#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ቀኑ ቅዳሜ ነው። ሴቬሊያ ከተማ ላይ አንዣቦ የከረመው ዳመና ተበታትኖ ሰማያዊው ሰማይ በፀሐይ ብርሃን ተጥለቅልቆ ኗሪው በደስታ ሲንቀሳቀስ ይታያል።
ሶራ ከመኝው የተነሳው ዘግየት ብሎ ሲሆን ከመኝታው ተነስቶ ሳሎኑ ሲገባ አብረውት የሚኖሩት ሁለቱ የክፍል ጓደኞቹ
ሞዛምቢካዊው ኢናሲዬ እና ሴኔጋላው ዲያንካ ሲከራከሩ አገኛቸው:
“...አየህ የኛ የአፍሪካውያን ችግር በእለት ችግሮቻችን ላይ ካልሆነ በህልማችን በሐሳባችን... ላይ በትዕግስት መወያየት
መከራከር አንችልም: በግልፍተኝነት ስለ ዛሬ እናወራለን ዛሬ በምንፈፅመው እናዝናለን ወይንም እንረካለን።
ዛሬን ከትናንትና ከነገ ጋር ማነፃፀር ስለማንችል መቻቻሉም ያቅተናል: እና እኛ አፍሪውያን ከጊዜ የቁም እስር እራሳችንን ነፃ
አድርገን ጊዜን መጠቀም ስንጀምር! ሽንፈትና ድልን ልዩነቱን ስናውቅ በቅድሚያ ችግሮቻችንን እንፈታለን…” አለ ሞዛምቢካዊው
ኢናሲዬ:
“…በሃሣብህ እኮ እስማማለሁ፡ ችግሩ ግን እንደ ቡችላ ያለው አይናችንን ለመክፈት ገና ስናስብ የሰለጠኑት ህዝቦች ባለፉት ጊዜያት ከተጠቀሙበት መሳሪያ በተሻለና በረከሰ የረቀቀ መረብ እየጠለፉ ይጥሉናል: ለዚህ መፍትሄው ምን
ይሁን ነው? እኛ ፊደል እንዴት እንቁጠር ስንል አንዱ እርስ በራሳችን እንማማር ሌላው የሰለጠኑት ህዝቦች እንዲያስተምሩን
እንለምን... ሲል ጊዜያት ከነፉ፤ የጥቁር ህዝብ ህልም እንደ
ኪሊማንጃሮ ተራራ ቢከመር ጠብታ ተግባር ካልወጣው! አንዱ ሌላውን ወንድሙን ገሉ ማቅራራቱንና መፎከሩን ካላቆምንና ራሳችንን መግዛት ካቃተን ጥሩ ተገዥ መሆን ይሻለናል” ብሎ
የምፀት ሳቁን ሳቀ ሁለቱም ተሳሳቁ፡
“ጥሩ! ማን በማን ላይ እንደሳቀ ዳኝነቱን ወደፊት
እስከገልፅ አንዴ ይቅርታ ይደረግልኝ..."
“ሶራ! ሁለቱም እንደተመካከሩ ሀሉ በአድናቆት ዞረው
ጠሩትና
ዛሬ ምነው ምሽግን አለቅም ብለህ ዋልህ? ያች ኢትዬ
ስፔናዊት የምትሰራው የቤት ስራም ሰጥታህ
ነበር መሰል ሞዛምቢካዊው ኢናሊዬ የጓደኛውን ጉልበት መታ አድርጎ ቤቱን
ለሁለት በሣቅ አነቃነቁት።
ከባድ የቤት ሥራ ነበር የሰጠችኝ፡ ጥያቄዋን ሽ ጊዜ አነበብኩት በቃሌ አነበብኩት! መልሱ ግን ጠፋኝ። ጥያቄዋን
ካለእሷ ሊመልሰው የሚችል የለም:"
“ስለዚህ መልሱን ከመምህርት ኢትዮ ስፔናዊት ለማግኘት
ልትሄድ ነዋ!” ነዋ!
ቶሉ መሄድ! የጠፋኝን ቶሉ ማወቅ ከዚያ ጎበዝ
ደቀ መዝሙሯ መሆን እፈልጋለሁ።” የሁለቱንም ትከሻ መታ መ+ አድርጎ። ወደ ውስጥ ገብቶ ለባብሶ ወጣና፡-
“አጭርና ያልተንዛዛ አስተያየት አላማረብኝም አላቸዎሸ በየተራ እያያቸው።
“መልሱን ካለ አንድ ሰው አይመልሰውም" ሲል ዲያንካ
“እሷም መምህርት ኢትዮ ስፔናዊት ብቻ ናት..." አለ ኢናልዬ
“ትክክል!'' ብሎ የኢናሲዬን ትከሻ መታ መታ አድርጎ በሩን ከፍቶ ሲወጣ ሳቃቸው ከኋላው ተከተለው
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሶራና ኮንችት ከተዋወቁ በኋላ ኮንችት ቤት ማድሪድ
በሚገኘው ፒካሶ ሆቴል... ደጋግመው ተገናኝተዋል። ኮንችት በሶራ ግልፅነት በጎደለው ይሉኝታ በተበተበው ባህሪው ብዙ ጊዜ ትበሽቃለች።
ሶራ መብላት ትፈልጋለህ?" ስትለው
“አንችስ?” ሲላት በብስጭት
"እፈልጋለሁ! ወይንም አልፈልግም። ስለእኔ እኔ ስለአንተ ደግሞ አንተ መመለስ በቃ። የአንተ መፈለግ አለመፈለግ ከእኔ ጋር ምን አገናኘው" ትለዋለች
“የዛሬ ግብዣ የኔ ነው"
“ጥሩ ስለግብዣ ሃሳብህ አመሰግንሃለሁ። የት ነው የምትጋብዘኝ?
“የት ልጋብዝሽ?”
“ኦ! - አምላኬ!” በንዴት ትጦፍና፦
“ሰውን ልትጋብዝ ስትፈልግ በቅድሚያ የት ምን
እንደምትጋብዘው አስብ እሽ ፊቷ በንዴት እንደቀላ ትነግረዋለች
“ምነው ዝም አልሽ?
“ለምን ጠየቅከኝ?
“ስለማትጫወቺ ስለማትስቂ...”
"ሰው ቤት ከመሄድህ በፊት ልትገናኙ መቻል አለመቻላችሁን ደውለህ ፈቃድ ጠይቅ ! እኛ ሰዎች ለስራ ለጨዋታ
ለእረፍት... የምንመድበው ጊዜ አለ:: ሰዎችን በፕርግራማቸው
እንዳይጠቀሙ እንቅፋት መሆን ትልቅ ሃጢያት ነው: ገባህ!” ትለዋለች።
“የያዝሽውን እቃ ልያዝልሽ?
“ለምን?
“ይከብድሻል…”
“ፖልፋቮር /ይቅርታ/ እኔ ጡጦ የምታጠባው ህፃን ልጅህ አይደለሁም የሚከብደኝን መጀመሪያውንም አልይዝም።እሺ
በንዴት ትንጨረጨርበታለች ሶራ ባህሪዋ ሙልጭልጭ ይልበታል ሲያዝንላት ሲንከባከባት ሲሞክርና እንዲቀራረቡ ጥረት ሲያደርግ? አባባሉን በተቃራኒ ተረድታ በግሳፄ የህሊና ድዱን በርግጫ
ታወልቀዋለች:
እሱ ግን ይችላታል: ሆዱ እየተቀየመ አንደበቱ ግን
ያልፋታል።
“ዲስኮ ዳንስ ቤት ብዙ መቆየት አልወድም"
“ሶራ! ከኔ ጋር ግን'ኮ አብረህ…"
“ላስከፋሽ ስላልፈለግሁ"
“እብድ ነህ! የማትፈልገውን ለኔ ብለህ የምታደርግ?”
“ብቻሽን ትቼሽ መሄድ ስላልፈለግሁ"
“በቃህ አንተ ኖርህ አልኖር ለኔ ለውጥ የለውም 7
ገባህ! መዝናናት ስፈልግ ዘበኛ አላስከትልም: ማንንም ካለፍላጎቱ እንደ
ከዘራ ቆልምሜ የኔ ምርኩዝ ማድረግ አልሻም.." ታፈጥበታለች።
አብሯት ለመሆን እንደሚጓጓው ሁሉ ከሷ መለየቱንም ይፈልገዋል: ልዩነታቸው ብዙ ነው።
ኮንችት ባህሪው ግልፅ
ነው ሣቋን አንደ ጥሩ ሙዚቃ በስሜት ይደንስበታል: ችግሩ ድንገት እሳት ወዲያው ውሃ
ትሆንበታለች:: እሳት ስትሆን ሊሸሻት ይፈልጋል! ውሃ ስትሆን ደግሞ እንደ ፀበል በጨዋታዋ ይጠመቃል!
ሶራ ሜዳ ይሁን ገደል ስሜቱ በደመ ነፍሱ ሲጋልብም እሷ
ለሁሉም ነገር ምክንያት ትፈልጋለች: እየተሞላቀቀች
ጭኖችዋን ፓንቷን.. ስታሳየውና ጉሮሮውን ስታስጮህበት ስሜቱን
ስታስነጥስበት ትቆይና መላውን ሳትለው ድንገት
“መተኛት እፈልጋለሁ" ትለዋለች።
ትንሽ አንጫወትም?"
...የሰው ፍላጎት ሊገባህ ይገባል እሽ?" ቀልቡን ገፋበት መኝታ ቤቷ ትገባለች። እሱም ወጥቶ ይሄዳል። ቤቱ ሲሄድ ግን
ህሊናው እረፍት ሲነሳው ሰውነቱ እንደ እሳት ሲቀጣጠልበት
መታጠቢያ ቤት ይገባና ቀዝቃዛ ሻወር ገላው ላይ ያፈሳል፡ ለአያቷ
አገር ለኢትዮጵያ ያላት ናፍቆት ግልፅነቷ ሳቋ… ተክለ ቁመናዋ
እያወዛወዘው ሲያንጨዋልለው ፍላጎቱ ለእሷ ያለው ቀረቤታ
ከጓደኝነት ያለፈ ይሆንበታል።
ኮንችት ደጋግማ
የነገረችው ስሜትህንና ፍላጎትህን አትደብቅ ነው። ስለዚህ እየዋለ ባደረ ቁጥር ናፍቆቱ ጤና ሲነሳው
ስሜቱን ሊገልፅላት አሰበ: ድፍረቱና አጋጣሚው ጠፍቶ ለቀናት ተሰቃዩ:: አንድ ቀን ግን ደፈረ:
“ኮንችት?”
“አቤት" ያ እንደ ንስር አይን ተልቆ የሚበረበረው አይኗ
ከመናገሩ በፊት እየበሳሳው ውስጠ ሚስጥሩን አየበት።
“አፈቅርሻለሁ አላት ባጭሩ። ኮንችት ግን ይህን ስሜቱንና አባባሉን ቀደም ብላ እንደተረዳች ሀሉ፡
“ለምን አፈቀርኸኝ? በአባባሉ ሳትደነቅ ጠየቀችው
ተቁነጠነጠ! ግልጽ ሁን ብላ ወትውታ ግልፅ ሲሆን ደግሞ ዓለምን ያስጨነቀ ጥያቄ “ለምን?" እያለች በማስቸገሯ ተማረረባት።
ለምን አፈቀርኝ? ደግማ ጠየቀችው
“አስተሳሰብሽ ደስ ይለኛል” አንገቱ ላይ እንደቆሙበት ውሻ አይኑ እየተቁለጨለጨ መለሰላት።
“አስተሳሰቤን ገና መች ተረዳኸው። እኔ የማስበው ለአንተ እንግዳ ነው: የአንተ ደግሞ ለእኔ እንዲሁ አይገባኝም። ታዲያ
ሳንግባባ እንዴት አስተሳሰቤን አውቀህ አፈቀርኸኝ:"
“የምልሽ ፀባይሽም ደስ ይለኛል"
“ፀባዬ ምን አይነት ነው?"
“ግልፅ
“ፀባዬን እንዳልወደድኸው ግን ብዙ ምልክቶች አይቸብሃለሁ
"ቁመናሽ ደስ ይለኛል..."
“አንድን ሰው በማፍቀርና በመፈለግ መካከል ያለውን ልይነት ግን ታውቃለህ?"
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ቀኑ ቅዳሜ ነው። ሴቬሊያ ከተማ ላይ አንዣቦ የከረመው ዳመና ተበታትኖ ሰማያዊው ሰማይ በፀሐይ ብርሃን ተጥለቅልቆ ኗሪው በደስታ ሲንቀሳቀስ ይታያል።
ሶራ ከመኝው የተነሳው ዘግየት ብሎ ሲሆን ከመኝታው ተነስቶ ሳሎኑ ሲገባ አብረውት የሚኖሩት ሁለቱ የክፍል ጓደኞቹ
ሞዛምቢካዊው ኢናሲዬ እና ሴኔጋላው ዲያንካ ሲከራከሩ አገኛቸው:
“...አየህ የኛ የአፍሪካውያን ችግር በእለት ችግሮቻችን ላይ ካልሆነ በህልማችን በሐሳባችን... ላይ በትዕግስት መወያየት
መከራከር አንችልም: በግልፍተኝነት ስለ ዛሬ እናወራለን ዛሬ በምንፈፅመው እናዝናለን ወይንም እንረካለን።
ዛሬን ከትናንትና ከነገ ጋር ማነፃፀር ስለማንችል መቻቻሉም ያቅተናል: እና እኛ አፍሪውያን ከጊዜ የቁም እስር እራሳችንን ነፃ
አድርገን ጊዜን መጠቀም ስንጀምር! ሽንፈትና ድልን ልዩነቱን ስናውቅ በቅድሚያ ችግሮቻችንን እንፈታለን…” አለ ሞዛምቢካዊው
ኢናሲዬ:
“…በሃሣብህ እኮ እስማማለሁ፡ ችግሩ ግን እንደ ቡችላ ያለው አይናችንን ለመክፈት ገና ስናስብ የሰለጠኑት ህዝቦች ባለፉት ጊዜያት ከተጠቀሙበት መሳሪያ በተሻለና በረከሰ የረቀቀ መረብ እየጠለፉ ይጥሉናል: ለዚህ መፍትሄው ምን
ይሁን ነው? እኛ ፊደል እንዴት እንቁጠር ስንል አንዱ እርስ በራሳችን እንማማር ሌላው የሰለጠኑት ህዝቦች እንዲያስተምሩን
እንለምን... ሲል ጊዜያት ከነፉ፤ የጥቁር ህዝብ ህልም እንደ
ኪሊማንጃሮ ተራራ ቢከመር ጠብታ ተግባር ካልወጣው! አንዱ ሌላውን ወንድሙን ገሉ ማቅራራቱንና መፎከሩን ካላቆምንና ራሳችንን መግዛት ካቃተን ጥሩ ተገዥ መሆን ይሻለናል” ብሎ
የምፀት ሳቁን ሳቀ ሁለቱም ተሳሳቁ፡
“ጥሩ! ማን በማን ላይ እንደሳቀ ዳኝነቱን ወደፊት
እስከገልፅ አንዴ ይቅርታ ይደረግልኝ..."
“ሶራ! ሁለቱም እንደተመካከሩ ሀሉ በአድናቆት ዞረው
ጠሩትና
ዛሬ ምነው ምሽግን አለቅም ብለህ ዋልህ? ያች ኢትዬ
ስፔናዊት የምትሰራው የቤት ስራም ሰጥታህ
ነበር መሰል ሞዛምቢካዊው ኢናሊዬ የጓደኛውን ጉልበት መታ አድርጎ ቤቱን
ለሁለት በሣቅ አነቃነቁት።
ከባድ የቤት ሥራ ነበር የሰጠችኝ፡ ጥያቄዋን ሽ ጊዜ አነበብኩት በቃሌ አነበብኩት! መልሱ ግን ጠፋኝ። ጥያቄዋን
ካለእሷ ሊመልሰው የሚችል የለም:"
“ስለዚህ መልሱን ከመምህርት ኢትዮ ስፔናዊት ለማግኘት
ልትሄድ ነዋ!” ነዋ!
ቶሉ መሄድ! የጠፋኝን ቶሉ ማወቅ ከዚያ ጎበዝ
ደቀ መዝሙሯ መሆን እፈልጋለሁ።” የሁለቱንም ትከሻ መታ መ+ አድርጎ። ወደ ውስጥ ገብቶ ለባብሶ ወጣና፡-
“አጭርና ያልተንዛዛ አስተያየት አላማረብኝም አላቸዎሸ በየተራ እያያቸው።
“መልሱን ካለ አንድ ሰው አይመልሰውም" ሲል ዲያንካ
“እሷም መምህርት ኢትዮ ስፔናዊት ብቻ ናት..." አለ ኢናልዬ
“ትክክል!'' ብሎ የኢናሲዬን ትከሻ መታ መታ አድርጎ በሩን ከፍቶ ሲወጣ ሳቃቸው ከኋላው ተከተለው
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሶራና ኮንችት ከተዋወቁ በኋላ ኮንችት ቤት ማድሪድ
በሚገኘው ፒካሶ ሆቴል... ደጋግመው ተገናኝተዋል። ኮንችት በሶራ ግልፅነት በጎደለው ይሉኝታ በተበተበው ባህሪው ብዙ ጊዜ ትበሽቃለች።
ሶራ መብላት ትፈልጋለህ?" ስትለው
“አንችስ?” ሲላት በብስጭት
"እፈልጋለሁ! ወይንም አልፈልግም። ስለእኔ እኔ ስለአንተ ደግሞ አንተ መመለስ በቃ። የአንተ መፈለግ አለመፈለግ ከእኔ ጋር ምን አገናኘው" ትለዋለች
“የዛሬ ግብዣ የኔ ነው"
“ጥሩ ስለግብዣ ሃሳብህ አመሰግንሃለሁ። የት ነው የምትጋብዘኝ?
“የት ልጋብዝሽ?”
“ኦ! - አምላኬ!” በንዴት ትጦፍና፦
“ሰውን ልትጋብዝ ስትፈልግ በቅድሚያ የት ምን
እንደምትጋብዘው አስብ እሽ ፊቷ በንዴት እንደቀላ ትነግረዋለች
“ምነው ዝም አልሽ?
“ለምን ጠየቅከኝ?
“ስለማትጫወቺ ስለማትስቂ...”
"ሰው ቤት ከመሄድህ በፊት ልትገናኙ መቻል አለመቻላችሁን ደውለህ ፈቃድ ጠይቅ ! እኛ ሰዎች ለስራ ለጨዋታ
ለእረፍት... የምንመድበው ጊዜ አለ:: ሰዎችን በፕርግራማቸው
እንዳይጠቀሙ እንቅፋት መሆን ትልቅ ሃጢያት ነው: ገባህ!” ትለዋለች።
“የያዝሽውን እቃ ልያዝልሽ?
“ለምን?
“ይከብድሻል…”
“ፖልፋቮር /ይቅርታ/ እኔ ጡጦ የምታጠባው ህፃን ልጅህ አይደለሁም የሚከብደኝን መጀመሪያውንም አልይዝም።እሺ
በንዴት ትንጨረጨርበታለች ሶራ ባህሪዋ ሙልጭልጭ ይልበታል ሲያዝንላት ሲንከባከባት ሲሞክርና እንዲቀራረቡ ጥረት ሲያደርግ? አባባሉን በተቃራኒ ተረድታ በግሳፄ የህሊና ድዱን በርግጫ
ታወልቀዋለች:
እሱ ግን ይችላታል: ሆዱ እየተቀየመ አንደበቱ ግን
ያልፋታል።
“ዲስኮ ዳንስ ቤት ብዙ መቆየት አልወድም"
“ሶራ! ከኔ ጋር ግን'ኮ አብረህ…"
“ላስከፋሽ ስላልፈለግሁ"
“እብድ ነህ! የማትፈልገውን ለኔ ብለህ የምታደርግ?”
“ብቻሽን ትቼሽ መሄድ ስላልፈለግሁ"
“በቃህ አንተ ኖርህ አልኖር ለኔ ለውጥ የለውም 7
ገባህ! መዝናናት ስፈልግ ዘበኛ አላስከትልም: ማንንም ካለፍላጎቱ እንደ
ከዘራ ቆልምሜ የኔ ምርኩዝ ማድረግ አልሻም.." ታፈጥበታለች።
አብሯት ለመሆን እንደሚጓጓው ሁሉ ከሷ መለየቱንም ይፈልገዋል: ልዩነታቸው ብዙ ነው።
ኮንችት ባህሪው ግልፅ
ነው ሣቋን አንደ ጥሩ ሙዚቃ በስሜት ይደንስበታል: ችግሩ ድንገት እሳት ወዲያው ውሃ
ትሆንበታለች:: እሳት ስትሆን ሊሸሻት ይፈልጋል! ውሃ ስትሆን ደግሞ እንደ ፀበል በጨዋታዋ ይጠመቃል!
ሶራ ሜዳ ይሁን ገደል ስሜቱ በደመ ነፍሱ ሲጋልብም እሷ
ለሁሉም ነገር ምክንያት ትፈልጋለች: እየተሞላቀቀች
ጭኖችዋን ፓንቷን.. ስታሳየውና ጉሮሮውን ስታስጮህበት ስሜቱን
ስታስነጥስበት ትቆይና መላውን ሳትለው ድንገት
“መተኛት እፈልጋለሁ" ትለዋለች።
ትንሽ አንጫወትም?"
...የሰው ፍላጎት ሊገባህ ይገባል እሽ?" ቀልቡን ገፋበት መኝታ ቤቷ ትገባለች። እሱም ወጥቶ ይሄዳል። ቤቱ ሲሄድ ግን
ህሊናው እረፍት ሲነሳው ሰውነቱ እንደ እሳት ሲቀጣጠልበት
መታጠቢያ ቤት ይገባና ቀዝቃዛ ሻወር ገላው ላይ ያፈሳል፡ ለአያቷ
አገር ለኢትዮጵያ ያላት ናፍቆት ግልፅነቷ ሳቋ… ተክለ ቁመናዋ
እያወዛወዘው ሲያንጨዋልለው ፍላጎቱ ለእሷ ያለው ቀረቤታ
ከጓደኝነት ያለፈ ይሆንበታል።
ኮንችት ደጋግማ
የነገረችው ስሜትህንና ፍላጎትህን አትደብቅ ነው። ስለዚህ እየዋለ ባደረ ቁጥር ናፍቆቱ ጤና ሲነሳው
ስሜቱን ሊገልፅላት አሰበ: ድፍረቱና አጋጣሚው ጠፍቶ ለቀናት ተሰቃዩ:: አንድ ቀን ግን ደፈረ:
“ኮንችት?”
“አቤት" ያ እንደ ንስር አይን ተልቆ የሚበረበረው አይኗ
ከመናገሩ በፊት እየበሳሳው ውስጠ ሚስጥሩን አየበት።
“አፈቅርሻለሁ አላት ባጭሩ። ኮንችት ግን ይህን ስሜቱንና አባባሉን ቀደም ብላ እንደተረዳች ሀሉ፡
“ለምን አፈቀርኸኝ? በአባባሉ ሳትደነቅ ጠየቀችው
ተቁነጠነጠ! ግልጽ ሁን ብላ ወትውታ ግልፅ ሲሆን ደግሞ ዓለምን ያስጨነቀ ጥያቄ “ለምን?" እያለች በማስቸገሯ ተማረረባት።
ለምን አፈቀርኝ? ደግማ ጠየቀችው
“አስተሳሰብሽ ደስ ይለኛል” አንገቱ ላይ እንደቆሙበት ውሻ አይኑ እየተቁለጨለጨ መለሰላት።
“አስተሳሰቤን ገና መች ተረዳኸው። እኔ የማስበው ለአንተ እንግዳ ነው: የአንተ ደግሞ ለእኔ እንዲሁ አይገባኝም። ታዲያ
ሳንግባባ እንዴት አስተሳሰቤን አውቀህ አፈቀርኸኝ:"
“የምልሽ ፀባይሽም ደስ ይለኛል"
“ፀባዬ ምን አይነት ነው?"
“ግልፅ
“ፀባዬን እንዳልወደድኸው ግን ብዙ ምልክቶች አይቸብሃለሁ
"ቁመናሽ ደስ ይለኛል..."
“አንድን ሰው በማፍቀርና በመፈለግ መካከል ያለውን ልይነት ግን ታውቃለህ?"
👍27👎1
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
“ነገ ማታ እደውልልሃለሁ በመጭው ሦስት ቀናት
አልኖርም:: ጓደኛዬን ለመጠየቅና እግረ መንገዴን ለመሰናበት ባርሴሉና እሄዳለሁ... መልካም ጊዜ ለማሳለፍ ሞክር አሁን
መተኛት እፈልጋለሁ ኦርቫ" ብላው ከተቀመጠችበት ተነስታ ወደ መኝታ ክፍሏ ገባች:
በተቀመጠበት ህሊናው የስሜት ግጭት ተንቆራቆሰበት...
የሐሳብ ልዩነት.. ውሃና እሳት ትኩሳትና ብርድ... የስሜት
ጩሕት... የማይታኘክ ጉርሻ..
