አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
568 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_አርባ


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

...“ውሸቴን አይደለም ካልቨርት። እርግጥ ጥፋቱ የኔው የራሴ ነው::ወደ እርሷ ባልሄድ ምናልባት ያች ሴትዮ አግኝታ አታጠፋትም ነበር፡፡”

ካልቨርት በቆመበት ቁልቁል ናትናኤልን ተመለከተው፡፡ ወዲያው የሰማው ቀስ በቀስ እየሰረገ ወደ ሰውነቱ ሲገባ በፍራሿ ላይ ተቀምጦ ፊቱን ጉልበቶቹ መሃል ቀብሮ በፀጥታ ያለቅስ ጀመር፡፡ እልህና ንዴት ትከሻውን ሲሰብቁተ ናትናኤል ለጥቂት ደቂቃዎች በትዕግሥት ጠበቀውና ቀጠለ፡፡

“ከመሞቷ በፊት እናቷጋ ድሬዳዋ መሆንህን ብቻ ተነፈሰችልኝ፡፡”
ናትናኤል ታሪኩን በሙሉ አንድም ሳያስቀር እውርቶ ሲያበቃ ወደኋላ ፈቀቅ አለና ከፍራሹ ኋላ ያለውን ግድግዳ ተደግፎ ተቀመጠ።ለተከተሉት በርካታ ደቂቃዎች በክፍሉ ውስጥ ፀጥታ ሰፈነ፡፡ እልፎ አልፎ
ብቻ ካልቨርት መሃረቡን እያወጣ አፍንጫውን ሲያፀዳዳና ሳግ ሲተናነቀው
ከሚሰማው ድምፅ በስተቀር ዝምታ ሽፈናቸው፡፡

“ሲገድሏት እዛው ነበርክ ማለት ነው?” አለ ካልቨርት ጉንጮቹን ያረሰረሰውን እንባ እንኳን ለመጥረግ ሳይሞክር ካቀረቀረበት ከጉልበቶቹ መሃል ቀና ብሎ ናትናኤልን እየተመለከተው፡፡

ናትናኤል በዝምታ ጭንቅላቱን ነቀነቀ 'አዎ'

ካልቨርት በእንባ የደፈረሱ አይኖቹን ከጣሪያው ላይ ሰቅሎ የሚተናነቀውን እንባ ታገለው፡፡

“እና ምንድን እንድነግርህ ነው የምትፈልገው?” አለ በተሰበረ ድምፅ ጭንቅላቱን ወደፊት ጉልበቶቹ ላይ ጣል አድርጎ፡፡

“ሁሉን፤ እነማናቸው? . ምንድነው የሚሰሩት? አንተስ ለምን ተሰወርክ? ሁሉን ማወቅ እፈልጋለሁ፡፡”

“ዋጋ የለውም።” አለ ካልቨርት ዓይኖቹን ቦዘዝ አድርጎ፡፡ “እንዴት ዋጋ የለውም? ምስጢሩን ስረዳ ብቻ ነው ራሴንም ሆነ
አንተን ልረዳ የምችለው፤ እነዚህን ነፍሰ ገዳዮች ላቆማቸው የምችለው፡፡”

“ነፍሰ ገዳዮች አይደሉም::”

“ታዲያ ምንድናቸው? ከዚህ በላይ ምን ትፈልጋለህ?”
ነገርኩህ ነፍሰ ገዳዮች አይደሉም!” በስጨት አለ ካልቨርት፡፡
ድጋሚ መሃረብ አውጥቶ አፍንጫውን እያጸዳዳ፡፡

“የምሥራችን የገደሏት እነርሱ ፡ መሆናቸው እንዳልተዘነጋህ
እርግጠኛ ነኝ”
“እነሱ አይደሉም፡፡ አስታውስ… የገደለቻት ሴት…”
“ያው ነው!” አቋረጠው ናትናኤል።
“ያው እይደለም!” ካልቨርት በስጨት አለ። “ማነው ስምህ.…
ናትናኤል ነው ያልከኝ? ብዙ የማታውቀው ነገር አለ፡፡ ምንም አታውቅም ማለት ይቀላል፡፡ ነፍሰ ገዳዮች አይደሉም።አዎ ጓደኛህን ገድለውብህ ይሆናል!አንተንም ሊያሳድዱ ይችላሉ ግን አንተ እንደምትለው አይደሉም፡፡”

“የፈለጉትን ይሁኑ፡፡ ብቻ ልናቆማቸው ይገባል፡፡ ትሰማኛለህ?”
“ልናቆማቸው አይገባም፡፡ ተስፋችን እነርሱ ብቻ ናቸው። የቀረን ጭላንጭል ብርሃን ቢኖር የእነርሱ ዓላማ ብቻ ነው፡፡ ዳር መድረስ አለባቸው።”

ናትናኤል የሚያዳምጠው ሁሉ እንቆቅልሽ ሆነበት፡፡

“ምንድነው የምታወራው የሚስሩትን ትደግፋለህ ማለት ነው?
ወይስ…”

ካልቨርት በመስማማት ጭንቅላቱን ነቀነቀ፡፡

“ታዲያ ለምን ተሰወርክ…እነሱስ ለምን ያሳድዱሃል ለምን ለሌሎች ህይወት መጥፋቱ ምክንያት ሆንክ?" ናትናኤል መጥፎ ስሜት ጉሮሮውን ሲተናነቀው ተሰማው፡፡ “ጓደኛዬ የሞተው ለምን ይመስልሃል? ቤቴን ትቼ ጠፍቼ የቀረሁ ለምን ይመስልሃል? አንተ እዚህ አረቄ በምትጋትበት ሰዓት ሌሉች የአንተን ዱካ ሲያፈላልጉ በጥይት እየታደኑ ነበር፡፡ ይገባሃል የምልህ?” በንዴት ተንቀጠቀጠ ናትናኤል።

ካልቨርት ቀና ብሎ በቁጣ የተጨማተረውን የናትናኤልን ፊት
ተመለከተና ድጋሚ አቀረቀረ፡፡

የተቀመጡበት ክፍል በር ተከፍቶ የምሥራች እናት በትሪ ላይ ሁለት ሳህኖች ይዘው ገቡ፡፡ በቅመም የሚሰራው ምግብ ሽታ ከጓዳ ተነስቶ በተከፈተው በር አልፎ የተቀመጠበት ድረስ አወዳቸው፡፡ ከተዘጋው መስኮት ጀርባ ከጓሮ ሴቶች ምግብ ሲያሰናዱ ዕቃ ሲያጣጥቡ የሳህን ኳኳታ ሳቅ ጨዋታ ልጆች ሲጨፍሩ... ልጃገረዶች 'አበባዬ ሆያ… ለምለም…. ' እያሉ ሲዘፍኑ ይሰማል፡፡ ዘመን መለወጫ... መስከረም እንድ... አዲስ እመት፡፡

“ሰሉ ቁርሳችሁን አድርጉ፡፡” አሉ ሴትዬዋ ትሬውን ፍራሹ ጥግ እያስቀመጡ፡፡ ወዲያው በእንባ ያባበጠውን የካልቨርትን ፊት ሲያዩ ደንገጥ ብለው ቆሙ፡፡

“እግዜር ይስጥልንመቼም አስቸገርንዎት።” አለ ናትናኤል የተፈ
ጠረውን ድንጋጤ ለማርገብ፡፡

የምሥራች እናት ቶሎ ፊታቸውን መለሱና ከክፍሉ ወጡ፡፡ ሴትየዋ ቢወጡም ሁለቱ ሰዎች ምግቡን ለመብላት እጃቸውን አላነሱም፡፡

“ናትናኤል በእኔ ምክንያት ስለተፈጸመው ሁሉ እጅግ አዝናለሁ፡፡ግን ልነግርህ የምችለው ነገር የለም፡፡” አለ ካልቨርት ሴትየዋ ዘግተውት የሄዱት በር ላይ አፍጥጦ::

“በጣም ጥሩ!” : ናትናኤል ከተቀመጠበት ትፈናጥሮ ተነሳ ምሥጢሩን አወጣዋለሁ፡የማውቀውን ሁሉ በአገርና በውጭ ለሚገኙ ጋዜጠኞች እበትነዋለሁ፡፡ እርግጠኛ ነኝ… የማወጣው ፍንጭ ምንም ትንሽ ቢሆን ያንተን አድራሻ ይጨምራል፡፡ያ ደግሞ ከትክክለኛው ጆሮ እንደሚደርስ አልጠራጠርም!” ናትናኤል ያለማወላወል ወደ በሩ አመራ፡፡

“ረጋ በል ናትናኤል… ረጋ በል… ምን እያደረግህ እንደሆነ አታውቅም!” አለ ካልቨርት ከተቀመጠበት በርግጎ እየተነሳ፡፡ “ለህይወቴ ፈርቼ ወይ አድራሻዬን እንዳታወጣ ሰግቼ አይምሰልህ ግን አንተ የማትረዳው የከፋ ጥፋት እንዳትፈጽም ስለምፈራ ነው::”

የካልቨርት መደናገጥ ናትናኤልን የልብ ልብ ሰጠው፡፡

“ጊዜዬን አታጥፋ! ለጓደኛዬ ሞት ምክንያት ሆነሃል፡፡ ከአሁን ወዲያ
ግን ለእንዳንተ አይነቱ ጅል ህይወቴን አደጋ ላይ አልጥልም::” ናትናኤል
የክፍሉን በር ከፍቶ ቆመ፡፡ “ትነግረኛለህ አትነግረኝም?”

ካልቨርት በተስፋ መቁረጥ ራሱን አወዛወዘና ተመልሶ ከፍራሹ ላይ
ዘፍ አለ፡፡

“ቀጥል… እውነቱን ነው የምፈልገው፡፡” አለ ናትናኤለ በሩን ዘግቶ ካልቨርት ጎን ፍራሹ ላይ እየተቀመጠ፡፡

“ከየት እንደምጀምር አላውቅም፡፡” ካልቨርት በባዶው አየር ላይ አፈጠጠ፡፡

“ከኔ ልጀምር ከእነርሱ?” አለ በለሆሳስ ናትናኤልን ሳይሆን እራሱን የሚጠይቅ ይመስል።

“ከሚቀድመው ጀምርልኝ::” ናትናኤል እያበረታታው::

“በወታደራቂ አታሺነት ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኘው የአገሬ ኤምባሲ ውስጥ እንድሰራ ከመመደቤም በፊት በአገሬ የአየር ወለድ ኮማንዶ ሠራዊት ውስጥ በኋላም በተለያዩ አገሮች በወታደራዊ አታሼ የሥራ መደብ ሰርቻለሁ፡፡ በዚሁ የስራ መደብ ሉሳካ በሚገኘው ኤምባሲያችን ውስጥ እየስራሁ በነበርኩበት ጊዜ ነው... ደቡብ አፍሪካ በነጮች ስር በነበረች ጊዜ.. የደቡብ አፍሪካ የነጮች የስለላ ድርጅት ተደራሲ ወኪል አድርጎ የመለመለኝ፡፡ ወድጂ አልነበረም፡፡ ያኔ ባለትዳር ነበርኩ፡፡ ባለቤቴ ከመሞቷ በፊት ነው የማይሆን ነገር ሳደርግ ያዘኝ:: የሚፈልጉትን ካላቀበልኳቸወ ያደረኩት ሁሉ በፎቶግራፍ ከተደገፈ ማስረጃ ጋር ለባለቤቴ እንደሚደርሳት አስጠነቀቁኝ:: እወዳት ነበር፡፡ አሁን ይቆጨኛል...ያኔ ግን ከባለቤቴ ጋር መለያየቱ ሞት መስሎ ታየኝ፡፡ ወጥመዳቸው ውስጥ ገባሁላቸው፡፡”

“ምንድን ነበር ካንተ የሚፈልጉት፡፡”

“ያን ጊዜ ናሚቢያ ነፃነቷን ገና አልተቀዳጀችም ነበር፡፡ የስዋፖ
ሽምቅ ተዋጊዎች ከአንጎላና ከዛምቢያ ከፍተኛ ድጋፍ ይሰጣቸው ነበር፡፡
የጦር ሠፈሮችም ነበሯቸው፡፡ በተለይ ከዛምቢያ የሚነሱ የስዋፖ አደጋ ጣይ
ቡድኖች በካኘሪቪ ሰርጥ ውስጥ በተደጋጋሚ በነጮቹ ላይ ጥቃት ያደርሱ ነበር፡፡ ያንን ነበር ከእኔ ለማግኘት የሚሹት ስዋፖ በዛምቢያ ውስጥ ስለሚያደርገው እንቅስቃሴ፡፡ ለነገሩ እዛ የቆየሁት በጣም ለአጭር ጊዜ ነዉ ሁለት ዓመት አይሞላም፡፡ ቢሆንም በጊዜው
👍3
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_አርባ_አንድ


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

....“ዝግጅቱ በተጀመረ በሦስተኛው ወር ምሥጢሩ አፈትልኮ ተገኘ፡፡ ማን አወጣው? እንዴት አወጣው? የሚታወቅ ነገር የለም፡፡ብቻ በእንግሊዞቹ
ኦብዘርሸርና በፈረንሳዮቹ አፍሪካን ዲፌንስ ላይ ያዕቅዱ ፍንጭ ታትሞ
ወጣ፡፡ እውነቱን ንገረኝ ካልካ ምሥጢሩን ያወጣው የዕቅዱ ጠንሳሽ እራሱ
ነበር፡፡”

“እንዴት? የዛ ምሥጢሩን ሰምን?”

