አትሮኖስ
286K subscribers
117 photos
3 videos
41 files
568 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_አርባ_ስምንት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ

....በልሁ አስር ብር ሰጣትና በተረፈው አንቺ ጠጪ እኔ ግን መንገድ ላይ ደክሞኛልና ወደ ማረፊያዪ ልሂድ አላት።
በጥሩ ስሜትና ፈገግታ ተሰነባበቱ
የበልሁ የማግስቱ የመጀመሪያ ስራ አስተናጋጇ በጠቆመችው
አቅጣጫ ሄዶ ያቺን መናፈሻ ማግኘት ነበር።ብዙ ሳይቸገር
አጎኛት፡፡ ሲያዩዋት ደስ የምትል መናፈሻ የነበረች ትመስላለች፡፡ ግቢዋ በልዩ ልዩ ተክል ያሸበረቀ ነው፡፡ ዋናው ቡና ቤት መሀል ላይ ይገኛሉ፡፡ በአራት ማእዘን ቅርፅ ጥርብ ድንጋይ የተሰራ ነው:: በየአትከልቱ መሀል አልፎ አልፎ
የፈራረሱ መዝናኛ ጎጆዎች ይታያሉ። ከአንዱ ወደ ሌላው መተላለፍያ መንገድ በሲሚንቶ የተሰራ ነው፡፡ አሁን ግን የዛፎቹ ቅርንጫፍ ስለማይከረከም እየተዘጉ ያሉ ይመስላሉ፡፡ በዚያ ላይ የወፎች ኩስ ተንጠባጥቦባቸው
ተዥጎርጉረዋል፡፡
የግቢው ዙሪያ አጥር ከታች አንድ ሚትር ያህል በግንብ፡ ከላይ ደግሞ የዚያኑ ያህል በብረት
ፍርግርግ የታጠረ ነው፡፡ ዋና መግቢያው በር በብረት መዝጊያ ተከርችሟል፡፡ አንድ ሰው ብቻ ይጠብቀዋል፡፡
በልሁ የዚያች መናፈሻ የቀድሞ ገፅታ በአይነ ልቦናው ታየውና እንባ እንባ አለው፡፡ አስቻለውን በዚያ ውስጥ አስታወሰው፡፡ አስቻለው አሁን እዚያ ውስጥ እያለ ነገር ግን ቢጠራው አልሰማ፣ እጁን ቢዘረጋ አልደርስበት ያለው
ይመስል ሆዱ ባባ፡፡ እንባውም ፈሰሰ፡፡ መሀረቡን አውጥቶ አይኑን ጠረግ ሲያደርግ ድንገት ድምፅ ሰማ፡፡ ከመናፈሻዋ በር ጠባቂ በኩል ነበር፡፡
“ምን አሉኝ ጌታዬ?» ሲል በልሁ ወደ ሰውየው እያየ ጠየቀው፡፡
ሰውየው አሁንም ተናገሩ።ነገር ግን በትግርኛ ስለነበር ለበልሁ አልገባውም።
ሰውየው ከስልሳ አለፍ የሚላቸው ይመስላሉ የሰማያዊ ካኪ ቱታ ለብሰው ራሳቸው ላይ የዘበኛ ቆብ
አድርገዋል። እሳቸውም አማርኛ በደንብ አይችሉ ኖሮ በእጃቸው እያመለከቱ « ወዲያ ወዲያ..»
አሉት በልሁም ከዚህ አካባቢ ሂድ ማለታቸው እንደሆነ ገብቶት ከቦታው መራቅ ጀመረ፡፡
ከአባ ሻውል በስተደቡብ አቅጣጫ በሚወስደው አቧራማ መንገድ ላይ ዝም ብሎ ይራመድ ጀመር፡፡ ያ አካባቢ ከሌላው የአስመራ አካል ጋር ሲነጻጸር
ደከም ያሉ ናቸው:: ሞቅ ደመቅ ያሉ ቡና ቤቶች አይታዩበትም ትንንሽ ግሮሰሪዎች ጠላና እንዲሁም አረቄ ቤቶች ይበዙበታል።
በልሁ ድንገት በል በል አለውና ከከንድ ጠላ ቤት ውስጥ ገባ ሰዓቱ ገና ከአራት ብዙም አላለፈም፡፡ ነገር ግን በርካታ ጠጪዎች ቤቱ ውስጥ አሉ፡፡ ባለ ጠላ ቤቷ ሳይሆኑ የማይቀሩ
ወደ ሃምሳ የሚጠጋቸው ቀይ ረጅም ዘንካታ የሆኑ ሴት ወይዘሮ ወንበር ላይ ጉብ ብለው በየመደቡ ላይ ተቀምጠው ከሚጠጡ ሰዎች ጋር ይጫወታሉ። ቋንቋቸው ትግረኛ ነው።
በልሁ ገብቶ ሲቀመጥ ምን ልታዘዝ የሚል አስተናጋጅ ከፊቱ
አልቀረበም፡፡ ጠላ ቤት ነውና መስተንግዶው የታወቀ ነው፡፡ አንዲት በኑሮዋ ጎስቆል ያለች ልጅ እግር ሴት በጣሳ ጠላ ይዛለት ቀረበች፡፡ በእጁ ሰጠችው፡፡በልሁ ጠላውን ቀመስ ሳያደርግ ወለሉ ላይ ቁጭ አደረገው።
እኒያ ነጫጭ የሀገር ልብስ ለብሰው ወንበር ላይ ቁጭ ያሉት ቀይ መልከ መልካም ሴት በልሁን
አየት አደረጉና «ብርጭቆ ክህቦም» አሉት በትግርኛ። «ምናሉኝ እማማ!» አለና በልሁ «ትግርኛ አልችልም» አላቸው
«ዋይ!» አሉና ሴትዮዋ «ብርጭቆ ይሰጥህ ወይ ማለቴ እኮ ነው፡፡» አሉት «አያስፈልግም እማማ! አመሰግናለሁ!» አለና ጣሳውን አንስቶ ፉት አለ።
«የሸዋ ሰው ነህ?» ሲሉ ጠየቁት ሴትየዋ ፈገግ እያሉ፡፡
«አዎ» አላቸው፡፡ በልሁ ያቺን የማታዋን አስተናጋጅ አስታወሳት፡፡
«አይዞህ የኔ ልጅ! በል ጠጣ!» አሉትና ሴትዮዋ ወደ ሌለች ጠጪዎች ዞር በማለት ጨዋታቸውን ቀጠሉ፡፡
በልሁ አልፎ አልፎ ጠላውን ፉት እያለ የሚያወሩት ነገር ባይገባውም የጠጪዎችን ወሬ ሲያዳምጥ ብዙ ቆየ፡፡ በየመሀሉ ግን ልቡን ዳዳ የሚያረገው
ነገር አለ፡፡ ሊናገር አሁን አሁን ሲል ድንገት ሴትዮዋ ቀድመው አናገሩት:
«ተጫወት የኔ ልጅ!፡፡» አሉት በልሁን ፈገግ ብለው እያዩ፡፡ በልሁ
ጣሳውን እያነሳ ሳለ ሴትዮዋ ቀጠሉ፡፡ «ቋንቋችንን አታውቀው፣ እንዴት እናርግህ?» አሉት እጆቻቸውን በጡቶቻቸው ስር አጣምረው ፊት ለፊት
እየተመለከቱት፡፡
«አረ ይሁን ምንም አይደል» ብሎ በልሁ ወዲያው ደግሞ በዚህ
አካባቢ የሚያውቁት የሚሲዮኖች ሀኪም ቤት ይኖር ይሆን እማማ?» ሲል ጠነቃቸው።
ሴትዮዋ ትንሽ አሰብ አደረጉና «እነዚያ ጥልያኖቹ?» ሲሉ ጠየቁት፡፡ «ይሆናሉ በእርግጥ ፈረንጆች ናቸው»
«ከዚህ ወደታች በኩል ነበሩ፡፡ ነገር ግን አሁን እኮ ከዚያ ቦታ «ለቀዋል?» በልሁ አሁንም ደንገጥ እያለ
«ምን ያህል ጊዜ ሆናቸው?
«ቆዩ እኮ!»
«ምን ያህል ጊዜ ሆናቸው?»
ሴትዮዋ በቀጥታ ለበልሁ ምላሽ ሳይሰጡ ወደ ጠጪዎቹ ዞር በማለት በትግሪኛ ያነጋግሯቸው ጀመር፡፡ ደግመው ደጋግመው ከተመላለሱ በኋላ ሴትዮዋ ፈታቸውን ወደ በልሁ መለስ አድርገው «ከዓመት በላይ ይሆናቸዋል ነው የሚሉኝ» አሉት።
በልሁ እንደገና ወሽመጡ ቁርጥ አለ ፡፡ አጋጣሚዎች ለምን
እንደሚደጋገሙበት ግራ ገባው፡፡ እዝን ባለ ፊት ትክዝ ባለ አነጋገር «በቃ ይተውት እማማ!» እላቸውና ጣሳውን አንስቶ ፉት ካለለት በኋላ መልሶ አስቀመጠው፡፡ ወደ መሬት እጎንብሶ ራሱን ደጋግሞ ወዘወዘው፡፡
«ልትታከም ኖሯል?» ሲሉ ሲትዮዋ ጠየቁት፡፡
«አይደለም፡፡ እነሱ ጋር ይሰራ የነበረ ሰው እፈልግ ነበር፡፡» አላቸውና አሁንም ጎንበስ አለ።
«አየየ... ለቀዋላ!» ብለውት ሲትዮዋ ወደ ጨዋታቸው ተመለሱ፡፡
በልሁ ከዚያ በኋላ ብዙ መቆየት አልፈለገም፡፡ ውስጡም ተናደደ፡፡
እስከ አሁን ባገኘው መረጃ የአስቻለው ዱካ በቀላሉ እንደማይገኝ፡ ምናልባትም
ጭራሽ ላይገኝም እንደሚችል ፈራ፡፡ ተስፋው እየጨለመ ሄደ፡፡
ወዲያው አንድ ነገር ታየው፡፡ ወደ አረፈበት ሆቴል መብረር፡፡ አዎ
ሄደ፡፡ በጠራራ ፀሐይ በአንሶላና ብርድ ልብስ ጥቅልል ብሎ ተኛ አስቻለውን እንዳያገኝ ከጋረደው የጭንቅ ጉም ያመለጠ መስሎት፡፡
የሰው ልጅ የቱንም ያህል ቢያሰብ፡ ቢጨነቅ ወይም ቢናደድ፡ ቢበሳጭ አልያም ቢፈራ በአጠቃላይ በየትኛውም ስሜት ውስጥ ቢሆን በህይወት
ለመሰንበት የግድ የሚያስፈልገው አንድ ነገር አለ፡ ምግብ፡፡ በልሁ በአንሶላና በብርድ ልብስ ውስጥ ቢደበቅም አላመለጠውም፡ አጅሬ ርሀብ ከውጭ ሳይሆን ከውስጥ የሚነሳ እሳት ነውና አንጀቱን ይሞረሙረው ጀመር፡፡ ከአንድ ጣሳ ጠላ ሌላ የቀመሰው ነገር ባለመኖሩ ከቀኑ ዘጠኝ ሠዓት አካባቢ ከተኛበት ሰቅስቆ
አስነሳው:: ምግ አይሉት ራት አደባልቆ ሊበላው ወደ ሆቴሉ ራስቶራንት ወረደ፡፡ ሚሲዮኖቹ ሀኪሞች ይሰሩ ከነበሩበት አካባቢ በመልቀቅ ዜና ተበሳጭቶ
ሳይበላ ሳይጠጣ በመዋሉ መንፈሱ ድክምክም ብሎበት የነበረው በልሁ ምሳ በልቶ ቀዝቀዝ ያለ ለስላሳ ከውሃ ጋር እየቀላቀለ ሲጠጣ በዚያው ልክ ተነቃቃ፡፡
ረጋ ብሎ ማሰብ ጀመረ።
አንድ ነገር ታየው ሚሲዮኖቹ
ሀኪሞች እንደ መሆናቸው መጠን
ከክፍለ ሀገሩ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት ጋር በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ግንኙነት ሊኖራቸው እንደሚችል ታሰበው ምናልባትም የስራ ፈቃድ ሊኖራቸው ይገባል " ያ ከሆነ ደግሞ ወቅታዊ ሪፖርቶች ይጠበቅባቸው ይሆናል፡፡ በዚያው መጠን በሁለቱ አካላት መካከል መቀራረብና የአድራሻ ልውውጥ ሊኖር ይችላል “ሚሲዬኖቹ እዚያው አስመራ ካሉም እዚያው
👍131
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ


....«ይቅርታ የኔ ወንድም» ብሎ ጉዳዩን አጠር እድርጎ እስረዳው፡፡
ወጣቱ ርምጃውን ቀጠለ፡፡ በልሁ ግን እዚያው ባለበት አቀርቅሮ
ቆመ ወጣቱ አስቻለውን በዓይን እንደሚያውቀው ተረድቷል ፡፡ ነገር ግን የሰራተኞች በመኪና መግባትና መውጣት ጉዳይ መኖሪያቸው የግድ በዚያ
አካባቢ ላይሆን እንደሚችል አመሰከተው፡፡ በዚያው ልክ በልሁ ተስፋ ቆረጠ፡፡በነገው ዕቅዱ ላይ ብቻ አተኮረ፡፡ ሲያስብበት ውሉ ሲያስብበትም አደረ፡፡