ከጥቁርና ነጭ ቀለም የተውጣጣው የቀይ ዳማ ቀለሟ ዞማ ፀጉሯ ከለግላጋ ቁመናዋ ጋር ፈጣን አስተሳሰቧ ሁሌም ጎልታ
እንድትታይ ያደርጋታል።
መርከበኛው አባቷ ፍራንሲስኮ ፔሶ ቤኒ በስራው ምክንያት
ከናቷ ከሎካዬ ጋር ለብዙ ወራት ተለያይቶ ሲቆይ ከህፃንነቷ ጀምሮ ናፍቆት ቢንጣትም እንኳን የተሟላው ኑሯቸው
ጨዋታ ወዳዱ አባቷ በየመዝናኛው ከናቷ ጋር ይዟት ስለሚዞር አብሯት
ስለሚቦርቅ ደስተኛ ሆና ለማደግ አስችሏታል።
በተማሪነቷ የስካውት አባል የነበረችውና በስካውትነቷ ብዙ ጉዞዎችን ከእድሜ እኮዮችዋ ጋር ያደረገችው ቅርፀ ማራኪዋ ኮንችት
ጊታር መጫወትን በጋራ ማዜምንና ከእስፔናውያን ባህላዊ ዳንስ በተጨማሪ የምዕራባውያንን ውዝዋዜ በስልት አጣጥማ የማቅረብ
ተሰጥኦዋ ተደጋጋሚ አድናቆትን ስላተረፉላት ከዘጠኝ ዓመት እድሜዋ ጀምሮ ጊዜዋ “የፋሽን ሾው" ስራ እየሰራች የራሷ ገቢ
እስከማግኘት አስችሏት ነበር።
አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን ከፈፀመች በኋላ በባልትና ሳይንስ ትምህርት ሰልጥና ከሙያዋ ይልቅ በሞዴሊስትነት
ሥራ በመሰማራት በጂምናዚዬም አካላዊ እንቅስቃሴ በማድረግ
ለሚስስ ካታሉንያነት ሁለት ጊዜ ተወዳድራ በሶስተኛው ሚስስ ካታሉንያ በመባል የቁንጅና ዘውዷን ደፍታለች።
ኮንችት በህፃንነት ያየችው አፍሪካዊ አያቷ ኤድዋርድ ሎካዬ ብቸኝነቱ ዝምታውና ደስታ አልባ ሆኖ ኖሮ ከሚናፍቃቸው ዘመዶቹ
ተገናኝቶ ያሰበው ሳይሳካለት ማለፉ እንደ እግር እሳት ሁሌም
ያቃጥላታል። አይቶት በማያውቀው እንደ ሰማይ በተዘረጋ ውቅያኖስ ላይ ጭነው ፖርቶሪኮ ውስጥ ኗሪ ለነበረው ለኤድዋርድ ጃኒፌር የተሸጠው አያቷ ከአንዱ አለም ወደ ሌላ ዓለም ከተወሰደ በኋላ
በቋንቋም በአስተሳሰብም ልዩ ሆኖ ፖርቶሪኮ ውስጥ በተነሳው የርስ በርስ ጦርነት እንደ አባቱ የሚቆጥረው ጌታው ኤድዋርድ ጃኒፈር
ወደ አሜሪካ ሜሪላንድ ሸሽቶ በመሄዱ እንግሊዘኛና እስፓኒሽ ቋንቋ
አፍንጫውን ተይዞ ተምሮ የዕለት ፍላጎቱን ለማርካት የታክሲ ሾፌር ሆነ።
ከዚያ ከኮንችት ሴት አያት ከራሚሬዝ ኦርኔዝ አኜስ ጋር
በአጋጣሚ ተገናኝተው የኮንችት አያት አኜስና ሉካያ እናቷን ከሪናን በመውለድ ስፔን ውስጥ አ ብረው መኖሩ ጀመሩ። ሎካዬ በተለያየ ጊዜ በአፍሪካ ጉብኝት አድርጎ ዘመዶቹን ፈልጎ ለማግኘት ቢሞክርም
ሊሳካለት አልቻለም ነበር:
በስተ እርጅናው ጣልያን ሮም ላይ የተደረገውን የማራቶን ውድድር ለመመልከት ሄዶ ግን ባጋጣሚ የአገሩ ፍንጭ ቢታወቅም ሽምግልናውና ጤና ማጣቱ ተዳምረው
ምኞቱን አሰናከለባት።
ኮንችት አያቷ ለመሞት ቀናት ሲቀሩት ጠርቷት ወደ
አታክልቱ ቦታ ሰውነቱ እየተንቀጠቀጠ ወስዷት ትክ ብሎ እያያት።
“ለሰባት ዓመት ልጅ አደራ መተው ምንኛ ይከብዳል
መሰለሽ” አለና አፉን በመሀረብ ይዞ ሲስል ቆይቶ፡
“አሁ ካንች ሌላ ማንስ አደራዬን ሊቀበል ይችላል-" ሲል ኮንችት የሚለውን ነገር ስላልገባት ግራ ገብቷት ስትቁለጨለጭ፡-
“የዘመዶቼን አገር አላውቅም ነበር። ጠንካራነቴ አሁን
የነበረውን ፍንጭ የዛኔ ቢኖረኝ ኖሮ ምን ነበረበት ግን አልሆነም
የኔ ልጅ ይህች ትንሽ ባንዲራ በልጅነቴ አሁን ስሙን ከማላውቀው
የገጠር ከተማ ከአባቴ ጋር ሄጄ አይቻት ነበር። በህፃንነት ልቦናዬ ያን
ጊዜ ስትውለበለብ ያየኋት ባንዲራ ሮም ላይ ሯጩ ይዟት አየኋት እና እንኪ ያዣት በጥንቃቄም አስቀምጫት! ሲሆንልሽ ግን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ | ባንዲራ ወደ አለባት ኢትዮጵያ ወደሚሏት
ሃገር ሂጂ።
"ይህም መቀመጫ ስንተራሳት ስቀመጥባት ምንድናት?' እያልሽ የምትጠይቂኝ መቀመጫዬም 'በርኮቶ' ትባላለች በኮዬጉዎች።
“ምን?” አለች ኮንችት
ኩዬጕ ኩዬጉዎች… የኔ ዘመዶች የሚቀመጡባት
መቀመጫ ናት" ሳሉ እንደገና አሳለው ላቡ በግንባሩ ተንቆረቆረ
ወደ ሰማይ ቀና ብሎ፦
“ልዑል እግዚአብሔር! እባክህ ትንሽ ትንሽ ጊዜ ስጠኝ አለና እግዚአብሔርን ተማፅኖ፣ “አጠገባቸው ትልቅ ወንዝ አለ::
ሱርማዎች ኦሞ ይሉታል: ከወንዙ ተሻግረሽ ትንሽ ስትሄጂ ኩችሩ የሚባል መንደር አለ፡፡
ሰላም ሲሉ አሹቃ ይላሉ። አሳ አጥማጆች አትክልተኞች ከዱር ማር ሰብሳቢዎች ናቸው" እንደገና ሳለ፤ ቀና ብሉ ሰማዩን ተመለhተ።
ኮንችት የሚለው አልገባትም በጨቅላ ህሊናዋ ግን ስቃዩ
አሳዝኗታል።
“ሁሉንም ፅፌልሻለሁ ባንዲራዋን ከዘነጋኋት ዘመዶቼም ከመኖሪያቸው ለቀው ከሆነ ልፋትሽ መና ይቀራል። ወለላዬ እስቲ
እነዚያ ቆንጂዬ ጣቶችሽ? አላት ድንገት:: ሁለቱንም እጆችዋን ዘረጋችለት:: ጊዜ አልነበረውም መጣደፍ ነበረበት፡፡
ጳ..ጳ አርጎ በጥቁሩ ከንፈሩ በየተራ ሳማቸው: ጉንጯን
ሊስማት ፈለገ¦ ግን ፈራ ሳሉ ቢተላለፍባትስ:
“እንኪ በላስቲኩ
አሮጌ ካርቶን ውስጥ ይኸው ከትቼልሻለሁ። የኔ ልጅ እኒያን ዘመዶቼን ቀንቶሽ ካገኘሻቸው
እዘኝላቸው እንዳንች ንፁሆች ናቸው፡፡ ሎካዬ ናፍቋችኋል ሰላም
ብሏችኋል! በያቸው: ሞቷል አትበያቸው: ስንት ጊዜ በእኔ ይዘኑ ለእኔ ያልቅሱ አለ በያቸው ሲረጋጉ ደግሞ እኔ ነኝ ሎካዬ በያቸው እንደ ህፃን ያምኑሻል መጠራጠር አያውቁም ፤የሚጠራጠር ራሱ ሌባ ነው ይባል የለ! እነሱ ግን እንደ ዶሮ እየጫሩ
ተዛዝነው ያገኙትን ሲለቅሙ ይውሉና የኩችሩ ጫካ ክንፍ ውስጥ እንደ ጫጩት እየተሰገሰጉ ሙቀታቸውን እየተጋሩ ይተኛሉ…"
አሳለው! ሰውነቱ ራደ ላቡ ወረደ።
በይ ሄጂ ተጫወቺ እ..ኔ
ደ.ግ.ሞ እ ..ሁ ልረፍ” አላት ተስፋ በቆረጠ አስተያየት እያያት የአደራ ካርቶኗን ታቅፋ ስትሄድ ፈገግ ብሎ ከኋላዋ ለመጨረሻ ጊዜ ተመለከታት።
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
“ነገ ማታ እደውልልሃለሁ በመጭው ሦስት ቀናት
አልኖርም:: ጓደኛዬን ለመጠየቅና እግረ መንገዴን ለመሰናበት ባርሴሉና እሄዳለሁ... መልካም ጊዜ ለማሳለፍ ሞክር አሁን
መተኛት እፈልጋለሁ ኦርቫ" ብላው ከተቀመጠችበት ተነስታ ወደ መኝታ ክፍሏ ገባች:
በተቀመጠበት ህሊናው የስሜት ግጭት ተንቆራቆሰበት...
የሐሳብ ልዩነት.. ውሃና እሳት ትኩሳትና ብርድ... የስሜት
ጩሕት... የማይታኘክ ጉርሻ..
ከጥቁርና ነጭ ቀለም የተውጣጣው የቀይ ዳማ ቀለሟ ዞማ ፀጉሯ ከለግላጋ ቁመናዋ ጋር ፈጣን አስተሳሰቧ ሁሌም ጎልታ
እንድትታይ ያደርጋታል።
መርከበኛው አባቷ ፍራንሲስኮ ፔሶ ቤኒ በስራው ምክንያት
ከናቷ ከሎካዬ ጋር ለብዙ ወራት ተለያይቶ ሲቆይ ከህፃንነቷ ጀምሮ ናፍቆት ቢንጣትም እንኳን የተሟላው ኑሯቸው
ጨዋታ ወዳዱ አባቷ በየመዝናኛው ከናቷ ጋር ይዟት ስለሚዞር አብሯት
ስለሚቦርቅ ደስተኛ ሆና ለማደግ አስችሏታል።
በተማሪነቷ የስካውት አባል የነበረችውና በስካውትነቷ ብዙ ጉዞዎችን ከእድሜ እኮዮችዋ ጋር ያደረገችው ቅርፀ ማራኪዋ ኮንችት
ጊታር መጫወትን በጋራ ማዜምንና ከእስፔናውያን ባህላዊ ዳንስ በተጨማሪ የምዕራባውያንን ውዝዋዜ በስልት አጣጥማ የማቅረብ
ተሰጥኦዋ ተደጋጋሚ አድናቆትን ስላተረፉላት ከዘጠኝ ዓመት እድሜዋ ጀምሮ ጊዜዋ “የፋሽን ሾው" ስራ እየሰራች የራሷ ገቢ
እስከማግኘት አስችሏት ነበር።
አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን ከፈፀመች በኋላ በባልትና ሳይንስ ትምህርት ሰልጥና ከሙያዋ ይልቅ በሞዴሊስትነት
ሥራ በመሰማራት በጂምናዚዬም አካላዊ እንቅስቃሴ በማድረግ
ለሚስስ ካታሉንያነት ሁለት ጊዜ ተወዳድራ በሶስተኛው ሚስስ ካታሉንያ በመባል የቁንጅና ዘውዷን ደፍታለች።
ኮንችት በህፃንነት ያየችው አፍሪካዊ አያቷ ኤድዋርድ ሎካዬ ብቸኝነቱ ዝምታውና ደስታ አልባ ሆኖ ኖሮ ከሚናፍቃቸው ዘመዶቹ
ተገናኝቶ ያሰበው ሳይሳካለት ማለፉ እንደ እግር እሳት ሁሌም
ያቃጥላታል። አይቶት በማያውቀው እንደ ሰማይ በተዘረጋ ውቅያኖስ ላይ ጭነው ፖርቶሪኮ ውስጥ ኗሪ ለነበረው ለኤድዋርድ ጃኒፌር የተሸጠው አያቷ ከአንዱ አለም ወደ ሌላ ዓለም ከተወሰደ በኋላ
በቋንቋም በአስተሳሰብም ልዩ ሆኖ ፖርቶሪኮ ውስጥ በተነሳው የርስ በርስ ጦርነት እንደ አባቱ የሚቆጥረው ጌታው ኤድዋርድ ጃኒፈር
ወደ አሜሪካ ሜሪላንድ ሸሽቶ በመሄዱ እንግሊዘኛና እስፓኒሽ ቋንቋ
አፍንጫውን ተይዞ ተምሮ የዕለት ፍላጎቱን ለማርካት የታክሲ ሾፌር ሆነ።
ከዚያ ከኮንችት ሴት አያት ከራሚሬዝ ኦርኔዝ አኜስ ጋር
በአጋጣሚ ተገናኝተው የኮንችት አያት አኜስና ሉካያ እናቷን ከሪናን በመውለድ ስፔን ውስጥ አ ብረው መኖሩ ጀመሩ። ሎካዬ በተለያየ ጊዜ በአፍሪካ ጉብኝት አድርጎ ዘመዶቹን ፈልጎ ለማግኘት ቢሞክርም
ሊሳካለት አልቻለም ነበር:
በስተ እርጅናው ጣልያን ሮም ላይ የተደረገውን የማራቶን ውድድር ለመመልከት ሄዶ ግን ባጋጣሚ የአገሩ ፍንጭ ቢታወቅም ሽምግልናውና ጤና ማጣቱ ተዳምረው
ምኞቱን አሰናከለባት።
ኮንችት አያቷ ለመሞት ቀናት ሲቀሩት ጠርቷት ወደ
አታክልቱ ቦታ ሰውነቱ እየተንቀጠቀጠ ወስዷት ትክ ብሎ እያያት።
“ለሰባት ዓመት ልጅ አደራ መተው ምንኛ ይከብዳል
መሰለሽ” አለና አፉን በመሀረብ ይዞ ሲስል ቆይቶ፡
“አሁ ካንች ሌላ ማንስ አደራዬን ሊቀበል ይችላል-" ሲል ኮንችት የሚለውን ነገር ስላልገባት ግራ ገብቷት ስትቁለጨለጭ፡-
“የዘመዶቼን አገር አላውቅም ነበር። ጠንካራነቴ አሁን
የነበረውን ፍንጭ የዛኔ ቢኖረኝ ኖሮ ምን ነበረበት ግን አልሆነም
የኔ ልጅ ይህች ትንሽ ባንዲራ በልጅነቴ አሁን ስሙን ከማላውቀው
የገጠር ከተማ ከአባቴ ጋር ሄጄ አይቻት ነበር። በህፃንነት ልቦናዬ ያን
ጊዜ ስትውለበለብ ያየኋት ባንዲራ ሮም ላይ ሯጩ ይዟት አየኋት እና እንኪ ያዣት በጥንቃቄም አስቀምጫት! ሲሆንልሽ ግን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ | ባንዲራ ወደ አለባት ኢትዮጵያ ወደሚሏት
ሃገር ሂጂ።
"ይህም መቀመጫ ስንተራሳት ስቀመጥባት ምንድናት?' እያልሽ የምትጠይቂኝ መቀመጫዬም 'በርኮቶ' ትባላለች በኮዬጉዎች።
“ምን?” አለች ኮንችት
ኩዬጕ ኩዬጉዎች… የኔ ዘመዶች የሚቀመጡባት
መቀመጫ ናት" ሳሉ እንደገና አሳለው ላቡ በግንባሩ ተንቆረቆረ
ወደ ሰማይ ቀና ብሎ፦
“ልዑል እግዚአብሔር! እባክህ ትንሽ ትንሽ ጊዜ ስጠኝ አለና እግዚአብሔርን ተማፅኖ፣ “አጠገባቸው ትልቅ ወንዝ አለ::
ሱርማዎች ኦሞ ይሉታል: ከወንዙ ተሻግረሽ ትንሽ ስትሄጂ ኩችሩ የሚባል መንደር አለ፡፡
ሰላም ሲሉ አሹቃ ይላሉ። አሳ አጥማጆች አትክልተኞች ከዱር ማር ሰብሳቢዎች ናቸው" እንደገና ሳለ፤ ቀና ብሉ ሰማዩን ተመለhተ።
ኮንችት የሚለው አልገባትም በጨቅላ ህሊናዋ ግን ስቃዩ
አሳዝኗታል።
“ሁሉንም ፅፌልሻለሁ ባንዲራዋን ከዘነጋኋት ዘመዶቼም ከመኖሪያቸው ለቀው ከሆነ ልፋትሽ መና ይቀራል። ወለላዬ እስቲ
እነዚያ ቆንጂዬ ጣቶችሽ? አላት ድንገት:: ሁለቱንም እጆችዋን ዘረጋችለት:: ጊዜ አልነበረውም መጣደፍ ነበረበት፡፡
ጳ..ጳ አርጎ በጥቁሩ ከንፈሩ በየተራ ሳማቸው: ጉንጯን
ሊስማት ፈለገ¦ ግን ፈራ ሳሉ ቢተላለፍባትስ:
“እንኪ በላስቲኩ
አሮጌ ካርቶን ውስጥ ይኸው ከትቼልሻለሁ። የኔ ልጅ እኒያን ዘመዶቼን ቀንቶሽ ካገኘሻቸው
እዘኝላቸው እንዳንች ንፁሆች ናቸው፡፡ ሎካዬ ናፍቋችኋል ሰላም
ብሏችኋል! በያቸው: ሞቷል አትበያቸው: ስንት ጊዜ በእኔ ይዘኑ ለእኔ ያልቅሱ አለ በያቸው ሲረጋጉ ደግሞ እኔ ነኝ ሎካዬ በያቸው እንደ ህፃን ያምኑሻል መጠራጠር አያውቁም ፤የሚጠራጠር ራሱ ሌባ ነው ይባል የለ! እነሱ ግን እንደ ዶሮ እየጫሩ
ተዛዝነው ያገኙትን ሲለቅሙ ይውሉና የኩችሩ ጫካ ክንፍ ውስጥ እንደ ጫጩት እየተሰገሰጉ ሙቀታቸውን እየተጋሩ ይተኛሉ…"
አሳለው! ሰውነቱ ራደ ላቡ ወረደ።
በይ ሄጂ ተጫወቺ እ..ኔ
ደ.ግ.ሞ እ ..ሁ ልረፍ” አላት ተስፋ በቆረጠ አስተያየት እያያት የአደራ ካርቶኗን ታቅፋ ስትሄድ ፈገግ ብሎ ከኋላዋ ለመጨረሻ ጊዜ ተመለከታት።
👍20
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
“…ሶራ- የባህል ትንሽ ትልቅ አለው ብዬ ላነፃፀር
አልሻም። ልምዴና እውቀቴ ገና ውስን ነው: የባህል ልዩነት ግን አኗኗር ልዩነት እንደሚያመጣ አውቃለሁ፡፡
“ሁሉም ሰው ያለበትን አካባቢ ከሌላው በተሻለ ያውቃል! ይጠቀማል አያቴም ከለመደው ባህል ወጥቶ ካለፍላጎቱ ወደ
አለመደው ባህል ከመጣ በኋላ አስተሳሰቡ ከዘመነው ህብረተሰብ አንፃር ያነሰ ቢሆንም ከዚህኛው ህብረተሰብ የተሻለ ትዕግስትና ጨዋነት የነበረው ከዚህኛው የነበረው በመሆኑ ሴት አያቴን አስባውና
አልማው ያልነበረውን በጥቁር ፍቅር እንድትንቦራችና አያቴ ከዚህ
ዓለም በሞት ከተለየ በኋላም ፍቅሩ ጥቁር ድመት አቅፋ እንድትውል አድርጓታል፡
“ወንድ አያትሽን በመልክ ታውቂያቸዋለሽ? ሶራ ጠየቃት:
“ልጅ ነበርኩ እንጂ አስታውሰዋለሁ። ከእንጨት ጠርቦ የሰራት ትንሽና ልዩ በርጩማው ላይ ቁጭ አንዳንዴም ጋደም ብሎ
ይንተራስና ሽቅብ ሽቅብ እያየ ሰማዩ ላይ ማፍጠጥ ይወዳል:
“እኔም ከሌሎች ጋር ስሆን መዝለልና መጫወት
እንደማልወድ ሁሉ እሱ ደረት ወይ ትከሻ ላይ ሆኜ ግን ለረጅም ጊዜ
ከሚቆዝመው ጥቁርና ልዩው አያቴ ጋር ፀጥ ስለምል ሴት አያቴ፡-
“ሎካዬ! ካንተ ጋር ስትሆን ለምን ዝም እንደምትል
ታውቃለህ?" ስትለው ዘወር ብሎ ወይም አይኖቹን ከሰማዩ ላይ መልሶ ያያታል።
“ስለምትፈራህ ነው አንተ ስ
ለህፃንም ለአዋቂም ዝግ ነህ አዕምሮህ የዕድሜ ልዩነትን አይገምትም! መሣቅ መጫወት ለልጆች
ምን ያህል ጠቃሚ መሆኑን አታስብም…” ትለውና ለመውሲድ እጅዋን ስትዘረጋልኝ በእንቢታ ደረቱ ውስጥ ድብቅ እላለሁ፡
“ወለላዬ! ሂጂ፤ አብረሽኝ መሆንሽን እየዘነጋሁ በዝምታ እኔ የምፈራው አንሶኝ አንችንም አስፈራሁሽ ውሰጃት :ኜስ
ላጫውታት አልታደልሁም" ይላታል። ያን ጊዜ በትናንሽ እጆቼና እግሮቼ ቁልፍ አድርጌ እይዘውና “አልሄድም' እላለሁ
“ያኔ ሴት አያቴ ትኩር ብላ ታየንና ቀስ ብላ መጥታ
ትከሻውን ተደግፋ! …ሎካዬ ለምን ደስተኛ አትሆንም እወድሃለሁ እኮ መሣቅ መጫወት ግን ልትለምድልኝ አልቻልክም: ለምን
ታሳቅቀናለህ! ስትለው ዝም ብሏት ይቆይና፡-
"አኜስ እባክሽ ተይኝ" ይላታል:
ከኔ በላይ የሚቀርብህ ማን ሊመጣ ይችላል፡፡ ጭንቀትህ ውስጣዊ ብሶትህ ጊዜ የማይሽረው ዝምታህ ምንድነው?” ስትለው፡-
“የአባቴ ልማድና ወግ ከብቶቼ…"ሃሳቡን ሳይጨርስ
አይኖቹን ይጨፍናል
“የአንተ አገር ከብቶች ከኛ ይለያሉ?"
“እንዴታ! ይለያሉ እንጂ።"
“በምን?”
“በማእረግ ፧ አኜስ! ከብት ከስጋና ወተቱ ይልቅ ቅሩ
ያጠግባል። በምላሱ ሲልስሽ በሽንቱ ስትታጠቢ እነሱ እያገሱ አንች
እያንጎራጎርሽ ስትከተያቸው
ስትውይ የሆዳቸውን
ጩኸት እያዳመጥሽ
ትንፋሻቸውን እየሞቅሽ
አብረሻቸው ስትተኝ…
የህይወት ቁርኝቱ የተፈጥሮ ሰንሰለቱ በፍቅር የተገመደ ነውር ።
“እዚህ ግን ከብቶችና እኔ አረም ነን። የምግብ ክምር
ይሰጠንና ታስረን የምንውል ማግሳትና ማንጎራጎር የማንችል…"ሲላት ሴት አያቴ በወንድ አዬቴና ላይ ያለ የሌለ እርግማን ታወርድበታለች፡፡
“ምንም ሳይመልስላት አይኖቹን አድማስ ላይ ይተክላል። የእጅ ጣቶቹ ግን የሰራ አካላቴን ሳይታክቱ
ስለሚደባብሱኝ የመጨረሻውን ሳላውቅ እንቅልፍ ጭልጥ አድርጎ ይወስደኛል፡፡
“እና! የሴት አያቴ ዘመዶች ሴት አያቴን፡
“አፍሪካዊው ሎካዬን በማግባቷ ብዙ ነር ጎድሏታል እያሉ
ኢያቴን ለምን አብራው እንደምትኖር ሲጠይቋት-
ዝምታው ልቤን በፍቅር የባህር ጨው አድርጎታል::
የፍቅር ነፃነቴም ያስደስተኛል ሎካዬን እንለያይ ብለው እሺ እህትና ወንድም እንሁን 'እንዳልሽ' ከማለት ሌላ ታቃውሞ ግዴታዬ መለማመጥ ፍርሃት ስለማላይበት ከእሱ መለየት የማይታሰብ ነው ብላ አፋቸውን ታሲዛቸዋለች:
“ወንድ አያቴ ሎካዬ በግር መጓዝም ይወዳል! በተለይ
በረፍት ቀኑ ከተማው መሃል ካለው መናፈሻ የተወራረደ ሰው ሄዶ አያጣውም እፅዋት ስር ይገባና አላፊ
አግዳሚውን ሳያይ እንደ ስነ
ፍጥረት ተመራማሪ አይኑን ሰማዩ ላይ ሰክቶ በርጋታ ለብዙ ጊዜ ይቀመጣል።
ሶራ ወንድ አያቴ ማንም ሊረዳው ከሚችለው በላይ ውስጡ ናፍቆት ትዝታ የቦረቦረው ነበር ዘመናዊነት ደስታን ሊፈጥርለት አልቻለም በረጅሙ ህይወቱ ካገኘው ልምድ ይልቅ
የልጅነት ዘመነ ትዝታ እሱነቱን ሽፍኖለታል: ድሮ ስለ አያቴ ባሰብኩ ቁጥር የሱን ትውልድ ቦታ እንደ ገነት እቆጥረው ነበር።
እናቴ ግን አፍሪካ ድህነት ችግር….የተከመረባት ሰዎቹም እርስ በርሳቸው የሚበላሉ እንደሆኑና ሲኦል እንጂ ገነት እንደሊለባት
ስትነግረኝ ሌላ ሃሳብ በአእምሮዬ መፈጠር ጀምሮ ነበር። ይህች አለም ጥቁርና ነጭ አምላክ ያላት ሁለት ገነት የሚገኝባት ሆና
አንዱ የሌላው ጠላት እንደሆነ ይስማኝ ነበር፡፡
"አያቴ ስለ ወንድ አያቴ ሁለት ተቃራኒ እምነቶች ነበሯት በአንድ በኩል ዝምታውንና ጅንነቱን የምትወድለት ቢሆንም በሌላ በኩል ደግሞ አብረው ለመዝናናት ለመወያየት ስለማይችሉ ፀጉሯን እየነጨች ትበሳጫለች ያም ሆኖ ግን እናቴ እንደነገረችኝ ከሆነ
አያቴ ለወንድ አያቴ በተደጋጋሚ በፍቅር ስትናዘዝለት ሰምታታስች
ለምሳሌ እንድ ቀን አያቴ ከሁዌልቫ በስተምእራብ አስራ አምስት ኪሎሜትር ላይ ከሚገኘው የብርቱካን ማሳቸው አያቴን ይዛት
ትሄዳለች እዚያ ሲደርሱ ግን ወንድ አያቴ አልነበረም፡
“ስለዚህ እናቴ ከሪና ሁሌም እንደምታደርገው ወደ ብርቱካን ማሳው ገባ ብላ ብርቱኳን እየላጠች ስትበላ የቀሚሷ ጫፍ እየያዘች
ስትዘፍንና ስትዝናና ቆይታ አያቴን ወደተለየችበት ቦታ ስትመጣ አያቴን ታጣታለች።
“ደጋግማ ተጣርታ ወይ የሚላት ሲጠፋ የትም አትሄድም በሚል እራሷን አረጋግታ አያቴን አኜስን ስትፈልጋት እመስኖው
ውሃ ቦይ ትደርስና ውስጡ
ገብታ እየተንቦጫረቀች ስትሄድ የመስኖውን ውሃ ከሚስበው ሞተር ቤት ደረሰች፡፡
የሰው ድምፅ የሰማች መስሏት ፀጥ ስትል ድምፁ
ጠፋባት፡ ልትጣራ ፈለገች
ከመጣራቷ በፊት ግን ቀርቦ የራቃት ድምጽ ተመልሶ መጣ! ከሞተሩ ቤት የሚመጣውን ድምጽ በጆሮዋ ያዘችው። የሚያቃስት ሰው ድምጽ ነው የእናቷ! ደነገጠች ወደ
ሞተሩ ቤት ሄዳ በፍርሃት በጭላንጭል አየች እናቴን ከእግር ጥፍሯ እስከ ጸጉሯ አንዳች ነገር ነዘራት፡፡ ድምፁ እንደገና ቀሰቀሳት
አያቴ አኜስ ናት! ድምፅዋ ቁርጥርጥ እንደሚቀጣ ህፃን ትንፋሽዋን በሲቃ ውጥር ይልና ደሞ ይጠፋባታል፤
በመጨረሻ ድምፁ
መጠኑን ጨምሮ መጣ
የሁለት ሰው ድምፅ የሉካዬና አኜስ ጨመረ ድምፁ እናቴ ተጨነቀች። ልትሮጥ ዘወር ስትል
የፎይታ ድምጽ ሰማች። ከዚያ አያቴ ተረጋግታ ስትናገር ሰማቻት፡
“አመሰግናለሁ ሎካዬ የልቤን ነው ያደረስከው ከከሪና ጋር ወደ አንተ ስገሰግስ እንዲህ አንጀቴን እንደምታርሰው እርግጠኛ
ነበርሁ። የውጭ በግ…
የልጋ ላይ ግን አንበሳ ነህ. ብላ ስትናዘዝላት እናቴ አያቴን ሰምታታለች።
“ይህ ደግሞ ሴት አያቴ
ወንድ አያቴን የምታፈቅረው
በዲፕሎማሲያዊ አነጋገር በዝምታው ነው ትበል እንጂ ጌታውን እንዳዬ ውሻ እግሩ ስር የሚያልወሰውሳት ሚስጥሩ ሴላ ነው፡፡
ሶራ የሚገርምህ ግን እናቴ ያችን ቀን ፆታዬን
ያወቅሁበትና ረሃቤን ለማዳመጥ ትእግስት የጎደለኝና የተመኘሁትን
ያጣሁበት ቀን ናት' ብላ ታስታውሳለች፡፡
ይህ በሆነ ከአምስት ዓመት በኋላ ግን እናቴ ከአባቴ
ከፍራንሲስኮ ፔሶ ቤኒ ጋር ከሁዌልቫ ወደ ሊዝበን ለጉብኝት ስትሄድ
ተዋውቀው ግንኙነታቸውና መግባባታቸው እየጨመረ ሲሄድ የብርቱካን ማሳቸውን ልታሳየው ቀጠረችው፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
“…ሶራ- የባህል ትንሽ ትልቅ አለው ብዬ ላነፃፀር
አልሻም። ልምዴና እውቀቴ ገና ውስን ነው: የባህል ልዩነት ግን አኗኗር ልዩነት እንደሚያመጣ አውቃለሁ፡፡
“ሁሉም ሰው ያለበትን አካባቢ ከሌላው በተሻለ ያውቃል! ይጠቀማል አያቴም ከለመደው ባህል ወጥቶ ካለፍላጎቱ ወደ
አለመደው ባህል ከመጣ በኋላ አስተሳሰቡ ከዘመነው ህብረተሰብ አንፃር ያነሰ ቢሆንም ከዚህኛው ህብረተሰብ የተሻለ ትዕግስትና ጨዋነት የነበረው ከዚህኛው የነበረው በመሆኑ ሴት አያቴን አስባውና
አልማው ያልነበረውን በጥቁር ፍቅር እንድትንቦራችና አያቴ ከዚህ
ዓለም በሞት ከተለየ በኋላም ፍቅሩ ጥቁር ድመት አቅፋ እንድትውል አድርጓታል፡
“ወንድ አያትሽን በመልክ ታውቂያቸዋለሽ? ሶራ ጠየቃት:
“ልጅ ነበርኩ እንጂ አስታውሰዋለሁ። ከእንጨት ጠርቦ የሰራት ትንሽና ልዩ በርጩማው ላይ ቁጭ አንዳንዴም ጋደም ብሎ
ይንተራስና ሽቅብ ሽቅብ እያየ ሰማዩ ላይ ማፍጠጥ ይወዳል:
“እኔም ከሌሎች ጋር ስሆን መዝለልና መጫወት
እንደማልወድ ሁሉ እሱ ደረት ወይ ትከሻ ላይ ሆኜ ግን ለረጅም ጊዜ
ከሚቆዝመው ጥቁርና ልዩው አያቴ ጋር ፀጥ ስለምል ሴት አያቴ፡-
“ሎካዬ! ካንተ ጋር ስትሆን ለምን ዝም እንደምትል
ታውቃለህ?" ስትለው ዘወር ብሎ ወይም አይኖቹን ከሰማዩ ላይ መልሶ ያያታል።
“ስለምትፈራህ ነው አንተ ስ
ለህፃንም ለአዋቂም ዝግ ነህ አዕምሮህ የዕድሜ ልዩነትን አይገምትም! መሣቅ መጫወት ለልጆች
ምን ያህል ጠቃሚ መሆኑን አታስብም…” ትለውና ለመውሲድ እጅዋን ስትዘረጋልኝ በእንቢታ ደረቱ ውስጥ ድብቅ እላለሁ፡
“ወለላዬ! ሂጂ፤ አብረሽኝ መሆንሽን እየዘነጋሁ በዝምታ እኔ የምፈራው አንሶኝ አንችንም አስፈራሁሽ ውሰጃት :ኜስ
ላጫውታት አልታደልሁም" ይላታል። ያን ጊዜ በትናንሽ እጆቼና እግሮቼ ቁልፍ አድርጌ እይዘውና “አልሄድም' እላለሁ
“ያኔ ሴት አያቴ ትኩር ብላ ታየንና ቀስ ብላ መጥታ
ትከሻውን ተደግፋ! …ሎካዬ ለምን ደስተኛ አትሆንም እወድሃለሁ እኮ መሣቅ መጫወት ግን ልትለምድልኝ አልቻልክም: ለምን
ታሳቅቀናለህ! ስትለው ዝም ብሏት ይቆይና፡-
"አኜስ እባክሽ ተይኝ" ይላታል:
ከኔ በላይ የሚቀርብህ ማን ሊመጣ ይችላል፡፡ ጭንቀትህ ውስጣዊ ብሶትህ ጊዜ የማይሽረው ዝምታህ ምንድነው?” ስትለው፡-
“የአባቴ ልማድና ወግ ከብቶቼ…"ሃሳቡን ሳይጨርስ
አይኖቹን ይጨፍናል
“የአንተ አገር ከብቶች ከኛ ይለያሉ?"