“ቆይ… ዝም ብለህ ተከተለኝ.… እርግጥ ይህ የእኔ መላምት ነው… ግን ዳር ስንደርስ አንተ እራስህ ተመሳሳይ መላምት ላይ እንደምትደርስ እርግጠኛ ነኝ፡፡ እንዳልኩህ ምሥጢሩ አፈተለከ፡፡ ይህ እንደተሰማ የተለያዩ የአፍሪካ ባለሥልጣናት ከወዲያ ወዲህ ሲሯሯጡ ሰነበቱ፡፡ ውጤት ወታደራዊ ዝግጅቱ እራሱን በቻለ ምስጢራዊ መልክ እንዲካሄድና በማንኛውም አገር የሚገኝ ቅርንጫፍ ክፍል በቀጥታ ከዋናው ማዘዣ ካልሆነ በስተቀር በሚገኝበት አገር የመከላከያ ሚኒስቴርም ሆነ ሌላ መንግሥታዊ አካል ጣልቃ ገብ ቁጥጥርም ሆነ ተፅዕኖ እንዳይደረግበት ስምምነት ላይ ተደረሱ፡፡

“ዓላማው ዝግጅቱን አንድ ወጥ
በሆነ መልኩ ለማፋጠንና ምሥጢሩም እንዳይባክን ለመጠበቅ ተብሎ የተቀየሰ ነበር፡፡ በሌላ መልኩ ለተመለከተው ደግሞ ስምምነቱ አገሮች በተናጠል በክልላቸው ውስጥ በሚደረገው ወታደራቂ ዝግጅት ላይ መረጃ እንዳያገኙ የሚያግዳቸው ሆነ፡፡ ይህንን ስምምነት ተቃውሞ የሚቆም አገር ደግሞ ቀደም ሲል የተከሰተው አደነት የምሥጢር መዝረክረክ እንደማይፈጠር ማረጋገጫ ማቅረብ ሊኖርበት ሆነ፡፡ የዚህን ዓይነት ዋስትና መስጠት ደግሞ ለማንኛውም አገርዐአዳጋች ነው፡፡ ያም ሆነ ደሀ ምሥጢሩ በጨቅላ ደረጃው በማፈትለኩ ከዛ በኋላ የወታደራዊ አካሉ እቅሰቃሴ ሁሉ ከኣገሮች ቁጥጥር ውጭ በምስጢር
ለመሆን በቃ፡፡ ይሀን ነበር የፈለገው የዕቅዱ ባለቤት-እንቅስቃሴውን ያላታዛቢ
በቀጥታና በምስጢር መምሪት፡፡ ከዚያ ጊዜ በኋላ የአፍሪካ መሪዎች
የሚያጊንት መረጃ ሁሉ ከዋናው ማበዣ በሚተላለፉ በገባዎች ላይ ብቻ
የተወሰነ ሆነ፡፡

በሌላ ቋንቋ የአፍሪካ መሪዎች የሚያውቁት የእንቅስቃሴው መሪ እንዲያውቁ የሚፈቅድላቸውን ብቻ ሆነ:: ይህም እያንዳንዱ አገር አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኝ ኤምባሲው ባስቀመጠው የወታደራዊ አታሼው
በኩል ብቻ የሚፈጸም ነበር፡፡

“የወታደራዊ አካሉ መረብ እየሰፋና እየተጠላለፈ በመጣ ቁጥር
በየአገሩ የሚገኙ እውቀት ችሎታና ተሰሚነት ያላቸወ የጦር ባለሙያዎች
በጥንቃቄ እየተጠኑና አየተመዘኑ በዚሁ አካል ይዋጡ ጀመር፡፡ ብቻ ምን
ልበልህ..በሁለት ዓመታት ውስጥ እጅግ ጠንካራ፤ እጅግ ሰፊ፧ እጅግ ምስጢራዊ ወታደራዊ አካል አፍሪካ ውስጥ በስውር ተገንብቶ አበቃ:: አልፎ ኣልፎ አንዳንድ ባለስልጣኖች የወታደራዊ ኣካለን አለቅጥ ምስጢራዊ መሆንና መግዘፍ፡ የመቃወም ፍንጭ ሲያሳዩም ያለምንም ምህረት በተናጠል እየተለቀሙ ተወገዱ፡፡ ከዚህ ወዲያ ማንኛውም ምስጢሩን የሚያውቅ ባለሥልጣን ድምፁን ዝቅ እድርጎ መናገርን መረጠ፡፡”

ይህን 'አካል የምትለውን ማነው የሚመራው?” ናትናኤል ጠየቀው፡፡

“በትክክል እነማን እንደሆኑ አላውቅም...ግን ከአፍሪካ አገሮች ሁሉ
የተውጣጡ የጦር አዛዦች እንደሆነ አውቃለሁ፡፡”

“እሺ ቀጥል።”

“ሁኔታው በዚህ ላይ እንዳለ ከሁለት ወር በፊት ወደ አገሬ ተጠራሁ፡፡ አገሬ ውስጥ የቆየሁት ግን ለእራት ሰዓታት ብቻ ነበር፡፡
ሞንሮቪያ እንደደረስኩ ወደ መከላከያ ሚኒስቴር ተወስጀ ስለዚሁ ኣካል
መጠነኛ ገለፃ ከተደረገልኝ በኋላ ለሚቀጥሉት ሦስት ወራት ግልጋሎቴን
ለዚሁ አካል እንደምሰጥና ተጨማሪ መመሪያዎችንም ለመቀብል ወደ ሌላ
ስፍራ የምወሰድ መሆኑ ተነገረኝ፡፡

“እንዳልኩህ ሞንሮቪያ ከደረስክ ከአራት ሰዓታት በኋላ በሌላ አነስተኛ አውሮፕላን የሁለት ሰዓታት ጉዞ እድርጌ ከአንድ በረሃማ ቦታ አረፍን፡፡ ቦታው የቶ እንደሆነ ለመናገር ያስቸግራል። እርግጥ ባንዲራ
ተሰቅሉ ይውለበለባል ግን ባንዲራው አንድ ነው፤ የአፍሪካ አንድነት
ድርጅት ባንዲራ “ከአውሮፕላኑ እንደወረድኩ ማረፊያ ቦታ ተሰጠኝ፡፡ ከእኔ ቀደም ብለው የደረሱ ነበሩ፤ እኔ ከገባሁ በኋላም ሌሎች በተከታታይ ከተለያዩ
እገሮች በሄሊኮኘተሮችና በአነስተኛ አውሮፕላኖች እየተጫኑ ገቡ፡፡ በማግስቱ
ፕሮግራሙ ተጀመረ፡፡ በአጠቃላይ አስራ እንድ ነበርን፡፡ በኋላ እንደተረዳሁት
ሁላችንም በአዲስ አበባ በተለያዩ የአፍሪካ አገሮች ኤምባሲዎች ውስጥ
እንድንሰራ የተመረጥን ነበርን፡፡ እንደውም አንድ ሁለቱን ኤአዲስ ኣበባ ውስጥ ቀደም ብዬ አውቃቸው ስለነበር እዛ በረሃማ ቦታ በቆየሁባቸው ጥቂት
ቀናቶች ልቀርባቸው ችዬ ነበር፡፡ በነገራችን ላይ የሞሮኮ ወታደራዊ አታሼ የነበረው መሃመድ ባስሪ እኔ በነበርኩባቸው ቀናቶች እዛው ነበር፡፡ ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በወሩ ከጊነው ሰው ጋር ተገድሎ ተገኘ፡፡”

“ምን ላይ ነበር የኘሮግራሙ አትኩሮት?» ናትናኤል ወደፊት አዝምሞ ጠየቀው፡፡

“ዝርዝር ነጥቦች ውስጥ አልገባም፡፡ በአጠቃላይ የቆየነው ለሁለት ሳምንታት ነበር፡፡ በመጀመሪያው ሳምንት በአፍሪካ ወቅታዊ ችግር ላይ ነበር ያተኮርነው፡፡ በሁለተኛው ሳምንት ግን ስለ 'ቆንጆዎቹናሰ ስለዓላማው! ስለእን ቅስቃሴው ነበር በጥቅሉ፡፡ በአጭሩ ከመጪው የአፍሪካ መሪዎች ስብሰባ
በኋላ የአፍሪካ መንግሥታት እንደማይኖሩ ነበር የተገለጸልን፡፡››

“ምን ማለት ነው ይሄ?” ናትናኤል ግራ ገባው::
“ነገርኩህ'ኮ ከጥቂት ቀናት በኋላ የምትኖረው አፍሪካ አንድ አፍሪካ
ብቻ ትሆናለች::”

“እንዴት? አልገባኝም፡፡”ናትናኤል የሚያዳምጠው ቅዥት መሰለው፡፡

“የስብሰባው ጊዜ ሲደርስ ጠቅላላ የአፍሪካ መሪዎች ተጠቃለው
አዲስ አበባ ይገባሉ፡፡ ይህ ከተገባደደ በኋላ በመላው አፍሪካ በየአገሩ ያሉ
የአካሉ ቅርጫፍ ክፍሎች በያሉበት አገር ውስጥ መፈንቅለ መንግሥት
አድርገው ሥልጣን ይጨብጣሉ፡፡ ከዚያ በኋላ ማንኛውም መመሪያ ከአፍሪካ
አንድነት ድርጅት ይወጣል፡፡ በአዲስ አበባ በየአገሮች ኤምባሲዎች ውስጥ
በሚገኙ ወታደራዊ አታሼዎች አማካኝነት መመሪያዎች እንደአስፈላጊነቱ ለየአገሮች ይተላለፋሉ፡፡ አበቃ::”

“እንዴ! ስንት መፈንቅለ መንግሥት ማለት ነው?” ናትናኤል ካልቨርቶን አተኩሮ ተመለከተው፡፡ ሰውየው ድጋሚ የሰከረ መሰለው፡፡

“ሃምሳ ሦስት፡፡”
“የፈጣሪ ያለህ! ይህ'ኮ እልቂት ነው፤ ሃምሳ ሦስት አገሮች ውስጥ ጦርነት መፍጠር እኮ ማለት ነው::መቼም ሁሉም አሜን ብሎ አይቀበልም:: ጦርነት ይኖራል፡፡”

“እልቂት አይደለም፡፡ ይኽው አካል ተብትቦ ያልያዘው ወገን በዝብዞ
ያላወቀው ምስጢር በየትኛውም አገር አታገኝም፡፡ ውስጥ ውስጡን በየአገሩ
ጠንካራና ተሰሚ ደጋፊዎች አሉት፤ ውስጥ ውስጡን የየአገሩን ደካማ ጎን
አብጠርጥሮ ያውቃል፤እነማን መያዝ መታሰር.መወገድ አለባቸው? እነማን
ሊታመኑ ይገባል? እነማን ባንዳዎች ናቸው? እነማን ዲቃላዎች ናቸው?
እነማን ንፁህ አፍሪካውያን ናቸው? ሁሉ ይታወቃል።”

“አሁጉራዊ መከላከያ የተባለውስ? ማለቴ" ናትናኤል ግራ ገባው::

“ሽፋን ነው:: አየህ... ወታደራዊ አካሉ የአፍሪካ መንግሥታት እያወቁና ሙሉ ድጋፍ እየሰጡት በምስጢር ለመነቃነቅና የዚህን ዓይነት ስፋት ያለው ወታደራዊ ዝግጅት ለማድረግ በየአገሩ የሚገኙትን ከፍተኛ መኮንኖችን በስሩ ለማሰባሰብ አንድ ተቀባይነት ያለው ሽፋን ያስፈልገው
ነበር፡፡ አህጉራዊ የመከላከያ ሃይል ተስማሚ ሽፋን ነበረ፡፡”

“እና የአፍሪካ መንግሥታት ሁሉ ስለእንቅስቃሴው ምንም
አያውቁም ማለት ነው?''

“ያውቃሉ፡፡ዝግጅቱ ሁሉ: ተቀነባብሮ በየአገሩ ያሉ ቅርንጫፍ ኣካላት
👍3
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_አርባ_ሁለት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ


...የሠራሁትን ጥፋት ለአገሬ መንግሥት እንደሚያሳውቁ እስጠነቀቁኝ፡፡ በዚህ
ላይ እንዳለን የጊኒና የሞሮኮ አታሼዎች ተገደሉ፡፡

“አየህ... እኔ ምስጢሩን ላወጣ አልፈለግሁም:: እርግጥ በአንድ
ወቅት በገዛ አገሬ ላይ ሰልያለሁ፡፡ በመላው አፍሪካ ላይ ይህን በደል
ልፈጽም አልቻልኩም፡፡ የምከዳው አንዲትን አገር ሳይሆን መላውን አፍሪካ
ነበር፡፡ እንዳስፈራሩኝ ከዚህ ቀደም የሰራሁትን ወንጀል ቢያወጡ: ደግሞ
ያለጥርጥር እንደጊኒና ሞሮኮ ወታደራዊ አታሼዎች መሰበሬ ሆነ:: ተሰወርኩ፡፡” ካልቨርት የያዘውን ግማሽ መለኪያ አረቄ ጨልጠው::

“የጊኒና የሞሮኮ አታሼዎች ምስጢር አውጥተው ነው ማለት ነው ለሞት የበቁት?” አለ ናትናኤል ፊቱን አኮማትሮ።

“በእርግጥ አላውቅም.… ግን ሊሆን ይችላል፡፡ አየህ.. ይኸው አካል
የተጠናከረ የመረጃ መረብ አለው:: ከፍተኛ ቁጥጥርም ያደርግብናል፡፡
ምንም እንኳን ቀደም ብሎ ስለ እያንዳንዳችን ጥልቅ ጥናት የተደረገ ቢሆንም አንዳንድ ያልታሰቡ ሁኔታዎች ለመቋቋም ሲባል ይከታተሉናል፡፡ አስፈላጊ ሲሆን ደግሞ በሁለቱ ኣታሼዎች ላይ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ከፍተኛ የአፍሪካ ባላሥልጣናት ላይም የተፈጸመውን ግድያ ከመፈጸም ወደኋላ የሚል ኃይል አይደለም፡፡ብቻ ሁለቱ አታሼዎች ምሲጥር፡ አውጥተዋል ብዬ ስመናገር ያዳግተኛል አውጥተውት ቢሆን እስካሁን ብዙ መፍረክረኮች ይከተሉ ነበር፡፡ቢሆንም አመኔታ እስከታጣብን ድረስና የአንተ መኖር ለአፍሪካ ስጋት
እስከሆነ ድረስ ያለማመንታት ትወገዳለህ፡፡ ብዙዎቹ ተወግደዋል፡፡ ለዚህ ነው ከሁሉ የተሰርኩ፤ ከምደግፋቸውም ከምፀየፋቸውም የተሰወርኩ፡፡እኔም እንደሌላው አፍሪካዊ አፍሪካ አንድ ሆና ማየት እፈልጋለሁ፡፡”

"በመጀመሪያ ለሌላ ባዕድ ድርጅት መስራትህን እንዴት ሳይደርሱበት ቀሩ?”

“ስህተት ነው፡፡ ስህተት ነው የፈፀሙት፡፡ እርግጥ ጠንቃቃ ነበርኩ፤ ቢሆንም መሳሳታቸው በጊዜው እኔንም ያስደነገጠኝ ጉዳይ ነበር።”

“ከጠፋህስ ሰኋላ እንዴት ሊያገኙ አልቻሉም? ማለቴ መንግሥት የሚደግፋቸው እስከሆነ ድረስ አንተን ማደን ያን ያህል አስቸጋሪ አይሆንም...
ሌላውን ብንተወው እንኳን አድራሻህን እንድትነግራቸው የምሥራችን
ሊያስገድዷት ይችሉ ነበር፡፡ እኔ'ኮ ግራ የሆነብኝ ይህን ያህል በመላው አፍሪካ
እየተርመሰመስ ያለ ኃይል አድኖ ሊያገኘው ያልቻለውን ሰው እንዴት እኔ
ላገኝህ ቻልኩ?”

