በዚያ ቀን፣ ልክ የዛሬ 82 ዓመት፣ የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም. በተካሄደው ጭፍጨፋ አዲስ አበባና አካባቢዋ ውስጥ ብቻ ወደ 30 ሺህ ኢትዮጵያውያን ተገድለዋል። የየካቲት 12 ሰማዕታት ቀን፣ ዘንድሮ 82ኛ ዓመቱ ላይ ነው። የካቲት 1929 ዓ.ም.የሚያክል ለኢትዮጵያ የመከራና የጽልመት ወራት ኖሮ አያውቁም። በጣም የሚገርመው፣ በዚሁ በወርኃ የካቲት 1888 ዓመተ ምህረትም ከሰባ ሺህ በላይ ወገኖቻችንን መሥዋዕት አድርገናል። ግፈኛው የንጉሥ ኡምቤርቶ ጦር፣ በጄኔራል ባራቴሪ እየተመራ ሃይማኖት ሊቀለብስ፣ መሬት ሊቆርስ፣ ነፃነታችንን ሊገስ መጥቶ ማጭድና ጎራዴ፣ ጦርና ጋሻ የያዙትን በመድፍና በዘመኑ መሳሪያዎች ፈጃቸው።
ከአርባ አንድ ዓመታት በኋላ ተመልሶ ለወረራ የመጣው በማርሻል ሩዶልፍ ግራዚያኒ የሚመራው የፋሺስትም ጦር፣ ከየካቲት 12 ቀን እስከ የካቲት 14 ድረስ ባሉት ሦስት ቀናት ከሠላሳ ሺህ በላይ ሰላማዊ ኢትዮጵያውያንን ገደላቸው።
#የመታሰቢያ #ሐውልታቸው
ሀውልቱ የወራሪው የጣሊያን ወታደሮች በግፍ የጨፈጨፏቸውን 30ሺ ያህል ሰዎች ለመዘከር የቆመ ነው፡፡ ግራዚያኒ ሰራዊቱን እና መኳንንቱን ጠርቶ ፣ ህዝቡን ሰብስቦ የአሁኑ አዲሰ አበባ ዩኒቨርስቲ ቀደም ሲል ገነተ ልዑል በሚል ይታወቅ በነበረው በአፄ ኃይለስላሴ ቤተ መንግስት ውስጥ የተለመደ የእብሪት ንግግሩን በማሰማት ላይ ነበር፡፡ ግራዚያኒን ለመግደል አመቺ ቦታ እና ጊዜ ሲጠባበቁ የነበሩት አብርሐም ደቦጭ እና ሞገስ አሰግዶም የያዙትን ቦምብ አከታትለው ወረወሩበት፤ ግራዚያኒም ቆሰለ፡፡ ከዚያች ቅፅበት በኋላ በማንኛውም ሁኔታ የተገኘ ኢትዮጵያዊ ሁሉ በግፍ ተጨፈጨፈ፡፡ አዲሰ አበባም በንፁሀን የደም ጎርፍ ተጥለቀለቀች፡፡ በህፃናት ለቅሶ በእናቶች ዋይታ ተዋጠች፡፡ በወቅቱ የተፈጠረው ሁኔታም ኢትዮጵያውያን በድፍረት እና በወኔ ጠላትን እንዲፋለሙ ብርታት ሆናቸው፡፡ እነዚህን ያለርህራሄ የተጨፈጨፉ ንፁሀን ዜጎች ለማሰታወስም ዛሬ በየካቲት 12 ሆስፒታል ፣ በአዲሰ አበባ ዩኒቨርስቲ እና በቀድሞዉ በአንበሳ ግቢ መካከል 6ኪሎ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ የሰማዕታቱ ሃውልት ቆሟል፡፡
በዚህ ሀውልት ቀረፃ ላይ ኢትዮጳያውያን ባለሙያዎችም ተሳትፈዋል፡፡ ሀውልቱ 28 ሜትር ቁመት ያለው ሲሆን ባለ ሶስት ማዕዘንም ነው፡፡ ሀውልቱ የተሰራው በሁለት የዩጎዝላቪያ ዜግነት ያላቸው ባለሙያተኞች ሲሆን በሀውልቱ ላይ ኢትዮጵያውያን በጣሊያን ወታደሮች በግፍ ሲገደሉ የሚያሳዩ ቅርፃ ቅርፆችም ይስተዋላሉ፡፡ ሀውልቱ ከቅርፃ ቅርፆቹ ባሻገር የተለያዩ ፅሁፎችም አሉት፡፡
