አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ሰመመን


#ክፍል_አርባ_አራት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

....ለጥያቄዋ መልስ በመጠበቅ ዐይነት ሦስቱንም ተመለከተቸቻው ፡ ዐይኖቿ አንድ ቦታ እይረጐም በነጭ ቆዳዋ
ላይ ሰማያዊ መሳይ ሥራሥሮቿ ዐልፎ ዐልፎ ይታያሉ ።ገጽታዋ ላይ ፍቅርና ትሕትና ይነበባል ።

ዮናታንና እስክንድር ቡና ሲመርጡ እቤል ሻይ አለ ።ሚስታቸው ወደ ጓዳ ከመሔዷ በፊት ዮናታን ክንዷን ይዘው እጅዋ ላይ ሳም እያረጓት ። ለመልካም መስተንግዶዋ
ምስጋናቸውን የሚገልጹበት መንገድ ነበር

እስክንድር ዐይኑን ማመን አቃተው ወይም ያየው ነገር ሕልም መሰለው ። እውነት ፍቅር ይሆን ? አለ በልቡ ።የትዳር ዕድሜአቸውን ለማወቅ ጓጓ አፍላ ፍቅረኞች ካልሆኑ በስተቀር ተጋብተው በቆዩ ሰዎች መሐል አይቶ የማያውቀውን ሁኔታ ማየቱ ነው ያስደነቀው ያውም በእንግዳ ፊት !

“ ሊብሊንግ ሚስቴም እናቴም ናት ። የሕይወት ጣእም የሚታወቀኝ እሷን አጠገቤ ሳገኛት ነው አሉ ዮናታን ፥
ሚስታቸው ወደ ጓዳ ከገባች በኋላ ። “ ሰውን ማስደሰት መቻል ቀላል ነገር አይደለም ። ሊብሊንግ ይህን ችሎታ በተፈጥሮዋ ታድላዋለች ። ሁል ጊዜ ደስተኛ ነች እንደሚገባኝ ፡ ደስታዋን የምታገኘው ሰዎችን በማስደሰት ነው ።
አቤል ሁኔታዎች እስኪመቻቹለት ከእኛ ጋር እንዲኖር ሐሳቡን ቀድማ ያቀረበችልኝ እሷ ናት ።

አቤል በጥያቄ መልክ ዐይኑን እቁለጨለጨ ።

ከአሁን በፊት የት ታውቀኛለች ?ብሎ ነበር ራሱን የጠየቀው ። ማንኛውም ነገር በዮናታን ሊደርሳት እንደሚችል ወዲያው ገመተ። ወደዚህ ቤት የመምጣቱ ሐሳብ ከእሷ መመንጨቱን ሲሰማ በልቡ ውስጥ ለሴትዮዋ ልዩ ስሜት ተፈጠረበት

“ ከተጋባችሁ ? ” ሲል እስክንድር ፈራ ተባ በሚል ድምፅ ጠየቀ ።

“ ኦ! ስድስት ዓመት ያህል ሆኖአል ። በርሊን በነበርኩበት ጊዜ፡አንዴ ታምሜ ተኝቼ ሐኪም ቤት ውስጥ አስታማሚዬ ሆና ነው ያገኘኋት ። ”

ዮናታን ይህን ሲናገሩ ድምፃቸው የተለየ ቃና ነበረው ።የፍቅረኞች የመጀመሪያ ትውውቅ በልባቸው ታላቅ ትውስት
ጥሎ ያልፋል ። ዮናታንም ለእስክንድር በሰጡት መልስ ሳቢያ ከስድስት ዓመት በፊት የተፈጸመ ትውስት ውስጥ ገቡ .....
ዮናታን በምሥራቅ ጀርመን ውስጥ በሚገኘው ትልቅ ዩኒቨርስቲ የድኅረ ምረቃ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ለተወሰኑ ዓመታት በምቦልት ዩኒቨርስቲ የፍልስፍና መምህር ሆነው አገልግለው ነበር ። እዚያ ሳሉ አንድ ጊዜ የሆድ ውስጥ ሕመም ያድርባቸውና በርሊን ቤክ እሚባለው
ሆስፒታል ይገባሉ ።

በርሊን ቤክ ፣ ከመሃል ከተማው ሀያ ኪሎ ሜትር ያህል ይርቃል ። ውስጡ በአምስት ግቢዎች ተከፍሎ ፡ በጠቅላላ
ዐሥር ሺህ አልጋዎች ያሉት ሰፊ ሆስፒታል ነው ። ዮናታን የተኙት፡“ታይል አይንስ” በሚባለው ግቢ፡ “ እስታስዩን አይን ሁንደርት ሲ ” ክፍል ውስጥ ነበር ።
በማገገም ላይ እንዳሉ አንዲት ነርስ ሲያዩ ልባቸው ይደነግጣል ። ይህች ነርስ ፊቷ ላይ ፈገግታ የተሳለ እንጂ እንደ ሌላው ሰው አንዳንድ ጊዜ ብቻ የምትሥቅ አትመስልም ። ሕሙማንን ለመጎብኘት ስትገባ በሕመም የደከመ ስሜታቸውን በፈገግታ ታነቃቃዋለች ። በውስጥ ቁስል
የዳመነ ፊታቸውን ፈገግታዋ ብርሃን ሆኖ ያፈካዋል ። መስተንግዶዋ ፍቅር የሞላበት በመሆኑ'በክፍሏ ሕሙማን ዘንድ ተወዳጅ ነበረች ። ወደ በሽተኞቹ ክፍል ለመግባት የጉብኝት ወይም የመድኃኒት ዕደላ ሰዓት እስኪደርስ ወይም እነሱ በደወል እስኪጠሩዋት አትጠብቅም ። ብቅ ጥልቅ እንዳለች
ነው የምትውለው ። ልማድ ሆኖባት ሁሌ ትቸኩላለች ።እናም አንድ ቦታ ቆማ አትቆይም ።

ዮናታን ልባቸው ከደነገጠላት ጊዜ ጀምሮ ይህን ችኮላዋን አልወደዱላትም ። ክፍላቸው ገብታ ስትወጣ ፀሐይ
ብልጭ ብላ ድርግም ያለች ያህል ስሜታቸው ይከፋ ጀመር ።

ሥራዋን ጨርሳ ወደ ቤትዋ ልትሔድ በሽተኞቹን ስትሰናበታቸው። የዮናታን ልብ ይረበሽ ነበር ።ሌሊት አልመዋት አድረው ጠዋት ዐይኗን የሚያዩበትን ጊዜ መናፈቅ ሲጀምሩ ልባቸው ፍቅር ፍለጋ ዳዴ እያለ መሆኑን ገመቱ ። ሞኒካ የሚለው ስም አሁንም አሁንም ጆሮአቸው፡ ውስጥ ይደውል ጀመር ።

አንድ ቀን ከሥራ በኋላ እንደ ልማዷ ልትሰናበታቸው ወደ ክፍላቸው ስትግባ ዮናታን እጅዋን ያዝ አድርገው ቅሬታቸውን ተነፈሱላት ።

"ቆይ እንጂ አትቸኩዪ ። ትንሽ አጫውችኝ ሁሌ መቸኮል ምንድነው ?” አሏት ።

ሞኒካ ፈገግ ብላ ፍቃዳቸውን ለመፈጸም አልጋቸው አጠገብ ትንሽ ቆመች ።

“ እውነት ለምንድነው እንዲህ የምትቸኩዬው ” ሲሉ ጠየቋት ።

“ ልማድ ሆኖብኝ ነው ። በምሰራበት ጊዜ ፍጥነቴ አይታወቀኝም ” አለችና : ትንሽ አሰብ አድርጋ ! “ በዚህ በአራት ዓመት ውስጥ ያፈራሁት ጸባይ ነው” አለቻቸው ።

“ ግን ምነው ! ለምን ? ” አሏት ።

“ለአፍላ ፍቅሬ ያገኘሁት ማካካሻ ራሴን ከይዲያ ወዲህ በማራወጥ ዕረፍት መንሣት ነበር ” አለቻችው ሰሜቷን
ግልጽ አድርጋ።

ከዚህ ንግግሯ ጋር ፊቷ ፍም ሲመስል ተመለከቱት ። ስሜቷ መጨፍገጉን አገጽታዋ ላይ አጠኑ ሰው ሠራሽ
የሚመስሉት ዐይኖችዋ፡በቅርቧ ያለውን ነገር ለማየት የተከለከሉ ይመስል በመስኮቱ ማዶ ከሚታየወው ባዶ ሰማይ ላይ ዐረፉ ።

“ ነገሩ እንዲህ ነው ” ስትል ቀጠለች ። “ ከአራት ዓመት በፊት አፈቅረው የነበረው ወጣት የመጀመርያዬ ነበር ። በመሆንም እጭር ጊዜ ውስጥ ሙሉ ልቤንና ፍቅሬን ሰጥቼው ነበር ለማለት እደፍራለሁ ። ነገር ግን ሁለት ዓመት ባልሞላው ጊዜ ውስጥ ጥሎኝ ጠፋ” አለችና ዝም !

“ የት ነው የጠፋው ?” አሏት ዮናታን ፥ ተመስጠው ።

“ ወደ ምዕራብ ጀርመን። እኔ የሰማሁት ጠፍቶ ከሔደ በኋላ ነው እንጂ ምንም ያማከረኝ ነገር አልነበረም ። በእርግጥ
ልቡ መሸፈቱን በአንዳንድ ንግግሮቹ ገምቼ ነበር ። አብዛኛውን ጊዜ በአስተሳሰብ እንጋጫለን ። እኔ በፋሽስቶች ላይ ከፍተኛ ጥላቻ አለኝ ። በሂትለር ዘመን በናዚዎች ታስሮ የማቀቀው አባቴ ቆስሎ በእኔም ላይ ከባድ ተጽዕኖ ነበረው ።ፍቅረኛዬ ግን ያለፈው ትውልድ በፋሺዝም ምን ያህል
እንደ ተሠቃየ ለማጤን ደንታ አልነበረውም በኣፍላ ስሜት ግፊት እኔደሚነቃነቅ እገምት በር ። እናም መጨረሻውን እንደዚያ አደረገወ ። ”

ዮናታን በኀዘን ከንፈራቸውን መጠጡ።

“አያሳዝነኝም ። ልቤን አሳዝኖት ነው የሔደው ”አለች ሞኒካ ፥ ራሷን እየነቀነቀች “ ነገር ግን እሱን ብጠላውም ልቤ ውስጥ የተተከለውን ፍቅር በቀላሉ መንቀል
አልቻልኩም ነበር። ስለዚህ ራሴን በሥራ በማዋከብ ልረሳው ሞከርኩ ። በሚረባውም ፥ በማይረባውም ነገር ነበር ራሴን የማደክመው ። በማያሰፈልግበት ቦታ እፈጥን ነበር ። እየቆየ ሲሔድ ይህ ልማድ እውስጤ ሥር እየሰደያ መጣ። አሁን ያለ ሥራ ለአጭር ጊዜም ቢሆን መቀመጥ አልችልም ። መንፈሴም የሚረካው ፈጠን ፈጠን እያልኩ ከሠራሁ ነው ”አለቻቸውና ፥ ደመናውን ከፊቷ አባርራ ፈገግ አለች ።

ታሪኳ ዮናታንን አጥንታቸውን ሰርስሮ ገብቶ ወደ ፍቅር መዳህ የጀመረ ልባቸውን እደፋፍረው። ነገር ግን ፥
በአፍላነቱ የተጎዳወን የሞኒካን ልብ ለማዳን መቻላቸውን እርግጠኛ አልነበሩም እድሜአቸውን ለማመዛዘን ሞከሩ ።
በዐሥር ዓመት ያህል ይበልጧታል ። ይህ ሁሉ የእንምሮ ማመንታት ነው እንጂ ፥ ፍቅሩ ያለ ምንም ፍርሃት በልባቻው ውስጥ እያደገ መጥቷል ።

ሞኒካም ዮናታን ታሪኳን በተመስጦና በትካዜ ካዳመጡዋት ጊዜ ጀምሮ ስሜታቸውን በማጤን ልቧ ውስጥ ለየት
ያለ አዲስ ስሜት ሲያብብ ተሰማት እና የእሷም ልብ እንደ እሳቸው ልብ ወደ ፍቅር በመዳህ ላይ ሳለ መንገድ ላይ ተገናኙ።

የዘመን መለወጫ በዓል ሲከበር፡ ዮናታን እዚያው ሐኪም ቤት ውስጥ
#ሰመመን


#ክፍል_አርባ_አምስት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

አቤል ካምፓሱን በለቀቀ ማግሥት ሳምሶንም ጓዙን ይዞ ስለ ወጣ እስክንድር ፊቱን ወደ ዩኒቨርስቲው ማዞር አስጠልቶት ሦስት ቀን ያህል መኖሪያ ቤቱ ነበር የሰነበተው ። እዚያም ሆኖ የአቤልን ጉዳይ ለማስፈጸም ወዲያ ወዲህ
ማለቱ አልቀረም ። ብርቅነሽን አነጋግሮአት አቤል ያካፈላትን ምስጢር ለቢልልኝ እንድትነግራቸው አድርጓል ። መጀመሪያ ብርቅነሽ ፍርድ ቤት የመቅረብ ያህል ቆጥራው እምቢ ብላ አስቸግራው ነበር ። በብዙ ውትወታና ማሳመን ነው ወደ ቢልልኝ የወሰዳት ። ከእሷም ሌላ አቤል ቀድሞ በርቀት ካስተዋወቀው ሰዎች መሐል ለሥነ ልቡናው ምርምር ጥቂት
ይረዳሉ ብሎ የገመታቸውን ከቢልልኝ ጋር በመመካከር አነጋግሮአቸዋል ። እሱም እንደ ዮናታን በጓደኛው በአቤል ጉዳይ ውስጥ እጁን ማስገባቱና አንዳንድ ጠቃሚ ውጤቶች ማስገኘቱ አስደስቶት የበለጠ እንዲገፋበት እያደረገው
ነበር ።

በአራተኛው ቀን ወደ ካምፓስ ሲገባ ሁለት ሴቶች በጥብቅ ሲፈልጉት እንደ ሰነበቱ ድብርት ነገረው ። ቶሎ ሐሳቡ ውስጥ የመጣችበት ማርታ ነበረች ።

” ምን ዐይነት ሴቶች ? ” አለው ፡ ለማወቅ ቸኩሎ።

“ አንዷ ወፍራም ቀይ ፡ አንዷ መጠነኛ ወይም ሁለቱም አጭሮች ” ካለው በኋላ ፥ የነገሩትን ስም አስታውሶ ።ድብርት“ ቤተልሔምና ትዕግሥት የሚባሉ” አለው
“ አሃ ! ” አለ እስክንድር ። የተፈለገበት ምክንያት ምን እንደሆነ ለመገመት ጊዜ አልወሰደበትም ። ነገር ግን በጣም የጓጓው ስለ አቤል የሚቀርብለት ጥያቄ ከትዕግሥት ከራሷ አፍ ይወጣ እንደሆን ለመስማት ነበር ።
ሁለቱም በምሳ ሰዓት ወደ መመገቢያው አዳራሽ ሊገቡ ሲሉ አገኛቸው ።
በእግር በፈረስ ስትፈለግ የት ነው እንዲህ የጠፋኸው ? ” አለችው ቤተልሔም ።

በመኪና ብትፈልጉ ፡ ታገኙኝ ነበር ! ” ሁለቱም ሴቶች በቀልዱ ሣቁ ።

“ ማርታኮ ፡ ሔደች ! ” አለችው ቤተልሔም ሣቋን ገታ አድርጋ

“ የት?” አላት የደመ ነፍሱን ።

“ ወድቃ ፡ ትላንት ሻንጣዋን ይዛ ግቢውን ለቀቀች ። ”

"እና? እና እኔ ታዲያ እኔ ምኗ መሰልኳት የማርታን መርዶ የጨዋታ መክፈቻ የምታደርግልኝ ”አለ እስክንድር በልቡ ።

“ በራሷ ጥፋት ነው ” አለች ቤተልሔም ፡ ከእስክንድር መልስ ስታጣ ።

“ እንዴት ? ”

"ጸባይ የላትም ። ጸባይ ቢኖራት ኖሮ ህእ ! ” አለችው ፥ እንደ ሕፃን ልጅ ለምቦጭዋን ጥላ ።

“ ጸባይ ወይስ ጭንቅላት ?” እለ እስክንድር በሐሳቡ ።ምን ለማለት እንደ ፈለገች ገብቶታል ። ወዲያው ትዝ ያለው
ማርታ ለማን አጥላልታ ያወራችለት ነገር ነበር ።

“ ያንተስ ጓደኞች ?” አለችው ትዕግሥት በድንገት ።ስለ አቤል ለማወቅ ካላት ጉጉት የተነሣ፥ ሌላውን ጨዋታ
ለስማት ትዕግሥት አጥታ ነበር ።

“ ሳምሶን ወድቆ ተባረረ” አላትና አቋረጠ
ቤተልሔም የሳምሶንን ስም ሲጠራ እሱ ራሱ አጠገቧ የቆመ ያህል ሽምቅቅ አለች ከፍርሀቷ ብዛት ተደብቃው ከርማ ግቢውን ለቅቆ መሔዱን ካረጋገጠች በኋላ ነበር
ከመኝታ ክፍሏ መውጣት የጀመረችው ።

እስክንድር የሳምሶንን መባረር ብቻ ተናግሮ ስለ አቤል ምንም ነገር ሳያነሣ ያቋረጠው ሆነ ብሎ ነበር ። ትዕግሥት
ደፍራ ትጠይቀው እንደሆን ሊፈትናት ፈልጎ ነበር ትዕግሥት ዐይን ዐይኑን አየችው የምትፈልገውን እንዲነግራት በዐይኗ ለመነችው ። ነገር ግን ከእስክንድር አፍ ጠብ ያለ ነገር ኣልነበረም ።

“አቤልስ ? ” አለችው ደፍራ ። ድምጿ ግን ድክምክም ብሎ ነበር።

እስክንድር ደስ አለው ። ትዕግሥት ለመጀመሪያ ጊዜ የአቤልን ስም በጓደኛው ፊት መጥራቷ በእርግጥም ትልቅ ለውጥ ነበር ። ደስታዊው ስላስደነገጠው ቶሎ መልስ አልሰጣትም ። እሱም ድምፅ እንደ እሷው እንዳይደካክም መጠ ንቀቅ ነበረበት ።

“ አበል እንኳ አልወደቀም ። ግን እሱም ካምፓሱን ለቅቆ ወጥቶአል ” አላት ።

እስክንድር ይህን ሲናገር ከትዕግሥት ፊት ላይ የጠበቀውን ለውጥ አልተመለከተም አቤል ግቢውን መልቀቁ ያስደነግጣታል ብሎ ነበር ። ነገር ግን ትዕግሥትም ሆነች
ቤተልሔም ለነዚህ ዜና እንግዳ አልነበሩም ። አቤል በዮናታን መኪና ሻንጣውን ጭኖ የወጣ ዕለት ነበር ያዩት ተማሪዎች ወሬውን ቀምመው ሲያራቡ ነው የሰነበቱት ። እና አሁን የትዕግሥት ጉጉት የአቤል መውደቅ ትክክለኛ መሆኑን
ማረጋገጥ ብቻ ነበር ።

“ ታዲያ ካልወደቀ ለምን ካምፓሱን ለቅቆ ወጣ ? " አለችወ ትዕግሥት በጥርጣሬ ።

“ በሌላ ምክንያት ነው ”አላትና እስክንድር ለአመላለስ ተቸግሮ ፡ “ ሰፊ ነው ነገሩ ፣ በቁም ጨዋታ የሚያልቅ አይደለም ” አለ።
አላመነችውም ፊቷ ላይ ጥርጣሬ አነበበ የተከፋው ገጽታዋ አቤል ወድቋል ብላ እንደ ደመደመች ይናገራል ።ይህ እስክንድርን ብዙ አላስጨነቀውም ጊዜውን ጠብቆ ሁሉን ነገር እንድታውቀው ይደረጋል ። ዋናው ነገር በሩ መከፈቱ ነውጅ የአቤልን ስም እንስታ በግልጽ መጫወት ጀምራለች።

"ግን ምን ይሆን ' ወይስ ማን ይህን ያደፋፈራት ?? ሲል አሰበ ።

ከደስታው የተነሣ ምሳውን በሚበላበት ጊዜ ጉዳይ እንዳለበት ሰው እየተጣደፈ ቶሎ ቶሎ ነበር የጎረሰው ምግቡን ቶሎ ጨርሶ ያንን ሰው የበዛበት አዳራሽ ለቅቆ ወጥቶ ብቻውን ከሐሳቡ ጋር እየተሣሣቀ ለመፈንደቅ ካልሆነ በስተቀር ፡ ሌላ የሚሔድበት ቦታ አልነበረውም ።

መኝታ ክፍሉ ገብቶ እንደ ወትሮው አጭር የቀን እንቅልፍ ለመተኛት ቢሞክርም አልሆነለትም ከውጭ ይዞት የገባው ደስታ ጠፍቶ ትካዜ ተጫጫነው ። ከክፍሉ ውስጥ አቤልንና ሳምሶንን ማጣቱ ቅር ቅር አሰኘው ወና ቤት ውስጥ የገባ ይመስል ሰውነቱን ቀፈፈው ። ለሚቀጥሉት አራት ወራት በዚህ ክፍል ውስጥ የሚያሳልፈው ሕይወት
በጣም ብቸኛ ሆኖ ታየው ። በእርግጥ አጠንቡ ድብርት አለ ግን ድምፁ ከማይሰማ ሰው ጋር እንዴት ይኖራል ?

ሳምሶን "ጉልቤው" መኝታ ክፍሉን ምን ያህል ያደምቀው እንደ ነበር የገባው አሁን ነው » እየፈሳም ሆነ እየዘለለ ወይም ድብርትን እያበሽቀ ክፍሉን ሕይወት ይሰጠው ነበር ። መቼም መለያየት ክፉ ነው» ፤ እንደዚያ የሚያበሽቀው ድብርት እንኳ ሳምሶን ሲባረር ተገላገልኩ አላለም
ከልቡ ነበር ያዘነላት እስክንድር እንደ ተጋደመ ስለ ሳምሶን ሲያስብ የተለያዩበት ቀን ትዝ አለው ። በሰላም አልነበረም የተለያዩት ።

ሳምሶን ሰው ሳያየው ተደብቆ ካምፓሱን ለመልቀቅ ከለሊቱ አስራ አንድ ሰዓት አካባቢ ዕቃውን ሲያሰነዳዳ እስክንድር ድንገት ከእንቅልፉ ባነነ ። ሆኖም አዝማሚያው ስለገባው እስከ መጨረሻው ልመልከት ብሎ ፊቱን ከአንሶላው ውስጥ ሳያወጣ ጭጭ ብሎ ያዳምጥ ጀመር። ሻንጣውን አዘገጃጅቶ ጨርሶ ሲወጣ በሩጋ ሲደርስ ከአንሶላው ውስጥ አሾልቆ ተመለከተውና ፡ “ ሳምሶን ! ” ብሎ በኃይለ ቃል ጠራው።

"ምነው ? ! ”አለ ሳምሶን ዘወር ብሎ ከቁጣ ባልተናነሰ ድምፅ ስለተነቃበት ተናዶ ነበር።

"ምን ሆነሃል ? ”

"መሄዴ ነው"

“ ታዲያ እንዲህ ነው እንዴ የሚኬደው ? ምነው ሳምሶን ? የተወሰነ ጊዜም ቢሆን በጓደኝነት አሳልፈናል ። ቻው ብለኸን በሰላም ሸኝተንህ ፥ ብንለያይ ምናለበት ? መውደቅ በአንተ አልተጀመረ ! ” አለው እስክንድር ፥ ሆድ ብሶት ።

“ ሸኝ አልፈልግም ! ያው ሰፈር እንገናኛለን” ! ብሉ ጥሎት ሔደ ።

ሰው ለምን ድክመቱን ለመሸፈን ሲል እውሬ ይሆናል?” አለ እስክንድር በልቡ ። በሳምሶን አልበሸቀበትም " እንዲያውም ፡ “ በዚህ በንዴቱ ሰዓት ምግብ ቢቀርብለት
እንደ ቀድሞው ይበላ ይሆን ? ” ብሎ አስቦ ሣቅ አለ ። “ ጥርሳሞች ! ” ሲል በሐሳቡ ታየው ።ሰው
👍1
#ሰመመን


#ክፍል_አርባ_ስድስት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

....ቢልልኝና ረዳቶቻቸው በስብሰባው አዳራሽ ቀድሞው ቦታቸውን ይዘዋል ። ከዩኒቨርስቲው አስተዳደርና ትምህርት
ክፍል በአቤል ላይ የተካሔዶውን የሳይኮሉጄ ጥናት እንዲያዳምጡ
የተጋብዙ፥ እንግዶች እየተንጠባጠቡ ገቡ

ዮናታን ፈገግታ በፈገግታ ሆነው አዳራሹ መግቢያ በር ላይ ከእስክንድር ጋር ቆመው ለእንግዶቻቸው ሞቅ ያለ ሰላምታ በመስጠት ላይ ይገኛሉ። እስክንድር ከዮናታ ግዙፍ ቁመና ስር ግብቶ አንድ ፍሬ ልጅ ይመስላል። እንግዶቻቸውን
አስገብተው ከጨረሱ በኋላ እነሱም ገብተው ተቀመጡ።

ቢልልኝ ንግግሩን ለመክፈት ተነስተው ጎሮሮአቸውን ሲሰሉ አዳራሹ ጸጥ አለ ።

“ እንግዶቻችን ፡ እንኳን ደኅና መጣችሁ የዛሬው አርዕስታችን በዐይን ፍቅር የተለከፈ ወይም የተጠመደ አንድ ወጣት ነው ። የሥነ ልቦና ጥናት ክፍላችን በዚህ
ወጣት ችግር ላይ አቅሙ በፈቀደ መጠን ጥናት አድርጎ ውጤቱን ይዞ ቀርቧል ። ”

እንግዶቹ መሐል ጥናቱ የተካደበት ወጣት ማን እንደሆነ የሚያቁ ስለነበሩ፥ በስሜታቸው ውስጥ ወጣቱን የማወቅ ጉጉት ያዛቸው ። አቶ መአምርና ዶክተር አጥናፉ እንዲሁም ሌሎች ከአሁን በፊት ዮናታን የአቤልን ጐዳይ ያናገሯቸው ሰዎች ቸል ያሉት ጉዳይ አድጎ እዚህ መድረሱ ሳያስደንቃቸውም ሳያሳፍራቸዉም አልቃረም የአንድ
ተማሪ የዓይን ፍቅር ችግር፡ ክብደት ተሰጥቶት ይህን ያህል መጠናቱ አስገርሞአቸው አዳራሹ ወስጥ እንዲያው ለትዝብት የተቀመጡም አልጠፉም

በመጀመሪያ ለዚህ ተማሪ ግላዊ ችግር አትክሮትና ክብደት ሰጥተውት ሳይታክቱ ጥረት በማድረግ ለደከመለት
ለፍልስፍና መምህር ዮናታን ምስጋና እንዳቀርብ ይፈቀድልኝ ። ”

”ሞቅ ያለም” ባይሆን ድጋፉን የሚገልጽ መጠነኛ ጭባ ጨባ ሲሰማ ፥ ዮናታንም ሳያስቡት ለራሳቸው እያጨበጨቡ
ነበር ።

ዮናታን በዕውቀቱ የሚተማመኑበት ጎበዝ ተማርያቸው ሲደክም ወይም ሲሰንፍ እያዩ ቸል ቢሉት ኖሮ የአቤል ውስጣዊ ችግር ተዳፍኖ ውጤቱ ከዩኒቨርስቲው መባረር ነበር በዚህም ሆነ በሌላ ተመሳሳይ ችግር ከአሁን በፊት በርካተታ ጎበዝ ተማሪዎች በአጭር እንደ ቀሩ ጥርጥር የለውም።

በመደበኛ ተማሪነት ወደ ዩኒቨርስቲያችን ከሚገቡት መሐል አብዛኛዎቹ ወጣቶች ናቸው ። ጥሩውንና ገንቢውን ነገር በፍጥነት እንደሚቀበሉ ሁሉ ፥ ለአደጋና ለአፍራሽ ነገሮችም በቀላሉ ይጋለጣሉ። ቀዩኒቨርስቲያችን በተካሔው የሳይኮሎጂ ጥናት ወሠረት የተማሪዎች ዋነኛ ችግር፥
ሦስት ናቸው ። አንደኛ ፡ ወላጆቻቸው ችግረኞች በሆኑ ተማሪዎች ላይ የሚታየው የኢኮኖሚ ችግር ነው ። ይኸው ችግራቸው እያስገደዳቸው የዩኒቨርስቲ ትምህርታቸውን እያቋረጡ የወጡ ተማሪዎች አልጠፉም ። ሁለተኛ ፡ የማርክ ወይም የደረጃ ችግር ነው ። ማንኛውም ተማሪ አነስተኛ ውጤት ማግኘት አይፈልግም ። ነገር ግን ፉክክር እስካለ ድረስ መበላለጥ አለ ። ይህን ሐቅ መቀበል አቅቷቸው ፥ ወይም ለጥናት
የሚያደርጉት ጥረትና የሚያገኙት ውጤት አልገጣጠም እያላቸው ከራሳቸው ጋር የሚጣሉም ሞልተዋል ። ሦስተኛ
በሁለቱ ትርጉም ጾታዎች ግንኙነት ላይ የሚታየው ችግር ወይም በድፍን ፍቅር ” እየተባለ የሚጠራው ነው ።

ዛሬ ይዘን የቀረብነው በዚ በሦስተኛው ችግር የተጠመደ ወጣት አርዕስት ነው። ወደ ወጣቱ ጉዳይ ከመግባታችን በፊት ፍቅር የሚለውን ቃል ለማተት እንገደዳለን
እዚህ ላይ የማተኩረው በሁለቱ፡ ጾታዎች መካከል ዕድሜን ተከትሎ የሚመጣው ፍቅር ላይ ነው ።

“ ፍቅር በልባችን ውስጥ ታላቅ ቦታና ክብደት ያለው :ከልባችን ወጭ ግን የሚገባውን ክብደትትና አትኩሮት የነፈግነው ጉዳይ ነው ብል ማጋነን አይመስለኝም » አንድ ፈላስፋ እንዳለው ፥ ዓለምን የሚያንቀሳቅሷት ፍቅርና ረሃብ
ናቸው አንጋፋው ሳይኮሎጂስት ፎሮይድ የፍቅርን ክብደት ሲገልጽ ጥሳቻ ማለት ሞት ነው ፍቅር ደግሞ ከጥላቻ የጠነከረ ነው እናም ፍቅር ከሞት ይጠነክራል ማለት ነው” ይለዋል ። በመሠረቱ ጤናማ የሆነና ጤናማ ያልሆነ የፍቅር ዐይነት አለ ሌላው የሥነ ልቡና ጥናት ሊቅ ሆርኒ
እንደሚለው ጤናማ ያልሆነው የፍቅር ፍላጎት ጠንክሮ ሊገለጽ የሚችለው ለፍቅር ባለን ከመጠን ያለፈ ግምት ነው ።

“ ለመሆኑ ፍቅር ምንድን ነው ? ከባድ ጥያቄ ነው። አብዛኛዎቻችን ፡ፍቅር ዕውር ነው” እንላለን ። ነገር ግን ፍቅር ዕውር አይደለም። ፍቅርን በግድ ዕውር የምናደርገው እኛው ነን ። ወይም በፍቅር ላይ ዕውራኑ እኛ ነን ለማለት እደፍራለሁ ። ይህም ራሱን የቻለ ምክንያት አለን ። የባህል ኋላ ቀርነታችን ፍቅርና ወሲብን ውስጥ ውስጡን እንድናደርጋቸው እንጂ በአደባባይ እንዳንወያይባቸውም። ስለሚያፍነን ?ወይም ከልጅነታችንና ከዝቅተኛ ክፍል ጀምሮ በትምህርት
መልክ ስለማይሰጥ ይመስለኛል ዕውር የሚሆንብን ። አሁንም ሌላው ሳይኮሎጂስት አንግያል እንዲህ ይላል ። “እውነተኛ ፍቅር ዕውር አይደለም ፤ እንዲያውም ዐይናማ ነው ሌሎች የማያዩትን ያያል ። ”

“በርካታ የሥነ ልቡና ጥናት ሊቃውንት ለፍቅር በቅርጽ የተለያየ በይዘቱ ግን የተቀራረበ ትርጓሜ ሰጥተውታል ።
ይሁንና አብዛኛዎቹ “ ፍቅር መተሳሰር ነው በሚለው የተስማሙ ይመስላል ። ሆርኒ እንደሚለው ፍቅር ራስን በግብታዊነት ለሌላው የመስጠት ችሎታ ነው ። ከአብዛኛው የቀን ተቀን ገጠመኛችን እንደምንረዳው ፍቅር የመላማመድም
ውጤት ነው ።

ይህ እንግዲህ በጥቅሉ ለፍቅር ያለን ግምት ነው ።ወደ ዋናው አርዕስተ
ነገራችን ስንመጣ ፥ አቤል የተጠመደው
በዐይን ፍቅር ሆኖ እናገኘዋለን ።

ከተሳታፊዎቹ መሐል አንድ ሰው እጁን ሲያወጣ አይተው ቢልልኝ ንግግራቸውን አቋረጡ ሰውየው ይቅርታ ጠይቆ ጥያቄውን ቀጠለ “ የዐይን ፍቅር የሚለው አርዕስት እንግዳ ነው የሆነብኝ ። ደሞም ለፍቅር ከተሰጠው ሐተታ ጋር የሚጋጭ መስለኝ ። እና በመጀመሪያ ይህንን ሊያብራሪልኝ ቢችሉ።

ጠያቂዉ እጅ ነሥቶ ተቀመጠ ቢልልኝ ቀጠሉ "

“ወደያዚያ ልመጣ ነበር ። በእርግጥም የዓይን ፍቅር ለብዝዎቻችን እንግዳ አርዕስት እንደሚሆን እገምታለሁ ።
በሌላ ስያሜ ፤አስቸጋሪ በመሆኑ ነው በዚሁ ሰም መጥራት የተገደድነው። ወይነቱ የደመ ነፍስ ፍቅር ነው ። አንድን
ነገር አይቶ መወደድ ስሜት ልብ ሲደንግጥ ማንኛውም ዐይነት ፍቅር የሚጀምረው ከዐይንኮ ነው ያላዩት
ሀገር አይናፍቅም ” ይባል የለ ! አይተው ሳያልሙ መላመድ ሆነ መተባበር አይኖርም የሚወዱት ነገር ዓይን ውስጥ ከተቀረጸ በኋላ ነው መተሳሰሩ የሚቀጥለው ። ነገር ግን አይቶ በመውደድ ስሜት ልብ የደነገለጠለት ሰው ተቀራርቦ በአካልና በመንፈስ መተሳሰሩ ቀርቶ በዐይን ልማድ ላይ
ብቻ ሲወሰን ፥ ከዐይን ፍቅር የተሻለ ስያሜ እናገኝለትም።

ይህ ዐይነቱ ሁኔታ” ነው በአቤልና በወደዳት ኮረዳ መሐል የታየው በጥናታችን እንደደረስንበት
አቤል ትዕግሥት አዳነ የምትባለዋን የመጀመሪያ ዓመት ተማሪ አይቶ ልቡ ውስጥ ከቀረጻት ጀምሮ እነሆ ለአራት ወራት ያህል ያለ አንዳች የተቀራረበ ግንኙነት በዐይኑ ብቻ ወዶአታል ።
በቅርቡ ለውጡን ከተከታተሉት ሰዎች መረዳት እንደቻልነው አቤል ትዕግስትን ቀርቦ ባያነጋግራትም ፥ ቀጥተኛ
የአፍቃሪ ስሜት ይታይበት ነበረ ። በቂ ያለመብላት እንቅልፍ ማጣት ትምህርቱን መጥላትና ብቸኛ መሆን በዐይን ፍቅር ከተጠመደ ወዲህ ያሳያቸው የጸባይ ለውጦች ናቸወ፡፡ ልጅቷን ሳያያት ውሎ መደር፤ አይችልም ። ነገር ግን ይህን እይታውንም ሆነ ውስጣዊ መውደዱን ሰው እንዳያውቅበት በመጠንቀቅ ብቻውን ተሰቃያቷል ። ደረጃው ይለይ እንጂ ትዕግሥት ራሷም ከቀን በኋላ የዐይን
👍1
#ሰመመን


#ክፍል_አርባ_ሰባት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

“ሕመሙ በአቤል ላይ ሊጠነክርበት የቻለው ፍቅሩ ከዐይን ባለማለፉ ነው የሚል ግምት አለን ። የዐይን ፍቅር
የሚጠነክርበት ምክንያት የወጭውን ወይም ያጓጓውን ክፍል ብቻ ስለሚወድ ነው ። ተቀራርቦ ውስጣዊ ገጽታዎችን የሚተያዩበት አፍላ ፍቅር የሕመም ኃይሉ ሊቀንስ ይችላል ፤ ምክንያቱም በሰዎች መልክም ሆነ ባህርይ ፍጹምነት የለምና ነው ። ለዐይን ፍቅር አቤል የመጀመሪያ ሰው ኣይደለም ። ችግራቸው አድጎ እንዲህ አደባባይ ባይወጣም የዚህ
በሽታ ምርኮኞች ጥቂት አይደሉም ። መልካሙ ተበጀ
“ ሰላምታ ኣልሰጠኋት # አላነጋገርኳት ፥ በዐይን ብቻ እያየሁ አንድ ዓመት ወደድኳት ”” እያለ የሚጫወተው ዘፈን
በብዙ ሰዎች መወደዱና በዘፈን ምርጫ ፕሮግራም በተደጋጋ መቅረቡ ችግሩ በጥቂት ሰዎች ብቻ ያልተወሰነ መሆኑን
ያስገነዝበናል ።

ቢልልኝ ንግግራቸውን አቋርጠው ለጥያቄ ፋታ ሰጡ ።ነገር ግን ሁሉም በተመሳሳይ ከማዳመጥ በቀር ለጥያቄ እጁን
ያወጣ አልተገኘም ።

“ መልካም ! ” ሲሉ ቀጠሉ ቢልልኝ ፣ “ የእቤል ፍቅር ከዐይን ያላለፈበትንና ስሜቱን ደብቆ በግሉ የሚሰቃይባቸውን ምክንያቶች በመጠኑ አይተናል ። እስቲ ደግሞ የትዕግሥት መልክ ወይም ቁመና አቤልን እንዴት ሳበው ?ወይም ትዕግሥት አቤል ዓይን ወሰጥ እንዴት ልትገባ
ቻለች ? የሚለውን ነጥብ እናያለን ። ለዚህ ጥናት እንዲረዳን የትዕግሥትን ፎቶግራፍ ወስደን ከአቤል የሕይወት ታሪክ ጋር ለማስተያየት ሞክረን ነበር ። ሆኖም ፥ በአገራችን የሥነ ልቡና ጥናት አሁን ካለበት ዝቅተኛ ደረጃና የኢኮኖሚ
ችግር አንጻር አቤል ከጎንደር ሕይወቱ ጀምሮ የተቀራረባቸው ዋና ዋና የሴት ምስሎች ማግኘት አስቸጋሪ ሆኖብናል ። በጎንደር ዉስጥ አንድ ዋርካ ሥር አዘውትረው ን ይገናኙ የነበሩ ሁለት ፍቅረኞች በአቤል የልጅነት ጭንቅላት
ውስጥ ከፍተኛውን ቦታ ይዘው ይገኛሉ ። ምናልባትም የልጅቷ መልክ ወይም ቁመና ከአሁኗ ትዕግሥት ጋር የሚመሳ
ሰልበት አለ የሚል ግምት አለን ።
አቤል አንድ ቀን አብሯት ላደረው ሴትኛ አዳሪ እንዳጫወቻት

(ይህን ስታነቡ የተሰማቹ ስሜት እኔንም ተሰምቶኛል ግን በጊዜው ችግር አልነበረውም መሰለኝ)

ከሆኔ ፥ ትዕግሥትን ከዱሮ ጀምሮ የሚያውቃት ይመስለዋል ። ነገር ግን አቤልና ትዕግሥት በተለያየ ክፍለ ሀገር ስላደጉ፡የቆየ ትውውቅ ሊኖራቸው አይችልም ።ቁም ነገሩ፡የእሷን የመሰለ መልክ ከልጅነቱ ጀምሮ ሳያስበው
ጭንቅላቱ ውስጥ ተቀርጾበታል ማስት ነው ። ፎሮይድ እንደሚለው ፍቅር የሚጀምረው በልጅነት ነው ። በልጅነታ
ችን የምናፈቅረውና የምንፈልገው ሰው በጭንቅላታችን ውስጥ ተደብቆ እድጎ ነው- በጉልምስናችን ጊዜ ምርጫችን
የሚሆነው ። የመልክ ወይም የውበት ማነጻጸሪያችንም የሚመሠረተው ባደግንበት አካባቢ ዓይን ነው ። በሀገራችን በተዘዋዋሪም ቢሆን ይህን ሐቅ የሚያንጸባርቁ አንዳንድ አባባሎች አሉ ። ለምሳሌም ፥ ባልና ሚስት ከአንድ ዉሃ ይቀዳሉ ” ሲባል በሁለቱም ውስጥ ተቀርጾ ያደገና ተግናኙ በኋላ የዳበረ ተመሳሳይ ስሜትና ምርጫ መኖሩን ያሳያል ። ሌላው ደግሞ ፡ የ እናትህን የመሰለች እስክታገኝ ሚስት አታገባም ” የሚለውም አነጋገር የሚያሳየን የውበት ማነጻጸሪያዎቻችን ከልጅነት ጀምሮ ጭንቅላታችን ውስጥ የሚቀረጹት ወላጆቻችን ወይም ሌሎች በአካባቢው
በቅርብ የምናገኛቸው ሰዎች መሆናቸውን ነው ።

“ ጀርመናዊው ፈላስፋ ሾፐንሀወር የፍቅረኛ ምርጫን በሚመለከት እንዲህ ብሎ ነበር “ ለፍቅር ምክንያት ከሚሆነው ነገር ዘጠኝ አሥረኛው በአፍቃሪው ወስጥ ያለ ነው። አንድ አሥረኛው ምናልባት በተፈቃሪው ላይ ይኖር ይህናል ። ” ይህም የሚያሳየን አንድ ሰው አፍቅሮ የሚመርጠው ራሱኑ ወይም በውስጡ ያለውን ስሜት እንጂ ከውጭ
አለመሆኑን ነው ። ለማንኛውም ይህ የአፈቃቀር ሁኔታ ለእኛ እንጂ ለአቤል ችግር የለውም ።

ዐይን አይከለከልም : አቤል አይቷል ። መውደድ አይከለከልም ፡ ያያትን ወዷል ። ነገር ግን ፥ ፍቅሩ በዐይን በመወሰኑ ማስደሰቱ ቀርቶ ትርፉ ሕመም ሆኖበታል
እና አሁን እንዴት እንርዳው ነው ጥያቄው ዮናታን አቤልን ለመርዳት በግላቸው ብዙ ጥረዋል ። ከትዕግሥት ጋር አሁን ያለበት ሁኔታ ጤናማ መልክ እንዲይዝ ለማድረግ
ከተቻለ እኛም ከመርዳት ወደኋላ አንልም ሆኖም በትምህርቱ ረገድ ለሚኖረው ችግር የአካዳሚክ ኮሚሽኑን ርዳታ
እንጠብቃለን አቤል በልጅቷ ፍቅር ከተጠመደበት ጊዜ ጀምሮ ፡ “ ትምህርቱ ላይ በጤናማ አዕምሮ ላለመቀመጡ
በርካታ ማስረጃዎች አሉ ምግብ አዳራሽ ውስጥ ከተማሪው መሐል ወድቆ ታሟል፤ በአእምሮ ንክነት ሳይኪያትሪስት ድረስ ተወስዶ ታክሟል " እኚህንና የመሳሰሉትን ማስረጃዎች በመደገፍ አቤል በዚህ ሴሚስተር የተከታትላቸው ኮርሶች ተሰርዘውለት በሚቀጥለው ዓመት እንደገና እንዲጀምራቸው የአካዳሚክ፦ ኮሚሽኑን ፈቃድ እንጠይቃለን ።

“ በእኛ በኩል ያለው ዝግጅት ይኸው ነው አስተያየትም ሆነ ጥያቄ ካለ መድረኩን ለሌሉች እለቃለሁ ። ”

ቢልልኝ ጨርሰው ከተቀመጡ በኋላ ፡ ለተወሰኑ ደቂቃዎች ያህል ከጎን ለጎን መወያየት ያለፈ ጥያቄ አልነበረም
ዮናታን ተነሥተው አሁን አቤል ያለበትን ሁኔታና ከእሳቸው ጋር ለተወሰነ ጊዜ እንዲኖር መወሰናቸውን ለስብሰባው
ገለጹ " ይህ ሁኔታ የብዙዎቹን ስሜት ለእርዳታ ገፋፍቶ ነበር ዮናታንን ተከትሎ አንድ ሌላ ሰው ለመናገር ተነሣ ።

“ ትንሽ ነገር እንድናገር ይፈቀድልኝ " በእውነት ይህ ጉዳይ አትኩሮት ተሰጥቶት ለዚህ መድረክ መቅረቡ ደስ ያሰኛል እኔ እስከማውቀው ድረስ ጎበዝ ተማሪዎቻችን
በፍቅርም ሆነ በሌላ ማኅበራዊ ችግር እየተደናቀፉ ትምህርታቸውን ሲያቋርጡ እስካሁን ዩኒቨርስቲያችን ብዙም
ትኩረት አልሰጣቸውም ። አንድ ተማሪ ያፈቀራት ልጅ ገድሎ ጓደኛውንም ለመግደል ሲፈልግ ሌላው ሲያብድ
የሥነ ልቡና ጥናት መሰሉችም ሆኑ ዩኒቨርስቲው በቸልታ ነው የተመለከቱት ። ወይም ድርጊቶች ከተከናወኑ በኋላ
ዜናውን ከማድነቁ ላይ ነው የተተኮረው ። ለመሆኑ ፡ ጎበዝ ተማሪያችን በትምህርቱ ሲደክምና ደረጃው ሲቀንስ ያገኘውን ሰጥተን ባወጣ ያውጣህ ከማለት በቀር ተማሪውን በግል ጠርተን ለማጤን ወይም ችግሩን ለማማከር የሞከርን ስንቶቻችን ነን ? ይህ ለማንም መምህር የሚከብድ ርዳታ አይደለም ። ! የሚያሳዝን ቸልተኝነት ያለብን ይመስለኛል አሁን ግን መልካም አጀማመር ነው የታየው ። እንግፋበት እላለሁ ። እኔም ማንኛውንም ዐቅሜ የሚፈቅደውን ርዳታ ለማድረግ ከጎናችሁ እቆማለሁ ። ”

ሰውየው ከኋላ ስለነበር፡ ዮናታን ዘወር ብለው በአድናቆት ተመለከቱት ። እንግዳ አልነበረም ። እዚያው ግቢ የታሪክ መምህር ነው ። “ ወይ ልብ ለልብ አለመተዋወቅ ! አሉ ዮናታን በሐሳባቸው

ቢልልኝ የሰውየው ሐሳብ የግድ እንዲናገሩ ገፋፋቸው ። መልካም ነው ። ድጋፍህን ተቀብለናል ። ሆኖም እዚህ ላይ መታወቅ ያለበት የእኛ ዓላማ የሚያተኩረው ግለሰቦችን በማስታመም ላይ ሳይሆን ችግራቸውን ወስደን አጠቃላይ መፍትሔ ከመፈለጉ ላይ ነው ። ይህ ደግሞ በዩኒቨርስቲያችን ውስጥ ብቻ ሳይሆን ፥ ከዚህ ውጭም መጠናትና መታሰብ ያለበት ነገር ነው ። የዩኒቨርስቲው አባላት ከማኅበረሰቡ የወጡ ናቸው ። ችግሩንም ይዘው የሚመጡት ከማኅበረሰቡ ነው ። ለምሳሌ ፥ በየአካባቢውና በየትምህርት ቤቱ ፍቅር በማኅበራዊ ኑሮ ክፍልነቱ ግልጽ ተደርጎ ትምህርት ቢሰጥበት ፡ ሁለቱም ጾታዎች መፋቀሪያ ጊዜያቸው ላይ ሲደርሱ እንዲህ ዐይነት ችግር አይገጥማቸውም ግልጽና ጤናማ ዜጋ ለማፍራት ከአካባቢው ከሥር ከመሠረቱ ነው
#ሰመመን


#ክፍል_አርባ_ስምንት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

...ዮናታን ቤታችው ሲደርሱ፥ ሞኒካ የስብሰባውን ሁኔታ ለመስማት ጓጉታ በሕንፃው መናፈሻ በኩል ቁልቁል እየተመለከተች መምጫቸውን በመጠባበቅ ላይ ነበረች ።

“ እንዴት ነው ? ” አለቻቸው ፡ ከፊቷ ላይ የማይጠፋ ፈገግታዋን ብልጭ አድርጋ "

“ ደስ የሚያሰኝ ስብሰባ ነበር " በብዙ ሰዎች ላይ ቀና ስሜት አሳድረናል” አሏት፡እጅዋን ይዘው ወደ ውስጥ እየገቡ ጥናቱንም ቢልልኝ በጥሩ መልክ አቅርበውታል የጥናቱን ጽሑፍ ከእሳቸው ተውሼ ሰሞኑን አመጣልሻለሁ”

ሞኒካ ስብሰባው ላይ ለመገኘትና በአቤል ላይ የተካሔደውን ጥናት ለማዳመጥ ከፍተኛ ጉጉት ነበራት ጥናቱ የቀረበው በአማርኛ ስለ ነበር በደንብ የማትሰማው ቋንቋ ሆኖባት ነው የቀረችው።

“ አካዳሚክ ኮሚሽኑስ ምን አለ ? ” ስትል ጠየቀቻቸው "

“ የእነሱ መደበኛ ስብሰባ ገና ከአራት ቀን በኋላ ነው ።ሆኖም ስብሰባችን ላይ የነበሩት የኮሚሽኑ አባላት በግል ተስፋ ሰጥተውኛል ። እና ጥሩ ውጤት እጠብቃለሁ ።

ዮናታን ከሚስታቸው ጋር እያወሩ ልባቸው አቤልን ለማየት ጓጉቶ ነበር • ሳሎን ውስጥ ሲያጡት የት እንዳላ
ለማወቅ ሞኒካን መጠየቅ አላስፈለጋቸው? በቀጥታ ወደ መጻሕፍት ክፍላቸው ሔዱ ። በሩን በዝግታ ከፍተው
ሲገቡ'አቤል በሚያነበው መጽሐፍ ክፉኛ ተመስጦ አገኙት ።
ሊረብሹት አልፈለጉም ። በሩን በዝግታ ዘግተው ለመመለስ ቢያስቡም እጃቸው የበሩን እጀታ መጎተት አልቻለም ለአቤል አንዳች ነገር ሊነግሩት ፈለጉ ። ቀን ምን እንደሚነግሩት ወይም ደስታቸውን እንዴት እንደሚገልጹለት አያውቁም ነበር። አቤል በእሱ ጉዳይ ስብሰባ መካሔዱን አያ
ውቅም ። ጉዳዩ ክብደት ተሰጥቶት አደባባይ መቅረቡ በአንድ በኩል ሊያስደስተው ቢችልም በሌላ በኩል ደግሞ የሚደብቀው የዐይን ፍቅር መጋለጡ ስሜቱን ሊጎዳው ስለሚችል፥ ይህን በማመዛዘን ዮናታን ሆነ ብለው ነበር ያልነገሩት አሁንም ይህን ሊነግሩት አልፈለጉም። እንዲሁ ብቻ በፈገግታ የደስታ ስሜታቸውን ሊያስተላልፉለት አሰቡ ።

ወደ ውስጥ የጫማቸው ድምፅ አቤልን ከተመሰጠበት አባነነውና ካቀረቀረበት መጽሐፍ ቀና አለ ። ፈገግታቸውን
ሲያይ ፡ ምን አገኙ ይሆን ? ብሎ አልተደነቀም ። ንባብ ላይ ተቀምጦ በማግኘታቸው የተደሰቱበት መሰለው ።
“ እንደምን ውለሃል ? ” አሉት ፡ እንዲህ የሳበው መጽሐፍ ምን እንደሆነ ለማወቅ ዐይናቸውን ወደ ርዕሱ እየወረወሩ
ደኅና ፡ ሲገቡ አልሰማሁዎትምኮ ” አላቸው ፡ የደረሰበት ገጽ እንዳይጠፋው ማዕዘኑ ላይ እያጠፈ ።

የሚያነበው “ ማን አገንስት ሄምሰልፍ ! ” “ ሰው ራሱን ሲጻረር ! የሚለው የዶክተር ሜኔንገር መጽሐፍ ነበር " ዮናታን ይህን አርዕስት ሲያዩ ደነገጡ ። ካልጠፋ
መጽሐፍ ይኽን ለምን መረጠው ? የሚል ጥርጣሬ አደረባቸው፤ፈገግታቸው በአንድ አፍታ ጠፋ ። ፈጥነው ሊጠይቁት ግን አልደፈሩም ። ከውጭ ይዘውት የመጡት የደስታ ስሜት ከውስጥ ጥቀርሻ ሲለብስ ተሰማቸው ።

“ ወደ ውጭ ወጣ ብለን እንናፈስ ? ዛሬ ንባብ ላይ ብዙ የቆየህ ይመስለኛል ” አሉት ' ስሜቱ በመጥፎ ነገር ተወጥሮ ከሆነም ወጣ ብሎ መናፈሱ ይሻለዋል በሚል ግምት ።

“ በደስታ!” አላቸው ከተቀመጠበት እየተንጠራራ ።

አመላለሱም ሆነ የፊቱ ብርሃን ከውስጡ መጥፎ ስሜት የወጠረው ሰው አይመስልም ። ዮናታን በግምታቸው ግራ
ተጋቡ ።

ሊብሊንግ ፡ ሽርጥሽን አውልቂና ወጣ እንበል ”አሏት ሚስታቸውን ወደ ሳሎኑ ተመልሰው ።

ሞኒካ ቤት ውስጥ ከሆነች ከወገቧ ነጭ ሽርጥ አይጠፋም።

“ አቤልስ ይመጣል ? ”አለቻቸው ፈቃደኛነቱን ለማረጋግጥ ።

“ አዎ ፡ እወጣለሁ ብሏል ” አሏትና " ወደ ጆሮዋ ጠጋ ብለው ፥ የዛሬ ውሎው እንዴት ነው ? ” አሏት ፡

የመጽሐፉ አርዕስት እየከነከናቸው ነበር
“ ደኅና ነው የዋለው ። እንዲያውም ንባብ ከመጀመሩ በፊት እሱ ባደገበት አካባቢ ያለውን የጋብቻ ሥነ-ሥርዓት ሲያጫውተኝ ነበር ” አለቻቸው ሽርጧን እየፈታች ።

ዮናታን ውጭ ወለው ቤት ሲገቡ ስለ አቤል ሁኔታ መጠየቅ ልማዳቸው ነበር ። አቤልም ዮናታን ቤት መኖር ከጀመረበት ጊዜ አንሥቶ ያሳየው ለውጥ ቀላል አልነበረም » እብሯቸው ሲኖር ሳምንት ሆኖታል ። ከእራሱ ጋር መታረቅ ጀምሯል ለውጡ የሞኒካ የድካም ውጤት ነው
ማለት ይቻላል ።

ለመጀመሪያው ሁለት ቀን አቤል ራሱን ገዝቶ ቤት ውስጥ መቀመጡ በጣም አስቸግሮት ነበር " ትዕግሥት በሐሳቡ
እየመጣችበት ብረር ብረር ይለው ነበር ። ሲጠላው የነበረው ዩኒቨርስቲ ይናፍቀዋል ትንሽም ቀለል የሚለው እስክንድር መጥቶ አጫውቶት ሲሔድ ነበር ።

ዮናታንና ሚስታቸውም ይህን ችግሩን ሳይረዱለት አልቀሩም ። ሐሳቡን ከትዕግሥትም ሆነ ከሌላ መጥፎ
ስሜት ለማዘናጋት የተጠቀሙበት ዘዴ መንፈሱ ለሥራ መወጠር ነበር ለቀን ተቀን እንቅስቃሴው ፕሮግራም
አውጥተውለታል ። ሞኒካ ምግብ በምታበስልበት ሰዓት አብሯት ሆኖ የምግብ አሠራሯን እያጠና በአንዳንድ
ማኅበራዊ አርዕስቶች ላይ ይወያያሉ በቀን የተወሰነ ሰዓት እሷ ጀርመንኛ ታስተምረዋሶች ። እሱም በፈንታው
ለተወሰነ ሰዓት አማርኛ ያስተምራታል ። ይህ አቤል ከመምጣቱ በፊት የዮናታን ሥራ ነበር ። ስለዚህ ማታ ማታ ሞኒካ ቀን የተማረቻቸውን አንዳንድ አዳዲስ የአማርኛ ቃላት ስትናገር፥ ዮናታን ወደ አቤል እየመተለከቱ ፥ ጥሩ ረዳት አገኘሁ እንዲያው ከኔ የተሻለ ዘዴ ሳይኖርህ አይቀርም ” በማለት ይክቡታል ። በመጀመሪያ ለንባብ የተመደበለት የተወሰነ ሰዓት ነበረው ውሎ ሲያድር ወደ ንባቡ ፍቅር ሲመለስ ግን፡ለንባብ ከተቀመጠበት ስፍራ የሚነሣው .
በቀስቃሽ ሆነ ። ከንባብ ውጭ ለመዝናናት ያህል በቤት ውስጥ የሚያገኛቸውን የጀርመን ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ሥዕላዊ መግለጌ የያዙ መጻሕፍት ማገላበጠት በመንፈስ
ውስጥ የጥሩ ሕይወት ስሜት ያሳድርበት ነበር ። የሀገር ውስጥና የውጭ ሙዚቃ በሙሉ ጆሮው ሰምቶ ለማድነቅ
የቻለው በዚህ ሳምንት ውስጥ ነው ። ትርጉሙም ሆነ ጣዕሙ ሲገባው ያልቻለውና ዮናታን የሚያደንቁትና በተመስጦ ያሚያዳምጡት፡የእነ ቫግነርና ቤትሆቭን ክላሲካል ሙዚቃ ነው "
ቤት ውስጥ ሙዚቃ ማዳመጡ ቢያስደሰተውም አንዳንዴ ትካዜ ስለሚጫነው ፥ ለመቆጠብ ወይም ብቸኝነት በማያጠቃው ሰዓት ብቻ ለማዳመጥ ተግዶ ነበር ።

ቀን በዚህ ዐይነት ውሎ ወደ ማታ ላይ ሦስቱም ነፋስ ለመቀበል ወደ ከተማው ጸጥታማ ቦታዎች ብቅ ይላሉ ።
አሰልሠው ሲኒማ ይገባሉ ። ይህን የመሰለው የሕይወት እንቅስቃሴ አቤልን ከብቸኝነት ስሜቱ በማዘናጋት ሐሳቡ
አንድ ነገር ላይ ብቻ በማተኮር እንዳይሠቃይ ከፋፍሎታል ። ያም ሆኖ ትዕግሥትን እያሰበ ሳይጨነቅ አያድርም
ግን ጭንቀቱ እንደ ቀድሞው አልነበረም ፡ በሥራ በተወጠረ አእምሮ ወይም ደክሞ እንቅልፍ በፈለገ ጭንቅላት ስለሆነ የሚያስባት ፥ ያን ያህል አይረበሽም ።

አቤል ከብርቅነሽ ቀጥሎ በሕይወቱ የገጠመችው ግልጽ ሴት ሞኒካ ነች ። በአንድ ምሽት ዕድሜም ቢሆን
የብርቅነሽ ትሑትና ግልጽ ተፈጥሮ በልቡ ተቀርጿል ። ምናልባትም የብርቅነሽ ግልጽነት ከማይምነቷ ጋር የተያያዘ
የልብ ክፍትነትና የጥሬነት ውጤት ሊሆን ይችላል ። የሞኒካ ግልጽነት ግን ምሁራዊ ጥልቅ ትርጉምና ድምቀት አለው ። ከአኳኋኗ መረዳት እንደሚቻለው “የምንፈጽመው ጥሩም ሆነ መጥፎ ነገር የህልውናችን ነጸብራቅ ነው ፤ ስለሆነም
እኛነታችንን ደብቀን መሠቃየት የለብንም ፤ መጥፎ የምንለውን አምቀን ጥሩ የምንለውን ብቻ የምንተነፍስ ከሆነ
ውስጣችን ገምቶ ደማችን ይደፈርሳል የምትል ትመስላለች አቤል በቀላሉ ነው የተግባባት
👍4
#ሰመመን


#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

ከገና ማዕበል ያመለጠው ተማሪ፥ የዩኒቨርስቲ ውስጥ ዕድሜው መራዘሙን ካረጋገጠ በኋላ መረጋጋት ይታይበታል ። የሁለተኛው ሴሚስተር ትምህርት ቢጀመርም ገና ሞቅ ሞቅ ባለማለቱ አንገቱን መልሶ ቀለም ላይ የደፋ ተማሪ
እምብዛ!” ነው ። ሆኖም ፋታ ፈጥሮአቸው የነበሩት ቀልድ ፥ትችት።ውንጀላና ተረብ ተግ ብለዋል ።

ትዕግሥት ማጥናት አልጀመረችም ። የወረቀት ዘር ማየት ያስጠላት ትመስላለች ትምህርት ክፍሉ ውስጥ እንኳ ከመምህራኑ ገለጻ ሙሉ በሙሉ ማስታወሻ መውሰዷን ትጠራጠራለች ። ምክንያቱ አንዳንዴ ሐሳቧ እያመለጣት
ወደ ወጭ መብረር ጀምሯል ፤ በግልጽ ያልተከተላት ስሜት ሲፈታተናት ይሰማታል ከውስጧ አንዳች ነገር የጎደለ ይመስላታል። ምናልባት በቢልልኝ አገላለጽ ለፍቅር የተዘጋጀው ሥፍራ ሳይሆን አይቀርም የሚረብሻት ።

እቤል ሕመሙን አጋብቶባት እንደ ሄደ ለመገመት ብዙ ጊዜ አልወሰደባትም ። መኝታ ክፍሏ መግባት መውጣትም አስጠልቷታል ። ጸባይዋ ቢንቋሸሽም ፡ በመጠኑ ለምዳት የነበረችው ጓደኛዋ ማርታ ነበረች ። እሷ ከተባረረች ወዲህ በደንብ ቀርባ የምትጫወተውን የሴት ጓደኛ አላገኘችም ። ከቤተልሔም ጋር ዐልፎ ህልፎ ይገናኛሉ ። ሆኖም በግቢው ውስጥ የቤተልሔም ስም እየቆሸሽ ስለ መጣ ትዕግሥት አብራ እንዳትታማ በመፍራት ቀስ በቀስ እየራቀቻት
ነበር ። አቤል ግቢውን ለቅቆ ከወጣ ወዲህ ለዐይኗ ማሳረፊያ ያገኘችው ሰው እስክንድር ነው ፡ ሳታየዉ ወይም
አግኝታው የተለመደውን “ ታዲያስ ፥ ታዲያስ ” ሰላምታ ሳትለዋወጥ ውላ
አታውቅም ።

እስክንድርም ቢሆን፥የትዕግሥትን መግቢያና መውጪያ ሰዓት ጠብቆ ነው የሚገኛት ፥ ከመኝታ ክፍሉ ጠዋት
ሲወጣ ስለ አቤል ሁኔታ ፍርጥርጥ አርጎ አጫውቷት መፍትሔውን እንዲወያዩበት ሊለምናት ያስብና ፡ በሚያገኛት ጊዜ ልቡ ይከዳዋል ። በዮናታን ፊት የፎከረውንና እሷን ሲያገኛት ምላሱ መተሳስሩን ሲያመዛዝን ራሱን ታዘበው ።
“ አቤልስ ቢደነግጥላትም ቢፈራትም ወዷት ነው ፤እኔ ደግሞ ያሰብኩትን ልነግራት መፍራቴ ለምንድን ነው ? ” እያለ
ከራሱ ጋር መሟገቱ አልቀረም ። ግን ለእስክንድር አልታወቀውም እንጂ፥ ስለ አቤል ጠልቆ ሳያነሳባት ከትዕግሥት ጋር
ግንኙነቱን ማጠናከሩ ለዓላማው ጥሩ መንገድ አመቻችቶለት ነበር ። በአንዴ ነጥቡ ላይ ደርሶ ዱብ ዕዳ ከማውረድ ፥ ቀስ በቀስ አለማምዶ ከነጥቡ ላይ መድረሱን መልሱ የእሽታ እንዲሆን ይበልጥ ይረዳል ።

ትዕግሥትን ከአቤል ጋር ለማገናኘት አማራጭ መንገዶችን ዮናታንና ቢልልኝ ተነጋግረው ነበር ። ትዕግሥትን ድንገት ወስዶ አቤል ፊት ማቅረቡን ቢልልኝ አልደገፉትም ምናልባትም ካለፈው ልምዳቸው በመነሣት ሊሆን ይችላል።
አንዴ እንዲሁ ተመሳሳይ ችግር የገጠመው ተማሪ የሚፈልጋትን ልጅ አቅርበው እናስተዋውቅህ ሲሉት፡ ካልገደልኳት ብሎ የተጋበዘው ነገር ምንጊዜም አይረሳቸውም ። እና አሁን ያቀረቡት ሐሳብ በመጀመሪያ አቤል ስለ ትዕግሥት ቀና አመለካከት እንዲኖረው መኮትኮትና አጠገቡ ከመድረሷ በፊት በስልክ እንድታነጋግረው ወይም ደብዳቤ እንድትጽፍለት ማድረግ ነበር ። ደብዳቤ መጻፍዋ የተሻለ መንገድ ሆኖ ተመረጠ ። ይህን ለማስፈጸም በሙሉ ልብ ኃላፊነቱን
የወሰደው እስክንድር ነበር ። ታዲያ አሁን ተግባሩ ላይ ሲዲርስ የምን ወገቤን ያዙኝ ነው ?

ሲያምጥ ከርሞ፡አንድ ቀን እንደ ምንም ደፍሮ ሔደ ። ከመኝታ ክፍሏ አስጠራትና ፡ “ ለጥብቅ ጉዳይ እፈልግሻለሁ ” አላት ። በቆይታ የሚያወሩበት ቦታም ችግር ነበር
እነትዕግሥት ቀድሞ ያጠኑበት የነበረው ከዋናው ቤተ መጹሕፍት ጀርባ ያለው ዋርካ አካባቢ ታየው ። ግን ሁለታችንን
ብቻ እዚያ ዋርካ ሥር ሲያዩን ተማሪዎች ምን ይሉናል ? የሚል ሥጋት እደረበት በመጨረሻም ካወጣ ካወረደ በኋላ ሌላ ቦታ በማጣቱ “ ያሉትን ይበሉ ወደ
ዋርካው ሥር ይዟት ሔደ
እንዴት እንደሚጀምርላት ግራ ገብቶት ትንሽ ተጨነቀ። ግን ዝም ማለትም አልቻለም ። ዐይኖችዋ ውስጥ የጥያቄ
ምልክቶች ተደርድረው ያየ መሰለው ።

“ ሁለታችንም ሳንጠላው የምንሸሸው አርዕስት ነው አላት በድንገት ።

“ ምን ? ” አለችው ፥ ነገሩ ቢገባትም ከእሱው ይምጣ በሚል ስሜት ።

የእቤልን ነገር ሁለቱ በተገናኙ ቁጥር ዳር ዳር ሳይሉ ስለማይለያዩ አሁን ስለእሱ ሊያወራት መሆኑን ትዕግሥት አላጣቸውም ። ስሜቷን ደብቃ ነው እንጂ ወሬውን ለመስ ማት ቸኩላለች

ስለ አቤል በደንብ ላጫውትሽ ብዬ ነው ?” አላት ።

ፈቃደኛነቷን በአፏ ሳይሆን በዐይኖቿ ነው የግለጸችለት ።

አጫወታት ነው ረበሻት የሚባለው ? የለም ! ማጫወት ላይ ላዩን ሲሆን ነው ። ከሥር ከመሠረቱ ጀምሮ ልብን እያናጉ
መንፈስን እያወራጩ ፥ ቁስልን እየቀሰቀሱ ስሜትን እያንገላቱ የሚናገሩት ነገር፡ “ መረበሽ ” የሚለውን ቃል ቢይዝ ይሻላል ። እስክንድር እንደዚያ ነው ያደረገው ። ሳያስበው የእሱም ስሜት አርዕስተ ነገሩ ውስጥ ሰምጦ እየተንገላታ ስለ አቤል የሚያውቀውን ሁሉ ነገራት። እሷን ካየበት
ዕለት ጀምሮ በግሉ የተቀበለውን ሥቃይ አሁን የት እና በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ዘረዘረላት እያወራላት ገጽታዋን ገመገመ ከንፈሯ በቅጽበት ሲከስል ታየው ። ፊቷ በአንዴ ጠወለገ ። አዲስ ነገር ተናግሮ
አልረበሻትም ። አብዛኛው የምታውቀው ነገር ነው ። አብዛኛው ከአቤል ጋር አንድ ሴሚስተር ሙሉ በዐይናቸው የተለዋወጡት የጥናት ፥ የቁጣ ፥ የሥቃይና የእልህ ድምፅ አልባ
ግንኙነት ነው።

“ ታዲያ ጥፋተኛው ማነው ? ” አለችው ንግግሩን መጨረሱን ካረጋገጠች በኋላ
ዐይኖችዋ ያቀረሩትን ዕንባ ሲያይ ስሜትዋ ተጋባበት።ግን እሱ የማልቀስ ችግር አለበት ፤ዕንባው ቶሎ አይመጣለትም ።

ለፍርድ አስቸጋሪ ነው ። ሁለታችሁም ጥፋተኛች አይደላችሁም ። እየተፈላለጉ መራራቅን ፡ “ የፍቅር እንቆቅልሽ ” ብንለው ይሻላል ” አላት ።ዝም አለችው ። እሱም ዝም ብሎ ተመልከታት ። የአቤልን ስሜት ያደነዘዘውን የመልኳን ውበት ማጥናት ፈለገ ።ግን ከዳመነ ፊቷ ላይ ውበት ለማጥናት መሞከሩ አስቸጋሪ
ሆነበት ።

በረዥሙ ተነፈሰች የጭንቅ አተነፋፈስ ። የታባቱ !በሥቃይ የታመቀው አየር ወጣ ።

“ አሁን አንገብጋቢው “ ጥያቄ ጥፋተኛው ማነው?”ሳይሆን ፥ “ መፍትሔው ምንድነው ?” ይመስለኛል” አላት እስክንድር ።

“ ምን መፍትሔ አለው ? ” አለችው ፡ ተስፋ በቆረጠ ድምፅ።

“ አለው እንጂ ።አቤል ይወድሻል ፥ ይፈልግሻል ማወቅ የሚፈልገው ያንቺ ምላሽ ምን እንደሆን ነው ። ካንቺ
መረዳት እንደ ቻልኩት ደግሞ አንቺም ትፈልጊዋለሽ ፤ትወጂዋለሽ ። ይህን ስሜትሽን በደብዳቤ ብትገልጪለት
ችግሩ ይቃለላል ። ”

ደብዳቤ ”አለችው ; ሳይተዋወቁ የምትጽፍለት ደብዳቤ ምን እንደሚሆን ግር ብሏት ።

"አዎ ደብዳቤ !"

"ምን ብዬ ?"
“ በቃ ለእሱ ያለሽን ስሜት ነዋ ! ”

አሰበች ፤ደብዳቤ ። አዎ ጥሩ መንገድ ነው ስትጽፍ አጠገቧ የምታፍረው ወይም የምትፈራው አቤል አይኖርም ወረቀቱ ሳይ የምታሰፍራቸው ቃላት ፈንቅለዋት ማልቀስ ቢዳዳትም ማልቀስ ትችላለች ። ታዛቢ አይኖርባትም ። የምትጽፈው ነገር ከጭንቅላቷ ውስጥ እየፈለቀ ኣሁን አሁን
አሰኛት ።

“ ካልሆነም ረቂቁን እኔ ልጻፍልሽ ” አላት እስክንድር፡ ዝም ስትልበት ጊዜ የቸገራት መስሎት ።

ግድ የለም ፤ እኔው እሞክራለሁ ” አለችው ፥ በሐሳቧ የምትጽፍበትን ቦታ እየመረጠች ምቹ ቦታ የለም ።
የመኝታ ክፍል ጓደኞቿ ከተኙ በኋላ፥ ሌሊት ተነሥታ የመጻፍ ሐሳብ መጣላት ።

“ ጥሩ እንግዲህ ፥ ጸፊና ሰጪኝ ። እኔ አደርስልሻ
#ሰመመን


#ክፍል_ሃምሳ


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

....ለማንኛውም አሁን ከለማ ጋር ግንኙነታችን ተቋርጧል።

"በቃ?"

" አዎ " ከእንግዲህ በዚህ አይነት የምንቀጥል አይመስለኝም ። በእሱ የተነሣ ነው ፡ እንዲህ ስሜ የጠፋው ። ”

ሁለቱም ዝም አሉ። እስክንድር ለሁኔታው ያልተዘጋጀበት ሆኖ ነው ለአፋጣኝ ጥያቄም ሆና መልስ የተቸገረው።
ቤተልሄም ግን በዝምታው መርከብ ተሳፍራ ወደ ኋላዋ ከለማ ጋር የተጣሉበት ቀን ደርሳ ነበር።

የሁለተኛ ሴሚስተር ትምህርት ተጀምሮ ልማ ምንም ኮርስ እንደማያስተምራት ካረጋግጠች በኋላ ፥ ቤተልሔም ሸርተት ለማለት ትጀምራለች ። ጭራሹን ለአንድ ሳምንት ያህል ትሰወርበታለች።ለማ ልቡ ይጠረጥርና በዚያው ሳምንት ግቢ ውስጥ ፈልጎ ካገኛት በኋላ ፥ ቤቱ ድረስ እንድትመጣ ነብር ሆኖ ይቀጥራታል ።

"ምን ሆነሽ ነው እንዲህ የጠፋሽው!" እንደ ብራቅ ጮህባት።
"ስላልተመቸኝ ነው"
"ይህው ነው መልስሽ?" አላት በሽቆ።
ዐይኗን ሰብራ ዝም አለች ። አኳኋኑ አስፈራት ። ገላጋይ በሌለበት ባዶ ቤት ውስጥ የያዛት እንደሆን ማን ይደርስላታል ? ሽንቷ ወጠራት ።
"ምን መሰለህ ለማ" አለችው እንባ በተናነቀው ድምፅ ዬኒቨርስቲዉ ውስጥ ስሜን እያጠፉ ነው ። ከአንተ ጋር ባለኝ ግንኙነት ክፉኛ ታምቻለሁ ። ሰላም ይሉኝ የነበሩ ተማሪዎች ሁሉ ዘግተውኛል !
"እና ? ”
“ እና ለአንተም ስም ሆነ ለእኔ ይህን ግንኙነታችንን ብናቋርጠው ይሻላል ብዬ ነው። እኔ እዚያ ግቢ ውስጥ መኖር
እልቻልኩም ፡ ሰውነቴ አለቀ” አለችው ፡ ለቅሶ እየቃጣት
እንዲሁ ነች ። እስክንድርን ጠርታ ፥ “ ጓደኛዬ ሁን ” እንዳለችው መሆኑ ነው ። ብልጠቷ ስልት የለውም ። ይህ ስልት ያጣው ብልጠቷ ለማን አብከነከነው ።

“ ስሚ ! ” አላት ። መቀጠል አልቻለም ። ጉሮሮው ላይ የሆነ ነገር ተናነቀው ። ከወጣትነት ባለፈ ዕድሜው የእልህ ዕንባ እንዳያነባ ፈራ ። እናም ከምላሱ ይልቅ እጁን ማንቀሳቀስ መረጠ ። የራስጌ ኮመዲኖውን ከፍቶ አንድ ወረቀት አወጣና ሰጣት ።

ምንድነው ? አለችው ።
አንብቢው ! አላት ፡ ዐይኑን አፍጥጦ ።

በዚሁ ሳምንት ውስጥ ቢሮው ወስጥ በድብቅ ተጥሎ ያገኘው ወረቀት ነበር ። ቤተልሔም ተቀብው ማንበብ ጀመረች።

ጽሑፉ በቅጡ አልተቀነባበረም ። በግጥም ይጀምርና
ምሁር ሰማ ዘቀጠ ...

ኅሊናውን ለሴት ሽጠ ...

ካለ በኋላ ፥ በስድ ንባብ ይቀጥላል ። ቃላቱ ተስፋ መቁረጥን ያመለክታሉ ። በለማ ላይ የተደረደሩ ተራ ስድቦች ነበሩ ።
በመሐል ደግሞ

... ወሲብ አንጎል ሆኖ ሲያስመርቅ እያየሁ ፡ የእኔ ጥናት ከንቱ እንዲያው ተሠቃየሁ አወይ እኔ ፡ አወይ እኔ ! ሴት አለ መሆኔ !...” ይልና፡ ተመልሶ ስድቡን ይቀጥላል ።

አንብባ ጨርሳ ቀና ስትል፥ የምትናገረውን ለመስማት ዐይን ዐይኗን ተመለከታት ። ለእሷ ሲል የተጋፈጣቸው ችግሮች በውስጧ ኅዘን እንዲፈጥሩባት ነበር ሃሳቡ ። እንዲህ ዐይነት ነገሮችን ሥራዬ ብሎ ነው የሚነግራት ። አንዴም በመጀመሪያው ሴሚስተር አንድ ጓደኛው መቼም የቅርቤ ነው ብሎ ሊመክረው ፥ “ ለማ እዚህ ግቢ ውስጥ በአንዲት
ልጅ ምክንያት ስምህ እየተበከለ ነው ” ብሎ ሲጀምር' ለማ በሽቆ ፡ “ ስለዚህ ጉዳይ ምንም አታንሣብኝ ። ተፈጥሮን
ተመክሮ አይመልሰውም ! ማንም የፈለገውን ሊል ይችላል” ብሎ ዘግቶታል ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ መምህራንም
እየታዘቡት መሆናቸውን ሊነግረው ነበር ጓደኛዉ የፈለገው ነገር ግን ለማ የሚበገር ሰው አልሆነም።

በወቅቱ ይህንንም ለቤተልሔም አጯውቷታል ።በአንቺ የተነሳ ያየሁት አበሳ" አይነት መሆኑ ነው። ታዲያ ያኔ ቤተልሄም አዝና ከንፈሯን መጥጣለት
ነበር ።

"አበሻ ነገር መፈትፈት ልማዱ ነው ! አትጨነቅ ” በማለትም አበረታታዋለች ። አሁን ግን ግጥሙን አንብባ የዚያን ዐይነት መልስ አልሰጠችውም ፡፡ እንዲያውም ለአፍራሽ ሐሳቧ መንገድ የጠረገላት ነው የመሰላት......

እና ፥ ከዚህ ሁሉ ነገር በኋላ ወዴት ነው። ሸርተት የምትይው ? አላት አፍጥጦ።

“ እኔስ የፈራሁት ይህንኑ አይደል ? ” አለችና ጽሑፉ ክፉኛ እንደ ቆረቆራት ሁሉ ዐይኗን አሸች ። ዕንባው ደግሞ ራሱ ካልፈቀደ እንደ ፈለጉት አይመጣ ! ዐይኗን ምራቅ እንዳትቀባ ለማ አጠገቧ ቆሟል።

መጀመሪያ ለምን ነበር የቀረብሽው ? ” አላት እስክንድር።

" ፈራሁኛ ! ”
"ምን ? "
"ማትስ እንዳልወድቅ ። እኔ የቁጥር ዘር ጠላቴ ነው ።

ፍቅር ብቻ ሳይሆን እልህ ጭምር ነበር የያዘው ። አስተያየቱ አላማራትም ጡንቻው ላይ አባብጠው የተጋደሙት
ሥሮች አሰፈሯት ። ከተቀመጠችበት ቀስ ብላ ተነችና ወደ በሩ አምራች ።

የት ልትሔጂ ነው ? ” አለና ፥ አጠገቡ የነበረውን አምቦ ውሃ ጠርሙስ አንስቶ ግንባሯ ላይ አነጣጠረ።
“ውይ ለማ ! ” ብላ ጮሃ ጣውላው ላይ ቁጭ አለች ።
“ ሸርሙጣ ! ” አላት አጠገቧ ደርሶ ቁልቁል እየተመለከታት
የሚለማመጡና የተቆጡ ዐይኖች ሽቅብና ቁልቁል ተፋጠጡ ። ለማ ደፍሮ እጁን ሊያሳርፍባት አልቻለም ። አቅፎ
ለማባበልም ልቡ ያን ያህል አላላም ።

"ስሚ ፤ በሦስት ቀን ውስጥ አስበሽበት መልሱን ንገሪኝ። የሦስት ቀን ዕድሜ ሰጥቼሻለሁ ! ” አላት እንዳፈጠጠ ።

ቤተልሄም ከጣውላው ላይ ቶሎ አልተነሳችም” በድንጋጤ ከጭኗ ሥር ሽንት ጠብ ያለ ስለ መስላት እንዳይታይባት ፈራች ። ነገር ግን ሰውነቷን ዐልፎ ጣውላው ላይ
የደረሰ አልነበረም...

ያን ዕለት እንደ ምንም ከክፍሉ ከወጣች በኋላ መንገድ ላይ በጕዳዩ እሰበችበት ። የይህሆን ጨዋታ ነው ። የለማ ኮንትራት አልቋል ። አብራው ከቀጠለች ለሚቀጥሉት ዓላማዎቿ ዕንቅፋት ይሆንባታል ። ከአንድ ወንድ ጋር ብዙ መታየት ሴሎች የጥቅም መንገድን ወመዝጋት ነው ። ጥቅሙን የሚያሳድድ ሰው በአንድ ነገር ላይ መርጋት አይችልም ትርፉን ከኪሳራው እያሰላ በሚያዋጣው መንገድ መንቀሳቀስ አለበት ... እና ለማ እስኪረሳት ድረስ ከዐይኑ ለመሰወር ወሰነች። ከዚህ ውሳኔ በኋላ ስሟን ለማደስ በግቢው ውስጥ አብራው
የምትታይ ተማሪ ስታስብ ፥ እስክንድር በሐሳብዋ ብቅ አለ ። ብዙ ተማሪዎች ከዘጓት በኋላ እሱ ሳይለወጥ እንደ
ወትሮ ሰላም ይላት ስለ ነበር ነው የታሰባት......

እስክንድር በሆዱ ሣቀ። የግልጽ ሰው ሳይሆን የብልጥ አንበሳ ምስል ከፊቱ የቆመ መሰለው ለጥቅም የቆመች
አንበሳ ! ሣር ባየችበት ሁሉ የምታጎነብስ በግ ፤ ግን ደግሞ እንስሳ ለማዳ ነው ያበላውን ያጠጣውን ፥ የቀረበውን ቶሎ
ያፈቅራል ።

«ግን ታዲያ አብራችሁ ስትቆዩ ከለማ ጋር ፍቅር አልያዘሽም ? ” ሲል ጠየቃት ።

“ ኤጭ ! ” አለች በንቀት
"እሺ ፤ እሱስ ፍቅር ቢይዘው ኖሮ ? ”

“ እእይ እኔ አስቀድሜ ነግሬዋለሁ" አለች ግንባሯን አኮማትራ
"ምን ብለሽ ?
“ አሜሪካ የመሔድ ሐሳብ እንዳለኝ እጮኛዬ እየጠበቀኝ ነው።
ሣቁ እንዳያመልጠው እየሞከረ ፥ ዋና ይዘሽ በትርፍ እየተጫወትሽ ነዋ ! ” አላት
ፈገግ ብላ ዝም አለች ።

“የእኔም ጓደኝነትስ ምሽን እስካሳደርስሽ ድረስ ነዋ!”አላት ድንገት ግልፍ ብሎት ።

ወይኔ ! ካንተ ጋር እኮ እንዲሁ ጓደኝነት ነው ” አለችው ፥ ድንገተኛ ቁጣው አስደንግጧት ።

“ እንዲሁ ጓደኝነት ብሎ ነገር ምንድነው?” ሲል አሰበ። ሐሳቡ ከውስጥ ጥቀርሻ እየለበሰ ሲመጣ ተሰማው ። የአሁኗ
ቤተልሔም ሳትሆን ነገ የምትይዘው ቦታና የምትፈጽመው ተግባር ነው የታየው በዚህ ዐይነት ብላሽ ጥበብ ከዩኒቨርስቲ የምትረቅ ሴት ፥ በሥራ ዓለም ስትሠማራም መሰሎቿን ታፈራና ትመለምል እንደሆን እንጂ ያስተማራትን ሕዝብ
👍4
#ሰመመን


#ክፍል_ሃምሳ_አንድ


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ


...ማሰብና መጀመር የተለያዩ ሆነውበት ተቸግሯል አቤል ። ሐሳቡ በጣም ይመጥቅበታል ።ሊጽፍ ያሰበው ነገር መጽሐፍ ይሆንበታል ። ለሐሳቡ ወግ የሚያግኝለትም አይመስለው ። ወረቀቱን ይዞ ቁጭ ሲል ግን ከብዕሩ ጠብ የሚል ነገር ይጠፋል ። ባዶ ወረቀት ላይ ማን ፎር ሂምሰልፍ” ከሚል አርዕስት ጋር መፋጠጥ ብቻ !

“ችግሩ ከቋንቋው ይሆን ? ” ሲል አሰበ ። በሰው ቋንቋ ከምቸገር ሓሳቤን እንደ ልቤ ላንቆረቁርበት በምችለው በራሴ ቋንቋ ለምን አልፅፍም?።

ባዶውን ወረቀት ከአጠገቡ አገለለና መጽሐፍ ገለጠ ለጽሑፉ የሚጠቅመውትን መጽሐፎች መርጦ አውጥቶ ጠረጴዛው ላይ ከምሯል ። መጻፍ ከመጀመሩ በፊት በዚህ አርዕስት
ጐዳይ ላይ የተጻፉ ብዙ መጽሐፎች ማንበብ እንዳለበት ስለ ተረዳ፡ ሰሞኑን እያነበበ ነበር። ችግሩ ግን አለ ከሚያነበው መጽሐፍ ላይ ብዙ ሰዓት መቆየት አለ መቻሉ ነው ከመጽሐፉ ውስጥ ጠቃሚ ሐሳብ ሲያገኝ የእሱ ሐሳብ ቀድሞ ይሐጥቅና ጻፍ ጻፍ ይለዋል

አሁንም ከተቀመጠበት ተነሥቶ ትንሽ ተንጎራደደ ። ከመንጐራደዱ ጋርም የሚጽፈው ነገር ብልጭ አለለት
ሰው ከራሱ ጋር የሚጣላው ለምንድነው ? በግል ምኞትና ግብ አእምሮው ተወጥሮ ሲጨነቅ ነው ። ነገር ግን የሰው ልጅ የመጨረሻ ግቡ እኛ እንጂ እኔ መሆን የለበትም ከራሱ ጋር ሊታረቅ የሚችለው በዚህ እምነት ተጠምቆ ከግሉ ይልቅ ለማኅበራዊ ችግር ክብደት ሲሰጥና ደስታውን ከኅብረተሰቡ ጣፋጭ ሕይወት ውስጥ ለማግኘት ሲሞክር ነው ። ሰው በመጀመሪያ ለሕያውነቱ ከፍተኛ ግምት መስጠትና ማድነቅ አለበት ። ይህን ካመነ ደግም ማናቸውም በውስጡ የሚከሠቱ ነገሮች የሕያውነቱ ነጸብራቆች ስለሆኑ
እንዳመጣጣቸው ተቀብሎ መፍታት እንጂ ለችግሮች ምረታት የለበትም ። ሰው በትግሉ በተጸጥሮ ላይ ፍጹም የበላይነቱን መቀዳጀት አለበት ።

እቤል መጻፍ የፈለገውን መቋጠሪያ ሐሳብ ያገኝ መሰለው ደስ ደስ አለው። በአንጻሩ ግን ከውስጡ አዘናጊ ስሜት ይታግለው ነበር ። " አይ አቤል ፤ አሁንስ ጅል ሆንክ አዲስ ሐሳብ ያፈለቅክ መስሎህ ነው ? ስንት ፈላስፋዎች ብለውት ብለውት የበቃውን ነገር እንዴት እንደ አዲስ ታነሳዋለህ ? እባክህ ይልቅ ያልተሳበ አዲስ ነገር ፈልግ ።ለዚያውስ በዚህ ዓለም ላይ ምን ያልተባለ ነገር አለ ?”

አቤል የራሱ ስሜት አስጠላው ለምንድነው ስሜቱን ገንቢውን ትቶ አፍራሹ ላይ የሚሮጠው? አዲሱ ሰው ሁሉን ነገር “ ተብሏል” እያለ ራሱን የሚያዘናጋ ከሆነና እጁን አጣምሮ ከተቀመጠ ነገር ተበላሸ ከአሁን በፊትም ማንም ቢሆን ፍጹም አዲስ ነግር ይዞ አልተሄዶም ። ሁሉም እውቀቱን የቀመረው በተከሠረት ወይም በተባለ ነገር ላይ እየቆመ ነው።እና አቤል አቤልሽ ! ይልቅ ደፍረህ ጀምር የአቅምህን ሞክር ፤ ጫር ! ” አለና እንደገና ቁጭ አለ።

እንዴት እንደሚጀምረው ቁልጭ ብሎ ታየው " ሰፊ አርዕስት ነው የያዘው ፤ስለዚህ በንዑስ ርዕስ ከፋፍሎ እያንዳንዷን ንዑስ ክፍል በጽሑፍ ማስረጃና በሕይወት ገጠመኝ
አስደግፎ ማስኬድ ! ሰውነቱን አንዳች የደስታ ስሜት ወረረው ። ሐሳቡ ካለበት መጥቆ ሲሮጥ ንዑስ ርዕሱ ልጓም ሆኖ
ያዘለት ። ሰው የራሱ ወዳጅ የሚሆንበትን ሐሳብ ከመደርደሩ በፊት ከራሱ ጋር የሚጣላባቸውን ሁኔታዎች ለመደርደር ተገደደ ። እዚህ ላይ ለመድረስ ደግሞ፥ ሰው በተፈጥሮ ይዟቸው የሚወጣውንና ከአካባቢው የሚቀስማቸውን ዐብይት ጸባያት ይዞ መነሣት ነበረበት ። የጅማሬ ሐሳቡን በዚህ ንዑስ ርዕስ ሥር አጠቃልሎ ፥ “ በዚህ ዓለም ላይ ታላቅና
ክቡር ፍጡር ነው” ሲል ጀመረ ።

በተመስጦ እየጻፈና ደጋፊ ሐሳቦች ፍለጋ መጽሐፎች እያገላበጠ ትንሽ እንደ ቆየ ፡ ሞኒካ ሻይ ይዛለት መጣች።

የአምስት ሰዓት ሻይ ነበር ። ጊዜው ከምኔው እንደ ሮጠ ገረመው
“ ጽሑፉን ጀመርኩት “ ኮ ” አላት ፡ ገና እየገባች ሳለች ።

“ ዳስ ኢስት ሸን ” አለችው ሞኒካ • ፈገግ ብላ ደስታዋን በመግለጽ ።

አቤል ይህንኑ “ ጀመርኩት ” የሚለውን ቃል ለዮናታንም ለመንገር ተቻኮለ ። እንዲያመጡለት የጠየቃቸውን የቀድሞ የተበላሹ የጥናት ጽሑፎቹን ባመጡለት ጊዜ ፥ የገባላቸው ቃል ትዝ አለው ። ወረቀቶቹን ተቀብሎ ፊታቸው በክ
ብሪት ካቃጠለ በኋላ ፥ አሁን ከፊትዎ የቆመው አዲሱ አቤል ነው ። አዲስ ጽሑፍ አዘጋጅቶ ያሳይዎታል ” ብሏ
ቸው ነበር ። አሁን ዮናታን የሚመጡበት የምሳ ሰዓት ራቀበት።

ሞኒካ አሁን እቤል ያለበትን ጥሩ ስሜት ካረጋገጠች በኋላ፥ ወደ መኝታ ክፍሏ ሔዳ አንድ ጉርድ ፎቶግራፍና የታሸገ
ኢንቬሎፕ ይዛ ተመለሰች ።

“ ይህችን ልጅ ታውቃታለህ ? ” አለችው ፥ ፎቶውን ዐይኑ ሥር አቅርባ ።ፉት ብሎ የነበረውን ሻይ ቶሎ መዋጥ አቃተው
የልብ ትርታ የሚቀሰቅስ ምስል ! አስደንግጦ የሚያስደስት ምስል ! “ ማወቅ ብቻ ነው!? አምልኬባታለሁ እንጂ!” ሊላት ፈለገ። የሞኒካ ቶሎ መልስ መፈለግ ግን፥ አቤል ነገሩን አመዛዝኖ እንዲናገር ጊዜ አልሰጠውም ።

አዎ ! አላት ፥ ሌላውን ስሜቱን ዋጥ አድርጎ
“ የት ? ”
“ ዩኒቨርስቲ ውስጥ አንድ ሴሚስተር ሙሉ በዐይን ፍቅር የማቀቅኩላት ናት” አላት ቃናው በተለወጠ ድምፅ ።

“ ከዚህ ፎቶዋ ጋር ደብዳቤ ልካልሃለች ” አለችና የታሸገውን ፖስታ ሰጠችው። ፈጥኖ ተቀበላት ። ነገር ግን ፈጥኖ መቅደድ አልቻለም ። አንዳች ነገር እጁን የያዘው ይመስል ተንቀጠቀጠ ።

በሚያነብበት ጊዜ ነጻ እንዲሆን በማሰብ ሞኒካ ክፍሉን ለቅቃለት ወጣች ። ደብዳቤዉንና ፎቶዉን ከእስክንድር
ከተቀበሰች ሁለት ቀን አልፎአል ።ለአቤል ወድያውኑ ያልሰጠችው እንዲህ ጥሩ ስሜት እስኪታይበት በመጠበቅ ነበር።

አቤል ደብዳቤዉን ግልጾ ማንበብ ጀመረ፡-

አቤል፥ ስምህን ደብዳቤ ላይ ለመጀሪያ ጊዜ ስጽፈው የተሰማኝን ስሜት ልገልጽልህ አልችልም ። የምወደውንና
የምፈልጎውን ቃል መጥራት ለምን እንደሚያስፈራኝ ሊገባኝ አልቻለም ። የዚህን ደብዳቤ ረቂቅ ብታየው ትግረማለህ ። ስርዝ፤ ድልዝዝ ብቻ ነው። ከስሜቴ ጋር ክፉኛ መታገሌን በዚህ መገመት ትችላለህ ።

ይህን ደብዳቤ እንድጽፍልህ ያደፋፈረኝ እስክንድር ነው ። ጥሩ ጓደኛ ነው ያለህ እሱ ባይገፋፋኝ ኖሮ እንዲሁ ስሜቴን አምቄ ውስጥ ውስጤን እሠቃያለሁ እንጂ ከቶም አልሞክረውም ነበር ። አንተ በእኔ የተነሣ የተቀበልከውን ስቃይ ስሰማ ለብቻዬ ተደብቄ ስቅስቅ ብዬ ነው ያለቀስኩት ፤ግን ጥፋተኛው ማን ነው ? አየህ አቤል ! እኔ መቼም ሴት ነኝ ፤ደፍሬ መጥቼ እንዳነጋግርህ የአካባቢ ተጽዕኖ
አለብኝ ። አንተ ግን በሩቅ ከምትሠቃይ ቀርበህ ! ብታነጋረኝና እወድሻለሁ ብትለኝ ምን ነበረበት ።

“ሕመምህ ጠልቆ የተሰማኝ አሁን ነው ። ለካስ ፍቅር ተገጣጥሞ ካልሰመረ ሥቃይ ነው። በካምፓስ ውስጥ አንተን በዐይኔ ካጣሁበት ጊዜ ጀምሮ ያለሁበትን ሁኔታ ልገልጽልህ አልችልም ። አንተን ለማየት እናፍቃለሁ ፣ ብቸኝነት ያሰቃየኛል ፥ አካባቢዩ ያስጠላኛል ፤ጥናት ያንገሸግሸኛል ፣ሁሉ ነገር ከብዶና መርሮ ይታየኛል ። እውነቴን ነው የምልህ
የተፈጥሮ ክሥተት ባይሆን ኖሮ፡ አፍላ ፍቅር ፈጽሞ እያስመኝም
“ በመጀመሪያው ሴሚስተር ከትምህርቴ እንዳልሰናከል እፈራ ስለ ነበር፡ ፍቅርህን ክፉኛ ተቃውሜዋለሁ›
አሁን የተረዳሁት ነገር ቢኖር ግን ፥ ፍቅር ታግለው የሚጥሉት ነገር አለመሆኑን ነው ። ገና መጀመሪያ የዩኒቨርስቲውን ግቢ ስረግጥ ካየኸኝ ጀምሮ በዐይን እንደምትከተለኝ ያልተረዳሁልህ እንዳይመስልህ እያንዳንዷ እይታ ከንግግር የበለጠ ተሰምታኛለች። እንዲያውም አንዳንዴ ቃላት
1👍1🥰1
#ሰመመን


#ክፍል_ሃምሳ_ሁለቴ


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ


...የጠዋት ፀሐይ የማንንም ፈቃድ ሳትጠይቅ ፈገግ ብላ በዝግታ ወደ ጥናት ክፍሉ ገባች ። ፈገግታዋ ሙቀት እንጂ
ድምፅ ስለ ሌለው ፥ አቤል ቶሎ አላያትም እያዘገመች የተቀመጠበት ወንበር ላይ ደርሳ ግራ ጐኑን ስትሞቀው ነቃ ከእንቅልፉ ሳይሆን በተመስጦ ይሠራው ከነበረው ጽሑፍ ላይ እና ብዕሩን ወረቀቱ ላይ ወርውሮ በተቀመጠበት ተንጠራራ ። ሰውነቱን አፍታታ ።

እጁ ላይ ሰዓት የለም ። ነገር ግን፥ከንጋቱ ሁለት ሰዓት አካባቢ መሆኑን ለመገመት አልተቸገረም” ። ከተቀመጠበት
ሳይነቃነቅ ሦስት ሰዓት ያህል መቆየቱ አላስገረመውም ። ከሌሊቱ ዐሥር ሰዓት ከእንቅልፉ እየነቃ እስከ ንጋት ድረስ
መሥራት፡ሰሞኑን ልማድ እያደረገው መጥቷል ። በንጹሕ አእምሮ ስለሚሠራ፥ ፍሬያማ ውጤትም አግኝቶበታል ።
ዮናታን ይህንኑ በመመልከት ለማንቃት እንዲረዳው የሳሎ ኑን ባለደወል የጠረጴዛ ሰዓት መኝታ ክፍሉ ውስጥ አድርገውለታል ። ቀን ቀን ለጥናት ጽሑፉ የሚረዱትን መጽሐፎች ሲያገላብጥ ውሎ በዚች በለሊቷ ሰአት መጻፉ ጥሩ መንገድ
ሆኖለታል።

ተንጠራርቶ ሲያበቃ ከተቀመጠበት ተነሣ ወደ በረንዳ መናፈሻ ብቅ ብሎ ፀሐይዋን ሙሉ በሙሉ ሊሞቃት ፈለግ ። የሰንበት ፀሐይ ! ጭለማው ገልጦ የእሑድ ፀሐይ ብቅ ካለች ከውጭ የሚመጣ ሰው አለ ስለዚህ የእሑድ እንግዳውን ለመቀበል ጸጉሩን ማበጣጠር ልብሱን መቀየር ነበረበት።

ጸጉሩን ሲያበጥር ልቡ ድቤ መምታት ጀመረ ። ዕረፍ ብለው አያሳርፉት ነገር ! የልብን ከበሮ አይቆጠሩት ነገር !
የገዛ ልቡ አናደደው ። ድንገት የበሩን ደወል የሰማ መሰለው ተሳስቷል ። ናፍቆት የፈጠረ ደውል ካልሆነ በስተቀር ፡ በክፍሉ ውስጥ የተሰማ ድምፅ የለም ። የሹካ ማንከያና የስሐን ድምፅ ግን በርግጥ ከሌላኛዉ ክፍል ይሰማል ።
ያቺ ሞኒካ ስትንደፋደፍ ነው ። መቼም እሷ ጠዋት መተኛት አትወድ።

ወደ በረንዳው መናፈሻ ወጥቶ ከፎቁ ቁልቁል ተመለከተ ። የዮናታን መኪና እቦታዋ የለችም ። ጠዋት ሲነሡ
ስለሰማ፡የት እንደሔዱ አላጣውም። በአስፋልቱ ሳይ ከሚሠሩ መኪናዎች መሐል ነጥሎ የሚለያት ይመስል ዐይኑን ወደ ሩቅ ወረወረ ። የቤት መኪናዎች እምብዛም የሉም ። ታክሲዎች ናቸው ሽቅብ ቁልቁል ውር ውር የሚሉት ።

ቆሞ መጠበቁ ሰለቸው ። የቆመበት ጊዜ ከዐሥራ አምስት ደቂቃ ባይበልጥም ለእሱ የዓመት ያህል ረዘመበት
“ምን ሆነው እንዲህ ቆዩ ? ” አለ በሐሳቡ፡ አልሔድም ብላቸው ይሆን ? ወይስ የሙሽራ ልብስ አልብሰው ሊያመጧት
ይሆን ? ?

ትዕግሥቱ አልቆ ወደ ውስጥ ተመለሰና ሞኒካ ጋ ሔደ።ወጥ ቤት ውስጥ ምግብ እያበሰለች ነበር ። የቡታ ጋዙን ሦስቱም ምድጃ ድስት ተጥዶበታል ። ሰርግ ሰርግ ሸተተው ፤ የወጡ ሽታ ራብ ለቀቀበት ። ቁሌቱ ገና ይንተሸተሻል ። የበሰለው ደግሞ ክዳኑን ሽቅብ እየገፈተረ ይንተከ
ተካል ። ሞኒካ ፊት ላይ ክፉኛ መቻኮል አነበበ ።

“ ምን ልርዳሽ ? ” አላት ። እሷም ፈገግ ብላ " ከምድጃው ላይ አንዱን ድስት አውርዳ ፥ ቡና በማንቆርቆሪያ
እንዲጥድላት ነገረችው ፡ሁለቱም የሥራ ድርሻቸው ላይ አትኩረው እግረ መንግዳቸውን ስለ ጽሑፍ ሥራው ሁኔታ መጨዋወት ላይ እንዳሉ ድንገት ደወሉ ተንቃጨለ።

አቤል ሲሰማው በላብ ተጠምቀ ፣ጭንቅ አለው ፤የልቡ ትርታ ፍጥነቱን ጨመረ ። ምን ሰው ያስደነግጣሉ ! ቀስ ብለው አይደውሉም እንዴ ? ” የቡና ማንቆርቆሪያ ክዳን እንደ ወደቀበት ያስተዋለው ቆየት ብሎ ትንሽ ከተረጋጋ በኋላ ነው።

ሞነካ ዋናውን በር ከፍታ እንግዶቿን ስትቀበል አቤል ወጥ ቤት ውስጥ እንደ ቆመ ጆሮውን ላከ። የተነባበረ የጫማ ድምፅ ። የማን የማን ይሆን ? የዮናታን ፡ የእስክንድር ፡ የሚሰማው የወንዶች ድምፅ ብቻ ሆነበት ። የልቡ ምት ስላስፈራው ደረቱን በእጁ ደገፈ ። ወዲያው ግን ሞኒካ ራሷን በእንግሊዝኛ ስታስተዋውቅ ስለ ሰማ አዲስ ሰው
መምጣቱን ገመት ።

ያላበውን እጁን አጠገቡ ያገኘው ነገር ላይ ጠራረገ ።ግንባሩን ፡ ጉንጩን ዐይኑን በእጁ አሻሸ እንደ ቆመ ጸጉሩን አበጣጠረ ። የሸሚዝ ኮሌታውን እያስተካከለ በረዥሙ ተነፈሰ ጭንቀት የሚያባርር፥ ፍርሐት የሚያስወግድ አተነፋፈስ : እና ርምጃውን በልቡ እየቆጠረ ወደ ሳሎን ገባ ።

ከአጭር ጠይም ሴት ልጅ ጋር ዐይን ለዐይን ተገጣጠሙ ። የሁሉም ፊት በፈገግታ ደምቆአል " ፈገግታው ሁሉ ለአቤል ጐልቶ የታየው የትዕግሥት ነው " በጉንጭ መሰርጐድ የታጀበ ፈገግታ ! ይህን ፈገግታዋን ለመጀመሪያ ጊዜ ካየው አንሥቶ ከአምስት ወር ራብ በኋላ ማየቱ ነው ። የሚወደውን የጉንጯን ስርጉድ ቀርቦ ሲያይ የመጀመሪያው ጊዜው መሆኑ ነው ። ማንን ቀድሞ መጨበጥ እንዳለበት ግራ ገብቶት ሲርበተበት አብራው የቆየችውን
ሞኒካንም እንደ አዲስ ጨበጣት ።

ለእስክንድር ያለዉን ስሜት ቆንጥጦ መያዝ አልቻለም ። ስሜቱ ፈንቅሎት ጉንጩን ጥብቅ አድርጐ ሳመውና
ይህ ሁሉ የአንተ ጥረት ያስገኘው ፍሬ ነው አስው ። ፊቱን በቅጽበት ወዶ ዮናታን መል። እና ደግሞ የርስዎ ? ” አላቸው ። ፍቅሩን በዓይኑ ከመግለጽ ቀቀር ተንጠራርቶ ሊስማቸው አልደፈረም ። ሦስተኛ ባለውለታውን ሲያመሰግን ዘወር ሲል ከአጠገቡ አጣት ። ሞኒካ ድስት ሲገነፍል ሰምታ እየሮጠች ወደ ወጥ ቤቱ ተመልሳ ነበር ።

ትዕግሥት በነጭ የሀገር ልብስ ነው የመጣችው።አቤል ይህንኑ ለብሳ የተመለከተቀትን እሑድ ወዲያው አላስታወሰም " ቆይቶ ቆይቶ ነው ከእነ ማርታ ጋር ሰርግ ቤት ስትሄድ ልብሳው እንደ ነበር ያስታወሰው። ሰላምታውንና ምስጋናውን ጨርሶ ሲቀመጥም ልቡ እልተረጋጋም ነበር ።ይበልጥ የትርታውን ፍጥነትና አስጭናቂነት ጨመረ
ዘሎ ዘሎ አንዴ ቀጥ እንዳይል ፈራ።

ትዕግሥት ማለት እሷ ነች ። ታዲያ የተመኙትን ሲያገኙ መንቀጥቀጥ ነው ? ደብዳቤዉ ያሳደረበት ስሜትና ሲገናኙ የደረሰው ሁኔታ ባለመገጣጠሙ በልቡ በሸቀ። ያ ሁሉ የፍቅር ቃላት ጋጋታ ምን ዋጠው ? ይኖራል ! ጸጥታውን የሚሰብርለት ድምፅ አጥቶ ነው እንጄ በሁለቱም ውስጥ አለ ።

አቤል ኤቼዳች ቃል መተንፈስ ፈልጎ ምላሱን ተጠራጠረው " ምናልባት የተሳሰረበት እንደሆንስ ? ከፍቅር
እመቤቱ ፊት የተቀመጠው ገላው የሚንቀጠቀጥ ጀርክ የሚመታ መሠለው።

በድንገት ዐይኑ የእጁ ጠባሳ ላይ ዐረፈ ምግብ አዳራሹ ውስጥ የወደቀ ጊዜ የወጡ ፍንጣቂ ያተረፈለት ጠባሳ ።
መጥፎ ስሜት አልተናነቀውም መጥፎ የልብ ጠባሳ ነበር እንጂ የእጅ ጠባሰ ምንም አይደለም ። የልቡን ቁስል ደብዳቤዋ ባመነጨበት እንባ ካጠበው ሰንብቷል ።

ተጫወቺ የሚል ቃል እንደ ምንም ከአፉ
ገፍትሮ አወጣ ።

ትዕግት በእሺታ ፈገግ አለች ፈገግታዋ ጠዋት ከሥራው ላይ ካባነነችው ፀሐይ ይበልጥ ደምቆ ታየው።

ሳያስቡት የዝምታው ባሕር ዮናታን እስክንድርም ውጧቸው ነበር ። ከተቀመጡ ጀምሮ ቃል አልተነፈሱም
ታዛቢ ባይሆኑም ታዛቢ መሰለዋል ። ወጥ ቤት ውስጥ የሚንተሽተሽው ምግብ ሽታ የእስክንድርን አንጀት እያላወሰው ነበር። በአፉ ምራቅ ሲሞላ ተሰማው።

"በመጀመሪያ የመኝታና የጥናት ክፍሎችህን ለትእግስት አሰጎብኛት ! አሉ ዮናታን በቤቱ ውስጥ እንቅስቃሴና ድምፅ ለመፍጠር በማሰብ።

አቤል ከትዕግሥት ጋር ተነሣ" ዮናታንና እስክንድርን በዝግታ ከኋላቸው ተከተሏቸው ።

“ ፍቅራቸው በጥሩ መልክ ይቀጥል ይሆን ? ” አለ እስክንድር በሹክሹክታ ድምፅ ፥ ወደ ዮናታን ጆሮ ጠጋ ብሎ ።
ቢቀጥል መልካም ነው ። ባይቀጥልም አቤልን እንዳለፈው አይጐዳውም ። ተቀራርበው ቃላት ከተለዋወጡ
ዐይኑን መግለጥ ይችላል አሉ ዮናታንም በሹክሹክታ በአቤልና
👍2🥰2
ሊቀበላቸው መዘጋጀቱን ፧እንዴት ይጠርጥሩት? እነሱ የሚያውቁት በወዳጃቸው፡ በባለውለታቸውና
በድሮ ጐረቤታቸው በአባባ ብራቱ ቤት ተገኝተው ጸበል፤ ጸዲቅ ሊቀምሱ፤ ሊጨዋወቱ ነው፡፡ ተዘገጃጅተው ለመሄድ ተነሱ......
ጠዋት ላይ መቶ አለቃ ድንበሩ እንዲጽናና፡ እንዲረጋጋ ተደርጐ፤ እህል ውሃ ከቀመሰ በኋላ፤ ልጆቹ ወደሱ እየመጡ እንደሆነ ተነገረው፡፡ ከዚያም በእድርተኞቹና በወዳጅ ዘመዶቹ ተከቦ አይኖቹን በበሩ አጥር ለይ እያንከራተተ በናፍቀት ይጠባበቅ ጀመር። ልጆቹ ከአሁን አሁን መጥተውለት እስከሚስማቸው፣ እስከሚያቅፋቸው፡ አንገታቸው ላይ ተጠምጥሞ እስከሚያነባ ድረስ ተጣድፎና፤ በጉጉት ተውጦ፤ ከአጥሩ በር ላይ አይኖቹን ሳይነቅል መጠባበቁን ቀጠለ፡፡ ትህትና ትህትና...ትንሿ ትህትና... ቆንጅዬዋ ትህትና፣ የሚወዳት ልጁ እንዴት ሆና
ይሆን? ማንን አክላ ይሆን? እንደዚያ የሚንሰፈሰፍላት ትህትና...
አንዱዓለም ትንሹ የአካሉ ክፋይ ጋሻዬ የሚለው ወንድ ልጁ ፣ እንደ አህያ ጡት ሁለት ብቸኛ ልጆቹ፡፡ በድንገት እንደተለያቸው ሲቀር ለዘመናት ናፍቆታቸው ውስጡን ሲቦረቡረው የኖረው፣ ዐይኖቹ ደም እስከሚያለቅሱ ድረስ ያለቀሰላቸው ልጆቹ ተያይዘው ይመጡልሃል ተብሎ ከተነገረው በኋላ፤ እሰከሚያያቸው፤ እስከሚያገኛቸው ፤ ድረስ አላምን አለ፡፡ እንደ ባለቤቱ እንደ አመልማል እነሱም ከድተውት እንዳይሆን ልቡ ፈርቶና በጥርጣሬ ተውጦ መጠባበቁን ቀጠለ... በንግግራቸው መሰረት እነ ሻለቃ ልክ ቤት መድረሳቸውን ሲያውቁ አባባ ብራቱ ከደጅ
ተቀበሏቸውና....
ዛሬ ጸበል ጻዲቁ የተዘጋጀው ከኔ ቤት ሳይሆን እዚህ ከናንተ ቤት ነው!" አሉና የጐረቤታቸውን የእነትህትናን አጥር በር ብርግድ አድርገው ከፈቱት፡፡ የአብራኩን ክፋዮች ዓይናቸውን ለማየት የአስራ
አንድ አመታት ናፍቆቱን ሊወጣ የሚጠባበቀው እንግዳ እዚያ ከሰዎች
መካከል ሆኖ ደጅ ደጁን ሲናፍቅ በሩ ብርግድ ብሎ ተከፈተ፡፡ የሱም ልብ
ከበሩ ጋር አብሮ ተበረገደ..አባባ ቢራቱ ቀድመው ገቡ፡፡ ከዚያም ሻለቃ
ብሩክ ተከተለ፡፡ እንግዳው ልቡ ከቦታዋ ተነቃነቀች፡፡ቀጥሎ...ቀጥሎ አዎን! ! እሷ ናት! እሷ ናት! ! ትህትና ናት!! ትንሿ ልጄ ናት! የኔ ፍቅር ናት!! እናቴ ናት!! አዎን ! አዎን! ደርባባዬ ናት!! እንደ እብድ
አይነት ሆኖ፤ እጆቹን በሰፊው ዘርግቶ፤ እያለቀሰ፤ እየጮኽ፤ ተነሳ... ምን ያደርጋል? ውስጡ በሃዘንና በመከራ ተደቁሶ አቅም አነሰውና ድንቅፍቅፍ ብሎ ሊወድቅ ሲል ሰዎች ተረባርበው ደገፉት፡፡ ከዚያም ራሱን ከደጋፊዎቹ እጅ አላቀቀና “ትህትናዬ... ትሁቴ ልጄ... ህይወቴ
አካሌ... እንዱዓለሜ..! የኔ ጌታ! ጌታዬ! እናታችሁስ የታለች?
አመልማልዬስ የታለች? የታለች? እናታችሁ?! ጥሯትና ተቀበሉኝ!
ልጆቼ! ኑ ሳሙኝ ልጆቼ ኑ ሳሙኝ ...ኑ! ...ኑ! ...ኑ! ወደዚህ” እንባውን
እንደ ጉድ እያጉረፈ እጆቹን እያርገበገበ በሁለመናው ሊያቅፋቸው እያለቀሰ፤ እየሳቀም፣ እየሳቀ ፧ እያለቀሰም፣ እንደ እብድ ዓይነት ሆኖ፤ እየተደነቃቀፈ፧ ወደ ልጆቹ ተንደረደረ... ትህትናም አንዱዓለምም ከፊት ለፊት ወደ እነሱ የሚመጣው ሰው ሞትን ድል ነስቶ የተነሳ፣ በአካል የሚያዩት ሰው፤ እሱ የሚወዱት፤ የሚያፈቅሩት፤ ገና በልጅነታቸው የተለያቸው አባታቸው፣ አለኝታቸው መቶ አለቃ ድንበሩ
መሆኑን፤ ያ እንደ ነፍሱ የሚወዳቸው አባታቸው መሆኑን፤ ያ ገና ናፍቆቱን የተነጠቁትና ትንሿ ልባቸው በሀዘን
የተሰበረችለት፤መመኪያ ፤አለኝታቸው፤ እሱ ራሱ መቶ አለቃ ድንበሩ
ለማወቅ ጊዜ አልወሰደባቸውም ነበር፡፡ ሥጋ ለሥጋ የሚነጋገርበት የራሱ ቋንቋ ስላለው እሱነቱን ለማወቅ እንዴት ሊሳናቸው ይችላል ? ስጋ የራሱ ቋንቋ እንጂ ምን ሌላ ቋንቋ ያስፈልገዋል እግዚኦ! በዚያን አባታቸው መሆኑን ባውቁ ጊዜ ስሜት? የማይታመን ታሪክ! ሊሆን የማይችል አንደሀውልት ደርቀው ከቀሩበት ሳይንቀሳቀሱ፤ እንደምስሶ ከተገተሩበት ቦታ ንቅንቅ ሳይሉ፤ እሱ በሰዎች ተደግፎ እያለቀሰ፣ እየሳቀ ፣እየሳቀ እያለቀሰም ሄዶ እላያቸው ላይ
ተጠመጠመ...
የተፈጥሮ ህግ አቅጣጫዋን ለወጠች? የቀንና የሌሊት መፈራረቅ ህግ ቀረ? ወንዞች ሽቅብ ይፈስ ጀመረ? ፀሐይዋስ በምስራቅ ወጥታ በምዕራብ መጥለቋን አቆመች? መሬት በፀሐይ ዙሪያ መሽከርከሯ ታበቃና ወንዞች ሽቅብ መፍሰስ ከጀመሩ ብቻ ነው የሞተ ሰው ሊነሳ የሚችለው፡፡
ሁለቱም በጭንቅላታቸው ውስጥ የነጐድጓድ ድምፅ ያስተጋባ መሰላቸው፡፡
ዓይኖቻቸውን ጨፈኑ፡፡ ገለጡ፡፡ ጨፈኑ፡፡ ገለጡ፡፡ ህያው ነው፡፡ ነገሩ ህልም አይደለም፡፡ ከረጅም ዓመታት በፊት ወጥቶ የቀረውና ሞቷል ብለው ተስፋ
የቆረጡበት አባታቸውን በህይወት ማግኘት ማለት ሊቋቋሙት ከሚገባው
በላይ የሚያስደነግጥ ደስታ ነውና፤ ደንግጠው ያለ እንቅስቃሴ እንደ
ሀውልት በቆሙበት ቦታ ላይ፤ እሱ ደርሶ እላያቸው ላይ ሲጠመጠም፣
ከገቡበት ሰመመናዊ የህልም ዓለም ወጥተው፣ ገሀዳዊውን እውነታ ሲረዱ፣ አባታቸውን በአካል ዳብሰው ሲያስተውሉት፣ በተለይ የትህትና
ሁኔታ እጅግ የሚያሳዝን አንጀት የሚበላ ነበር፡፡ በሰመመን ውስጥ ሆነው፤ በሚንቀጠቀጡ እጆቻቸው ይደባብሱት
ጀመር... ህልም ያለመሆኑን፣ ሥጋ የለበሰ አባታቸው መቶ አለቃ ድንበሩ መሆኑን፣
ሲያረጋግጡ፤ አስተቃቀፋቸው፣ አሳሳማቸው፤ በአጠቃላይ ሁኔታቸው
ሁሉ እጅግ ልብ የሚነካና እዚያ የነበሩትን ሁሉ በእንባ ያራጨ ነበር።
ከዚያም አባትና ልጆች ተቃቅፈው እንደ ስስት እንጀራ እርስ በርስ እየተሻሙ፤ አንገት ለአንገት ተቃቅፈው ሲሳሳሙ ከቆዩ በኋላ፤ ሻለቃ የፈራው ነገር ሁሉ ሆነ :: በዚያች ግቢ ውስጥ ተፈጥሮ እንቅስቃሴዋን ለየት አደረገች፡፡ ፀሃይዋ ጥቁር ግርዶሿን ጣለችና ብርሀንዋን ከለከለች፡፡
ነፋሱም አስገመገመና በዚያች ትንሽ ግቢ ውስጥ አዋራውን ወደ ሰማይ አስነሳ!! ለዚህች አስገራሚና ውብ ቀን ላልታደለችው ሚስኪን የሰማይ አሞራ ጭምር በድጋሜ ዋይ! ዋይ! እያለ አለቀሰላት፡፡ አንገት ለአንገት ተቃቅፈው፤ ለዚያች ይህንን የመሰለውን አስደሳች ቀን ለአንድ ቀን እንኳ ለማየት ላልታደለችው ከርታታ፤ እዬዬ ብለው በእንባ ተራጩላት።
ሁለቱ የትህትና ልጆች በቤተሰቡ ለቅሶ ተደናግጠውና በእናታቸው እግር ላይ የሙጥኝ ብለው ተጠምጥመው የለቅሶው ተካፋዮች ሆኑ፡፡ ሳያውቁት
እነሱም የደስታውና የሀዘኑ ተካፋይነታቸውን አሳዩ :: ድንቅ! ነው ፀሐይዋ እንደጠለቀች አልቀረችም! በሌላ በኩል በተራራው አናት ላይ ብርሀኗን ፈንጥቃለች.. አዲስ ህይወት ይመጣል... አዲስ ህይወት ይቀጥላል...ህዝቡ በዋይታና በደስታው መሃል እየዋዠቀ አብሯቸው ወዲያና ወዲህ ሲሯሯጥ፣ ሻለቃ ብሩክ በደስታ ተሞልቶ፤ እንባውን ከፊቱ ላይ አየጠራረገና ካሜራውን ደጋግሞ እየተጫነ ለነገው ትዝታ የዛሬውን እጅግ አስደናቂውንና አስገራሚውን እውነታ መቅረጹን ቀጠለ.........!!!

ተፈጸመ

ታሪኩ ይህን ይመስላል አስተያያታችሁ ለሰጣችሁኝ እንዲሁም በንባብ አብራችሁኝ ለነበራችሁ ሁሉ በጣም አመሰግናለው ዛሬም አንብባችሁ ስትጨርሱ የተለመደውን አስተያየት እጠብቃለው በ @atronosebot አድርሱኝ። ሌላው #ሰመመን ድርሰት በቅርቡ መጠናቀቁን ታውቃላቹ በተቻለኝ መጠን ለመመለስ ሞክሪአለሁ ያልመለስኩት ካለም ምስጋናዬ አሁን ይድረሳቹ በጣም አመሰግናለው ከቡዙዎቸለ ግን ልቤን የነካኝ አንድ አስተያየት አለ በድምፅ የተላከልኝ ስለሆነ ሁላችሁም ብትሰሙት ደስ ይለኛል 👇
👍32