“ሊያገኙኝ ያልቻሉት ስላልሞከሩ ብቻ ነው፡፡ለመሰወር እንደቆረጥኩ
ከዚህ በፊት ያጠፋሁትን ጥፋት በገዛ አገሬ ላይ የሰራሁትን ወንጀል በሙሉ
ዘርዝሬ በጽሁፍ አስተላዕፍኩላቸው፡፡ይህንንም ያለፈ ጥፋቴን እንደማስፈ
ራሪያ በመጠቀም የባዕድ የስለላ ድርጅቶች ምስጢሩን ከእኔ ለማግኘት
በመጣር ላይ መሆናቸውንና ምስጢሩን አውጥቼ ከዳተኛ ከመሆን አለበለዚያም ነጮቹ ያለፈ ስራዬን ይፋ አውጥተው ለጥፋት ሳይዱርጉኝ በፊት ለመጥፋት መወሰኔን ገለጽኩላቸው፡፡ ሆኖም እኔን አድነው ለማግኘት ቢጥሩ ወይም የምሥራችን ለማስገደድ ቢሞክሩ ደብቄ የያዝኩት ምሥጢር የጋዜጦች ቆሎ እንደሚሆኝ እስፈራራኋቸው፡፡” ካልቨርት በቀኙ የጨበጠ ውን ባዶ መለኪያ አተኩሮ ተመለከተው፡፡ “ለዚህ ነው ሳይተናኮሉኝ ባለሁበት ሊተውኝ የመረጡት። ድምጼን አጥፍቼ ጭንቅላቴን ቀብሬ ሰዓቷ እስክትደርስ ከታገለኩ ከዚያ ወዲያ ሊበቀሉኝ እንደማይሞክሩ እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ ምክንያት አይኖራቸውማ፡፡ ለምስጢራቸው ደህንነት ስል ነዋ የተሰወርኩት፡፡”

“ታዲያ የምሥራችን ለምን ገደሏት?”
“እመነኝ እነሱ አይደሉም የገደሏት… ነጮቹ ናቸው፡፡”
“እነማን ናቸው ነጮቹ?”
“እንግሊዞቹ አስራኤላውያኑ… አላውቅም”
“እንዴት ለምን?”
“አየህ እንዳልኩህ ከመጥፋቱ በፊት በምሥራች ላይ አደጋ ሲደርስ
ምሥጢሩን እንደማመጣ ዝቼ ስለነበር ጥበቃ ይደረግላት ነበር በስውር፡፡”

“በማን?”
“በቆንጆዎቹ።”
“ማን እንዳይጎዳት?”
“በብስጭት ምሥጢሩን ይፋ እንዳደርገው ሲሉ ነኞቹ የምሥራችን
ሊያፍኗት ወይ ሊገሏት ይችላሉ ብለው በመፍራት ይመስለኛል። አንተም
ከሆቴሏ ድረስ ሄደህ አንድ ክፍል ውስጥ አስገብተሃት ስትዘጋ የነጮቹ
ቅጥረኛ መስለሃቸው አንድ ነገር እንዳታደርጋት በመፍራት ይሆናል
ቆንጆዎቹ ሊያቆሙህ የሞከሩት፡፡”

“ግን እንዴት ነው ነገሩ?” ናትናኤል ግራ ተጋባ፡፡ “ያ የባዕድ የሆነ የስለላ ድርጅት ኢትዮያውያንን መልምሎ አሰማርቷል ማለት ነው? የገደለቻት ሴት'ኮ ያለ ጥርጥር ኢትዮጵያዊት ነች::” አለ ናትናኤል ሲቲና ፊቱ ላይ ግጥም ስትልበት::

“አይደለም አይደለም::” አለ ካልቨርት የናትናኤል ውሱን እውቀት ነገሩን ሁሉእንዳዘበራረቀበት ሲረዳ፡፡ “ለነጮቹ የስለላ ድርጅት በአዲስ አበባ
ውስጥ የመስክ ስራ እየሠራላት ያለ ሞሳድ ነው፡፡ እሥራኤል ቀደም ሲል
ከዓመታት በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ የኢትዮጵያ አይሁዳውያንን
መልሳ ወደ አዲስ አበባ በብዛት አስገብታ የመረጃ ስራ እያሰራቻቸው ነው::”

“ለምን?” ናትናኤል አቋረጠው፡፡ “እሥራኤል ለምን ብላ ለነጮቹ
ትሠራለች? ከኢትጵያ ጋር ያላት ግንኙነት መጥፎ አይደለም!እንደውም ግንኙነታችን ከመቼውም ጊዜ የተሻለ ነው::”

“የስለላ መረብ የምትዘረጋው በጠላትህ ላይ ብቻ አይደለም። ስለላ በአጭሩ መረጃዎችን መሰብሰቢያ መንገድ እንጂ የግድ አንዱ አንዱ ካለው
ጥላቻ የሚመነጭ አይደለም፡፡
አስታውስ እሥራኤል በ1980ዎቹ መጨረሻ በዋንኛ ደጋፊዋ በዩናይትድ ስቴትስ ላይ ሳይቅር ስለላ ስታካሂድ ተደርሶባታል፡፡ አይደለም፡፡ እሥራኤል ከኢትዮጵያ ጋር ካላት ግንኙነት ጋር የተያያዘ አይደለም::”

“ታዲያ ለምን?” ናትናኤል አፈጠጠ፡፡

“በመጀመሪያ ነገሩ የተለመደ ነው::የተለያዩ የመረጃ ቤቶች አንዱ
ለአንዱ ውለታ መፈጻጸሙና መረጃ መለዋለጠ የተለመደ ነው፡፡ ግን
እሥራኤል እዚህ ውስጥ አጇን የከተተችው ለራሷ ስትል ነው፡፡ አየህ
አፍሪካ ተባብራ ለመንቀሳቀስ ከቻለች ምናልባት በግብጽና በጥቂት የሰሜን
አፍሪካ አገሮች ገፋፊነት አጥፊ እርምጃ በእርሷ ላይ እንዳይፈጸም የሰጋች
ይመስለኛል ለዚህ ነው ሁኔታውን ከወዲሁ ለመከታተል የመረጠችው::”

“እና…. የምሥራችን የገደሏት…”
ቆንጆዎቹ አይደሉም፡፡ የነጭ ጠላቶቻችን ናቸው::” አለ ካልቨርት አቋርጦ::

“ታዲያ እሁን ምን ልታደርግ ነው? ምሥጢሩን ልታወጣ ነው
ወይስ…?”

ካልቨርት ጭንቅላቱን ነቀነቀ፡፡

“ስታየኝ ጅል እመስላለሁ? በፍጹም! ሊያታልሉኝ ሲሞክሩ...
እንዳችንን በአንዳችን ላይ ሊያነሳሱ ሲሞክሩ እያየሁ እንዴት እጃጃላለሁ?”

“ጥሩ፡፡ አሁን ምንድነው ማድረግ ያለብን?” ናትናኤል ዙሪያው
ድቅድቅ ጨለማ ሆነበት፡፡
“መጠበቅ፡፡”
“ምኑን?”
“ቀኑን፡፡”
“የቱን ቀን?”
“የስብሰባውን ቀን፤ አፍሪካ አንድ የምትሆንበትን.…”
“አንችልም!” ናትናኤል ከተቀመጠበት ተፈናጥሮ ተነሳ።
“ለምንድነው የማንችለው.…የቀሩን ሦስት ቀናት ብቻ ናቸው፡፡ ከዚያ በኋላ ነፃ ነን፡፡”

“ይይዙናል!” አለ ናትናኤል በጭንቀት ተወጥሮ፡፡
“አያገኙንም፡፡”

“ያገኙናል፡፡ ባቡር ጣቢያው ድረስ ተከታትለውኛል ! አይቼዋለሁ፡፡
ሽጉጡኝ ከትከሻው በላይ ይዞ ሊቀጥፈኝ ሲንደረደር እነዛን አይኖቹን አይቻቸዋለሁ! ትሰማኛለህ? ! ድጋሚ ካገኘኝ ስሜን እንኳን አይጠራም፡፡ በጆሮ ግንዴ ነው የሚለቅብኝ! ትሰማኛለህ? ! መሞት አልፈልግም፡፡ በጤና ከቤቴ መመለስ ነው የምፈልገው!” ናትናኤል ሰውነቱ ሳይታወቀው ከቁጥጥሩ ውጭ ሲሆንበት ጭንቅላቱን በሁለት እጆቹ ግጥም አድርጎ ይዞ መሃል ወለሉ ላይ ቆመ፡፡

“ቁጭ በል…” አለ ካልቨርት
👍1
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_አርባ_ሦስት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ


“ይሰማኛል ይሰማኛል ቀጥል፡፡” አለ ጀነራሉ በሬድዮው መቀበያ
ላይ አጎንብሶ::

በሬድዮው ክፍል ውስጥ የክፍሉ ሠራተኞች ያልሆኑ ባለሥልጣናት
ከጀኔራሉ ጀርባ ቆመው ይጠባበቃሉ፡፡ ክፍሉ ውስጥ ያለው አየር ለክፍሉ
ሠራተኞችና ከውጭ ተግተልትለው ለገቡት ለሁሉም የማይበቃ ይመስል
እያንዳንዱ ሰው ትንፋሹን ይዞ በጭንቀት ተወጥሯል፡፡

“ጀኔራል” አለ ከድሬዳዋ.. የቃል ሪፖርት የሚያደርገው አንድሬ ኦማሪ በሚንኮሻኮሻው የሬዲዮ መልዕክት ማስተላለፊያ ውስጥ “ኦኘሬሽኑ
ያለምንም ችግር እየተካሄደ ነው፡፡ መውጫ በሮች ተዘግተዋል፤ ቃል
የገባህልኝ የስልክ ግንኙነት ግን ገና አልተቋረጠም፤ ሰውየውን በተመለከተ
እንዳንድ ፍንጮችን አግኝተናል፡፡ ከባቡር ጣቢያ ከሸሽ በኋላ የገባበትን
መጠጥ ቤት አግኝተን ወደ እንድ ጋራዥ እንደመሩትና ከጋራዥም ባለቤት
ጋር ተገናኝቶ እንደነበር ደርሰንበታል፡፡ ጊዜው የዓመት በዓል ስለሆነ
የጋራቹን ባለቤት ለማግኘት እቤታቸው ድረስ ልጆቼን ልኬአለሁ፡፡ በተረፈ
በተቻለኝ መጠን አትኩሮት ሳልስብ ፎቶግራፉን የያዙ ሰዎች በከተማው
አሰማርቼ እያሰስኩ ነው፡፡”

ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ የሚለው አንድሬ የደረሰበትን ደረጃ አንድነትና በአንድ በሬድዮው ውስጥ ሲያስተላልፍ አዲስ : አበባ በሬድዮ መቀበያው ክፍል ያሉት ሁሉ በፀጥታ ሲያዳምጡ ቆዩ::

“አንድሬ” አለ ጀኔራሉ “ስልኩን ያላቋረጥኩበት ምክንያት እያንዳንዱን የውጭ ጥሪ እየተከታተልን ስለሆነ መረጃ ለማስተላለፍ ሲሞክር ግንኙነቱን አቋርጠን ስልኩ አድራሻ እንድናጠምደው ስል ነው፡፡ የቤት ለቤት ፍተሻ ለምን እንዳልጀመርክ ግን…”

“አስፈላጊ አይደለም::” አለ አንድሬ ጀኔራሉ መጨረሱን እንዳሳወቀው “በቀላሉ እጄ ላስገባው እችላለሁ:: ከጋራዥ ከገባ በኋላ በተናጠል
የአንድ ሰው አድራሻ ጠይቆ የጋራዥ ባለቤት እንዳመላከቱት ደርሼበታለሁ::
የጋራዥን ባለቤት አግኝቼ አድራሻውን እስካገኘሁ ድረስ ምንም አስጊ ሁኔታ
ይኖራል ብዬ አልገምትም፡፡”

የሬድዮው መልዕክት ተላልፎ እንዳለቀ ከአንድ ሰዓት በኋላ በድጋሚ
የሚቀርበው ሌላ የሬድዮ ሪፖ'ርት እስኪደርስ ድረስ ከሬድዮው ክፍል ውስጥ ተስብስበው የነበሩ ሁሉ ጀኔራሉን ተከትለው ወጡ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ናትናኤልና የየምሥራች እናት ከቤት ወጥተው በጠባቧ የከረኮንች መንገድ በዋናው መንገድ አቅጣጫ ራቅ ብለው ሄዱ፡፡ ከአንድ አነስተኛ ቤትዐእንደደረሱ የየምሥራች እናት ከባለቤቶቹ ጋር በኦሮምኛ ቋንቋ እያወሩ አስክትለወት ገቡ፡፡ ከቤት ከገቡ በኋላ የቤቱ ባለቤት ደርባባ ወፍራም ሴትዮ ከፊት ለፊቱ ድክ ድክ እያሉ ስልክ ወዳለበት ክፍል አስገቡት፡፡

ናትናኤል የስልኩን እጀታ አንስቶ አዲስ አበባ ርብቃጋ ደወለ፡፡ የደወለበት ስልክ ሲነሳ ሁለት ጊዜ ቃቃ… ሲል ተሰማው፡፡

ሃሎው… ” አለው ወፈር ያለ የወንድ ድምጽ፡፡
“እባኮት ርብቃን ነበር፡፡”
“ናትናኤል ስልኩን እንዳትዘጋው። ልናነጋግርህ እንፈልጋለን፡፡» አለ
ያው ወፈር ያለ ድምጽ።
“ማነህ?”
“ማን እንደምሆን መገመት ትችላለህ፡፡ አብርሃምን አስታውስ..
ሌሎቹንም አስታውስ ርብቃ በእጃችን ነች::” ለአንድ አፍታ ሰውየው ዝም
አለ፡፡ “የት ነው ያለኸው? ንገረኝ።” .
“ጫፏን ብትኳት ምስጢራችሁን እንደምነዛው እወቁ! ታዳምጠኛለህ?!” አለ ናትናኤል ድንጋጤውን በቁጣ ለመሽፈን እየታገላ፡፡

ናትናኤል አትችልም::ምንም መንገድ የለህም፡፡ ከድሬዳዋ የሚወጣ :
ማንኛውም የስልክ ጥሪና ፖስታ ሁሉም በቁጥጥራችን ውስጥ ነው፡፡
በጥቂት ሰዓታት ውስጥ በእጃችን ትገባለህ፡፡ ይህ ከመሆኑ በፊት በፈቃድህ
ያለህበትን ቦታ ንገረኝ..ስማ… ”

“ኮሎኔል ትንሽ ድምጽ እንፈልጋለን” አለ ሰውየው በሌላ ስልክ ውስጥ ለሚያዳምጠውና በርብቃ ኣልጋ ጎን ለቆመው ኮሎኔል ማርቆስ፡፡

ናትናኤል የስቃይ ድምጽ ጆሮው ላይ ኣንጫረረበት …እሪታ. የሴት
ልጅ... የስቃይ እዬዬ
“ሰማህ? ርብቃ ነች፡፡ ምን እያደረግናት እንደሆነ ልነግርህ አልሞክርም:: እመነኝ እራስህን ትጠላለህ፡፡ ናትናኤል እመነኝ መፈጠርህን ትጠየፋለህ፡፡ምስጢሩኝ ካልቨርት እንዳገኘኸው እገምታለሁ! . ዓላማችን ለጋራ ጥቅም ነው፡፡ እጅህን ስጠን፡፡ ምንም ጉዳት አይደርስብህም፡፡”