እባክዎን ካለዎት ጊዜ ላይ ደቂቃዎች ወስደው ይህን ፒቲሽን በመፈረም ለየካቲት 12/1929 ዓ.ም ጭፍጨፋ ሰማእታት ያሎትን አጋርነት ያሳዩ።
ቫቲካንና የጣሊያን መንግስተም ይፋዊ ይቅርታ እንዲጠይቅና ተገቢውን ካሳ እንዲከፍሉ ያድርጉ።
100,000 ፊርማ ነዉ የሚያስፈልገዉ ግን እስካሁን 6558 ብቻ ነው ማግኘት የተቻለው የሁላችንም ጉዳይ ነው ትንሽ ደቂቃ ወስደን እንፈርም
https://www.gopetition.com/petitions/vatican-apology-for-ethiopian-holocaust.html
#ክብር #ለተሰውት #ሰማዕታት……..!!!
ከአርባ አንድ ዓመታት በኋላ ተመልሶ ለወረራ የመጣው በማርሻል ሩዶልፍ ግራዚያኒ የሚመራው የፋሺስትም ጦር፣ ከየካቲት 12 ቀን እስከ የካቲት 14 ድረስ ባሉት ሦስት ቀናት ከሠላሳ ሺህ በላይ ሰላማዊ ኢትዮጵያውያንን ገደላቸው።
#የመታሰቢያ #ሐውልታቸው
ሀውልቱ የወራሪው የጣሊያን ወታደሮች በግፍ የጨፈጨፏቸውን 30ሺ ያህል ሰዎች ለመዘከር የቆመ ነው፡፡ ግራዚያኒ ሰራዊቱን እና መኳንንቱን ጠርቶ ፣ ህዝቡን ሰብስቦ የአሁኑ አዲሰ አበባ ዩኒቨርስቲ ቀደም ሲል ገነተ ልዑል በሚል ይታወቅ በነበረው በአፄ ኃይለስላሴ ቤተ መንግስት ውስጥ የተለመደ የእብሪት ንግግሩን በማሰማት ላይ ነበር፡፡ ግራዚያኒን ለመግደል አመቺ ቦታ እና ጊዜ ሲጠባበቁ የነበሩት አብርሐም ደቦጭ እና ሞገስ አሰግዶም የያዙትን ቦምብ አከታትለው ወረወሩበት፤ ግራዚያኒም ቆሰለ፡፡ ከዚያች ቅፅበት በኋላ በማንኛውም ሁኔታ የተገኘ ኢትዮጵያዊ ሁሉ በግፍ ተጨፈጨፈ፡፡ አዲሰ አበባም በንፁሀን የደም ጎርፍ ተጥለቀለቀች፡፡ በህፃናት ለቅሶ በእናቶች ዋይታ ተዋጠች፡፡ በወቅቱ የተፈጠረው ሁኔታም ኢትዮጵያውያን በድፍረት እና በወኔ ጠላትን እንዲፋለሙ ብርታት ሆናቸው፡፡ እነዚህን ያለርህራሄ የተጨፈጨፉ ንፁሀን ዜጎች ለማሰታወስም ዛሬ በየካቲት 12 ሆስፒታል ፣ በአዲሰ አበባ ዩኒቨርስቲ እና በቀድሞዉ በአንበሳ ግቢ መካከል 6ኪሎ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ የሰማዕታቱ ሃውልት ቆሟል፡፡
በዚህ ሀውልት ቀረፃ ላይ ኢትዮጳያውያን ባለሙያዎችም ተሳትፈዋል፡፡ ሀውልቱ 28 ሜትር ቁመት ያለው ሲሆን ባለ ሶስት ማዕዘንም ነው፡፡ ሀውልቱ የተሰራው በሁለት የዩጎዝላቪያ ዜግነት ያላቸው ባለሙያተኞች ሲሆን በሀውልቱ ላይ ኢትዮጵያውያን በጣሊያን ወታደሮች በግፍ ሲገደሉ የሚያሳዩ ቅርፃ ቅርፆችም ይስተዋላሉ፡፡ ሀውልቱ ከቅርፃ ቅርፆቹ ባሻገር የተለያዩ ፅሁፎችም አሉት፡፡
