ ስትደርስ ደውልልኝ፡፡ አይ መች ስልክ አለኝ፡፡በል በአሚናታ ቤት ደውልልኝ መጥታ ታገኘኛለች” ብሎ አጎቴ
ፈገግ አለ።

“እሽ እደውላለሁ” ብየ በፈገግታ መለስኩ።

“ልጆች ኑ ወንድማችሁን ተሰናበቱት። የት እየሄደ እንደሆነ አላውቅም ግን ይቅናህ እንበለው” አለ አጎቴ። ማቲልዳ፣ ኮና እና
ሶሞ ባልዲ እንደያዙ ወደ ደጃፍ መጡ። ውሃ ሊቀዱ ሊሄዱ ነበር፡፡ አቀፉኝ እና በመንገዴ እንዲቀናኝ ተመኙ። አክስቴ ጪስ ጪስ እንደሸተተች ከኩሽና ቤት መጥታ አቀፈችኝ። “ የትም ብትሄድ ቤትህን ጠረን መሽተት አለብህ። ይሄ ላንተ የምሰጥህ ሽቶየ ነው”አለች በፈገግታ:: አጎቴ ተነስቶ አቀፈኝ እጆቹን ትክሻየ ላይ አድርጎ “መልካም ምኞቴ ካንተ ጋር ነው። በኋላ ለእራት እጠብቅሃለሁ” ብሎ ወደ ደጃፍ ወጣ፡፡

ስለ ኒው ዮርክ ያለኝ አመለካከት የሚመነጨው ከራፕ ሙዚቃዎች ነበር። ሰዎች መንገድ ላይ የሚታኮሱበት እና ምንም እንዳልተፈጠረ የሚመስሉበት፣
ማንም የማይጓዝበት ይልቅ በስፖርት መኪኖች ለጭፈራ እና ለሁከት የሚሄድበት ቦታ አድርጌ ነበር በአዕምሮዬ የሳልኩት። እንደዚህ አይነት የእብድ ቦታ መገኘት አልፈልግም። ሃገር ቤት በቅቶኛል::

ጆን ኤፍ ኬኔዲ አለም አቀፍ አየር ማረፍያ ስንደርስ ጨልሞ ነበር። 4፡30 ነበር። ዶር ታምባን ለምን በጠዋት እንደጨለመ
ጠየቅኩት።” (Winter ) በጋ ስለሆነ” አለኝ። “አሃ”ብየ ራሴን ነቀነቅኩ ግን በጠዋት መጨለም የሚለው ነገር ሊገባኝ
አልቻለም:: Winter ዊንተር የሚለውን ቃል በሼክስፔየር ጹሑፎች አውቀዋለሁ ግን ትርጉሙን እንደገና ማየት ያለብኝ
ይመስለኛል።

ዶ/ር ታምባ ፓስፖርታችንን ይዞ ሄደ እና ከኢምግሬሽን ሰዎች ሁሉንም ነገር አስረድቶ አለፈ። ሻንጣችንን አገኘን ወደ
ተንሸራታች በሮች አመራን። ዶ/ር ታምባ ውጭ ነበር። ባህ እና እኔ በተንሸራታች በሩ ስናልፍ በጣም ቀዝቃዛ ንፋስ ተቀበለን።ቆዳየ ሲኮማተር ይሰማኛል፣ ፊቴ ሊሰማኝ አልቻለም፣ እና ጆሮዬ
ተቆርጦ የወደቀ ይመስላል፣ እጣቶቼን አመመኝ ጥርሴም ተንቀጠቀጠ። ንፋሱ በሱሪየ እና ሸሚዜ አልፎ ገብቷል፤ ምንም
የለበስኩ አልመስለኝ አለ፡እየተንቀጠቀጥኩ ነበር። በህይወቴ
እንደዚህ በርዶኝ አያውቅም። ሰው እንዴት ነው ከዚህ ሃገር የሚኖረው? ብዬ አሰብኩ፡፡ ዶ/ር ታምባ ታክሲ ይዞ እኔ እና ባህን አስገባን እና ለሹፌሩ ወረቀት ላይ እያነበበ ወደ የት መሄድ እንደሚፈልግ
👍2
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_ሀያ

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው

...በቀጣዩ ቀን ጠዋት አንድ ደረጃ ወርዶ ወደ ሚገኘው ካፍቴሪያ ሄድኩ። ከሃያ ሶስት ሃገራት የተወጣጡ ሃምሳ ሰባት ህጻናት ቁርስ ሊበሉ እና የተባበሩት መንግስታት የመጀመሪያ አለም
አቀፍ የህጻናት ፓርላማን ለማስጀመር እየተጠባበቁ ነበር::ከሊባኖስ፣ ካምቦዲያ፣ ኮሶቮ፣ ብራዚል፣ ኖርዌይ፣ የመን፣ሞዛምቢክ፣ ፍልስጤም (ፓላስታይን)፣ ጓቲማላ፣ አሜሪካ (ኒው
ዮርክ)፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ፔሩ፣ ሰሜን አየር ላንድ፣ ህንድ፣ ፓፕዋ ኒው ጊኒ፣ ማላዊ እና ሌሎች ሃገራት የተውጣጡ ህጻናት ነበሩ።ባህ እና ዶ/ር ታምባን እየፈለኩ እያለ አንዲት ነጭ ሴት ወደ
እኔ መጣችና እራሷን አስተዋወቀችኝ፡፡

“ክርስቲን እባላለሁ ከኖርዌይ ነው የመጣሁት” ብላ እጇን ለሰላምታ ዘረጋች::

“እስማይል ከ ሴራሊዮን” ብየ እጇን ጨበጥኳት። ወረቀት አወጣች እና ስሜን ደረቴ ላይ ለጥፋ የቁርሱን ሰልፍ
እንድቀላቀል ካደረገች በኋላ ፈገግ እያለች ወደ ሌሎች ህጻናት ሄደች፡፡ በሰልፉ የተከተልኳቸው ሁለት ታዳጊዎች ሰምቸው
በማላውቅ ባዕድ ቋንቋ ያወሩ ነበር። እነሱ የሚፈልጉትን ያውቁ ነበር፡፡ እኔ ግን ምን እንደምፈልግ ወይም የምግቦቹ ስሞች ምን እንደሚባል እውቀቱ አልነበረኝም፡፡ በቆይታየ ሙሉ ግራ ተጋብቼ ነበር። “እንደነሱ” እያልኩ አዛለሁ ወይም ሌሎች ሳህን ላይ ያየሁትን አነሳ ነበር።

ከቁርስ በኋላ ሁለት ህንጻዎች አልፈን ወደ መሰብሰቢያው ህንጻ ሄድን። አሁንም በረዶ ይዘንብ ነበር፡፡ አፍንጫዬ፣ ጆሮዬ
እና ፊቴ ከአሁን ካሁን ወደቀ ብዬ በምሰጋበት፤ በዚህ ቀፋፊ ብርድ
ባለበት ሃገር እማ መኖር የለብኝም አልኩ ለራሴ።

በመጀመሪያው ቀን ስለ እየራሳችን አወራን አንዱ ስለ አንዱ ህይወታቸውን አደጋ ላይ ጥለው ነበር ወደ ጉባኤው የመጡት።
ሌሎቹ ደግሞ ወደ ጎረቤት ሃገር መቶ ኪሎ ሜትሮችን ካቁረጡ በኋላ ነበር በረራ ማድረግ የቻሉት። በደቂቃዎች ውስጥ ክፍሉ አስቸጋሪ የልጅነት ጊዜ ያሳለፍን ታዳጊዎች ተሰበሰብንበት
መሆኑን ተረዳን፡፡ ከትውውቅ በኋላ አስተባባሪዎች ስለ ራሳቸው ነገሩን፡፡

አብዛኞቹ አስተባባሪዎች በተለያዩ ተራድኦ ድርጅቶች የሰሩ ናቸው፡፡ አንድ አጠር ያለች ፣ ረጅም ጥቁር ፀጉር እና ጎላ ጎላ
ያለ አይን ያላት ሴት ግን “ እኔ ተረት ነጋሪ ነኝ” አለችን። ስሟ ሎራ ሲም ነበር ሁኔታዋ ገርሞኝ በትኩረት አዳምጣት ነበር።
እጆቿን እየተጠቀመች እያንዳንዱን ቃል ረግጣ በአፅንኦት ትናገር ነበር፡፡ ንግግሯን ከመጨረሷ በፊት የእሷን ስልጠና
ለመውሰድ ወሰንኩ፡፡ ታሪካችንን እንዴት በሚመስጥ እና ተፅዕኖ በሚፈጥር መልኩ መናገር እንዴት እንደምንችል
አስተምራችኋለሁ አለች፡፡ ኒው ዮርክ ከተማ ተወልዳ ያደገች አንዲት ነጭ ሴት እንዴት ተረት አዋቂ እንደሆነች ገርሞኛል።

ያን ቀን ሎራ አይኗ ባህ እና እኔ ላይ አርፎ ነበር። የሳሳ ቲሸርት እና ሱሪ ለብሰን ማሞቂያው አካባቢ ኩርምት ብለን
ተቀምጠን ነበር፡፡ ብርድ አጥንታችን ሰርስሮ ሳይገባ አልቀረም፡፡አሁንም አሁንም ያንቀጠቀጠን ነበር። በምሳ እረፍት ስዓት ሎራ ወደ እኛ መጥታ
ብርድ የሚከላከል ጀኬት አላችሁ?” ብላ
ጠየቀችን።ራሳችንን እየወዘወዝን እንደሌለን ነገርናት። ምሽት
ላይ ጃኬት፣ ኮፍያ እና ጓንት ይዛልን መጣች፡፡ ደስ አለኝ። አሁን ከተማውን ዘወር ዘወር ብዬ መመልከት እችላለሁ። ከአመታት በኋላ ሎራ ጃኬቷን ልትሰጠኝ ብትል ግን አልተቀበልኩም::
የሴት ጃኬት ስለነበር! ያኔ ግን የወንድ ይሁን የሴት ጉዳይህ አልነበረም እያለች ትቀልድብኛለች።

ባህ እና እኔ ከስራ ጋር እየተቀራረብን መጣን። እንዳንዴ በጣም ልጅ ሁኜ የሰማኋቸውን ተረቶች ትነግረናለች::
ከአትላንቲክ ውቅያኖስ ባሻገር ያለች አንዲት ነጭ ሴት እንዴት የሃገሬን ብሎም የጎሳየን ወግ እና ታሪክ እንዳወቀች እንቆቅልሽ ይሆንብኝ ነበር። ከአመታት በኋላ ደግሞ እናቴ ሆነች። እጣ ፈንታ ወይስ አጋጣሚ? አንድ ተረት አዋቂ እና የወግ ባህል ካለው ማህበረሰብ የወጣ ልጅ ተረት አዋቂ የሆነች እናት በኒው
ዮርክ ሲያገኝ::

ኒው ዮርክ በገባሁ በሁለተኛው ቀን ወደ አጎቴ ደወልኩ።አሚናታ ነበር ያነሳችው። “እስማኤል ነኝ። አጎቴን ማግኘት
እችላለሁ?ብየ ጠየቅኩ።
“ላምጣቸው ከሁለት ደቂቃ በኋላ ደውል” ብላ ዘጋችው።ደውልኩ። አጎቴ ሲያነሳው “ ኒው ዮርክ ከተማ ነው ያለሁት”
አልኩት።
“እንግዲህ አምንሃለሁ።ሰሞኑን እኮ አላየሁህም።” ብሎ ፈገግ አለ፡፡ መስኮት ከፍቼ የኒው ዮርክ ን ጫጫታ አሰማሁት።
አይ ፍሪ ታውን አይመስልም፡፡ እና እንዴት ነው?” በጣም ይበርዳል” ስለው መሳቅ ጀመረ።

ምናልባት የምዕራቡ አለም አቀባበል ይሆናል። ስትመለስ ሁሉንም ነገር ትነግረኛለህ። ወደ ውጭ መውጣት ከሌለብህ አትውጣ::

እሱ ሲያወራ በቤቱ ግቢ የሚያልፈውን ኮረኮች መንገድ አስታወስኩ። የአክስቴ ሾርባ ውል አለብኝ፡፡

ጠዋት ጠዋት በረዶ የተከመረበትን መንገድ አቋርጬ ሂጄ ጉባኤውን እታደም ነበር። ችግራችንን ያሳለፍነውን ሰቆቃ
ስለ ልጆች በተለይዩ ሃገራት ያሉ ህጻናት
ስለሚገጥሟቸው ችግሮች እና መፍትሄዎቻቸው እንወያይ ነበር። ከረጅም ውይይት በኋላ ግን ፊታችን ወደፊት
የሚመጣውን ደስታ በማሰብ እና በተስፋ ይበራል፡፡ ለችግሮች መፍትሄ ስናቀርብ እና ዓለም እንዲያውቀው ስናደርግ ደግሞ ጉዳታችንን ያከምን ወደ በጎ የቀየርን ይመስላል።

በሁለተኛው ቀን ማታ የማሊው ማዱካ እና እኔ በምዕራብ በኩል በአርባ ሰባት ማዞሪያ ስንራመድ ሳናስበው ወደ ታይምስ አደባባይ እየተጠጋን ነበር። ህንጻዎችን እና የሚጣደፈውን ሰው
በማየት ተጠምደን እያለ ብዙ ብርሃን አየን፡፡ በትላልቅ እስክሪኖች የተለያዩ ማስታወቂያዎች ይቀርቡ ነበር። በምስል የተደገፈ ሙዚቃ እና ብዙ ቁጥሮችም ይዞሩ ነበር። ሁሉም በጨረፍታ
ታይቶ በፍጥነት ይቀየራል። በምናየው ነገር ተገርመን ለደቂቃዎች ገረን ቆምን :: ብርዱ እንኳን አልተሰማንም። ልብስ
ቤቶች እና ሌሎች ሱቆችን በመስኮት አፍጠን ስናይ የሚያብረቀርቁ
ህንጻዎች እና የመኪኖች ድምፅ ደግሞ ህልም እስኪመስለን ቀልባችንን ገዛ፡ ወደ ሆቴል ስንመለስ ለሌሎች ልጆች ያየነውን
ነገርናቸው:: ከዛን ቀን በኋላ ሁላችም ምሽት ምሽት ታይምስ አደባባይ እንድንሄድ ተደረገ።
ማዱካ እና እኔ ከቡድን ጉብኝት በፊት አንዳንድ ቦታዎችን ጎብኝተናል በሮክፌለር ፕላዛ የተዋበ ግዙፍ የገና ዛፍ፣የመላዕክት ቅርጻ ቅርጸ እና ብዙ ሰዎች የበረዶ ሸርተቴ ሲጫወቱ ተመልክተናል። በበረዶ ሸርተቴ ሰዎች በተደጋጋሚ እምቧለሌ ሲዞሩ ማዱካ እና እኔ ግን ሰዎች ምን እንዳስደስታቸ አልገባነም፡፡ የአለም ንግድ ማዕከልንም አይተናል፡፡ አንድ ቀን
በባቡር ስንሄድ ማዱካን “እንዴት ነው ሁሉም ሰው ዝምተኛ የሆነው” ብዬ ጠየቁኩት፡፡ ባቡሩን ዞሮ ቃኘና “ እንደ እኛ ሃገር የህዝብ ማመላለሻ አይደለም” አለ። እያንዳንዱን ነገር በአዕምሮዬ ለመያዝ እና በኋላ ለአጎቴ፣ ለአጎቴ ልጆች እና ለመሐመድ ለመንገር እታገል ነበር፡፡ ያምኑኛል ብየ አልጠበቅኩም::

በጉባኤው መጨረሻ ቀን እያንዳንዱ ህጻን ስለመጣበት ሃገር እና ስላሳለፈው ሁኔታ ንግግር እንዲያደርግ ተደረገ።
ዲፐሎማቶች እና የተለያዩ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰዎች ነበሩ። ሙሉ ልብሳቸውን ለብሰው በስርዓት ተቀምጠው በጥሞና ያዳምጡን
ነበር፡፡ ከፍሪ ታውን ይዠው የመጣሁት የተጻፈ ንግግር ቢኖርም ከልቤ ለመናገር ወሰንኩ። ስላሳለፍኩት ጊዜ እና ስላለኝ ተስፋ በአጭሩ ተናገርኩ:: ተስፋዬ ጦርነት እንደሚያበቃ ሲሆን ይሄ
👍1
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_ሀያ_አንድ

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው

አንዳንዴ ማታ ማታ ለቤተሰቦቼ መሐመድን ጨምሮ (አሁን ከእኛ ጋር ነው የሚኖረው) ስለ ጉዞዬ እነግራቸው ነበር።
ሁሉንም ነገር አስረዳቸው ነበር፡፡ አየር ማረፊያውን፣ አውሮፐላኖቹን በአውሮፐላን መስኮት አሻግሮ ደመናን ማየት የሚሰጠውን ስሜት ሳይቀር እነግራቸው ነበር፡፡ ስነግራቸው የናፍቆት ስሜት ይሰማኝ ነበር። በአምስተርዳም አየር ማረፊያ እግረኛ መንገድ ስንቀሳቀስ ብዙ ነጮች ቦርሳቸውን እየጣሉ እና በተለያየ አቅጣጫ ሲሯሯጡ ትዝ ይለኛል።
ስለተዋወቅኳቸው ሰዎች፣ ስለ ኒው ዮርክ ረጃጂም ፎቆች፣ ስለ ስስ በረዶቿ እና ሰዎች መንገድ ላይ እንዴት እንደሚሰዳደቡ ሳይቀር ነገርኳቸው።

“የሚገርም ጉዞ ነው” ይላል አጎቴ፡አንዳንዴ በእውኑ አለም የሌለ አዕምሮዬ ውስጥ ለእኔ ብቻ የተከሰተ ይመስለኝ ነበር።

መሐመድ እና እኔ በኤድዋርድ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንደገና ትምህርት ጀመርን። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ሁኜ ጠዋት ትምህርት ቤት ስሄድ ትዝ ይለኛል። የወደቁ የማንጎ ቅጠሎችን የሚጠርጉ መጥረጊያዎች ድምፅ እና የደነበሩ ወፎች ጫጫታ ታጅበን ወደ ትምህርት ቤት ስሄድ ትዝ ይለኛል።ትምህርት ቤቱ በጨቃ ጡብ እና ቆርቆሮ የተሰራ ትንሽ ህንፃ ሲኖረው ህንፃው በር አልነበረውም:: ከጥበቱ የተነሳ ሁሉንም ተማሪ መያዝ አይችልም ነበር። ብዙ ክፍለ ጊዜ ውጭ በማንጎ
ዛፍ ስር ጥላ ነበር የምንማረው:: መሐመድ በ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የነበረውን የትምህርት መሳሪያ እጥረት በደንብ ያስታውሳል። ብዙ ጊዜ ደግሞ መምህራን በእርሻ ያግዝ እንደነበር ይነግረኛል። ዘር በመዝራት፣ በመኮትኮት እና
በማጨድ ያግዝ ነበር። አብዛኞቹ መምህራን ኑሮቸውን በእርሻ ይደጉሙ ነበር። ብዙ ባወራሁት ቁጥር ብዙ ነገር እንደዘነጋሁ ማወቅ ጀምሬለሁ፡፡ ተማሪነትን ክፍል ውስጥ መቀመጥ፣
ማስታወሻ መያዝ፣ የቤት ስራ፣ ጓደኛ መያዝ እና ብሽሽቁን ሁሉ ረስቼዋለሁ ። አሁን ግን እንደገና ወደዛ ለመመለስ ጓጉቻለሁ:: በፍሪ ታውን የመጀመሪያ የትምህርት ቀን ግን ሁሉም ተማሪዎች ከእኔ እና መሐመድ እርቀው ነበር የተቀመጡት::በአንዴ የምንገድላቸው ነበር የመሰላቸው። እንዴት እንደሰሙ
ባላውቅም ታዳጊ ወታደሮች እንደነበርን አውቀዋል፡፡በጦርነቱ ልጅነታችንን ብቻ አይደለም ያጣነው ስማችንም ከዚህ ስቃይ እና መከፋትን ካተረፍንበት መጥፎ ገጠመኝ ጋር እንዲጠራ ሁኖ ጠልሽቷል።

ቀስ ብለን ነበር ቤት ምንመለሰው። ቀስ ብሎ መራመድ ለማሰብ፤ ህይወት ወደየት አቅጣጫ እየተጓዘ እንደሆነ
ለመገምገም እድል ስለሚሰጥ ደስ ይለኝ ነበር። ህይወቴ ካለፈው እንደማይብስ እርግጠኛ ነበርኩ። እሱም የመፅናኛ እና ፈገግታየ ምንጭ ነበር። ቤተሰብ የአንድ ቤተሰብ አባልነትን ገና እየተለማመድኩ ነው፡፡ ለሰዎችም መሐመድ ጓደኛየ እንደሆነ መናገር ስለ ጀመርኩ ብዙ ማብራራት አይጠበቅብኝም።
ያለፈውን ታሪኬን መርሳት እንደማልችል አውቃለሁ። ነገር ግን ስላለፈው ማውራት ማቆም እና ዛሬን በአዲስ ህይወት መኖር
እፈልጋለሁ።

እንደተለመደው በጠዋት ነበር የተነሳሁት። ተነስቼ በቤታችን ጀርባ የሚገኝ ጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ ተቀምጨ
የከተማውን መንቃት እጠብቃለሁ። ግንቦት 25, 1997 የተኩስ እሩምታ ሰማሁ።ከተማዋ ከተለመደው ድምፅ ወጥታ በተኩስ እሩምታ ደነቆረች። የተኩስ እሩምታ በሃገሪቱ የህዝብ መወሰኛ ሁሉንም ከእንቅልፍ ቀስቀስ። እኔም ደጃፍ ላይ ወደ ነበረው አጎቴ
ምክር ቤት አካባቢ ነበር የሚሰማው።የተኩስ እሩምታው
ምን እየተካሄደ እንደለ አላወቅንም። ወታደሮች ግን በፓዲባ መንገድ ሲሯሯጡ የጦር መኪኖች ሲንቀሳቀሱ አይተናል። የተኩስ እሩምታው እየጨመረ ሌሎች የከተማውን ክፍሎች እያካለለ ነበር የቀጠለው:: የከተማው አዋቂ ስዎች ደንግጠው በፍርሃት እየረዱ በራቸው
ደጃፍ ላይ ተቀምጠዋል። መሐመድ እና እኔ ተያየን። ወደሱ ተጠጋሁ።

ረፋድ ሲሆን ማዕከላዊ እስር ቤት ተከፍቶ እስረኞች ተለቀቁ። ከእስር ከመውጣታቸው በተጨማሪ አዲሱ መንግስት ለእስረኞች መሳሪያ አደለ። አንዳንዶቹ በቀጥታ ወደ ፈረዱባቸው ዳኞች እና ጠበቆች በመሄድ እነሱን እና ቤተሰቦቻቸውን ገደሉ ቤታቸውንም
አቃጠሉ፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ወታደሮች ቀድሞው የጀመሩትን ዘረፋ ተቀላቀሉ:: የሚቃጠሉ ቤቶች ጪስ አየሩን ሞልቶ ከተማዋን በጭጋግ ሸፈናት::

አንድ ሰው በሬዲዩ ወጥቶ ራሱን አዲሱ የሴራ ሊዮን ፕሬዝደንት እንደሆነ አወጀ:: ስሙ ጆኒ ፖል ኮሮማ ሲሆን የአብዮታዊ ጦር ኃይሎች ምክር ቤት መሪ እንደነበር ተናገረ። ምክር ቤቱ በዲሞክራሲያዊ ምርጫ የተመረጠውን ፕሬዝደንት
ቲጃን ከባህን ከስልጣን ለማስወገድ በጦር መኮንኖች የተመሰረተ ነበር።
የኮሮማ መፈንቅለ መንግስቱን ለማካሄድ እንዳቀረበው ምክንያት መጥፎ ነበር፡፡ ሁሉም ነገር በቁጥጥር ስር እንደሆነ እና ሁሉም ሰው ወደ ስራ እንዲወጣ ምክር ሰጠ።

ከንግግሩ ጀርባ ግን የተኩስ እሩምታ እና የተቆጡ ወታደሮች ሲሳደቡ ሲጨፍሩ ይሰማል።

ምሽት ላይ በሌላ አዋጅ አማጺዎች እና ጦሩ የሲቪሉን መንግስት “ለሃገር ጥቅም” ሲባል ለመገልበጥ እንደተቀናጁ
በሬድዮ ተነገረ። አማጺዎች እና ጦር ግንባር የነበሩ ወታደሮችከተማውን ማጥለቅለቅ ጀመሩ፡፡ ሃገሪቱ ሙሉ ለሙሉ ወደ ስርዓት አልበኝነት ገባች። እየሆነ ያለው ሁሉ አላማረኝም:: ጠላሁት ወደ ቀድሞ ህይወቴ መመለስ አልችልም:: አሁን ግን በህይወት የማመልጥ አልመስልህ አለኝ፡፡

አማጺዎች እና ወታደሮቹ የባንክ ካዝናን መስበር፣ ፈንጅ ማፈንዳት፣ ሰዎችን አስቁሞ መበርበር መዝረፍ ጀመሩ::
ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን እና የዮኒቨርሲቲ ግቢዎችን ተቆጣጠሩ። ደጅ ተቀምጦ ከመመልከት በስተቀር ምንም
የሚሰራ ነገር የለም:: አጎቴ የጀመረውን ቤት ለመጨረስ ወሰነ።በጠዋት ጀምረን እስከ ረፋድ ድረስ መስራት ጀመርን። የተኩስ እሩምታው ከቀን ቀን እየባሰ ከቤት መውጣት አስፈሪ እየሆነ መጣ፡፡ በጀምላ ብዙ ሰዎች ተገደሉ። ስለዚህ ብዙም ሳንቆይ ስራውን አቆምነው።

የታጠቁት ኃይሎች በከተማው ሱቆች እና ገበያ የሚገኘውን ምግብ በጉልበት ነጥቀው ወሰዱ። ከውጭ የሚመጣው ምግብ እና ከክፍለ ሃገር ወደ ከተማ የሚገባው ምግብ ቆሟል። ሎራ
ገንዘብ ትልክልኝ ስለነበር የቆጠብኩት ትንሽ ገንዘብ ነበረኝ ። ወደ ከተማው ወጥቼ ሩዝ፣ ደሮ፣ አሳ እና ሌሎች የታሸጉ ምግቦችን ለመግዛት ወሰንኩ፡፡ ወደ ገበያ መሄድ ግን አደጋ ነበረው። የበፊት
የጦር ሜዳ ጓደኞቼን ቢገኙኝ እና ከጦርነቱ እራሴን ማግለሌን

ቢያውቁ ይገሉኛል። ቤት መቀመጥ ደግሞ አልችልም ምግ መፈለግ ይኖርብኛል።

አንድ ድብቅ ገበያ እንዳለ እና የተለያዩ የማይገኙ የምግብ አይነቶች ለተራው ህዝብ እንደሚሸጥ ሰማን፡፡ ዋጋው ገበያ
ከመደበኛ ዋጋ ሁለት እጥፍ ቢሆንም ከአደጋ ያተርፋል።በጠዋት ማንም አንዳያየን አንገታችንን ደፍተን ወደ ገበያው
አመራን። ሩዝ፣ የወይራ ዘይት፣ ጨው፣ አሳ ገዝተን ልንወጣ ስንል መኪና እና ወታደሮች ዘለው ወረዱ። ወደ ህዝቡ
በመጠጋት የማስጠንቀቂያ ተኩስ ወደ ሰማይ ተኮሱ። በድምጸ ማጉያ አዛዡ የምግብ ዘምቢላችንን መሬት ላይ እንድናስቀምጥ እና እጃችንን ራሳችን ላይ እንድናስቀምጥ ትዕዛዝ ሰጠ።በድንጋጤ ለመሮጥ የሞከረች አንዲት ሴት ግንባሯ በጥይትተመታ:: ሁሉም ሰው ተረበሸ። እኛም ምግባችንን ይዘን ሮጥን።

ወደ ዋናው መንገድ ስንደርስ “ግድያ ይቁም” የሚል መፈክር ያነገቡ ሰልፈኞች አየን፡፡ ነጭ ቲሸርት እና ራሳቸው ላይ ነጭ
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_ሀያ_ሁለት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው

ሰዎች በፍጥነት እየሮጡ በእኛ በኩል መጡ። ከኋላ ወታደሮች ያባሯቸው ነበር፡፡ እኛም ከፊት መምራት ጀመርን። መሐመድ እና እኔ በውስጥ ለውስጥ መንገዶች ሩጠን በታጠረ መንገድ
ደረስን። ታጣቂዎች አካባቢውን ይጠብቁ ነበር። ምሽት እስኪሆን የውሃ መውረጃ ቦይ ውስጥ ለስድስት ስዓታት ተንጋላን ተኛን።

ከሞት ለመትረፍ በለሊቱ መንቀሳቀስ ሳይሻል አይቀርም ብለን ነበር እስኪመሽ ፀየቆየነው:: ከእኛ ጋር የተወሰኑ ሰዎች ነበሩ:: ሰማያዊ ቲ ሸርት ያደረገ እና ግንባሩን እያለበው በተደጋጋሚ
የሚጠርግ ተማሪ፣ በፍርሃት የምትንቀጠቀጥ በሃያዎቹ
የምትገኝ ሴት እና ቲ ሸርቱ በሌላ ሰው ደም የተጨማለቀ ፂማም ሰውየ አብረውን ነበሩ። በጣም አዝኛለሁ መጥፎ ስሜትም
ተሰምቶኛል ግን ጦርነት እንደማያቁት እንደ እነዚህ ሰዎች አልፈራሁም። አጎቴ እንዳይጨነቅ ብቻ ነበር ሃሳቤ። የፍርድ ቀንን እንደመጠበቅ ምሽቱ በጣም ራቀብን። በመጨረሻ ቀስ ብሎ
እየጨለመ ድንግግዝ ካለ ብኋላ ሙሉ ጨለማ ሆነ ምሽት ገባ።

አጎቴ አይኖቹ እንባ አዝለው ደጃፍ ተክዞ ተቀምጦ አገኘሁት። ሲያየኝ ከተቀመጠበት ዘሎ ተነስቶ አቀፈኝ። በእቅፉ ውስጥ እንዳለሁ ከዚህ በኋላ ወደ ከተማ መሄድ እንደለለብን ነገረን።
አማራጭ ግን አልነበረንም! ምግብ ለማግኘት መውጣት ነበረብን፡፡

ተኩሱ ለተከታታይ አምስት ወራት የከተማው የማጀቢያ ድምፅ እስኪመስል ቀጠለ፡፡ ጠዋት ቤተሰቦች ደጃፍ ላይ
ተቀምጠው ይመለከታሉ። ታጣቂዎቹ ሲዘረፉ፣ ሲገድሉ እና ሴቶችን ሲደፍሩ ከልካይ አጡ። በሚቃጠሉ ቤቶች የፌዝ ሲስቁ ይስማል።አንድ ምሽት ጎረቤታችን ሬዲዮ ከፍቶ መንግስትን የሚወነጅል ጣቢያ ያዳምጣል። ወዲያው ገልባጭ መኪና ሙሉ ወታደር መጣና ቤታቸው ፊት ለፊት ቆመ፡፡ ሰውየውን፣ባለቤቱን እና ልጆቹን አውጥተው ተኩሰው ገደሏቸው::

ለሶስት ሳምንታት ያህል ከቤት መውጣት ፈራን፡፡ ቆይቶ ግን ተኩሱም እብደቱም ተለመድ፡፡ ተባራሪ ጥይት ሊገድላቸው
ቢችልም ሰዎች ግን የቀን ተቀን ንሮቸውን ቀጠሉ፡፡ ህጻናት ምን እንደተተኮስ በመገመት ይጫወታሉ። AK47 G3 HPG ወይም መትረጊስ እያሉ ይገምታሉ። ከመሐመድ ጋር አለት ላይ ዝም ብለን ተቀምጠን እናስባለን። ከጦርነቱ ለማምለጥ የተጓዝነው
ረጅሙን መንገድ አስታውስኩ። ረጅም መንገድ ብንጓዝም አሁን ጦርነቱ ደርሶብናል።

ኒው ዮርክ ካለችው ሎራ ጋር ለአምስት ወራት ያህል መገናኘት አልቻልኩም። ከዛ በፊት በየጊዜው ደብዳቤ እንለዋወጥ
ነበር። ደህና እንደሆነችና ራሴን እንድጠብቅ ትነግረኛለች።ደብዳቤዎቿ ለስራ ከምትንቀሳቀስባቸው የተለያዩ ሃገሮች ነበር የሚመጡት። ልደውልላት ብፈልግም አልቻልኩም። የሴራሊዮን ቴሌ ኮም ሴራ ቴል ስራ አቁሟል። በየቀኑ የስዓት እላፊ እስከሚደርስ ደጃፍ ላይ ቁጭ ብለን ከተማውን እንመለከታለን።
ተረት ማውራት፣ ቀልድ እና መዚቃ ከቆሙ ቆይተዋል። ነገሮች ብለን ተስፋ ብናደርግም በተቃራኒው ሁኔታው
እየባሰበት ነበር የሚሄደው:: አጎቴም አመመው። በቅርብ ከሚገኘው ሱቅ ማስታገሻ ብገዛለትም ህመሙ እየበረታበት መጣ፡፡ አክስቴ ሳሊ በግድ ልታበላው ብትፈልግም ይተፋዋል።
ሁሉም ሆስፒታሎች እና መድሃኒት ቤቶች ተዘግተዋል።በከተማ የሚገኙ ዶክተሮች እና ነርሶችን ማፈላለግ ጀመርን።
አብዛኞቹ ሃገር ለቀው ተሰደዋል፡፡ ሃገር ለቀው ያልወጡት ደግሞ ከቤት ,መውጣት ይፈራሉ፡፡ አንድ ምሽት አጎቴ በሽታው ባሰበት ሰውነቱ እተንቀጠጠ እኔን ተመለከተኝ። ተስፋው ተሟጦ ማለቁ ከአይኖቹ ይታያል። ከንፈሩ የሆነ ነገር ሊናገር ተንቀጥቅጠው
ቆሙ። አጎቴ አረፈ። ደነገጥኩ። እንዴት ነው ለባለቤቱ ምነግራት?! እሷ እኮ ውሃ እያሞቀችለት ነበር። ትንሽ ቆይታ
ውሃውን ይዛ መጣች እና ከሁለታችን ላይ ለቀቀችብን። የባሏን ህልፈት ማመን አልቻለችም:: የኔ የምላቸውን ሰዎች እንዳጣሁ ነው።

ቤቱ በለቅሶ ተደባለቀ። የአጎቴ ልጆች ከእንግዲህ ማን ሊንከባከበን ነው? እንዴት በዚህ አስቸጋሪ ወቅት እንዴት ይሄ
ይሆንብናል ይሄዳል ? እያሉ ያለቅሱ ነበር።

የአጎቴ ቀብር በሚቀጥለው ቀን ተፈፀመ። አስቸጋሪ ወቅት ቢሆንም ብዙ ሰዎች በቀብሩ ቦታ ተገኙ። አክስቴ መምጣት
ብትፈልግም አልቻለችም:: ከቤት ከመውጣታችን በፊት ተዝለፍልፋ ወደቀች። በመቃብሩ ቦታ ኢማሙ ሱራ ካደረሰ በኋላ አጎቴ ግብአተ መሬቱ ተፈፀመ። ሰዎች ወዲያው ወደ ቤታቸው
ተበተኑ። መቃብሩ ጎን ተቀምጩ አጎቴን አወራሁት። አጎቴ “የሚረዳህ ሰው ስላላገኘን ይቅርታ” አልኩ። በጣም እንደምወደው እና አድጌ እንዲያየኝ እፈልግ እንደነበር እንደሚያውቅ ተስፋ
አደረኩ፡፡ እጆቼን አፈር ጨብጬ አለቀስኩ።

የአጎቴ ቀብር ከተፈፀመ ከተወሰኑ ቀኖች በኋላ ሎራን በስልክ ማግኘት ቻልኩ፡፡ ኒው ዮርክ መምጣት ከቻልኩ እሷ ቤት ማረፍ እንደምችል ጠየቅኳት፡፡ እሽ አለች።
በሃሳቤ ይታየኛል” አልኳት። ጊኒ
ጊኒ ኮናክሪ ስደርስ እንደምደውልላት ነገርኳት፡፡ ኮናክሪ የጊኒ ዋና ከተማ ስትሆን በጊዜው ጊኒ ብቸኛዋ ሰላማዊ ጎረቤት ሃገር እና ብቸዋ ከሴራ ሊዮን መውጫ በር ነበረች:: መውጣት ነበረብኝ፡፡ ከቆየሁ ተመልሼ ወታደር እሆናለሁ ወይም እምቢ ብየ የቀድሞ ጓደኞቼ ይገድሉኛል። አገግመው የነበረ አንዳንድ ጓደኞቼ እንደገና ወደ ጦር ተቀላቅለዋል።

በደረቅ ለሊት ፍሪ ታውንን ለቅቄ ወጣሁ። ከመሐመድ በስተቀር መሄዴን
ለማንም አልተናገርኩም:: አክስቴ
ከተፅናናች በኋላ የእኔን መሄድ እንደሚነግራት ከመሐመድ
ተነጋግረናል። ከባሏ ሞት በኋላ ጀርባዋን ለአለም እና በአለም ለሚኖር ሁሉ ሰጥታለች፡፡ ህዳር 1 1997 ነበር የወጣሁት።ሳይነጋ መውጣት ነበረብኝ፡፡ በለሊት መጓዙ ከ ደህንነት አንፃር
የተሻለ ነበር። ግማሾቹ ታጣቂዎች ተኝተዋል የቀሩት ወታደሮች ደግሞ በለሊት ከሩቅ ማየት ይከብዳል። የተኩስ እሩምታው ፀጥ ረጭ ባለው ከተማ ይስተጋባል። ብርድ አየር እየመታኝ የሽተተ አስክሬን እና ባሩድ እያሸተትኩ መጓዝ ጀመርኩ። ለመሐመድ ስደርስ አሳውቅሃለሁ ብየ ተጨባበጥን። ትክሻየን መታ መታ ከማድረግ ውጪ ምንም አልተናገረም::

የተወሰኑ ልብሶቼን የያዘ አንድ ትንሽ ቆሻሻ ሻንጣ ብቻ ነበር የያዝኩት:: ትልቅ እና የሚስብ ሻንጣ መያዝ ለአደጋ ያጋልጣል።
ታጣቂዎች ከፍ ያለ ዋጋ ያለው ጠቃሚ ነገር እያሸሽህ ስለሚመስላቸው ሊተኩስብህ ይችላሉ። መሐመድን ትቼ ጎህ ሳይቀድ ፈጠን ብየ መጓዜን ቀጠልኩ፡፡ ጨለማው ግን ያስፈራል።
የስልክ እንጨት ተደግፌ ተነፈስኩ። ራሴን ማበረታታት ጀመርኩ:: መውጣት አለብኝ ካልሆነ ወደ ጦሩ መመለሴ ነው።
ይሄን ማሰብ እንኳ አልፈልግም፡፡ የመኪና ድምፅ ስሰማ ቶሎ ብየ ወደ ቦይ ነገር በመግባት ተደበቅኩ፡፡ በመንገድ ላይ ብቸኛው ሲቭል እኔ ነበርኩ፡፡ የፍተሻ ጣቢያዎችን አንዳንዴ ቦይ ውስጥ
በጉልበቴ እየዳሁ ወይም በቤቶች ጀርባ ተደብቄ አለፍኩ። በሰላም ወደ አንድ አሮጌ የአውቶብስ ጣቢያ ደረስኩ። ብዙ ሰዎች ነበሩ።በሰላሳዎች የሚገኙ ወንዶች፣ ሴቶች እና ህፃናት። በአውቶብስ
ውስጥ መጨረሻ ወንበር ላይ ተቀመጥኩ። ሹፌሩ እየዞረ ሂሳብ
ከተቀበለ በኋላ ጉዞ ጀመረ፡፡ መንገዱ ለብዙ አመታት አገልግሎት ውጭ ስለነበር አውቶብሱ ከቅጠል እና ቅርንጫፍ
ጋር እየተላተመ በዱር ውስጥ የሚሄድ ነበር የሚመስለው። ጎህ እስኪቀድ ቀስ ብሎ ነበር የተጓዘው:: አንድ ቦታ ላይ ሁላችን ወርደን መኪናው አንድ ዳገት መውጣት ነበረበት፡፡ ሁላችንም
ዝም ብለን ፊታችን በፍርሃት ከብዶ ነበር፡፡ ወደ አውቶብሱ ተመልሰን ከገባን በኋላ
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_ሀያ_ሶስት(የመጨረሻ ክፍል)

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው


አስር ስዓት ሲሆን አውቶብሱ ካምቢያ ከምትባል ከተማ አደረሰን። የመጨረሻ ፌርማታው ነበር። ፍሪ ታውንን ለቀን
ከመጣን ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳፋሪዎቹ ፊት ተፈታ። ግን ብዙም አልቆየም! ድንበር ለማለፍ ክፍያ ስንጠየቅ የሁሉም ፊት መልሶ ተኮማተረ አጉረመረምን፡፡ ሁሉም ሰው ከካልሲው
ውስጥ፣ ከውስጥ ሱሪ እና ከረባት ሳይቀር የተረፈ ገንዘብ ካለ ፈለገ። ሶስት መቶ ሊዮንስ (የሴራሊዮን ገንዘብ) ነበር
የተጠየቅነው:: አንድ ሰው ከገዛ ሃገር ለቆ ለመውጣት ለምንድን ነው ሚከፍለው? አሰብኩ ግን መከራከር አልችልም:: ከፈልኩ:: የይለፍ ወረቀቱ ላይ ማህተም እንደተደረገልኝ ወዲያው ወደ ጊኒ
ደንበር ተሻገርኩ። ዋና ከተማዋ ኮናክሪ ለመድረስ ደግሞ ገና ብዙ መንገድ ይቀረኛል። ወደ ከተማው የሚወስድ አውቶብስ ለማግኘት ቶሎ ቶሎ መራመድ ጀመርኩ። ጊኒ ውስጥ የሚነገር
የትኛውንም ቋንቋ መናገር አልችልም ምን ማድረግ እንዳለብኝም አላሰብኩበትም ነበር። ትንሽ አስጨነቀኝ ግን ከሃገሬ በህይወት መውጣቴ ትልቅ ነገር ነው::
ኮናክሪ የሚሄድ አውቶብሶች የጊኒ ወታደሮች ባቆሟቸው ኬላዎች በኩል ነበር የሚቆሙት፡፡ በኬላዎቹ ተጠግተው
በፈለጉት መጠን የጊኒን ገንዘብ የሚመነዝሩ ሰዎች ነበሩ።

ወታደሮቹ ይሄን ጥቁር ገበያ የሚከላከሉ መስሎኝ ነበር ግን ግድ አይሰጣቸውም:: ገንዘቤን ቀይሬ ወደ ኬላው ተጠጋሁ። ደንበሩ ላይ ያሉ ወታደሮች ወይ እንግሊዝኛ መናገር አይችሉም ወይ
ደግሞ እንደሚችሉ ማሳወቅ አይፈልጉም:: መሳሪያቸውን ብቻ
በተጠንቀቅ ይዘዋል፡፡ ቀና ብየ ማየት አልፈለኩም። ከዚህ በፊት ወታደር እንደነበርኩ እና አሁን ግን ትቼው እሸሸሁ መሆኑን ማሳበቅ አልፈለኩም::

አውቶብሱን ለማግኘት ጥቁር ቡናማ የሆኑ የጣውላ ቤቶችን ማለፍ ነበረብኝ። ውስጥ ወታደሮች የሰዎችን ሻንጣ ይበረብራሉ።ሰዎች ደግሞ መረጃዎቻቸውን ለሃላፊዎች ያሳያሉ። የእኔ ተራ ሲደርስ ወታደሮቹ ሻንጣየን ከፍተው በውስ ጡ ያለውን ሁሉ መሬት ላይ ዘረገፉት። ብዙ እቃ ስላልነበረኝ ለመሰብሰብ እና መልሶ ለመክተት ብዙም አያስቸግርም፡፡ ሁለት ቲ ሸርት፣ ሁለት
ዉስጥ ሱሪ እና ሶስት ጥንድ ሱሪዎች ብቻ ነበሩ::

ከጣውላ ቤቱ ስወጣ መረጃዎቼን ማሳየት ነበረብኝ፡፡ ብዙ ጠረጴዛዎቹ እና ወታደሮች ደግሞ የማንጎ ዛፍ ስር ነበሩ።
መሳሪዎቻቸው ወንበራቸው ላይ ወይም የአንዳንዶቹ ጠረጴዛዎቹ ላይ ተቀምጦ ነበር፡፡ ለማን ማሳየት እንዳለብኝ
አላውቅም::

አንድ ወታደር ወደ እሱ እንደሄድ ምልክት አሳየኝ። እጁን ዘረጋ እና የይለፍ ወረቀቴን ተቀበለኝ። ወታደሩ በማይገባኝ አንድ
ቋንቋ ተናገረ።የይለፍ ወረቀቴን የደረት ኪሱ ውስጥ አስገባው እና እጁን ጠረጴዛ አድርጎ አትኩሮ ተመለከተኝ። አቀረቀርኩ
ወታደሩ አገጩን ቀና አደረገኝ፡፡ የይለፍ ወረቀቴን ከኪሱ አውጥቶ መረመረ። አይኑ ቀላ ፊቱ ላይ ፈገግታ ይታይ ነበር።
እጁን አጥፎ ተደላድሎ ተቀመጠ። ፈገግ አልኩ እሱም ሳቀ።በቋንቋው የሆነ ነገር አለና እጁን እንደገና ጠረጴዛው ላይ አደረገ።ፈገግታው እየጠፋ ሄደ፡፡ የተወሰነ ገንዘብ እጁ ላይ አስቀመጥኩ።
የይለፍ ወረቀቴን ከኪሱ አውጥቶ ሰጠኝ እና በሩ እንዳልፍ ጠቆመኝ፡፡

ብዙ አውቶብሶች ስለነበሩ ወደ ኮናክሪ ለመሄድ አውቶብስ መያዝ እንዳለብኝ አላውቅም ግራ ገባኝ፡፡ ሰዎችን ለመጠየቅ ብሞክርም ማንም ሊረዳኝ አልቻለም:: የማውቀው ፈረንሳይኛ
ቃል bonjour ቦንጁር ብቻ ነበር፡፡

ግራ ገብቶኝ ቁሜያለሁ አንድ አልፎ ሂያጅ በኪሮ ቋንቋ ሲያጉረመርም ሰማሁትና “ ጤና ይስጥልኝ” ብየ ወደ ኮናክሪ
የሚወስደው አውቶብስ የትኛው እንደሆነ ጠየቅኩት። እሱም ወደ ዛው እንደሚጓዝ ነገረኝ እና ወደ ከአፍ እስከ ገደፉ ጢም
ብሎ የሞላ አውቶብስ ውስጥ ገባን፡፡ በየ ሃምሳ ሜትሩ ወደ አስራ አምስት የሚጠጉ ኬላዎች ላይ ወታደሮች ነበሩ እና ወታደሮቹ ምህረት የለሽ ነበሩ። ወታደሮቹ መክፈል የማችሉትን እየደበደቡ
ከአውቶብሱ ያወርዷቸዋል። እኔ ግን እድለኛ ነበርኩ። ከአጠገቤ የነበረው ሰውየ ልጅ ስለመሰልኳቸው ብዙ ኬላዎችን በነፃ አልፌያለሁ። የእሱን መረጃ ያያሉ እና የሁለታችንንም እሱን
ያስከፍላሉ፡፡ ሰውየው የገባው አይመስለኝም:: ገንዘብ ጉዳዩ አይደለም ኮናክሪ መግባት ብቻ ነበር የሚፈልገው:: የመግቢያ ክፍያው ሶስት መቶ ሊዮንስ እንደሆነ ሰዎች ሲያወሩ ሰማሁ።
መቶ ሊዮንስ ብቻ ነበር የቀረኝ፡፡ ምንድን ነው ማደርገው? ብየ ማሰብ ጀመርኩ። ይሄ ሁሉ መንገድ የመጣሁት ለከንቱ ነው? ወደ ፍሪ ታውን መመለስ እንኳ ብፈልግ የምመለስበት ገንዘብ የለኝም:: አይኖቼ እንባ አቀረሩ። ተረበሽኩ ከዚህ መውጫ መንገዱ አልታይህ አለኝ፡፡ አንድ የይለፍ ወረቀቱ የተመታለት ሰው ከኬላ ወደ አውቶብስ ሲመለስ ሻንጣውን ጥሎ አየሁ። የተወሰነ ካመነታሁ በኋላ እድሉን ልጠቀምበት ወሰንኩ። ሰልፉን ትቼ ሻንጣውን ይዤ ተከልኩት:: አውቶብስ ውስጥ ገብቼ መጨረሻ ወንበር ላይ ተደብቄ ተቀመጥኩ። አውቶብሱ ቀስ ብሎ ከወጣ በኋላ ፍጥነቱን ጨመረ። በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሃገሪቱ
ገባሁ በኋላ ግን ችግር ይሆናል፡፡

አውቶብሱ ወደ ኮናክሪ ሲደርስ መጨነቅ ጀመርኩ። ከደረስኩ በኋላ ምን እንደማደርግ አላውቅም:: የሴራሊዮን አምባሳደር ስደተኞች በጊዜዊነት ግቢው ውስጥ እንደሚያሳድር ሰምቻለሁ
ግን ኢምባሲው የት እንደሆነ እንኳ አላውቅም:: ጃሎህ ከሚባል
ፉላኒ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ አርብቶ አደር ጎሳ) ጋር ነበር የተቀመጥኩት። ጃሎህ ፍሪ ታውን እንደኖረ ነገረኝ፡፡ ስለ ጦርነቱ እና በሃገሪቱ ላይ ስላስከተለው ጉዳት አወራን። በኋላ ስልክ ቁጥሩን ሰጠኝ እና ከተማዋን ስንቀሳቀስ እርዳታ ካስፈለገኝ እንድደውልለት ነገረኝ። ማደሪያ እንደሌለኝ ልነግረው ፈለኩ ግን
ቀድሞኝ ወረደ። አብሮኝ የመጣውን ሴራ ሊዮናዊ ፈለኩ ግን ላገኘው አልቻልኩም። ከደቂቃዎች በኋላ አውቶብሱ ግዙፍ
መናሃሪያ ውስጥ ገባ። ወጥቼ ሁሉም ሲሄድ ተመለከትኩ። ተነፈስኩ እና እጆቼ ራሴ ላይ ጭኜ ወደ አግድም ወንበር ሂጄ
ተቀመጥኩ። ፊቴን በእጆቼ ሸፍኜ “ለሊቱን ሙሉ ከዚህ መቀመጥ አልችልም” ብየ ለራሴ አጉረመረምኩ።

ብዙ ታክሲዎች ነበሩ እና አውቶብሱ መናሃሪያ የደረሱ ሰዎች ሁሉ ይዟቸዎል። እኔም ብቸኛ ሚሄድበት የጠፋው እንግዳ
መስየ መታየት ስላልፈለኩ አንዱ
ታክሲ ውስጥ ገባሁ። ሹፌሩ በፈረንሳይኛ ሲናገር ወዴት እንደምሄድ እየጠቀኝ እንደሆነ ገመትኩ። ሴራ ሊዮን ቆንስላ አ ኢምባሲ” ብየ ነገርኩት።በመስኮት ስመለከት የመብራት ምሶሶዎች ላይ የመንገድ መብራቶቹ ተንበርግገው
ተንጠልጥለዋል። ብርሃናቸው ከጨረቃ ብርሃን ሳይበልጥ አይቀርም። ታክሲው ኢምባሲው ፊት ለፊት ቆመ እና የምፈልገው ቦታ ይዞኝ እንደመጣ
ለማረጋገጥ ወደ አረንጓዴ፣ ነጭ እና ሰማያዊ ባንዴራ ጠቆመኝ፡፡ራሴን በማወዛወዝ ትክክል እንደሆነ ከገለፅኩለት በኋላ ከታክሲው ወረድኩ
በኤንባሲው በር ላይ ጠባቂዎቹ በኪሪዎ የይለፍ ወረቀቴን እንዳሳይ ጠየቁኝ፡፡ አሳየኋቸው እና ወደ ግቢው እንድገባ ፈቀዱልኝ::

በግቢው ውስጥ ከሃምሳ በላይ ሰዎች ሲኖሩ እንደእኔ መጠጊያ ያጡ ሳይሆኑ አይቀሩም፡፡ አብዛኖቹ ትራስ ብቻ አድርገው ተጋድመዋል። ጓዛቸውን ወይም ሻንጣቸውን ከጎናቸው አስቀምጠዋል። ሰዎቹ ማታ ማታ ከዚህ የሚያድሩ ሲሆን ቀን ቀን ወደ ውጭ ይወጣሉ። ጥግ ላይ ቦታ አገኘሁ እና መሬት ተቀምጨ ጀርባየን ወደ ግድግዳው አስጠጋሁ። ስዎቹን ሳይ
ከጦርነቱ ለማምለጥ ያለፍኩባቸው ሰፈሮች ትዝ አሉኝ።