“ርብቃ ምንም አታውቅም!” ናትናኤል ስልኩ ውስጥ አምባረቀ

አዎ ስለማታውቅ ነው ያለማቋረጥ የምናሰቃያት...በአንተ ኃጢያትአበሳዋን የምናሳያት፡፡ የምታውቀው ነገር ቢኖር በዚህ ሁሉ ስቃይ ውስጥ ማንኛውንም ምስጢር ደብቃ መያዝ አትችልም ነበር…ግን አሁንም እጅህን እስካልሰጠኸን ድረስ የጀመርነውን ኣናቋርጥም፡፡ አስታውስ.በማህፀኗ የያዘችውኝ፡፡”

ናትናኤል በስልኩ ውስጥ ድጋሚ የስቃይና የጣር እሪታ ተሰማው፡፡
“ናትናኤል ” ያው ድምጽ ቀጠለ፡፡ “ጊዜ የለንም፡፡ ያለህበትን ቦታ ንገረን፡፡ እዚህ እሷጋ እናመጣሃለን እመነኝ፡፡” “ለሶስተኛ ጊዜ ያው የስቃይ ድምጽ በሩቁ በረጅሙ አንቋረረ፡፡

ናትናኤል ጉሮሮውን ተናነቀው ጭንቅላቱን ነዘረው፡፡ ዓይነ ተጭበረበረበት

“ተዋት! ተዋት! በቃ .. ድሬዳዋ ነኝ”
“አውቃለሁ ድሬዳዋ መሆንህን፡፡ ግን ድሬዳዋ የት?”
“ሰፈሩን አላውቀውም፡፡ ትንንሽ ቤቶች ያሉበት ኣካባቢ ነው፡፡”
ናትናኤል ጭንቅላቱ ውስጥ የሚነዝረውን ስቃይ መቋቋም አቃተው፡፡
“በአካባቢህ ምን የሚታይሀ ነገር አለ? ሆቴል.…ህንፃ ማንኛውም
ምልክት:”
“ቤት ውስጥ ነው ያለሁት፡፡ መኖሪያ ቤት ውስጥ ነው፡፡”
“ስልክ ቁጥሩን ንገረኝ፡፡”
ናትናኤል የስልክ ቁጥሩን አነበበለት፡፡
“ጥሩ፡፡ የትም ሳትነቃነቅ እዛው ባለህበት ጠብቀን፡፡ ካልቨርት አብሮህ ነው ያለው?”
“አይደለም:: ግን ቅርብ ነው፡፡ ላመጣው እችላለሁ፡፡” አለ ናትናኤል
በጭንቀት እየተውተረተረ፡፡

“ጥሩ፡፡ በፍጥነት ፈጽመው፡፡ : ተጠንቀቅ፡፡ ካልቨርት ሳይነግርህ
እንዳልቀረ እርግጠኛ ነኝ፥ እኛ ብቻ አይደለንም ከተማውን እያሰስን ያለነው፡፡
ናትናኤል በእነሱ እጅ መውደቅ የለብህም፡፡ ነጮቹ:: ተግባባን?”

“አዎ… አዎ አያገኙኝም… በጥንቃቄ አመጣዋለሁ… ብቻ ርብቃን አታሰቃይዋት፡፡ ምንም አታውቅም፡፡”

“ከአሁኗ ደቂቃ ጀምሮ ማንም የቀሚሷን ጫፍ አይነካም! እመነኝ ናትናኤል፡: ቅሪት የሆነችን ሴት ቀሚስ ገልቦ ማሰቃየት ምን ያህል አስጠሊታና ሰቅጣጭ እንደሆን ብታውቅ ችግሬን ትረዳልኝ ነበር፡፡ በእጄ
ያለችው ሴት ርብቃ እርጉዝ ነች! ለማድረግ የምጠየፈውን እያደረግሁ ነው፡፡ አንተ ብቻ ነህ ልታቆመኝ የምትችል፡፡”

ናትናኤል ስልኩን ዘግቶ ለጥቂት ደቂቃዎች ባለበት ፈዝዞ ቆመ፡፡ በደም የተጨማለቀ፣ ያበጠና የዘጓጎነ ፊት ታየው:: የእርጉዝ ሴት ፊት… የርብቃ:: ሁለት እጆቹን ዓይኖቹ ላይ ጭኖ ፊቱ ላይ የተደቀነውን አስፈሪ ምስል ሊያጠፋው ታገለ። የዘጎነና የበለዘው ምስል ግን ይበልጡን እየደመቀ ደም እየጎረሰ እየደፈረሰ… እየረሰረሰ መጣበት፡፡ ምንም የማታውቀው የእሱ ርብቃ በሱ ኃጢያት ቀሚሷ ይዋ ትቦጫጭቆ ጀርባዋ ተገልቦ ራቁቷን በጅራፍ ስትተለተል ታየችው... ሰውነቱን ኣንቀጠቀጠው፡፡

ፈጠን ብሎ ስልኩ ካለበት ክፍል ወጣና የየምስራችን እናት አስከትሎ በጥድፊያ እየተራመደ ወደ ካልቨርት አመራ፡፡

“ደህና ነች?” አሉት የየምሥራች እናት መንገድ ላይ ከጎን ከጎኑ ሱክ ሱክ እያሉ፡፡

"እ..."

“ደህና ነች ወይ አልኩ… ምስርዬ.… " አሉት ፈገግ ብለው::
“ታገናኘኛለህ ብዬ ስጠብቅህ'ኮ ስልኩን ዘጋህብኝ፤ ምነው?»

“እ…እ… አዎ… አ… ደህና ነች” አላቸው፡፡ ኮረኮንቹ መንገድ እየተወለካከፈ እየተጣደፈ ወደ ካልቨርት፡፡
🥰1
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_አርባ_አራት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

....ናትናኤል ባለበት እንደቆመ በእልህ የሚርገበውን ካልቨርትን ሲመለከት የፈጸመው ስህተት ወለል ብሎ ታየው፡፡

“እጇን እየጠመዘዙ ሲያስጮኋት መፈረካከስ ጀመርክ.. እዬዬዋን
ስትሰማ ስለሰጡህ ቃልኪዳን መስበክ አማረህ… ናትናኤል የሚወዱት ሰው
አደጋ ላይ ሲወድቅ ምን እንደሚሰማ አውቀዋለሁ፡፡ እንዳንተ ለደቂቃዎች
ሳይሆን ለቀናት ለሳምንታት አብሮኝ ከርሟል። ይህ ብቻ አይደለም፤
የሚወዱትን ማጣት ምን ምን እንደሚልም ቀምሼዋለሁ። አሁን ድንገት
ወጣ ብለህ የፍቅረኛህን ለቅሶ አዳምጠህ ስለመጣህ ካንተ ጋር በአንድ ሲባጎ ተሸብቤ ወደ መቃብራ እንድነዳ ትጠይቀኛለህ? !ኦ ! ኢየሱስ!”

ናትናኤል ድምፅ ሳያሰማ ባለበት እንደቆመ ቆየ።

“ኣብረኸኝ ትጠፋለህ ወይስ እጅህን ትሰጣለህ? ” አለ ካልቨርት የሴት
ነጠላ ጫማውን ኣጥልቆ ሰፊ የሴት ቦርሳውን ዚፕ ከመዝጋቱ በፊት ድንገት
ቀና ብሎ እየተመለከተው፡፡

አብሬህ እጠፋለሁ፡፡” አለ ናትናኤል ጥርሱን ነክሶ እንባውን እየታገለ፡፡

“ትረፍ ሲልህ ጥሩ መንገድ መርጠሃል” አለ ካልቨርት ከስፊው ቦርሳው ውስጥ አንድ ትንሽ ሽጉጥ አውጥቶ እየፈተሽ፡፡ “እጅህን ልትሰጥ ብትወስን ኖሮ እዚሁ ጨርሼህ ልሄድ ነበር የወሰንኩት፡፡ መቼም አይኔ እያየ እየመራህ እንድታሲዘኝ ልተውህ አልችልም፡፡ በል ቶሎ እንውጣ፡፡” አለ ካልቨርት ሽጉጡን ፈትሾ አቀባብሎ መጠበቂያውን ብቻ ባለበት ትቶ መልሶ
ቦርሳው ውስጥ እየከተተው፡፡

ካልቨርት የሴት ልብስ ለብሶ በላዩ ላይ ድሪያውን ተከናንቦ ናትናኤል ደግሞ ከወገቡ በታች ሽርጡን እንዳሸረጠ በነጭ ሸሚዝ ከትንሿ ክፍል ተከታትለው ወጡ፡፡

“ወዴት ልትሄዱ ነው?” አሉ የየምሥራች እናት ድምፅ ሰምተው ከጓዳ ብቅ እያሉ፡፡
“ሰላም ነው፡፡ወደ አዲስ አበባ ነው የምንሄደው በላቸው፡፡” አለ
ካልቨርት በእንግሊዝኛ ቋንቋ ፈጠን ብሎ፡፡ “እና ስላደረጉልኝ ሁሉ በደንብ
አመስግንልኝ፡፡”

ናትናኤል ካልቨርት ያለውን በአማርኛ ተርጉሞ ለሴትየዋ ተናገረ፡፡

“ውዴታዲያ ብትሄዱስ በዓመት በዓል ነው እንዴ! ምነው ዋል አደር ብትሉ፡፡” አሉ የተከፉ የሚመስሉት ሴትዮ ካልቨርት ለብሶት የመጣውን የሴት ልብስ ድጋሚ ለብሶ ሲያዩ ምስጢሩ እያጓጓቸው፡፡

“ብንሄድ ይሻላል፡፡ የምሥራች ትጠብቀናላች:: ዛሬ ከሰዓት መግባት
አለብን፡፡”

“በአውሮፕላን ነው የምትሄዱ?” አሉ ሴትየዋ፡፡
“አዎ፡፡” አላቸው ናትናኤል፡፡
“ውይ አፈር በበላሁ! ደብዳቤ እንኳን ሳልጥፍ!” ኣሉ ሴትየዋ
እጃቸውን ሽርጣቸው ሳይ እየጠራረጉ “ማነሽ እመ… እመቤት ወረቀት
ወዲህ በይ ...ቶሎ...”
“አይ… ” አቋረጣቸው ናትናኤል እንዳያዘገይዋቸው ሰግቶ፡፡ “ሰሞኑን
ከቻልኩ ተመልሼ እመጣለሁ ከምሥራች ጋር፡፡ መልዕክት ግን እነግሮለታለሁ፡፡ አሁን ቶሎ መሄድ አለብን፡፡”

ሊወጡ ሲሉ ካልቨርት ከቦርሳው ውስጥ በርካታ ገንዘብ አውጥቶ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ምሥጋና እየደረደረ ለሴትየዋ ዘረጋላቸው፡፡

“በቁልቢው! ኧረ እኔ'ቴ! እዚህም ሆኖ የተቀበልኩት'ኮ ሁሉን ላሟላበት አቅም ስለሌለኝ እንጂ. ደግሞ የምን ክፍያ አመጣችሁብኝ? የልጄ ባልንጀሮች ልጆቼም አይደላችሁ? ግድ የለም 'እግዜር ይስጥህ የኔ ልጅ በልልኝ በኣ
አፉ በቋንቋው፡፡” አሉ ሴትየዋ ፊታቸውን ወደ ናትናኤል መልሰው፡፡

የምሥራች እናት ቤት ወጥተው ብዙም ሳይርቁ ከአንድ አነስተኛ ቡና ቤት ገቡና ጥግ ላይ ጨለምለም ያለ ቦታ መርጠው ተቀመጡ፡፡

“አዲስ አበባ ነው ለመሄድ ያሰብኩት::” አለ ካልቨርት ቦታ ይዘው እንደተቀመጡ፡፡ “በዚህ ሰዓት ተመልሰው እመህላችን ይገባሉ ብለው አይጠረጥሩንም:: ወደዚያው ማምራታችንን በትክክል እስካልደረሱበት ደግሞ ሠላም ልናገኝ የምንችለው አዲስ አበባ ውስጥ ብቻ ነው፡፡”

“ታዲያ ለምን ለየምሥራች እናት እውነቱን እንድነግራቸው ነገርከኝ?” አለ ናትናኤል፡፡

“አውቄ ነው:: ተባራሪ የሚሄድበትን፤ የሚሽሽበትን በትክክል አይናገርም። ሴትየዋ ቢያወሩም ዋጋ የሚሰጠው የለም፡፡ ይልቅ እንዴት አድርገን ወደ አዲስ አበባ መሄድ እንደምንችል ነው ያልተገለፀልኝ፡፡”

“ሦስት አማራጭ ነው ያለን አውሮፕላን- ባቡር መኪና፡፡”

“አውሮፕላኑን እርሳው:: ባቡር አንድ አማራጭ ነው:: ቢሆንም በጣቢያዎች ላይ ሰዎች ሊኖሩአቸው ይችላል፡፡ አውቶቡስ ጣቢያዎችም ተመሳሳይ ናቸው”

“እያቆራረጥን መጓዝ እንችላለን፡፡” አለ ናትናኤል ዝም ብለው ተቀምጠው ያዘዙትን ሻይ ሲጠጡ ከቆዩ በኋላ፡፡

“እንዴት?”
“ለጊዜው ክድሬዳዋ ብእግርም ቢሆን መውጣት.… ከዛ በኋላ የጭነት
መኪናዎችና የቤት መኪናዎች እየተከራየን እያቆራረጥን መጓዝ
እንችላለን፡፡”

“በእግር እስከየት ድረስ እንሄዳለን?” አለ ካልቨርት ትክሻው ላይ ካነገበው ከሰፊው የሴት ባርሳው ውስጥ አነስተኛ የአገር ጎብኚ ካርታ አውጥቶ እመሃል ካለው ጠረጴዛ ላይ እየዘረጋ፡፡ «እዚህ ነው ያለነው፡፡ አለ ካልቨርት የሌባ ጣቱን ድሬዳዋ ላይ ተክሎ፡፡ «እዚህ ነው መድረስ ያለብን፡፡ጣቱን ከድሬዳዋ አንስቶ አዲስ አበባ ላይ ጫነው፡፡

“እዎ..ይኽውልህ አንደኛው መንገድ በሐረር አቅጣጫ አድርጎ አለማያ ከመድረሱ በፊት ወደ ግራ ታጥፎ አሰበ ተፈሪ ይገባና ከዚያ ወዲያ በሚኤሶ አድርጎ ወደ አዲስ አበባ ይደርሳል፡፡ የተለመደው መንገድ ይህ ይመስለኛል፡፡”

“ይመስለኛል? አታውቀውም እንዴ?” አለ ካልቨርት ደንገጥ ብሎ፡፡

“እውነቱን ለመናገር አላውቀውም.. የመጀመሪያ ጊዜዬ ነው ድሬዳዋ ስመጣ፡፡”