እባክዎን ካለዎት ጊዜ ላይ ደቂቃዎች ወስደው ይህን ፒቲሽን በመፈረም ለየካቲት 12/1929 ዓ.ም ጭፍጨፋ ሰማእታት ያሎትን አጋርነት ያሳዩ።
ቫቲካንና የጣሊያን መንግስተም ይፋዊ ይቅርታ እንዲጠይቅና ተገቢውን ካሳ እንዲከፍሉ ያድርጉ።
100,000 ፊርማ ነዉ የሚያስፈልገዉ ግን እስካሁን 6558 ብቻ ነው ማግኘት የተቻለው የሁላችንም ጉዳይ ነው ትንሽ ደቂቃ ወስደን እንፈርም
https://www.gopetition.com/petitions/vatican-apology-for-ethiopian-holocaust.html
#ክብር #ለተሰውት #ሰማዕታት……..!!!
GoPetition
Ethiopian Genocide 1935-1941 and Vatican Complicities
We, the undersigned, appeal to the international community...all Governments, the United Nations, the European Union,…
👍1
#ንቀን_ያለፍነው_ቃል
ከለታት አንድ ቀን፣ ወደ ቤቷ ሄድኩኝ
ጥቅል ጎመን አርዳ፣ እንጉዳዩን ጠብሳ
ጋበዘችኝ ምሳ
ሙያዋን አደነቅሁ
ገበታው ሲነሳ
ካያቷ ተዋወቅሁ።
አረጋዊት ናቸው፣ እድሜያቸው የገፋ
ድሮ ልጅ እያሉ፣ አይናቸው የጠፋ
በድሜያቸው በረካ፣ በፅዋቸው ጭላጭ
አምሯቸው ብሩህ፣ ልሳናቸው ምላጭ
ወግ ማውጋት ጀመሩ
ቃል እያለዘቡ
ቃል እየጠረቡ፣ ቃል እያሳመሩ
ሀረግ አለዝበው፣ ዘይቤ እየነቀሱ
በጸጥታ ሞቶ፣ ያላጀብ ተቀብሮ
የተረሳ ታሪክ እየቀሰቀሱ
እንደ መቅረፀ ድምፅ፣ ጆሮየን ጠመድሁት
አጥብቆ ገረመኝ
ያረጋዊቷ ወግ፣ ቅድም ከበላሁት
ከንጉዳዩ ዝልዝል፣ የበለጠ ጣመኝ።
ጸሐፌ ትዛዛት ቸል ብለው ያለፉት
ዜና ነጋሪዎች፣ አይተው የገደፉት
ያገሬን ሰው ገድል፣ መከራ ፍስሐ
ሳልታክት ቀዳሁት፣ ልክ እንዳርብ ውሃ።
ከጥሞናየ ላይ ላፍታ ተፋትቼ
ጋባዤን ፈለግኋት
ፊትለፊቴ አየኋት
ያቻት ያቻትና
ከሶፋው ላይ ሆና
እግሮቿን ዝርግትግት፣ ሰውነቷን ዘና
እንደፊት መስተዋት
ዘመናይ ሞባይሏን፣ ፊቷ ስር ደቅና
ከስልኳ ሰሌዳ፣ ፊደል ትነካለች
ፎቶ ታምሳለች፣ ኢሜል ትልካለች
ያያቷ ጣፋጭ ወግ፣ ላፍታ እንኳ መች ደንቋት
ሜሴንጀር ዋትሳፕ፣ ኢሞ ቴሌግራም
ሁሉን የወሬ ቋት
ትበረብራለች፣
ካሥር አመት በፊት
ለረፍት ከከተማ፣ ወደ ገጠር ሄጄ
ደጅ ላይ ማለዳ፣ ፀሐይ ስር ተጥጄ
አያቴ ብቅ ብሎ
ከተቀመጥሁበት የወይራ ግንድ ላይ፣ ራሱን አዳብሎ
“ያኔ ጎበዝ ሳለሁ” ብሎ ወግ ሲወጥን
አልባሌ ወሬ፣ እኔን የማይመጥን
የሰማሁ ይመስል፣ በኀይል አዛግቼ
ከካፖርቴ ኪስ ውስጥ፣ መጽሐፍ አውጥቼ
(የማርክስ፣ የፍሮይድ ምናልባት የኒቼ?)