“እንዴታ! ይለያሉ እንጂ።"
“በምን?”
“በማእረግ ፧ አኜስ! ከብት ከስጋና ወተቱ ይልቅ ቅሩ
ያጠግባል። በምላሱ ሲልስሽ በሽንቱ ስትታጠቢ እነሱ እያገሱ አንች
እያንጎራጎርሽ ስትከተያቸው
ስትውይ የሆዳቸውን
ጩኸት እያዳመጥሽ
ትንፋሻቸውን እየሞቅሽ
አብረሻቸው ስትተኝ…
የህይወት ቁርኝቱ የተፈጥሮ ሰንሰለቱ በፍቅር የተገመደ ነውር ።
“እዚህ ግን ከብቶችና እኔ አረም ነን። የምግብ ክምር
ይሰጠንና ታስረን የምንውል ማግሳትና ማንጎራጎር የማንችል…"ሲላት ሴት አያቴ በወንድ አዬቴና ላይ ያለ የሌለ እርግማን ታወርድበታለች፡፡
“ምንም ሳይመልስላት አይኖቹን አድማስ ላይ ይተክላል። የእጅ ጣቶቹ ግን የሰራ አካላቴን ሳይታክቱ
ስለሚደባብሱኝ የመጨረሻውን ሳላውቅ እንቅልፍ ጭልጥ አድርጎ ይወስደኛል፡፡
“እና! የሴት አያቴ ዘመዶች ሴት አያቴን፡
“አፍሪካዊው ሎካዬን በማግባቷ ብዙ ነር ጎድሏታል እያሉ
ኢያቴን ለምን አብራው እንደምትኖር ሲጠይቋት-
ዝምታው ልቤን በፍቅር የባህር ጨው አድርጎታል::
የፍቅር ነፃነቴም ያስደስተኛል ሎካዬን እንለያይ ብለው እሺ እህትና ወንድም እንሁን 'እንዳልሽ' ከማለት ሌላ ታቃውሞ ግዴታዬ መለማመጥ ፍርሃት ስለማላይበት ከእሱ መለየት የማይታሰብ ነው ብላ አፋቸውን ታሲዛቸዋለች:
“ወንድ አያቴ ሎካዬ በግር መጓዝም ይወዳል! በተለይ
በረፍት ቀኑ ከተማው መሃል ካለው መናፈሻ የተወራረደ ሰው ሄዶ አያጣውም እፅዋት ስር ይገባና አላፊ
አግዳሚውን ሳያይ እንደ ስነ
ፍጥረት ተመራማሪ አይኑን ሰማዩ ላይ ሰክቶ በርጋታ ለብዙ ጊዜ ይቀመጣል።
ሶራ ወንድ አያቴ ማንም ሊረዳው ከሚችለው በላይ ውስጡ ናፍቆት ትዝታ የቦረቦረው ነበር ዘመናዊነት ደስታን ሊፈጥርለት አልቻለም በረጅሙ ህይወቱ ካገኘው ልምድ ይልቅ
የልጅነት ዘመነ ትዝታ እሱነቱን ሽፍኖለታል: ድሮ ስለ አያቴ ባሰብኩ ቁጥር የሱን ትውልድ ቦታ እንደ ገነት እቆጥረው ነበር።
እናቴ ግን አፍሪካ ድህነት ችግር….የተከመረባት ሰዎቹም እርስ በርሳቸው የሚበላሉ እንደሆኑና ሲኦል እንጂ ገነት እንደሊለባት
ስትነግረኝ ሌላ ሃሳብ በአእምሮዬ መፈጠር ጀምሮ ነበር። ይህች አለም ጥቁርና ነጭ አምላክ ያላት ሁለት ገነት የሚገኝባት ሆና
አንዱ የሌላው ጠላት እንደሆነ ይስማኝ ነበር፡፡
"አያቴ ስለ ወንድ አያቴ ሁለት ተቃራኒ እምነቶች ነበሯት በአንድ በኩል ዝምታውንና ጅንነቱን የምትወድለት ቢሆንም በሌላ በኩል ደግሞ አብረው ለመዝናናት ለመወያየት ስለማይችሉ ፀጉሯን እየነጨች ትበሳጫለች ያም ሆኖ ግን እናቴ እንደነገረችኝ ከሆነ
አያቴ ለወንድ አያቴ በተደጋጋሚ በፍቅር ስትናዘዝለት ሰምታታስች
ለምሳሌ እንድ ቀን አያቴ ከሁዌልቫ በስተምእራብ አስራ አምስት ኪሎሜትር ላይ ከሚገኘው የብርቱካን ማሳቸው አያቴን ይዛት
ትሄዳለች እዚያ ሲደርሱ ግን ወንድ አያቴ አልነበረም፡
“ስለዚህ እናቴ ከሪና ሁሌም እንደምታደርገው ወደ ብርቱካን ማሳው ገባ ብላ ብርቱኳን እየላጠች ስትበላ የቀሚሷ ጫፍ እየያዘች
ስትዘፍንና ስትዝናና ቆይታ አያቴን ወደተለየችበት ቦታ ስትመጣ አያቴን ታጣታለች።
“ደጋግማ ተጣርታ ወይ የሚላት ሲጠፋ የትም አትሄድም በሚል እራሷን አረጋግታ አያቴን አኜስን ስትፈልጋት እመስኖው
ውሃ ቦይ ትደርስና ውስጡ
ገብታ እየተንቦጫረቀች ስትሄድ የመስኖውን ውሃ ከሚስበው ሞተር ቤት ደረሰች፡፡
የሰው ድምፅ የሰማች መስሏት ፀጥ ስትል ድምፁ
ጠፋባት፡ ልትጣራ ፈለገች
ከመጣራቷ በፊት ግን ቀርቦ የራቃት ድምጽ ተመልሶ መጣ! ከሞተሩ ቤት የሚመጣውን ድምጽ በጆሮዋ ያዘችው። የሚያቃስት ሰው ድምጽ ነው የእናቷ! ደነገጠች ወደ
ሞተሩ ቤት ሄዳ በፍርሃት በጭላንጭል አየች እናቴን ከእግር ጥፍሯ እስከ ጸጉሯ አንዳች ነገር ነዘራት፡፡ ድምፁ እንደገና ቀሰቀሳት
አያቴ አኜስ ናት! ድምፅዋ ቁርጥርጥ እንደሚቀጣ ህፃን ትንፋሽዋን በሲቃ ውጥር ይልና ደሞ ይጠፋባታል፤
በመጨረሻ ድምፁ
መጠኑን ጨምሮ መጣ
የሁለት ሰው ድምፅ የሉካዬና አኜስ ጨመረ ድምፁ እናቴ ተጨነቀች። ልትሮጥ ዘወር ስትል
የፎይታ ድምጽ ሰማች። ከዚያ አያቴ ተረጋግታ ስትናገር ሰማቻት፡
“አመሰግናለሁ ሎካዬ የልቤን ነው ያደረስከው ከከሪና ጋር ወደ አንተ ስገሰግስ እንዲህ አንጀቴን እንደምታርሰው እርግጠኛ
ነበርሁ። የውጭ በግ…
የልጋ ላይ ግን አንበሳ ነህ. ብላ ስትናዘዝላት እናቴ አያቴን ሰምታታለች።
“ይህ ደግሞ ሴት አያቴ
ወንድ አያቴን የምታፈቅረው
በዲፕሎማሲያዊ አነጋገር በዝምታው ነው ትበል እንጂ ጌታውን እንዳዬ ውሻ እግሩ ስር የሚያልወሰውሳት ሚስጥሩ ሴላ ነው፡፡
ሶራ የሚገርምህ ግን እናቴ ያችን ቀን ፆታዬን
ያወቅሁበትና ረሃቤን ለማዳመጥ ትእግስት የጎደለኝና የተመኘሁትን
ያጣሁበት ቀን ናት' ብላ ታስታውሳለች፡፡
ይህ በሆነ ከአምስት ዓመት በኋላ ግን እናቴ ከአባቴ
ከፍራንሲስኮ ፔሶ ቤኒ ጋር ከሁዌልቫ ወደ ሊዝበን ለጉብኝት ስትሄድ
ተዋውቀው ግንኙነታቸውና መግባባታቸው እየጨመረ ሲሄድ የብርቱካን ማሳቸውን ልታሳየው ቀጠረችው፡፡
👍32
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ትልቁ የሮማ ስታዲዬም በተመልካቾች ተጨናንቋል፡፡
መንገዶች ተጣበዋል
ለተሽከርካሪ ዝግ በሆነው መንገድ ላይ ህዝቡ
እንደ ጉንዳን ይርመሰመሳል፡ ሳቅ ጨዋታ, ዳንኪራ ሁሉም እንደየግል ዝንባሌው ያሻውን ይፈፅማል። ከዘመናዊው ስታዲዬም
በጣልያንኛ በእንግሊዝኛ• በፈረንሳይኛ… ስለውድድሩ ታላቅነት ስለ ውድድሩ አጀማመር ተወዳዳሪዎች ምርጥነት ስለ ያሸንፋሉ
ተብለው ስለሚገመቱ አትሌቶች በተለያየ ቋንቋ ይተነበያል።
አኜስ ሎካዬን ወደ ሮማ እንዲሄድና ውድድሩን እንዲያይ ያግባባቸው ከብዘ ልፋትና ድካም በኋላ ነው፡፡
“…ሉካዬ ውድድሩን ማዬት መቻል አለብን!” ስትለው:
"አኜስ አንች ሂጂ እኔ ግን እዚሁ መቆየት እፈልጋለሁ።
ምናልባት አንቺ ከተመለሽ በኋላ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ሄጄ ዘመዶቼን ብፈልግ ደስ ይለኛል"
“ሎካዬ አብረኸኝ እንድትሆን እፈልጋለሁ: ጣልያን ውስጥ ጥሩ የመዝናናት እድል ይኖረናል። ወንድሜና ሴት ጓደኛው አብረን እንድንሆን ይፈልጋሉ ልጃችንም ክሪናም ከሁለታችን ጋር መሆኑን
እንደምትመርጥ ነግራኛለች፡፡
“ሊሆን ይችላል አኜስ ከእነሱ ይልቅ አንች እኔን በሚገባ ታውቂኛለሽ፡ ሮማ በመሄድ ደስተኛ ይሆናል ብለሽ እንደማትገምች
ነው የማስበው፡ እዚህ ብሆን ግን ቢያንስ የልጅነት ጊዜዬን እያሰብኩ
በፀጥታው ልዝናና እችላለሁ: ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስም በመሄድ
በማዕበሉ ውሃ እግሮቼን እየነከርሁ ለመደሰት እሞክራለሁ: ሮም ሄጄ ግን ጎንና ጎኔ ጨዋታ ወዳድና ደስተኛ ሰዎች ይቀመጡና
እየጎነታተሉ እንድጫወት ተፅዕኖ ያደርጉብኛል፡፡ እየቆየ ግን ዝምታዬ እየከበዳቸው ሲመጣ ይሸሹኛል። ያኔ ጩኸቱ በሚያስበረግግ
ፀጥታ እዋጥና አዕምሮዬ ይረበሻል። ስለዚህ አኜስ! እባክሽን እኔን እንሂድ ማለትሽን ተይኝና ከሌሉች ጋር ሄደሽ ተዝናንተሽ ተመለሽ አላት ረጋ ብሎ
“ኦ አምላኬ! ለምን ይኸን ቅዠትህን አታቆምም። ስግብግብ አትሁን እሽ! ለሌሎች ደስታ ማሰብ መቻል ኦለብህ፡ ግትርነትህንና
የገነተረ አስተሳሰብህን አለዝበው" አፈጠጠችበት፡፡
…ለሌሎች ደስታ ማሰብ መቻል አለብህ አባባሏ ውስጡን ረበሸው፡ ሉካዩ ራሱን አይወድም ሌሎች ደስ ሲላቸው ማየት
ያረካዋል። እራሱን ግን ለማዝናናት እንዳይችል በልጅነቱ ከወላጆቹና
ከዘመዶቹ ካደገበት ቀዬ ነጥቀው በጭንቀት በሃዘን… እያለቀሰ!
ማንነታቸውን የማያውቃቸው ሰዎች እንደ
አውሬ ደስታውን
ገነጣጥለው በልተውበታል፡ ተስፋውን አምክነውበታል፧ ስሜቱን ጭምትርትር አድርገው አኮራምተውበታል፡፡ እድሜው እየጨመረ
በሄደ ቁጥር ከጠባሳው በታች ሊድን የማይችል የቁስሉ ጎሚ እየበረታበት መጣ። ራሱን ሊያክም ሞከረ ውስጡ ግን እያመረቀዘ በሰራ አካላቱ የስቃይ መርዙ ተሰራጨ፡
“አኜስ! ለምን ስቃዬን አትረጅልኝም ሁሌ ለሞን አሸናፊነት ትመርጫለሽ!"
“ሎካዬ! ተው እንዲህ ምርር አትበል ልለይህ አለመፈለጌ
ላንተ ካለማሰብ የመጣ ነው ብለህ ታስባለህ? እንደዚያማ ላለማሰብ
ሞክር" ብላ አንገቷን ሰበር ስታደርግ ሎካዬ ጠጋ ብሎ ፀጉሯን ደባበሰና፡-
“ይቅር በይኝ እሽ አብረን እንሄዳለን" ሲል ቀና ብላ
አይታው እንባዋ ከአይኖችዋ ረገፉ:: ሎካዬ ግን እንባዋን ማየቱ
ከብዶት ፀጉሯን ስሞ ወጣ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በተለያየ ቀለማት ያሸበረቁ ወጣት ወንዶችና ሴቶች ሜዳውን ሞልተው እክሮባት ሲያሳዩ እንደቆዩ እውቁ ጣሊያናዊ አቀንቃኝ
ከሙዚቃው ጋር አጣጥሞ ድምፁ ሲያስረቀርቀው በስቴዲየሙ ውስጥ
ያለው ህዝብ አድናቆቱን በጭብጨባ በፉጨት በጩኸት በጥሩንባ በከበሮ
ሲገልፅ ድምፃዊው አሳ እንደሚውጥ ትልቅ አሳ ፉን
ከፍቶ ሲዘፍን በስታዲየሙ ዙሪያ የተደገኑት ማጉያዎች ድምፁን አስተጋቡት:: አሁንም ጭብጨባ ጩኸት ደስታ ሁካታ ሆነ፤
ጭፈራው ቀለጠ፡ ርችት ተለኮሰ፡፡
ከዚያ ከያገሩ የመጡት ሯጮች ወደ መወዳደሪያው ቦታ ሲወጡ ተመልካቹ
ቆሞ በጭብጨባ
ተቀበላቸው፡፡ ከያገሩ
ስለተወከሉት ተወዳዳሪዎች ማንነት ጋዜጠኞች በየቋንቋው መዘርዘር
ቀጠሉ፡
አኜስ ሎካዬ ከሪናና የአኜስ ወንድም ከሴት ጓደኛው ጋር
ሮም ስታዲዬም ናቸው: ከሎካዬ በስተቀር ሁሉም ያጨበጭባሉ ብድግ ቁጭ ይላሉ ይለፈልፋሉ… ሎካዬ ግን በብዙ ሺ ህዝብ መሀል ሆኖ ያልማል የልጅነቱን ህይወት የወላጆቹን ቀዬ...
ተወዳዳሪዎች ተደረደሩ፤ ችቦው ተለኮሰ፤ ማራቶን የሮማ ማራቶን ተጀመረ፡
ከዚያ በስቴዲየሙ ውስጥ የጥቂት አትሌቶች ገድልና
በዛኔው ውድድርም ያሸንፉ ይሆናል የሚለው ግምት ተለፈፈ፡፡አውሮፓውያን አሜሪካውያን ሩቀ ምስራቆች የአሰለፏቸው
አትሌቶች መጠን በ ውድድር አፍሪካውያን ተወዳዳሪዎችም በተወሰኑ አትሌቶች መወከላቸው ተነገረ፡፡
ከክርስቶስ ልደት በፊት በአራት መቶ ዘጠና በፔርሽያና አቴና በተፈጠረው ድንገተኛ የጦር ወረራ ትንኮሳ የተደናገጡት
አቴናውያን ፊዲፒደስ የተባለውን ጀግና ስፖርት ላኩት: ፊዲፒደስም
ለሃምሳ ሰዓታት ካለ ምግብና መጠጥ ሩጦ መልዕክቱን አድርሶ
በመመለሱ ውጊያው ተጀመረ፡፡
የአምባገነኑ የፔርሺያ ኃይል
ግን የማታ ማታ ሟሾ የውጊያው ድል ፎክሮ ጦር አውድማ ከሄደው ከፔርሽያው መሪ
ከዳሪዮስ እጅ ወጥቶ አቴናውያን እጅ ገባ፡፡
የአቴና ፍቅር ያማለለው ጀግናው ሯጭና ተዋጊ
ፌዲፒደስም ያንን ያገሩን ታላቅ ድል ሲያይ ደስታ
ፈንቅሎት አቅጠበጠው ስለዚህ ያንን ታላቅ ድል ለወገኑ ለማብሰር ቂጤማ
የያዘች እርግቡን ህሊናው ቆጥ ላይ አስፍሮ ሀያ ሁለት ማይልስ ካለ እረፍት የተነሳውን ክቡር ቃል ሊያደርስ ሮጠ፡፡
ፊዲፒደስ ከተማ
ሲደርስ አካሉ ደክሞ ! ሕይወቱ የተንጠለጠለችው ጠንካራ ሞራሉ ላይ ነበርና ወገን ሊያገኝ ያን
እንደ አልማዝ የሚያንፀባርቅ ቃል እያከለከለከ “ቪክትሪ" ብሉ ቃሏን ብቻ አሰምቶ ህዝቡ ሲደሰት እሱ ግን ሕይወቱን ለአገሩ ድል ሰዋ እየሳቀ አንቀላፋ!
መልካም ሥራና እውነት
ግን ውሎ አድሮ ከትቢያ
መነሳታቸው የክብር ሥፍራቸውን መያዛቸው አይቀርምና በአስራ
ስምንት መቶ ዘጠና ስድስት ግሪኮች የፊዲፒደስን ውለታ ለመክፈልተ ተስማሙ፡፡ መልካሙ ስሙን ከመቃብር ውጭ ሊያውለበልቡት
አቀዱ! ስለዚህ ባምላካቸው መሪ በዜውስ ስም ሰይመው የኦለምፒክ
ማራቶን ጀመሩ… ያ የመልካም ስራ ሽቶ መዓዛም አለማችንን
አወዳት፡፡ ከዚያ የማራቶን ሩጫ ውድድር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱንና በምዕራባውያን አገሮች በተለይ ሩጫን ዘመናዊ
ለማድረግ ሳይንሳዊ አሰለጣጠን ዘዴዎች እየተስፋፉ መምጣታቸውን አትሌቶች ከህፃንነታቸው ጀምሮ እየተመለመሉ ድንቅ
ተወዳዳሪዎችን ማፍራት መቻሉም ተናገረ፡፡
ሚዲያዎች ተወዳዳሪዎች የደረሱበትን ማን እየመራ
እንደሆነ ገለፁ፡፡የሚመራው አፍሪካዊ' ነው ሲባል ስለ ዘመናዊ የሩጫ አሰለጣጠን ዘዴ የሰማው ተመልካች ግራ የገባው መሰለ፡፡ብዙዎች ግን በማራቶን እሩጫ ትልቁ ዘዴ ትንፋሽን መጠበቅና ሃይልን እየቆጠቡ ቆይቶ የተወስነ ርቀት ሲቀር አፈትልኮ እንደ
ቀስት መወርወር ነው፡፡ ሲጀመር አካባቢ የቀደመ በስተመጨረሻ አትሌቶችን እየተሰናበተ ውራ ይወጣል' እየተባባሉ ተሳለቁ፡፡
ህዝቡን ከሚያዝናና ዝግጅቶች ጣልቃ ላይ የማራቶን ተወዳዳሪዎች ደረጃ እንደገና ተጠቀሰ:: አሁንም “አፍሪካዊው
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ትልቁ የሮማ ስታዲዬም በተመልካቾች ተጨናንቋል፡፡
መንገዶች ተጣበዋል
ለተሽከርካሪ ዝግ በሆነው መንገድ ላይ ህዝቡ
እንደ ጉንዳን ይርመሰመሳል፡ ሳቅ ጨዋታ, ዳንኪራ ሁሉም እንደየግል ዝንባሌው ያሻውን ይፈፅማል። ከዘመናዊው ስታዲዬም
በጣልያንኛ በእንግሊዝኛ• በፈረንሳይኛ… ስለውድድሩ ታላቅነት ስለ ውድድሩ አጀማመር ተወዳዳሪዎች ምርጥነት ስለ ያሸንፋሉ
ተብለው ስለሚገመቱ አትሌቶች በተለያየ ቋንቋ ይተነበያል።
አኜስ ሎካዬን ወደ ሮማ እንዲሄድና ውድድሩን እንዲያይ ያግባባቸው ከብዘ ልፋትና ድካም በኋላ ነው፡፡
“…ሉካዬ ውድድሩን ማዬት መቻል አለብን!” ስትለው:
"አኜስ አንች ሂጂ እኔ ግን እዚሁ መቆየት እፈልጋለሁ።
ምናልባት አንቺ ከተመለሽ በኋላ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ሄጄ ዘመዶቼን ብፈልግ ደስ ይለኛል"
“ሎካዬ አብረኸኝ እንድትሆን እፈልጋለሁ: ጣልያን ውስጥ ጥሩ የመዝናናት እድል ይኖረናል። ወንድሜና ሴት ጓደኛው አብረን እንድንሆን ይፈልጋሉ ልጃችንም ክሪናም ከሁለታችን ጋር መሆኑን
እንደምትመርጥ ነግራኛለች፡፡
“ሊሆን ይችላል አኜስ ከእነሱ ይልቅ አንች እኔን በሚገባ ታውቂኛለሽ፡ ሮማ በመሄድ ደስተኛ ይሆናል ብለሽ እንደማትገምች
ነው የማስበው፡ እዚህ ብሆን ግን ቢያንስ የልጅነት ጊዜዬን እያሰብኩ
በፀጥታው ልዝናና እችላለሁ: ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስም በመሄድ
በማዕበሉ ውሃ እግሮቼን እየነከርሁ ለመደሰት እሞክራለሁ: ሮም ሄጄ ግን ጎንና ጎኔ ጨዋታ ወዳድና ደስተኛ ሰዎች ይቀመጡና
እየጎነታተሉ እንድጫወት ተፅዕኖ ያደርጉብኛል፡፡ እየቆየ ግን ዝምታዬ እየከበዳቸው ሲመጣ ይሸሹኛል። ያኔ ጩኸቱ በሚያስበረግግ
ፀጥታ እዋጥና አዕምሮዬ ይረበሻል። ስለዚህ አኜስ! እባክሽን እኔን እንሂድ ማለትሽን ተይኝና ከሌሉች ጋር ሄደሽ ተዝናንተሽ ተመለሽ አላት ረጋ ብሎ
“ኦ አምላኬ! ለምን ይኸን ቅዠትህን አታቆምም። ስግብግብ አትሁን እሽ! ለሌሎች ደስታ ማሰብ መቻል ኦለብህ፡ ግትርነትህንና
የገነተረ አስተሳሰብህን አለዝበው" አፈጠጠችበት፡፡
…ለሌሎች ደስታ ማሰብ መቻል አለብህ አባባሏ ውስጡን ረበሸው፡ ሉካዩ ራሱን አይወድም ሌሎች ደስ ሲላቸው ማየት
ያረካዋል። እራሱን ግን ለማዝናናት እንዳይችል በልጅነቱ ከወላጆቹና
ከዘመዶቹ ካደገበት ቀዬ ነጥቀው በጭንቀት በሃዘን… እያለቀሰ!
ማንነታቸውን የማያውቃቸው ሰዎች እንደ
አውሬ ደስታውን
ገነጣጥለው በልተውበታል፡ ተስፋውን አምክነውበታል፧ ስሜቱን ጭምትርትር አድርገው አኮራምተውበታል፡፡ እድሜው እየጨመረ
በሄደ ቁጥር ከጠባሳው በታች ሊድን የማይችል የቁስሉ ጎሚ እየበረታበት መጣ። ራሱን ሊያክም ሞከረ ውስጡ ግን እያመረቀዘ በሰራ አካላቱ የስቃይ መርዙ ተሰራጨ፡
“አኜስ! ለምን ስቃዬን አትረጅልኝም ሁሌ ለሞን አሸናፊነት ትመርጫለሽ!"
“ሎካዬ! ተው እንዲህ ምርር አትበል ልለይህ አለመፈለጌ
ላንተ ካለማሰብ የመጣ ነው ብለህ ታስባለህ? እንደዚያማ ላለማሰብ
ሞክር" ብላ አንገቷን ሰበር ስታደርግ ሎካዬ ጠጋ ብሎ ፀጉሯን ደባበሰና፡-
“ይቅር በይኝ እሽ አብረን እንሄዳለን" ሲል ቀና ብላ
አይታው እንባዋ ከአይኖችዋ ረገፉ:: ሎካዬ ግን እንባዋን ማየቱ
ከብዶት ፀጉሯን ስሞ ወጣ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በተለያየ ቀለማት ያሸበረቁ ወጣት ወንዶችና ሴቶች ሜዳውን ሞልተው እክሮባት ሲያሳዩ እንደቆዩ እውቁ ጣሊያናዊ አቀንቃኝ
ከሙዚቃው ጋር አጣጥሞ ድምፁ ሲያስረቀርቀው በስቴዲየሙ ውስጥ
ያለው ህዝብ አድናቆቱን በጭብጨባ በፉጨት በጩኸት በጥሩንባ በከበሮ
ሲገልፅ ድምፃዊው አሳ እንደሚውጥ ትልቅ አሳ ፉን
ከፍቶ ሲዘፍን በስታዲየሙ ዙሪያ የተደገኑት ማጉያዎች ድምፁን አስተጋቡት:: አሁንም ጭብጨባ ጩኸት ደስታ ሁካታ ሆነ፤
ጭፈራው ቀለጠ፡ ርችት ተለኮሰ፡፡
ከዚያ ከያገሩ የመጡት ሯጮች ወደ መወዳደሪያው ቦታ ሲወጡ ተመልካቹ
ቆሞ በጭብጨባ
ተቀበላቸው፡፡ ከያገሩ
ስለተወከሉት ተወዳዳሪዎች ማንነት ጋዜጠኞች በየቋንቋው መዘርዘር
ቀጠሉ፡
አኜስ ሎካዬ ከሪናና የአኜስ ወንድም ከሴት ጓደኛው ጋር
ሮም ስታዲዬም ናቸው: ከሎካዬ በስተቀር ሁሉም ያጨበጭባሉ ብድግ ቁጭ ይላሉ ይለፈልፋሉ… ሎካዬ ግን በብዙ ሺ ህዝብ መሀል ሆኖ ያልማል የልጅነቱን ህይወት የወላጆቹን ቀዬ...
ተወዳዳሪዎች ተደረደሩ፤ ችቦው ተለኮሰ፤ ማራቶን የሮማ ማራቶን ተጀመረ፡
ከዚያ በስቴዲየሙ ውስጥ የጥቂት አትሌቶች ገድልና
በዛኔው ውድድርም ያሸንፉ ይሆናል የሚለው ግምት ተለፈፈ፡፡አውሮፓውያን አሜሪካውያን ሩቀ ምስራቆች የአሰለፏቸው
አትሌቶች መጠን በ ውድድር አፍሪካውያን ተወዳዳሪዎችም በተወሰኑ አትሌቶች መወከላቸው ተነገረ፡፡
ከክርስቶስ ልደት በፊት በአራት መቶ ዘጠና በፔርሽያና አቴና በተፈጠረው ድንገተኛ የጦር ወረራ ትንኮሳ የተደናገጡት
አቴናውያን ፊዲፒደስ የተባለውን ጀግና ስፖርት ላኩት: ፊዲፒደስም
ለሃምሳ ሰዓታት ካለ ምግብና መጠጥ ሩጦ መልዕክቱን አድርሶ
በመመለሱ ውጊያው ተጀመረ፡፡
የአምባገነኑ የፔርሺያ ኃይል
ግን የማታ ማታ ሟሾ የውጊያው ድል ፎክሮ ጦር አውድማ ከሄደው ከፔርሽያው መሪ
ከዳሪዮስ እጅ ወጥቶ አቴናውያን እጅ ገባ፡፡
የአቴና ፍቅር ያማለለው ጀግናው ሯጭና ተዋጊ
ፌዲፒደስም ያንን ያገሩን ታላቅ ድል ሲያይ ደስታ
ፈንቅሎት አቅጠበጠው ስለዚህ ያንን ታላቅ ድል ለወገኑ ለማብሰር ቂጤማ
የያዘች እርግቡን ህሊናው ቆጥ ላይ አስፍሮ ሀያ ሁለት ማይልስ ካለ እረፍት የተነሳውን ክቡር ቃል ሊያደርስ ሮጠ፡፡
ፊዲፒደስ ከተማ
ሲደርስ አካሉ ደክሞ ! ሕይወቱ የተንጠለጠለችው ጠንካራ ሞራሉ ላይ ነበርና ወገን ሊያገኝ ያን
እንደ አልማዝ የሚያንፀባርቅ ቃል እያከለከለከ “ቪክትሪ" ብሉ ቃሏን ብቻ አሰምቶ ህዝቡ ሲደሰት እሱ ግን ሕይወቱን ለአገሩ ድል ሰዋ እየሳቀ አንቀላፋ!