“በእየሱስ! ከኔ አትሻልማ!” አለ ካልቨርት ወደኋላ ወንበሩ ላይ ተደግፎ፡፡

“አታስብ አማርኛ እስከተናገርኩ ድረስ የትም ይዤህ መሄድ እችላለሁ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ፡፡ ይኸውልህ... ሌላው አማራጭ ደግሞ ከሞላ ጎደል ከባበር ሃዲዱ ጋር ጎን ለጎን የሚሄደው የየረር ጎታ መስመር ነው፡፡ ይታይሃል በዚህ እድርጎ.” . ናትናኤል ወደ አዲስ አበባ ሊያመሩ
የሚችሉባቸውን ሁለት የመኪና መንገዶች አንድ በአንድ ለካልቨርት አሳየው፡፡

እኔ ሁለተኛውን እመርጣለሁ፡፡ እንዴልከው ብዙም የማይዘወትር ከሆነ አለ ካልቨርት፡፡

“ጥሩ፡፡ ግን ከዚያ በፊት ልብሶቻችንን መቀየር አለብን። ቤት ስንመጣ የምሥራች እናት እይተውናል፡፡አዳኞቻችን ከጠነከሩባቸው ፈርተው
ሊናገሩ ይችላሉ፡፡”

መዝድ ከመጀመራቸው በፊት ናትናኤል ከአንድ የልብስና የጫማ ሱቅ ገብቶ ለካልቨርት የሚሆን ሽርጥናጫማ፣ ለሁለቱም ደግሞ የእስላም ቆቦች ገዝቶ ተመለሰ፡፡ ከአንድ ቡና ቤት መጸዳጃ ቤት ውሰጥ ካልቨርት የለበሰውን የሴት ልብስ በአዲሱ ሼርጥ ከቀየረ በኋላ የወንድ ጫማውን ተጫምቶ መኪና ፍለጋ ወጡ።

“ጎን ለጎን ባንሄድ ጥሩ ነው። የሚፈልጉት ሁለት ሰዎችን ስለሆነ ዓይናቸው ጥንድ መንገደኞች ላይ ይበልጥ ጠንቃቃ ይሆናል፡፡አንተ ከፊት ከፊቴ ሂድ፡ እኔ በቅርብ ርቀት እከተልሃለሁ።” አለ ካልቨርት፡፡

"እንጠፋፋለና።”

“አንጠፋፋም፡፡ ብቻ አተ ከጀርባህ መኖሬን ለማረጋገጥ አትገላመጥ፡፡ ኣማርኛ የምትናገር አንተ ስለሆንክ በተቻለ መኪናውን ቶሉ ለማግኘት ብቻ ሞክር፡፡ እኔ እከተልሃለሁ። አታስብ፡፡ ለአት እዲስ ነው እንጂ እኔ የኖርኩበት ዓለም ነው ድብብቆሽ፡፡” አላ ካልቨርት፡፡
«እ..ናትናኤል ሊይዙን ቢችሉም ቀድመው የሚይዙት አንዳችንን ነው…አንተን ከያዙህ ዕሩቅ ስለማይህ ችግር የለውም! አመልጣለሁ፡፡ እኔን ከያዙኝ ግን የጥይት ድምፅ ስትሰማ ሳትገላመጥ ሳትደናገጥ ለማምለጥ ሞክር፡፡አንተንም ከያዙህ የምመክርህ የገዛ ሕይወትህን እንድታጠፋ ነው፡፡ አለበለዚያ
የሚከተለውን ለመሸከም መምረጥህ ነው፡፡”

“መሣሪያ እኮ
👍2
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_አርባ_አምስት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ


....ደውዬ አነጋግራቸዋለሁ። እስካልለቀቋትና በሰላም እስካልተዋት
ድረስ ዕቅዳቸውን እንደማወጣ አስጠነቅቃቸዋለሁ፡፡”

“እንበልና ሊለቋት ባይስማሙስ?”
“አዝረከርከዋለኋ ጉዳዩን! እየተለቀመ ይጎባታል፡፡” ናትናኤል ንዴት ወረረው::

“አየህ... እዚህ ላይ ነው የማንስማማው:: ልንገርህ... ይህን ምስጢር ልታወጣ ብትሞክር ቀድሜ የምቀነጥስህ እኔ ነኝ፡፡” አለ ካልቨርት ሽጉጥ የከተተበትን ኪሱን በቀኝ እጁ መታ መታ እያደረገ፡፡

“ምን ለማለት ነው?” አለ ናትናኤል ዓይኖቹን አጥብቦ፡፡

“ሰምተኸኛል፡፡ ባጭሩ ምስጢሩን ለማውጣት ብትሞክር ቀድሜ
እገድልሃለሁ፡፡ ናትናኤል ኣንድ ተስፋ ቢኖረን... አንድ ጭላንጭል ቢታየን
እሱንም ልታጨልመው ስትሞክር ዝም ብዬ አልመለከትህም::” ቆፍጠን አለ
ካልቨርት፡፡

“ተስፋ… ተስፋ አትበልብኝ ሰባቴ…” ናትናኤል የተሰማውን ንዴት መደበቅ አልቻለም የነፍሰ ገዳዮች ጥርቅም...““ የወንበዴዎች ሆያሆዬ አይደለም ተስፋ
የሚፈነጥቅብኝ ተስፋ አይደለም፡፡ የሚታየኝ..እልቂት ነው ጥፋት ውድቀት፡፡”

“ታዲያ ለምኑ ፈራህ? ለአፍሪካዊ እልቂትና ፍጅት፣ ጥፋትና ዉድቀት ከመቼ ወዲህ ባዳ ሆነበት? በዘርና በጎሳ፣ በፖለቲካና በሃያማኖት ሰበብ የገዛ ወንድሙን በየጫካው በጥይት እየጠዘጠዘ እየቆላ ላለ አዳኝ ታዳኝ ሕዝብ እልቂትና ፍጅት እዲስ ናቸው? የገዛ መንጋጋው ሊያላምጠው የሌለው የገዛ ጨጓራው ሊሰለቅጠው የሌለው ነጋ ጠባ ከኣውሮፓ ኣራጣ አበዳሪዎች ጓዳ ለማይጠፋ ድሀ ህዝብ ወድቀት ብርቅ ሆነ? ለምነ ፈራህ ..ምን እንዳይመጣ ሰጋህ? ከዜሮ በታች ቁጥር አለ? ከአፍሪካ በታች ገሃነም አለ? ብንሻውም እንኳን ከዚህ በታች የምንወርድበት የምናዘቅጥበት ስፍራ የለም አትስጋ፡፡”

“አንዱ የተፋጀ ዝንተ ዓለም ቢፋጅ… አንዴ የወደቀ ዘለአለም ቢወድቅ ምን ገዶኝ ማለትህ ነው?" አለ ናትናኤል በሃሳሱ የመጣችበት ግን ዘውዲቱ ነበረች… ተጎድቸ ያላቀልኝ ሸርሙጣ… ምኔ ይጎዳል?

“አላልኩም፡፡ ለደዌአቸው መድሃኒቱ እዚያው እመህላቸው አፍሪካ ውስጥ መሆኑን መቀበል ተስኗቸወ ከባዕድ ጋር እየተመሳጠሩ ከመጤ ጋር እየተሻረኩ የገዛ ወንድሞቻቸውን ዕልቂት የሚያራቡ አፍሪካውያን ናቸው፡፡ አፍሪካ አንድ መሆን አለባት።”

“እንድነት'ኮ በዘፈቀደ በአየር ላይ አይመስረትም፡፡” አለ ናትናኤል
ስሜቱን ለማስረዳት ተቸግሮ። “እኔ'ኮ ውህደትን አልተቃወምኩም፡፡ ግን
ፖለቲካዊ አንድነት የኤኮኖሚያዊና የማህበራዊ ዕድገት ጥንቅር ውጤት
ነው፡፡ ከዚያ ውጭኮ ውህደት ጭፍን ውህደት ዲሞክራሲን ችላ ማለት ብቻ
ሳይሆን ኢሳይንሳዊ ነው፡፡”

“ፐ! ኢሳይንሳዊ ሳይንሳዊ ቅራቅንቦ! በአፍሪካ ውስጥ ከነፃነት ወዲህ ስንት ሳይንሳዊ ፖሊሲዎችና ሳይንሳዊ ዕቅዶች በወረቀት እንደሰፈሩ አንድ ፈጣሪ ብቻ ነው የሚያውቅ፡፡ የየትኛው አፍሪካዊ አገር ኤኮኖሚ ሲያብብ ሲፈካ… የየትኛው አፍሪካዊ አገር ማህበራዊ ኑሮ ሲለመልምና ሲምነሸነሽ ታየ? በላ ንገረኝ!”

“ታዲያ እኮ የዚህ ምክንያቱ ዲሞክራሲያዊ ሂደት ስለሌለ ነው፡፡
ዲሞክራሲና ሠላም በሌለበት ዕድገት የለም…” አለ ናትናኤል፡፡

“ውህደት ነው መልሱ!” ዕልህ ያጨናነቀው የካልቨርት ድምፅ
አቋረጠው:: “ልክ እንዳንተ በርካታ አፍሪካውያን ከፖለቲካ ውህደት በፊት
ኤኮኖሚያዊ ግንባታ ሊቀድም እንደሚገባና የፖለቲካን ውህደት ወደፊት
ልንቀዳጀው የምንችል ግብ አድርገው ያቀርቡታል፡፡ ነገር ግን ማስተዋል
የሚገባን የምንጓጓለት ኤኮኖሚያዊ ጥንካሬ ሊፈጠር የሚችለው ሙሉ
ፈቃደኝነት የተሞላበት መደጋገፍና መረዳዳት በአፍሪካ አገሮች መሃከል
ሲሰፍን ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ መደጋገፍና መረዳዳት በቅድሚያ
የሚጠይቀው ነገር አለ የጋራ ፖለቲካዊ መድረክ፡፡”

“አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ…” አለ ናትናኤል አቋርጦት፡፡ “አፍሪካውያንን፤ ምንድነው ሊያስተሳስረን የሚችል? የአፍሪካ አንድነትና በሥነ ስርዓቱ የተደከመበት ዓላማ ነው፡፡ አልሆነም እንጂ፡፡”

“ከባድ ጥያቄ!” ካልቨርት ጭንቅላቱን ወደኋላ ጥሎ የማሾፍ ሳቅ ሳቀ። “ምንድነው የውህደታችን መሠረት? በእየሱስ ምን እንድልህ ትፈልጋለህ? የሴንጎር ኒግሪትዩድ? የሴኩትሬ አፍሪካዊ ብሄረተኝነት?የንክሩማን የቅኝ ግዛት እስክ ቁስል ጠባሳ? አይደለም፡፡ ለእኔ ባዶ ሆዳችን ነው አንድ የሚያደርገን! የመሰንበትና ያለመሰንበት ጥያቄ ነው
የሚያስተባብረን፡፡ ተነጣጥለን ልንሞላው ያልቻልነውን ከርሳችንን .. ለየብቻ
ቆመን ልናረጋግጠው ያቃተንን ሰላምና ደህንነታችንን እጅ ለእጅ ተያይዘን
ልንጋፈጠው ይገባል! በእኔና በአንተ እግር ላይ የወደቀን ቋጥኝ ለማንሳት የእኔና ያንተን የዝምድና ግንድ መቁጠርና መመርመር አያሻንም።

በመጀመሪያ እግሮቻችን ከመጨፍለቃቸው ፡ በፊት ተረዳድተን ቋጥኙን ከላያችን ማንሳት አለብን፡፡ አለቀ፡፡ የአፍሪካ ውህደት የተደከመበት ነው ላልከው... እርሳው:: ለእኔ አይዋጥልኝም:: በቆንጆ ቆንጆ ከተሞች ቆንጆ ቆንጆ ህንፃዎች እየገነቡ የአፍሪካ ድርጅት'፤ 'የአፍሪካ… ኮሚሽን የአፍሪካ...
ኢንስቲትዩት እያሉ ስም ማውጣት ትንሽ ትንሽ እየሰሩ ብዙ ብዙ የሚከፈላቸውና በሽንጠ ረጃጅም ቆንጆ ቆንጆ የአውሮፓ መኪናዎቻቸው ቆንጆ . ቆንጆ ኮረዶችን እየጫነ መዞር ሥራቸው የሆነ : ውድ ውድ
ኤክስፐርቶችን ማሰባሰብ አፍሪካን አንድ አያደርጋትም::”

“እኔኮ ሊገባኝ ያልቻለው…" ናትናኤል የጀመረውን ሳይጨርስ ለጥቂት ሰኮንዶች ዝም አሉ፡፡ “እሺ ሆነ እንበል፡፡ እንዲያው ድንገት አፍሪካ አንድ ሆናለች ብለህ በመገናኛ መስመሮች ስትለፈልፍ፡ ሌላውን ተወው አፍሪካውያን እራሳቸው ምን ይላሉ? ፍጹም ያላሰበበትና በማኀበራዊና ኢኮኖሚያዊ ህብረት ያላለፉብት ወንድማማችነታቸውን አጠናክረው በሚገባ ያልተዋወቁበት… ድንገተኛ ዱብ ዕዳ ሲመጣባቸው ምን ይላሉ?