ገለብ ገለጥ ሳደርግ፣ እሱ ይህን አይቶ
የጀመረውን ቃል፣ አንጠልጥሎ ትቶ
ለጥናት ነው መሰል፣ እዚህ መቀመጥህ፣
ወግድልኝ በለኝ፣ እንዳልበጠብጥህ”
ብሎ ይወገዳል
አድማጭ ካጣጭ ጋራ ወደሚገኝበት፣ ጠላ ቤት ይሄዳል።
አያቴ ከሞተ፣ አመታት አለፉ
ፀፀት ጭንቅላቴን፣ በብረት መዳፉ
እየኮረኮመኝ
ሀፍረት በሸኮናው፣ እየረመረመኝ
በራሴ ስበግን
ምን ሆኘ ነበር ግን
ምን ነክቶኝ ነበር ግን?
በማለት አጥብቄ ራሴን ስረግም
ይሄውና ዛሬ
ጋባዤን አየኋት፣ ታሪኬን ስትደግም።
አንድም በመሰልቸት፣ አንድም በቸልታ
ወይ ባወቅሁሽ ናቅሁሽ፣ አለያም በወረት
የያዝነውን ዳቦ፣ ቆጥረነው ከኮረት
ጠላ ከሚጠጣ፣ ቆሎ ከሚበላ
እድፍ ከሚለብሰው
ለዐይን ከማይሞላ
ካንድ ስም አልባ ሰው
ምን ጥበብ ይገኛል? በሚል ተዘናግተን
በቻይና ቅፅር ጡብ፣ ጆሯችንን ዘግተን
ልቦና ቆልፈን
ንቀን ያለፍነው ቃል፣ ንቆ ነው ያለፈን።
#ክብር_ለአያቶቻችን_ለተንቀሳቃሽ #ላይብሬራችን
ከለታት አንድ ቀን፣ ወደ ቤቷ ሄድኩኝ
ጥቅል ጎመን አርዳ፣ እንጉዳዩን ጠብሳ
ጋበዘችኝ ምሳ
ሙያዋን አደነቅሁ
ገበታው ሲነሳ
ካያቷ ተዋወቅሁ።
አረጋዊት ናቸው፣ እድሜያቸው የገፋ
ድሮ ልጅ እያሉ፣ አይናቸው የጠፋ
በድሜያቸው በረካ፣ በፅዋቸው ጭላጭ
አምሯቸው ብሩህ፣ ልሳናቸው ምላጭ
ወግ ማውጋት ጀመሩ
ቃል እያለዘቡ
ቃል እየጠረቡ፣ ቃል እያሳመሩ
ሀረግ አለዝበው፣ ዘይቤ እየነቀሱ
በጸጥታ ሞቶ፣ ያላጀብ ተቀብሮ
የተረሳ ታሪክ እየቀሰቀሱ
እንደ መቅረፀ ድምፅ፣ ጆሮየን ጠመድሁት
አጥብቆ ገረመኝ
ያረጋዊቷ ወግ፣ ቅድም ከበላሁት
ከንጉዳዩ ዝልዝል፣ የበለጠ ጣመኝ።
ጸሐፌ ትዛዛት ቸል ብለው ያለፉት
ዜና ነጋሪዎች፣ አይተው የገደፉት
ያገሬን ሰው ገድል፣ መከራ ፍስሐ
ሳልታክት ቀዳሁት፣ ልክ እንዳርብ ውሃ።
ከጥሞናየ ላይ ላፍታ ተፋትቼ
ጋባዤን ፈለግኋት
ፊትለፊቴ አየኋት
ያቻት ያቻትና
ከሶፋው ላይ ሆና
እግሮቿን ዝርግትግት፣ ሰውነቷን ዘና
እንደፊት መስተዋት
ዘመናይ ሞባይሏን፣ ፊቷ ስር ደቅና
ከስልኳ ሰሌዳ፣ ፊደል ትነካለች
ፎቶ ታምሳለች፣ ኢሜል ትልካለች
ያያቷ ጣፋጭ ወግ፣ ላፍታ እንኳ መች ደንቋት
ሜሴንጀር ዋትሳፕ፣ ኢሞ ቴሌግራም
ሁሉን የወሬ ቋት
ትበረብራለች፣
ካሥር አመት በፊት
ለረፍት ከከተማ፣ ወደ ገጠር ሄጄ
ደጅ ላይ ማለዳ፣ ፀሐይ ስር ተጥጄ
አያቴ ብቅ ብሎ
ከተቀመጥሁበት የወይራ ግንድ ላይ፣ ራሱን አዳብሎ
“ያኔ ጎበዝ ሳለሁ” ብሎ ወግ ሲወጥን
አልባሌ ወሬ፣ እኔን የማይመጥን
የሰማሁ ይመስል፣ በኀይል አዛግቼ
ከካፖርቴ ኪስ ውስጥ፣ መጽሐፍ አውጥቼ
(የማርክስ፣ የፍሮይድ ምናልባት የኒቼ?)
ገለብ ገለጥ ሳደርግ፣ እሱ ይህን አይቶ
የጀመረውን ቃል፣ አንጠልጥሎ ትቶ
ለጥናት ነው መሰል፣ እዚህ መቀመጥህ፣
ወግድልኝ በለኝ፣ እንዳልበጠብጥህ”
ብሎ ይወገዳል
አድማጭ ካጣጭ ጋራ ወደሚገኝበት፣ ጠላ ቤት ይሄዳል።
አያቴ ከሞተ፣ አመታት አለፉ
ፀፀት ጭንቅላቴን፣ በብረት መዳፉ
እየኮረኮመኝ
ሀፍረት በሸኮናው፣ እየረመረመኝ
በራሴ ስበግን
ምን ሆኘ ነበር ግን
ምን ነክቶኝ ነበር ግን?
በማለት አጥብቄ ራሴን ስረግም
ይሄውና ዛሬ
ጋባዤን አየኋት፣ ታሪኬን ስትደግም።
አንድም በመሰልቸት፣ አንድም በቸልታ
ወይ ባወቅሁሽ ናቅሁሽ፣ አለያም በወረት
የያዝነውን ዳቦ፣ ቆጥረነው ከኮረት
ጠላ ከሚጠጣ፣ ቆሎ ከሚበላ
እድፍ ከሚለብሰው
ለዐይን ከማይሞላ
ካንድ ስም አልባ ሰው
ምን ጥበብ ይገኛል? በሚል ተዘናግተን
በቻይና ቅፅር ጡብ፣ ጆሯችንን ዘግተን
ልቦና ቆልፈን
ንቀን ያለፍነው ቃል፣ ንቆ ነው ያለፈን።
#ክብር_ለአያቶቻችን_ለተንቀሳቃሽ #ላይብሬራችን