ሰኞ ዕለት ጠዋት ከረፋፍዶ ከመኝታው ተነሳ፡፡ አለባበሱንም ለየት አደረገው፡፡ ዲላ ውስጥ ለሰርግ ወይም ለየት ባለ ድግስ ካልሆነ በቀር አዘውትሮ
የማይለብሰውን ደብዘዝ ያለ ሰማያዊ ሙሉ ልብስ ለብሶ የጥቁርና የነጭ ቡራቡሬ ክራባት አሰረ፡፡ ጥሩ ቁርስ በላ፡፡ ትናንት ቦታውን አጥንቶት ወደነበረው የክፍለ ሀገሩ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አመራ ከጠዋቱ ሶስት
ሰዓት አካባቢ ከቅጥር ግቢው ውስጥ ገባ፡፡ የአስተዳደር ምክትል ሰራ አስኪያጅ የሚል ጽሁፍ ወዳለበት ቢሮ ልቡ አደላ፣ በፀሐፊዋ በኩል ከመራና በር ላይ ቆሞ
«ጤና ይስጥልኝ» አላት፡፡
«አብሮ ይስጠን» አለችና ፀሃፊዋ ከመቀመጫዋ ብድግ አለች፡፡ አጠር ብላ ወፈር የምትል፡ የቀይ መልከ መልካም የሆነች ዕድሜዋ ወደ አርባ የሚጠጋት ሴት ወይዘሮ ናት፡፡ አጠር ያለ ፀጉሯን ጆንትራ አበጥራለች፡፡
«ሃላፊውን ማነጋገር እችላለሁ?»
«ስለምን ጉዳይ?»
በልሁ የልቡን መዘርዘር አልፈለገም ያን ጉዳይ ካነሳ ይህ አይመለከታቸውም ልትለው እንደምትችል አሰባና «የግል ጉዳይ ነው፡» አላት።
በኋላ፡ የምታዝንለት መስሎት «የመጣሁትም ከሲዳሞ ነው» ሲል ገለጸላት፡፡
ፀሐፊዋ ወንበር እያሳየችው ይቀመጡ» ብላ ወደ አለቃዋ ቢሮ
ገባች፡፡ ብዙ ፡ ሳትቆይ ወዲያው ተመለሰችና "ይግቡ አለችው "
የሃላፊው ቢሮ ለየት ያለ ነው፡፡ መጠነ ሰፊ ወለሉ በአረንጓዴ ቀለም ምንጣፍ የተሸፈነ መስኮቱ በነጭ ስስ እና ቀይ ወፍራም መጋረጃ የተከለለ ከስድስት የማያንሱ ወንበሮች ያሉት ትልቅ የእንግዳ ጠረጴዛ የተንጣለለበት
ግድግዳው ሹሯማ ቀለም የተቀባና ደስ የሚያሰኝ ገፅታ ያለው ነው፡፡
ሃላፊው አቶ ካህሳይ ገብሩም መልካ መልካም ነው፡፡ ድምቅ ብሎ ቀይ ጥቁር ሰማያዊ ሙሉ ልብስ በነጭ ሸሚዝና ጥቁሩ በዛ ያለበት ቡራቡሬ ካራባት ያደረገ፣ አፍንጫው ሰልከክ ዓይኖቹ ጎላ ያሉና ዕድሜው ከአርባ አምስት
ዓመት የማያንሰው ጎልማሳ ነው።
«ጤና ይስጥልኝ አለ በልሁ ወደ ውስጥ ገብቶ ሃላፊውን እጅ እየነሳ
«አብሮ ይስጠን» ብሎ ካህሳይ ከወንበሩ ብድግ ብሎ ተቀበለው፡፡
ስማቸውን በመለዋወጥ እጅ ለእጅ ተጨባበጡና በካህሳይ ግብዣ በልሁ ከእንግዳ መቀበያ ወንበር ላይ ተቀመጠ።
«ምን ልርዳዎት አቶ በልሁ?» ሲል ካህሳይ በልሁን ጠየቀው፡፡
«ችግር ገጥሞኝ ነው አቶ ካህሳይ»
«ምን ዓይነት ችግር?
በልሁ የመጣበትን አገርና ለምን ወደ አስመራ እንደመጣ በአጭሩ
ከአስረዳ በኋላ «ወንድሜ በሚሲዮኖች ክሊኒክ ውስጥ ይሰራ እንደነበር ተጠቁሜ ነበር ።
የሚሰኒዮቹን የስራ ቦታ አጠያይቄ ባገኘውም ነገር ግን ከአንድ ዓመት በፊት ከዛ ቦታ እንደለቀቁ ሰማሁ፡፡ ምናልባት ከሙያ አንጻርና
የምታውቸው ከሆነና አሁን የሚገኙበትን ቦታ ትጠቁሙኝ ከሆነ ብዩ ነበር፡፡» አለና በልሁ ካህሳይን ቀና ብሎ ተመለከተው፡፡
«የት አካባቢ የነበሩት ናቸው?» ሲል ካህሳይ በልሁን ጠየቀው::
«ቀበሌውን በትክክል አላወኩትም፡፡ ነገር ግን አባ ሻውል ከሚባለው ቦታ ወረድ ብሎ በምዕራባዊ የከተማዋ ዳርቻ የሚገኝ ክሊኒክ እንደ ነበር ማወቅ ችያለሁ።
ካህሳይ ሚሲዮኖቹን ያወቃቸው ይመስላል፡፡ አንገቱን ነቅነቅ ነቅነቅ ካደረገ በኋላ «ታዲያ እኮ እነሱ አስመራ ውስጥ አይደሉም ቦታ የቀየሩት ጠቅላላ ከሀገር ተባርረዋል አለውደ
«ተባርረዋል?» ሲል ጠየቀ በልሁ፡፡ ዓይኖቹ ፍጥጥ ብለው
በካህሳይ ላይ ተተከሉ፡፡
«ከዓመት በላይ ሆናቸው»
«በምን ምክንንያት ተባረሩ አቶ ካህሳይ? ምናልባት ወንድሜም አብሮ ተባሮ ይሆን?» ሲል በስጋት ስሜት ውስጥ ሆና ጠየቀው፡፡
ወንድምክ እንኳ ከብሮ ሊባረር የሚችልበት ሁኔታ የለም፡፡ እነሱ የተባረሩት በሀገር ውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ገቡ ተብሎ ነው፡፡»
«በፖለቲካ?»
«በመሆኑ ነዋ ለነገሩ እነርሱም አያርፉ ነገሮች ሁሉ እንደራሳቸው
ሀገር እየመሰላቸው የኛ መንግስት አካሄድ ሳይጥማቸው ሲቀር በአገኙት አጋጣሚ ሁሉ ወጋ ማድረግ ይወዳሉ፡፡ አለ ካህሳይ ፈገግ ብሎ የበላሁን ምላሽ እየጠበቀ።
በልሁ ፈጥኖ ለካህሳይ መልስ መስጠት አልፈለገም ወይም አልቻለም ዓይኑን ብቻ ትክል አድርጎ ካህሳይን ያየው ጀመር፡፡ እንዲያውም ቀስ በቀስ ዓይኖቹ በእንባ ይሞሉ ጀመር፡፡
«ምነው አቶ በልሁ?» ሲል ካህሳይ የበልሁ ስሜት መለዋወጥ አስገርሞት ጠየቀው፡፡
በልሁ አሁንም መልስ ከመስጠት ይልቅ ፊቱን በካህሳይ ላይ መልሶ
ወደ ጠረጴዛው በማጎንበስ በእንባ የሞላውን ዓይኑን በመሀረብ ይጠርግ ጀመር፡፡
«አቶ በልሁ» አለ ካህሳይ ይበልጥ እየደነገጠ፡፡
«ሆዴ አዘነ አቶ ካህሳይ!»
«ምነው? ወንድምህ አብሮ የተባረረ መሰሎህ?
«አይደለም አቶ ካህሳይ የዕድሉ ነገር እሳዝኖኝ ነው ፡፡" አለና ንግግሩን በማራዘም «አዩ አቶ ካህሳያ፣ ወንድሜ የጤና ባለሙያ እንጂ ፖለቲከኛ አልነበረም፡፡ ነገር ግን በሄደበት ቦታ ሁሉ የፖለቲካ መዘዝ አልለቀው አለው
አሁንም የዓይኖቹን እንባ እየጠራረገ፡፡
«ማለት?»
«ወንድሜ ገና ልጅ ሳለ የሚረዳው ወንድሙ በፖለቲከኞች ተገደለበት
በችግር ተማረ፡፡ በስንት ስቃይ ትምህርቱን ጨርሶ ስራ ከያዘም በኋላ አሁንም ፖለቲከኞች ሰላም ነስተው ሲያዋከቡት ኖሩ፡፡ የኋላ ኋላም በግፍና በተፀዕኖ ወደዚህ ክፍለ ሀገር በ እናት ሀገር ጥሪ ሽፋን እስገድደው ላኩት፡፡ በእነሱ ጦስ አካሉን አጣ፡፡ እዚሁ ከተማ ውስጥ እየተውትሮ ያርፍባት የነበረችው ሰራዩ መናፈሻ ደግሞ ከፖለቲካ ጋር በተያያዘ መዘጋቷን ሰማሁ፡፡ እነሆ አሁን ደግሞ
እርስዎም አሰሪዎቹ በፖለቲካ ጉዳይ ከሀገር መባረራቸውን እየነገሩኝ ነው፡፡ ይህ የፖለቲካ ጉዳይ እኔም እንዳላገኘው ምክንያት ሊሆን ነው፡፡ ታዲያ ይሄ
አያሳዝንም እቶ ካህሳይ?» ሲል በልሁ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ለካህሳይ ገለፀለት::
ካህሳይ ገብሩ በሰማው ታሪክ፣ በበልሁ አለቃቀስና የነገሮች አገላለፅ የእሱም ልብ ነካ፡፡ በልሁን ያህል ግርማ ሞገሱ ግጥም ያለ የወጣት ጠንበለል ከፊቱ ቁጭ ብሎ እንባውን እያፈሰሰ ብሶቱን ሲገልጽላት የእሱም አንጀት
ተላወሰ፡፡ ወንድ ልጅ ሲከፋው እንባው ምን ያህል ቅርብ እንደሆነ ከመቼውም ጊዜ በላይ ሲረዳ ሆዱ ተንቦጫቦጨ በሀዘን ሰሜት ራሱን ደጋግሞ ወዘወዘና በልሁን ትኩር ብሎም ተመለከተው። በልሁ አሁንም ንግግሩን ቀጠለ
«በቃ እኮ አቶ ካህሳይ ከእንግዲህ ወንድሜን ላላገኘው ነው።አለው እንባው በአይኖቹ ላይ ተቋጥሮ ሰማይ እየመሰለ።
ካህሳይ ገብሩ አሁንም ላፍታ ያህል በሀዘን ዓይን ከተመለከተው በኋላ ራሱን ለረጅም ግዜ ወዝውዞ በረጅሙ ተነፈሰና «ለመሆኑ የወንድምህ ስም ማን ይባላል?» ሲል ጠየቀው።
👍9
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሃምሳ


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ


.....«አመሰግናለሁ አቶ ካህሳይ!» አለ በልሁ በአክብሮትና በትህትና እጅ እየነሳ።
«የት ነው ያረፍከው?» ሲል ጠየቀው ካህሳይ፡፡
«ኒያላ ሆቴል ሃያ አራት ቁጥር፡፡»
ጥሩ አቶ በልሁ በተረፈ እግዚኣብሔር ከአንተ ጋር ይሁን፡፡» ብሎ በልሁን በሰላምታ ለመሸኘት ከወንበሩ ላይ ብድግ አለ፡፡ በልሁም ብድግ አለና ለሁለተኛ ጊዜ የከበረ ምስጋናውን አቅርቦ ተጨባብጠው ተሰነባበቱ፡፡