“ምን ይላሉ?” ካልቨርት መልሶ ጠየቀ፡፡ “አየህ… ኣንተ በተላያዩ የአፍሪካ አገሮች ያለውን ህዝብ የፖለቲካ አመለካከት አልተረዳህም:: አፍሪካ ውስጥ ፖለቲካ ግለሰብአዊ ነው፡፡ ግለሰቦች ፖለቲካን ይፈጥሩታል እንጂ የፖለቲካ አመለካከት ግለሰቦችን አይቀርጽም ምክንያቱም ፖለቲካ ራስን መጠበቂያ መሣሪያ ነው
አፍሪካ ውስጥ ጥያቄው የትኛው የፖለቲካ መስመር ለእድገት ይበጃል
አይደለም:: ጥያቄው የትኛው የፖለቲካ መስመር ሥልጣን ላይ ያሰነብተኛል ነው ለዚህ ነው ፖለቲካ ግለሰብአዊ ነው
የምልህ፡ ነፃ አፍሪካ አንድ ብትሆን አፍሪካውያን የሚሉት 'አፍሪካ አንድ
ሆነች ነው:: በቃ::”

ያሉባት መኪና ድንገት ፍጥነቷን አብርዳ ከኋላዋ የአቧራ ቁልል አንስታ፡፡ ወደ ቀኝ ስትታጠፍ፡ ቤኬ መገንጠያ ላይ ደርሰናል ብለው አሰቡ፡፡ ለአንድ አፍታ ተያዩ፡፡ ወዲያው ካልቨርት ወደጎን አዝምሞ ከሹፌሩ ጀርባ ያለችውን ትንሽ መስኮት እየደበደበ ሹፌሩ መኪናዋን እንዲያቆም በምልክት ይወተውተው ጀመር፡፡

“ምንድነው? ምንድነው የምታደርገው?” አለ ናትናኤል የካልቨርት ፈሊጥ አልገባህ ሲለው፡፡

“አቁም በለው፡፡ እቃ ጥለሃል በለው::” አለ ካልሸርት ፊቱን ወደ ናትናኤል መልሶ፡፡

ናትናኤል ወደ መስኮቱ ተጠግቶ ለሹፌሩ ዕቃ መጣሉን በምልክት ሲያስረዳው ሹፌሩ መኪናውን አብርዶ ጥግ አስያዛት፡፡

“ምን ሆናችኋል?” ጮኸ ሹፌሩ ጭንቅላቱን ጠምዝዞ፡፡
“ምንድነው የፈለከው? አለ ናትናኤል በተራው ፊቱን ወደ ካልቨርት መልሶ::

"መጣሁ፡፡” አለ ካልቨርት:: ከጭነት መኪናዋ ጀርባ ዘሎ ወረደና ወደ ሹፌሩ ሄደ፡፡ የሽፌሩን በር ከፍቶ ያለሃተታ የሹፌሩን ክንድ ጨመደደና ጎትቶ አወረደው፡፡ የሚነጫነጨው
👍2
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ


....“ጥሩ እንዳትነቃነቅ::" አለ አራተኛው ሰው መሣሪያውን ደግኖ እንደያዘ ወደ ጭነት መኪናው እየተጠጋ፡፡ በእርጋታ ወደፊት እየተራመደ በዓይነ ጭነቱን ያዳብስ ጀመር፡

እራቅ ብለው ሁኔታውን በዝምታ ይከታተሉ የነበሩት ሦስት ሰዎች የመሃሉ ድንገት ተጣራና ጭንቅላቱን ወደኋላ መታ አደረገ፡፡ ወዲያው ወደ ጭነት መኪናው የተጠጋው አራተኛው ሰው ፊቱን መልሶ ወደ ጓደኞቹ ሮጥ ብሎ ተመለስና ሰብሰብ ብለው ይነጋገሩ ጀመር፡፡
“ጠዋት ምንያህል መኪናዎች ቀድመዋችሁ ወደ አዲስ አበባ
ተነስተዋል?” አለ አራተኛው ሰው ፊቱን ወደ ጭነት መኪናው ሹፌር
መልሶ ድምፁን ከፍ አድርጎ፡፡

“አንድ ሶስት አራት ይሆናሉ፡፡” አለ ከጭነት መኪናው ወርዶ የቆመው ሹፌር፡፡

ወዲያው አራቱ ሰዎች ሮጥ ሮጥ እያሉ ሬንጅሮቨራቸው ውስጥ ገቡና በአዲስ አበባ አቅጣጫ በረሩ፡፡
“ኡፍ .…ፍ!!” አለ ካልቨርት ጭንቅላቱን በተኛበት ጆንያ ላይ ጥሎ፡፡
“ሄዱ? ” አሉ ናትናኤል ሽራውን እንደተከናነበ በሹክሹክታ፡፡
“አዎ፡፡ ያለቀልን መስሎኝ ነበር::”

የጭነት መኪናው ሹፌር መኪናው ውስጥ ገብቶ ሲንቀሳቀሱ በተቻላቸው መጠን መንፈሳቸውን አረጋግተው መመካከር ያዙ፡፡

“ያላጥርጥር በየከተሞቹ ኬላዎች ላይ ይጠብቁናል፡፡ በተለይ ወደ አዲስ አበባ እየቀረብን ስንመጣ አስቸጋሪ ነው የሚሆንብን፡፡” እለ ናትናኤል፡፡
“አዎ፡፡ : ካአሁን ወዲያ ወደየትኛውም ከተማ መግባት የለብንም፡፡ ወደ ከተሞች ስንቀርብ እየወረድን ከጀርባ በግማሽ ክብ ቅርፅ በእግር ማለፍ ነው ያለን አማራጭ፡፡”

“ከናዝሬት ወዲያ ያለውን አካባቢ አውቀዋለሁ! መንገዱን በሩቅ
እይታ እስከተከተልን ድረስ ችግር አይገጥመንም::አለ ናትናኤል፡፡
ናዝሬት ከተማ ሲደርሱ እንድ አምስት ኪሎ ሜትር ሲቀራቸው ከተደበቁበት ሸራ ውስጥ ብቅ ብቅ እያሉ ከኋላና ከፊት ሌላ ተሽከርካሪ አለመኖሩን ካረጋገጡ በኋላ በጭነት፡ ላይ እየዳሁ ወደ መኪናወ ኋላ ተጠጉ፡፡
ሸራው የተጠፈረባቸውን ወፋፍራሃም ገመዶች የሙጢኝ ጨምድደው ይዘው
ቁልቁል ተንጠለጠሉ፡፡

“ተጠንቀቅ፡፡ አስፋልቱ ላይ ኣንዳታርፍ፡፡ በሁለት እግሮችህ ለማረፍና ለመቆም አትሞክር፤ ከዘለልክ በኋላ ጭንቅላትህን ቀብረህ ተንከባለል፡፡ እኔ ስዘል ተመልከት፡፡” አለ ካልቨርት በወጣትነት ዘመኑ በአገሩ ውስጥ ያሳለፋቸውን የኮማንዶ ህይቱን እያስታወሰ፡፡ "

በሰላሳ ሜትር ርቀት ልዩነት ሁለቱም የተንጠላጠሉባቸውን ገመዶች እየለቀቁ ከጭነት መኪናው ላይ ተፈናጠሩ፡፡ ካልቨርት አልተጎዳም፤ ናትናኤል ግን ግራ ክንዱ ክፉኛ ተገሸለጠ፡፡

“አስፋልቱ ላይ አትረፍ፡ እያልኩህ እንዲያውም ተርፈሃል፡፡ወደጎን
ባትንከባለል ኖሮ ይሄ አስፋልት ጭንቅላትህን ነበር የሚፈረክስልሀ፡፡” አለ
ካልቨርት እየሮጠ መጥቶ ናትናኤልን ደግፎ እያነሳው፡፡

አውራ መንገዱን እየራቁ፤ እየሸሹ የናዝሬትን ከተማ በስተቀኝ
ጀርባዋ ዞሯት::

"መንገዱ ወደቀኝ የሚታጠፍ፡ ስለሆነ ከዚህ በኋላ በቀጥታ መስመር ብንሄድ ወይም በሃያ አምስት ኪሎ ሜትር ላይ በዱከምና በሞጆ መሃል መንገድ ላይ ብቅ እንላለን፡፡ አለ ካልቨርት ካርታውን አውጥተው ሲያጠኑት ከቆዩ በኋላ፡፡

እንዳለው ከሦስት ሰዓት ተኩል የእግር ጉዞ በኋላ በሞጆ ከተማ አልፈው ከአውራ ጎዳናው ጋር ተገናኙ:: ብዙም ሳይቆዩ አነስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ የገጠር አውቶቡስ አስቁመው ተሳፈሩ፡፡

“አዲስ ፈለጥ!“ ይላሉ አውቶብሱ ውስጥ ከሹፌሩ ጀርባ የተቀመጡ አዛውንት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው፡፡ “ከአውቶብሱ ገብቶ
መፈተሽ የአባት... “ቆብህን አውልቅ፤ ክንብንብህን አውርድ ብሎ ነገር
ምንድነው? ወቸጉድ!”

“የሚፈልጉት ሰው አለ መሰለኝ::” አለ ባሻገር የተቀመጠ ልጅ እግር፡፡

ታድያ ቢኖርስ ባለፍንበት ከተማ ሁሉ እየቆምን ቆብና ክንብንባችንን መገፈፍ የአባት ነው?ልማድ ነው? ወይ ፈጣሪ?” ሽማግሌው ተቆጠ፡፡

“ምንድነው?” አላቸው ናትናኤል ከጎኑ የተቀመጡትን ሴትዮ::

“እንጃ! ባለፍንበት ከተማ ሁሉ መሣሪያ ደግነው እንደ ሽፍታ ሲበረብሩን ቆዩ፡፡” አሉት ሴትየዋ መደነቃቸውን፣ መገረማቸውን ለማሳየት እጃቸውን አፋቸው ላይ ጣል አድርገው፡፡

“እነማን ናቸው?” ናትናኤል ግራ የተጋባ መስሎ ጠየቃቸው፡፡

“ምኑን አወቄው ብቻ ከወለንጭቲ የጀመሩ ሰባቴ እያስቆሙ ሁለት
ሁለት፥ሦስት ሦስት እየሆኑ እንዲህ እንዲህ እያደረጋቸው ሲበረብሩን ዋሉ፡፡
ሆ! እንደ አነሳሳችንኮ ገና ቅድም ታዲስ አበባ ደርስን ነበር ጊዮርጊስ ይይላቸው”

ናትናኤል ዞር ብሎ ካልቨርትን ሹክ አለው::

ደብረዞይት ሊደርሱ ትንሽ ሲቀራቸው ተጠቃቀሱና መጀመሪያ ካልቨርት እራቅ ብሎ ደግሞ ናትናኤል ተከታትላው ወረዱ፡፡

“ምንድነው?” አለ ካልቨርት አውቶቡሱ ውስጥ የተባለውን ሁሉ አጣርቶ ለመረዳት ጓጉቶ፡፡

ናትናኤል አውቶቡሱ ውስጥ የሰማውን ሁሉ ዘርዝሮ ነገረው፡፡

“ከአሁን ወዲያ መኪና ላይ መውጣት የለብንም::” አለ ካልቨርት፡፡
“ታዲያ እንዴት አናደርጋለን?”
“አሁን ሁለታችንም የተዳከምን ይመስለኛል፡፡ ለጊዜው ከመንገድ
ፈቀቅ ብለን እንረፍና ከጨለመ ወዲያ ሌሊቱን መንገዱን ተከትለን በእግራችን እንቀጥላለን፡፡ ከበረታንና ሰሰዓት አምስት ኪሎ ሜትር ብንጓዝ እንኳን ከምሽቱ አንድ እስከ ጠዋቱ አንድ ሰዓት ስልሳ ኪሎ ሜትር ሽፈንን ማለት ነው:: ፀሐይ ስለማይበረታብን የምንሸነፍ፡ አይመስለኝም፡፡”
ከመንገዱ በስተቀኝ እርቀው ገብተው
ለብቻዋ በቆመች የግራር ዛፍ ስር በደረታቸው ተደፍተው ለማረፍ
ሞከሩ::እየጠለቀች ያለችው ፀሐይ እንደጌጥ ብታብረቀርቅም ሙቀቷ እየከዳት መጣ፡፡ አውላላ ሜዳ ላይ ብቻውን እየተመላለሰ የሚጋልበው ቀዝቃዛ ነፋስ ሰውነታቸውን ጠዘጠዘው፤ ምግብ ሳያገኝ ሁለተኛ ቀኑን የያዘው
ሰውነታቸውም ከፊት የተደቀነውን መንገድ ቁጭ አድርጎ ተዳከመ፡፡ ቢሆንም ፀሐይ ልትሸሽግ ሲዳዳት ከተኙበት ተነስተው የመንገዱን ጥግ ይዘው በአዲስ አበባ አቅጣጫ ጉዞአቸውን በእግር ተያያዙት፡፡

“እርምጃህን አትቀያይር በአንድ ዓይነት ፍጥነት አንድ አይነት ስፋት ተራመድ አለበለዚያ ይደክምሃል፡፡” አለ ካልቨርት እጆቹን እያወናጨፈ፤ “ከጎን ከጎኑ የሚንቶሰቶሰውን ናትናኤልን ዞር ብሎ
ተመልክቶ፡፡

አልፎ አልፎ በሩቁ የመኪና መብራት ሲታያቸው ፈጠን ብለህ ከአውራ መንገዱ እራቅ እያሉ መሬቱ ላይ በደረታቸው አየተኙ እያሳለፉ መንገዳቸውን ያለንግግር ቀጠሉ፡፡ ሁለት ጊዜ ጅቦች ሲያጋጥሟቸውም ሁለቱንም ጌዜ የካልቨርት ሽጉጥ የጥይት ጩኹት አተረፋቸው፡፡

እንዳሰሱት እስከጠዋቱ አንድ ሰዓት ድረስ አልተጓዘም፡፡ ከጠዋቱ አስራ አንድ ሰዓት አካባቢ አቃቂ ከተማ እንደደረስ ያለዕረፍት መቀጠል እንደማይችሉ ስለተረዱ ከመንገዱ ወጥቶ እራቅ ካለ ጫካ ውስጥ ገብተው ካልቨርት እንቅልፍ ይዞት ጭልጥ አለ፡፡ናትናኤል እስካሁን ያሳለፋውን ሁኔታዎች አንድ በአንድ በህሊናው እየመላለሰ ይቃኝ ጀመር፡፡ ርብቃ…
አብርሃም… የቢሮ አለቃው.… ወታደራዊ አታሼዎቹ… ነጭዋ ሲትሮይን
የምሥራች ዘውዲቱ… አዲስ አበባ ድሬዳዋ…ካልቨርት ይህ ሁሉ ውጣ
ውረድ ከርብቃ ስቃይና ከእርግዝናዋ ጋር እየተሰባጠረ ይታየው ጀመር፡፡
ርብቃን ለማዳን ምን ማድረግ አለበት? አወሬዎቹን መጋፈጥ? ከአውሬዎቹ
ጋር መደራደር? ካልቨርት ምስጢሬን ይዤ ልሙት ባይ ነው፡፡ ካልቨርትን እንደገና ማግባባትና ማሳመን ይቻላል? ወይስ የሞተ ፡ ነገር ነው? ለማናቸውም ለካልቨርት ምንም ፍንጭ ማሳየት የለበትም… ማናቸውንም ጉዳይ ከካልቨርት መደበቅ ይኖርበታል፡፡

የተጫናቸው ድካም በዙሪያቸው ከነበረው የማለዳ ውርጭ የከበደ
👍1
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሃምሳ


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ


...“አሁን ገና ሰው መሰልክ?” አለ ካልቨርት ፊቱ ፈገግታ ለብሶ፡፡
“አይዞህ አንተም ውሃ ሲገላምጥህ ሰው ትመስላለህ::” ናትናኤል ፀጉሩን በፎጣ እያደራረቅ ወደተከራዩት የሆቴል ክፍል ገብቶ ከኋላው በሩን ዘጋው፡፡
“ህ! ! ህ ለሁሉም ጊዜ አለው::”አለ ካልቨርት ከተቀመጠበት ተነስቶ የሚቀይረውን አዲስ ልብስ ተሸክሞ ወደ መታጠቢያ ቤት እየሄደ፡፡

ካልቨርት ከክፍሉ ወጣ እንዳለ ናትናኤል ፈጠን ብሎ ካልቨርት ከጥግ ያስቀመጠውን ቦርሳ ይፈትሽ ጀመር፡፡ እንደተመኘውና እንዳሰበው፣
እንዳቀደው የካልቨርትን ሽጉጥ ቦርሳው ውስጥ አገኘሁ፡፡ ሽጉጡን ቶሎ ብሎ
ከቦርሳው ውስጥ አወጣና ካርታን አውጥቶ ጥይቱን ቆጠረ፡፡ ሰባት ጥይት
በቂ ነው፡፡ ካርታውን በቦታው መለሰና ሽጉጠን አቀባብሎ መጠበቂያውን
ለቆ በሩን እያየ ካልቨርትን ይጠባበቅ ጀመር፡፡ ምርጫ የለውም... ሌላ
ምንም ምርጫ የለውም!