መልካም ሥራና እውነት
ግን ውሎ አድሮ ከትቢያ
መነሳታቸው የክብር ሥፍራቸውን መያዛቸው አይቀርምና በአስራ
ስምንት መቶ ዘጠና ስድስት ግሪኮች የፊዲፒደስን ውለታ ለመክፈልተ ተስማሙ፡፡ መልካሙ ስሙን ከመቃብር ውጭ ሊያውለበልቡት
አቀዱ! ስለዚህ ባምላካቸው መሪ በዜውስ ስም ሰይመው የኦለምፒክ
ማራቶን ጀመሩ… ያ የመልካም ስራ ሽቶ መዓዛም አለማችንን
አወዳት፡፡ ከዚያ የማራቶን ሩጫ ውድድር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱንና በምዕራባውያን አገሮች በተለይ ሩጫን ዘመናዊ
ለማድረግ ሳይንሳዊ አሰለጣጠን ዘዴዎች እየተስፋፉ መምጣታቸውን አትሌቶች ከህፃንነታቸው ጀምሮ እየተመለመሉ ድንቅ
ተወዳዳሪዎችን ማፍራት መቻሉም ተናገረ፡፡
ሚዲያዎች ተወዳዳሪዎች የደረሱበትን ማን እየመራ
እንደሆነ ገለፁ፡፡የሚመራው አፍሪካዊ' ነው ሲባል ስለ ዘመናዊ የሩጫ አሰለጣጠን ዘዴ የሰማው ተመልካች ግራ የገባው መሰለ፡፡ብዙዎች ግን በማራቶን እሩጫ ትልቁ ዘዴ ትንፋሽን መጠበቅና ሃይልን እየቆጠቡ ቆይቶ የተወስነ ርቀት ሲቀር አፈትልኮ እንደ
ቀስት መወርወር ነው፡፡ ሲጀመር አካባቢ የቀደመ በስተመጨረሻ አትሌቶችን እየተሰናበተ ውራ ይወጣል' እየተባባሉ ተሳለቁ፡፡
ህዝቡን ከሚያዝናና ዝግጅቶች ጣልቃ ላይ የማራቶን ተወዳዳሪዎች ደረጃ እንደገና ተጠቀሰ:: አሁንም “አፍሪካዊው
👍25🥰2👏2❤1🔥1😁1
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታረ
“ሶራ ልታስብበት ይገባል" አለችው በጥሞና እያየችው፡
"ወደ ኢትዮጵያ አብሬሽ ልሂድና የአያትሽን የትውልድ ቦታ ላፈላልግሽ እፈልጋለሁ፡፡ ያሳየሽኝ መቀመጫ ታችኛው የኦሞ ወንዝ አካባቢ ነዋሪ የሆኑ ማህበረሰቦች በሙሉ ይጠቀሙበታል። ኤርቦሬ
ሐመር በና ካሮ መቀመጫው በእርግጥም የኦሞ ህዝቦች ብቻ
እንደሆነ አምናላሁ" አላት።
ጥሩ! እኔ የተዘጋጀሁት ለአንድ ሰው በሚበቃ ባጀት ነው" በግልፅ ችግሯን ገለፀችለት፡
“እኔ ደግሞ የራሴን እችላለሁ በዚያ በኩል አታስቢ"
አመሠግናለሁ ሶራ በእውነት አንተን ማግኘቴ ያላሰብሁት
እድል ነው" ብላ ፈገግ አለችለት::
ሶራና ኮንችት በዚህ መልክ ለአፍሪካ ጉዞዋቸው
መሰናዶአቸውን አብረው ቀጠሉ፡፡
ከሁዌልቫ ሊዝበን በመርከብ የሚፈጀወ ጊዜ ግማሽ ቀን ብቻ ነው፡፡ ከጅበላርታር ለንደን በሚወስደው የጉዞ መስመር መርከቡ
አቅጣጫውን ካስተካከለ በኋላ ተጓዡ እንደየግል ፍላጎቱ ተሰማራ፡፡
ኮንችትና ሶራ በመርhቡ ግራ ጎን ባለው ማማ ላይ ወጥተው በርቀት የተዘረጋውን የአትላንቲክ ውቅያኖስ እያዩ ተቀምጠዋል፡፡
ኮንችትና ሶራ የለበሱት ነጭ ቲሸርት ነው፡፡ በሁለቱ መካከል የአለባበስ ልዩነቱ ኮንችት ነጭ አጭር ቀሚስ በሰፊ ቀበቶ ሶራ
ደግሞ ቡላ ሲልክ ሱሪ መልበሳቸው ነው፡፡ ሁለቱም ጥቁር የፀሐይ መነፅር አድርገዋል። ቀኑ ሞቃታማና ፀሐያማ ነው፡፡
ወደ ሊዝበን የመሄዱን ሐሳብ ያመጣችው ኮንችት ናት ሶራን የተለያዩ ቦታዎችን ሙዚዬሞችን ታሪካዊ ቦታዎችን መዝናኛዎችን… እንዲያይ ብዙ ጊዜ እየጋበዘች ወስዳዋለች፡፡
ስለ ፖርቹጋሎች ምን ታውቃለህ?" አለችው አንድ ቀን በማድሪድ ከተማ መናፈሻ ውስጥ እንደተቀመጡ፡፡
“ባህረተኞችና ቅኝ ገዥዎች እንደነበሩ"
“አዎ! ፖርቹጋሎች ማንም እሚያውቃቸው በባህር ላይ
ህይወታቸውና ለቅኝ ገዥነት በብዙው የዓለም ክፍል በተለይም በአፍሪካና በላቲን አሜሪካ ያደርጉት የነበረውን ቅኝት ነው፡ ይህ ጥንት ሌላው ስለእነሱ ያውቅ የነበረው እውቀት ነው በአሁን ሰዓት ግን ፖርቹጋል ብዙ ቱሪስት የሚስተናገድባት አገር ናት።
“ሙዚየሞቻቸው የዓለምን ቅርስ የያዙ ናቸው ይባላል።
ስለ ዓለም ይበልጥ ማወቅ የማፈልገው ይህ ትውልድ ደግሞ ቅርሶች አሉ የተባለበት መጉረፉ የተለመደ ነው፡፡
“አፍሪካ የራሷ ካሏት ቅርሶች ይልቅ በአውሮፓ ያሏት ቅርሶች ይበልጣሉ፡ የሚያሳዝነው ግን አፍሪካ ለቅርሷ የባለቤትነት
መብት የላትም፡፡ በኮለኒያሊስቶች የተዘረፈችው ቅርስ አሁንም የእነሱ ኪስ ማድለቢያ ነው፡፡
“ከኢትዮጵያ የመጡ
ቅርሶች ከዚህ በፊት ፈረንሳይ እንግሊዝ ጣሊያን… ሄጄ አይቻለሁ፡፡ ፖርቹጋልም እንደዚሁ ብዙ
የሃይማኖት መጽሐፍትና የታሪክ ቅርሶች አሉ: አንዳንዴ ሳስበው እንዲያውም ኢትዮጵያውያን
የታሪክ የባህል ተመራማሪዎች ወደ ፊት በአገራቸው ታሪክና ባህል ላይ ምርምር ማድረግ ቢፈልጉ ዋቢ ቅርሶችን ለማየት ወደ አውሮፓ ብቅ ማለታቸው የግድ
ይመስለኛል
“አውሮፖና በሌላው የሰለጠነው ዓለም አንድ ወቅት የቅርስ ዝርፊያ የነበረ ቢሆንም አሁን ግን በስምምነት አንዱ ዘንድ ያለው ወደ ሌላው እየተመለሰ ነው። ባይመለስ እንኳን የዛ ቅርስ ባለቤት
የሚሆነው በመጀመሪያ ባለቤት የነበረው አገር ነው፡፡ ለዚህ ውጤት
ግን ብዙዎች ልሳናቸው እስኪዘጋ እየጮሁ ታግለዋል፡፡ ግዞት ስደት
እስራትም ደርሶባቸዋል: አሁን ግን ቀስ በቀስ ህልማቸው እውን
እየሆነ ነው:
ሶራ አንተም ፖርቹጋል ያሉትን ሙዚየሞች ስታይ
እርግጠኛ ነኝ ብዙ የአገርህን ቅርሶች ታያለህ የኢትዮጵያ ቅርሶች
የሚል ጽሁፍ ግን አይታይባቸውም፡፡ አንድ እውነት ግን በህሊናህ
ይመጣል! ቅርስ ለአንድ ሀገር ህዝብ ማንነት ምን ያህል አስፈላጊ
መሆኑን ትገነዘባለህ፡፡
የአውሮፓውያን ስልጣኔ ባሰባሰቡት ቅርስ ላይ የተመስረተ ነው ለቅርሶች ልዩ ከበሬታ መስጠትም የአንድ ሃገር ስልጣኔያዊ
ብስለት መለኪያ ነው፡
“ሶራ ስለ! ሌላውን ለማወቅ ከሌላው ለመማር ራስሀን
ለማነፃዐር ያጣኸውን ለመፈለግ… ጉብኝት አስፈላጊ ነው" አለችው፡፡
ልክ ነሽ ኮንችት ለምን ለጊዜው ፖርቹጋልን አብረን
አናይም?” አላት፡
“በደስታ! ሶራ" ብላ ሳቋን ለቀቀችው: ኪሊሊ... የሚለውን ሳቋን ሰማው: ናፍቆት ነበር ሣቋ::
“ሳቅሽ ደስ ይለኛል አላት ፈገግ ብሎ፡፡
“አመለግናለሁ” አለችው። ኪሊሊ ብላ እየሳቀች:: እያያት አሰበ: ሌላውን ማወቅ ነው….. የተናገረችውን አስታወሰ፡
አውሮፓውያን ስልጣኔ ባሰባሰቡት ቅርስ ላይ የተመሰተ ነው ገረመው: በልተህ በልተህ ወደ አገርህ አንጋጥ ተሪቱማ እሱም
አገር አለ፡፡ ተግባሩ ግን ጠፋ፡፡ ሌላው እስኪጀምረው መጠበቅ አንዱ የአፍሪካውያን ችግር ነው። እና የሚጠቅመውን ሁሉ ለአገሩ ጆሮ
ለማድረስ ለአገሩ ሕዝብ ለማሳየት የተማረውን ዜጋ ህሊና ለማንኳኪያ ከእንቅልፍ ለመቀስቀሻ ሊጠቀምበት እንደሚገባ ቃል ገባ: እራሱን ግን ተጠራጠረው “ፍርፋሬ ያዘናጋኝ ይሆን?” አለ።
ኮንችት ያለውን አልሰማችም፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሁለቱ መንገደኞች መርከቡ ጉዞ ከጀመረ በኋላ
ጨዋታቸውን ጀመሩ፡፡
“…ለወላጆቼ የመጀመሪያ ነኝ፡ ከኔ በታች ሁለት ታናናሽ
ወንድሞች አሉኝ፡ በተለይ ከኔ ተከታይ ጋር በሰፊ አልጋ አብረን ነበር የምንተኛው።
አባቴ ፍራንሲስኮ ፔሶ ቤኒ ለወደፊቱ መፃኢ እድላችን
ስለሚያስብ ገንዘብ ለማስቀመጥ ቢጥርም ግማሽ ኢትዮጵያዊቷ እናቱ
ካሪና ግን ለግል ውበቷ ብቻ የምትጪነቅ አባካኝ በመሆኗ አባቴ
እንዳሰበው ገንዘብ የማስቀመጥ ህልሙ አልሳካ ሲለው በእናቴና
በአባቴ መካከል አለመጣጣሙ እየበዛ በመምጣቱ ተለያዩ በዚህ
ሳቢያ አባቴ ወደ ቤታችን የሚመጣው በጣም እየቆዬ ሆነ፡ እኔ ደግሞ የመጀመሪያ ልጅ እንደመሆኔ መጠን የአባቴን ፍቅር በምሻበት
ወቅት ላገኘው ባለመቻሌ ከልቤ ጠላሁት ስለዚህ ከአባቴ ይልቅ ለኢትዮያዊው አያቴ ለሎካዬ ሆነ ፍቅሬ” ብላ ክሊሊ… ብላ ሳቀች
እሱም ፈገግ አለ ጉሮሮዋን ለማራስ የቆርቆሮ ቢራዋን ለመክፈት ዘወር ስትል የቢራው ቆርቆሮ ወደቀባት ለማንሳት ጎንበስ ስትል
አየው ጥቁር ፓንቷን
አፈር አለና ፊቱን ወደ አትላንቲክ ውቂያኖስ አዙሮ
ሲመለከት hርቀት የሆነ ብረት አዬ
ኮንችት ተመልከች ያ ምንድው?” አላት።
መርከብ ነው የመሬት ክብነትን ስትማር ስለዚህ
አልተማርህም..."
አዎ አሁን ትዝ አለኝ: ሳታይ የተማርሽው ቶሎ
ይዘነጋል እሽ ጨዋታሽን ቀጥይ? አላት አንጋጣ አንዴ ጉንጯን ሞልታ ተጎነጨችና
"ኧህ ብላ ጨዋታዋን ያቆመችበትን አሰብ በማድረግ
ቸበርቻቻ ወዳጅዋን እናቴን ግን እወዳት ነበር በፊት
እንነገርሁህ በቁመናዬ ሳቢያ በትርፍ ጊዜዬ የግል ገቢ ማግኘት የጀመርሁት ገና በህፃንነቴ ቢሆንም እናቴ እናደ ሌሉች ልጆች
አስባ ልብስ ስለማትገልኝና ከሷ የምጠብቀውን አንድም ቀን "ቆንጆ ብላኝ ስለማታውቅ ለእሷ የነበረኝ ፍቅር እየሟሽሽ የጥላቻ
ስሜት ህሊናዬን ይተናነቀው ጀመር አንድ ቀን እንዲያውም አባቴ ጠፍቶ ከርሞ በመጣበት አጋጣሚ
እናቴና አባቴ አንድ ላይ በሚገኙበት ወቅት ጠባቂ በነበረኝ ገንዘብ ላይ ስጦታ ገዝቼ አልጋቸው ላይ አስቀመጥኩላቸ
ንግግሯን ሳትጨርስ ሶራ
አቋረጣትና
ይቅታ ስላቋረጥኩሽ የዚያን ጊዜ የስንት ዓመት ልጅ ነበረሽ።
ምናልባት የአስራ አራት ዓመት ከዚያ አይበልጠኝም
አለችው።
እሽ ቀጥይ አላት ሶራ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታረ
“ሶራ ልታስብበት ይገባል" አለችው በጥሞና እያየችው፡
"ወደ ኢትዮጵያ አብሬሽ ልሂድና የአያትሽን የትውልድ ቦታ ላፈላልግሽ እፈልጋለሁ፡፡ ያሳየሽኝ መቀመጫ ታችኛው የኦሞ ወንዝ አካባቢ ነዋሪ የሆኑ ማህበረሰቦች በሙሉ ይጠቀሙበታል። ኤርቦሬ
ሐመር በና ካሮ መቀመጫው በእርግጥም የኦሞ ህዝቦች ብቻ
እንደሆነ አምናላሁ" አላት።
ጥሩ! እኔ የተዘጋጀሁት ለአንድ ሰው በሚበቃ ባጀት ነው" በግልፅ ችግሯን ገለፀችለት፡
“እኔ ደግሞ የራሴን እችላለሁ በዚያ በኩል አታስቢ"
አመሠግናለሁ ሶራ በእውነት አንተን ማግኘቴ ያላሰብሁት
እድል ነው" ብላ ፈገግ አለችለት::
ሶራና ኮንችት በዚህ መልክ ለአፍሪካ ጉዞዋቸው
መሰናዶአቸውን አብረው ቀጠሉ፡፡
ከሁዌልቫ ሊዝበን በመርከብ የሚፈጀወ ጊዜ ግማሽ ቀን ብቻ ነው፡፡ ከጅበላርታር ለንደን በሚወስደው የጉዞ መስመር መርከቡ
አቅጣጫውን ካስተካከለ በኋላ ተጓዡ እንደየግል ፍላጎቱ ተሰማራ፡፡
ኮንችትና ሶራ በመርhቡ ግራ ጎን ባለው ማማ ላይ ወጥተው በርቀት የተዘረጋውን የአትላንቲክ ውቅያኖስ እያዩ ተቀምጠዋል፡፡
ኮንችትና ሶራ የለበሱት ነጭ ቲሸርት ነው፡፡ በሁለቱ መካከል የአለባበስ ልዩነቱ ኮንችት ነጭ አጭር ቀሚስ በሰፊ ቀበቶ ሶራ
ደግሞ ቡላ ሲልክ ሱሪ መልበሳቸው ነው፡፡ ሁለቱም ጥቁር የፀሐይ መነፅር አድርገዋል። ቀኑ ሞቃታማና ፀሐያማ ነው፡፡
ወደ ሊዝበን የመሄዱን ሐሳብ ያመጣችው ኮንችት ናት ሶራን የተለያዩ ቦታዎችን ሙዚዬሞችን ታሪካዊ ቦታዎችን መዝናኛዎችን… እንዲያይ ብዙ ጊዜ እየጋበዘች ወስዳዋለች፡፡
ስለ ፖርቹጋሎች ምን ታውቃለህ?" አለችው አንድ ቀን በማድሪድ ከተማ መናፈሻ ውስጥ እንደተቀመጡ፡፡
“ባህረተኞችና ቅኝ ገዥዎች እንደነበሩ"
“አዎ! ፖርቹጋሎች ማንም እሚያውቃቸው በባህር ላይ
ህይወታቸውና ለቅኝ ገዥነት በብዙው የዓለም ክፍል በተለይም በአፍሪካና በላቲን አሜሪካ ያደርጉት የነበረውን ቅኝት ነው፡ ይህ ጥንት ሌላው ስለእነሱ ያውቅ የነበረው እውቀት ነው በአሁን ሰዓት ግን ፖርቹጋል ብዙ ቱሪስት የሚስተናገድባት አገር ናት።
“ሙዚየሞቻቸው የዓለምን ቅርስ የያዙ ናቸው ይባላል።
ስለ ዓለም ይበልጥ ማወቅ የማፈልገው ይህ ትውልድ ደግሞ ቅርሶች አሉ የተባለበት መጉረፉ የተለመደ ነው፡፡
“አፍሪካ የራሷ ካሏት ቅርሶች ይልቅ በአውሮፓ ያሏት ቅርሶች ይበልጣሉ፡ የሚያሳዝነው ግን አፍሪካ ለቅርሷ የባለቤትነት
መብት የላትም፡፡ በኮለኒያሊስቶች የተዘረፈችው ቅርስ አሁንም የእነሱ ኪስ ማድለቢያ ነው፡፡
“ከኢትዮጵያ የመጡ
ቅርሶች ከዚህ በፊት ፈረንሳይ እንግሊዝ ጣሊያን… ሄጄ አይቻለሁ፡፡ ፖርቹጋልም እንደዚሁ ብዙ
የሃይማኖት መጽሐፍትና የታሪክ ቅርሶች አሉ: አንዳንዴ ሳስበው እንዲያውም ኢትዮጵያውያን
የታሪክ የባህል ተመራማሪዎች ወደ ፊት በአገራቸው ታሪክና ባህል ላይ ምርምር ማድረግ ቢፈልጉ ዋቢ ቅርሶችን ለማየት ወደ አውሮፓ ብቅ ማለታቸው የግድ
ይመስለኛል
“አውሮፖና በሌላው የሰለጠነው ዓለም አንድ ወቅት የቅርስ ዝርፊያ የነበረ ቢሆንም አሁን ግን በስምምነት አንዱ ዘንድ ያለው ወደ ሌላው እየተመለሰ ነው። ባይመለስ እንኳን የዛ ቅርስ ባለቤት
የሚሆነው በመጀመሪያ ባለቤት የነበረው አገር ነው፡፡ ለዚህ ውጤት
ግን ብዙዎች ልሳናቸው እስኪዘጋ እየጮሁ ታግለዋል፡፡ ግዞት ስደት
እስራትም ደርሶባቸዋል: አሁን ግን ቀስ በቀስ ህልማቸው እውን
እየሆነ ነው:
ሶራ አንተም ፖርቹጋል ያሉትን ሙዚየሞች ስታይ
እርግጠኛ ነኝ ብዙ የአገርህን ቅርሶች ታያለህ የኢትዮጵያ ቅርሶች
የሚል ጽሁፍ ግን አይታይባቸውም፡፡ አንድ እውነት ግን በህሊናህ
ይመጣል! ቅርስ ለአንድ ሀገር ህዝብ ማንነት ምን ያህል አስፈላጊ
መሆኑን ትገነዘባለህ፡፡
የአውሮፓውያን ስልጣኔ ባሰባሰቡት ቅርስ ላይ የተመስረተ ነው ለቅርሶች ልዩ ከበሬታ መስጠትም የአንድ ሃገር ስልጣኔያዊ
ብስለት መለኪያ ነው፡
“ሶራ ስለ! ሌላውን ለማወቅ ከሌላው ለመማር ራስሀን
ለማነፃዐር ያጣኸውን ለመፈለግ… ጉብኝት አስፈላጊ ነው" አለችው፡፡
ልክ ነሽ ኮንችት ለምን ለጊዜው ፖርቹጋልን አብረን
አናይም?” አላት፡
“በደስታ! ሶራ" ብላ ሳቋን ለቀቀችው: ኪሊሊ... የሚለውን ሳቋን ሰማው: ናፍቆት ነበር ሣቋ::
“ሳቅሽ ደስ ይለኛል አላት ፈገግ ብሎ፡፡
“አመለግናለሁ” አለችው። ኪሊሊ ብላ እየሳቀች:: እያያት አሰበ: ሌላውን ማወቅ ነው….. የተናገረችውን አስታወሰ፡
አውሮፓውያን ስልጣኔ ባሰባሰቡት ቅርስ ላይ የተመሰተ ነው ገረመው: በልተህ በልተህ ወደ አገርህ አንጋጥ ተሪቱማ እሱም
አገር አለ፡፡ ተግባሩ ግን ጠፋ፡፡ ሌላው እስኪጀምረው መጠበቅ አንዱ የአፍሪካውያን ችግር ነው። እና የሚጠቅመውን ሁሉ ለአገሩ ጆሮ
ለማድረስ ለአገሩ ሕዝብ ለማሳየት የተማረውን ዜጋ ህሊና ለማንኳኪያ ከእንቅልፍ ለመቀስቀሻ ሊጠቀምበት እንደሚገባ ቃል ገባ: እራሱን ግን ተጠራጠረው “ፍርፋሬ ያዘናጋኝ ይሆን?” አለ።
ኮንችት ያለውን አልሰማችም፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሁለቱ መንገደኞች መርከቡ ጉዞ ከጀመረ በኋላ
ጨዋታቸውን ጀመሩ፡፡
“…ለወላጆቼ የመጀመሪያ ነኝ፡ ከኔ በታች ሁለት ታናናሽ
ወንድሞች አሉኝ፡ በተለይ ከኔ ተከታይ ጋር በሰፊ አልጋ አብረን ነበር የምንተኛው።
አባቴ ፍራንሲስኮ ፔሶ ቤኒ ለወደፊቱ መፃኢ እድላችን
ስለሚያስብ ገንዘብ ለማስቀመጥ ቢጥርም ግማሽ ኢትዮጵያዊቷ እናቱ
ካሪና ግን ለግል ውበቷ ብቻ የምትጪነቅ አባካኝ በመሆኗ አባቴ
እንዳሰበው ገንዘብ የማስቀመጥ ህልሙ አልሳካ ሲለው በእናቴና
በአባቴ መካከል አለመጣጣሙ እየበዛ በመምጣቱ ተለያዩ በዚህ
ሳቢያ አባቴ ወደ ቤታችን የሚመጣው በጣም እየቆዬ ሆነ፡ እኔ ደግሞ የመጀመሪያ ልጅ እንደመሆኔ መጠን የአባቴን ፍቅር በምሻበት
ወቅት ላገኘው ባለመቻሌ ከልቤ ጠላሁት ስለዚህ ከአባቴ ይልቅ ለኢትዮያዊው አያቴ ለሎካዬ ሆነ ፍቅሬ” ብላ ክሊሊ… ብላ ሳቀች
እሱም ፈገግ አለ ጉሮሮዋን ለማራስ የቆርቆሮ ቢራዋን ለመክፈት ዘወር ስትል የቢራው ቆርቆሮ ወደቀባት ለማንሳት ጎንበስ ስትል
አየው ጥቁር ፓንቷን
አፈር አለና ፊቱን ወደ አትላንቲክ ውቂያኖስ አዙሮ
ሲመለከት hርቀት የሆነ ብረት አዬ
ኮንችት ተመልከች ያ ምንድው?” አላት።
መርከብ ነው የመሬት ክብነትን ስትማር ስለዚህ
አልተማርህም..."
አዎ አሁን ትዝ አለኝ: ሳታይ የተማርሽው ቶሎ
ይዘነጋል እሽ ጨዋታሽን ቀጥይ? አላት አንጋጣ አንዴ ጉንጯን ሞልታ ተጎነጨችና
"ኧህ ብላ ጨዋታዋን ያቆመችበትን አሰብ በማድረግ
ቸበርቻቻ ወዳጅዋን እናቴን ግን እወዳት ነበር በፊት
እንነገርሁህ በቁመናዬ ሳቢያ በትርፍ ጊዜዬ የግል ገቢ ማግኘት የጀመርሁት ገና በህፃንነቴ ቢሆንም እናቴ እናደ ሌሉች ልጆች
አስባ ልብስ ስለማትገልኝና ከሷ የምጠብቀውን አንድም ቀን "ቆንጆ ብላኝ ስለማታውቅ ለእሷ የነበረኝ ፍቅር እየሟሽሽ የጥላቻ
ስሜት ህሊናዬን ይተናነቀው ጀመር አንድ ቀን እንዲያውም አባቴ ጠፍቶ ከርሞ በመጣበት አጋጣሚ
እናቴና አባቴ አንድ ላይ በሚገኙበት ወቅት ጠባቂ በነበረኝ ገንዘብ ላይ ስጦታ ገዝቼ አልጋቸው ላይ አስቀመጥኩላቸ
ንግግሯን ሳትጨርስ ሶራ
አቋረጣትና
ይቅታ ስላቋረጥኩሽ የዚያን ጊዜ የስንት ዓመት ልጅ ነበረሽ።
ምናልባት የአስራ አራት ዓመት ከዚያ አይበልጠኝም
አለችው።
እሽ ቀጥይ አላት ሶራ
👍21
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
“እናቴም አባቴም ስለዚያ የልጅነት ስጦታዬ ትንፍሽ ሳይሉኝ ስጦታውን ግን እየተቀባበሉ ሲያዩት አይቻቸዋለሁ ይህ ደሞ አይወዱኝም ማት ነው የሚል ስሜት ፈጠረብኝና
ያልደነደነችው ልቤ ሐዘን እንደ ደሰቀ ዳቦ ነካከተች ከዚያን ቀን በኋላ ከነሱ የምለይበትን ቀን ማሰላሰል ጀመርሁ
“በየቀኑም ከነሱ ለመራቅና እነሱን ለመርሳት ስል የወንድ ጓደኛ ያዝሁ
የያዝኋቸውን የወንድ ጓደኞቼን እንድርቃቸው ተገደድሁ።
“እናቴ እንደነገርሁ የስነ አዕምሮ ትምህርት እውቀት
አላት ይሄ እከሌ የሚባለው የወንድ ጓደኛዬ ነው ስላት፡-
የጨካኝ ሰው መልክ ነው ያለው፡፡ ወንጀል ለመሥራት ወደ ኋላ አይልም…” ትለዋለች ወይም ደግሞ፡-ዠ
“ይኸ ጅላጅል ነው: የታወረ አዕምሮ ያለው ነው፡፡ እና
እሱን ስትመሪ መኖር ትፈልጊያሽ" ትለኛለች፡፡ ሌላውን ሳስተዋውቃት
ደግሞ፡-
ይኸ ጭልፋ አፍንጫ አንድ ቀን አይንሽን ያወጣዋል: እንደ ጣውላ የተላገ የሚመስል የወንድ ቅርፅ የሌለው... እኔ አንችን
ብሆን ኖሮ ከሱ ጋር በሆንሁ ቁጥር በጥላቻ አስመልስ ነበር….እያለች ስታጥላላብኝ ከያዝኋቸው የወንድ ጓደኞቼ በሙሉ ራቅሁ: በኋላ ግን ወደ ቤታችን አልፎ አልፎ ብቅ ከሚለው የእናቴ ጓደኛ
ልጅ ጋር ግንኙነት ጀመርሁ፡
ፔድሮ ይባላል፡ ሙልቅቅ ያለ ባህሪው መያዣ መጨበጫ የሌለው ነው፡፡ ከፍቅር ይልቅ የጦርነት ታሪክ ማውራት ይወዳል:
ህዝብ ከተጨናነቀበት መዝናኛ መሃል ይወስደኝና ጉሮሮው እስኪሰነጠቅ እየጮኸ ጩኸትና ሁካታ አልወድም' ይለኛል ማን
ለምኖህ መጣህ? ደሞ ማንስ ጩኸት ይወዳል እንዳንተ ካለው ደደብ
በስተቀር' እልና በሃሳቤ እነቂው እነቂው ያሰኘኛል፡፡ አማራጭ ግን አልነበረኝም፡፡ ወላጆቼን ለመርሳት ስል በሄደበት ሁሉ እንደ ግል
ውሻው ካለሰንሰለት እየተሳብሁ እሄድለታለሁ! ሁኝ ያለኝንም እሆንለት ጀመር፡፡ እናቴም ከእሱ ጋር መሆን ደገፈችልኝ
የማላይበትን ውበት እየደረደረች አይታይሽም፧ እስኪ ተመልከች
እያለች እራሴን አይነ ስውር እንደሆንሁ እስክቆጥር ድረስ ግራ አጋባችኝ፡፡ ስለዚህ ፔድሮን በእናቴ ግፊት ልወደው ሞከርኩ፡
“የግንኙነቴን ጥልቀትና እንደ እንቁላል ተጠንቅቄ
እንደያዝሁት የተገነዘበው
ፔድሮ ግን ልቡ እያበጠ
ለፍቅር የዘረጋሁሉትን ልቤን ይጠብሰው ጀመር! እየቆየም በመጥፎ ባህሪው እየወጋጋ ማድማቱን ቀጠለ፡፡ ከእሱ ከተለየሁ ብቸኝነቱን ስለማልችለውግን
ስቃዬን አምቂ በትዕግስት እየተለማመጥሁ
የሞዴሊስነት ፍላጎቴን ገትቼ ለሶስት ዓመታት የመከራ ጊዜ አሳለፍሁ?።
“ሶራ! የሚገርምህ ደግሞ ያ የጭራቅ ልጅ አንድም ቀን "ቆንጆ ነሽ" ብሎኝ አያውቅም፡፡እንደወላጆቼ እሱም አሞካሽቶኝ
አለማወቁ ደግሞ ፍርሃት ለቀቀብኝ፡፡ ከውጪ ሰው ይልቅ እነሱ ቆንጆ ነሽ ቢሉኝ ደስተኛ እሆን ነበር፡ ይህን ባለማለታቸው ግን
እራሴን ለማወቅ ወደ ሞዴሊስትነቱ ሞያ ተመለስሁ፡፡ ጅምናዚዬም
መሄድ አዘወተርሁ፡ በቁንጅና ውድድር ከተመረጡት አንዷ ብሆንም
ማሸነፍ ባለመቻሌ በገንሁ፡፡ ፔድሮ ያኔም ይጀነንንብኝ ነበር በመጨረሻ በቁንጅና ውድድሩ ባሽነፍሁበት እለት እናቴ አበባ አበረከተችልኝ፤ እሱ ግን ሳይመጣ ቀረ፡፡
“የሚገርምህ ያን ጭራቅ እንዲያ አንጀቴን እየበጣጠሰ ሲጥለው ልርቀው አልቻልሁም፡፡ ስለዚህ ከስፔን ውጭ ሄዶ ሥራ መስራት ማስታወቂያ ሲወጣ ከቤተሰቦቼ ለመራቅና እፎይታን
ለማግኘት አመች በመሆኑ እሱም እንዲወዳደርና አብረን እንድንሄድ
ጠየኩት፡፡
“ምን እንዳለኝ ታውቃለህ? ማራኪዋን አገሬን ጥዬ የትም አልሄድም አለኝ፡፡ የዚያን ቀን ብቻ ደፍሬ ገሃነም ግባ ብየው
በማስታወቂያው መሰረት ሄጄ አፍሪካ በተለይም አያቴ አገር ኢትዮጵያ እንዲመድቡኝ ጠየኳቸው፡፡ ሆኖም አላሰመረም፡ ሌሎች የአፍሪካ አገሮች እንጂ ኢትዮጵያ ከዝርዝሩ
ውስጥ እንደሌለችበት ሲነግረኝ እጢዬ ዱብ አለች፡፡ ከዚያ በኋላ ግን
ምርጫዬ አስፈላጊ ስላልነበረ የትም መድቡኝ ስላቸው ቡርኪናፋሶ
መደቡኝ፡፡
ሶራ የሚሳዝንህ ፔድሮ ውጭ አገር እንደማይሄድ
እንዳልነገረኝ ሁሉ ሃሣቤን ቀይሬ ተወዳድሬ ላቲን አሜሪካ ብራዚልን አግኝቻለሁና አብረን እንሃድ' አለኝ፡፡
የዛኑ እለት እኔጋ የነበረውን የአፓርታማችንን ቁልፍ
ወርውሬለት ሁለተኛ አጠገቤ እንዳይደርስ አስጠንቅቄው ሄድሁ፡፡ ከሱ
ከተለየሁ በኋላ ግን አይኔ የፈረጠ እስኪመስለኝ ድረስ ሳለቅስ አደርሁ: ጠዋት ከመኝታዬ ስነሳ ትክክለኛ ውሳኔ መወስኔን በመረዳቴ ትልቅ እፎይታ ተሰማኝ፡፡
“በልጅነቴ የወላጅ.
ከአደግሁ በኋላ ደግሞ የፍቅረኛዬ 'አፈቅርሻለሁ' አለማለት የማልወደድ
ቢያደርገኝም ወደ አፍሪካ ከመሄዴ ሦስት ወራት በፊት
የተዋወኳቸው የተለያዩ ወንዶች ግን ውበቴን እያዩ የተንጠለጠለ ሥጋ እንዳየ ድመት እየተቁለለጩ ሲያላዝኑ ስሰማና በተለይም
በጓደኝነት የያዝሁት ፎራንችስኮ መላ ሰውነቴን እየላሰ “ቆንጆ ነሽ…
ውሸት ነው!.." እያለ ደርቆ የነበረውን ሞራሌን በፍቅር ዜማ ሲያረሰርሰው ድርቆሹ ሞራሌ እንደገና ለመለመ፤ እንደገና ታነፀ….አፍሪካ ሄጄ ስመለስ ግን የቁንጅናን ትልቁን ትርጉም አወቅሁት‥
አካላዊ ሳይሆን ህሊናዊ መሆኑን….
“ሶራ! ይታይሃል ከፊት ለፊታችን ሊዝበን ናት
የፖርቹጋል ዋና ከተማ፡፡ ወደ ጕብኝት ቦታችን እየደረስን ነው" ብላው ከመርከቡ መቀመጫ ተነሳችና ሄድ ብላ ወገቧን ለማንቀሳቀስ ከወገቧ እጥፍ ብላ ስፖርት ስትሰራ አየው ጥቁር ፓንቷን…
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
"ሔሉ… ሔሉ… ካርለት አልፈርድ ነኝ ከአዲስ አበባ"
"ሃይ ካርለት! ደህና ነሽ? ስፖንሽኛውን ስታቀላጥፈው
ገረመኝ እኮ"
“እውነትሽን አመሰግናለሁ፡፡
አዲሳባ ከመጣሁ
አምስተኛ ቀኔ ነው፡፡ ወደ ሐመር ከአንድ ሣምንት በኋላ እሄዳለሁ፡፡ መቼ ልትመጭ አስሰሻል?"
“አዝናለሁ ላገኝሽ የምችል አይመስለኝም፤ ምክንያቱም እኔ ከማድሪድ ወደ ሮም ከዚያ ወደ አዲሳባ የምበረው የዛሬ አስራ
አምስት ቀን ነው፡፡ ባገኝሽ ደስ ይለኝ ነበር፡፡
“አልችልም ኮንችት ቶሉ መሄድ አለብኝ፡፡ ምናልባት…" ካርለት ፀጥ ብላ አሰበችናi “ምናልባት አዲሳባ ስትመጭ የሚቀበልሽ ሰው ላስተዋውትሽ እችላለሁ፡፡ ሔሎ! …”
“አመሰግናለሁ ካርለት፡፡ አንችን ማግኘት ካልቻልኩ ለጊዜው ችግር የሚያጋጥመኝ አይመስለኝም፧ አብሮኝ የሚመጣ ኢትዮጵያዊ
አለ ሔሎ!"
“ሔሎ ኢትዮጵያዊ!” ካርለት አዕምሮዋ ደነሰባት፡፡
“ጥሩI እንግዲያው እዚህ ከመጣሽ በኋላ" ተቀጣጠሩና ካርለት ስልኩን ዘጋችው፡፡ በአይነህሊናዋ ኮንችትን ልታስታውሳት
ሞከረች ረጅም ሸንቀጥ ያለች ውብ ጠይም! ካርለት ከንፈሯን እንደ ጡጦ ጠብታ እራሷን ወዘወዘች፡፡
::::::::::::::::::::::::::::::
ካርለት ዋና የለመደችበትን
ጊዜ አታስታውሰውም፡
ምናልባት በእናቷ ሆድ ካለበለዚያም ገና ጨቅላ እያለች፡ ቁም ነገር
ብሎ የነገራት የለም፡፡ ጥሩ ዋናተኛ ሆና ነው ራሷን የምታውቀው፡
ግዮን ሆቴል የሄደችውም ለመዋኘት ነው፡፡ ብቅ ጥልቅ, ብቅ ጥልቅ
ውሃው ውስጥ ግልብጥ እያለች የግዮንን ሆቴል መዋኛ በቁመትና በወርዱ እየዋኘች አሳ ሆና ለመቆየት፡፡ ከዚያ ፎጣዋን አንጥፋ ገላዋን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
“እናቴም አባቴም ስለዚያ የልጅነት ስጦታዬ ትንፍሽ ሳይሉኝ ስጦታውን ግን እየተቀባበሉ ሲያዩት አይቻቸዋለሁ ይህ ደሞ አይወዱኝም ማት ነው የሚል ስሜት ፈጠረብኝና
ያልደነደነችው ልቤ ሐዘን እንደ ደሰቀ ዳቦ ነካከተች ከዚያን ቀን በኋላ ከነሱ የምለይበትን ቀን ማሰላሰል ጀመርሁ
“በየቀኑም ከነሱ ለመራቅና እነሱን ለመርሳት ስል የወንድ ጓደኛ ያዝሁ
የያዝኋቸውን የወንድ ጓደኞቼን እንድርቃቸው ተገደድሁ።
“እናቴ እንደነገርሁ የስነ አዕምሮ ትምህርት እውቀት
አላት ይሄ እከሌ የሚባለው የወንድ ጓደኛዬ ነው ስላት፡-
የጨካኝ ሰው መልክ ነው ያለው፡፡ ወንጀል ለመሥራት ወደ ኋላ አይልም…” ትለዋለች ወይም ደግሞ፡-ዠ
“ይኸ ጅላጅል ነው: የታወረ አዕምሮ ያለው ነው፡፡ እና
እሱን ስትመሪ መኖር ትፈልጊያሽ" ትለኛለች፡፡ ሌላውን ሳስተዋውቃት
ደግሞ፡-
ይኸ ጭልፋ አፍንጫ አንድ ቀን አይንሽን ያወጣዋል: እንደ ጣውላ የተላገ የሚመስል የወንድ ቅርፅ የሌለው... እኔ አንችን
ብሆን ኖሮ ከሱ ጋር በሆንሁ ቁጥር በጥላቻ አስመልስ ነበር….እያለች ስታጥላላብኝ ከያዝኋቸው የወንድ ጓደኞቼ በሙሉ ራቅሁ: በኋላ ግን ወደ ቤታችን አልፎ አልፎ ብቅ ከሚለው የእናቴ ጓደኛ
ልጅ ጋር ግንኙነት ጀመርሁ፡
ፔድሮ ይባላል፡ ሙልቅቅ ያለ ባህሪው መያዣ መጨበጫ የሌለው ነው፡፡ ከፍቅር ይልቅ የጦርነት ታሪክ ማውራት ይወዳል:
ህዝብ ከተጨናነቀበት መዝናኛ መሃል ይወስደኝና ጉሮሮው እስኪሰነጠቅ እየጮኸ ጩኸትና ሁካታ አልወድም' ይለኛል ማን
ለምኖህ መጣህ? ደሞ ማንስ ጩኸት ይወዳል እንዳንተ ካለው ደደብ
በስተቀር' እልና በሃሳቤ እነቂው እነቂው ያሰኘኛል፡፡ አማራጭ ግን አልነበረኝም፡፡ ወላጆቼን ለመርሳት ስል በሄደበት ሁሉ እንደ ግል
ውሻው ካለሰንሰለት እየተሳብሁ እሄድለታለሁ! ሁኝ ያለኝንም እሆንለት ጀመር፡፡ እናቴም ከእሱ ጋር መሆን ደገፈችልኝ
የማላይበትን ውበት እየደረደረች አይታይሽም፧ እስኪ ተመልከች
እያለች እራሴን አይነ ስውር እንደሆንሁ እስክቆጥር ድረስ ግራ አጋባችኝ፡፡ ስለዚህ ፔድሮን በእናቴ ግፊት ልወደው ሞከርኩ፡
“የግንኙነቴን ጥልቀትና እንደ እንቁላል ተጠንቅቄ
እንደያዝሁት የተገነዘበው
ፔድሮ ግን ልቡ እያበጠ
ለፍቅር የዘረጋሁሉትን ልቤን ይጠብሰው ጀመር! እየቆየም በመጥፎ ባህሪው እየወጋጋ ማድማቱን ቀጠለ፡፡ ከእሱ ከተለየሁ ብቸኝነቱን ስለማልችለውግን
ስቃዬን አምቂ በትዕግስት እየተለማመጥሁ
የሞዴሊስነት ፍላጎቴን ገትቼ ለሶስት ዓመታት የመከራ ጊዜ አሳለፍሁ?።
“ሶራ! የሚገርምህ ደግሞ ያ የጭራቅ ልጅ አንድም ቀን "ቆንጆ ነሽ" ብሎኝ አያውቅም፡፡እንደወላጆቼ እሱም አሞካሽቶኝ
አለማወቁ ደግሞ ፍርሃት ለቀቀብኝ፡፡ ከውጪ ሰው ይልቅ እነሱ ቆንጆ ነሽ ቢሉኝ ደስተኛ እሆን ነበር፡ ይህን ባለማለታቸው ግን
እራሴን ለማወቅ ወደ ሞዴሊስትነቱ ሞያ ተመለስሁ፡፡ ጅምናዚዬም
መሄድ አዘወተርሁ፡ በቁንጅና ውድድር ከተመረጡት አንዷ ብሆንም
ማሸነፍ ባለመቻሌ በገንሁ፡፡ ፔድሮ ያኔም ይጀነንንብኝ ነበር በመጨረሻ በቁንጅና ውድድሩ ባሽነፍሁበት እለት እናቴ አበባ አበረከተችልኝ፤ እሱ ግን ሳይመጣ ቀረ፡፡
“የሚገርምህ ያን ጭራቅ እንዲያ አንጀቴን እየበጣጠሰ ሲጥለው ልርቀው አልቻልሁም፡፡ ስለዚህ ከስፔን ውጭ ሄዶ ሥራ መስራት ማስታወቂያ ሲወጣ ከቤተሰቦቼ ለመራቅና እፎይታን
ለማግኘት አመች በመሆኑ እሱም እንዲወዳደርና አብረን እንድንሄድ
ጠየኩት፡፡
“ምን እንዳለኝ ታውቃለህ? ማራኪዋን አገሬን ጥዬ የትም አልሄድም አለኝ፡፡ የዚያን ቀን ብቻ ደፍሬ ገሃነም ግባ ብየው
በማስታወቂያው መሰረት ሄጄ አፍሪካ በተለይም አያቴ አገር ኢትዮጵያ እንዲመድቡኝ ጠየኳቸው፡፡ ሆኖም አላሰመረም፡ ሌሎች የአፍሪካ አገሮች እንጂ ኢትዮጵያ ከዝርዝሩ
ውስጥ እንደሌለችበት ሲነግረኝ እጢዬ ዱብ አለች፡፡ ከዚያ በኋላ ግን
ምርጫዬ አስፈላጊ ስላልነበረ የትም መድቡኝ ስላቸው ቡርኪናፋሶ
መደቡኝ፡፡
ሶራ የሚሳዝንህ ፔድሮ ውጭ አገር እንደማይሄድ
እንዳልነገረኝ ሁሉ ሃሣቤን ቀይሬ ተወዳድሬ ላቲን አሜሪካ ብራዚልን አግኝቻለሁና አብረን እንሃድ' አለኝ፡፡
የዛኑ እለት እኔጋ የነበረውን የአፓርታማችንን ቁልፍ
ወርውሬለት ሁለተኛ አጠገቤ እንዳይደርስ አስጠንቅቄው ሄድሁ፡፡ ከሱ
ከተለየሁ በኋላ ግን አይኔ የፈረጠ እስኪመስለኝ ድረስ ሳለቅስ አደርሁ: ጠዋት ከመኝታዬ ስነሳ ትክክለኛ ውሳኔ መወስኔን በመረዳቴ ትልቅ እፎይታ ተሰማኝ፡፡
“በልጅነቴ የወላጅ.
ከአደግሁ በኋላ ደግሞ የፍቅረኛዬ 'አፈቅርሻለሁ' አለማለት የማልወደድ
ቢያደርገኝም ወደ አፍሪካ ከመሄዴ ሦስት ወራት በፊት
የተዋወኳቸው የተለያዩ ወንዶች ግን ውበቴን እያዩ የተንጠለጠለ ሥጋ እንዳየ ድመት እየተቁለለጩ ሲያላዝኑ ስሰማና በተለይም
በጓደኝነት የያዝሁት ፎራንችስኮ መላ ሰውነቴን እየላሰ “ቆንጆ ነሽ…
ውሸት ነው!.." እያለ ደርቆ የነበረውን ሞራሌን በፍቅር ዜማ ሲያረሰርሰው ድርቆሹ ሞራሌ እንደገና ለመለመ፤ እንደገና ታነፀ….አፍሪካ ሄጄ ስመለስ ግን የቁንጅናን ትልቁን ትርጉም አወቅሁት‥
አካላዊ ሳይሆን ህሊናዊ መሆኑን….
“ሶራ! ይታይሃል ከፊት ለፊታችን ሊዝበን ናት
የፖርቹጋል ዋና ከተማ፡፡ ወደ ጕብኝት ቦታችን እየደረስን ነው" ብላው ከመርከቡ መቀመጫ ተነሳችና ሄድ ብላ ወገቧን ለማንቀሳቀስ ከወገቧ እጥፍ ብላ ስፖርት ስትሰራ አየው ጥቁር ፓንቷን…
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
"ሔሉ… ሔሉ… ካርለት አልፈርድ ነኝ ከአዲስ አበባ"
"ሃይ ካርለት! ደህና ነሽ? ስፖንሽኛውን ስታቀላጥፈው
ገረመኝ እኮ"
“እውነትሽን አመሰግናለሁ፡፡
አዲሳባ ከመጣሁ
አምስተኛ ቀኔ ነው፡፡ ወደ ሐመር ከአንድ ሣምንት በኋላ እሄዳለሁ፡፡ መቼ ልትመጭ አስሰሻል?"
“አዝናለሁ ላገኝሽ የምችል አይመስለኝም፤ ምክንያቱም እኔ ከማድሪድ ወደ ሮም ከዚያ ወደ አዲሳባ የምበረው የዛሬ አስራ
አምስት ቀን ነው፡፡ ባገኝሽ ደስ ይለኝ ነበር፡፡
“አልችልም ኮንችት ቶሉ መሄድ አለብኝ፡፡ ምናልባት…" ካርለት ፀጥ ብላ አሰበችናi “ምናልባት አዲሳባ ስትመጭ የሚቀበልሽ ሰው ላስተዋውትሽ እችላለሁ፡፡ ሔሎ! …”
“አመሰግናለሁ ካርለት፡፡ አንችን ማግኘት ካልቻልኩ ለጊዜው ችግር የሚያጋጥመኝ አይመስለኝም፧ አብሮኝ የሚመጣ ኢትዮጵያዊ
አለ ሔሎ!"
“ሔሎ ኢትዮጵያዊ!” ካርለት አዕምሮዋ ደነሰባት፡፡
“ጥሩI እንግዲያው እዚህ ከመጣሽ በኋላ" ተቀጣጠሩና ካርለት ስልኩን ዘጋችው፡፡ በአይነህሊናዋ ኮንችትን ልታስታውሳት
ሞከረች ረጅም ሸንቀጥ ያለች ውብ ጠይም! ካርለት ከንፈሯን እንደ ጡጦ ጠብታ እራሷን ወዘወዘች፡፡
::::::::::::::::::::::::::::::
ካርለት ዋና የለመደችበትን
ጊዜ አታስታውሰውም፡
ምናልባት በእናቷ ሆድ ካለበለዚያም ገና ጨቅላ እያለች፡ ቁም ነገር
ብሎ የነገራት የለም፡፡ ጥሩ ዋናተኛ ሆና ነው ራሷን የምታውቀው፡
ግዮን ሆቴል የሄደችውም ለመዋኘት ነው፡፡ ብቅ ጥልቅ, ብቅ ጥልቅ
ውሃው ውስጥ ግልብጥ እያለች የግዮንን ሆቴል መዋኛ በቁመትና በወርዱ እየዋኘች አሳ ሆና ለመቆየት፡፡ ከዚያ ፎጣዋን አንጥፋ ገላዋን
👍20🥰1
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ሰማዩ ከአድማስ እስከ
አድማስ ዙሪያውን በከዋክብት ተጥለቅልቋል፡፡ አንዳንዶቹ ብርሃናቸው ደመቅ የሌሎቹ ደግሞ ፈዘዝ ቢልም ሁሉም ይብለጨለጫሉ፡ ብልጭ ድርግም፤ ብልጭ ድርግም
እያሉ፡ ጨረቃ የለችም ዳመናም የለም። ሰማዩ ግን ተውቧል፡፡ጨለማው
ለትናንሾቹ ከዋክብት ጠቅሟቸዋል። ውበታቸውን
የምትነፍጋቸው ጨረቃ፤ መኖራቸውን ጭራሽ የምታጠፋው ፀሐይ
የለችም።
“በህይወቴ እንዲህ እልፍ
አዕላፍ ከዋክብት አይቼ
አላውቅም፡፡ ለካ ሰማዩ ለእግር መቋሚያ የሌለው በከዋክብት የተጠቀጠቀ ነው!” አለና ወደ ሰማዩ አንጋጠጠ፡፡ ከዋክብቱ በድቅድቅ ጨለማው እየፈነደቁ ብርሃናቸውን ቦግ እልም ያደርጋሉ፡
“ድንቅ ነው ታምር፧ የጨለማ ውበት!” አለች ለምለሙ ሳር ላይበጀርባዋ
እንደተንጋለለች፡፡ ሁለቱም ግን አንዱ ሌላው ያለውን አልሰማም።
የጉደር ፏፏቴ ይንፏፏል፡፡ የጉደር ወንዝ ለሁለት ተከፍሎ አንዱ ከደልዳላው መሬት ላይ ተወርውሮ ድንጋይ ላይ ይፈጠፈጥና
ለሰዎች አይን የሚማርክ ነጭ አረፋ ፈጥሮ ህሊናን አርክቶ ሲፈስ ፧ በስተግራ ያለው ደግሞ አክሮባቱን ሳያሳይ በኩራት ቁልቁል እየፈሰሰ ከፏፏቴው ጋር ተመልሶ ይገናኛል፡፡ ወንዝ ሆኖ ለመፍሰስ… ትዝ
አለው ስዩምን ወንዙ፡፡
“ድንጋዩ ላይ ተፈጥፍጦ አረፋ የደፈቀው ውሃና በሰላም የተጓዘው ውሃ እንደገና ሲገናኙ ልዩነት አይኖራቸው ይሆን? የቱ
ይሆን እድሉን የሚያማርረው? ከድንጋይ ላይ ተላትሞ አረፋ
የደፈቀው ወይንስ ጓደኛው ያስቀናው ሰዎችን መማረክ ያልቻለው ውሃ ሆኖ ተፈጥሮ ከጎኑ የተለየው ውሃ እየተንፏፏ አረፋውን
ሲደፍቅ ሰዎች እጅ ወደ እሱ ሳይሆን ወደ ፏፏቴው ተቀስሮ እያዩ ወይ ነዶ እኔም
በውስጤ ያለውን አረፋ ደፍቄ አሳያቸው ነበር፡ ምን ያረጋል ውሃ መሆኔን ያኔ ያውቁ ነበር። እርጉም ጊዜ ግን እሱን ተመልካች
አጎረፈለት፤ እኔን አይቶ አድናቂ አሳጣኝ' ይል ይሆን! ብሎ አሰበ፡፡
ሁለቱም ፀጥታን ወዳጆች ናቸው በዚ ደግሞ
ተግባብተዋል፡ ጸጥታን የሚፈራ የራስ መተማመን የጎደለው ፈሪ
ነው፡፡ አካባቢውን የማያውቅ ጨቅላ አስተሳሰብ ያለው… ፀጥ ካላሉ የቅጠል ሹዋሹዋቴ አይሰማም የጨለማ ውበት አይታይም! የጽልመት ብርሃን የውበት ሚስጥር አይገለጥም… ፀጥታ የግዑዙ ዓለም ቁልፍ ነው የሚስጥራት መክፈቻ…
ይህን የተረዱት ጥቁሩና ነጯ ግንኙነታቸው ገና ያልጠበቀ ቢሆንም በፀጥታ ቋንቋ ተግባብተዋል፡፡ ሁለቱም የየራሳቸው ውበት
አላቸው ከቀለማቸው ጀምሮ።
ፏፏቴው ይንፏፏል የሌሊት ወፍ እንደ ንጋት ወፍ
የችሎታዋን እየዘመረች በጨለማው ትበራለች… ሁለቱም በየግላቸው
በፀጥታ የሙከራ መስሪያ ህሊናቸው ውስጥ እንደየአቅማቸው
ይመራመራሉ፡ ይቀንሳሉ ይደምራሉ አንዱ ሌላውን ያስባል፡፡
የጋዝ ምድጃው ላይ በብረት ድስት የጣዱት ፓስታ ክዳኑን
ሽቅብ እየገፋ ሲንፈቀፈቅ ግን ሁለቱም ከዚያ የፀጥታ ዓለማቸው ተመለሱ፡፡
ስዩም ከተቀመጠበት ተነስቶ ባትሪውን አብርቶ የብረት ድስቱን ክዳን ከፈተና ፓስታው መብሰል አለመብሰሉን አረጋገጠ
በስሏል… ለምግብነት ያመጡትን አቀራረቡ የጉደር ወይኑንም ዷ አድርገው ከፈቱ፡፡
"መልካም ራት!” አለችው፡፡
“ለአንችም” አላትና መብላት ጀመሩ
"ተወርዋሪ ኮከብ! ፈነደቀች፡፡
“ለብዙ ጊዜ ተወርዋሪ ኮከብ ስጠበቅ ነበር አሁን ግን አየሁ ዘግይቶም ቢሆን ያሰብሁት ይሳካል፡፡ አውሮፓ ውስጥ እንዲሁ ዓይነት እምነት አለ" አለችው፡፡ ስዩም ፈገግ ብሎ ራሱን ወዘወዘ ለአባባሏ እንግዳ አይመስልም፡፡
በሰባት ሰዓት ተኩል
ከአዲስ አበባ ተነስተው ገነት አዲሳለም ጊንጭ አምቦን እያዩ ጉደር የደረሱት ከምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት ላይ ነው፡፡ አምቦ ኢትዮጵያ ሆቴል ትልቁ ዋርካ ስር
ቁጭ ብለው ማራኪውን አትክልት ቦታ እያዩ ቆዩ፡
"ጥሩ አገር አለቻችሁ፡፡ ከአዲሳባ እዚህ ድረስ ትንፋሽ ቆራጩ ተፈጥሮ በደስታ እንዴት እንዳረካኝ ልገልፅልህ አልችልም”
አለችው።
"ገና ይቀርሻል: ጉደር ስንደርስ የጉደርን ተፈጥሮ ስታይ የማድነቂያ ቃል እንዳታጭ” አላት፡ በፈገግታ ግንባሯን ሰበሰበች፡፡
ከአምቦ አንድ አስር ኪሉ ሜትር እንደተጓዙ ጉደር ከተማ ገቡ፡ በከተማው መሃል አለፉ፡፡ ወደ ግራ ታጥፈው አልባሌ መዝጊያ
ያለው በር ላይ ቆሙ፡፡ ትህትና ያለው ዘበኛ እየሮጠ መጥቶ በሩን ከፈተላቸው፡፡ አናገሩት፡፡
ፏፏቴው ይንፎለፎላል፤ ድምፁን እየሰሙ ቁልቁል ወረዱና ብብቱ ስር ገቡ። ስዩም ካርለትን አያት “ዋው!” ብላ አፏን ከፍታ
አይኖችዋን ወረወረቻቸው አረፋው ላይ ለምለሙ ጫካ ላይ የበልግ እፀዋት ላይ… የመጨረሻዋ ማድነቂያ አባባሏ ሁለት ፊደል ሆነ “ዋው! ብቻ፡፡
ሁለቱም በልተው ጨረሱ
የጉደር ፏፏቴ ይሰማል
ካርለት የጉደርን ወይን በሁለት ብርጭቆ ቀድታ አንዱን ለስዩም ሰጠችው። “ለጤናችን ለኢትዮጰያውያን አዲስ ዓመት" አለችው:
በየመንገዱ ያየችው ቢጫ አበባ ከለምለም ቄጠማ ጋር በየሰዎች እቅፍ ላይ የነበረው አበባ፤ የኢትዮጵያ የአዲስ ዘመን አብሳሪ አደይ
አበባ እንደ ህፃንነቷ ከአረንጓዴው ለምለም መስክ እየቀነጠሰች
ችቦዋን ሞልታ መዓዛውን ባፍንጫዋ የሳበችው የአደይ አበባ ሽታ
መጣባት፡
ፏፏቴው ከብቶቹ ህፃናት… ቃናቸው ተዋህዶ “አደይ
አደይ አበባ…" እያሉ ያዜማሉ፡፡ ስዩም “ችቦው ተለኮሰ' አላት፡፡
“የምኑ” አለችው፡፡
“የአዲሱ ዓመት የአዲስ
ዘመን... የነገ ፈገግ አሉ
አንጋጠው ተጎነጩት ጉደሩን፡፡ ፀጥ አሉ እንደገና አዲሱን ነገ ህልሙን ነገ፤ ሽፍንፍኑን መጭ አመት እያዩ፡፡ ከዚያ ካርለት
ለመናገር ስትቁነጠነጥ አያት፡፡
“አመሰግናለሁ፡ በዚህ የደስታ ቀንህ አብሬህ እንድሆን ስለመረጥኸኝ" አለቸው:
“ምስጋና አያስፈልገኝም: ሌላ አብሮኝ ሊመጣ የሚችል ባለመኖሩ ነው" አላት፡፡
“ለምን?” አለችው ካርለት፡፡
“በአዲስ ዓመት ዋዜማ የአዲሳባን ሰው ወደ ገጠር ወጣ እንበል ብትይው ፀበል ይወስድሽና በመስቀል እያስደበደበ ሰባት ቀን
ቤት ያዘጋብሻል እብድ ነሽ ብሎ" አላት: በቀልድ አዘል አባባሉ ፈገግ አለችለት፡ ከጥርሷ ይልቅ ቀይ ከንፈሯን በከዋክብት የብርሃን ወጋገን አየው፡
ካርለት፧ እንግዳ ባህሪው
የሚገርማት ኢትዮጵያዊ
ዮትያትሪካል አርት ምሩቅ መሆኑን እንጂ የግል ህይወቱን አልዘረዘረላትም፡፡ የሴት ጓደኛ አለኝ ብሏት የነበረውም ትዝ አላት።
የሴት ጓደኛህስ ፍላጎትህን አትወድልህም?"
“እሷማ ሁሌም አብራኝ ነች፡፡ በውኔ ቀርቶ በህልሜም"
“አልገባኝም?" አለች ካርለት፡፡
"በገሃድ የሚሆነኝን አላገኘሁም !በምናቤ ግን
ፍቅርኛ አለችኝ
“ለምን?''
"የፈጠራ ሰዎች ግላዊ እምነታቸውን በተከተሉ ቁጥር ከህብረተሰቡ ጋር የነበራቸው የመግባባት ቅኝት እንደተበላሽ የሚገምተው ይበዛል። እነሱም የብቸኝነት ጥዑም ዜማው ያረካቸዋል፡፡ ስለዚv
ሌለች የሚወዱት ሙዚቃ ለእነሱ ጩኸት ይሆንባቸዋል፡፡
በምናቤ ግን ፍቅረኛ
“ቁም ነገሩ ግን ግላዊ ዓለማቸውም ውስጥ ሆነው
የህብረተሰቡን ህይወትና ቅላፄ ምንነት ለመረዳት ህሊናቸውን ወደ
ዱ ዓለም እየዶሉ እርቀው ይቀርባሉ፤ ከህዝቡ ጋር ይሆናሱ፤
፡
፡
#ክፍል_ሀያ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ሰማዩ ከአድማስ እስከ
አድማስ ዙሪያውን በከዋክብት ተጥለቅልቋል፡፡ አንዳንዶቹ ብርሃናቸው ደመቅ የሌሎቹ ደግሞ ፈዘዝ ቢልም ሁሉም ይብለጨለጫሉ፡ ብልጭ ድርግም፤ ብልጭ ድርግም
እያሉ፡ ጨረቃ የለችም ዳመናም የለም። ሰማዩ ግን ተውቧል፡፡ጨለማው
ለትናንሾቹ ከዋክብት ጠቅሟቸዋል። ውበታቸውን
የምትነፍጋቸው ጨረቃ፤ መኖራቸውን ጭራሽ የምታጠፋው ፀሐይ
የለችም።
“በህይወቴ እንዲህ እልፍ
አዕላፍ ከዋክብት አይቼ
አላውቅም፡፡ ለካ ሰማዩ ለእግር መቋሚያ የሌለው በከዋክብት የተጠቀጠቀ ነው!” አለና ወደ ሰማዩ አንጋጠጠ፡፡ ከዋክብቱ በድቅድቅ ጨለማው እየፈነደቁ ብርሃናቸውን ቦግ እልም ያደርጋሉ፡
“ድንቅ ነው ታምር፧ የጨለማ ውበት!” አለች ለምለሙ ሳር ላይበጀርባዋ
እንደተንጋለለች፡፡ ሁለቱም ግን አንዱ ሌላው ያለውን አልሰማም።
የጉደር ፏፏቴ ይንፏፏል፡፡ የጉደር ወንዝ ለሁለት ተከፍሎ አንዱ ከደልዳላው መሬት ላይ ተወርውሮ ድንጋይ ላይ ይፈጠፈጥና
ለሰዎች አይን የሚማርክ ነጭ አረፋ ፈጥሮ ህሊናን አርክቶ ሲፈስ ፧ በስተግራ ያለው ደግሞ አክሮባቱን ሳያሳይ በኩራት ቁልቁል እየፈሰሰ ከፏፏቴው ጋር ተመልሶ ይገናኛል፡፡ ወንዝ ሆኖ ለመፍሰስ… ትዝ
አለው ስዩምን ወንዙ፡፡
“ድንጋዩ ላይ ተፈጥፍጦ አረፋ የደፈቀው ውሃና በሰላም የተጓዘው ውሃ እንደገና ሲገናኙ ልዩነት አይኖራቸው ይሆን? የቱ
ይሆን እድሉን የሚያማርረው? ከድንጋይ ላይ ተላትሞ አረፋ
የደፈቀው ወይንስ ጓደኛው ያስቀናው ሰዎችን መማረክ ያልቻለው ውሃ ሆኖ ተፈጥሮ ከጎኑ የተለየው ውሃ እየተንፏፏ አረፋውን
ሲደፍቅ ሰዎች እጅ ወደ እሱ ሳይሆን ወደ ፏፏቴው ተቀስሮ እያዩ ወይ ነዶ እኔም
በውስጤ ያለውን አረፋ ደፍቄ አሳያቸው ነበር፡ ምን ያረጋል ውሃ መሆኔን ያኔ ያውቁ ነበር። እርጉም ጊዜ ግን እሱን ተመልካች
አጎረፈለት፤ እኔን አይቶ አድናቂ አሳጣኝ' ይል ይሆን! ብሎ አሰበ፡፡
ሁለቱም ፀጥታን ወዳጆች ናቸው በዚ ደግሞ
ተግባብተዋል፡ ጸጥታን የሚፈራ የራስ መተማመን የጎደለው ፈሪ
ነው፡፡ አካባቢውን የማያውቅ ጨቅላ አስተሳሰብ ያለው… ፀጥ ካላሉ የቅጠል ሹዋሹዋቴ አይሰማም የጨለማ ውበት አይታይም! የጽልመት ብርሃን የውበት ሚስጥር አይገለጥም… ፀጥታ የግዑዙ ዓለም ቁልፍ ነው የሚስጥራት መክፈቻ…
ይህን የተረዱት ጥቁሩና ነጯ ግንኙነታቸው ገና ያልጠበቀ ቢሆንም በፀጥታ ቋንቋ ተግባብተዋል፡፡ ሁለቱም የየራሳቸው ውበት
አላቸው ከቀለማቸው ጀምሮ።
ፏፏቴው ይንፏፏል የሌሊት ወፍ እንደ ንጋት ወፍ
የችሎታዋን እየዘመረች በጨለማው ትበራለች… ሁለቱም በየግላቸው
በፀጥታ የሙከራ መስሪያ ህሊናቸው ውስጥ እንደየአቅማቸው
ይመራመራሉ፡ ይቀንሳሉ ይደምራሉ አንዱ ሌላውን ያስባል፡፡
የጋዝ ምድጃው ላይ በብረት ድስት የጣዱት ፓስታ ክዳኑን
ሽቅብ እየገፋ ሲንፈቀፈቅ ግን ሁለቱም ከዚያ የፀጥታ ዓለማቸው ተመለሱ፡፡
ስዩም ከተቀመጠበት ተነስቶ ባትሪውን አብርቶ የብረት ድስቱን ክዳን ከፈተና ፓስታው መብሰል አለመብሰሉን አረጋገጠ
በስሏል… ለምግብነት ያመጡትን አቀራረቡ የጉደር ወይኑንም ዷ አድርገው ከፈቱ፡፡
"መልካም ራት!” አለችው፡፡
“ለአንችም” አላትና መብላት ጀመሩ
"ተወርዋሪ ኮከብ! ፈነደቀች፡፡
“ለብዙ ጊዜ ተወርዋሪ ኮከብ ስጠበቅ ነበር አሁን ግን አየሁ ዘግይቶም ቢሆን ያሰብሁት ይሳካል፡፡ አውሮፓ ውስጥ እንዲሁ ዓይነት እምነት አለ" አለችው፡፡ ስዩም ፈገግ ብሎ ራሱን ወዘወዘ ለአባባሏ እንግዳ አይመስልም፡፡
በሰባት ሰዓት ተኩል
ከአዲስ አበባ ተነስተው ገነት አዲሳለም ጊንጭ አምቦን እያዩ ጉደር የደረሱት ከምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት ላይ ነው፡፡ አምቦ ኢትዮጵያ ሆቴል ትልቁ ዋርካ ስር
ቁጭ ብለው ማራኪውን አትክልት ቦታ እያዩ ቆዩ፡
"ጥሩ አገር አለቻችሁ፡፡ ከአዲሳባ እዚህ ድረስ ትንፋሽ ቆራጩ ተፈጥሮ በደስታ እንዴት እንዳረካኝ ልገልፅልህ አልችልም”
አለችው።
"ገና ይቀርሻል: ጉደር ስንደርስ የጉደርን ተፈጥሮ ስታይ የማድነቂያ ቃል እንዳታጭ” አላት፡ በፈገግታ ግንባሯን ሰበሰበች፡፡
ከአምቦ አንድ አስር ኪሉ ሜትር እንደተጓዙ ጉደር ከተማ ገቡ፡ በከተማው መሃል አለፉ፡፡ ወደ ግራ ታጥፈው አልባሌ መዝጊያ
ያለው በር ላይ ቆሙ፡፡ ትህትና ያለው ዘበኛ እየሮጠ መጥቶ በሩን ከፈተላቸው፡፡ አናገሩት፡፡
ፏፏቴው ይንፎለፎላል፤ ድምፁን እየሰሙ ቁልቁል ወረዱና ብብቱ ስር ገቡ። ስዩም ካርለትን አያት “ዋው!” ብላ አፏን ከፍታ
አይኖችዋን ወረወረቻቸው አረፋው ላይ ለምለሙ ጫካ ላይ የበልግ እፀዋት ላይ… የመጨረሻዋ ማድነቂያ አባባሏ ሁለት ፊደል ሆነ “ዋው! ብቻ፡፡
ሁለቱም በልተው ጨረሱ
የጉደር ፏፏቴ ይሰማል
ካርለት የጉደርን ወይን በሁለት ብርጭቆ ቀድታ አንዱን ለስዩም ሰጠችው። “ለጤናችን ለኢትዮጰያውያን አዲስ ዓመት" አለችው:
በየመንገዱ ያየችው ቢጫ አበባ ከለምለም ቄጠማ ጋር በየሰዎች እቅፍ ላይ የነበረው አበባ፤ የኢትዮጵያ የአዲስ ዘመን አብሳሪ አደይ
አበባ እንደ ህፃንነቷ ከአረንጓዴው ለምለም መስክ እየቀነጠሰች
ችቦዋን ሞልታ መዓዛውን ባፍንጫዋ የሳበችው የአደይ አበባ ሽታ
መጣባት፡
ፏፏቴው ከብቶቹ ህፃናት… ቃናቸው ተዋህዶ “አደይ
አደይ አበባ…" እያሉ ያዜማሉ፡፡ ስዩም “ችቦው ተለኮሰ' አላት፡፡
“የምኑ” አለችው፡፡
“የአዲሱ ዓመት የአዲስ
ዘመን... የነገ ፈገግ አሉ
አንጋጠው ተጎነጩት ጉደሩን፡፡ ፀጥ አሉ እንደገና አዲሱን ነገ ህልሙን ነገ፤ ሽፍንፍኑን መጭ አመት እያዩ፡፡ ከዚያ ካርለት
ለመናገር ስትቁነጠነጥ አያት፡፡
“አመሰግናለሁ፡ በዚህ የደስታ ቀንህ አብሬህ እንድሆን ስለመረጥኸኝ" አለቸው:
“ምስጋና አያስፈልገኝም: ሌላ አብሮኝ ሊመጣ የሚችል ባለመኖሩ ነው" አላት፡፡
“ለምን?” አለችው ካርለት፡፡
“በአዲስ ዓመት ዋዜማ የአዲሳባን ሰው ወደ ገጠር ወጣ እንበል ብትይው ፀበል ይወስድሽና በመስቀል እያስደበደበ ሰባት ቀን
ቤት ያዘጋብሻል እብድ ነሽ ብሎ" አላት: በቀልድ አዘል አባባሉ ፈገግ አለችለት፡ ከጥርሷ ይልቅ ቀይ ከንፈሯን በከዋክብት የብርሃን ወጋገን አየው፡
ካርለት፧ እንግዳ ባህሪው
የሚገርማት ኢትዮጵያዊ
ዮትያትሪካል አርት ምሩቅ መሆኑን እንጂ የግል ህይወቱን አልዘረዘረላትም፡፡ የሴት ጓደኛ አለኝ ብሏት የነበረውም ትዝ አላት።
የሴት ጓደኛህስ ፍላጎትህን አትወድልህም?"
“እሷማ ሁሌም አብራኝ ነች፡፡ በውኔ ቀርቶ በህልሜም"
“አልገባኝም?" አለች ካርለት፡፡
"በገሃድ የሚሆነኝን አላገኘሁም !በምናቤ ግን
ፍቅርኛ አለችኝ
“ለምን?''
"የፈጠራ ሰዎች ግላዊ እምነታቸውን በተከተሉ ቁጥር ከህብረተሰቡ ጋር የነበራቸው የመግባባት ቅኝት እንደተበላሽ የሚገምተው ይበዛል። እነሱም የብቸኝነት ጥዑም ዜማው ያረካቸዋል፡፡ ስለዚv
ሌለች የሚወዱት ሙዚቃ ለእነሱ ጩኸት ይሆንባቸዋል፡፡
በምናቤ ግን ፍቅረኛ
“ቁም ነገሩ ግን ግላዊ ዓለማቸውም ውስጥ ሆነው
የህብረተሰቡን ህይወትና ቅላፄ ምንነት ለመረዳት ህሊናቸውን ወደ
ዱ ዓለም እየዶሉ እርቀው ይቀርባሉ፤ ከህዝቡ ጋር ይሆናሱ፤
👍21👎1😁1
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ከሉ ሆራ ጎይቲ አንተነህን ሐመር ካደረሳት በኋላ አስር ቀን በማይሞላ ጊዜ ተመልሶ እንደሚመጣና እሱ አዲሳባ ለተወሰኑ ቀናት
ሲቆይ ካርለት ደግሞ ወደ ሐመር ለመሄድ እቅድ ነበራቸው፡፡ ከሎ ሆራ ግን የውሃ ሽታ ሆነባት፡፡
“ምን ነካው?” እያለች ብዙ አሰበች ካርለት: ደህንነታቸውንና
ያጋጠመውን ችግር ግን ማወቂያ አንዳችም የመገናኛ እድል
አልነበራትም፡ ስልክ ደብዳቤ ፋክስ ኢሜል.. አንዳቸውንም የሉም: ሐመር ውስጥ መገናኛ ዘዴው “ላልሰማው አሰማ" የሚለው ዘዴ ነው:: መንገደኛ ሲገናኝ በርኮቶው ላይ ቁጭ ይልና ሰዉ ከብቱ
ቀየው. ሰላም መሆኑን በጥሞና ይነጋገራል: አዲስ ነገር ደስታ ችግር ግጭት ካለ ያየው ላላየው ይነግራል፡፡ ወይንም የሰማው ከሆነ ሰማሁ ብሎ ያወራል፡፡
አስቸኳይና ጊዜ የማይሰጥ
ማህበረሰቡን የሚጎዳ ችግር ካለ ግን ሁለት እጃቸውን ያቆላልፉና ከትንፋሻቸው የሚወጣውን
አየር የእጅ ጣታቸውን ከፈት ከደን በማድረግ ድምፅ ይፈጥራሉ፡፡ የሰማው ላልሰማው በተመሳሳይ መልኩ እየነፋ ያስተላልፋል፡፡ ያን
ጊዜ ዋናው መንገድ ላይ የሚሄድ ሐመር ሁሉ ጫካ ጫካውን አድፍጦ እየተጓዘ ባለ ጠበንጃው ጠበንጃውን ባለ ጦሩ ጦሩን… ሁሉም ያለውን እየያዘ እየተሰበሰበ መንደሩን የሚጠብቁ እነ እከሌ እከሌ ከብቶች ዘንድ እነ እከሌ እነ እከሌ እየተባለ አሳሾች,ሸማቂዎች
ሰላዮች ይመደቡና የመጣባቸውን ችግር በጋራ
ይጋፈጣሉ፡፡ ሰላም ሲሆንም አንዱ ለሌላው እያሰማ ወደ እለት የኑሮውን ይመለሳል፡፡ በሐመር ይኸ ነው ለዘመናት የቆየው መገናኛ:
“ምናልባት መኪናዋ ተበላሽታ ይሆን? ወይንስ መንገዱ ተበላሽቶ ድልድይ ተሰብሮ…" እያለችም አሰበች ካርለት መልስ ግን
አጣች! መላ ምት ብቻ:: ስለዚ አዲሳባ ተቀምጣ ከምትጨነቅ መሄዱን መረጠች፡፡
በምን እንደምትሄድ ግን ጨነቃት። በትራንስፖርት መኪና መሄዱን አሰበች እንዲያውም እስካሁን በትራንስፖርት መኪና
ከተማ ውስጥ ካልሆነ በስተቀር ሄዳ አታውቅም፡ ችግሩ ግን ጓዟ
ብዙ ነው፡
እዚሆ ሆኜ በሃሳብ ከመጨነቅ መሄዱ ይሻለኛል ካለስራ አዲሳባ መቀመጡ ደግሞ ራሱን የቻለ ትልቅ ችግር ነው' ብላ
አሰበች: ለጊዜው የሚያስፈልጋትን ብቻ ይዛ ሌላውን ሌላ ጊዜ ከሎ
እንዲወስድላት ብታደርግ እንደሚሻላት አመነች፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።፡።
ካርለት ታክሲ ተኮናትራ መርካቶ የክፍለሃገር አውቶብስ መናኸሪያ ስትደርስ የሚተራመሰው ሰው ለጉድ ነው: ሆንኮንግና
ህንድ አገር ግን እንዲያ ያለውን ትርምስ ስለለመደችው አልተገረመችም፡፡ ባለታክሲው ደንበኛዋ ነው፡ ታክሲዋን ወደ ዜድ ሙዚቃ ቤት አቅራቢያ አቆሞ ጓዟን ተከፋፍለው መንገዱ አቆራርጠው ከሚተራመሰው ህዝብ መካከልም አልፈው በሰፊው በር በኩል ወደ መናኸሪያው ገቡ፡
“ድሬዳዋ ደሴ ለቀምት በካቻማሊ በዋሊያ" እያሉ
ሰውን የሚጎትቱት እሷንም ጎነታተሏት! ያስፈራሉ። ስነ ስርዓቱ ቅጥ የለውም
ለዝርፊያና ቅሚያ አመች ነው: አለንጋ የያዙት ዘበኞች
ስርዓቱን ለማስጠበቅ ከአቅም በላይ ሆኖባቸዋል፡፡ መንደኛው ግን እራሱን ይጠብቃል። ካርለት ሻንጣዋን በትከሻዋ አንጠልጥላ በሁለት
እጅዋ ከፊት ለፊቷ አጥብቃ ይዛ ገባች፡፡ ታክሲ ነጂው
የሚያዣብቡትን ይክላከላል፡፡ እንደ ሽንት ቤት ዝንብ ግር ብለው
ይመጡና እሱን ሲያዩ ገለል ይሉላታል
“አርባምንጭ አንደኛ አርባምንጭ
ሁለተኛ ከሚለው
አውቶበስ ዘንድ ደረሰ! ለመስቀል የሚጓዘው መንገደኛ ከአውቶብሉ
በስተኋላ አቧል። “ትኬት ይኖራል?” ታክሲ ሾፌሩ ካርኒ ቆራጮችን
በየተራ ጠየቃቸው: “አልቋል ባክህ ገለል ገለል በሉ ካለበለዚያእቃችሁ አይገመትም• አይጫንም፤ ስለዚህ ማርፈዳችሁን እወቁ…" አለ እንደኛው ካርኒ ቆራጭ በስጨት ብሎ። አንድ ብልጣ ብልጥ
ለእራሱ እየተጠጋ “እስኪ እሽ በሉ ማርፈዱ የሚጎዳን እኛን ነው…"አለ፡፡ መስማማት የለም። ሁሉም እቃውን ጭኖ ፊት አካባቢ
ተቀምጦ ለመጓዝ ጓጉቷል፡፡ ደሞ መስቀል ነው። የዓመቱ መገናኛ ዓውዳመት! ካርኒ ቆራጩ አኩሩፎ “ያውላችሁ" ብሎ ወጣና ተደናግጣ ከቆመችው ካርለት ጎን ቆመ:: አየችው አያት! ታለትንሽ ጊዜ ተያዩ፡፡
ካኪ ካፖርት ሁለት ጥራዝ ካርኒ ጭንቅላቱ ላይ ደግሞ
ፎጣ ጠምጥሟል፡ ፊቱ ምጥጥ ያለ ጠይም መልከ መልካም ግን ነገረኛ መሳይ ነው። ሲያናግሩት አይናገርም:: ከመሰላቸት ወይም ከኩራት ይሁን እግዜር ይወቀው
"አርባምንጭ ዘላቂ ምንም ትኬት የለም ለሷ ነበር”
አለው ታክሲ ሾፌሩ ጠጋ ብሎ። አላናገረውም! ካርለትን ግን እንደገና አያትና፦
ነገርኩህ አይደለም የኔ ወንድም አልቋል" አለና የሚያስብ መሰለ: እስኪ አንዴ የት ነው እባካችሁ ሁለት ትኬት ገዝቶ አንድ
ወንበር ላይ መቀመጥ እፈልጋለሁ ያለ ሰው ነበር”
“የታል?" አለ ታክሲ ሾፌሩ: ካርለት! ነገሩን ለማጣራት
ፈለገች በእንግሊዘኛ የሚገልፅላት ግን ጠፋ።
ዩ ዌት" አላት ታክሲ ሾፌሩ ለከት ባጣ እንግሊዘኛ::
“ቆይ ግዴለም እኔ አናግረዋለሁ ብሎ እቃውን እየገመተ መጫን ተጀመረ ከዚያም የአትወብሱ
በር ሲከፈት ግፊያው
ያስፈራል፡፡ ሽማግሌዎች, ህፃን የያዙ ሴቶች….. እየተወረወሩ በግፊያው እየተሽቀነጠሩ ጉልበት ያለው እየበረቃቀሰ ገባ ካርለት ገረማት፡፡
“ሁሌም እንዲህ ይሆን ወይንስ ዛሬ ብቻ? ነፍስ እስኪጠፋ ነው የሚጠበቀው? ምናለ በወንበር ቁጥር ወይንም በሌላ ዘዴ የማንም መብት ሳይነካ መንገደኛው ቢስተናገድ' ብላ አዘነች፡፡
“እስኪ ነይ እቃሽ እላይ ይውጣ ጫንላት” አለ ካርኒ
ቆራጩ በምልክት። ካርለት ተከትላው አውቶቡስ ውስጥ ገባች፡፡መንገደኛው ገና ተረጋግቶ አልተቀመጠም። ሲገባ ከነበረው ትርምስ
ግን ይሻላል፡፡
“የኔ ወንድም አንተ ነህ አይደለም ሁለት ትኬት
የያዝኸው?"
“አዎን! እኔ ነኝ። አንዱ ጎን ካልተቀመጥሁ' ብሎ ለምን
አያፈጥብኝ: እኔ ደልቶኝ መሰለው ሁለት ትኬት መግዛቴ፡ ሰላም ፈልጌ ነው መሳቀቅ ጠልቼ ነው. አሁን ግን ሰላም ነው አስበህ
ልትጠይቀኝ በመምጣትህ አመሰግናለሁ። ለዚህ አይደል እኔስ ቀደም
ብዬ አደራ ማለቴ አለው ፂሙን በቀኝ እጁ ቁልቁል እሞዠቀ፡፡
የለም አመጣጤ ለሌላ ነው። ይህች የሰው አገር ሰው ናት… እባክህ ተባበራት ብዙም አታስቸግርህም። ገንዘቡን ተቀብያት እሰጥሃለሁ።”
ኖ የለም እኔ አፓርታይድ አይደለሁ ጥቁር ነጭ የምል!መሳቀቅ መጨነቅ ስለማልፈልግ ብቻ ነው። ይህንን ደግሞ አስረድቻችሁ ተስማምተናል በጭራሽ አጠገቤ ሰው አይቀመጥም፡"
“…እባክህ ተባበራት መስሪያ ቤታችን እኮ ይህን ጉዞ ሲያዘጋጅ ገንዘብ ማግኘት ብቻ ሳይሆን ህዝቡንም ለመርዳት ነው"
አለው።
“ይኸ እኮ ነው የጠላሁት። ሰላም ለማግኘት ብዬ ገንዘቤን አውጥቼ ያላሰብሁት አተካራ ገዛሁበት: ጭቅጭቅ አልፈልግም እሽ!
ገንዘቤን! ያው ቦታዋ” አለ: ካርለት ሰላሣ ሁለት ብር ከአስር ሣንቲም ከፈለችው: ለታክሲ ሾፌሩም ኪራዩን ከጉርሻ ጋር ስትሰጠው በደስታ ፊቱ በርቶ ተሰናብቷት ሄደ፡
አጠገቧ የተቀመጠው ሰው አንድ አነስ ያለች ጀሪካን አንድ በመጠኑ ከትንሽዋ ጀሪካን ከፍ ያለ እንደ ህጻን በእቅፉ ይዟል። ሰፊ
ኮት የወታደር ቦት ጫማ ተጫምቷል! ፀጉሩ ዞማ ነው አበጣጠሩ ግን ለከት የለውም! ፊቱ ከፊሉ በፂሙ ተሸፍኗል! ከንፈሩ
አይታይም…
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ከሉ ሆራ ጎይቲ አንተነህን ሐመር ካደረሳት በኋላ አስር ቀን በማይሞላ ጊዜ ተመልሶ እንደሚመጣና እሱ አዲሳባ ለተወሰኑ ቀናት
ሲቆይ ካርለት ደግሞ ወደ ሐመር ለመሄድ እቅድ ነበራቸው፡፡ ከሎ ሆራ ግን የውሃ ሽታ ሆነባት፡፡
“ምን ነካው?” እያለች ብዙ አሰበች ካርለት: ደህንነታቸውንና
ያጋጠመውን ችግር ግን ማወቂያ አንዳችም የመገናኛ እድል
አልነበራትም፡ ስልክ ደብዳቤ ፋክስ ኢሜል.. አንዳቸውንም የሉም: ሐመር ውስጥ መገናኛ ዘዴው “ላልሰማው አሰማ" የሚለው ዘዴ ነው:: መንገደኛ ሲገናኝ በርኮቶው ላይ ቁጭ ይልና ሰዉ ከብቱ
ቀየው. ሰላም መሆኑን በጥሞና ይነጋገራል: አዲስ ነገር ደስታ ችግር ግጭት ካለ ያየው ላላየው ይነግራል፡፡ ወይንም የሰማው ከሆነ ሰማሁ ብሎ ያወራል፡፡
አስቸኳይና ጊዜ የማይሰጥ
ማህበረሰቡን የሚጎዳ ችግር ካለ ግን ሁለት እጃቸውን ያቆላልፉና ከትንፋሻቸው የሚወጣውን
አየር የእጅ ጣታቸውን ከፈት ከደን በማድረግ ድምፅ ይፈጥራሉ፡፡ የሰማው ላልሰማው በተመሳሳይ መልኩ እየነፋ ያስተላልፋል፡፡ ያን
ጊዜ ዋናው መንገድ ላይ የሚሄድ ሐመር ሁሉ ጫካ ጫካውን አድፍጦ እየተጓዘ ባለ ጠበንጃው ጠበንጃውን ባለ ጦሩ ጦሩን… ሁሉም ያለውን እየያዘ እየተሰበሰበ መንደሩን የሚጠብቁ እነ እከሌ እከሌ ከብቶች ዘንድ እነ እከሌ እነ እከሌ እየተባለ አሳሾች,ሸማቂዎች
ሰላዮች ይመደቡና የመጣባቸውን ችግር በጋራ
ይጋፈጣሉ፡፡ ሰላም ሲሆንም አንዱ ለሌላው እያሰማ ወደ እለት የኑሮውን ይመለሳል፡፡ በሐመር ይኸ ነው ለዘመናት የቆየው መገናኛ:
“ምናልባት መኪናዋ ተበላሽታ ይሆን? ወይንስ መንገዱ ተበላሽቶ ድልድይ ተሰብሮ…" እያለችም አሰበች ካርለት መልስ ግን
አጣች! መላ ምት ብቻ:: ስለዚ አዲሳባ ተቀምጣ ከምትጨነቅ መሄዱን መረጠች፡፡
በምን እንደምትሄድ ግን ጨነቃት። በትራንስፖርት መኪና መሄዱን አሰበች እንዲያውም እስካሁን በትራንስፖርት መኪና
ከተማ ውስጥ ካልሆነ በስተቀር ሄዳ አታውቅም፡ ችግሩ ግን ጓዟ
ብዙ ነው፡
እዚሆ ሆኜ በሃሳብ ከመጨነቅ መሄዱ ይሻለኛል ካለስራ አዲሳባ መቀመጡ ደግሞ ራሱን የቻለ ትልቅ ችግር ነው' ብላ
አሰበች: ለጊዜው የሚያስፈልጋትን ብቻ ይዛ ሌላውን ሌላ ጊዜ ከሎ
እንዲወስድላት ብታደርግ እንደሚሻላት አመነች፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።፡።
ካርለት ታክሲ ተኮናትራ መርካቶ የክፍለሃገር አውቶብስ መናኸሪያ ስትደርስ የሚተራመሰው ሰው ለጉድ ነው: ሆንኮንግና
ህንድ አገር ግን እንዲያ ያለውን ትርምስ ስለለመደችው አልተገረመችም፡፡ ባለታክሲው ደንበኛዋ ነው፡ ታክሲዋን ወደ ዜድ ሙዚቃ ቤት አቅራቢያ አቆሞ ጓዟን ተከፋፍለው መንገዱ አቆራርጠው ከሚተራመሰው ህዝብ መካከልም አልፈው በሰፊው በር በኩል ወደ መናኸሪያው ገቡ፡
“ድሬዳዋ ደሴ ለቀምት በካቻማሊ በዋሊያ" እያሉ
ሰውን የሚጎትቱት እሷንም ጎነታተሏት! ያስፈራሉ። ስነ ስርዓቱ ቅጥ የለውም
ለዝርፊያና ቅሚያ አመች ነው: አለንጋ የያዙት ዘበኞች
ስርዓቱን ለማስጠበቅ ከአቅም በላይ ሆኖባቸዋል፡፡ መንደኛው ግን እራሱን ይጠብቃል። ካርለት ሻንጣዋን በትከሻዋ አንጠልጥላ በሁለት
እጅዋ ከፊት ለፊቷ አጥብቃ ይዛ ገባች፡፡ ታክሲ ነጂው
የሚያዣብቡትን ይክላከላል፡፡ እንደ ሽንት ቤት ዝንብ ግር ብለው
ይመጡና እሱን ሲያዩ ገለል ይሉላታል
“አርባምንጭ አንደኛ አርባምንጭ
ሁለተኛ ከሚለው
አውቶበስ ዘንድ ደረሰ! ለመስቀል የሚጓዘው መንገደኛ ከአውቶብሉ
በስተኋላ አቧል። “ትኬት ይኖራል?” ታክሲ ሾፌሩ ካርኒ ቆራጮችን
በየተራ ጠየቃቸው: “አልቋል ባክህ ገለል ገለል በሉ ካለበለዚያእቃችሁ አይገመትም• አይጫንም፤ ስለዚህ ማርፈዳችሁን እወቁ…" አለ እንደኛው ካርኒ ቆራጭ በስጨት ብሎ። አንድ ብልጣ ብልጥ
ለእራሱ እየተጠጋ “እስኪ እሽ በሉ ማርፈዱ የሚጎዳን እኛን ነው…"አለ፡፡ መስማማት የለም። ሁሉም እቃውን ጭኖ ፊት አካባቢ
ተቀምጦ ለመጓዝ ጓጉቷል፡፡ ደሞ መስቀል ነው። የዓመቱ መገናኛ ዓውዳመት! ካርኒ ቆራጩ አኩሩፎ “ያውላችሁ" ብሎ ወጣና ተደናግጣ ከቆመችው ካርለት ጎን ቆመ:: አየችው አያት! ታለትንሽ ጊዜ ተያዩ፡፡
ካኪ ካፖርት ሁለት ጥራዝ ካርኒ ጭንቅላቱ ላይ ደግሞ
ፎጣ ጠምጥሟል፡ ፊቱ ምጥጥ ያለ ጠይም መልከ መልካም ግን ነገረኛ መሳይ ነው። ሲያናግሩት አይናገርም:: ከመሰላቸት ወይም ከኩራት ይሁን እግዜር ይወቀው
"አርባምንጭ ዘላቂ ምንም ትኬት የለም ለሷ ነበር”
አለው ታክሲ ሾፌሩ ጠጋ ብሎ። አላናገረውም! ካርለትን ግን እንደገና አያትና፦
ነገርኩህ አይደለም የኔ ወንድም አልቋል" አለና የሚያስብ መሰለ: እስኪ አንዴ የት ነው እባካችሁ ሁለት ትኬት ገዝቶ አንድ
ወንበር ላይ መቀመጥ እፈልጋለሁ ያለ ሰው ነበር”
“የታል?" አለ ታክሲ ሾፌሩ: ካርለት! ነገሩን ለማጣራት
ፈለገች በእንግሊዘኛ የሚገልፅላት ግን ጠፋ።
ዩ ዌት" አላት ታክሲ ሾፌሩ ለከት ባጣ እንግሊዘኛ::
“ቆይ ግዴለም እኔ አናግረዋለሁ ብሎ እቃውን እየገመተ መጫን ተጀመረ ከዚያም የአትወብሱ
በር ሲከፈት ግፊያው
ያስፈራል፡፡ ሽማግሌዎች, ህፃን የያዙ ሴቶች….. እየተወረወሩ በግፊያው እየተሽቀነጠሩ ጉልበት ያለው እየበረቃቀሰ ገባ ካርለት ገረማት፡፡
“ሁሌም እንዲህ ይሆን ወይንስ ዛሬ ብቻ? ነፍስ እስኪጠፋ ነው የሚጠበቀው? ምናለ በወንበር ቁጥር ወይንም በሌላ ዘዴ የማንም መብት ሳይነካ መንገደኛው ቢስተናገድ' ብላ አዘነች፡፡
“እስኪ ነይ እቃሽ እላይ ይውጣ ጫንላት” አለ ካርኒ
ቆራጩ በምልክት። ካርለት ተከትላው አውቶቡስ ውስጥ ገባች፡፡መንገደኛው ገና ተረጋግቶ አልተቀመጠም። ሲገባ ከነበረው ትርምስ
ግን ይሻላል፡፡
“የኔ ወንድም አንተ ነህ አይደለም ሁለት ትኬት
የያዝኸው?"
“አዎን! እኔ ነኝ። አንዱ ጎን ካልተቀመጥሁ' ብሎ ለምን
አያፈጥብኝ: እኔ ደልቶኝ መሰለው ሁለት ትኬት መግዛቴ፡ ሰላም ፈልጌ ነው መሳቀቅ ጠልቼ ነው. አሁን ግን ሰላም ነው አስበህ
ልትጠይቀኝ በመምጣትህ አመሰግናለሁ። ለዚህ አይደል እኔስ ቀደም
ብዬ አደራ ማለቴ አለው ፂሙን በቀኝ እጁ ቁልቁል እሞዠቀ፡፡
የለም አመጣጤ ለሌላ ነው። ይህች የሰው አገር ሰው ናት… እባክህ ተባበራት ብዙም አታስቸግርህም። ገንዘቡን ተቀብያት እሰጥሃለሁ።”
ኖ የለም እኔ አፓርታይድ አይደለሁ ጥቁር ነጭ የምል!መሳቀቅ መጨነቅ ስለማልፈልግ ብቻ ነው። ይህንን ደግሞ አስረድቻችሁ ተስማምተናል በጭራሽ አጠገቤ ሰው አይቀመጥም፡"
“…እባክህ ተባበራት መስሪያ ቤታችን እኮ ይህን ጉዞ ሲያዘጋጅ ገንዘብ ማግኘት ብቻ ሳይሆን ህዝቡንም ለመርዳት ነው"
አለው።
“ይኸ እኮ ነው የጠላሁት። ሰላም ለማግኘት ብዬ ገንዘቤን አውጥቼ ያላሰብሁት አተካራ ገዛሁበት: ጭቅጭቅ አልፈልግም እሽ!
ገንዘቤን! ያው ቦታዋ” አለ: ካርለት ሰላሣ ሁለት ብር ከአስር ሣንቲም ከፈለችው: ለታክሲ ሾፌሩም ኪራዩን ከጉርሻ ጋር ስትሰጠው በደስታ ፊቱ በርቶ ተሰናብቷት ሄደ፡
አጠገቧ የተቀመጠው ሰው አንድ አነስ ያለች ጀሪካን አንድ በመጠኑ ከትንሽዋ ጀሪካን ከፍ ያለ እንደ ህጻን በእቅፉ ይዟል። ሰፊ
ኮት የወታደር ቦት ጫማ ተጫምቷል! ፀጉሩ ዞማ ነው አበጣጠሩ ግን ለከት የለውም! ፊቱ ከፊሉ በፂሙ ተሸፍኗል! ከንፈሩ
አይታይም…
👍16❤2🔥1
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
“እኔ ሰላም ፈላጊ ነኝ፡ በሰላም አብረው እንዲኖሩ ከብርሃን ወደ ጨጎጎታሙ ጨጓራዬ ውስጥ አስገብቻቸው እነሱ ተባብረው እኔን አንደማጥቃት እርስ በርሳቸው ካልተስማሙና ከተጣሉ የከፋው ተበደልሁ ባይ በሁለት መንገድ (በጁ ምልክት እያሳያት
ወይም በላይ ወይ በታች መውጣት ይችላል። እኔ ደድግሞ በጠየቁኝ
አቅጣጫ በሬን እከፍታለሁ" ብሎ ፈገገ፤ ካርለት ግን ሳቋን መቆጣጠርን ተሳናት፡ ወርቃማ ፀጉሯ እስኪርገፈገፍ ተሳፋሪው ሁሉ እየዞረ እስኪያያት… ሳቀች እሱ ግን ፀጥ አለ፤ እንቅልፍ እንቅልፍ አለው ተኛ! ካርለት ትከሻ ላይ፤ ወርቃማ ፀጉሯ እንደ በቆሉ ጭራ ፊቱን ሲነካካው የናቱን ጡት እንደሚጠባ ህፃን ፍርክስክስ ብሎ ተኛ
“ኩርር… ኩርርር. እያደረገ፡፡
ዝዋይ ላይ አውቶቡስ ለቁርስ ሲቆም ነቃ። ከጠዋቱ አራት ሰዓት ተኩል ነው: ሰዉ ሁሉ ወረደ: ካርለት ካለፂማሙ ሰው
የምታውቀው የለም:: ስለዚሀ አብረው ወረዱ፡፡
የኢትዮጵያውያን ምግብ ለሷ አዲስ አይደለም። ግን
ለተወሰኑ ወራት እርቃው ቆይታለች፡፡
እሱ ጥሬ ክትፎ እሷ ዳቦና ሻይ አዘው ሲበሉ ቆዩና፡-
“ስለ ከቡ ነገርኩሽ" አለ ፂሞ:
“ማነች ከቡ?"
“ሚስቴi ለጋብቻ ስጠይቃት ፂማም ነህ' ብላ ናቀችኝ፡ ዝም ብዬ ጥረቴን ቀጠልሁ፡፡ ፂሙ አያስጠላሽም፤ምኑን ልትስሚው ነው' ብለው ሲያጥላሉባትም እኔ ጥረቴን እንደቀጠልሁ ነበር፡ አንድ
ቀን ታድያ ተሳካልኝ ለትዳር እንደምፈልጋት የተማርሁ መሆኔን ላዬ ሞኛ ሞኝ ቢሆንም ውስጤ ግን ዘመናዊ እንደሆነ በአለማችን ካሉ በጣት ከሚቆጠሩ ደስተኞች መካከል አንዱ መሆኔን…
እየዘረዘርሁ ሳጫውታት ቆየሁ፡፡ ምኗ ሞኝ መሰለችሽ! ቆቅ ነች:
ከምታየውና ከሰማችው ጋር እኔ ያልኋት ሁሉ ተምታታባት ከቡ!
“ሰርቲፍኬቴን ስቀበል የተነሳሁትን ፎቶ ሳሳያት ግን ውሃ ሆነች፡ ፍንጥር ፍንጥር ማለቷን ቀነሰች፡ ያኔ ጠልፎ እሚጥላትን ምላሴን እያወናጨፍሁ እግሯን አንስቼ እግሬ ላይ አደረግሁና የርግብ
አሳሳም ስሚያት ወጥቼ ስሄድ የጨው መላሾ እንደቀመሰ ከብት
እየተከተለችኝ ለምን አትመጣም መሰለሽ!" ብሎ ሳቁን ለቀቀው፡፡
ካርለት ስለ አንድ ነገር መናገር በጀመረ ቁጥር መጨረሻው አስቂኝ
መሆኑን መጠበቅ ጀምራ ስለነበር እሷም አብራው
ሳቀችና የሆነ ነገር
በህሊናዋ ትዝ አላት እንግዳ አባባል፡
“ምንድነው የርግብ አሳሳም''
“አታውቂም? ብዙው ኧረ በጠቅላላው ሰው የሚያውቅ አይመስለኝም" አላትና ቀና አለ፡፡ “እኔ ግን የተማርሁት ከርግቦች
ነው፡፡ ቆርቆሮዬ ላይ ሲ
ሲዳሩ አይቼ፡፡
“ታያለሽ ከንፈሬ አካባቢ ያለውን ፂሜን ለመሳም ከፈለግሁ ከሴቷ አፍ ውስጥ ገብቶ ጉሮሮዋን ያንቃታል፡፡ እኔ ደግሞ ችግር
መፍጠር አልወድም፤ ለምን ብዬ! ሰው ሁሉ የሌላው ሳይጨመር የራሱ ችግር መቼ አነሰው… ስለዚህ እኔ እንደ እርግብ አፌን
ስከፍትላት ክቡ ከንፈሯን ውስጥ ትጨምረዋለች ያኔ እጠባታለሁ ከንፈሯን: ያ ነው የእርግብ አሳሳም! ያ የርግብ አሳሳም ነው ነው
ከቡዬን እንደ ከብት እያንደረደረ እቤቴ ያስገባት፡፡ ፂሜ ችግር
ስለማይፈጥርባት ቅቤ እየቀባች ሽሩባ ትሰራኝ ጀመር፡፡ ከዚያ እንዲያውም ልቧ እየራራ እንደ ሰናፍጭ የሚሰነፍጥ ፍቅሯን
እየመገበች ይኸው ያየኝን ሁሉ አጠገብህ ካልተቀመጥን' እያስኘ
የሚያስጎመጅ ሰው ወጣኝ" አላትና ሳቀ ተሳሳቁ…..
አውቶብሱ እንደገና ጉዙውን ሲቀጥል ፂሞ ከያይነቱ
ጎንጨት አድርጎ ተኛ: ካርለት እንግዳ ባህሪው ገርሟታል። አጠገቡ
መቀመጧን እንዳልጠላችው አሁን ግን ከነበረው ሰው
ልትግባባው የምትችለው ከሱ የተሻለ እንዳልነበር ተሰማት።
አውቶብሱ የላንጋኖንና የሻላን ደን እያቆራረጠ ሲጓዝ ሙቀቱ እየጨመረ የዳቦ መጋገሪያ ፍም ላይ የተቀመጡ ያህል
ያተኩስ ጀመር። የአውቶብሱ መስኮትና በር ባጠቃላይ ክርችም ብሎ
ተዘግቶ ህዝቡ በላብ ሻወር ይታጠባል፡ መስኮቱን ለምን
እንደማይከፍቱት ፂሞን ጠይቃው የአውቶብስ መስኮት አትክፈቱ•
ብርድ ይመታችኋል ያለው ዶክተር ባይታወቅም ልጅ አዋቂውን ቃሉን አክብሮ በሙቀት መቀቀል መምረጡን ነግሯታል፡ ስለዚህ የለበሰችውን ጃኬት አውልቃ በነጭ ቲሸርት ሆና የሙቀት ቅጣቷን
እየተቀበለች ለማረፍ ከፊት ለፊቷ ካለው ወንበር የብረት ዘንግ ላይ ራሷን ደገፍ አደረገች፡፡
ሙዚቃው ማንቧረቁ አልቆመም፡፡ አውቶብሱ ማርሹን እየቀያየረ ይጓዛል፡ ካርለት እንደ ቀልድ እንቅልፍ ወስዷት ቆይታ የአውቶብሱ ሹፌር አህያ ድንገት ልትገባበት ስትል ፍሬኑን ያዝ
ሲያደርግ ከወንበሩ ጋር ተጋጨችና ብንን ብላ ደንግጣ ተነሳች፡፡
ፂሞ ያነባል። ብጥስጥስ ያለች መጽሐፉን፡ ትንሽ ቆይቶ ከትልቁ ኪሱ ወረቀቶች ያወጣና ያነብ ጀመር፡ ካርለት
ተደንቃ አየችው፡፡ ልታምን አልቻለችም፡፡ ማንም ሰው ያደርገዋል ብላም አትገምትም፡:
የምን ወረቀቶች ናቸው?”
“ወረቀቶቹ አያቸው ግንባሩን ሽቅብ ሰብሰብ አድርጎ፡፡
"ቁም ነገር ያላቸው ወረቀቶች ናቸው፡፡"
ላያቸው እኮ ቆሻሻ አለባቸው?”
“አዎ አይነምድር አው፡ ግን ደርቋል፡፡ ሳነሳው እንኳን ብዙም አልደረቀም ነበር፡ ይኸ ጃኬት ግን ለእኔ ብቻ ሳይሆን ለመሃረቤና
ስለሚፈጥር እዚያው ደረቀ፡፡
ለወረቀቶችም ሙቀት
እስክርቢቶ አይበረክትልኝም ሙቀቱ ያገነፍለዋል፡፡"
“ወረቀቶቹን ከየት ነው ያገኘሃቸው?''።
“በየሄድሁበት መፀዳዳትም ባልፈልግ ሽንት ቤት መሄድ
አዘወትራለሁ የተፃፈውን ማንበብ ሱስ ሆኖብኛል፡ አሁን አሁን ደግሞ አንዳንድ ሽንት ቤቶች ውስጥ ያሉ ቅርጫቶች ላይ ሰው
ተፀዳድቶባቸው እማገኛቸው ወረቀቶች ሽንት ቤቶች ከመፀዳጃነት
አልፈው ወደ መፃህፍት ቤትነት እየተቀየሩ ነው
የሚያሰኝ ነው፡፡
“በአማርኛ ሆነ እንጂ ይህን ብታነቢው የወደቅሽበትን
ሳታውቂው ሶስት ቀን ተኝተሽ ትከርሚ ነበር" አላት፡፡
“ቆሻሻ ወረቀቱን አትጠየፍም?"
“እጠየፋለሁ እንጂ! ግን ጠቃሚ ነገር ኣለበት፡፡ ጠቃሚ ነገር ደግሞ ቆሻሻ አለው ተብለቀ አይጣልም፡፡ ቆሻሻ ማለት ጥቅም
የማይሰጥ ተራ ነገር ነው፡፡
“ይገርምሻል ካለ እነዚህ'' ጀሪካኖቹን ጠቁሞ አሳያት
“...ካለ እነዚህና ካለ ከቡ የረባም ጓደኛ የለኝ፡፡ ምናልባት እኔ ወይ እነሱ ቆሻሻ ስለሆን ይሆናል ከብዙው የሥራ ጓደኞቼ ጋር
የማልግባባው ታዲያልሽ…" የትንሽዋን ጀሪካን ክዳን ከፍቶ ወደ መስታዋቱ ዞሮ አንደቀደቀና
“…ታዲያልሽ ከሽንት ቤት ቅርጫት ቆሻሻ ወረቀት አንስተህ እንዴት እኪስህ ትከታለህ ያሳዝናል! ይህን የሚፈጽም ህሊናው
የተስተካከለ ሰው የለም ካለ እብድ በቀር' ብለው አጥላሉኝ፡፡
“አንድ ቀን ታድያ ሁለት ቀያይ ብሮችን ይዥ ሽንት ቤት ገባሁና በብሩ ተፀዳጅቼ ወጣሁ፡፡ ከኔ የሚቀጥለው አላየኝም ገባ ብሎ ሲወጣ ተመልሼ ብገባ የተፀዳዳሁባቸውን የብር ኖቶች ወስዷቸዋል
ደሞ ሌላ ቦታ ሄጄ በሁለት አምስት አምስት ብሮች ተፀዳዳሁ ... ቀጥሎ የገባው ሲወጣ ብሮቹ የሉም፡፡ hዚያ ደግሞ በአንድ አንድ ብር ሞከርኩ፤ እነሱም ተወሰዱ ታዲያልሽ!ብሮቹ ከእለት ጥቅም
ሌላ ጠቃሚ አይደሉም፤ ማንም ሰው ግን ቆሽሸው ቢያገኛቸውም ወደ ኪሱ ይላቸዋል፡፡
“እና እኔ ለይወት ጠቃሚ ቁም ነገር ያለውን ቆሻሻ ወደ
ኪሴ ብል ያለፋሁበትን ገንዘብን ፈልጌ አይደል? እውቀት ጠምቶኝ
እንጂ፡፡ ስለዚህ ምኑ ያስነውራል" ከት ከት ብሎ ሳቀ፡ ካርለት አንገቷን በአድናቆት ወዘወዘች፤ አልሳቀችም፡፡
“ኢትዮጵያ ውስጥ የፍልስፍና ሰዎችም አሉ፡፡ ማህበረሰቡ ግን እንደ ቆሻሻ ያያቸዋል፧ እነሱ ግን ለአገሪቱ ጠቃሚ እሴቶች
ነበሩ…" የትልቁ ጀሪካን ክዳን እንደገና ተከፈተ፡፡ ደቅ ደቅደቅ…
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
“እኔ ሰላም ፈላጊ ነኝ፡ በሰላም አብረው እንዲኖሩ ከብርሃን ወደ ጨጎጎታሙ ጨጓራዬ ውስጥ አስገብቻቸው እነሱ ተባብረው እኔን አንደማጥቃት እርስ በርሳቸው ካልተስማሙና ከተጣሉ የከፋው ተበደልሁ ባይ በሁለት መንገድ (በጁ ምልክት እያሳያት
ወይም በላይ ወይ በታች መውጣት ይችላል። እኔ ደድግሞ በጠየቁኝ
አቅጣጫ በሬን እከፍታለሁ" ብሎ ፈገገ፤ ካርለት ግን ሳቋን መቆጣጠርን ተሳናት፡ ወርቃማ ፀጉሯ እስኪርገፈገፍ ተሳፋሪው ሁሉ እየዞረ እስኪያያት… ሳቀች እሱ ግን ፀጥ አለ፤ እንቅልፍ እንቅልፍ አለው ተኛ! ካርለት ትከሻ ላይ፤ ወርቃማ ፀጉሯ እንደ በቆሉ ጭራ ፊቱን ሲነካካው የናቱን ጡት እንደሚጠባ ህፃን ፍርክስክስ ብሎ ተኛ
“ኩርር… ኩርርር. እያደረገ፡፡
ዝዋይ ላይ አውቶቡስ ለቁርስ ሲቆም ነቃ። ከጠዋቱ አራት ሰዓት ተኩል ነው: ሰዉ ሁሉ ወረደ: ካርለት ካለፂማሙ ሰው
የምታውቀው የለም:: ስለዚሀ አብረው ወረዱ፡፡
የኢትዮጵያውያን ምግብ ለሷ አዲስ አይደለም። ግን
ለተወሰኑ ወራት እርቃው ቆይታለች፡፡
እሱ ጥሬ ክትፎ እሷ ዳቦና ሻይ አዘው ሲበሉ ቆዩና፡-
“ስለ ከቡ ነገርኩሽ" አለ ፂሞ:
“ማነች ከቡ?"
“ሚስቴi ለጋብቻ ስጠይቃት ፂማም ነህ' ብላ ናቀችኝ፡ ዝም ብዬ ጥረቴን ቀጠልሁ፡፡ ፂሙ አያስጠላሽም፤ምኑን ልትስሚው ነው' ብለው ሲያጥላሉባትም እኔ ጥረቴን እንደቀጠልሁ ነበር፡ አንድ
ቀን ታድያ ተሳካልኝ ለትዳር እንደምፈልጋት የተማርሁ መሆኔን ላዬ ሞኛ ሞኝ ቢሆንም ውስጤ ግን ዘመናዊ እንደሆነ በአለማችን ካሉ በጣት ከሚቆጠሩ ደስተኞች መካከል አንዱ መሆኔን…
እየዘረዘርሁ ሳጫውታት ቆየሁ፡፡ ምኗ ሞኝ መሰለችሽ! ቆቅ ነች:
ከምታየውና ከሰማችው ጋር እኔ ያልኋት ሁሉ ተምታታባት ከቡ!
“ሰርቲፍኬቴን ስቀበል የተነሳሁትን ፎቶ ሳሳያት ግን ውሃ ሆነች፡ ፍንጥር ፍንጥር ማለቷን ቀነሰች፡ ያኔ ጠልፎ እሚጥላትን ምላሴን እያወናጨፍሁ እግሯን አንስቼ እግሬ ላይ አደረግሁና የርግብ
አሳሳም ስሚያት ወጥቼ ስሄድ የጨው መላሾ እንደቀመሰ ከብት
እየተከተለችኝ ለምን አትመጣም መሰለሽ!" ብሎ ሳቁን ለቀቀው፡፡
ካርለት ስለ አንድ ነገር መናገር በጀመረ ቁጥር መጨረሻው አስቂኝ
መሆኑን መጠበቅ ጀምራ ስለነበር እሷም አብራው
ሳቀችና የሆነ ነገር
በህሊናዋ ትዝ አላት እንግዳ አባባል፡
“ምንድነው የርግብ አሳሳም''
“አታውቂም? ብዙው ኧረ በጠቅላላው ሰው የሚያውቅ አይመስለኝም" አላትና ቀና አለ፡፡ “እኔ ግን የተማርሁት ከርግቦች
ነው፡፡ ቆርቆሮዬ ላይ ሲ
ሲዳሩ አይቼ፡፡
“ታያለሽ ከንፈሬ አካባቢ ያለውን ፂሜን ለመሳም ከፈለግሁ ከሴቷ አፍ ውስጥ ገብቶ ጉሮሮዋን ያንቃታል፡፡ እኔ ደግሞ ችግር
መፍጠር አልወድም፤ ለምን ብዬ! ሰው ሁሉ የሌላው ሳይጨመር የራሱ ችግር መቼ አነሰው… ስለዚህ እኔ እንደ እርግብ አፌን
ስከፍትላት ክቡ ከንፈሯን ውስጥ ትጨምረዋለች ያኔ እጠባታለሁ ከንፈሯን: ያ ነው የእርግብ አሳሳም! ያ የርግብ አሳሳም ነው ነው
ከቡዬን እንደ ከብት እያንደረደረ እቤቴ ያስገባት፡፡ ፂሜ ችግር
ስለማይፈጥርባት ቅቤ እየቀባች ሽሩባ ትሰራኝ ጀመር፡፡ ከዚያ እንዲያውም ልቧ እየራራ እንደ ሰናፍጭ የሚሰነፍጥ ፍቅሯን
እየመገበች ይኸው ያየኝን ሁሉ አጠገብህ ካልተቀመጥን' እያስኘ
የሚያስጎመጅ ሰው ወጣኝ" አላትና ሳቀ ተሳሳቁ…..
አውቶብሱ እንደገና ጉዙውን ሲቀጥል ፂሞ ከያይነቱ
ጎንጨት አድርጎ ተኛ: ካርለት እንግዳ ባህሪው ገርሟታል። አጠገቡ
መቀመጧን እንዳልጠላችው አሁን ግን ከነበረው ሰው
ልትግባባው የምትችለው ከሱ የተሻለ እንዳልነበር ተሰማት።
አውቶብሱ የላንጋኖንና የሻላን ደን እያቆራረጠ ሲጓዝ ሙቀቱ እየጨመረ የዳቦ መጋገሪያ ፍም ላይ የተቀመጡ ያህል
ያተኩስ ጀመር። የአውቶብሱ መስኮትና በር ባጠቃላይ ክርችም ብሎ
ተዘግቶ ህዝቡ በላብ ሻወር ይታጠባል፡ መስኮቱን ለምን
እንደማይከፍቱት ፂሞን ጠይቃው የአውቶብስ መስኮት አትክፈቱ•
ብርድ ይመታችኋል ያለው ዶክተር ባይታወቅም ልጅ አዋቂውን ቃሉን አክብሮ በሙቀት መቀቀል መምረጡን ነግሯታል፡ ስለዚህ የለበሰችውን ጃኬት አውልቃ በነጭ ቲሸርት ሆና የሙቀት ቅጣቷን
እየተቀበለች ለማረፍ ከፊት ለፊቷ ካለው ወንበር የብረት ዘንግ ላይ ራሷን ደገፍ አደረገች፡፡
ሙዚቃው ማንቧረቁ አልቆመም፡፡ አውቶብሱ ማርሹን እየቀያየረ ይጓዛል፡ ካርለት እንደ ቀልድ እንቅልፍ ወስዷት ቆይታ የአውቶብሱ ሹፌር አህያ ድንገት ልትገባበት ስትል ፍሬኑን ያዝ
ሲያደርግ ከወንበሩ ጋር ተጋጨችና ብንን ብላ ደንግጣ ተነሳች፡፡
ፂሞ ያነባል። ብጥስጥስ ያለች መጽሐፉን፡ ትንሽ ቆይቶ ከትልቁ ኪሱ ወረቀቶች ያወጣና ያነብ ጀመር፡ ካርለት
ተደንቃ አየችው፡፡ ልታምን አልቻለችም፡፡ ማንም ሰው ያደርገዋል ብላም አትገምትም፡:
የምን ወረቀቶች ናቸው?”
“ወረቀቶቹ አያቸው ግንባሩን ሽቅብ ሰብሰብ አድርጎ፡፡
"ቁም ነገር ያላቸው ወረቀቶች ናቸው፡፡"
ላያቸው እኮ ቆሻሻ አለባቸው?”
“አዎ አይነምድር አው፡ ግን ደርቋል፡፡ ሳነሳው እንኳን ብዙም አልደረቀም ነበር፡ ይኸ ጃኬት ግን ለእኔ ብቻ ሳይሆን ለመሃረቤና
ስለሚፈጥር እዚያው ደረቀ፡፡
ለወረቀቶችም ሙቀት
እስክርቢቶ አይበረክትልኝም ሙቀቱ ያገነፍለዋል፡፡"
“ወረቀቶቹን ከየት ነው ያገኘሃቸው?''።
“በየሄድሁበት መፀዳዳትም ባልፈልግ ሽንት ቤት መሄድ
አዘወትራለሁ የተፃፈውን ማንበብ ሱስ ሆኖብኛል፡ አሁን አሁን ደግሞ አንዳንድ ሽንት ቤቶች ውስጥ ያሉ ቅርጫቶች ላይ ሰው
ተፀዳድቶባቸው እማገኛቸው ወረቀቶች ሽንት ቤቶች ከመፀዳጃነት
አልፈው ወደ መፃህፍት ቤትነት እየተቀየሩ ነው
የሚያሰኝ ነው፡፡
“በአማርኛ ሆነ እንጂ ይህን ብታነቢው የወደቅሽበትን
ሳታውቂው ሶስት ቀን ተኝተሽ ትከርሚ ነበር" አላት፡፡
“ቆሻሻ ወረቀቱን አትጠየፍም?"
“እጠየፋለሁ እንጂ! ግን ጠቃሚ ነገር ኣለበት፡፡ ጠቃሚ ነገር ደግሞ ቆሻሻ አለው ተብለቀ አይጣልም፡፡ ቆሻሻ ማለት ጥቅም
የማይሰጥ ተራ ነገር ነው፡፡
“ይገርምሻል ካለ እነዚህ'' ጀሪካኖቹን ጠቁሞ አሳያት
“...ካለ እነዚህና ካለ ከቡ የረባም ጓደኛ የለኝ፡፡ ምናልባት እኔ ወይ እነሱ ቆሻሻ ስለሆን ይሆናል ከብዙው የሥራ ጓደኞቼ ጋር
የማልግባባው ታዲያልሽ…" የትንሽዋን ጀሪካን ክዳን ከፍቶ ወደ መስታዋቱ ዞሮ አንደቀደቀና
“…ታዲያልሽ ከሽንት ቤት ቅርጫት ቆሻሻ ወረቀት አንስተህ እንዴት እኪስህ ትከታለህ ያሳዝናል! ይህን የሚፈጽም ህሊናው
የተስተካከለ ሰው የለም ካለ እብድ በቀር' ብለው አጥላሉኝ፡፡
“አንድ ቀን ታድያ ሁለት ቀያይ ብሮችን ይዥ ሽንት ቤት ገባሁና በብሩ ተፀዳጅቼ ወጣሁ፡፡ ከኔ የሚቀጥለው አላየኝም ገባ ብሎ ሲወጣ ተመልሼ ብገባ የተፀዳዳሁባቸውን የብር ኖቶች ወስዷቸዋል
ደሞ ሌላ ቦታ ሄጄ በሁለት አምስት አምስት ብሮች ተፀዳዳሁ ... ቀጥሎ የገባው ሲወጣ ብሮቹ የሉም፡፡ hዚያ ደግሞ በአንድ አንድ ብር ሞከርኩ፤ እነሱም ተወሰዱ ታዲያልሽ!ብሮቹ ከእለት ጥቅም
ሌላ ጠቃሚ አይደሉም፤ ማንም ሰው ግን ቆሽሸው ቢያገኛቸውም ወደ ኪሱ ይላቸዋል፡፡
“እና እኔ ለይወት ጠቃሚ ቁም ነገር ያለውን ቆሻሻ ወደ
ኪሴ ብል ያለፋሁበትን ገንዘብን ፈልጌ አይደል? እውቀት ጠምቶኝ
እንጂ፡፡ ስለዚህ ምኑ ያስነውራል" ከት ከት ብሎ ሳቀ፡ ካርለት አንገቷን በአድናቆት ወዘወዘች፤ አልሳቀችም፡፡
“ኢትዮጵያ ውስጥ የፍልስፍና ሰዎችም አሉ፡፡ ማህበረሰቡ ግን እንደ ቆሻሻ ያያቸዋል፧ እነሱ ግን ለአገሪቱ ጠቃሚ እሴቶች
ነበሩ…" የትልቁ ጀሪካን ክዳን እንደገና ተከፈተ፡፡ ደቅ ደቅደቅ…
👍27🥰2😁2❤1
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሦስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ሲሚንቶና ብረት የጫነው ኤንትሬ ከሌሊቱ አስር ሰዓት
ከእርባምንጭ ተነሳ፡፡ ያጓራል ያቃስታል ይንቶሰቶሳል. ጉራው
እንጂ ጎዞው የኤሊ ነው፡፡ ማዝገም… ከአርባምንጭ ቀይ አፈር ሁለት መቶ ስምንት ኪሎ ሜትር ለመጓዝ አስራ ሁለት ሰዓት ፈጀበት፡፡ሲሚንቶና ብረቱ ላይ ያሉት ተሳፋሪዎች የተሳፈሩት ተለምነው
ሳይሆን ለምነው ነው፡ ወደ ጂንካ የሚሄድ አስተማማኝ
ትራንስፖርት የለም፡፡ ወደዚያ መሄድ የፈለገ አማራጭ እንደሌለው አውቆ በአጋጣሚው መጠቀም አለበት፡፡ ካለበለዚያ ሲቀላና ሴቻ እያለ ሲንገላወድ ይከርማታል፡፡
የሚያንሰፈስፈው ውርጭ እያኮማተረው የማያተኩሰው የፀሐይ ሙቀት እያቃጠለው አይኑ ጆሮው አፍንጫው፦ አፉ አቧራ እየቃመ ከመሬት ርቆ ጭነት ላይ የወጣው ተሳፋሪ ለሁሉም
ሳይሳቀቅ ጭንቅላቱን በጨርቅ ቢጤ ጠቅልሎ በሁለቱ እጁ ካቦውን
ጥርቅም አድርጎ ይዞ እየተናጠ መጓዝ ነው፡፡ ታዲያ አቀበት ቁልቁለቱ ጫካና ሜዳው አይጠገብም፡፡ እንደ ጥሩ ትርዒት እየተቀያየረ ያዝናናል፧ “ሣይደግስ አይጣላ" እንዲሉ!
ካርለት አልፈርድ አርባ ምንጭ መቆየት አልፈለገችም፡፡በእርግጥ በቦታ አመራረጡ ምሥራቅ አፍሪካ ወደር አይገኝለትም
ተብሎ በውጭ ዜጎች የተመሰከረለት የበቀለ ሞላ ሆቴል ሁለት ቀለማቸው የተለያዩ ሐይቆች (ጫሞና አባያ) በርካታ የሆኑ ምንጮች በኢትዮጵያ ከሚገኙት ታላላቅ ተራሮች አንዱ ጉጂ ተራራና ከስሩ የኢኳቶሪያል የዝናብ ደን ያለው ተፈጥርው የማይሰለቻት ቢሆንም ችግሩ ሐመሮች ናፍቀዋታል።
የሐመሩን የፍዬል ቆዳዋን የሐመር ጎረምሶች የሽለሟትን የእጅ አንባር በአስሩም እጣቷ የምትጠቀምበትን ቀለበት የአንገቷን ጨሌ ስታይ የሐመር ትዝታዋ አገረሸ፡፡ መከባበሩ መተዛዘኑ አብሮ
መብላት መጠጣቱ ጫካውና መንደሩ ተራራውና ሜዳው
በተለይም የኢቫንጋዲ ጭፈራው ውልብሎ ታያት፡ ወደ ሐመር የምትሄድ ሳይሆን ከሐመር እንደምትመለስ ሁሉ! ልቧ እንደ ፅናፅል በፍርሃት ተንሿሿ፡ ፊቷ ገረጣ የሐመር ተፈጥሮአዊ ህይወት
ራባት፡፡
አጠገቧ ከኤንትሬው ጀርባ መኪናው ቆጥ ላይ ብዙ ሰው ሰፍሯል፡፡ ወታደር ተማሪ ነጋዴ ቄስ ሳይቀር አለ፡፡ ቀልዱ ጨዋታው ያስቀናል፡፡ ሰዎች ሁሌም ችግር ሲበዛባቸው ደጎች
ተዛዛኞች... መሆናቸው ያለ ነው፡ ካርለት ሁሉንም ስታጤን ቄሱ ሌላው ሲጫወት ዝም ብለው ሲያዳምጡ ይቆዩና ፈርጠም ብለው
ማሳረጊያ ሲሰጡ አስተውላቸዋለች፡፡ በእርግጥም የሚጫወቱት
አይገባትም ፤ ሆኖም ግን ይንከባከቧታል፡፡ አይናቸውን ወርወር
ያደርጉና ፈገግ ይሉላታል፡፡ እየደጋገሙ ያዩዋታል፡፡ ብታናግራቸው በወደደች ግን የቋንቋ ችግር አለ በመካከላቸው፡፡ እሳቸው ስለ እሷ እያሰቡ እንደሆን ገምታለች፡፡ ጠይቃ ሃሣባቸውን ማወቅ ባለመቻሏ ግን በተራዋ እሷም ስለ እሳቸው ማሰብ ጀመረች
ኢትዮጵያ የተለያዩ ሃይማኖቶች ያሉባት ሃገር ነች፡ ክርስቲያኑ ሙስሊሙ… ህዝቡ የአንዱ ወይም የሌላው ተከታይ ነው በአመዛኙ፡ የአገሪቱ ታሪክና የባህል መዘክርም የሚገኙ ናቸው፡፡ ካርለት አንዴ ሰሜን ኢትዮጵያን ለመጎብኘት አክሱም ላሊበላ ባህርዳር ጎንደር ሄዳ ብዙ ቤተክርስቲያኖችንና መስጊዶችን ጎብኝታለች፡ በምስራቅም እንዲሁ ማየት የሚገባትን አይታለች፡፡
ግን ደብረብርሃን ስላሴ
ጎንደርን በጎበኘችበት ጊዜ
የሚባለውን ታሪካዊ ቤተ ክርስቲያን ካየች በኋላ ከሁለት ወንድ መነኮሳት ጋር ያደረገችው የሣሣብ ልውውጥ አይረሳትም፡፡
ደርቡሾችና ግራኝ ሞሐመድ ብዙውን የጎንደር ቤተ
መንግሥትና ቤተ ክርስቲያን ሲያፈርሱና ሲያቃጥሉ ደብረብርሃን ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ግን ከመፍረስና ከመቃጠል ተርፏል፡ ሁሉም
አልደረሱበትም፡፡ እና ቤተክርስቲያኑ በወቅቱ
የነበረውን የአገሪቱን
የህንፃ ሥራ ጥበብ ምጥቀት የሚያረጋግጥ ነው፡፡
አፀደ ግቢው በውስጡ ያሉት ሥነ ስዕላቱ በመፅሐፍ ቅዱስ
ላይ ስሟ ሰባ ጊዜ ተደጋግሞ የተጠቀሰላትን ኢትዮጵያን ሃይማኖታዊ
ጥንካሬና ድንቅ የቤተ ክህነት ሥርዓት የሚያረጋግጥ ነው፡፡
ልጅ እግሩ መነኩሴ ለካርለትና ስአስጎብኚዋ የቤተ ክርስቲያኗን ታሪካዊነት ሲያስረዱዋቸው ከቆዩ በኋላ ከደብሩ
ከመውጣታቸው በፊት አንድ ጠና ያሉ መነኩሴ መግቢያው እድሞ
ካለው ሁለት ክፍል አንደኛው በር ላይ ዳዊታቸውን ሲደግሙ አየችና ከመነኩሴው ጋር ለመነጋገር ፎቁ ላይ ወጣች፡፡
መነኩሴው የተቀመጡት ! እሳቸውና ልጅ እግሩ
ከሚኖሩበት ክፍል
በሩ ላይ ነው፡: ከጎን ያለችው ክፍል ቢሮ ናት፡፡
ካርለትና አስጎብኝዋን ሲያዩ መነኩሴው ከተቀመጡበት
ተነሱና በትህትና ተቀበሏቸው፡፡ ወደ ውስጥ ግቡ እንዳይሉ ካርለት
ሴት ናት፡፡ ሴት ደግሞ ወደ መነኩሴ መኖሪያ ቤት አትገባም! ስለዚህ በረንዳ ላይ ቁጭ አሉ፡፡
አባ ከሰል ላይ በበራድ ውሃ ሞልተው ጣዱና ተመልሰው
ለወግ መጀመሪያ እህሣ እንደምን ናችሁ" አሉ፡ የመጀመሪያ ቋንቋቸው ትግርኛ መሆኑ ከአነጋገራቸው ይታወቃል፡
“እንዴት መነኩሴ ሆኑ?" ብላ ጠየቀቻቸው ካርለት
በአስተርጋሚዋ፡፡
“በአያልቅበቱ ፈቃድ ነዋ ካለ እሱ ፈቃድ ምን የሚሆን አለ" አምላካቸውን ሽቅብ አዩ፡፡ እግዚአብሔር ከመንበሩ ላይ ተቀምጦ
ታያቸው በአይነ ህሊናቸው: ቶሎ ሰገድ ብለው አይናቸውን መለሱ፡፡
እዚህ ምን አገልግሎት ይሰጣሉ?"
እህ የእግዚአብሔርን ቤት! ቤተ ክርስቲያኒቱን አገለግላለሁ ተደብር ደብር እየሄድሁ እግዚአብሔርን ማገልገል ነው ሥራዬ፡ ሌላ
ዓለማዊውን ህይወትማ ትቸው መጥቻለሁ,," ቀና ብለው ሁለት እጆቻቸውን ዘርግተው አጮልቀው
አዩ ወደ መንበሩ
“ቤተሰብ ልጅ አልነበረዎትም? ካርለት ሌላ ጥያቂ ጠየቀቻቸው፡
“ነበረኝ እንጂ! ግና ከአንድዬ ምን የሚበልጥ አለ!-" አዩ ሽቅብ፡፡ካርለት ከመነኩሴው ጋር ብዙ ሃሣብ ተለዋወጠችና ደስ
አላት፡
መነኩሴው ሻዩን በብርጭቆ ቀዱና በቀለምሻሽ ዳቦ ቆራርሰው ሰጧቸው ለነካርለት፡፡
“አባ… ሻዩ ፈልቷል አይመጡም ወይ" ጠና ያሉት መነኩሴ ልጅ እግሩን መነኩሴ ጠሩአቸው፡፡
“…ከቤተ-ክህነት ሙያ ሌላ ምን ሙያ አላችሁ?"
“ኧረገይ ከዚህ ሌላ ደግሞ ምን ሞያ ይኖረናል! ኧረ
የለንም፡፡"
“የሃይማኖት ተከታዩ ወደ ቤተ-ክርስቲያኗ ሲመጣ ምንድን ነው የምታስተምሩት?”
“መንፈሳዊ ትምህርት መንፈሳዊ ትምህርት ይማራል! ቅዱሳት መጽሐፍት ይነበበለታል…"
“ቤተ ክርስቲያኗን ስታገለግሉ ለእናንተ የሚያስፈልገው
መሠረታዊ ነገር ይሟላላችኋል?
“ኧረገይ! ኧረ ችግር ነው ችግሩማ እንዲህ በአጭር ጊዜ ተነስቶ አያልቅም ልጅ እግሩ መነኩሴ ተከዝ አሉ፡
"እርስዎ ሃይማኖትዎ ምንድነው? ጠና ያሉት መነኩሴ አንዴ አስተርጓሚዋን ሌላ ጊዜ እሷን እየተመለከቱ ጠየቋት፡፡
“የካቶሊክ ሃይማኖት ተከታይ ነኝ፡” ሁለቱም መነኮሳት ቀና ብለው አዩዋትናı “አሃ አሉ ባንድነት እንደ መደንገጥ ብለው፡፡
“በእኛ ሃገር መነኮሳት ከመንፈሳዊ እውቀታቸው ሌላ የሞራል ትምህርትና የሙያ ስልጠና ይሰጣቸዋል፡ ስለዚህ መነኮሳት ምዕመናኑ ወደ ቤተ ክርስትያን ሲመጡ መንፈሳዊ ብቻ ሳይሆን
ሞራላዊ ትምህርትም ያስተምራሉ፡
“የመነኮሳት እርዳታ በመንፈሳዊና ሞራላዊ ትምህርትም ብቻ
ሳይሆን በስልጠና ባገኙት
ሙያ በህክምና. በጓሮ አትክልት በእንጨትና ብረታብረት ሥራ….. ወዘተ ህዝቡን ያገለግሉታል፡፡
ስለዚህ መነኮሳት የራሳቸው ገቢ ያላቸው፤ ህዝቡን የሚረዱ ምፅዋት
የማይጠይቁ ነገር ግን ለህብረተሰቡ መንፈሳዊና ሞራላዊ ትምህርት
እየሰጡ በሙያ ሰልጥነው ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን አገርን ወገንን… መርዳት መቻሉን አርአያን ሆነው የሚያስተምሩ አባቶች ናቸው
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሦስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ሲሚንቶና ብረት የጫነው ኤንትሬ ከሌሊቱ አስር ሰዓት
ከእርባምንጭ ተነሳ፡፡ ያጓራል ያቃስታል ይንቶሰቶሳል. ጉራው
እንጂ ጎዞው የኤሊ ነው፡፡ ማዝገም… ከአርባምንጭ ቀይ አፈር ሁለት መቶ ስምንት ኪሎ ሜትር ለመጓዝ አስራ ሁለት ሰዓት ፈጀበት፡፡ሲሚንቶና ብረቱ ላይ ያሉት ተሳፋሪዎች የተሳፈሩት ተለምነው
ሳይሆን ለምነው ነው፡ ወደ ጂንካ የሚሄድ አስተማማኝ
ትራንስፖርት የለም፡፡ ወደዚያ መሄድ የፈለገ አማራጭ እንደሌለው አውቆ በአጋጣሚው መጠቀም አለበት፡፡ ካለበለዚያ ሲቀላና ሴቻ እያለ ሲንገላወድ ይከርማታል፡፡
የሚያንሰፈስፈው ውርጭ እያኮማተረው የማያተኩሰው የፀሐይ ሙቀት እያቃጠለው አይኑ ጆሮው አፍንጫው፦ አፉ አቧራ እየቃመ ከመሬት ርቆ ጭነት ላይ የወጣው ተሳፋሪ ለሁሉም
ሳይሳቀቅ ጭንቅላቱን በጨርቅ ቢጤ ጠቅልሎ በሁለቱ እጁ ካቦውን
ጥርቅም አድርጎ ይዞ እየተናጠ መጓዝ ነው፡፡ ታዲያ አቀበት ቁልቁለቱ ጫካና ሜዳው አይጠገብም፡፡ እንደ ጥሩ ትርዒት እየተቀያየረ ያዝናናል፧ “ሣይደግስ አይጣላ" እንዲሉ!
ካርለት አልፈርድ አርባ ምንጭ መቆየት አልፈለገችም፡፡በእርግጥ በቦታ አመራረጡ ምሥራቅ አፍሪካ ወደር አይገኝለትም
ተብሎ በውጭ ዜጎች የተመሰከረለት የበቀለ ሞላ ሆቴል ሁለት ቀለማቸው የተለያዩ ሐይቆች (ጫሞና አባያ) በርካታ የሆኑ ምንጮች በኢትዮጵያ ከሚገኙት ታላላቅ ተራሮች አንዱ ጉጂ ተራራና ከስሩ የኢኳቶሪያል የዝናብ ደን ያለው ተፈጥርው የማይሰለቻት ቢሆንም ችግሩ ሐመሮች ናፍቀዋታል።
የሐመሩን የፍዬል ቆዳዋን የሐመር ጎረምሶች የሽለሟትን የእጅ አንባር በአስሩም እጣቷ የምትጠቀምበትን ቀለበት የአንገቷን ጨሌ ስታይ የሐመር ትዝታዋ አገረሸ፡፡ መከባበሩ መተዛዘኑ አብሮ
መብላት መጠጣቱ ጫካውና መንደሩ ተራራውና ሜዳው
በተለይም የኢቫንጋዲ ጭፈራው ውልብሎ ታያት፡ ወደ ሐመር የምትሄድ ሳይሆን ከሐመር እንደምትመለስ ሁሉ! ልቧ እንደ ፅናፅል በፍርሃት ተንሿሿ፡ ፊቷ ገረጣ የሐመር ተፈጥሮአዊ ህይወት
ራባት፡፡
አጠገቧ ከኤንትሬው ጀርባ መኪናው ቆጥ ላይ ብዙ ሰው ሰፍሯል፡፡ ወታደር ተማሪ ነጋዴ ቄስ ሳይቀር አለ፡፡ ቀልዱ ጨዋታው ያስቀናል፡፡ ሰዎች ሁሌም ችግር ሲበዛባቸው ደጎች
ተዛዛኞች... መሆናቸው ያለ ነው፡ ካርለት ሁሉንም ስታጤን ቄሱ ሌላው ሲጫወት ዝም ብለው ሲያዳምጡ ይቆዩና ፈርጠም ብለው
ማሳረጊያ ሲሰጡ አስተውላቸዋለች፡፡ በእርግጥም የሚጫወቱት
አይገባትም ፤ ሆኖም ግን ይንከባከቧታል፡፡ አይናቸውን ወርወር
ያደርጉና ፈገግ ይሉላታል፡፡ እየደጋገሙ ያዩዋታል፡፡ ብታናግራቸው በወደደች ግን የቋንቋ ችግር አለ በመካከላቸው፡፡ እሳቸው ስለ እሷ እያሰቡ እንደሆን ገምታለች፡፡ ጠይቃ ሃሣባቸውን ማወቅ ባለመቻሏ ግን በተራዋ እሷም ስለ እሳቸው ማሰብ ጀመረች
ኢትዮጵያ የተለያዩ ሃይማኖቶች ያሉባት ሃገር ነች፡ ክርስቲያኑ ሙስሊሙ… ህዝቡ የአንዱ ወይም የሌላው ተከታይ ነው በአመዛኙ፡ የአገሪቱ ታሪክና የባህል መዘክርም የሚገኙ ናቸው፡፡ ካርለት አንዴ ሰሜን ኢትዮጵያን ለመጎብኘት አክሱም ላሊበላ ባህርዳር ጎንደር ሄዳ ብዙ ቤተክርስቲያኖችንና መስጊዶችን ጎብኝታለች፡ በምስራቅም እንዲሁ ማየት የሚገባትን አይታለች፡፡
ግን ደብረብርሃን ስላሴ
ጎንደርን በጎበኘችበት ጊዜ
የሚባለውን ታሪካዊ ቤተ ክርስቲያን ካየች በኋላ ከሁለት ወንድ መነኮሳት ጋር ያደረገችው የሣሣብ ልውውጥ አይረሳትም፡፡
ደርቡሾችና ግራኝ ሞሐመድ ብዙውን የጎንደር ቤተ
መንግሥትና ቤተ ክርስቲያን ሲያፈርሱና ሲያቃጥሉ ደብረብርሃን ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ግን ከመፍረስና ከመቃጠል ተርፏል፡ ሁሉም
አልደረሱበትም፡፡ እና ቤተክርስቲያኑ በወቅቱ
የነበረውን የአገሪቱን
የህንፃ ሥራ ጥበብ ምጥቀት የሚያረጋግጥ ነው፡፡
አፀደ ግቢው በውስጡ ያሉት ሥነ ስዕላቱ በመፅሐፍ ቅዱስ
ላይ ስሟ ሰባ ጊዜ ተደጋግሞ የተጠቀሰላትን ኢትዮጵያን ሃይማኖታዊ
ጥንካሬና ድንቅ የቤተ ክህነት ሥርዓት የሚያረጋግጥ ነው፡፡
ልጅ እግሩ መነኩሴ ለካርለትና ስአስጎብኚዋ የቤተ ክርስቲያኗን ታሪካዊነት ሲያስረዱዋቸው ከቆዩ በኋላ ከደብሩ
ከመውጣታቸው በፊት አንድ ጠና ያሉ መነኩሴ መግቢያው እድሞ
ካለው ሁለት ክፍል አንደኛው በር ላይ ዳዊታቸውን ሲደግሙ አየችና ከመነኩሴው ጋር ለመነጋገር ፎቁ ላይ ወጣች፡፡
መነኩሴው የተቀመጡት ! እሳቸውና ልጅ እግሩ
ከሚኖሩበት ክፍል
በሩ ላይ ነው፡: ከጎን ያለችው ክፍል ቢሮ ናት፡፡
ካርለትና አስጎብኝዋን ሲያዩ መነኩሴው ከተቀመጡበት
ተነሱና በትህትና ተቀበሏቸው፡፡ ወደ ውስጥ ግቡ እንዳይሉ ካርለት
ሴት ናት፡፡ ሴት ደግሞ ወደ መነኩሴ መኖሪያ ቤት አትገባም! ስለዚህ በረንዳ ላይ ቁጭ አሉ፡፡
አባ ከሰል ላይ በበራድ ውሃ ሞልተው ጣዱና ተመልሰው
ለወግ መጀመሪያ እህሣ እንደምን ናችሁ" አሉ፡ የመጀመሪያ ቋንቋቸው ትግርኛ መሆኑ ከአነጋገራቸው ይታወቃል፡
“እንዴት መነኩሴ ሆኑ?" ብላ ጠየቀቻቸው ካርለት
በአስተርጋሚዋ፡፡
“በአያልቅበቱ ፈቃድ ነዋ ካለ እሱ ፈቃድ ምን የሚሆን አለ" አምላካቸውን ሽቅብ አዩ፡፡ እግዚአብሔር ከመንበሩ ላይ ተቀምጦ
ታያቸው በአይነ ህሊናቸው: ቶሎ ሰገድ ብለው አይናቸውን መለሱ፡፡
እዚህ ምን አገልግሎት ይሰጣሉ?"
እህ የእግዚአብሔርን ቤት! ቤተ ክርስቲያኒቱን አገለግላለሁ ተደብር ደብር እየሄድሁ እግዚአብሔርን ማገልገል ነው ሥራዬ፡ ሌላ
ዓለማዊውን ህይወትማ ትቸው መጥቻለሁ,," ቀና ብለው ሁለት እጆቻቸውን ዘርግተው አጮልቀው
አዩ ወደ መንበሩ
“ቤተሰብ ልጅ አልነበረዎትም? ካርለት ሌላ ጥያቂ ጠየቀቻቸው፡
“ነበረኝ እንጂ! ግና ከአንድዬ ምን የሚበልጥ አለ!-" አዩ ሽቅብ፡፡ካርለት ከመነኩሴው ጋር ብዙ ሃሣብ ተለዋወጠችና ደስ
አላት፡
መነኩሴው ሻዩን በብርጭቆ ቀዱና በቀለምሻሽ ዳቦ ቆራርሰው ሰጧቸው ለነካርለት፡፡
“አባ… ሻዩ ፈልቷል አይመጡም ወይ" ጠና ያሉት መነኩሴ ልጅ እግሩን መነኩሴ ጠሩአቸው፡፡
“…ከቤተ-ክህነት ሙያ ሌላ ምን ሙያ አላችሁ?"
“ኧረገይ ከዚህ ሌላ ደግሞ ምን ሞያ ይኖረናል! ኧረ
የለንም፡፡"
“የሃይማኖት ተከታዩ ወደ ቤተ-ክርስቲያኗ ሲመጣ ምንድን ነው የምታስተምሩት?”
“መንፈሳዊ ትምህርት መንፈሳዊ ትምህርት ይማራል! ቅዱሳት መጽሐፍት ይነበበለታል…"
“ቤተ ክርስቲያኗን ስታገለግሉ ለእናንተ የሚያስፈልገው
መሠረታዊ ነገር ይሟላላችኋል?
“ኧረገይ! ኧረ ችግር ነው ችግሩማ እንዲህ በአጭር ጊዜ ተነስቶ አያልቅም ልጅ እግሩ መነኩሴ ተከዝ አሉ፡
"እርስዎ ሃይማኖትዎ ምንድነው? ጠና ያሉት መነኩሴ አንዴ አስተርጓሚዋን ሌላ ጊዜ እሷን እየተመለከቱ ጠየቋት፡፡
“የካቶሊክ ሃይማኖት ተከታይ ነኝ፡” ሁለቱም መነኮሳት ቀና ብለው አዩዋትናı “አሃ አሉ ባንድነት እንደ መደንገጥ ብለው፡፡
“በእኛ ሃገር መነኮሳት ከመንፈሳዊ እውቀታቸው ሌላ የሞራል ትምህርትና የሙያ ስልጠና ይሰጣቸዋል፡ ስለዚህ መነኮሳት ምዕመናኑ ወደ ቤተ ክርስትያን ሲመጡ መንፈሳዊ ብቻ ሳይሆን
ሞራላዊ ትምህርትም ያስተምራሉ፡
“የመነኮሳት እርዳታ በመንፈሳዊና ሞራላዊ ትምህርትም ብቻ
ሳይሆን በስልጠና ባገኙት
ሙያ በህክምና. በጓሮ አትክልት በእንጨትና ብረታብረት ሥራ….. ወዘተ ህዝቡን ያገለግሉታል፡፡
ስለዚህ መነኮሳት የራሳቸው ገቢ ያላቸው፤ ህዝቡን የሚረዱ ምፅዋት
የማይጠይቁ ነገር ግን ለህብረተሰቡ መንፈሳዊና ሞራላዊ ትምህርት
እየሰጡ በሙያ ሰልጥነው ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን አገርን ወገንን… መርዳት መቻሉን አርአያን ሆነው የሚያስተምሩ አባቶች ናቸው
👍24🥰2👎1