ስድስት ቀናት አለፉ፡ አንዲያውም በልሁ አስመራ ከገባበት ቀን ጀምሮ ሲቆጠር አሥረኛ ቀን፡፡ የአስቻለው ዱካ ግን አልተገኘም፡ ጭራሽ እየራቀ ሄደ፡፡ የካህሳይ ገብሩ ጥረትም አልተሳካ፡ የአስቻለው ስም በየትኛውም
ኤን ጂ ኦ የሰው ሀይል ሪፖርት ውስጥ ተካትቶ አልተገኘም፡፡ በልሁ በቀጠሮው ቀን ወደ
ካህሳይ ቢሮ ብቅ ባለበት ወቅት የተነገረው ይኸው መጥፎ ዜና ነበር፡፡
በልሁ ከዚያ በኋላ ማድረግ የፈለገው አንድ ነገር ብቻ ነበር፡፡ ሳይታክት ሴይሰለች በአስመራ ከተማ ውስጥ በሚገኙ ቡና ቤቶች ሁሉ እየተዘዋወረ ሰለ
እስቻለው ወሬ መጠየቅ፡፡ የበልሁ ሀሳብ በየቡና ቤቱ እየተዘዋወረ
አስተናጋጆችን በማነጋገር ምናልባት አስቻለው ያዘወትርባት በነበረችው ስራዬ መናፈሻ ውስጥ ይሰሩ የነበሩ የሆቴል ሰራተኞችን ከአገኘሁ የሚል ነበር፡፡
በእርግጥም አነስተኛ ሻይ ቤቶችና ኬክ ቤቶች ሳይቀሩ በአስመራ ዋና ዋና መንገዶች ላይ የተኮለኮሉትን ቡና ቤቶች ሁሉ ጎበኛቸው፡፡ ከቀትር በፊት ሲሆን ሻይ ቡና፣ ወደ አመሻሹ ላይ ደግሞ ቢራ ወይም ሌላ ዓይነት መጠጥ እየያዘ በመቀመጥ ብዙዎቹን አነጋገረ፡፡ ሆኖም ፍንጭ እንኳ ሊያገኝ አልቻለም።እንዳያውም
ከሚጠጣው ሻይና ቡና ብዛት የተነሳ ከንጀቴ ተቃጠለ፡፡ ቢራና የአልኮል መጠጡም በተለይ ሌሊት ሌሊት እንቅልፍ እየነሳው ተቸገረ።
በዚህ ሁኔታ ላይ ሰንብቶ ልፋቱ ሁሉ መና ሲቀርበት ሌላ ሙከራ
ሊያደርግ አሰበ በቀጥታ ወደ ዲላ ስልክ መደወልና ታፈሙን ማግኘት በእሷ በኩል የሀምሳ አለቃ መንጋ ዳርጌን ለማግኘት መሞከር፡፡ ሀሳቡም ምናልባት የሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ያን ከአስቻለው ጋር ለመገናኘት ምክንያት የሆነውን የአስመራ ኗሪ ጓደኛውን አድራሻ የሚያቀው ከሆነ ሊጠይቀውና በእሱ እየታገዘ ወደ አስቻለው ለማምራት ነበር በልሁ ይህን ያሳሰጡ አስመራ በገባ በአሥራ አንደኛው ቀን በዕለተ ዕሁድ ላይ ሆኖ ነው፡፡ ታፈሡንም ሆነ የሀምሳ
አለቃ መኮኮንን ዳርጌ ያን ከአስቻለው ጋር ለመገናኘት ምክንያት አለቃ መኮንን ዳርጌን በቀላሉ በስልክ ሊያገኝ የሚችለው በመስሪያ ቤት በኩል
ስለሆነ ስልክ የመደወል ሙከራውን በማግስቱ ሰኞ ሊያደርግ ወሰነ፡፡
ይህን ሀሳብ ያሰሳሰለው በኒያላ ሆቴል ውስጥ አልጋ ላይ ጋደም ብሎ ነው፡፡ ከውሳኔ ላይ የደረሰውም በዕለቱ ወደ አስር ሰዓት አካባቢ ነው፡፡ በዚያ አልጋ ላይ ለብዙ ጊዜ ቆይቶ ስለነበር ከውሳኔ በኋላ በአስመራ መንገዶች ላይ ጥቂት ሊዘዋወር ፈለገ፡፡ ለባብሶ ወጣ፡፡ ጥቂት ሲዘዋወር ከቆየ በኋላ ሳያስበው
ከዚያ አስመራ የገባ ዕለት ጎራ ባለበትና ስለ አስቻለው ለመጀመሪያ ጊዜ ያወያያት የቡና ቤት አስተናጋጅ በምትሰራበት ሆቴል እግሮቹ አደረሱት፡፡
ጥቂት ለማረፍና ከልጅቷም ጋር ጥቂት ሊጨዋወት ከስቦ ጎራ አለ፡፡ ቁጭ አለና ቢራ አዘዘ፡፡ ልጅቷን ግን በዓይኑ ቢፈልጋትም ሊያያት አልቻለም ወይ
የጠዋት ተረኛ ሆና አሊያም በሌላ ምክንያት በእለቱ በሆቴሉ ውስጥ የለችም እሱ ግን ብቻውን ቁጭ ብሎ ሲጠጣ አመሽ፡፡ ከምሽቱ ሁለት ሠዓት አካባቢ ሂሳቡን ከፈለና ወደ ማረፍያው ኒያላ ሆቴል አመራ።
ልክ እንደደረሰ የአልቤርጎውን በር ከፍቶ ወደ አልጋው ሊራመድ ሲል
እንዲት ለሁለት የታጠፈች ወረቀት ወለሉ ላይ ታየችው፣ በበሩ ስር ወደ ውስጥ የተወረወረች ትመስላለች፡፡ ልቡ ደንገጥ አለና ትኩር ብሎ ተመለከታት፡፡ወዲያው ብድግ አድርጎ ሲያያት አጭር መልእክት ይዛለች።
«አቶ በልሁ፣ ከዚህ በታች በተገለጸው ስልክ ቁጥር ስዩም ብለው ይደውሉ።» ይላል የያዘችው መልእክት።
«እ» አለ በልሁ ሁለመናውን ነዘር አደረገው፡፡ «ማነው ስዩም ማለት?» አለ ብቻውን እየተነጋገረ።
ጉዳዩ ከእስቻለው ጋር የተያያዘ መልዕክት ካለው ብሎም ጓጓ፡፡ ቀስ እያለ ሲያስበው ግምቱ ይበልጥ ጠነከረ፡፡ ጭራሽ ስልክ ለመደወል ቸኮለ፡፡ ያቺ ወረቀት ከእጁ ሾልካ የምትጠፋበት መስሎት በመዳፉ ውስጥ ጭብጥ አደረጋትና በችኮላ የአልቤርጎውን በር ዘግቶ ወደ ውጭ በረረ፡: ኒያላ ሆቴል አጥር ግቢ ወጥቶ መንገዱ ላይ እንደ ደረሰ በመንገድ ላይ በቡድን ሆነው እየሄዱ የነበሩ
ሰዎችን በጅምላ ጠየቃቸው፡፡
«ስልክ፡ በቅርብ የት አገኛለሁ ወንድሞቼ?»
«በዚያም በዚህም ሞልቷል!» አለው ከመንገደኞች አንዱ፡፡ በልሁ
በየት አቅጣጫ መሮጥ እንዳለባት ሲያስብ አሁንም ከመንገደኞች አንዱ ወደ ቀኝ አቅጣጫ እያመለከተ «በዚህ በኩል በቅርብ ታገኛለህ» አለው።
በልሁ በዚያው አቅጣጫ ሮጠ፡፡ አንድ ሁለት ሱቆች ውስጥ ሲጠይቅ አንዱ ጋር ስልክ አያስደውሉም፣ ሌላኛው ደግሞ ለጊዜው ስልኩ ተበላሽቶ ኖሮ
«አይሰራም» አለችው ሱቅ ጠባቂዋ፡፡ በጠየቀበት በአምስተኛው ሱቅ ውስጥ አገኘና ደወለ።
«ሄሎ» አለችው አንዲት ሴት
«አቶ ስዩምን ፈልጌ ነበር የኔ እመቤት»
«ይጠብቁ!» ብላው ሴትየዋ የስልኩን እጀታ በሆነ ነገር ላይ
ስታስቀምጥና በርቀት እጠራር ስልክ ይፈልግሀል ስዩም" ስትል በስልኩ ውስጥ ተሰማው፡፡ በልሁ ከስዩም ድምጽ በፊት ወደ ስልኩ እየቀረበ ስለመሆኑ ለማወቅ
ኮቴውን በጥንቃቄ ያዳምጥ ጀመር፡፡ በእርግጥም ተሰማው::
«ሄሎ!» አለ አንድ ሰው።
«አቶ ስዩም ነዎት ጌታዬ?»
«አዎ ነኝ»
«በልሁ እባላለሁ፡፡ አልቤርጎ ውስጥ መልዕክትዎን አግኝቼ ነው፡፡»
«እ ነዎት? አስቻለው ፍሰሀ የሚባል ሰው በመፈለግ ላይ ያሉት?»
«አዎ ጌታዬ!» አለ በልሁ፡፡ ልቡ በድንጋጤ ትርትር ሊል የደረሰ
መሰለው::
«ታዲያ ለምን አመሹ? በጊዜ አይደውሉም ነበር? እኔ እኮ አስር ሠዓት አካባቢ ነበር መልዕክቱን ያስቀመጥኩልዎት፡፡» አለ ስዩም፡፡
እኔም እኮ በዚያው አካባቢ ነው ከክፍሉ የወጣሁት፣ ለጥቂት ተላልፈን እንደሆነ አንጂ!» አለና በልሁ አጋጣሚው እንዳያመልጠው በመስጋት “ወይ እኔ ወደ እርሶ ልምጣ?” ሲል ጠየቀው፡፡
«መቼ? አሁን?»
«ምንም ችግር የለብኝም ጌታዬ
«ቸኩለዋል ማለት ነው?»
(በጣም አቶ ስዩም፡ እጅግ በጣም
«በቃ እኔ እመጣለሁ፡፡ ባይሆን እንዳንጠፋፋ ከክፍልዎ ይጠብቁኝ፡፡»
«ንቅንቅ አልልም ጌታዬ!»
«እሺ መጣሁ፡፡»
ለበልሁና ለስዩም መተዋወቂያ አስቻለውን የመፈለግ ስራ እንደ
ምልክትነት የመውሰዱ ጉዳይ ነገሩ ከአስቻለው ጋር የተያያዘ ስለመሆኑ የበለጠ ተስፋ አደረበት፡፡ ግን አስቻለውን የሚያስገኝ ይሆን ወይስ ሌላ ሁኔታውን የሚያውቅበት አጋጣሚ? የበልሁ የዚያች ቅፅበት ሀሳብና ስጋት ሆነ፡፡ ግን የሆነው ይሁን፣ በልሁ ዛሬ ስዩምን ማግኘት አለበት፡፡ ስዩም ደግሞ 'መጣሁ አለው እንጂ በምን ያህል ደቂቃ እኒያላ ሆቴል ሊደርስ እንድሚችል
አልገፀለትም። በስልክ ያነጋገረው ሩቅ ይሁን ከቅርብ ቦታ ሆኖ ይሁን አይሁን አያውቅም ለማንኛውም ከቀጠሮ ቦታ ቀድሞ መድረስ ነበረበትና ስልክ ከደወለበት ሱቅ ጀምሮ እስከ ኒያላ ሆቴል የመኝታ ቤት ቁጥር ሃያ አራት ድረስ ያለውን መንገድ በሩጫ ጨረሰው የፎቁን ደረጃዎች እንኳ በሩጫ ነው የረመረማቸው:: ክፍሎ ደርሶ በሩ ላይ ሰው ያለመቆሙን ሲያረጋግጥ ብቻ እፎይ አለ፡፡ ወደ ክፍሉ ከመግባቱ በፊት ሽንጥና ሽንጡን ይዞ በመቆም የሩጫ ትንፋሹን ጨረሰና በሩን ከፍቶ ወደ ውስጥ
👍91
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሃምሳ_አንድ


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ


...«እታች ቡና ቤት ውስጥ ሻይ እየጠባሁ እጠብቅሀለሁ፡» ተረጋግተህ ለባብስና ና
በዚሁ ተስማምተው ስዩም ከፎቁ ላይ ወደ ታች ወደ ቡና ቤቴ ወረደ.
በልሁ ግን ከመደናገጡና ከመቸኮሉ የተነሳ የአለባበስ ቅደም ተከተሉ ሁሉ ጠፋበት። ሳይፀዳዳና ሳይተጣጠብ ልብሱን ለባባሰ ሲያስታውስ የሚቀሩት ነገሮች አሉ።እንደገና መፀዳጃ፡ ከዚያም ወደ ፀጉር ማበጠር ግን ሁሉም ነገር በችኮላና በጥድፍያ ነው።
ሁሉንም ነገር እንደምንም ጨራርሶ ወደ ሆቴሌ ተንደርድሮ ሲወርድ ስዩም ያዘዘውን ሻይ ጠጥቶ ጨርሷል ፡፡ በልሁም” እንዲጠጣ ጋበዘው በልሁ ግን እሺ አላለም"፡ ይልቁንም የስዩምን የሻይ ሂሳብ ለመክፈል ተሽቀዳደመና ከፈለ፡፡ ከቡና ቤቱ ወጡና በስተግራ በኩል ወደ አባ ሻውል በሚወስደው ሰፊ
የአስፋልት መንገድ ላይ ወደ አስቻለው ቤት ጉዞ ተጀመረ፡፡ ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ተኩል አካባቢ ሆኗል፥
በልሁ ከስዩም ጋር አብሮ እየተራመደ ሳለ እግሮቹ በፍርሀት
ይንቀጠቀጣሉ፡፡ ከንፈሮቹ እየደረቁ ደጋግሞ በምላሱ ያርሳቸዋል፡፡ ጭራሽ ከስዩም እኩል ከጎኑ ሆኖ ለመራመድ እየፈራ ወደ ኋላ ቀረት ቀረት ይላል፡፡ብዙ ከተጓዙ በኋላ አንዲት የሀገር ልብስ የለበሱ ሴት ወይዘሮ አንዲት ልጅ እግር ቢጤ ሴት ዘንቢል አስይዘው ከፊትለፊት ሲመጡ አዩአቸው:: ከጥቂት ርምጃዎች በኋላ ይበልጥ ተቀራረቡ፡፡በኋላም ተገናኙ
«በጠዋት ወዴት እማማ አብረኸት?» ሲል ስዩም ቀድሞ ጠየቃቸው፡፡
«ለገበያ ወደ ኣባ ሻውል፡፡» አሉት ወይዘሮ አብረኸት በእጃቸው
ስዩምን ሰላም እያሉ በአይናቸው ደግሞ በልሁን እየተመለከቱ።
የት እንደሚያውቁት የሚያሰላስሉ ይመስላሉ፡፡
«የተዋወቁት፣ የአገር ወዳድ ወንድም ነው::»አላቸው ስዩም ፈገግ ብሎ ሁለቱንም ተራ በተራ እየተመለከታቸው፡፡
«አገር ወዳድ የኛ?» አሉ ወይዘሮ አብረኸት አሁንም በልሁን ትኩር
ብለው እያዩት::
«አዎ»
«ከአሁን ቀደም አላየሁህም እንዴ የኔ ልጅ?» ሲሉ ጠየቁት በልሁን::
«አይተውኛል፡፡ ከጥቂት ቀናት በፊት ከቤትዎ ጠላ ጠጥቻለሁ፡፡
«እኮ የሚሲዮኖችን ሀኪም ቤት የጠየከኝ?»
«አዎ»
«ዋይ የአገር ወዳድ ወንድም ኖረሀል እንደ? ታዲያ ገልፀህ አትነግረኝም" ኖሯል እንዴ ልጄ ቤቱን እኮ አሳይህ ነበር። ከኔም ጋር ብዙም አንራራቅ፣ ያው የጎረቤት ያህል ነው።
«አላወቅሁን የኔ እናት»
ወይዘሮ አብረኸት ወደ ስዩም ፊታቸውን መለስ አድርገው «ግን አገር ወዳድ ከኔ ቤት እልም ብሎ
መጥፋቱ ምን ሆና ይሆን ስዩሜ»? ለወትሮው እንኳ እኔ ጋር
ብቅ ሳይል አይውል አያድርም ነበር፡፡ ወይስ ያ ያመኛል የሚለው ነገር እየጠናበት ሄደ? ይኸው ዓይኑን ከአየሁት ሶስት ወይም አራት ወር ሊሞላኝ ነው።»አሉት
«እያመመው ነው እማማ አብረኸት»
«በቃ ደከመው?»
«መሰለኝ፡፡» አለ ስዩም በዓይኑ ሰረቅ አድርጎ በልሁን እያየ፡፡
የወይዘሮ አብረኸትና የስዩም ቃለ ምልልስ ለበልሁ የመርዶ ያህል
አስደንጋጭ ነበር፡፡ ብቻ ጣልቃ መግባት አልፈልግም፡፡ የሆዱን በሆዱ እምቅ አድርጎ የመጨረሻውን ለማየት በፍርሀት ይጠብቃል፡፡
ወይዘሮ አብረኸት ደረታቸውን በቡጢ መታ መታ እያደረጉ «ልጄን!ልጄን! ልጄን » ካሉ በኋላ «እስኪ ከተመቸኝ ዛሬ ከሠዓት በኋላ ብቅ እላለሁ፡አሊያም ነገ መጥቼ አየዋለሁ፡፡» ብለው ተሰናብተዋቸው ወደ ግቢያቸው አመሩና ስዩምና በልሁም መንገዳቸውን ቀጠሉ፡፡
በልሁና ስዩም የያዙትን የኮረንኮች መንገድ በመቀጠል ወደ ታች
ሲወርዱ ከወይዘሮ አብረኸት ቤት መድረሳቸውን በልሁ ልብ አለ፡፡ በዚያው ልክ ወደ አስቻለው ቤት መቃረባቸውን ተረዳና ልቡ የድንጋጤና የፍርሃት ከበሮ ይመታ ጀመር፡፡ የወይዘሮ አብረኸትን ቤት አልፈው ጥቂት ከተጓዙ በኋላ
ስዩም በግራ በኩል የሚገኝ አንድ አቋራጭ መንገድ ይዞ ታጠፈ፡፡ በልሁም ተከተለ፡፡ ጥቂት ከተራመዱ በኋላ ስዩም አሁንም በሌላ የግራ ኣቅጣጫ በሚወስድ መንገድ ይዞ ወደ ላይ ታጠፈ፡፡ በልሁ አሁንም ተከተለ፡፡ በፕላን
የተሰሩ አምስት ቤቶችን አልፈው ስዩም የስድስተኛውን ቤት የውጭ በር አንኳኳ፡፡
በዚህ ጊዜ በልሁ ሁለመናውን ላብ አጠለቀው፡፡ ትንፋሹ በረከተ፡፡
ደረቱ ወጣ ገባ ሆዱ ሞላ ሞሽሽ ይል ጀመር፡፡ በሩ እስኪከፈት ድረስ ሽንጥና ሽንጡን ይዞ በመቆም አንዴ ወደ መሬት ሌላ ጊዜ ወደ ሰማይ እያየ ተቅበጠበጠ፡፡ የአስቻለው መገኘት ነገር እንደ ህልም እልም ብሎ ይጠፋ
እየመሰለው ልቡ ቷ ቷ ቷ ይል ጀመር፡፡
የውጪው በር ተከፈተ፡፡ ፊትለፊት ከጥርብ ድንጋይ የተሰራ ዘመናዊ
ቪላ ቤት ለዓይናቸው ገጭ አለ፡፡ በረንዳው በብረት ፍርግርግ ተሰርቶ ነጭ ቀለም የተቀባ፡ የበርና መስኮቶቹ መስታወት ነጣ ባለ መጋረጃ አሸብርቀው የጥሩ
ኗሪዎች መኖሪያ የሚመሰል ነው:: ግቢው ተስተካክሎ የተደለደለ፡ በየአጥሩ አጠገብ የአበባ ተክሎች
የሚታዩበት እምር ድምቅ ያለ ነው።
ስዩም ወደ ዢላው አላመራም። በስተግራ በኩል ወደ ጓሮ በሚወስድ ቀጭን የእግር መንገድ ይዞ ተራመደ። በልሁም ተከተለው። በጓሮ በኩል አራት ክፍሎች ያሉት ረጅም የስነርቪስ ቤት አለ፡፡ የተሰራው ከጥርብ
ድንጋይ ቢሆንም ነገር ግን ሲሚንቶ የሌለው ደረቅ ካብ ነው፡፡ የአራቱም ሰርቪስ ክፍሎች በር መዝጊያቸው የቆርቆሮ ነው ስዩም መካከል ላይ ከሚገኙት ክፍሎች
ወደ አንዷ ተራመደና ገና በሩ ላይ እንደደረሰ «እንዴት አደርክ አገር
ወዳድ? ሲል ወደ ውስጥ ተናገረ፡፡ ቤቱ ገርበብ ብሎ" ተከፍቷል።
ከውስጥ በኩል ለስዩም ሰላምታ የተሰጠው የምላሽ ድምጽ ግን በተለይ ለበልሁ እጅጉን አስደንጋጭ ነበር እጅግ የደከመ እጅግ የሰለለና የአስቻለው ሊሆን ይችላል ብሎ ለማመን በጣም የሚያስቸግር ነበር፡፡ «ይመስገነው፡፡ ደህና ነኝ ስዩሜ!» የሚል ድምፅ ወጣ ከውስጥ በኩል፡ ግን ደግሞ ድምጽ እንደሚወጣ ላልጠበቀ ሰው ፍፁም ሊሰማ የማይችል ሁኔታ። የበልሁ ጆሮ ቀድሞ ባይ ኖሮ ሰው የተናገረ ሰለመሆኑ ባልታወቀው ነበር።
«እንዴት ነው ሻል አላለህ?» እያለ ስዩም ወደ ውስጥ ገባ በልሁ
ምንም አልተሻለኝም ስዩሜ፣ አሁንማ ከመኝታዬም ለመነሳት ሰው ሊያስፈልገኝ ነው፡፡ እየደከመኝና እያቃተኝ ሄደ፡፡ » የሚል ድምጽ ከውስጥ
ተሰማ፡፡ በዚህ ሰዓት በልሁ በር ላይ ቆሞ በፍርሀት ዓይን ወደ ውስጥ አየት ያደርግ ጀመር፡፡ ከራስጌው በኩል ክራንች ግድግዳ ተደግፎ አየ፡፡ በራስጌ ኮመዲኖ ላይ የምግብ ሳሀኖች ይታያሉ፡፡ ቀጥታ ወደ ታማሚው ሲያይ በግራ ፊቱ ላይ ጠባሳ ታየው፡፡ ነገር ግን ትራስ ላይ ካረፈው የታማሚው ጭንቅላት
በቀር ወደ ታች ያለተ ሰውነቱ ፍጹም ያለ አይመስልም፡፡ ከድምጹ መድከምና መሰለል በተጨማሪ የታማሚው ሰውነት ኣልቆ ከእልጋው ላይ የመጥፋቱ ነገር
ያ ሰው በእርግጥ አስቻለው ስለመሆኑ የበልሁ ልብ ሊያምን አልቻለም፡፡
«ስማ አገር ወዳድ! ዛሬ ደግሞ ዘመድ ዘዳድ ይዤልህ መጥቻለሁ፣ እስቲ እንደ ምንም ብለሀ ቀና በል፡ : " አለ ስዩም አልጋው ስር ቆሞ ታማሚውን
በተኛበት ቁልቁል እያየ::
«የኔ ዘመዶች እዚህ ድረስ አይመጡም፡፡» አለ ታማሚው ከውስጥ፡፡
👍8
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሃምሳ_ሁለት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ


....አስቻለውም እያለቀሰ በሀሳብ ደግሞ ወደ ዲላ ነጎደ፡፡ የሔዋንን አኳኋን
በእዝነ-ልቦናው ይመለከትው ጀመር፡፡ ከዓይኗ የሚፈሰው እንባዋ በስሜት ቆጠቆጠው:: የታሰረችበት እግር ብረት የእሱን እጅና እግር ሲከረክረው
ተሰማው፡፡ በዚህ ጊዜ አንዳች እንግዳ ስሜት ተፈጠረበትና ተነስ! ሂድ! ብረር ወደ ሲዳሞ!! » አለው።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ታፈሡ እንግዳሰው ከተፈጠረች ጀምሮ እንደ ሰሞኑ በሀሳብና በጭንቀት መንፈሷ ተናውጦ አያውቅም፡፡ ችግሩ የጀመራት የሀምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ
ስለ አስቻለው አጠቃላይ ሁኔታ በዝርዝር ከገለፀላቸው ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡ በልሁ አስቻለውን ፍለጋ ወደ አስመራ ከሄደ በኋላ ደግሞ ብሶባት ሰንብታለች፡፡ስጋቷም
በልሁ አስቻለውን ያገኘው ይሆን ወይስ ያጣው ይሆን? ቢያገኘው
እሺ ብሎ ይመጣላት ይሆን? ቢመጣስ የሔዋን ስሜታዊ ምላሽ ምን ሊሆን ይችል ይሆን? ከሚል ስጋትና ፍርሀት የሚመነጭ ነው፡፡
በእነዚህ አሳሳቢ ጉዳዮች በቂ ምላሽ ሳታገኝላቸው ውስጥ ውስጡን ሲበሏት፤ ሲያስጨንቋትና ሲያሳስቧት ድፍን አሥራ ሰባት ቀናት አልፉ፡፡ ዛሬ ግን ከሁሉም ነገር መቋጫ ቀን ላይ ደርሳለች፡ በልሁ አስቻለውን ፍለጋ ወደ
አስመራ ከሄደበት ቀን ጀምሮ ሲቆጠር አሥራ ስምንተኛ ቀን በእለተ ቅዳሜ፡፡
በተለይ ሔዋን በማታውቀው ሁኔታ ታፈሡ እንግዶች አሉብኝ
በማለት ማለዳ ተነስታ የድግስ ስራ ጀምራለች፡፡ ስጋና የመጠጥ ዓይነቶችን ጨምሮ በርካታ የምግብ ሸቀጦችን ገዝታ ሔዋንና ትርፌን በስራ ወጥራቸዋለች፡፡ ከአንድም ሁለትና ሦስት ምድጃዎችን በመጠቀም ይከትፋሉ፣ ያቁላላሉ፣ ይቀቅላሉ፡፡
የታፈሡ እጆች በስራ ይጠመዱ አንጂ ቀልቧ በቤት ውስጥ ወይም
በስራው ላይ አልነበረም፡፡ ሀሳቧ ሁሉ ይበታተናል፡፡ ከሔዋንና ከትርፈ ጋር የምትለዋወጠውን ጭውውት ከልቧ አታዳምጠውም፡፡ ብትስቅ እንኳ ሳቋ ለዛ የለውም፡፡ ለጭውውቱ የምትሰጠው ምላሽ ከርእሰ ጉዳዩ ጋር ብዙም አይጣጣምም፡፡ አልፎ አልፎ ከሀሳቧ ብንን ስትል ብቻ •ጭውውቱን እንደ አዲስ
ትጀምረዋለች፡፡
በግምት ከቀኑ አምስት ሠዓት አካባቢ ሳይሆን አይቀርም ታፈሡ ሌላ አስፈሪና አስደንጋጭ ክስተት ተፈጠረባት፡፡ ነገሩ የመነጨው ከወደ ሔዋን አካባቢ ነው፡፡
ሔዋን በልሁ አስቻለውን ፍለጋ ወደ አስመራ ስለመሄዱ አታውቅም፡፡ምናልባት አስቻለው ወደ ዲላ ባለመመለስ አቋሙ የፀና እንደሆነ፡ ወይም ጭራሽ ያልተገኘ እንደሆነ ደስታ በሽታ ሆኖ እንዳያሳቅቃት ሁኔታው ለእሷ
ድብቅ ነበር፡፡ በልሁ ቤተሰብ ሊጠይቅ ወደ ደብረ ብርሃን እንደ ሄደ ነው የተነገራት፡፡ እናም የበልሁን መምጣት የምትጠብቀው ከደብረ ብርሃን
እንደሚሆን አድርጋ ነው፡፡ ታፈሡን አናግራ ያስደነገጠቻትም ከዚሁ ጋር በተያያዘ ነው፡፡
ታፈሠዬ!ስትል ጠራቻት ሔዋን ትርክክ ባለ የከሰል ፍም ላይ
የተጣደ ድስት በረጅም ማማሳያ እያማሰለች፡፡
«ወዬ የኔ ወርቅ አለቻት ታፈሡ ወደ ሔዋን ዞር በማለት በዚያች
ሰዓት የሶፋ ጌጦች እያስተካከለች ነበር፡፡
«ዛሬ ሕልም አየሁ»
«ምን ዓይነት ሕልም ሔዩ?»
«በልሁ ከደብረ ብርሃን የመጣ ይመስለኛል፡፡ መንገድ ላይ ከረሜላ ገዝቶ ሲያላምጥ ቆይቶ ኖሮ ልክ እዚህ ሲደርስ የከረሜላዋን እላቂ ከአፉ
አውጥቶ ይሰጠኝ ይመስለኛል፡፡ ግን እጄ ላይ ሊያስቀምጣት ሲል ድንገት አምልጣኝ መሬት ላይ ትወድቅበታለች ብፈልጋትም አጣታለሁ፡፡ ወዲያው ደግሞ እኔም ያለሁበት ቦታ ይጠፋኛል፡፡» አለችና «ፍችው ምን ይሆን
ታፈሡዬ”? ስትል ጠየቀቻት፡፡
ኣ? አለች ታፈሡ ድንገት ሳታስበው፡፡ በሁለት እጆቿ ሽንጥና
ሽንጧን በመያዝ ቆማ ሔዋንን አተኩራ ታያት ጀመር፡፡
«መጥፎ ህልም ነው እንዴ ታፈሠዬ»
ለነገሩ የህልም ጥሩና መጥፎ የለውም፡ ህልም እንደ ፈቺው ነው ይባል የለ አለችና አሁንም ስሜቷን እፍን እድርጋ ወደ ሶፋ ማስጌጥ ስራዋ ተመለሰች፡፡
ግን ደግሞ ሃሳባ ሁለ ጥቅልል ብሎ ወደ ትናንት ምሽት ሁኔታዋ ነጎደ፡፡

የታፈሡ እንግዳሰው የትናንት ምሽት ሁኔታ የተለየ ነበር፡፡ ሰበቡ
በልሁ አስቻለውን ይዞ ዲላ ከተማ መግባቱ ነው:: በልሁ እስቻለውን ይዞ ከቀኑ ስምንት ሠዓት አካባቢ ዲላ እንደገባ በቀጥታ ወደ ታፈሡ ቤት ይዞት መሂድ አልፈለገም:: አማሆ ተብሎ በሚጠራው ሆቴል ውስጥ አሳረፈው፡፡ ለዚህ
ምክንያቱ አስቻለው አሁን በሚገኝበት ሁኔታ ላይ ሔዋን ብታየው ሊደርስባት
የሚችለውን የመንፈስ ስብራት በምን መልኩ መቀነስ እንደሚቻል ከታፈሡም ሆነ ከሌሎች ጋር መመካከር የሚያስችል ጊዜ ለመግዛት ነበር፡፡
በዚሁ መሠረት በዕለቱ ከአመሻሸ አስር ሰዓት አካባቢ ታፈሡ ወደ
ሆቴሉ ጎራ እንድትል በሚስጥር ላካባት፡፡ እሷም ጥሪውን ስትሰማ ከመደንገጧ የተነሳ ምን እንዳደረገች ሳይታወቃት የቤት ልብሷን እንደለበሰች፣ ነጠላ
ጫማዋን እንዳደረገች ብፌ ላይ ጣል አድርጋት የነበረች የአንገት ልብሷን ብድግ አድርጋ ነበር ወደ ሆቴሉ የበረረችው፡፡ 'ሰዎች ተጣልተው ድረሽልኝ ብለውኝ ነው' ብላ ባትናገር ኖሮ ያበደች መስሏቸው ሔዋንና ትርፌም
በተከተሏት ነበር፡፡ ብቻ ወደተነገራት ሆቴል ሮጣ ስትደርስ ወደ አልቤርጎው ማለፊያ አቅጣጫ እንኳ ጠፍቷት ነበር፡፡ በአመላካች እርዳታ እንደ ምንም
ገባች:: ፊትለፊት ወደ አልጋ ክፍሎች ስትመለከት በልሁ፣ መርዕድና የሃምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ከአንድ የአልቤርጎ ክፍል በር አጠገብ በረንዳ ላይ ቆመው አየች። እጅግ በሚያስገርም ጩኽት በልሁዪ !» ስትል ከርቀት ተጣራች።
ረጋ በይ ታፈሥ፡፡» አላት በልሁ ከአሯሯጧ በተጨማሪ የጥሪዋ
ድምፀት ውስጣዊ ስሜቷን አስረድቶት፡፡
ታፈሡ የበልሁን ማሳሰቢያ ከቁብ አልቆጠረችውም፡፡ ጆላላ የቤት ውስጥ ቀሚሷን ወደ ጉያዋ ሰብሰብ አድርጋ በመሮጥ ከመሀላቸው ጥልቅ አለች።
ወዲያው በበልሁ አንገት ወስጥ ተሸጉጣ ገና የአስቻለውን ሁኔታ ሳታውቀው በመባባት ስሜት ስቅስቅ ብላ ታለቅስ ጀመር።
«አይዞሽ ታፈሥ» አላት በልሁ እሱም ፊቱን በትከሻዋ ላይ እስደግፎ በእጁ ጀርባዋን እያሻሽ፡፡
«እናስ በልሁ?» አላችው ታፈሡ፡፡ የአስቻለውን ሁኔታ በድፍኑ
መጠየቋ ነው:: አሰቻለውን እገኘኸው? ይዘኸው መጣህ? ብሳ በዝርዝር ብትጠይቀው ምናልባት ምላሽ አሉታዊ ቢሆን ብላ ሰጋች፡፡
«እስቲ ነይ ወደ ውስጥ ግቢ፡፡ አለና በልሁ ወዳ አልቤርጎው ክፍል ፊቱን መልሶ ወደ ውስጥ ተራመደ፡፡ ታፈሡ ከፍርሀቷ የተነሳ በጥንቃቄ እርምጃ ከኋላው ተከተለችው፡፡ የሀምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌና መርዕድም ወደ ክፍሉ ገቡ።
ታፈሡ ከክፍሉ ውስጥ ገብታ ወደ አልጋው ስትመለከት አንድ ሰው
ተኝቶ አየች፡፡ ከአንገቱ በታች ያለው ሰውነቱ አልጋው ላይ የሚታይ
አይመስልም፡፡ የድዱ ስጋ አልቆ ጥርሶቹ ገጥጠዋል፡፡ የፊቱ ላይ አጥንቶችም እንደዚሁ፡፡ ዓይኖቹ እንባ አቅረው ሲያዩዋት አየች፡፡ የግራ ፊቱ ጠባሳ ያ የሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ የገለጸውን መልክ ያንፀባርቃል፡፡ ታፈሡ ያ ሰው
አስቻለው ስለመሆኑ ማመን ቢያዳግታትም በተለይ የፊቱ ጠባሳ፣ የግራ ዓይኑ
ልትጠፋ የደረሰች መሆኗ፣ የግራ ጆሮው ልጣፊ ስጋ መስሳ መታየቷና ከራስጌው በኩል ግድግዳ ተደግፎ የቆመ ክራንች መታየቱ የግዷን እንድትቀበለው አደረጋት፡፡ ብቻ አሁንም ጨርሳ ላለማመኗ ምስክር የሚሆን
👍8
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሃምሳ_ሦስት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ

....አስቻለውን የማገናኛውም ቀን ተወሰነ በማግስቱ ሰዓቱ ደግሞ ምግብ ተሰራርቶ ካለቀ በኋላ ወደ ሰባት ወይም ስምንት አካባቢ፡፡ በሚገናኙም ጊዜ የሔዋንን ልቦና ማደነጋገሪያ ዘዴ ተፈጠረ ከዚህ በኋላ ነበር ታፈሡ ወደ አስራ ሁለት ሰአት አካባቢ ወደ ቤቷ የተመለሰችው.

የዛሬው የድግስ ሽርጉድም የዚሁ ዕቅድና ፕሮግራም እንዱ አካል
መሆኑ ነው የሔዋን ህልም ግን የታፈሡን ልብ የባሰ አሸበረውና በባሰ ስጋት ውስጥ ገባች ይቺ ልጅ የዋህ ናትና አምላኳ ምን እየነገራት ይሆን? በማለት፡፡
ያም ሆኖ የድግሱ ስራ ቀጠለ፡፡ በያይነቱ ተካፋፍለው ይሰሯቸው የነበሩ የወጥ ዓይነቶች ሁሉ ደረሰ ቤት ተወለወለ፡፡ ተስተካከለ፡፡ ጊዜውም ደረሰ፡፡ ልክ ከቀኑ ሰባት ሠዓት ተኩል፡፡
የሚመጡትን እንግዶች በውል የምታውቅ ታፈሡ ብቻ ናት፡፡ ትርፌም ዋናው እንግዳ አስቻለው መሆኑን ታውቃለች፡ ታፈሠ ትናንት ማታ በሆነ ሰበብ ወደ ውጭ ጠርታ ለሔዋን ፍንጭ እንዳትሰጥ አስጠንቅቃ የአስቻለውን መምጣት በጆሮዋ ሽክ ብላታለችና፡፡ ሔዋን ግን ምንም ዓይነት ፍንጭ አልነበራትም፡፡ እሷ የምትጠብቀው የማታውቃቸውን የታፈሡን እንግዶች ብቻ ነው። ነገር ግን በዚያ ሠዓት ይመጣል ብላ ያላሰበችው ነው፡፡ ነገር ግን
ድንገት ከሁሉም ቀድማ ዓይኗን ወደ ውጭ በር ጣል ስታደርግ
የምታውቀውና የምትናፍቀው
ነገር ግን በዛ ሰዓት ይመጣል ብላ ያላሰበችው እንግዳ ብቅ ሲል አየችው።በልሁ ቡላማ ሱሪ በነጭና ሰማያዊ ቡራቡሬ
ሽሚዝ ለብሶ ነጣ ያለ ጃኬቱን ትከሻው ላይ አንጠልጥሎ
በፍጥነት ርምጃ እየገሰገሰ ወደ ታፈሡ ቤት መጣ፡፡
«እንዴ! ታፈሠዬ! ባልሁዩ መጣ!» አለች ሔዋን በልሁን ፍልቅቀቅ ብላ
እያየችና ጆርዋን እነታፈሡ ለሚሰጧት መልስ አቁማ::
«መጣ?» ብላ ታፈሡ ቶሎ ብላ ወደ በሩ በመራመድ ላይ ሳለች በልሁ ወዲያው ከች አለ።
«ታዲያስ! እንደምናችሁ?» እያለ እንደ አዲስ ሊስማት ወደ ታፈሡ
ተጠጋ::
«እንኳን ደህና መጣህ በልሁዬ?» አለች ታፈሡም አንገቱን እቅፍ
አድርጋ እየሳመችው፡፡
«ሔዩ?» አለ በልሁ ወደ ሔዋን እየተመለሰ::
«አቤት በልሀዬ!»
ደጋግመው ተሳሳሙ:: በልሁ ልክ እንደ ታፈሡና ሔዋን ትርፌንም
ከሳማት በኋላ ወዲያው ንግግር ጀመረ፡፡ የሮጠና የቸኮለም ይመስል እንደ ማለክለክ ይቃጣዋል፡፡ «እንዴት ነው፣ አዲስ ስሜት አይነበብብኝም?»
«ይመስላል፡፡ ግን ምንድነው?» አለችው ታፈሡ ዓይኖቿ በፍርሀት
እየተርገበገቡና ልቧ ከወትሮው እጥፍ እየመታ»
«አስመራ ደርሼ መጣሁ፡፡»
«እ» አለች ታፈሡ የደነገጠች መስላ ለመታየት እየሞከረች፡፡
«አስቻለውን እግኝቼ ይዤው መጣሁ፡፡»
በልሁና ታፈሡ እርስ በርስ የሚተያዩ ይምሰሉ እንጂ በዓይናቸው ሰረቅ እያረጉ በማየት የሚሰልሉት የሔዋንን ስሜት ነው::
ሔዋን የበልሁን
አስቻለውን እግኝቼ ያዤው መጣሁ የሚል ቃል ስትሰማ ልከ ሳያስብ
ሳይጠረጥር በኃይለኛ ጥፊ ድንገት ጆሮውን እንደተመታ ሰው ሰማይና ምድሩ ተቀላቀለባት፡፡ ዓይኗ ፈጠጠ፡፡ ጥርሷ ገጠጠ፡፡ አፏም ያለ ፍላጎቷ ቧ ብሎ
ተከፈተ፡፡ በአጠቃላይ የአንጎሏ የማሰብ ሥርዓት ተዛባ፡፡ በድን ሆነች፡፡
በልሁ ለጥያቄ ፋታ በማይሰጥ ፍጥነት ቶሎ ቶሎ ይናገር ጀመር ግን አንድ ነገር ልንገራችሁ
አስቻለው በድንገተኛ አደጋ ምክንያት አንዳንድ የአካል ጉዳቶች ደርሰውበታል፡፡ በእጅና በእግሩ ላይ የፕላስቲክ ልጣፎች
ይታያሉ፡፡ ለጊዜው የሚሄደውም በክራንች ነው፡፡ ፊቱም ላይ ትንሽ
ተጎድቷል:: ነገር ግን የፕላስቲክ ቆዶ ጥገና በተባለ የህክምና ጥበብ በአጭር ጊዜና በአስተማማኝ ሁኔታ ሁሉም ነገር ወደነበረበት ሁኔታ እንደሚመለስ
ሀኪሞች አረጋግጠውልናል፡፡ አለና አሁንም ፈጥኖ በመቀጠል «ልብ በሉ! በዚሁ የህክምና ጥበብ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ህክምናውን በተሟላ የሰውነት ስጋ ላይ ማድረግ ስለማይቻል አስቻለው በጣም በጣም እንዲከሳ ተደርጓል፡ለህይወት ማቆያ ብቻ እንጂ በቂ ምግብ አይወስድም፡፡ የመክሳቱም ምክንያት ይኸው ብቻ ነው፡፡ ከስቶ ስታዩት ሌላ ነገር መስሏችሁ እንዳትደነግጡ፡፡ እሺ!»
ፊቱን ወደ ውጭ በር መለስ ሲያደርግ አስቻለውና አጃቢዎቹ
ተከታትለው ብቅ ሲሉ አያቸው፡፡ ወዲያው ደግሞ «ያው አስቻለው እየመጣ ነው፡፡ ወጣ በሉና በእልልታ ተቀበሉት፡ : » አላቸው፡፡
በእርግጥም ሰዎች አስቻለውን አጅበው ከውጭ በር ላይ ደርሰዋል፡፡
ታፈሡና ትርፌ እልልታውን እያቀለጡ ወደ እንግዶቹ ሮጡ፡፡ ሔዋን ግን ከቆመችበት ንቅንቅ አላለችም፡፡ እንደ እንጨት ደርቃ ቀረች፡፡ በልሁ ከተናገረው ቃል እንዱንም አልተረዳችም፡፡ ቀድሞ ነገር ጆሮዋ እንኳ ስለመስማቱ ማንም እርግጠኛ አይደለም፡፡
«ሔዩ» ሲል ጠራት በልሁ ሁኔታዋን ተጠራጥሮት ለመሰለል ያህል፡፡ሔዋን ልክ እንደ አእምሮ ዘገምተኛ ሰው የቴለና የጀለ በሚመስል ድምጽ «እ» አለችው በደመ ነፍስ፡፡
ብቅ ብለሽ አስቻለውን አትቀበይውም እንዴ?»
ሔዋን ግን አሁንም ዝም፡፡ በልሁ ራሱ ክንዷን ያዝ አድርጎ የመጎተት
ያሀል ወስዶ በር ላይ ቢያደርሳትም ከዚያ ማለፍ አልቻለችም፡፡ እንዲያውም
የቤቱን በር የግራ በኩል መቃን ሙጥኝ አለች፡፡ ዓይኗ ከውጭ ከሚመጡት ሰዎች ላይ አልተነቀለም፡፡ ታፈሡና ትርፌ አስቻለውን በመሳም ላይ ናቸው፡፡
ነገር ግን ምን እየተደረገ እንዳለ ለሔዋን አይታዉቃትም፡፡ የአስቻለው አጃቢዎች ካሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌና መርዕድ ሌላ ሦስት የቀድሞ የስራ
ባልደረቦቹ ናቸው ከአስቻለው ጋር
ስድስት ታፈሡና ትርፌ ሴጨመሩ
ስምንት ሆነዋል፡፡ ለሔዋን ግን የሰዎቹ ብዛት አንድ ከተማ ነዋሪ
በሙሉ ሰላማዊ ሰልፍ የወጣ
መስሎ ነው የሚታያት ሰዎች ስለመሆናቸው እንኳን በውል አይታወቃትም በሰመመን ውስጥ
የሚታይ የአንዳች ፍጡራን
ትርምስምር መሰለዠሎ እንጂ፡፡ በህልም ይሁን በእውን ባለየላት ሁኔታ ሰው ሊመስላት ያልቻለ አንድ ፍጡር በክራንች የሚጎተት መስሎ ይታያታል ጤነኛው እግሩ እንኳ በውል እግር አይመስልም፡ ሱሪው ብቻ ይወዛወዛል፡፡
የፈቱም አጠቃላይ ገፅታ አስፈሪ ጭምብል ያጠለቀ መሰላት ሰው ስለመሆኑ እንኳ እርግጠኛ ሳትሆን
አስቻለው አጠገቧ ደረሰ።
«ሔዩ» አላት አስቻለው ከጤነኛውም ከጉዳተኛውም ዓይኖቹ እንባውን እያፈሰሰ፡፡ ለሔዋን ግን ድምጹ እንኳ የሰው አልመሰላትም፡፡ ስልል ያለና
በጣም የደከመ ነው፡፡ መልስ ሳትሰጠው ፍጥጥ ብላ ብቻ ትመለከተው ጀመር፡፡
«አላወቅሽኝም ሔዩ?»
«ሔዋን አሁንም ዝም፡፡»
«ሳሚው እንጂ ሔዩ!» አለች ታፈሡ አስቻለውን ደገፍ አድርጋ ከጎኑ በመቆም በአሁን ሠአት ከታፈሡ በኩል ለቅሶ የለም። በሔዋን አኳሀን ደንግጣ ሁለመናዋ ደርቋል፡፡ በልሁም ሆነ ሌሎቹ በትኩረት የሚከታተሉት
የሔዋንን ስሜት ነው፡፡ ያሰጋቸውም የልብ ህመምተኛ መሆኗ ነው፡፡
ሔዋን አሁንም በዚያ በተረበሽ ስሜት ውስጥ ሆኗ ልትገደል የተከበበች አውሬ ይመስል ዓይኗን በሁሉም ላይ ከማንከራተት በስተቀር ምላሽ መስጠት አልቻለችም አስቻለው ራሱ «ቀድም የፈራሁት ይሄን ነበር
ዘመዶቼ! አለና እያለቀሰ ፈቱን በሔዋን ትክሻ ላይ አሳረፈው፡፡ እዚያው ላይ ተደፍቶ ይንሰቀሰቅ ጀመር፡፡
👍7
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሃምሳ_አራት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ

....በቀድሞው የዲላ ከተማ አውቶብስ መናኸሪያ ፊትለፊት በግምት በሀምሳ ሜትሮች ርቆ ከታች በስተምዕራብ በኩል የሚገኘው «አባይ ፏፏቴ ሆቴል በዕለተ እሁድ ምሽት ለዘወትር ደንበኞች ዝግ ሆኖ ለየት ያሉ እንግዶች ሊስተናገዱበት ተዘጋጅቷል፡፡ ለክብር እንግዶች የተዘጋጀው መድረክ የተለያዩ
ቀለማት ባሏችው መብራቶች አጊጧል፡፡የድግሱ ታዳሚዎች ከመድረኩ ፊትለፊት በተዘጋጀላቸው ወንበርና ጠረጴዛ ላይ ተቀምጠዋል፡፡ ከታዳሚዎቹ
መሀል የሚበዙት የፖሊስ ሰራዊት አባላት ናቸው። መለዮ የለበሱት
ይበልጣሉ፡፡ ጠረጴዛዎቻቸው በነጭ ጨርቅና በላስቲክ ተሸፍነው ያልተከፈቱ
የቢራ ጠርሙሶች ተደርድረውባቸዋል አስተናጋጆች የመስተንግዶ ስራቸውን
ለማከናወን ጥግ ጥግ ይዘዋል:: በትላልቅ ድምጽ ማጉያዎች የሚለቀቀው ሙዚቃ አዳራሹን ያነቃንቀዋል፡፡ የድግሱ ታዳሚዎች ፊትለፊት በመድረኩ
ላይ የተዘረጋውን ልዩ ሶፋ እየተመለከቱ የክብር እንግዶችን ይጠባበቃሉ፡፡ልክ ከምሽቱ አስራ ሁለት ሠዓት ተኩል ላይ
ሙዚቃው ድንገት ቆመ:: በሙዚቃው ጩኸት ውስጥ እየተጨዋወቱ ይሳሳቁ የነበሩ እንግዶች ዝም ዝም አሉ፡፡ ቤቱ ፀጥ ረጭ አለ፡፡ ወዲያው አንድ የዝግጅት አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሳይሆን የማይቀር ጠየም ያለ ልጅ እግር ሰው ከሆቴሉ ጓዳ በኩል ወጥቶ ወደ መድረኩ ወጣ።
«እንዴት ዋላችሁ እንግዶቻችን?» አለ ፈገግ ባለ ሁኔታ እጆቹን
እያፍተለተለና በሆቴሉ ውስጥ የታደሙ እንግዶችን በሙሉ በዓይኑ እየቃኘ፡፡
«እግዚአብሔር ይመስገን!» የሚል ምላሽ ተሰጠው ከታዳሚዎቹ፡፡
«በቅድሚያ ጥሪያችንን አክብራችሁ ጊዜያችሁን መስዋት አድርጋችሁ በዚች ሰዓትና ቦታ ስለተገኛችሁልን በዕለቱ የክብር እንግዳና በዝግጅት አስተባባሪ ኮሚቴ ስም ምስጋናዬን ማቅረብ እወዳለሁ፡፡»
ከታዳሚዎቹ በኩል ሞቅ ያለ ጭብጨባ ተቀበለው::
«አመሰግናለሁ፡፡» አለና «ዛሬ በዚች ሠዓትና ቦታ የመገናኘታችን
ዓላማ ለሁላችንም ግልጽ ነው፡፡ እንደሚታወቀው ሰዎች በአንድ ወይም በሌላ አጋጣሚ ይተዋወቃሉ:: የትውውቁ መሰረት በአንድ አካባቢ መኖር፡ የስራ
ባህሪና ቦታ፣ ወይም ሌላ ሌላም ሊሆን ይችላል፡፡ ነገር ግን መተዋወቅና መግባባት ወይም መዋደድ እንዳለ ሁሉ በሆነ አጋጣሚ መለያየትም ይኖራል፡፡
የመለያያው መንገድና ዓይነትም እንደዚሁ ብዙ ነው፡፡ በጠብና በጥላቻ፣ በሞት በስራ ዝውውር... ወዘተ ሊሆን ይችላል፡፡ በአጠቃላይ በደስታም በሀዘንም
የተዋወቁና የተዋደዱ ሰዎች ሊለያዩ ይችላሉ::
«ዛሬ ልናከብረው የተዘጋጀነው የመለያየት በዓል ግን የሰላምና የደስታ ነው፡፡ አንድ የስራ ባልደረባችን ዕድገትና ሹመት አግኝቶ ከመካከላችን
በመለየት ወደ ሌላ አካባቢ ሊሄድ ስለመሆኑ ሁላችንም እናውቃለንና እስቲ ስለወንድማችን ደስታ መግለጫ ይሆን ዘንድ ሁላችንም እንዴ እናጨብጭብ»
ሲል በፈገግታ ዓይን እያየ ታዳሚዎቹን ጠየቃቸው።
አሁንም ሞቅ ያለ ጭብጨባ ተቀበለው::
“አመሰግናለሁ፡፡ ከዚህ ቀጥሉ የክብር እንግዳችን ከቅርብ ዘመድ
ወዳጆች ጋር በመሆን እየመጣ ስለሆነ ወደ መድረኩ በሚያልፍበት ሰዓት ሁላችንም ከተቀመጥንበት ብድግ በማለት በጭብጨባ እንድንቀበለው እያሳሰብኩ በኔ በኩል የመክፈቻ ንግግሬን እዚህ ላይ አበቃለሁ፡፡አመሰግናለሁ፡፡» በማለት እጅ ነስቶ ወደ መጣበት አቅጣጫ ተመለሰ፡፡
የድግሱ ታዳሚዎች የክብር እንግዳውን በዓይናቸው የሚጠብቁት ከውጭ በር በኩል ነበር፡፡ ነገር ግን ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ በዚያ የመክፈቻ
ንግግር ባደረገው ሰው እየተመራ ከወደ ጓዳ በኩል ድንገት ብቅ አለ፡፡ የክብር እንግዳው የሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ነው፡፡ የምክትል መቶ አለቅነትና
የወላይታ አውራጃ ፖሊስ አዛዥነት ሹመት እግኝቶ ሊሄድ ነው፡፡ ድግሱም እሱኑ ለመሸኘት ነው።
የቀድሞው የሀምሳ አለቃ፡ ዛሬ ግን የምክትል መቶ አለቅነት ማዕረጉን
መለዮ ለብሶ ከአስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢው ኋላ ተከትሎ ብቅ ሲል ታዳሚዎች በሙሉ ከተቀመጡበት ብድግ በማለት በማያቋርጥ ጭብጨባ ተቀበሉት፡፡
ከእሱ ኋላ ነጫጭ የሀገር ልብሷን ለብሳ እንቁጣጣሽ የመሰለችው ታፈሡ እንግዳሰው! ቀጥላ ሔዋን: ከእሷ ኋላ ደግሞ መርዕድ እሽቱ በመሆን ተከታተሉ፡፡ ሁሉም ለታዳሚዎች የጭብጨባ አቀባበል እጅ እየነሱ ወደ
መድረኩ አመሩ፡፡ ምክትል የመቶ አለቃ መኮንን ዳርጌ እና ታፈሡ ጎን ለጎን እንዲሁም ሔዋን ከታፈሡ ቀኝ በኩል፣ መርዕድ ደግሞ ከምክትል መቶ አለቃ
መኮንን ዳርጌ ግራ ጎን በመቆም ታዳሚዎች እንዲቀመጡ ጋበዙ፡፡ ታዳሚዎች ጭብጨባቸውን አቁመው ሲቀመጡ የክብር እንግዶችም በየቆሙበት አቅጣጫ ተቀመጡ፡፡ ሙዚቃው ተለቀቀ፡፡ አስተናጋጆችና የድግሱ አስተባባሪዎች በታዳሚዎች ፊት ተቀምጠው የነበሩ ጠርሙሶችን መክፈት ጀመሩ፡፡ መስተንግዶው ጦፈ፡፡
በርካታ የድግሱ ታዳሚዎች ታፈሡንና መርዕድን በከተማ ውስጥ ያውቋቸዋል፡፡ ሔዋንን ግን እንኳንስ በውል የሚያውቃት በዓይኑም ዓይቷት የሚያውቅ ስለመሆኑ ኣንድም ታዳሚ እርግጠኛ አልነበረም፡፡ ከሁሉም በላይ ታዳሚዎቹን ያስደነቃቸው በምን ምክንያትና ሰበብ ታፈሡና መርዕድ የምክትል መቶ አለቃ መኮንን ዳርጌ የቅርብ ዘመድ ወዳጆች ሊሆኑ እንደቻሉ
ነው፡፡ ያም ሆኖ ሁሉም በየሆዳቸው 'ወይ ጉድ! የሰው ዘሩና የግንኙነት መስመሩ እኮ አይታወቅም በማለት በግርምት አለፉት፡፡
የግብዣው ሥነ-ሥርዓት ቀጠለና በምክትል መቶ አለቃ መኮንን ዳርጌ ቀዳሚነት፡ በእነታፈሡ ቀጣይነት የብፌ ምግብ መነሳት ጀመረ፡፡ ታዳሚዎችም
በየአቀማመጥ ቅደም ተከተላቸው ተከታትለው ምግብ አነሱ፡፡ እራት መበላት ተጀመረ፡፡ የመጠጡ ግብዣም ተከታተለ፡፡ ምግብ ተበልቶ አብቅቶ፡ ሳህኖች
ከየጠረጴዛው ላይ ተነስተው: ጠረጴዛዎች በአስተናጋጆች ተወልውለው ካበቁ በኋላ መጠጡ ጭውውቱና የመዚቃው ጩኸት በቀጠለበት ሰዓት አሁንም
ለሁለተኛ ጊዜ ሙዚቃው ድንገት ቆመ፡፡ የታዳሚዎችም ወሬና ጫጫታ ወድያው ቆመና አዳራሹ ፀጥ ረጭ አለ ሰዓቱ በግምት ከምሽቱ ሁለት ተኩል አካባቢ ይሆናል፡፡ አሁንም ያ የመክፈቻ ንግግር ያደረገው ሰው ወደ መድረኩ ሲራመድ ታየ፡፡ ቀድሞ እንዳደረገው ሁለ ከታዳሚዎች ፊትለፊት በመቆም ታዴሚዎችን በፈገግታ እያየ።
«የተከበራችሁ እንግዶቻችን» ሲል ጀመረ፡፡ «ቀደም ሲል በመክፈቻ
ንግግሬ ላይ እንደጠቀስኩት የዛሬው ጉዳያችን የስራ ባልደረባችን የሆነው የቀድሞው የሃምሳ አለቃ ዛሬ ደግሞ...» እያለ ንግግሩን ጎተት በማድረግ ወደ
ኋላው ዞሮ ምክትል መቶ አለቃን ሳቅ እያለ ሲያይ ታዳሚውም ምክትል መቶ አለቃ መኮንን ዳርጌና እነታፈሡም ሳቁ።
«አፍሬም ፈርቼም ነው እኮ» አለ በመቀለድ ዓይነት::
ሳቅና ጭብጨባ ከታዳሚዎች ተቸረው፡፡
«አመስግናለሁ።» ብሎ እጅ ከነሳ በኋላ «በቀጣይ ሁለት ፕሮግራሞች አሉን፡፡ በመጀመሪያ የምንወደውና የምናከብረው ጓደኛችንና የስራ ባልደረባችን
ከመካከላችን ተለይቶ ሲሄድ ማስታወሻችን ያደርጋት ዘንድ ያዘጋጀንለትን ስጦታ ማበርከትና ከዚያ ቀጥሎም ምክትል መቶ አለቃ መኮንን ዳርጌ ስለ አግኘው
የማዕረግ ዕድገትና ሹመት እንዲሁም ከእኛ ከወዳጆቹ በመለየቱ ያደረበትን ስሜት አጠር ባለ ሁኔታ የሚገለጽበት ፕሮግራሞች ናቸው። በዚሁ ቅደም ተከተል ማከናወን እንዲቻል የአውራጃችን ፖሊስ አዛዥ የሆኑት መቶ አለቃ ብዙአየሁ አስራት ስጦታዋን እንዲያበረክቱልንና ምክትል መቶ አለቃም ወደ መድረኩ ጫፍ ቀረብ ብሎ እንዲቀበልልን ሁለቱንም እጋብዛለሁ። አመሰግናለሁ፡፡» ብሎ ከመድረኩ ወረደ።
👍113🔥1
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሃምሳ_አምስት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ

....«ታፈሡና ሔዋን የሚባሉ ካሉ በአስቸኳይ ቤት ድረስ ይምጡ። የሚል መልዕክተኛ መጥቶ ነው።» አለው፡፡
ምክትል መቶ አለቃ መኮንን ዳርጌ መልዕክቱን እንደሰማ ወደነታፈሡ ዞር ብሎ ሲያይ ለካ የተነገረውን መልዕክት እነሱም ሰምተውት ኖሮ አቆብቁበው እያዩት ኖሯል። «ምንድነው ሃምሳ አለቃ?» በማለት ታፈሡ ከተቀመጠችበት ተስፈንጥራ ተነሳች፡፡ ከመደንገጧ ብዛት የቀድሞውን ሃምሳ አለቃ በቀድሞ ማዕረጉ ጠራችው።
«በአስቸኳይ ቤት ድረስ ኑ ተብለዋል ይላል።» አላት ራሱም የድንጋጤ ስሜት እየተነበበበት፡፡
«ኧረ ፍጠኑ ብለዋችኋል!» አለ መልዕክተኛው።
ታፈሡ፣ሔዋንና መርዕድ የምክትል መቶ አለቃውንም ሆነ የድግሱ
ታዳሚዎችን ፈቃድ መጠየቅ የሚያስችል ፋታ እና ጊዜ እላገኙም። በታፈሡ መሪነት የእሽቅድምድም ያህል ተከታትለው ከአዳራሹም ወጡና ወደ ታፈሡ ቤት ሮጡ።
በዚህ ጊዜ የደግሱ ድባብ ፍፁም ተለወጠ፡፡ ምክትል መቶ አለቃ መኮንን ዳርጌ ራሱ ግራ ገብቶት በአለበት ቆሞ ቀረ። ታዳሚዎችም አንዴ በር በሩን ሌላ ጊዜ ምክትል መቶ አለቃ መኮንን ዳርጌን በመመልከት ዓይናቸው ይንከራተት ጀመር፡ ከጥቂት ቆይታ በኋላ ግን ጥቂት ፖሊሶች ወደ ታፈሠ ቢት ሄደዉ
የሆነውን ነገር እንዲያጣሩ ታዘዙና የእነታፈሡን ዱካ ተከትለው ገሰገሱ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በዕሰተ ረቡዕ ከማለዳ ጀምር የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ቀውጢ ሆኗል። ሰበቡ የመኪና አደጋ ነው። አንዲት በተለምዶ ውይይት በመባል የምትታወቅ ታክሲ በርካታ
የመድሐኒዓለም አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን አሳፍራ ከትምህርት ቤቱ በር ላይ በመድረስ ቁማ በማራገፍ ላይ ሳለች አንድ የፍሬን ችግር የነበረበት የከተማ አውቶብስ ከታክሲዋ ላይ በመውረድ ላይ የነበሩ ተማሪዎችን ጨፍልቃቸው ነው። በርካታ ሞተዋል፡፡ ሌሎች ፣ከፍተኛ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል። ከአደጋ ተረፉ የሚባሉ ተሳፋሪዎች
ብዙ አልነበሩም ከተማሪዎቹ በተጨማሪ ሌሎች መንገደኞችም የሞትና የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
የሞቱትም ሆኑ የቆሰሉት ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ነው የተወሰዱት። ይህ አደጋ ከጠዋቱ ሁለት ሰአት አካባቢ ደርሶ እረፈድ እያለ ሲሄድ ደግሞ የአደጋ ሰለባዎች ዘመድ አዝማድ ከቦታው እየደረሱ የሆስፒታሉን ቅጥር ግቢ በለቅሶ በእሪታና በጩኸት እያደበላለቁ የጨበጣ ውጊያ የሚካሄድበት ጦር ሜዳ አስመስለውት አርፍደዋል። ሕይወታቸው ያላለፈ የአደጋው ሰለባዎች የስቃይ ጩህት ከቤተሰቦቻቸው ኡኡታ ጋር ተላምዶ ያ ግቢ ግባተመሬት የሚፈፀምበት የመቃብር ቦታ መስሏል፡፡ የሆስፒታሉ ሐኪሞችና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች ስራ በዝቶባቸው የሚይዙትን የሚጨብጡትን አተው ተዋክበዋል። ቀደም ሲል አልጋ ይዘው ይታከሙ ህሙማን ጨርሶ ተረስተዋል ችግሩ ለአስታማሚዎች ተርፎ እነሱም በጭንቀት ወለሌ ይላሉ።
ከዚህ ችግር ተካፋይ አንዱ በልሁ ተገኔ ነው አስቻለው ደሞ ከሰሞኑ ጀምሮ ህመሙ ፀንቶበት ሰንብቷል በዚያው ልክ በልሁ አጠገቡ በመቆም የሚንከራተቱ የአስቻለውን አይኖች አከታትሎ ማየት የዘወትር ስራው ሆኗል። ሀኪም አይቶት በወጣ ቁጥር ለውጥ ያመጣለት እየመሰለው ቢጓጓም ነገር ግን የአስቻለው ሁኔታ ከዕለት ወደ እለት እያስፈራው ሄዷል።
አደጋው በደረሰበት እለትም የአስቻለው ነፍስና የበልሁ ዓይኖች ተፋጠው አረፈዱ ወትሮም እንደሚያርገው ሁሉ አሰሰቻለው በተኛበት አልጋ አጠገብ ቆሞ ቁልቁል እየተመለከተው ሳለ ከኮሪደር አካባቢ ድንገተኛ ጩህት ተሰማ ቀአደጋው ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባት የነበረች ልጅ ብዙም ሳትቆይ ህይወቷ አልፎ ኖሯል።ህልፈቷ የተነገራቸው ዘመዶቿ በዚያው አስቻለው በተኛበት ክፍል በር አካባቢ ጩህታቸውን ይለቃሉ የሟች ስም 'ሔለን' ኗሯል አልቃሹም " ሔለን ሔለንዬ ሔሉ" እያሉ ይጯጯሁ ጀመር።
ይህን የለቅሶ ጩኸትና የማቿን ስም እስቻለው በሰመመን ውስጥ ሆኖ ሰምቶት ኖሯል። በልሁ ጠጋ ብሎ እጁን እንዲያዘው ጠቀስው፡፡ በልሁ ጠጋ እንዳለት አስቻለው እጁን ያዝ አደረገና፡-
ሔዋን ምን ሆና ሞተች በልሁ?» ሲል ዓይኑን እያንከራተተ ጠየቀው።
«ምን?» አለ በልሁ ድንግጥ በማለት፡ ስለየትኛዋ ሔዋን ነው
የምታወራው አስቻለው?» ሲል መልሶ ጠየቀው፡፡
አስቻለው ልክ እንደ ጃጀ ሽማግሌ የበልሁን እጀ ጥብቅ አድርጎ በመያዝ ዓይኖቹን እያንከራተተ አትዋሸኝ በልሁ ሔዋን ሞታለች።» አለው።
በልሁ የባስ ተረበሸ፡፡ እሱ በጤናማ ስሜቱ የማቿ ስም ሔለን ስሰመሆኑ እርግጠኛ ቢሆንም ለእስቻለው ግን «ሔዋን የተባለ እንደሚመስለው ሲረዳ ስለ
አስቻለው የእሱ መንፈስ ተሰቃየ። ግን ብቻ ያስተማመንኩ መስሎት
«ሔዋን እኮ በአሁኑ ሠዓት ያለችው ዲላ ነው። ለሃምሳ አለቃ መኮንን
ዳርጌ ሽኝት እንደ ሄደች ገና አልመጣችም። ምናልባት ዛሬ ወደ ማታ ላይ ትመጣና ታያታለህ። አሁን የሚያለቅሱት ሰዎች ሔለን የምትባል ልጅ ሞታባቸው ነው።
ሔዋን አይደለም የሚሉት፡፡ አለው በማከታተልና ሽብር በተቀላቀለበት አነጋገር።

አስቻለው የበልሁን ንግግር ከቁብ አልቆጠረውም። ምናልባትም በትክክል እየሰማው ላይሆን ይችላል። የራሱን ንግግር ብቻ ቀጠለ።
«እኔንም እሷ በተቀበረችበት ቤተክርስቲያንና መቃብር ውስጥ ቅበሩኝ፡»
«ቀድሞ እሷ መች ሞተች?»
አስቻለው አሁንም የራሱን ቀጠለ። «በመቃብራችን ላይ እኛ በከንቱ
ሞተናል፥ እናንተ ግን አደራ ብለህ ፃፍበት፡»አለው የበልሁን እጅ ጭምድድ አድርጎ እንደያዘ፡፡
የበልሁ ጭንቀት ከመጨረሻው ጫፍ ላይ ደረሰ፡፡ ከአስቻለው ጋር መነጋገሩ ዋጋ እንደሌለው አመነ፡፡ ቢሆንም ባይሆን ሐኪም መጥራት እንዳለብት ታየው፡፡
እጁን ከአስቻለው እጅ ውስጥ እንደምንም ፈልቅቶ አላቀቀና በፍጥነት በሩን ከፍቶ ወጣ።
ከነርሶቹ ክፍል በር ላይ እንደደረሰ አስቻለውና በአካባቢው የተኙ
ህሙማንን የምትከታተለዋ ነርስ ከውስጥ ወደ ውጭ ስትወጣ አገኛት። የተለያዩ መድሐኒቶችን ይዛ ወደ ድንገተኛ ክፍል በመሄድ ላይ ነበረች።
«እመቤት ልጁ እኮ ደከመብኝ» አላት በልሁ ትንፋሹ በርክቶ እያለከለከ።
ነርሷን ሲስተር ብሎ መጥራት ሲገባው እመቤት ማለቱ መለማመጡና በአክብሮት
ማሳየቱ ነበር።
«ከወትሮው የተለየ ምን ለውጥ አየህበት» ስትል ነርሶም ከእርምጃዋ ቆም ብላ ጠየቀችው። የበልሁ ሁኔታ ትኩረቷን ስቦታል።
«ይቃዥ ጀመር»
«ምን እያለ?»
«ዝም ብሎ የሆነ ያልሆነውን»
«እስቲ ቆይ! ይህን መድሀኒት ድንገተኛ ክፍል ላድርስና መጥቼ አየዋለሁ።» ብላው ወደ ድንገተኛ ክፍል ለመሄድ ከፎቅ ወደ ምድር ቤት ወረደች።
በልሁ ከስጋቱና ከፍርሀቱ የተነሳ ነርሷን ሊያምናት አልቻለም። እድራሻዋ እንዳይጠፋበት ለመከታተል ተከትሏት ወረደ። የገባችበትን ክፍል አረጋግጦ
እስከምትመለስ ድረስ እዚያው በገባችበት ክፍል በር ላይ ቆሞ ይጠብቃት ጀመር፡፡
ነርሷ በዚያ በድንተኛ ክፍል ውስጥ ብዙ አልቆየችም፡፡ መድኒቶችን አድርሳ ከክፍሉ ወጣች። በሩ ላይ በልሁን ስታገኘው ስሜቱ ገብቷት ፈገግ
አለችና «የምቀር መስሎህ ነው አይደል» አለችው
👍7
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሃምሳ_ስድስት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ


....የኑዛዜውን ምስጢር እንዳገኘው ሁሉ የልብ እይታ
ተሰማው በረጅሞ ተንፍሶ ራሱን ወዘወዘ።
ወዲያው የሰው ኮቴ ተሰማው፡፡ ወደ አስቻለው ክፍል ዞር ብሎ ሲመለከት ሁለቱ ዶክተሮች ተከታትለው ሲወጡ አየ፡፡ ምን ሊሉት እንደሚችሉ በመጓጓት ትኩር ብሎ ሲመለከታቸው ያ የአስቸለው ዶክተር በእጁ ጠቀስ አደረገውና በልሁም ጠጋ ብሎ- ጆርውን ሲሰጠው «አይዞህ ደህና ነው፡፡» በተረፈ ነርሷ የምትሰጥህን ትዕዛዝ ተቀበል፡፡ ብሎት ወደ ቢሮው አመራ። በልሁ ከነርሷ የሚሰጠውን ትዕዛዝ
ለመስማት ጓጉቶ ከክፍሉ የምትወጣበትን ጊዜ በመጠባበቅ ላይ ሳለ ነርሷ ወዲያው ወጣች፡፡ በሩን መልሳ ዘጋችና እንዲያውም ቆለፈችው፡፡ በልሁ ወደ እሷ ሊራመድ ማሰቡን አውቃ “እዚያው ጠብቀኝ፡፡ አለችው፡፡
በልሁ ቀጥ ብላ ቆመ። ዓይኖቹ ግን በነርሷ ላይ ትክል አሉ። ልቡ
ደንገጥ አለና ከንፈሮቹን በምላሱ ያርስ ጀመር፡፡ ነርሷ ግን ወደ በልሁ ስትጠጋ ፈገግ ብላ ነው፡፡ በዚያው ፈገግታ በተላበሰ ሁኔታዋ የበለጠ ጠጋ አለችውና፡
«ደነገጥክ እንዴ?» ስትል ጠየቀችው።
«ፈራሁ»
«አይዞህ! ምንም አይለው። አሁን አንድ ለየት ያለ መድሐኒት
ሰጥተነዋል። መድሐኒቱ ግን የህመምተኛውን እንቅስቃሴና የትኩረት መለዋወጥ
አይፈልግም። ቢያንስ ለግማሽ ሰዓት ዕረፍትና የሀሳብ መረጋጋትን ይጠይቃል።ስለዚህ እንተም እንዳትገባ ብዬ በሩን ቆልፈዋለሁ፡፡ እኔ እስከምጠራህ ድረስ ዘወር
ዘወር እያልክ ራስህን አዝናና። እንዲያውም እታች ወርደህ ወደ ክበብ አረፍ ብትል ጥሩ ነው፡፡ እኔም ስፈልግህ በቀላሉ አገኝሀለሁ፡፡» አለችው ረጋ ባለ መንፈስ::
በልሁ አሁንም በረጅሙ ተነፈሰ፡ ምራቁንም ዋጥ አደረገ። የነርሷን
ትዕዛዝ መቀበል እንዳለበት ከዶክተሩም ተነግሮታል። የነርሷም አነጋገር ለዛ የተላበሰ ነው፡፡ ነርሷ ወደ ቢሮዋ ስታመራ እሱም ሶስተኛ ፎቅ ምድር ላይ ወደሚገኘው የሻይ ክበብ አመራ፡፡
ግማሽ ሰዓት ለበልሁ የግማሽ ዓመት ያህል ረዘመባት፡፡ ነገሩ ከጠዋቱ ጀምሮ ምንም ነገር በአፉ አልገባምና ርሀብም ተሰማው። ሰዓቱ ደግሞ ወደ ስድስት
ተኩል ተጠግቷል፡፡ ሻይና ኬክ አዘዘ። ፉት ፉት፣ ጎረስ ጎረስ አደረገ፡፡ ቡናም አዘዘ። ሲቀርብለት አሁንም ፉት ፉት እለ። ግን የሁሉም ነገር ጣዕም እህል ውሃ
አይለውም፡፡ ማጣፈጫው ስኳር ይሁን ጨው አይለይለትም፡፡ ትኩስ ይሁን ቀዝቃዛ
አይሰማውም፡፡ ስሜቱ ሁሉ በአስቻለውና በሁኔታው ዙሪያ ብቻ ሆነ፡፡ በመሀል የሔዋንና የመርዕድ ጉዳይ ትዝ አለው፡፡ «ዛሬም ላይመጡ?» አለ ለብቻው
አየተነጋገረ። «ትንሽ ልጠብቃቸውና ስልክ ደወዩ ችግራቸውን ማወቅ አለብኝ፡፡ ብቻ ነርሷ ስለ አስቻለው የምትነግረኝ ነገር ሰላም ይሁን!» እያለ በማሰብ በማሰላሰል ላይ ሳለ ሠዓቷ ደርሶ ደርሶ ኖሮ ያቺ ነርስ ድንገት ከፋቱ፡ ከች አለች፡፡
«ሻይ ቡና አልክ?» አለችውና ወንበር ሳብ አድርጋ ከአጠገቡ ቁጭ አለች።
«ሁሉንም አደረጉ።» አላት በልሁ በፍርሀት ዓይኑ እየተመለከታት፡፡
ነርሷ ቡና አዘዘች። እስከሚተርብላትም ድረስ ከበልሁ ጋር ጭውውት ጀመረች። ተነጋገሩ። በእርግጥም ብዙ ተወያዩ፡፡ ተግባቡም፡፡ ከዚያች ሠዓት ጀምሮ በልሁ ወደ ዲላ ስልክ ለመደወል ቁርጥ ሀሳብ ላይ ደረስ፡፡ ከነርሷ ጋር ተሰነባበቱና
እሷ ወደ ስራዋ ስትመለስ በልሁ ደግሞ ከሆስፒታሉ ቅጥር ግቢ ወጥቶ ስልክ ፍለጋ ኪዎስኮችን ይፈልግ ጀመር ።
ስልክ እንዳገኘ በቀጥታ መርዕድን ለማግኘት ወደ የአፄ ዳዊት ትምህርት ቤት ደወለ፡፡ ለጊዜው መርዕድን አላገኘውም፡፡ ስልኩን ያነሳው ሰው ግን መርዕድን
ከእሥር ደቂቃ በኃላ ሊያቀርብላት እንደሚችል ነገረው። ለካ ዛሬም ወደ እዲስ አበባ ጉዞ አልጀመሩም፡» አላ በልሁ፡፡ ዲላ ውስጥ እንድ ችግር እንዳለ ገመተ።የሆዱን በሆዱ አድርጎ ወደ አውራጃው ግብርና ጽህፈት ቤት ደወለ። በጓደኞቹ አማካኝነት ለታፈሡ ሊደርስለት የሚፈልገውን መልዕክት አስተላለፈ። ይህ ሁሉ
እስከሚሆንበት ድረስ መርዕድን የቀጠረበትም ሰዓት ደረሰና እንደገና ወደ አፃ ዳዊት
ትምህርት ቤት ደወለ፡፡ መርዕድን አገኘው፡፡

«ሀሎ መርዕድ!»
«እቤት!»
«አንተና ሔዋን እንመጣለን ያላችሁት ባለፈው ሰኞ አልነበረም እንዴ?
ነገር ግን ይኸው እስከዛሬ አልተነሳችሁም፡ ችግሩ ምንድነው?» ሲል ጠየቀው፡፡
መርዕድ ለበልሁ ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት የተቸገረ በሚመስል አኳኋን ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ እያለና እንደ መርበትበትም እያደረገው
«እ..እ...ካለ በኋላ «ግን እኮ ነገ ልንመጣ ተነስተናል» አለው፡፡

«ሔዋን ግን ደህና ናት?»
«ደህና ናት፡፡»
«በእርግጥ ነገ ወደዚህ ወደ አዲስ አበባ ጉዞ ትጀምራላችሁ?»
«እዎ፡ ወስነናል፡፡ »
«ጥሩ እሺ! እንዳትቀሩ፣ እጠብቃችኋለሁ፡፡»
ስልኩ ከሁለቱም በኩል ተዘጋ፡፡
የዕረቡ ቀትር ተጠናቀቀ፡፡ ፀሐይ ወደ ምዕራብ አዘቀዘቀች፡፡ አድማሱን አቅልታ ጨረሯን ወደ ላይ በመዘርጋት እሷ ግን ቁልቁል ሸሸች፡፡ ብላ ብላም ጠለቀች፡፡ ለዓይን መያዝም ጀመረ፡፡ የመንገድ መብራቶች ሁሉ በሩ፡፡
ከዋክብትና ጨረቃ የሰማይ ቦታቸውን ተረከቡ፡፡ ሌሊቱም ተጀመረ፡፡
ለበልሁ ግን ሁሉም ነገር ያው የቀን ያህል ነው፡፡ እንቅልፍ
እላስፈለገውም፡ በንቃት ያስባል፡፡ ዕረፍትም አላገኘም፡ የዘመኑን የሰዓት እላፊ ገደብ በራሱ ጥሶ በአዲስ አበባ አውራ መንገዶች ላይ ከወዲያ ወዲህ ይሯሯጣል፡፡ በሀሳቡ ሔዋንና መርዕድ ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ ስንቅና
ልብሳቸውን ሲያዘጋጁ እየታየ እሱ ደግሞ ማለዳ ተነስቶ ወደ ዲላ ለመብረር የኮንትራት መኪና ለማግኘት ይለፋል ወደ እኩለ ሌሊት ላይ የሚፈልገውን የመኪና ዓይነት አገኘ፡ ፈጣንና ጠንካራዋን
ባለ እንድ ጋቢና ቶዮታ መኪና በእርግጥም ገና ጎህ ሳይቀድ
ተሳፈረባት ከጨለማው ቅልቅል ጉዞ ወደ ዲላ ጀመረ፡፡
ከአፍንጫው መገተር የተነሳ "መጥረቢያ ፊት ሊባል በሚችል ብቄ ባለሙያ ሾፌር በምትነዳው
ቶዮታ መኪና ማልዳ በመነሳት የአዲስ አበባ መንገዶችን በግላጭ አግኝታ እንደ ንስር ትወረወርባቸው ጀመር ከአዲስ
አበባ ወጥታ አቃቂን፡ ዱከም፣ ደብረዘይትንና ሞጆን አቆራርጣ ወደ ሲዳሞ መስመር መታጠፊያውን መንገድ ስትይዝ ገና ከጠዋቱ አንድ ሰዓት እንኳ
በወጉ አልሞላም፡፡ከፍጥነቷ የተነሳ ከገመድ የተረፈው የሸራ ሽፋኗ
እየተርገበገብ ሳጮህ የእውቅ ዜመኛ ፉክራ ይመስላል፡፡ ጋቢናዋ በዝምታ ተሞልቶ ከኋላ በኩል ግን ድንቅ የተፈጥሮ ሙዚቃ እየተሰማባት ቶዮታዋ ወደ
ቆጋ ተጠጋች የአዋሽ ወንዝንም ገና በጠዋቱ ተሻገራቸው ከዚያም አልፎ ወደ አለም ጤና፡፡ ሾፌሩና በልሁ ለመጀመሪያ ጊዜ የተነጋገሩት ዝዋይ ከተማ ሊደርሱ ሲሉ ነው፡፡
«ስማ ሾፌር ቁርስ ያስፈልግህ ከሆነ ዝዋይ ከተማ ላይ አረፍ ብንል፡፡እሱን ካለፋን ዲላ ሳንደርስ የረባ ነገር አይገኝም፡፡» አለው በልሁ፡፡
«ለኔ ሳንይሆን ለአንተ ያስፈልግሃል፡፡ እኔ በጠዋት መብላት ብዙም አልወድም" : አንተ ቁርስ የምታደርግ ከሆን ልቁም» አለው ልክ እንደ
እንደ አፍንጫው ቅንድቡም ወጣ ወጣ ብሎ አስፈሪ ግርማ ሞገስ የተላበሰ ሾፈር፡፡
👍10🔥1
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሃምሳ_ሰባት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ


....ሔዋን በልሁን ስለ አስቻለው ሁኔታ ለመጠየቅ ፈራች። በአንድ በኩል ምላሹን ስትፈራ በሌላ በኩል ትክክለኛውን ሁኔታ ላይነግረኝ ይችላል የሚል ስጋት ያዛት። ነገር ግን ነገሩን ለማንሳት አንድ መላ መጣላትና ወዲያው ተጠቀመችበት።...
«አሁን ነገ ወደ አዲስ አበባ ስንሄድ የትርፌን መሞት ለአስቻለው እንነግረዋለን ወይስ....»ብላ ነገሯን በእንጥልጥል ተወችው።
በልሁ በፍጥነት መለሰላት «ይዋደዱ አልነበር እስካሁን ሆዱ ነግሮት ይሆናል።»አለና ዝም ብሎ በመስታወት ውስጥ ውጭ ውጭ ያይ ጀመር።
«ምናልባት ይደነግጥና አንድ ነገር ይሆናል ብዬ ፈርቼ እኮ ነው።» አለችው ሔዋን ስለ አስቻለው ሁኔታ ምርመራዋን ለመቀጠል።
«እስቲ እዚያው ስንደርስ እንደ ሁኔታው እናደርገዋለን።» እንደገና ፀጥታ። መኪናዋ ግን ሄደች፣ ነጎደች። ጩኮን አልፋ የዲላ ከተማ መዳረሻ ታየ።አንዳንድ ቤቶችም ብቅ ብቅ ማለት ጀመሩ። አንዳንድ ልቦች የፍርሃት ከበሮ ይመቱ ጀመር።መኪናዋ ግን ያለ ሀሳብ ናፍጣዋን እየጠጣች በረረች።የመጨረሻውን የለገዳራ ወንዝ ድልድይ ተሻግራ ከዲላ መውጫ የመጀመርያ ኬላ ፍተሻ ላይ ደረሰች።ደግነቱ ከአዲስ አበባ ወደ ዲላ ሲሄዱ ፍተሻ የለም። ያም የፍተሻ ኬላ ታለፈ። ዲላ ከተማን በሰሜንና በደቡብ ለሁለት የሚከፍለው ዳገተማ የአስፋልት መንገድ ተጀመረ ያም ቢሆን ከደቂቃዎች የበለጠ ጊዜ አልወሰደም። ልክ ሰባተኛ መንገድ ተብሎ በሚጠራው የጠጠር መንገድ ላይ ሲደርሱ በበልሁ አመልካችነት ቶዮታዋ ወደ ቀኝ ታጠፈች።ያ መንገድ በለቀስተኛ ተሞልቷል። ነጠላቸውን ያሸረጡ ሴቶችና ጋቢ የለበሱ ወንዶች አጥለቅልቀውታል። አንዳንዶቹ ወደ ታፈሡ ቤት አቅጣጫ ይሄዳሉ
አንዳንዶቹ ደርሰው የሚመለሱ ይመስላሉ። ሹፌሩ የገባው ነገር ነበርና የመኪናዋን ጡሩንባ ደጋግም ሲያንጧጧው ደርሰው ተመላሽ የነበሩ ለቀስተኞች ፊታቸውን ወደ ታፈሡ ቤት አቅጣጫ ይመለሱ ጀመር።
መኪናዋ ከታፈሡ ቤት የማያደርሰውን የመጨረሻ መንገድ ስትጀምር የታፈሡ ቤት አካባቢ ከነጉድጓዱ ብቅ አለ። ሁለት ድንኳን ተተክሎበታል። የሰው ነጭ ይርመሰመሳል። መኪናዋ ወደ ድንኮኑ ስትጠጋ ትልቅ ፎቶ ግራፍ ይዛ እንደ እብደት እንደ ስካር በሚያደርጋት ሴት እየተመራ ያ ሁሉ ሰው ወደ መኪናዋ ተንቀሳቀሰ። ህዝቡና መኪናዋ ሲገናኙ ሴትየዋ የታፈሡ እንግዳ ሰው፣ የያዘችው ፎቶ ግራፍ ደግሞ የአስቻለው ፍስሃ። ነገሮች ሁሉ ግልፅ ሆኑ፣ መርእድ ድንግጥ ሲል ሔዋን ደሞ ሁለመነዋ ደነዘዘ።መኪናዋ ከህዝቡ አጠገብ ስትደርስ ቀጥ ብላ ቆመች።ታፈሡ ወደ መኪናዋ የዕቃ መጫኛ ስትዞር በልሁ የጋቢናውን በር ከፈተና ዱብ አለ። በሩ ላይ ቆሞ ፈዝዞ ደንገዛ መንቀሳቀስ ያቃታትን ሔዋን እየተመለከተ«ሔዋን ፅኒ እንግዲህ! አስቻለው ሞቷል!» አላት።
ሔዋን ግን የሰማችው አትመስልም፣ ፍጥጥ ብላ ቀረች። በልሁ ትላንት መርዕድን በስልክ ባነጋገረበት ሰአት «ነገ ልንመጣ ተነስተናል»ሲለው 'እሺ ኑ' ብሎ
የመለሰለት በእርግጥም እንዲመጡና ልብ በሽተኛዋ ሄዋን መርዷዋን ከመስማቷ በፊት በእጁ እንድትገባለትና ሊፈጠር የሚችለውን አደጋ በእሱ እገዛ ለማስቀረት አስቦ ነበር። አሁን ግን ከዚያ አደጋ የሚያመልጥ አልመስል አለውና ደነገጠ
የሔዋን ፈዝዞ መቅረት አስፈራው። ብቻ የተቻለውን ያህል ለመሞከር በማሰብ መርእድ ገፋ እንዲያደርግለት ጠየቀውና ይበልጡኑ ግን እሱ እራሱ ስቅስቅ አድርጎ አቀፈና ወደ መሬት አወረዳት።
«ሔዩ» ሲል ጠራት ወደ ታች አዘቅዝቆ እያያት። ሔዋን ግን ዝም። ይልቁንም አይኖቿ ስልምልም እያሉ ከእቅፉ ውስጥ
ወደ ታች ወደ ታች ትንሸራተተበት ጀመር፡፡ በልሁ ፈራና በጩህት«ታፈሥ! ድረሽ ታፈሥ ድረሽ!»እያለ ይጣራ ጀመር። በቃል ታፈሱን እየተጣራ በእጁ ደግሞ ሔዋንን ለማቃናት ይጥራል ታፈሡ አልሰማችውም ። እሷ ራሷ በአስቻለው አስከሬን ሳጥን ላይ
ትንፈራፈራለች። ሔዋንን የሰው መዓት ከበባት። እየሆነች ያለችውን ነገር ለማየት አንዱ በሌላው ትከሻ ሳይ ሲንጠራራ አንዳንዱ ደግሞ «ዘወር በሉ! ገለል በሉ! አየር
ስጧት! አየር.…አየር እያለ ይጮሀል። ነገር ግን ሁሉም ነገር ምንም አልፈየደም፡፡ ሔዋን ላትመለስ እየሄደች ስለመሆኑ ምልክቶች ታዩ፡፡ እንቅስቃሴዋ ሁሉ ቆመ።

መርዕድ ለታፈሡ መልዕክት አድርሶ ኖሯል። ታፈሡ ያንን ሰው ሁሉ እየገፈታተረች ከመሀል ስትገባ በልሁ ቁጭ ብሎ በሁለት እጆቹ መሬት እየመታ ሲጮህ ሔዋን ደግሞ ዝርግትግት ብላ አገአቻቸው::
«ኣ» አለች አፏ ጉድጓድ መስሎ እስኪከፈት ድረስ። «እኮ ምንድን ነው!?» ካለች በኋላ ሜዳ ላይ ዝርር ያለችውን ሔዋንን ልክ እንደ ልጆች ቼ ፈረሴ ጨዋታ ጋለበችና የሔዋንን አገጭ ወዲያ ወዲህ እያገላበጠች አንቺ ሒዩ! አንቺ የኔ! አንቺ ሔዩ! ሐዩ ሔዩ!» ትላት ጀምር። ጀሮዋን በአፍና በአፍንጫ ላይ ብትለትምም ምንም ትንፋሽ አጣች፡፡ ጭራሽ እየቀዘቀዘች ሄደችባት፡፡
ታፈታሡ እንደዚያው ቼ ፈረሴ እንደጋለበቻት በሁለት እጆቿ ግራና ቀኝ መሬት እየመታች ዋይ! ዋይ! ዋይ! ዋይ አሁንም ደግማ «ዋይ! ዋይ! ዋይ! ዋይ!» ለሶስተኛ ጊዜ “ዋይ! ዋይ! ዋይ! ዋይ!» በዙሪያው ያለው ሕዝብ ሁሉ
በለቅሶ ተንጫጫ።
የሆነው ሁሉ ሆኗልና ቀጥሎ መሆን ያለበት መሆን ጀመረ፡፡ የሔዋን አስክሪን ከበልሁና ከታፈሡ እጅ ወጣ፡ የመጨረሻ ዝግጅት ለሚያደርላት
ለገናዦቿ ተላልፎ ተሰጠ። በታፈሡ ቤት በር ፊትለፊት በሚገኘው ሰፊ መንገድ ላይ የሚደረገው ረግዶ ግን ነዳጅ እንደተጨመረበት እሳት ይበልጥ ተቀጣጠለ፡፡
ከቀኑ ወደ ስድስት ሰዓት አካባቢ ሌላ አዲስ ከስተት ታየ፡፡ ትናንት በልሁ በመስሪያ ቤት ጓደኞች በኩል የእስቻለውን ሕይወት ማለፍ ለታፈሡ እንዲነገራት አድርጎ ነበርና ታፈሡም በተሰማት መሪር የሀዘን ስሜት መሀል የሔዋን አባትና እናት ትዝ ብለዋት ልጃቸውን ያላቅሷት ዘንድ በሔዋን በኩል ታውቀው በነበረ
የስልክ አድራሻ መልዕክቱ እንዲደርሳቸው አድርጋ ኖሯል። የሔዋን እናትና አባት መርዶውን እንደሰሙ ይበልጥ ያዘኑት ለልጃቸው ነበር፣ ሀዘኑን እንዴት
ትችለዋለች በማለት፡፡ መርዶውን ማታ እንደ ሰሙ ወደ ዲላ ለመብረር ሲዘጋጁ አድረው ክብረ መንግስት ወደ አለታ ወንዶ፡ ከዚያም ወደ ዲላ በመጓዝ ስድስት
ሰዓት አካባቢ በታፈሡ ደጅ እሚወርደው ሙሾ መሀል ገቡ፡፡ የሔዋን እናት ክንፋቸውን ዘርግተው እየሮጡ ወደ ሕዝቡ ሊቀላቀሉ የሚያሰሙት ጨኸት
«ልጄ! ልጄስ...! ልጄን አሳዩኝ! እሙዬን አገናኙኝ..» እያሉ ነው::
ምን እያሉ እንደሆነና ለጊዜሉ የራሳቸውን ማንነት ሕዝቡ ያልተረዳላቸው ቢሆንም ነገር ግን ቆየት እያለ ምስጢሩ ሲታወቅ የታፈሡ ጎረቤቶች ጠጋ ጠጋ
አሏቸው። ክንዳቸውን ከወዲያና እወዲሀ በመያዝ ቀስ ይበሉ! ረጋ ይበሉ ይሏትው ጀመር። እሳቸው ግን አሁንም «ልጄ የታለች? እሙዩ የታለች።ማለታቸውን ቀጠሉ። ባለቤታቸው አቶ ተስፋዬም ከኋላ ከኋላቸው እየተከተሉ ልክ እንደ ሔዋን እናት ይጮሀሉ፡፡ ያለቅሳሉ።
የታፈሡ ጎረቤቶች ሰብሰብ አሉና የሔዋንን እናት ወደ አንድ ገለጥ ወዳለ ቦታ ወስደው ትንሽ ለማረጋጋት እየሞከሩ በኋላ ስለሆነው ነገር ፍንጭ ሰጧቸው፡፡
👍13