ባያስማማስ ጭራሽ ባይስማማስ ፍንክች አልል ቢልስ? የራሱ ጉዳደ:: እዚሁ ይጨርሰዋል፡፡ አለዛም ትቶት ይሄዳል፤ ብቻውን ይጋፈጣቸዋል:: የሚላቸውን ካልሰሙትም ጉዳቸውን ያዝረክርክዋል፡፡ ጊዜ የለውም:: ነገ ሳይመሽ ርብቃን እጁ ማድረግ አለበት አለበለዚያ የሚመጣው አይታወቅም...
ናትናኤል ከአልጋው ግርጌ እንደቆመ የርብቃን መጨረሻ ሲያስብ ሊደርስባት የሚችለውን አደጋ ሲያሰላስል ትንፋሽ አጠረው፡፡

የነገዋ ፀሐይ ከመጥለቋ በፊት ርብቃን እጁ ማግባት አለበት፡፡አለበለዚያ በግርግርታ አንድ ነገር ሲያደርጓት…. - በማታወቀው ምስጢር የመስዋዕት በግ ቢያደርጓት...እርሱ ነፍሰን ስለወደደ የገዛ ደህንነቱን ስለፈለገ ብቻ ቢያጠፏት ከዚያ ወዲያ ምን ሊሆን ህይወቱ?' ናትናኤል ሽጉጡን ጨምድዶ እንደያዘ በተከራዩት ክፍል ውስጥ ካሉት አልጋዎች በአንደኛው ጫፍ ላይ ቁጭ አለና ካልቨርትን ይጠባበቅ : ጀመር፡፡ የራሱ ጉዳይ! ካልተስማማ ትቶት ይሄዳል፡፡ ሊቃወመው ወይ ሊያቆመው ከሞከረ ግን…. የራሱ ጉዳይ! ሞት ነው የሚጠብቀው፡፡ . ናትናኤል የጨመደደውን ሽጉጥ ወደግራ እጁ አዙሮ በላብ የተጠመቀውን የቀኝ እጁን ሱሪው ላይ ሞዥቀና ሽጉጡን ጨሰጠ፡፡

ብዙም ሳይቆይ ካልቨርት ፎጣውን ትከሻው ላይ ጥሎ መንገድ ላይ
ለብሶት የቆየውን በአቧራና በላብ የተበከለ ሽርጥና ሸሚዝ በጥያፌ በሁለት
ጣቶቹ አንጠልጥሎ የተከራዩትን ክፍል በር ከፍቶ ሲገባ የገጠመውን ትርዒት ማመን አቃተው፡፡

“ካልቨርት ምርጫ የለኝም...
የማይሆን ነገር እንዳደርግ
አታስገድደኝ::'' አለ ናትናኤል ከተቀመጠበት¨ ሳይንቀሳቀስ የያዘውን ሽጉጥ ቀና እያደረገ፡፡

“ምንድነው የምትሰራው? ምን ልትሆን ነው?” አለ ካልቨርት የተሸከመውን ቆሻሻ ልብስ ወለሉ ላይ እየዘረገፈ፡፡

“ከአንተ ምንም እርዳታ አልፈልግም፡፡ ርብቃ ያለችበትን ሁኔታ እያወቅሁ በዝምታ መጠበቅ ግን አልችልም:: አዝናለሁ ካልቨርት… ሽጉጥሀን ስለሰረቅሁ፡፡ ግን ምርጫ ያለኝም:: ይሀንን ካላደረግሁ እስረኛሀ እንደምታደርገኝ ግልጽ ነው፡፡”

“ስማ!” አለ ካልቨርት በንዴት መንፈስ ወደፊት አንድ እርምጃ እየተራመደ።

“አ! አ" ናትናኤል የሽጉጠን አፈሙዝ ካልቨርት ላይ ደግኖ ተነስቶ ቆመ፡፡ “እንዳትጠጋኝ፡፡ ሞኝ ነገር አትፈጽም:: ክፉ ነገር መፈጸም አልፈልግም፡፡ ግን ምርጫ የለኝም... ካስገደድከኝ ደፍቼህ ነው የምወጣው፡፡”

ካልቨርት ተስፋ በመቁረጥ አልጋው ላይ ቁጭ አለና ፊቱን ሁለት መዳፎቹ ውስጥ ቀበረ፡፡

ናትናኤል የምትሰራው ጥፋት ነው... ከአሁን ወዲያ ምንም ልትረዳት አትችልም፡፡ እጃቸው ውስጥ ነች፡፡”

“አስፈራራቸዋለሁ! አንተ የምስራችን እንዳይነኩ እንዳስፈራራሃቸው
አስፈራራቸዋለሁ፡፡”

“እናስ ከዛስ?”
“ይለቋታላ! ”
“ሞኝ አትሁን፡፡ እርግጥ ይለቋት ይሆናል… ግን ከለቀቋት ወዲያ እንደ ወጥመድ ነው የሚጠቀሙባት ምክንያቱም ወይ ሰስልክ ወይ በአካል ልትገናኛት መሞከርህ አይቀርም፡፡ እትጠራጠር ይይዙሃል።”

“ከያዙኝ ይያዙኝ ዝም ብዬ ግን አልቀመጥም”
“ባይስማሙስ? ባይለቋትስ?”
“አወጣዋለሁ ምሥጢራቸውን፡፡”

ካልቨርት ቀና ብሎ በቁጣ ፊት ናትናኤልን ገላመጠው፡፡

“እታደርገውም… የምትጎዳው እነሱን አይደለም አፍሪካን ነው፡፡ ነገሮችን አስፍቶ የሚያይ ጭንቅላት ካለህ የምልህ ይገባሃል፡፡ የዚህን ዓይነት ጥፋት ስታጠፋ ደግሞ በዝምታ አልመለከትህም፡፡”

“ሽጉጡ ያለው በእኔ እጅ ነው፡፡”

“ተኩስ! ፈሪ!” ካልቨርት ከተቀመጠበት ተፈናጥሮ ተነሳ፡፡

“ተጠንቀቅ ካልቨርት ማንኛውንም ነገር ማድረግ ይመለሳል ብለህ አታስብ እንደዛፍ ነው በቁምህ የምጥልህ፡፡” ናትናኤል ጥርሱን ነክሶ አፈጠጠ፡፡

የናትናኤልን አዝማሚያ ሲመለከት ካልቨርት ራሱን ነቀነቀና ተመልሶ አልጋው ላይ ተቀመጠ፡፡

“እና አሁን ምን ልታደርግ አሰብክ?” አለ ካልቨርት፡፡
“ጠዋት ስልክ ደውዬ እነግራቸዋለሁ፤ አስጠነቅቃቸዋለሁ፡፡ ከዚያ
ወዲያ የራሳቸው ምርጫ ነው፡፡”
“ናትናኤል እስቲ አስበው በቀላሉ ድምፃችንን ብናጠፋ ሁሉ ነገር
ጊዜውን ጠብቆ መድኃኒት ያገኛል እመነኝ ይለቋታል፡፡”

“ባይሳካስ ዕቅዱ ቢከሽፍስ? ጉዳቸውን ልመሰክር ለመደበቅ እንደሚገድሏት አታውቅም። ካልቨርት መፍጠን አለብኝ! አንድ ነገር ብትሆን ለራሴ ይቅርታ አላደርግለትም::"

“ናትናኤል ስሜትህ ያገባኛል… ምናልባት እኔም በአንተ ቦታ ብሆን ተመሳሳይ ስህተት ለመፈጸም እገፋፋ ይሆናል፡፡ ለምን እንዲህ አናደርግም..ጥፋት ማጥፋታችን ካልቀረ አንስተኛ ጥፋት ይሻላል፡፡” ካልቨርት ያሰበውን እቅድ ለናትናኤል በእርጋታ ተነተነለት፡፡

“አይሆንም! ይይዙናል፡፡”

“ይገባናል ሊይዙን ይችላሉ
እንዳልከው በስልክ ልታስፈራራቸው ብትሞክርም መያዝሀ አይቀርም፡፡ የእኔ መንገድ ይሻላል፡፡ሁልጊዜ የተሻለው አስተማማኙ መንገድ ይበልጥ አደገኛና ይበልጥ አስፈሪ! ይበልጥ አስደንጋጭ የሆነው ጤነኛ ሰው በጤነኛ አእምሮ
የማይመርጠው መንገድ ነው አትጠራጠር፡፡”

“ግን ቢይዙንስ?”
“አለቀልና! ምነው ፈራህ እንዴ?” ካልቨርት ፈገግ አለ፡፡ ««ቢያዙኝም ይያዙኝ አላልክም ዋናው ነገር ፍቅረኛህን ከመዳፋቸው ማውጣታችን የእነሱንም ዕቅድ እለማደናቅፋችን ነው... ለዚህ ደግሞ የተሻለው መንገድ የእኔ ነው:: ትስማማለህ?

ናትናኤል በዝምታ ማውጣትና ማውረድ ያዘ፡፡

“እትፍራ፡፡” አለ ካልቨርት ፈገግ ብሎ፡፡
“አልፈራሁም!” በስጨት አለ ናትናኤል፡፡
“እንግዲያው እንስማማ…” ካልቨርት ቀኝ እጁን ዘረጋለት
“እንተማመን ናትናኤል ደግሞ እሱን ሽጉጥ ዞር አድርገው:: ቢባርቅ
ሆዴን ነው የምትዘረግፈው::”
“ካልቨርት ልታታልለኝ ብትሞክር…” አለ ናትናኤል በጥርጣሬ ፊት ካልቨርት የዘረጋለትን እጁን እየተመለከተ፡፡ “ከአሁን በኋላ ሁለቴ ለማሰብ ጊዜ የለኝም:: አንዲት አጉል እንቅስቃሴ ካደረክ አጓጉል ነው የምትሆነው፡፡”

“ቃል እገባልሃለሁ፡፡”አለ ካልቨርት እጁን ወደፊት እንደዘረጋ፡፡

ናትናኤል ሽጉጡን ወደግራው አሻግሮ የተዘረጋውን የካልቨርትን እጅ በቀኙ ጨበጠው፡፡

“ጥሩ አሁን እቅዳችንን አንድ በአንድ ተንትነን እንነጋገርበት ካጠፋን አይቀር፡፡” አለ ካልቨርት ሁለት ወንበሮች አምጥቶ አንዱን ለናትናኤል አቀብሎት በሁለተኛው ላይ እየተፈናጠጠ፡፡

ፊት ለፊት ቁጭ ብለው በማግስቱ ስለሚፈፅሙት ተግባር አንድ በአንድ ተነጋገሩ ተመካከሩ ፤ ተከራከሩ፤ ተስማሙ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሰማዩ ጥርት ብሏል፡፡ ለጋዋ ፀሐይ ከእንቅልፏ እንደነቃች ሁሉ ከረጅሙ የክረምት ጨለማ በኋላ በሰማዩ ላይ ብቻዋን ትምነሸነሽበታለች:: አለፍ አለፍ እያሉ እንደ
👍1
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሃምሳ_አንድ


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ


....ከዋናው መንገድ ብዙም ሳይርቁ የመኖሪያ ቤቶች ከተደረደሩበት
የሠፈር ውስጥ መንገድ ዳር አንድ ጥግ ላይ መኪናቸውን አቆሙ፡፡

መኪናዋ ጥግ ይዛ እንደቆመች ፡ ናትናኤል የመኪናዋን ሬድዮ ከፈተው፡፡ ጎርናና የጋዜጠኛ ድምፅ መኪናዋ ውስጥ አስተጋባ፡፡

እንዲሁም የአንጎላና የሞሮኮ የሴኔጋልና የቡሩንዲ መሪዎች ከሰዓት በኋላ አቀባበል ሲደረግላቸው እስካሁን ወደ አፍሪካዋ ያልገቡት ሦስት የአፍሪካ መሪዎች ማለትም የሴራሊዮን የጋቦንና
የቡርኪናፋሶ መሪዎች ምሽቱን ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በወጣው ኘሮግራም መሠረት ዛሬ ሰኞ መስከረም አራት ምሽት በሁለት ሰዓት ተኩል ያልገቡት ሦስት የአፍሪካ መሪዎች ማለትም የሴራሊዮን የጋቦንና የቡርኪናፋሶ መሪዎች ምሽቱን ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በወጣው
ፕሮግራም መሠረት ዛሬ ሰኞ መስከረም አራት ምሽት በሁለት ሰዓት ተኩል
ላይ ጠቅላላ ፡ የአፍሪካ መሪዎች የሚገኙበት ስብሰባ ሲከፈት ይቅርታ
አድማጮቻችን አሁን ዘግይቶ የደረሰን ዜና አለ የሴራሊዮኑን መሪ
የያዘችው አውሮኘላን አዲስ አበባ ኢንተርናሽናል አውሮኘላን ማረፊያ
አርፋለች ኘሬዚዳንቱ፡ የክብር ሰላምታ ላቀረበላቸው.. አፀፋውን..…”

ናትናኤል ሬዲዮኑን ዘጋው፡፡
“ሁለት ቀሩ::” አለ ናትናኤል አይኖቹን አቦዝዞ ለራሱ እንደሚናገር ሁል፡፡

ጊዜው እየሄደ . ሰዓቱ እየቀረበ ሲመጣ ተራርቀው የዋሉት ደመናዎች እየተጠራሩ እጅ ለእጅ መያያዝ ጀመሩ:: ቀኑን ሙሉ ማን አለብኝ ብላ ያለርህራሄ ምድሪቷን ስትወቃት የዋለችው ፀሃይ የተባበሩትን
ደመናዎች ማለፍ ሲያቅታት ዙሪያው ቀዝቅዝ ተንፈስ አለ፡፡ ንፋሱ ብቻ
እንደ ወሬ ነጋሪ ከወዲያ ወዲህ ይመላለስ ጀመር፡፡

ሁለት ሰዎች የጫነች የቴሌኮሙኒኬሽን የጥገና መኪና ከአስመራ መንገድ ተነስታ በላይኛው ቤተመንግስት አድርጋ ፒያሳን ለሁላት ከፍላ ሲኒማ ኢትዮጵያ አጠገብ ስትደርስ ሊመሻሽ ተቃርቦ ነበር፡፡ መኪናዋ
አደባባዩን ዞረችና ቁልቁል ወረደች፡፡ ብዙም ሳትርቅ ከአንድ አፓርትመንት
ህንፃ የአጥር በር ፊት ለፊት ቆመች፡፡

“አቤት::” አለ አፈርማ ካፖርት የደረቡ የአፖርትመንቱ የማታ ዘበኛ የብረቱን በር ከፈት አድርገው ብቅ አሉና፡፡

“አንዴ ይክፈቱልን እባክዎት፡፡” አለ ከሾፌሩ ጎን የተቀመጠው ሰው ጭንቅላቱን በመስኮት ብቅ አድርጎ። “ስልከኞች ነን.… የተበላሸ ስልክ
ለመጠገን ነው፡፡”

ሽማግሌው እያቅማሙ የብረቱን በር ወለል አድርገው ከፈቱት፡፡
የቴሌኮሙኒኬሽኗ መኪና ወደ አፖርታማው ግቢ ገብታ ጥግ ይዛ ቆመች፡፡ወዲያው ካኪ ቱታ የለበሱ ሠራተኞች ፈጠን ብለው ከመኪናዋ ወርደው የጥገና መሣሪያዎቻቸውን የያዙባቸውን ቦርሳዎቻቸውንና ሌሎችንም
ዕቃዎቻቸውን አንግበው ወደ አፖርትመንቱ በር ተጣደፉ፡፡

ከመጀመሪያው ደርብ እንደደረሱ ወደግራ ብለው በጠባቡ መተላለፊያ ፊትና ኋላ ራመድ ራመድ እያሉ ቀጠሉ፡፡ 21 የተላጠፈበት በር አጠገብ እንደደረሱ ተያዩ:: ወዲያው በሩን አልፈው 22 የሚል ቁጥር የተለጠፈበትን የሚቀጥለውን በር አንኳኩ፡፡
“አቤት"አለች በሩን የከፈተችው ልጅ እግር ሴት ህፃን ልጅ እንደታቀፈች፡፡

“ከቴሌኮሙኒኬሽን ነው፡፡ በአካባቢው የተበሳሹ ስልኮች አሉ፡፡ የናንተንም ለማየት ነበር፡፡አላት ቀጠን ቀላ ያለው፡፡

“ደህና ነው የኔ ስልክ፡፡” አለች ሴትየዋ በተራ እያየቻቸው፡፡
“ገብተን እንየው?” አላት የመጀመሪያው ሰው፡፡
“ግቡ ግቡ፡፡“ አለች ሴትያዊ የታቀፈቻትን ህፃን ከመሬት አውርዳ በሩን በሰፊው እየከፈታችላቸው::

ካኪ ቱታ የለበሱት ሁለት ሰዎች ተከታትለው ገቡ፡፡
“ቅድም ስንደውል ያነጋገሩን እርሶ ኖት?” አላት ቀጠን ያለው፡፡
“አይ እዚህ አልደወላችሁም::”
“ምናልባት ሌላ ሰው አንስቶት እንዳይሆን…”
“እኔ ብቻ ነኝ ያለሁት በቤቱ፤ ከሷ በስተቀር፡፡” አለች ሴትየዋ ፈገግ
ብሳ የህፃን ልጇን ጭንቅላት እየደባበሰች፡፡ “እዚህ አልደወላችሁም፡፡”
ሰውየው የፈለገውን ያገኘ ይመስል ጊዜ ሳይወስድ ከቱታው ከስ ውስጥ ሽጉጥ አውጥቶ ሴትየዋ ላይ ደገነባት፡፡ ከጎኑ ቆሞ የነበረው ጥቁር ስው ያንጠለጠለውን የሸራ ቦርሳ ወደጎን ጥሎ በሚያስደንቅ ፍጥነት አፏን አፍኖ ወንበር ላይ አስቀመጣት፡፡ ሽጉጥ የያዘው ሰው ማልቀስ የዳዳትን ህፃን ልጅ ከመሬት አንስቶ ታቀፋት።

“ኣይዞሽ አንቺንም ሆነ ልጅሽን የመጉዳት ሃሳብ የለንም:: ነገር ግን ለመጮህ ወይ ለመሮጥ ብትሞክሪ ጥሩ አይሆንም ውጤቱ፡፡” አለ መሣሪያ የያዘው ሰው የሽጉጡን አፈሙዝ ህፃኗ ለስላሳ አንገት ውስጥ እያፍተለተለ፡፡

ሽጉጡን የያዘው ሰው ምልክት ሲሰጠው ኣፍዋን አፍኖ የያዛት ሰው ለቀቃት::

“ምንድነው የምትፈልጉት? የምትፈልጉትን ያዙና ውጡልኝ፡፡” አለች ልጇ አንጎት ስር የተሸጎጠውን ሽጉጥ የተመለከተችው እናት እየተርበተበተች::

“ሌቦችና ቀማኞች እይደለንም፡፡ ጉዳት ልናደርስብሽም አይደለም የመጣነው፡፡ እርዳታሽን ብቻ ነው የምንፈልገው፡፡” አላት ቀጠን ያለው ሰው ህፃኗን እንደታቀፈ ከተቀመጠችበት ወንበር አጠገብ በርከክ ብሎ፡፡
ምንድነው የምትፈልጉት?” አለች ሴትየዋ ኣይኖቿን በሁለቱ አፋኞች ላይ ተራ እያንከራተተች፡፡

እዚህ ጎረቤትሽ 21 ቁጥር ውስጥ ያለችውን ሴት ታውቂያታለሽ?"
አለ ልጇን የታቀፈው ሰውዬ ማልቀስ የጀመረችውን ህፃን በማባበል እየጣረ

“አዎ… ርብቃ ትባላለች… ልጄን ልቀቅልኝ፡፡”

ሀዋኗን የታቀፈው ሰው እየተቁነጠነጠች ያስቸገረችውን ህፃን ለእናቷ ካቅበለ በኋላ ወንበር ስቦ አጠገቧ ተቀመጠ፡፡

“ይህን ሰሞን አይተሻታል?” “ አለ የያዘውን መሣሪያ ከቱታው ኪስ
ውስጥ እየጨመረ::

“ኣሳየኋትም፡፡ ረጅም ጊዜ ነው ካየኋት.. ግን ሌሎች ሰዎች ወደ ክፍሏ ሲገቡና ሲወጠ አይቻለሁ፡፡ ምንድነው የምትፈልጉት ከኔ?” ሴትየዋ ልጇን እቅፍ አድርጋ ይዛ እየደባበሰች አፈጠሰችበት፡፡
“ምን ያህል ይሆናሉ ሰዎቹ?" ጠየቃት፡፡
“የቶቹ ሰዎች?” መልሳ ጠየቀችኑ፡፡
“ክፍሏ ውስጥ ያሉት ሰዎች፡፡"
“እኔ እንጁ ሲገቡና ሲወጡ ነው ያየኋቸው.. ውስጥ ይኑሩ አይኖሩ አላውቅም።

ቀጠን ያለው ሰው በርከክ ካለበት ተነስቶ በፀጥታ ከቆመው ጓደኛው ጋር በእንግሊዝኛ ቋንቋ በሹክሸከታ ያወራ ጀመር፡፡ ወዲያው ፊቱን ወደ
ሴትየዋ መለሰ፡፡

“እንዳልኩሽ እርዳታሽን እንፈልጋለን፡፡ ጉዳት ላይ እንድትወድቂ አንፈልግም። የምልሽን ያለማወላወል መፈጸም አለብሽ፡፡ አለበለዚያ ግን ያልጠበቅነው አደጋ ሊደርስ ይችላል፡፡”

“ምንድነው የምትፈልጉት?” አለች ሴትየዋ ግራ ተጋብታ፡፡ ተራ ሌቦችና ቀማኞች አለመሆናቸውን ስታረጋግጥ ድፍረቷ ተሰባስበላት፡፡ ኮስተር ብላ ተመለከተችው።

“አብረሽን ወደሚቀጥለው ክፍል ትሄጅና በሩን ታንኳኪያለሽ፡፡”
“እኔ የማላውቀው ሰው ቤት ሄጄ ኣላንኳኳም::” አለች ነገሩ ያልጣማት ሴትዮ የልጇን ጭንቅላት ጡቶቿ መሃል ቀብራ፡፡
“ምርጫ የለም፡፡ እምቢ ካልሽን እኛም የማንወደውን እንድንፈጽም እንገደዳለን፡፡” አለ ሽጉጡን የያዘው ሰው ጎንበስ ብሉ የህፃን ልጇን ጭንቅላት እየደባበሰ፡፡ “ተነሽ የፍርሃት መልክ አታሳዬ፡ በሯን
ካንኳኳሽ በኋላ ትጠባበቂያለሽ፡፡ በሩ ሲከፈት…” ማድረግ የሚገባትን ሁሉ
አንድ በአንድ እያስረዳ ክንዷን ይዞ ከተቀመጠችበት አስነሳት፡፡

ሴትየዋ ህፃን ልጇን እንደታቀፈች ከሁለቱ አፋኞቿ ጋር ክክፍሏ ወጥታ ጭር ባለው መተላለፊያ ወደሚቀጥለው ክፍል አመራች፡፡ ከጎረቤቷ ክፍል መዝጊያ እንደደረሱ ሁለቱ ሰዎች በበሩ ግራና ቀኝ ጀርባቸውን ለጥፈው ቆሙ:: ቀጠን ያለው ሰው ሽጉጡን አውጥቶ ደረቱ ላይ ለጥፎ
ያዘው በስተግራዋ ያለው ሰው ደግሞ ከሽራ
👍2
​​ወዳለችበት ክፍል እንድትገባና ድምፃቸውን እንዲያጠፉ ነገራት፡፡ ሴትየዋ
ወደ መኝታ ክፍሏ ስታመራ ካልቨርት በፍጥነት ወደ ዋናው በር ሄዶ
መዝጊያው መቆለፉን ኣረጋገጠ፡፡ ወዲያው መብራቱን አጥፍቶ በስሷ
የጨረቃ ብርሃን እየተመራ ወደ ናትናኤል ተጠጋ፡፡

“እነሱ ናቸው::” አለ ካልቨርት ስማቸውን መጥራት እንደፈራ ሁሉ በሹክሹክታ፡፡
በጨለማው ውስጥ ኣንዳቸው የአንዳቸውን ትንፋሽ እያዳመጡ
ተጠባበቁ፡፡ ከተቆላፈው በር ጀርባ በመተላለፊያው ላይ የእግር ኮቴዎች
ተሰማቸው፡፡ተከትሎም ከጎን ያለው ክፍል ሰር ተበርግዶ ሰዎች ተከታትለው
ሲገቡ ኣዳመጡ፡፡ ካልቨርትና ናትናኤል በጨለማው ውስጥ በፍርሃት
ተያዩ፡፡

የርብቃ ጩኽት ድንገት አስተጋባ፡፡

ናትናኤልና ካልቨርት በድንጋጤ ደርቀው ቀሩ፡፡ መተላለፊያው የእግር ኮቴ ተሰማቸው፡፡ ተጠባበቁ፡፡ የመኪና ድምፅ ሲጥጥ! አለ። ካልቨርት በቀስታ ወደ መስኮቱ ተጠጋ፡፡ ቀደም ብለው ከአፓርትመንቱ አጥር ግቢ በር ላይ ከቆሙት ሁለት ተደርበው ከቆሙ ሌሎች ሁለት መኪናዎች የወረዱ ስምንት ስዎች የያዙትን የጦር መሣሪያ ለመሸሸግ እንኳን ሳይሞክሩ ወደፊት እንደደገኑ የአፓርትመንቱን የአጥር በር አልፈው ተከታትለው ገቡ:: ከግቢው መሃል እንደደረሱ ከአፓርትመንቱ ከወጣ አንድ ሰው ጋር ሰብሰብ ብለው ተነጋገሩ፡፡ ወዲያው ሁለቱ ሰዎች ወደ መጡባቸው
መኪናዎች ሲመለሱ የተቀሩት ወደ አፓርትመንቱ ተጣደፉ፡፡ ካልቨርት ወደ
ናትናኤል ተመልሶ ያየውን ሁሉ ለናትናኤል አንሾካሾከለት፡፡

“አፓርትመንቱን የሚፈትሹ ይመስልሃል?”አለ ናትናኤል ጨለማው
ላይ አፍጥጦ፡፡

“ፈጣሪ አያድርገው::”
“ስንት ሰዓት ነው?” ናትናኤል ጠየቀ፡፡
“ሁለት ከሰላሳ፡፡” አለ ካልቨርት ሰዓቱን ወደ አይኑ አስጠግቶ፡፡

የመኝታ ቤቱ በር ተከፈተ:: ከውስጥ የሚወጣው ደብዛዛ ብርሃን የሳሎኑን ጨለማ ወገግ አደረገው የሆፃኗ እናት አንድ ነገር ታቅፋ ተጠጋቻቸው፡፡

“ተገላገለች፡፡” አለች በሚንቀጠቀጥ ድምፅ፡፡

"ባለ ግሮሰሪዋም አርጊት ቀረብ ብለው የህፃኑን ፊት ትኩር ብለው ተመለከቱት
ካልቨርትና ናትናኤል የሚመልሱት ግራ ገብቷቸው በጨርቅ በተጠቀለለው
አዲስ ህይወት ላይ አፈጠጡ፡፡

ወንድ ልጅ ተገላገለች:፡” አለች የህፃኗ እናት ድጋሚ ወንዶቹ ያልሰሟት ይመስል ዝም ሲሏት አሁንም ከወንዶቹ መልስ አላገኘችም። ሁለቱም ቡዝዝ ብለው እሩቅ ሄዱበት።


ቆንጆ ልጅ እይደለም?” አለች ከተደናገጡት ወንዶች መልስ ያጣችው ሴት ፊቷን ወደ አሮጊቷ መልሳ በአማርኛ::

“የዛሬ ልጆች ቆንጆዎች ናቸው::” አሉ አሮጊቷ አይኖቻቸውን ከህፃኑ ፊት
ላይ ሳያነቅሉ፡፡

ሴቶቹ፡፡ በአማርኛ ቋንቋ የተመላለሱት ያልገባው ካልቨርት ወደ ናትናኤል ፊቱን መልሶ ጠየቀው::

“ምንድነው ያሉት?

"የዛሬ ልጆች ቆንጆዎች ናቸው ነው ያሉት” አለው ናትናኤል የሚታገለውንና የሚተናነቀውን የደስታ እንባ እየታገለ፡፡

💫 ተፈፀመ 💫

#ቆንጆዎቹ ይህን ይመስላል በደራሲ ሠርቅ-ዳ በ 1988 የተዘጋጀው ቆንጆዎቹ ተወዳጅ መጽሐፍ ከዚህ በፊት ያነበባችሁት ለትውስታ ያላነበባችሁት ደግሞ በክፍል በክፍል ተዘጋጅቶ እንድታነቡት ቀርቦ ዛሬ ተጠናቀቀ ሁሌችሁም አስተያየታችሁን ብታደርሱኝ ደስ ይለኛል።

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍31