አትሮኖስ
286K subscribers
117 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#የታካሚው_ማስታወሻ


#ክፍል_ስምንት


#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)

ሜሪ፣ ቆንጅዬ የማሂ ጓደኛና የመስሪያ ቤታችን ሰራተኛ ናት።በቁንጅና አይተናነሱም፡፡ ሜሪ ግን፣ በእድሜ ልጅ ነች። ገና እንቡጥ፡፡ልጅነቷ ተጨማሪ ውበት ሆኗታል። ማሂ አንዳንዴ፣ በአንድ ቤትማ ሁለት ንግስት አይኖርም እያለች ትቀልዳለች፡፡ እኔን ጨምሮ፣ ብዙ ወንዶች ዐይናችንን ሜሪ ላይ ጥለንባታል፡፡ አለቃዬን ግን በፍፁም አልጠረጠርኩም ነበር፡፡

“እሱን ማን ጠየቀሽ? አሁን አንቺን ነው ማግኘት የፈለኩት፡፡”አለቃዬ እንደመቆጣት አሉ፡፡

“ምነው አልሰጥም አለችህ እንዴ?” ብላ ክትክት ብላ ሳቀች፡፡

“ስነ ስርዐት! እንግዲህ አትጨማለቂ፡፡ ስንት ሰዓት ልምጣና ልውሰድሽ?”

“የአንተ መምጣት አያስፈልገኝም፡፡ በትራንስፖርት እመጣለሁ።ከመጣሁ እደውልልሃለው። ቻው።” መልስ ሳትጣብቅ ስልኩን ዘጋችው፡፡ፊቷ በደስታና በድል አድራጊነት በርቷል እኔ የምፈራቸውና ማከብራቸው አለቃዬን፣ ፀሃፊያቸው እንዴት እንዲህ ተዳፈረቻቸው...? ከስራ ውጪ ሌላ ግንኙነት አላቸው ማለት ነው? ስልኩን እንደዘጋች፣ ፋታ አልስጠኋትም፡፡ በጥያቄ አጣድፋት ጀመር፡፡
“አንቺ፣ ጋሽ ሃይሌን፣ አለቃችንን ነው እንዲህ እየተመናቀርሽ ምታዋሪያቸው..?” ዐይኗ ላይ አፍጥጬ ጠየኳት፡፡

“አዎ፡፡ ምን አጠፋሁ?”

ትንሽ እንኳ ክብር የለሽም...? አለቃሽ ናቸውኮ፡፡ ሌላው ቢቀር አባትሽ ይሆናሉ፡፡ እላያቸው ላይ እኮ ነው ስልኩን የዘጋችው። ሲጀመር እንዴት ደወሉልሽ፣ ትግባባላችሁ?”

“ታዲያ ባንግባባ ምን ያስደውለዋል?፡፡ የዛሬን አያድርገውና ከስራ አይጠፋም ነበር።”

“ምን ማለት ነው? እስቲ በደንብ አስረጂኝ፤ ምንድን ነው ማላውቀው ነገር?”

“ከኔ ስር አይጠፋም ነበራ...! ከኔ ጋር መሆን ኩራቱ ነበር።ከስራ ሲወጣ፣ ከተማውን ሚዞረው እኔን ይዞ ነበር :: ቅዳሜና እሁድ ደግሞ፣ ሶደሬ፣ ላንጋኖ፣”

“ትዳር የለውም እንዴ?” እኔም እንደሷ አንተ ማለት ጀመርኩ።

“ባለትዳር አይዝናናም?” እየሳቀች መልሳ ጠየቀችኝ፡፡ ይሄን አታውቅም ቂል ብላ፣ ምትስቅብኝ መሰለኝ፡፡

“አይ፣ በጣም ጀንትል ነው፣ እንደምታወሪው አይነት ሰው
አይመስልም፡፡”

“ኪ....ኪ...ኪ..!” እግሮቿን እያነሳች፣ በረጅሙ ሳቀችብኝ፡፡

“ምነው ሳቅሽ?”

“ሃይላን ነው፣ ጀንትል ያልከው፣ ሴት ካየ ሳይመርጥ ሚልከሰከስ፣ እዚህ ግቢ ያሉትን ሴቶች ሳያማርጥ ካልተኛሁሽ የሚል፣ስሜቱን መቆጣጠር ማይችል ዝርክርክ? እኔን ሚያናድዱኝና ሚያበሳጨኝ ሴቶቹ ናቸው። ጓደኛዋን እንደተኛት እያወቀች፣እግራቸውን ከፍተው አብራውት ሚተኙት፡፡”

“ማለት፣ ጋሽ ሃይሌ፣ ከስታፎች ጋር ይወጣል እያልሽኝ ነው?”

“እንዴ...፣ አገር ያወቀውን ፀሃይ የሞቀውን አንተ አላውቅም እያልከኝ ነው?”

“እውነቴን ነው፤ እኔ ምንም አላውቅም፡፡”

“ስም ልጥራልህ እንዴ...፣ ፌቨን፣ ሳራ፣ ቤቲ፣ አሁን ደግሞ ተረኛዋ ሜሪ ነች፡፡ አሁን ከእርሷ ጋር ከንፏል።” ብስጭት እያለች ነው፡፡

“ቆይ፣ ሚስቱን አይፈራም እንዴ?"

“ሚስትና ልጆቹ አዲስ አበባ ናቸው። ማን ያየኛል ብሉ እዚህ ይንዘላዘላል እንጂ፡፡”

“በስማም! ቢያንስ አይደብረውም...?”

“አይደብረውም አልከኝ...? አሁን ጭራሽ ሜሪን ሚስቴን ፈትቼ ካላገባሁሽ እያላት ነው፡፡ ደግሞ መጥታ ትነግረኛለች።”

“እና ሜሪ አመነችው...?”

“አዎና፡፡ የሆነች ጅል፣ ከርፋፋ፡፡ ቀላል አምናዋለች፡፡ ደሞ ድንግል ናት፡፡”

“እና ድንድልናዋን ሰጠችው...?

ወጣችለት...?” ምሰማው ሁሉ
ማመን አቅቶኛል፡፡

“እንጃባቷ...! ሰጥታው ነው ሚሆነው፡፡ የሆነች ነፈዝ፡፡” በጣም የልብ ጓደኛሞች ነበር ሚመስሉኝ፡፡ ከአነጋገሯ ግን ሌላ ነገር ተሰማኝ፡፡

“እኔ ምልሽ፣ አንችም ተነካክተሽ ነበር እንዴ? በጣም የቀናሽ ትመስያለሽኮ፡፡"

“ማ...? እኔ ማሂ ቆንጆ ከዚ ሼባ ጋር? በስማም አንተ!”

“አይ እንደምታወሪለት ከሆነ፣ ሰውየው የሆነ ያሰራው ነገርማ አለው፡፡”

“ብወደውማ፣ መጀመሪያውኑ እሷን አላሰተዋውቀውም ነበር፡፡”

“እሺ ግን እንዴት ከአንድ አንድ ከያቤዝ ጋር ነሽ' ብሎ ሊገምት ቻለ?”

“እኔንጃ፡፡ ምንአልባት፣ መጀመሪያ የመጣህ ሰሞን፣ “ለመጀመሪያ
ግዜ ደስ ሚል ወንድ ልጅ ቀጠራችሁ ብዬው ነበር መሰለኝ፡፡ አልፎ አልፎ፣ ያምራል ያልሽው ልጅ ተመቸሽ?' እያለ ይቀልድብኛል፡፡ ከዛ ተነስቶ ይመስለኛል።”

“አ.ሃ... ለዛ ነው? ሌላስ ምን ያውቃል? ሁሉንም ነገር ነግረሽዋላ?”

“ያምሃል እንዴ? ምን ብዬ ነው ምነግረው?” የተቆጣች ለመምሰል ሞከረች፡፡ ፊቷ ግን በፈገግታ እንደተሞላ ነው፡፡ ውስጤ በንዴት ሲጨስ እየተሰማኝ ነው፡፡ ቀልዳብኛለች! ሚስጥር ይሁን
ተባብለን ነበር፡፡ አሁን ምንድነው ሚሆነው? ምንድነው ማደርገው?
በሃሳብ ጭልጥ አልኩ፡፡

“ተጫወት እንጂ! በሃሳብ ነጎድክ።”

“ግን ቢያንስ ስለሰውየው ይሄን ሁሉ ነገር እንዴት አልነገርሺኝም...?” የሆነች ጨዋታ እንደተጫወተች እየተሰማኝ ነው፡፡
“ግቢው ውስጥ ሁሉም ሚያውቀው ስለሆነ፣ አንተም ምታውቅ መስሉኝ፡፡”

“እርግጠኛ ነሽ፣ ለዛ ብቻ ነው ያልነገርሺኝ?”

“እንዴ...! ሌላ ምን ምክንያት ይኖረኛል?”

“እሱንማ አንቺ ነሽ ምታውቂው፡፡”

ስልኬ መዝፈን ጀመረች፡፡ ከሱሪ ኪሴ ውስጥ አውጥቼ ተመለከትኩ፡፡ ሳምሶን ነው፡፡ ስልኩን አነሳሁት፡፡

“ጎረምሳው፣ ምነው በእሁዱ ድምፅህን አጠፍህ? ማታ ይዘህ . ነው እንዴ ያደርከው...?

“እንደውም ደብሮኝ ልደውልልህ ስል ነው የደወልከው፡፡”

“ምነው? ምን አጋጠመህ ወጣቱ...?”

“ዝም ብሎ ድብርት ቢጤ ነው፡፡ የት ነህ ልምጣ...?”

“እቤት ነኝ ና።”

“መጣሁ ጠብቀኝ፡፡” ስልኩን ዘጋሁት፡፡

“ምን መሆንህ ነው? ምን እያደረክ ነው?” አለችኝ ማሂ እንዳኮረፈች ሆና።

“መሄድ አለብኝ፡፡ የማላውቀው ነገር ውስጥ ገብቼ እየዋኘው እንደሆነ ተሰምቶኛል፡፡ ቢያንስ ምን እየተካሄደ እንደሆነ ማወቅ አለብኝ፡፡

ተነሺ እንሂድ፡፡”

የጠጣነውን ጁስ ሂሳብ አየሁት፡፡ ሰማንያ ስምንት ብር፡፡ መቶ ብር አስቀምጬ፣ መልስ ሳልጠብቅ ተነሳሁ። ማሂም ተከትላኝ ተነሳች፡፡

ከግቢው በር ላይ ካለው መኪና ማቆሚያ ጋር ሄድን የቆመችው ቪትስ መኪናዬ ውስጥ ገባን፡፡

“የት ላድርስሽ?”

“አንተ የት ነው ምትሄደው?”

“ሳወራ እየሰማሽኝ አልነበር? ሳምሶን ጋር ነዋ፡፡” ተነጫነጭኩ፡፡

“እኔም አብሬህ እሄዳለሁ።”

“አይሆንም!” አምባረኩባት፡፡

“ለምን?”

“ብቻዬን ላናግረው ፈልጋለሁ፡፡”

“ቆይ ምንድነው እንዲህ የቀያየረህ? ምንድነው ይሄን ያክል ያናደደህ?”

“ከዚህ በላይ ምን ታደርጊኛለሽ? ምን አስበሽ ነው ይሄን ሁሉ ሚስጥር እስካሁን የደበቅሽኝ?” መኪናዬን አስነስቼ ከግቢ እየወጣሁ።

“ሆን ብዬ አልደበኩህም፡፡ ምታውቅ ስለመሰለኝ ነው አልኩህ እኮ!”

“ሃ...ሃ...ሃ...! እረ ባክሽ? አንቺ ወሬ ደግመሽ የምታወሪ ልጅ፣ገና ለገና ሰምቶ ይሆናል ብለሽ፣ ይሄን ሁሉ ወሬ ዝም አልሽ?!. ጥሩ ቀልደኛ ሆነሻል ባክሽ፡፡ አሁን የት ላድርስሽ?”

“በታክሲ መሄድ እችላለሁ፡፡ እዚህ ጋር አውርደኝ፡፡”

“እሺ!”

ንዴት በውስጤ እየፈላ ነው፡፡ ሳላንገራግር የመንገዱን ዳር ይዤ አቆምኩላት፡፡ ቦርሳዋን ከኋላ ወንበር አንስታ ተመናጭቃ ወረደች፡፡በቀጥታ ወደ ሳሚ ጋር ሄድኩና ተያይዘን ብቻችንን ስንሆን
የምናዘወትርበት ቤት ሄድን፡፡ ቢራ እየጠጣን ፑል መጫወት ጀመርን፡፡
ለወትሮው ስንጫወት በመበሻሸቅ እንሳሳቃለን፡፡ ዛሬ ቢቀልድብኝም
መልስ አልሰጠውም፡፡ ውስጤ ነገር ገብቷል፡፡ ማሂ የነገረችኝን ነገር
👍6
#የታካሚው_ማስታወሻ


#ክፍል_ዘጠኝ


#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)

አልደነቀውም፡፡ጭራሽ፣ወሬ ሊያስቀይረኝ ይሞክራል። እርሷ ጋር ደውሎ፣ በስልክ ስለኔ ያወሩትን ነገር ነገርኩት፡፡

"ጠብቄው ነበር!”

“ምኑን?”

“ይሄንን ነዋ፡፡ ልጅቷ ነገሯ አላማረኝም ነበር፡፡”

እንዴት?”

“በቃ አለባበሷ፣ ቢሮህ መመላለሷ፣ ብቻ ነግሬህ ነበር፡፡”

“ምን ብለህ?”

“ቀስ በል! አትቸኩል፡፡ የጅብ ችኩል ቀንድ ይነክሳል!' ብዬ ነግሬህ ነበር፡፡”

“እና ማሂ ያለችው እውነት ነው፡፡ ሰውዬው እንዲህ ያደርጋል?”

“ወንድሜ፣ ሰውየው በተወለደበት ቀዳዳ ተለክፏል፡፡ መሞቻውም እዛው እንደሚሆን ግልፅ ነው፡፡ ካ...ካ...ካ...፡፡ በዚህ እድሜ፣ሚስትና ልጆቹን አስቀምጦ ግቢ ውስጥ ያሉትን ሴቶች ሁሉ አትንኩብኝ ማለት...፣ እንደውም ደግ አደረክ! አንተ ወጣት ነህ፣ አላገበህም፣
መዝናናቱም፣ ሁሉም ባንተ ያምራል፡፡ እርሳው ባክህ፡፡ እንደውም ምሳችንን በልተን ሶደሬ እንሂድና ፈታ እንበል፡፡ ማሂንም ይዘናት እንሂድና ስትደጋግማት ታድራለህ፡፡ የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም፡፡
ካ...ካ...ካ...”

“ትቀልዳለህ አንተ፡፡”

“የምሬን ነው፡፡” አሁን እኔም በአለቃዬ ድርጊት መናደድ ጀምሪያለሁ፡፡ እልህ እተሰማኝ ነው፡፡

“እሺ ደውልላት፡፡”

ለማሂ ደወለላት። አታነሳም፡፡ የኔን መኪና አቁመን በሱ መኪና ሶደሬ ሄድን፡፡ በፍልውሃ ታጠብን፣ እኔ ዋኘሁ፡፡ ሶደሬ ብቻችንን ስንመጣ እንደሚያደርገው፣ በሲጋራው ምትክ ሺሻ አጨስ፡፡ ወደ መዋኛው ገንዳ ተመልስን ዶሮ አሩስቶ አዘን በቢራ እያወራረድን በላን፡፡ ሰውዬው ለሰው ያለው ንቀትና ድርጊቶች አበሳጭተውኛል። የሳሚ አይዞህ
ሲጨመርበት፣ ውስጤ ተጋፈጠው ተጋፈጠው እያለኝ ነው፡፡ “ድርጅቱ
የቤተሰቡ ሀብት ቢሆን ሰራተኞቹንም የግል ንብረቱ አደረጋቸው እንዴ?፣
ቀጠራቸው እንጂ አላገባቸው...፣ ደግሞ አንዷ ብትበቃውስ፣ ሁሉን አትንኩብኝ፣ ጭራሽ የጣልኩትንም አታንሱ..? ቅሌታም! ደስ ያለኝን አማርጣለሁ፡፡ እንደውም፣ ማሂንም ጨምሬ እልሁን አስጨርሰዋለሁ።”ለራሴ አልኩኝ፡፡ ማታ እቤት ስገባ ምሽት ሶስት ሰአት አልፎ ነበር፡፡ደክሞኝ ስለነበር ወዲያው እንቅልፍ ወሰደኝ፡፡

የተፈጠረውን ነገር አዕምሮዬ ሊረሳው አልቻለም፡፡ የሆነ ድራማ እየተሰራብኝ እንደሆን አሰላስላለሁ፡፡ “የት ነሽ...? ከማን ጋር ነሽ...? ካልተገናኝን...?” ያለጥርጥር ከሰውየው ጋር ግንኙነት ነበራቸው፡፡ያለምክንያት እንደዛ አላንጓጠጠችውም፡፡ ሰውዬው ከእርሷ ጋር ከርሞ፣ እንደዘበት አሽቀንጥሮ በሜሪ ተክቶ አቃጥሏታል፡፡ ለዛ ነበረ ሜሪን ጅል፣
ነፈዝ እያለች ስታጣጥላት የነበረው፡፡ መጫወቻ ኳሷ አድርጋ፣ አለቃዬን
በኔ እያስቀናችና እያበሸቀችው ነበር፡፡ እኔ ጅሉ፣ እንደፈለገችው ተወንኩላት፡፡ ወይኔ ተኩቻው! አጠምዳታለሁ ብዬ ሄጄ፣ የእርሷ ወጥመድ ውስጥ ሰተት ብዬ ልግባላት? ፀባዩን የቀየረብኝ ይሄን አውቆ
ነበር ለካ..። ግን ቀንቶ ነው? ወይስ አሁንም ይፈልጋታል..? ወይኔ፣ ተኩቻው!! እቺ ብሽቅ እንዲህ ትጫወትብኝ፡፡

ስራ መሄድ ያስጠላኝ ጀምሯል። ግን እንደምንም እመላለሳለሁ፡፡ ተነሳሽነቴምና ትኩረቴም ከሞተ ቆይቷል። ከአለቃዬም ሆነ ከሌላ ሰራተኛ፣ ምንም ያየሁት አዲስ ነገር የለም፡፡ ውስጤ ግን እንደ ክረምት
ቀዝቅዟል፡፡ ተኮማትሯል፡፡ ሳሚ ቢሮ እየመጣ ሻይ እንድንጠጣ ይዞኝ
ይወጣል፡፡ እንደበፊቱ መሳቅ መጫወቴ ጠፍቷል። ውስጤ መጥፎና አስጨናቂ ሃሳቦችን እየመረጠ ያመነዥጋል፡፡ ስትስልልህ ነበር የከረመችው፤ ሰውየው ሊያጠቃህ አድፍጧል!' እያለ ጭንላቴ
ያስጨንቀኛል፡፡ አሁን፣ ለጨዋታዎች ስሜት አልባ ሆኛለሁ፡፡ ማሂም ማኩረፌን ስታይሉ ፣ ቢሮዬ ተመላልሳ፣ ይቅርታ ጠየቀችኝ፡፡ ሻይ እንድንጠጣ ጠየቀችኝ፡፡ አይሆንም አልኳዋት፡፡ እንደውም፣ ሁለተኛ
ቢሮዬ እንዳትመጣ፣ ላገኛት እንደማልፈልግ አምርሬ ነገርኳት፤ ቢሮዬ
መምጣት አቆመች፡፡

ከግዜ ወደግዜ ያለ በቂ ምክንያት መናደዴ፣ መበሳጨቴ እየተባባሰ መጣ፡፡ ስራ ስለመልቀቅ ማሰብ ጀመርኩ፡፡ ከዚህ በፊት ስራ በማቆሜ ምክንያት ያደረስኩትን ጉዳት በማስታወስ ውስጤን እንዲረጋጋ ታገልኩት። ስራዬ ግን እንደቀደመው አስደሳች አልሆን አለኝ፡፡ ከነ ሳሚ ጋር ወጥቼ መዝናናትን አቆምኩኝ፡፡ በምትኩ ደብረዘይት እየተመላለስኩ ጫት በመቃም ከድባቴዬ ለመሸሽ ሞክራለሁ፡፡ በተደጋጋሚ ምቅምበት ጫት ቤት አሌክስና ሃብታሙ ሚባሉ ጉደኛሞችን ተግባባሁ፡፡ አሌክስ
ሃብታሙን ዶክ እያለ ይጠራዋል። አሌክስ በጣም ፈጣን፣ ተጫዋችና ከሰው ጋር መግባባት ደስ ሚለው ሰው ነው፡፡ ቀልድ ሲያወራ አጠገቡ የተቀመጡ ሁሉ እንዲሰማው ጮክ ብሎ እንድናዳምጠው በዐይኑ እየጋበዘ ነው፡፡

“ትናንት ማታ የተዋወኳት ቺክ ውበት!፣ ወይኔ...!” ብሎ አሌክስ ለሁላችንም እንደሚያወራ በየተራ ተመለከተን፡፡

“ስንት ሰዓት? ትናንት እዚህ አብረን አልነበርን?” ሃብታሙ ጠየቀ፡፡

“ከዚህ እንደወጣን፣ ጨብሲ ሳንል ጥለኸኝ ላሽ አላልክም?”

“እ...፣ እሺ፡፡”

“የጨብሲ ስላልነበረኝ፣ በወክ ልሰብረው ብዬ ስዞር፣ የሆነች ልዕልት ምትመስል ቺክ አላገኝም፡፡ ወይኔ..፣ ወይኔ..፣ ወይኔ ዐይን! ስታያት በድንጋጤ ደንዝዘህ ትቀራለህ፡፡” ሲያወራ በመደነቅ ግንባሩን
ይዞ እያወዛወዘ ነው፡፡

“እሺ፡፡ ከዛስ ከምን አደረስካት ታዲያ?”

“በስማም ፣ ሞትኩባታ! ጭውቴው ደግሞ እንዴት ስክት ስክት እንዳለልኝ፡፡ ነገረ ስራዬ ለራሴ ገርሞኝ፣ እቤት ከገባሁ በኋላ ስስቅ ነበር።”

“ወሬ አታጣ ! ድሮስ ምላሳም አይደለህ? ምን ብለሃት ነው፣እንዲህ የተገረምከው?”

“ድንገት እጇ ላይ ተጠምጥሜ፣ 'የኔ ልዕልት መሳይ፣ በናትሽ ምሪኝ በናትሽ?” ብዬ ስለምናት፣ መጀመሪያ “ምን ሆንክ?” አለችኝ ደንግጣ፡፡ 'ይኼን ውብ ዐይንሽን ሳይ፣ የእኔ ዐይን አፍሮ ነው መሰል
አላይ አለኝ፣ ብዥ አለብኝ፡፡ ዐይኔን ልጨፍነውና፣ እባክሽን ምሪኝ?” ስላት በሳቅ ሞተች?!” ብሎ ሲስቅ፣ ሁላችንም በድርጊቱ አብረነው ሳቅን፡፡ አሳሳቁ ሰው ላይ ይጋባል፡፡ የዐይኖቹን ትንንሽነትና በራሱ ላይ መቀለዱ ደግሞ፣ የበለጠ እንድንስቅ አደረገን፡፡ ስግባባቸው፤ ሃብታሙ፣ የእንስሳት ሃኪም እንደሆነ አወኩ። አሌክስ ደግሞ የተገኘውን ተባራሪ ስራ ሚስራ አፈ ቀላጤ።

አንድ ቅዳሜ ምሽት፣ አሌክስ ወጥተን የጨብሲ አንድ ሁለት ካልጋበዝኩህ ሞቼ እገኛለሁ ብሎ ድርቅ አለብኝ፡፡ እሺ ብዬው አብረን ወጣን፡፡ እየጠጣን በአስቂኝ ጨዋታዎች የታጀበ ደስ ሚል ምሽት
አሳለፍኩ፡፡ እርሱ ልጋብዝህ ብሎ ይዞኝ ወጥቶ፣ ሂሳቡን ጓደኛው ሃብታሙ ከፈለ፡፡ ስልክ ተለዋወጥን፡፡ ጓደኛሞች ሆንን፡፡ አሌክስ በቀላሉ ጎትቶ ከነሱ ጋር ቀላቀለኝ፡ከነሱ ጋር ስሆን፣ ከአስጨናቂ ሃሳቦቼ
እረፍት ስለማገኝ እኔም ደስተኛ ሆንኩ፡፡ ቅዳሜና እሁድ ውሎና አዳሬ ቢሾፍቱ ሆነ፡፡ ገና ሰኞ ስራ ስገባ ቅዳሜ ትናፍቀኛለች፡፡ ከነማሂ ጋር ካሳለፍኩ፣ ስድስት ሳምንት አለፈኝ፡፡ ሳሚ በተደጋጋሚ በአካልም በስልክም ምነው ጠፋህ ሲለኝ፣ ቢሾፍቱ የራሴን ስራ ለመጀመር ስላሰብኩ፣ ቅዳሜና እሁድ ያን ለማመቻቸት እዛ እንደማሳልፍ ነገርኩት።
ምን ስራ ልትጀምር ነው?' ሲለኝ፣ ሲያልቅ ብታየው ይሻላል፤ አልኩት፡፡ እሺ ብሎ ተወኝ፡፡

ከእንቅልፌ ስነቃ ከንጋቱ አንድ ሰዓት ተኩል ሆኗል፡፡ ማታ ስጠጣ ያደርኩበት ጭንቅላቴን ይወቅረኛል፡፡ ከፍተኛ ድካምና ድባቴ እየተሰማኝ ነው፡፡ የሰውነቴ መዛል ከእንቅልፍ የተነሳሁ ሳይሆን፣ ሃያ አራት ሰዓት ካለረፍት ስስራ ያደርኩ ነው ሚመስለው፡፡ ስራ መሄድ እንዳለብኝ ሳስብ እንባዬ መጣ፡፡ የፈለገው ይምጣ ብዬ
👍41
#የታካሚው_ማስታወሻ


#ክፍል_አስር


#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)

ስራ አርፍጄ ገባሁ፡፡ ላለባበሴ ትኩረት መስጠት አቁሚያለሁ።ትንሽ እንደተቀመጥኩ ማሂ ቢሮዬ ገባች፡፡

“እንዴት ነህ?”

“አለሁ፡፡ ምን ልታዘዝ?”

“ማወራህ ጉዳይ አለኝ፡፡ ሻይ ቤት መሄድ እንችላለን?”

“የሚያገናኘን የቢሮ ጉዳይ መሰለኝ፣ እዛ አልሄድም፡፡የምታወሪው ካለሽ፣ እዚሁ ማውራት ትችያለሽ፡፡”

“የቢሮ ጉዳይ አይደለም፡፡ የእኔና ያንተ የግል ጉዳይ ነው።”

“ማለት?"

“ግንኙነታችንን ማቆም ማንችልበት ነገር ተፈጥሯል፡፡ ላወራህ ፈልጋለሁ፡፡” ምን ለማለት እንደፈለገች ገመትኩ፡፡ አዞረኝ። ለቅፅበት በውስጤ ያሰብኩትን እውነት አታድርገው ብዬ ፀለይኩ፡፡ ደሜ ቀዝቅዞ
በድን ስሆን ተሰማኝ፡፡ ለተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ፣ ቀስ ብዬ ተነስቼ እንዳለችኝ ሻይ ቤት ሄድን፡፡ ፈንጠር ያለ ቦታ መርጬ ተቀመጥኩና፣

አረገዝኩ ልትዪኝ ባልሆነ...!” አልኳት እንደተቀመጥን፡፡

“አዎ ልልህ ነው፡፡ የወር አበባዬ ከመጣ ወር አልፎታል፡፡ አርግዣለሁ፡፡”

“ስለዚህ ያንተ ነው ልትዪኝ ነው?” ዐይኔ ጨለመብኝ::

“እና ከማን ሊሆን ይችላል? ምን ማለት ፈልገህ ነው? ቆይ ግን አንተ እኔን እንዴት ነው ምታስበኝ?” ተንጨረጨረች፡፡

“ቀስ በይ አትጩሂ! ይኸውልሽ ማሂ፣ አሁን ከማን ነው ሚለውን እንርሳው፣ ያንተ ነው ካልሽኝ ግን፣ እኔ በዚህ ሰዓት አባት
ለመሆን በአቅምም በስነ ልቦናም ዝግጁ አይደለሁም፡፡”

“ስለዚህ?” ብላ አፍጥጣ ተመለከተችኝ፡፡
“ሌላው ቢቀር ያለ አባት ፍቅር ሚያድግ ልጅ ለመውለድ ባታስቢው ይሻላል። አንድ ነገር ብታደርጊ ጥሩ ነው፡፡”

“ምን?! አንተ ሰው መሳይ ሰይጣን ምን አልከኝ? አላደርገውም፡፡አላደርገውም...! የነገርኩህም ሰው መስለኸኝ ነው እሺ፡፡ እንደዚህ አይነት ጭራቅ መሆንህን አላውኩም ነበር፡፡ አባትነትህ እንጦሮጦስ መግባት ይችላል፡፡” ተስፈንጥራ ተነስታ በተቀመጥኩበት ጥላኝ ሄደች፡፡

ወደ ቢሮዬ ተመለስኩ፡፡ በህይወቴ ምን እየሆነ እንዳለ ግራ ገባኝ፡፡ በራሴ ዝርክርክነት፣ አጥምደው እየተጫወቱብኝ ነው። እራሴን ጠላሁት፡፡ እንደዛ በላዬ ላይ ስትጫወት ከርማ፣ አሁን ደግሞ እንዲህ
ትለኛለች፡፡ እውነቷንም ቢሆን፣ ወደዚህች ትርጉም አልባ፣ ጭለማ አለም ሌላ ህይወት ለማምጣት በጭራሽ ምክንያት መሆን አልፈልግም፡፡

ተሰምቶኝ ማያውቅ ጥልቅ ብስጭትና ሃዘን ወረሰኝ፡፡ ቢሮዬን ቆልፌ ወጣሁ።

ወደ ቤት ገብቼ ስልኬን አጥፍቼ፣ ለቀናት ተሸሸግሁ፡፡ ማንንም ማግኘት አልፈልግም፡፡ ወደ ስራ መሄድ ሳስብ አስፈሪ ጭንቀት ይሰማኝ ጀመር። አሁን የሚሰሙኝ ስሜቶች፣ ከዚህ በፊት ስራ ልለቅ ስል የሚሰሙኝ ስሜቶች ናቸው፡፡ መሸሽ፣ መደበቅ፣ መሸሸግ፡፡ ከዚህ ቀደም
ያጠፋሁትን ላለመድገም፣ ለራሴ የገባሁትን ቃል ለመጠበቅ፣ በመከራ
ያገኘሁት ስራ ላለመልቀቅ፣ ስራዬን እንደምንም ለመቀጠል፣ ለቀናት
ከውስጤ ጋር ታገልኩ፡፡ ግን፣ አልሆነም፡፡ አልቻልኩም፡፡ ለአራተኛ ግዜ ስራዬን መልቀቅ ግድ ሆነብኝ፡፡ ቢሮ ሄጄ፣ ቁልፍና ንብረት ለማስረከብ ምትሆን እንጥፍጣፊ ትዕግስት አልነበረኝም፡፡ መልቀቂያ እንኳን
ሳልወስድ፣ ድንገት በብስጭት እንደወጣሁ ቀረሁ፡፡ ለካ ውስጤ፣
ሳይታወቀኝ ሞልቶ ነበር፡፡ እየጠጣሁ እብሰከሰካለሁ። እብከነከናለሁ።
ሁሌም እንደዛ ነበር፡፡ “ለምድን ነው ሁሌም እኔ ላይ እንዲህ ሚሆነው?
ለምንድን ነው ነገር ሚደራረብብኝ፣ በአንዴ ሚጨልምብኝ? ምን ብረገም
ነው?”

ህይወቴን ወደኋላ መለስ ብዬ መመልከት ጀመርኩ፣ ሁሉም ጥቁርና አድካሚ ሆኖ ታየኝ፡፡ በመውጣትና በመውረድ፣ በስቃይ ብቻ የተሞላ ሆኖ ተሰማኝ፡፡ ህይወት በአንዴ ላይ ታወጣኝና መልሳ ከአፈር
ትደባልቀኛለች፡፡ እንደዚህ አይነት ህይወት ሰለቸኝ፡፡ ታከተኝ፡፡ ቢበቃኝ

ይሻለኛል ብዬ ማሰብ ጀመርኩ፡፡አዕምሮዬ “ከዚህ እስስት ከሆነ ኑሮ ሞት በስንት ጣዕሙ' አለኝ፡፡ ያስፈራል፡፡ ያስጨንቃል፡፡ እንደዛ ማሰብ አልፈልግም፡፡ ማሰቤን ግን ማስቆም አልቻልኩም፡፡ አዕምሮዬ ደጋግሞ በማስረጃ ይሞግተኛል፡፡ መሞት መፍትሄ እንደሆነ ይነግረኛል፡፡ እራሴን
ስለማጥፋት ደጋግሜ አስባለሁ፡፡ ለቀናት ምን ማድረግ እንዳለብኝ አሰብኩ። ከዚህ ከተማ መውጣት፣ መሄድ እንዳለብኝ ወሰንኩ፡፡ ቢሾፍቱን እወዳታለሁ፡፡ የነፍሴ እስትንፋስ ገመድ እዛ የተቋጠረች እስኪመስለኝ ድረስ፡፡ ሲከፋኝም፣ ስደስትም ወደሷ እበራለሁ፡፡ የሀይቆቿ የማይረበሽ፣ የማይናወጥ ውሃ፣ ተረጋግቶ ያረጋጋኛል፡፡ ለግዜውም ተረጋግቼ
ለማስብ፣ ከጥቂት አስፈላጊ ካልኳቸው እቃዎች በስተቀር ያለኝን የቤት እቃ ባገኘሁት ዋጋ ሸጬ፣ ወደ ቢሾፍቱ ለመጓዝ ተነሳሁ፡፡

ከአዳማ ከተማ ወጥቼ ትንሽ እንደተጓዝኩ፣ መንዳት አቃተኝ፡፡
በአይኔ የሞላው እንባ እይታዬን ጋረደኝ፡፡ መኪናዋን ጠርዝ አስይዤ፣ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ፡፡ አዳማን ብቻ ሳይሆን ህይወትን ተሰናብቼ እየወጣሁ እንደሆነ ተሰማኝ፡፡ በዚህ ሰዓት እንዲህ እየሆንኩ እንዳለ ሊገምት የሚችል አንድም እንኳ ሰው እንደሌለ ሳስብ፣ ሆድ እቃዬ
እስኪበጠበጥ አለቀስኩኝ፡፡ በቁሜ ለራሴ ለሞተ ሰው እንደሚለቀስ ተንሰቀሰኩ፣ በቀብሩ ማንም እንዳልተገኘ ብቸኛ ሰው ለራሴ አነባሁ፡፡ሲወጣልኝ ተነስቼ ወደ ቢሾፍቱ ሄድኩኝ፡፡ ነገሮችን እስክወስን፣ ቤት መከራየት አልፈለኩም፡፡ መለስተኛ ሆቴል አልጋ ይዤ መቆየትን መረጥኩ፡፡ ሁሉ ነገር፣ ሰልችቶኛል፡፡ አስጠልቶኛል፡፡ ቤተሰቦቼንም ጨምሮ፡፡ አሁን እነ አሌክስንም ማግኘት አልፈልግም፡፡ ስለዚህ ሌላ መዋያ ዱከም ፈልጌ አገኘሁ፡፡ ደብረዘይት ማደሪያዬ ብቻ ሆነች፡፡ ማታ ማታ አብዝቼ እጠጣለሁ፡፡ ስሰክር በለሊት ነድቼ አዲስ አበባ ሄጄ
አጨፍር አድራለሁ። ሲነጋ እንዴት እዛ እንደመጣሁ እንኳ ትዝ እስከማይለኝ፡፡ አንዳንዴም፣ እራሴን መኪና ውስጥ አድሬ አገኘዋለሁ፡፡

አንድ ቀን በመኪና አደጋ ልሞት እንደምችል አስባለሁ፡፡ እሱማ እድል
ነው፣ እንደዛማ ከሆነ እግዜር ይወደኛል እላለሁ፡፡ እራሱን አጠፋ ከምባል፣ በመኪና አደጋ ሞተ መባል በስንት ጣዕሙ ብዬ አስባለሁ፡፡ የመጠጡ ብዛት ጨጓራዬን ነካው፡፡ ስጠጣ ያስመልሰኛል፡፡ ከሚሰማኝ አስጨናቂ ስሜት ለመውጣት ከመጠጣት ውጪ አማራጭ የለኝም፡፡
አላቆምኩትም፡፡ የመጠጥ አይነት እየቀያየርኩ እጠጣለሁ፡፡በየቀኑ ዱከም እየተመላለስኩ እየቃምኩ መንገደኛ ሃሳቦችን ሳስብ እውላለሁ። በምመለከተው ነገር ድንገት በሚመጡ ሃሳቦች እነጉዳለሁ፡፡ ይመለከተኛል፤ ይጠቅመኛል፤ ሳይል አዕምሮዬ ያገኘውን
ያላምጣል። አንዱን አነሳለሁ፤ እጥላለሁ። ሲመሽ እጠጣለሁ። ካደለኝ ክፍሌ ገብቼ እተኛለሁ፡፡ መሽቶ ይነጋል፤ ሌላ ቀን፡፡ አንዳንዴ፣ ለመኖር በሚደረግ ጥረት የሚፈጠር ግርግር ለቅፅበት ቀልቤን ያዝ ያደርገኝና ስለ ኑሮ አስባለሁ፡፡ ሰዎች ለመኖር ይወጣሉ፤ ይገባሉ፤ ይጭናሉ፤
ያወርዳሉ፤ ይመጣሉ፤ ይሄዳሉ፡፡ ይህ ግርግር አንዳንዴ እንደሰመመን ይታየኛል፡፡ነገሮች ላይ ትኩረቴ በጣም ቀንሷል፡፡ እያሰብኩ የነበረውን ሁሉ ቶሎ እረሳለሁ፡፡ ጭንቅላቴ በፍጥነት ወደ ተለመደው፣ አስጨናቂ ሀሳቦች ይመልሰኛል፡፡

ዱከም ቤተኛ እየሆንኩ ነው፡፡ ባለቤቷ ጠፋህ፣ አረፈድክ ማለት ጀምራለች፡፡
ስራ ለቅቄ እዚህ ከመጣሁ ሶስት ሳምንት ሆነኝ፡፡ ማታ ስጠጣ፣ ከነ አሌክስ ጋር እንገናኝ ጀመር፡፡ ስንጠጣ ጨዋታቸው፣ ዘፈኑ፣ ጭፈራው፣ ጭጋጋማ ህይወቴን የብርሃን ጭላንጭል ይፈነጥቅልኛል፣
ቅንጥብጣቢ ደሰታ፡፡ ሲነጋ ግን፣ የተለመደው ከፍተኛ ድብርት፣ ባዶነት፣
ተስፋ ቢስነት ቦታቸውን ይረከባሉ፡፡ ቀኑን እንደምንም አሳልፈውና ማታ እነ አሌክስን እየፈለኩ ድብርቴን እዋጋው ጀመር፡፡ አሌክስ ጨዋታ አዋቂ
👍4
#የታካሚው_ማስታወሻ


#ክፍል_አስራ_አንድ


#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)

“አንተ ብቻ አይደለኸም፡፡ ብዙ ሰው እንደዛ ይመስለዋል፡፡እንደውም ከዚህ ጋር በተያያዘ አንድ የእንስሳት ዶክተር ጓደኛዬ
የገጠመውን ልንገራችሁ፤” አለን እየሳቀ፡፡

“እሺ ንገረን፡፡”

“የንሰሃ አባቱ ዶክተር ሲባል፣ የሰው ሃኪም እንደሆነ ይመስላቸው፡፡”

“እሺ፡፡

“እና ንሰሃ ሊገባ እርሳቸው ጋር ይሄድና፣ አባቴ ሃጥያት ሰርቻለሁ፤ ይፍቱኝ ልሎት ነው የመጣሁት፤' ይላቸዋል፡፡ እሳቸውም
'ልጄ፣ ሰው ሆኖ ሃጥያት ማይሰራ ማን አለ? እግዚአብሄርስ ንሰሃን የሰራልን ይህን አውቆ አይደል? በል ንገረኝ ልጄ እፈታሃለው፤ ይሉታል።

አባቴ የኔስ ትንሽ ከበድ ያለ ነው፡፡ ይላል እየተቅለሰለሰ፡፡

አዬ ልጄ፣ ለሰው እንጂ ከብዶ ሚታየው፣ ለእርሱ ምን ይሳነዋል፣ አትፍራ ንገረኝ ልጄ፧' ይሉታል፡፡

“አባቴ ይፍቱኝ፣ ከታካሚዬ ጋር ወሲብ ፈፅሚያለሁ።

'አይ ልጄ፣ እንዳንተ ያሉ ዶክተሮች ሁሉ ሚወድቁበት፣ሚያጋጥም ነውኮ፡፡ አይዞህ ልጄ፣ ንሰሃ እሰጥሃለው፡፡ እግዚአብሄር
ይቅር ባይ ነው ፤ " ሲሉት፣

አባቴ እኔ ግን የእንስሳት ዶክተር ነኝ፣ ታካሚዎቼ... ብሎ ሳይጨርስ ደንግጠው፣

በስመአብ ወወልድ... እያሉ ሲደግሙ፣ እሱም ደንግጦ ወጥቶ ከንስሃ አባቱ በዛው ተቆራርጦ ቀረ፡፡” ካ....ካ... በጣም ሲያስቀን አመሸን፡፡

እነ ሃብትሽ በህይወቴ የቀሩኝ እንጥፍጣፊ ቅመሞች ሆነዋል፡፡ስለ ስራው ሲያወራ፣ የዶሮ እርባታ ስራ ጥሩ እንደሆነና ቢሾፍቱ ለዛ ስራ የተመቸች እንደሆነች ሲያወራ ሰማሁት። አስጨናቂ ሃሳቦቼ የተወሰነ ረገብ ብለውልኛል፡፡ ስልኬን ብዙ ግዜ ክፍት ማድረግ ጀመሪያለሁ፡፡ ሳሚና ማሂ አልፎ አልፎ ይደውላሉ፡፡ ማሂ በአቋሟ
ፀንታለች፡፡ እኔም እንደዛው፡፡ ሳሚ ስለማርገዟ ሰምቶ፣ አስረግዘህ ጠፋህ
አይደል?' እያለ ይቀልዳል፡፡ እስቅና ስለ ሜሪ እጠይቀዋለሁ፡፡ አሁንም ከሼባው ጋር እንደሆነች፣ ኤፍሬም ቦርኮ መንገድ ላይ እንደወጣና እንዳየው፣ በግቢው ያለውን አዲስ ነገር እየሳቀ ያወራኛል።

#እንጥፍጣፊ_መሻቶች...

ያለኝ ገንዘብ አየመነመነ ነው፡፡ አንድ ነገር ካላደረኩ፣ ከዚህ በኋላ ከአንድ ወር በላይ መንቀሳቀሻ ገንዘብ አይኖረኝም፡፡መኪናዬን ለመሽጥ በውስጤ ዝግጅት እያደረኩ ነው፡፡ ለመሸጥ ምን ማድረግ እንዳለብኝ እያሰላሰልኩ ስጠጣ አምሽቼ ተኛሁ፡፡ ከእንቅልፌ ስነቃ የተለየ ስሜት
እየተሰማኝ ነው፡፡ ደስ ሚል ስሜት፣ የፈነደቀ፣ የበራ ውስጠት እየተሰማኝ ነው፡፡ ከአልጋዬ እንደተነሳሁ፤

“ኋት ኤ ብራይት ዴይ ኢዝ ቱዴይ...?”

“ቱዴይ ኢዝ ሳተርዴይ...”

“ኢት ኢዝ ማይ ብርዝ ዴይ...።” ብዬ ሳላስበው ቅኔ ተቀኘሁ፡፡

ወይኔ... ዛሬ ልደቴ ነው እንዴ? እኔኮ አንዳንዴ ሳላስበው በልሳን ምናገረው ነገር አለ፡፡ ልደቴን አላውቀውም። ግን ማን ያውቃል፣ዛሬ ሊሆን ይችላል እኮ..፡፡ ቢያንስ አንድ ሶስት መቶ ስልሳ አምስተኛ
ትክክል የመሆን እድል አለኝ፡፡ ማክበር አለብኝ፡፡

ሻወሬን ወሰድኩኝ፣ ጺሜን ተለጫጨሁ፣ አፍተር ሼቭ፣ ሽቶ ተቀባባሁ። ድንገት እብደቴ እየተነሳ እንደሆነ ተሰማኝ፡፡ ከወራት በኋላ፣ ለመጀመሪ ግዜ ከውስጤ ሳልጠጣ ደስ ሚል ስሜት እየተሰማኝ ነው:: ፈገግ ልል፣ ልስቅ ልጫወት ነው:: እብደቴን አውቀዋለሁ። እወደዋለሁ።
እሱ ይሻለኛል። ዝለል፣ ዝላል፣ ፈንጥዝ፣ ፈንጥዝ ይለኛል። ህይወት የፈካች አበባ፣ ብሩህ ሆና ትታየኛለች፡፡ ቀላልና አጓጊ ያደርግልኛል። ለባብሼ ስጨርስ፣ ምሳ ደርሷል። ወጥቼ ለራሴ ምርጥ ክትፎ ጋበዘኩት።ከምሳ በኋላ መኪናዬን አስነስቼ ዝም ብዬ ነዳሁኝ፡፡ ወዴት፣ ለምን፣
እንደምሄድ አላውቅም፡፡ ብቻ ደስ ብሎኛል። ፍንትው፣ ብርት፣ እንዳልኩ
ሳላስበው እዛው ዱከም ደንበኛዬ ጋር እራሴን አገኘሁት። መሄጃ የለኝም
ገባሁ። ያልተለመደ፣ሞቅ ያለ ስላምታ ሰጠኋቸው። ደስ ሲለኝ መደበቅ
አልችልም:: ፊቴ ያሳብቃል።

“እንዴት ነሽ...? ሰላም ነዉ...?” አልኳት ባለቤቷን፡፡

“አለን፡፡ እንዴት ነህ አንተ? ግባ!።” የቤቱ ባለቤት ወደ ተለመደዉ ቦታዬ እየጠቆመችኝ፡፡

“ዛሬ እምሮብሃል። ፍክት ብርት ብለሃል። ምን ተገኘ?”

“ልደቴ ነው። ዛሬ ከበር መልስ ግብዣ በኔ ነው::”

“እንኳን ተወለድክልን። ልደትህ ከሆነማ፣ እኛ ነን መጋበዝ ያለብን።”

“አመሰግናለሁ። ግን፣ የደስታዬ ቀን ስለሆነ፣ ግብዣው በኔ ነው። ብቻ ዛሬ
ልዩ እንክብካቤ ያስፈልገኛለ፤” ብዬ ጥጌን ይዤ ተቀመጥኩ ብዙም ሳትቆይ ሚያስፈልገኝን ሁሉ አምጥታ
አስቀመጠችልኝ፡፡ ቤተኛ ሆኛለሁ። ሚያስፈልገኝን፣ ልኬን፣ ሁሉን
አውቃለች፡፡ ዛሬ እንደ ከዚህ ቀደሙ፣ ስልኬ ላይ አልተደፋሁም: መሄጃ
ስላጣው እንጂ መቃም ሳይሆን ሰው ነው ያማረኝ፡፡ ለሳምንታት ሰው አስጠልቶኝ ከሰው እንዳልሽሽው፣ ዛሬ ከሰው ማውራት፣ መቀለድና መሳቅ አማረኝ፡፡ ከእነርሱ ጋር እየተጫወትኩ፣ እየቀነጣጠብኩ መቃም ጀመርኩ፡፡ ትንሽ እንደቃምኩ፣ አንድ ጥቁር በጥቁር የለበሰች ረጅም፣ ቁመናዋ የተስተካከለ፣ ቆንጅዬ ልጅ ገባች፡፡ እንዳየኋት ዐይኖቼን
ተክዬባት ቀረሁ፡፡

መጀመሪያ እዚህ ቤት መምጣት የጀመርኩ ሰሞን፣ ባለቤትየዋ እዚህ ከሚመጡ ደንበኞቼ ለየት ትላለህ፤' ያለችኝ ትዝ አለኝ፡፡ ልጅቷ ፅድት ያለች ናት:: ውብና ማራኪ! እኔም እስከዛሬ እዚህ ቤት ሲመጡ ካየኋዋቸው ሴቶች ተለየችብኝ፡፡ ሳሎኑን ተሻግራ፣ በመጋረጃው ጀርባ

ወደ ውስጥ ገባች። ከቤቱ ባለቤት ጋር እንደጓደኛ ሰላም ተባብለው እየተሳሳቁ ያወራሉ፡፡ ቤተኛ ነች፤ ይተዋወቃሉ ማለት ነው? ግን ሲታዩ፣ ፍፁም በተለያየ ዓለም ውስጥ ያሉ ሰዎች ይመስላሉ፡፡ባለቤትየው፣ ሱስ ያጎሳቆላት ከሲታና የወየበች ናት፡፡ ይቺ ደግሞ፣ የቆዳዋ ጥራት፣ በታይቷ ውስጥ የሚታየው የተመቸው ሰውነት፣ ሱስ ባለፈበት አልፋ
ምታውቅ አትመስልም። እንዴት ተዋወቁ? ምን አገናኝቸው? ጓደኛማ በፍፁም ሊሆኑ አይችልም:: ከወደ ጓዳ ውስጥ የሚስማውን እንቅስቃሴ እያዳመጥኩ ግንኙነታቸውን ለመገመት እሞክራለሁ፡፡
ትንሽ ቆይታ ልጅቷ መጋረጃውን ከፍታ ወጣች:: በኔ ተቃራኒ ከመጋረጃው ጠርዝ መጅሊስ ላይ ተቀመጠች። ባለቤትየዋ ሺሻ አምጥታ ለኮሰችላት። አሁንም ያወራሉ። ሺሻውን ተቀብላ ማጨስ
ጀመረች፡፡ አትመስልም። በፍፁም ሱስ ባለፈበት ያለፈች አትመስልም።
እንደማያት አንድታውቅ ፈልጌያለሁ። ዐይኔን ተክዬ ቀረሁ:: እጅግ ውብ
ነች፡፡ ፀጉሯ ሉጫነቱ እርዝመቱ፣ ስስ ከንፈሮቿ ከተቀባችዉ ሊፒስቲክ
ጋር እንጆሪ ይመስላሉ። ጉመጣት ጉመጣት የሚል ስሜት ተሰማኝ።
ወተት እንደጠጣች ድመት፣ የራሴን ከንፈር በምላሴ ላስኩት፡፡ የቀይ
ዳማ ናት፡፡ ጥቁር አይኖቿን ሰማያዊ አይ ሻዶው ተቀብታቸዋለች። አማላይ የውበት እመቤት ትመስላለች፡፡

“ከእርሷ ጋር አድሬ ሲነጋ ልሙት.
ላፈር አይደለም ወይ የተፈጠርኩት...” የተባለላት ትመስላለች፡፡

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍31
#የታካሚው_ማስታወሻ


#ክፍል_አስራ_ሁለት


#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)

መተዋወቅ አለብኝ፡፡ ውስጤ አሻፈረኝ ሲል ይታወቀኛል።አሁንም ፈዝዤ ዐይኔን እሷ ላይ እንደተከልኩት ነኝ፡፡ ዐይን ለዐይን እየተጋጨን ነው። እንዳሞራ ጆፌዬን እንደጣልኩባት ያወቀች
ይመስለኛል። በእጄ ነይ እዚህ ጋር ብዬ ምልክት ልሰጣት አሰብኩ፡፡ወዲያው ጭንቅላቴ መልሶ፣ አይ እንደዛማ አይሆንም፤ እንደዛ ድፍረት ይመስላል። እሷን መናቅ ይመስላል፡፡ ያቡ ሌላ ዘዴ መፈለግ አለብህ፡፡ምን ብላት ይሻላል..? አዎ!፣ ልደት...!፡፡ ልደቴ ጥሩ መግቢያ በር
ይፈጥርልኛል!፡፡ የልደት ካርዴን ስቤ በደንብ መጫወት አለብኝ..!

ባለቤቷን ጠራሁና፣ “በይ የልደቴን ግብዣ አንድ ብዬ ባንቺ ልጀምር። እስቲ አንድ ሙሉ ተጋበዥልኝ፡፡ልደቴን እንድታደምቅልኝ የጠራሻትን እዛጋር ለተቀመጠችው መላዕክ የመሰለች ቆንጆም ምትፈልገውን ጋብዢልኝ፡፡ ባለልደቱም እኔ እንደሆንኩ ንገሪያት:
ልታደምቅ መጥታ ጠፍቼባት እንዳይሆን ብቻዋን የተቀመጠችው፤ አልኳት፡፡

“ኪ...ኪ...ኪ... በጣም አመሰግናለሁ!፣ መልካም ልደት በድጋሚ...::”

“አደራ መላእክቷ ልደቴን ታድምቅልኝ...!”

“ጣጣ የለውም፤ ልደቱ እንዲደምቅ የተቻለንን እናደርጋለ፤”ፈገግ እንዳለች ሄደች:: ወደ ውስጥ ገብታ ጫት ይዛ ወጣችና ከቆንጅዬዋ ልጅ ጋር ቁጭ አለች። እየተሳሳቁ ያወራሉ። ልጅቷ ቀና እያለች ወደኔ ትመለከታለች፡፡ ያልኩትን እየነገረቻት መሆን አለበት። ቀና ስትል ጠብቄ በዐይኔ ያዝኳት:: ጎንበስ አለች። ለሁለተኛ ጊዜ ጠበኳት፤ አገኘኋት፤
እድሉን አላባከንኩትም፤ በግንባሬ ሰላምታ ሰጠኋት። አላሳፈረችኝም፣
ከፈገግታ ጋር አፀፋውን መለሰችልኝ፡፡ ትንሽ ቆይታ ልጅቷ፣ ቦርሳዋን ይዛ
ከአጠገቤ መጥታ ተቀመጠች፡፡ ባለቤትየዋ ሺሻዋን አምጥታ አጠገባችን አስቀመጠችና፣

“አደራ፣ ዘመዴ ልደቱ ነው፣ በደንብ ተንከባከቢልኝ፤” አለች እየሳቀች፡፡ ስትስቅ ፊቷ አጥንትና ቆዳ ብቻ እንደቀረው ያሳብቃል።

“ዘመድሽ ዘመዴ ነው አታስቢ፡፡” ልጅቱ ፈገግ ብላ መለሰች፡፡

“እሺ፣ ባለ ልደቱ እንዴት ነህ ...?” አለችኝ ወደኔ ዞራ፡፡

“አለሁ፡፡ እንዴት ነሽ ቆንጂት...?”

“ልደት እንዴት ነው ታዲያ...?”

“አጀማመሩ በጣም አሪፍ ይመስላል። እዚህ ብቻዬን ላከብር መጥቼ፣ አንችን መላዕክት የመስልች ቆንጅዬ እግዜሩ ላከልኝ::”

“ምነው ልደትን ሚያክል ነገር በብቸኝነት?”

“ያው ሰው እያለ ሰው ሲጠፍ ምን ይደረጋል? አንቺን መሳይ ቆንጆ በልደቴ ሊሰጠኝ ይሆናላ!”

“ኪ.ኪ.ኪ...ኧረ? ደግሞ ቆንጆ እያልክ አታሙቀኝ፡፡”

የምሬን እኮ ነው በጣም ታምሪያለሽ፡፡ ፀሎቴን ሰምቶ መሆን አለበት፣ በልደት ቀኔ አንቺን ውብ የላከልኝ፡፡ ይቅርታ ግን ሳንተዋወቅ ለፈለፍኩብሽ፣ ስምሽን ማወቅ ይቻላል...?”

“ምስጢር ምትጠብቅ ከሆነ...”

“ምስጢር በመጠበቅስ አልታማም፡፡ ችግሩ እኔ የምነግራቸው ሰዎች ምስጢር አይጠብቁም እንጂ...”

“ኪ...ኪ....ኪ..፣ ሞዛዛ ነገር ነህ ባክህ፡፡ እሺ ሃናን እባላለሁ።”

“እኔ ያቤዝ እባላለሁ።”

እሺ፡፡” ብላ ዝም አለች፡፡

“ተማሪ፣ ሰራተኛ..?” የማልወደው ጥያቄ ሳላስበው አመለጠኝ፡፡ዝም ላለማለት እንጂ፣ ምንም ብትሆን አይገደኝም፡፡

“ሁለቱንም አይደለሁም፡፡”

“ማለት ..?”

“ለግዜው ቦዘኔ ነኝ፡፡” ፈገግ አለች፡፡

“እንዴ! ምንም ሳይሰሩ መኖር ይቻላል እንዴ?”

“እንግዲህ እኔ እየኖርኩ ነኝ ባይ ነኝ፡፡”

“ሃ...ሃ... ከተቻለ፣ ለእኔም ንገሪኝና እንዳቺ አምሮብኝ ልቦዝን፡፡”

“ቀልደኛ ነህ፡፡ ስራን የመሰለ ምን ነገር አለና ነው፣ ልቦዝን ምትለው?”

“አንቺ ነሽ ቀልደኛ፡አንቺን የመሰለ ቆንጆ እንዴት ስራ ያጣል?”

“በቁንጅና ነዉ እንዴ ስራ ሚገኘው? ለነገሩ ለግዜው ነው ያልኩህ፡፡”

“እንደዛ አትዪም ታዲያ፤ እሺ ምን ነበር የምትሰሪው?”

“እንዴ... ምነው እንዲህ አጥብቀህ ጠየከኝ? ልትቀጥረኝ አሰበክ መሆን አለበት? ኪ.ኪ.ኪ...፣ እሺ ፊልም ነበር የምሞክረው።"

“ዋው! በጣም ደስ ይላል። አክትረስ ነሻ?”

“እንደዛ ነገር፣ ሙከራ...።”

“አንተስ ምንድነው የምትሰራው?”

“ዶሮ እርባታ ነገር እየሞከርኩ ነው::”

በቀደም ለሳሚ የነገረኩትን ውሽት ለእሷም ደገምኩላት፡፡ ተስፋ የቆረጠ ስራ ፈትን ማን ይፈልጋል፣ አይደለም እቺን የመሰለች ውብ፡፡ ለወራት የጠፋውን የፆታ
ፍላጎቴን፣ ኬት ጎትታ እንዳመጣችው ገረመኝ፡፡ በባሌም በቦሌም ብዬ መጥበስ አለብኝ፡፡” ብዬ አሰብኩኝ፡፡

“አሪፍ ነው፡፡ ጎበዝ፡፡”

“በደረቁ አደረኩሽ አይደል? ፈታ በይ የፈለግሽውን እዘዢ፡፡ ዛሬ የደስታዬ ቀን ነው፡፡” ሃናን ተግባቢና ቀለል ያለች የደብረ ዘይት ልጅ እንደሆነች ተረዳሁ፡፡ አጥብቆ ጠያቂነቴ ግን አልተመቻትም፡፡ባለቤቷን ጠርቼ ተጨማሪ ሺሻና ምትጠጣውን አዘዝኩላት፡፡ ተቀብላ ማጨስ ጀመረች፡፡ አጭሳ ከአፏ የምታወጣው ጭስ ብዛት ይገርማል፡፡ጭሱን በትኩረት እስከ መጨረሻው በዐይኗ ትከተዋለች፡፡ ጭሱን
አፍጥጣ ስትመለከተው፣ ከውስጡ አንድ የሆነ መልስ ወይም መፍትሄ ምትፈልግ ትመስላለች፡፡ እንደዛ ሆና ሳያት፣ በውብ መልኳና የተመቸው በሚመስለው ሰውነቷ የተጋረደ መከፋት ያየው መሰለኝ፡፡ ሳላስበው እቺን የመሰለች ልጅ ለምን እዚህ ጭስ ውስጥ መደበቅ ፈለገች የሚል ሃሳብ ውስጥ ተዘፈኩ፡፡

“እንካ አጭስ፡፡” ከሄድኩበት ሃሳብ መለሰችኝ፡፡

“እኔ አልወድም፡፡”

“ምንም አይልህም፡፡ ማጨሻ ፒፓ ይምጣልህ?”

“ከሆነማ ያንቺው ፒፓ ይሻለኛል፡፡በዛውም ቆንጆ ከንፈርሽን፣ከፒፓው ላይ እስመዋለሁ፡፡”

“ይሄን ያኸል...? ሞዛዛ፡፡” ብላ ሳቀች፡፡

“የምሬን ነው፣ ከንፈርሽ በጣም ውብ ነው ፤ እንጆሪ ነው ሚመስለው፡፡”

“አመሰግናለሁ!”

“አኔ ደግሞ እንጆሪ በጣም እወዳለሁ፡፡”
ኪ.ኪ.....፣ ደስ ምትል ቀልደኛ ነህ ባክህ፣ ታዲያ ምን ይሻልሃል?”

“ምን እንደሚሻለኝማ በደንብ ታውቂያለሽ የልደቴ ስጦታ ቢሆንልኝ ደስታዬን አልችለውም፤” ብዬ ጠቀስኳት፡፡

“ደረቅ...” ብላ ታፋዬን ቸብ አደረገችኝ፡፡ ሺሻውን ወደኔ ዘረጋችልኝ፡፡ ተቀበልኳትና ለማጨስ ሞከርኩ፡፡ ትን ብሎኝ ያስለኝ
ጀመር፡፡

“ኪ.ኪ.ኪ፣ እውነትም አጭሰህ አታውቅም፧” ብላ ተቀብላኝ ማጨሷን ቀጠለች፡፡ ሳቀርባት ሰተት ብላ እየቀረበችኝ ነው፡፡ ምፈልገው ድረስ ስቤ ብወስዳት ምትጎተትልኝ መስሎ ተሰማኝ፡፡ ለመሞከር ዝግጁ ሆንኩ፡፡ በደንብ ዘና ብላ መጫወት ጀምራለች፡፡ ባለ ቤትየዋ፣ በየመሃሉ እየመጣች፣ “ተጫወቱ፣ አሁንማ እኔን እረሳችሁኝ፤” ትለናለች፡፡ ከሆነ ሰዓት ጀምሮ ሳወራት፣ ታፋዋን እየነካካው፣ እጆቿን እያሻሸሁ ነው፡፡
ምንም ክልከላ አልገጠመኝም፡፡ ሰዓቴን አየሁና፣

“ስዓቱ እንዴት ሄደ?”

“ስንት ሰዓት ነው?”

“አስራ አንድ ሊሆን ነው፡፡”

“ወሬ ይዘን አልታወቀንም፡፡”

“ኢንስታይን፣ “ከቆንጆ ሴት ጋር ሲሆኑ ሰዓቱ እራሱ ይሮጣል፣ ምቀኛ ነው፧' ያለው እውነቱን ነው ለካ፡፡”

“ኪ.ኪ.ኪ.፣ መቼ ነው የነገረህ?”

“ሃሃሃ...፣ ኧረ የት አግኝቼው? አለ ሲባል ሰምቼ እንጂ፡፡ እዚህ ሃገር ሁሉ ነገር አሉ አይደል...”

እጆቼን ወደ ፈለኩት እየስደድኩ ነው፡፡ አሁንም ክልከላ የለም፡፡ሳማት፣ ሳማት የሚል ስሜት ከቅድም ጀምሮ ወጥሮ ይዞኛል።ልቆጣጠረው የምችለው ስሜት አይደለም፡፡ ምን ማድረግ እንዳለብኝ
አሰብኩ፡፡ ደግነቱ ዛሬ፣ ብዙ ደምበኛ የለም፡፡ ነፃነት ተሰምቶኛል፡፡

“ተጫወት እንጂ! ዝም አልክ፡፡ ምን እያሰብክ ነው?” አለችኝ፡፡

“ያው ስላንቺ ነዋ፡፡ ውበትሽ ስሜታዊ ያደርጋል። ሳማት፤ሳማት
👍2
#የታካሚው_ማስታወሻ


#ክፍል_አስራ_ሦስት


#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)

“ያው ስላንቺ ነዋ፡፡ ውበትሽ ስሜታዊ ያደርጋል። ሳማት፤ሳማት፤ ይለኛል፡፡ ደግሞ ምርጥ ልጅ ነሽ፡፡ በፍፁም ላስቀይምሽ የማልፈልጋት አይነት ቆንጆ ነሽ፡፡ እንደ ድፍረት ቆጥረሽብኝ እንድታኮረፊኝ ደግሞ አልፈልግም፡፡ ምናባቴ ላድርግ ብዬ እያሰብኩ
ነበር፡፡” ከንፈሯን እያየሁ ደግሜ የራሴን ከንፈር በምላሴ ላስኩት፡፡

“አንተ እብድ. አታረገውም አይባልም እኮ፤” አለች ዐይኗን አፍጥጣ፡፡

ዝም ብዬ አየኋት፡፡

«ባይዘዌ ግልፅነትህ በጣም ደስ ብሎኛል። ስሜትህን በግልፅነት
መንገርህ፣ ያንተንም ስልጡንነት ያሳያል፤” አለችኝ ::

ደስ ብለኸኛል...? አሁን መድፈር አለብኝ፡፡ ብስማት ምንም አትለኝም፡፡ ከዚ በላይ ምን እንድነው ምጠብቀው? በመጀመሪያ ቀን ልሳምሽ ስላት፣ አፏን አውጥታ እሺ እንድትለኝ ነው? ስሜቴ ከምቆጣጠረው በላይ ሆነ፡፡ አድርገው አድርገው ይለኛል፡፡ በዐይኔ የቤቱን እንቅስቃሴ እከታተላለው፡፡ አሁን ቤቱ ባዶ ሆኗል፡፡ ባለቤቷም ውጪ
ከወጣች ቆይታለች፡፡ ላድርገው? በድንገት ብትገባብንስ? ደግሜ ሰዓቴን አየሁ፡፡ ጋድ! አሁን ሂድልኝ ቢባልኮ እንዲህ አይሮጥም፡፡

“ስዐቱ በጣም ሄደ፡፡ ወደ አገርሽ ሄደን ደግሞ፣ ልደቴን በፈሳሽ ብናከብር ምን ይመስልሻል? እዚሁ አስራ ሁለት ሰዓት ሊሆንኮ ነው፡፡”

“እዛማ የማውቀው ሰው ሊያየኝ ይችላል። ባይሆን እዚህ ምታውቀው ቤት ካለ...?”

“ችግር የለም፡፡ መኪና ይዣለሁ፡፡ እዛው ሰው ማያየን ቦታ እወስድሻለሁ።” ዝም አለች፡፡ ዝምታ መስማማት ነው፡፡ ባለቤቷ
መጠባበቅ ጀመርኩ፡፡ ባለቤትየው ወዲያው እስክትመጣ አድፍጬ መጠባበቅ ጀመርኩ ባለቤትየዋ ወድያው
ብቅብላ፣

“ተጫወቱ! ዝም አላችሁ፡፡ ምን ይጨመር...?” አለችን፡፡

“ሂሳብ ስሪልን፤” አልኳት፡፡ እዚህ ተጨማሪ ሰዓት ማባከን አልፈፈለኩም፡፡

“እሺ!” ብላ ልትሰራልን ወጣች፡፡ ከሃናን ጋር እየተጠጋጋን ሳናስበው ተጣብቀናል፡፡ ሙቀቷ ይሰማኛል፡፡ ሂሳብ ከፈልኩና፣

ተነሽ እንውጣ!” አልኳት ልብሴን እያረጋገፍኩ፡፡

እሺ ግን፣ አብሬህ አልወጣም፣ አንተ ውጣና ውጪ ጠብቀኝ፡፡”

አላንገራገርኩም፡፡ የመኪናዬን አይነትና ያቆምኩበትን ቦታ ነግሪያት ወጣሁ፡፡ አላስጠበቀችኝም፤ ቶሎ መጣች፡፡ የዱከምን ከተማ ወደኋላ እየተውኩ፣ ወደ ደብረዘይት ነዳሁት። ልደቴን ደስ የሚልና ልዩ እንዳደረገችልኝ፣ ስለ ልዩ ውበቷ፣ ስለ ከንፈሯ ልዩነት እያወራሁ በፍጥነት እከንፋለሁ፡፡ በአንድ እጄ መሪ ይዤ በሌላው እጄ በስስ ታይት የተሸፈኑት ታፋዎቿ መሃል ገባሁ፣ ሙቀቷ ረመጧ ለበለበኝ፡፡ እጄን አወጣሁትና እጆቿን ያዝኳቸው፡፡ በላብ ረስርሰዋል፡፡ ጣቶቼን በጣቶቿ መካከል ሰገሰኳቸው፡፡ አጥብቄ ጨመኳቸው፡፡ ምንም አታወራም ዝም.
ብቻ፡፡ ሁሉም ተፈቅዷል፡፡

በስሜት ባህር ቀልጠን ሰምጠናል፡፡
ወደ ክፍሌ በፍጥነት እየነዳሁ ነው፡፡ ወዴት ነው እንኳ ሳትለኝ ትከተለኛለች፡፡ ልከመርባት ቸኩያለው፡፡ ለምን እንደሆነ ባላውቅም፣ አምናኛለች፡፡ እንደበግ
እየተጎተተችልኝ ነው፡፡ የፈለኩትን ሁሉ ፈቅዳልኛለች፡፡ ከራሴ ሰውነት የሚወጣ ሙቀት በሸሚዜ አልፎ ፊቴን ይልፈኝ ጀመረ፡፡ ወደ ክፍሌ በሚወስደው የውስጥ መንገድ ታጠፍኩ፡፡ አሁንም ምንም አላለችም፡፡ ትንሽ እንደነዳሁ ከፊቴ ያለ ሚኒባስ አስፓልቱ ላይ መንገድ ዘግቶ ቆመ፡፡ ቸኩያለው፡፡ ደርቤ ላልፈው ስል፣ ከፊቴ ሌላ መኪና እየመጣ ነው፡፡
አክለፈለፈኝ፡፡ ወዲያው ሚኒባሱ ተንቀሳቀሰ፡፡ ጠጋ ስል፣ የተሰበሰቡ
ወጣቶች ተቆፍሮ የነበረውን መንገድ ያስተካከሉበት ገንዘብ እየጠየቁ
ነው፡፡ ግዜ የለኝም፣ እጄን ወደ ኪሴ ሰድጄ ያገኘሁትን ብር ሰጠኋቸው፡፡

“ያራዳ ልጅ...፣ ያራዳ ልጅ...

ይመችሽ...፡፡

መኪናሽን ሃመር ያርግልሽ፡፡”

በዜማ አዘል ምርቃት ሸኙኝ፡፡ ስንት ሰጥቻቸው ይሆን? ለነገሩ ስንትስ ብሰጣቸው፣ እኔ ይሄን የመሰለ መና ወርዶልኝ...፡፡ 'መኪናሽን ሃመር ያርግልሽ' ያሏት ምርቃት ከእዕምሮዬ ቀርታ በግድ ፈገግ አደረገችኝ፡፡ ቪትሴን ንቀዋት ነው? ለኔ ሃመሬ ናት፡፡

የክፍሉን በር፣ እንዴት ከፍቼ እንደዘጋሁት አላስታውስም፡፡ እንደቆምን በሩን አስደግፌ ተአምረኛውን ከንፈሯን መምጠጥ ጀመርኩ፡፡ በፍጥነት እራቁታችንን ሆንን፡፡ ረጅም ነች፡፡ በቁመት ብዙም አልበልጣትም፡፡ ልከኛ የተነፋፉ ጡቶቿን ለመዋጥ ዝቅ ስል፣ ራቁት
ገላዋን እታች ድረስ ሳየው፣ ከባድ ስሜት ተሰማኝና አልጋው ላይ በጀርባዋ አጋደምኳት፡፡ የገላዋ ልስላሴና የሰውነቷ ሙቀት ስሜቴን አላወሰው፡፡ ከውስጥ ሱሪዋ በስተቀር እራቁቷን ነች፡፡ እላዩዋ ላይ ተለጠፍኩባትና ተንጠራርቼ ከንፈሮቿን ጎረስኳቸው፡፡ በሁለት እጆቿ
ጆሮዎቼን ይዛ፣ ትስመኝ ጀመር፡፡ ትኩሳቴ ሲጨምር ይታወቀኛል፤ ስሜቴ ተንጠራራ፤ እየተሳሳምን እጄን ወደ ፓንቷ ላኩት፡፡ ፓንቷን ላወልቀው ስታገል ተረዳችኝ፡፡ ከንፈሯን ከከንፈሬ ሳታላቅቅ፣ ፓንቷን
እንዳወልቀው፣ እግሮቿን ወደላይ አጥፋ አመቻቸችልኝ፡፡

ስሜቴ በውስጤ ሲፈላ፣ ሲንተከተክ ይሰማኛል፡፡ ዋጣት፤ዋጣት፤ የሚል ስሜት ተሰማኝ፡፡ ልውጣት ከከንፈሮቿ ጀመርኩ።
ከንፈሮቿን ሳልጠግብ፣ አንገቷን፣ አንገቷን ሳልጠግብ፣ እየላስኳት ቁልቁል ወደ ጡቶቿ ወረድኩኝ፡፡ እልህ፣ ስግብግብነት፣ ውስጤን ወጥሮታል፡፡ የቱን ይዤ የቱን እንደምለቅ መምረጥ አቅቶኛል።
አንደኛውን ጡቷን እስከቻልኩት ያህል ዋጥኩት፡፡ ከወገቧ ወደላይ
ተንፈራገጠች፡፡ በስሜት ተቃጠልኩ፣ ጨስኩ፣ መትነን ጀመርኩ።መዋጥ አልሆንልህ ሲለኝ፣ እውስጧ መግባት፣ ገብቶ መሰንቀር አማረኝ፡፡ ታፋዎቿን ከፈትኳቸው፤ ያቃጥላሉ፡፡ ይፋጃሉ፡፡ በረጃጅም እግሮቿ፣ በለስላሳ ታፋዎቿ፣ መሀል ተንበረከኩኝ፣ ተርመሰመስኩላት::
በእግሮቿ ወገቤን አቅፋ ጎትታ ከራሱዋ
ጋር አጣበቀችኝ፡፡ እንደተመኘሁት ውስጧ ሰነቀረችኝ፡፡ በሙቀቷ ተቀቀልኩኝ፡፡ እራሳችንን እስክንስት፣ በስሜት ሰረገላ ተመነጠቅን፣ ከአለም ተነጠልን፡፡ ዳግም
የምንገናኝ እስከማይመስል ድረስ፣ ያበጠው ስሜቴ እስኪፈነዳና እስኪተነፍስ ድረስ፣ የቀረን እንጥፍጣፊ ሃይልና ጉልበት አልነበረንም፡፡ እንቅልፍ ወሰደን፡፡ ለእራት እንኳ መነሳት አቅቶን በዛው አደርን፡፡ የሆነ ሰዓት ላይ፣ እንደሰመመን እንደምታድር በስልክ ስታወራ ስማኋት፡፡

ለሊት ከእንቅልፌ ስባንን አጠገቤ ተኝታለች፡፡ ሳያት በጣም ደስ አለኝ፡፡ ህልም አይደለም፡፡ እውነት ነው፡፡ ፀጉሯ ተበታትኗል፣ ረጅምና ማራኪ ሰውነቷ ተበረጋግዷል፡፡ እርሷ ለጥ ብላ ተኝታለች፡፡ አልጋው ውስጥ ተገላብጬ ሰውነቷ ላይ ተለጠፍኩባት። ማታ የጠገብኳት
የመሰለኝ ደክሞኝ ነበር፡፡ ስሜቴ ዳግም ተላወሰ፡፡ አሁንም ውስጤ አልበረደም፡፡ እንድትነቃ አደረኳት፣ እንደ አዲስ እየተንገበገብኩ“እወድሻለሁ፣ በጣም ልዩ ነሽ፣ ስጦጠዬ ነሽ፡፡ እያልኩ እንደተላመደ
ሰው፣ የተለያየ አይነት የወሲብ ልፊያ እየቀያየርን በነፃነት ተላፍተን፣

ተመልሰን ተኛን፡፡ ጥዋት ስነሳ ሰዓቴ አራት ሰዓት ተኩል ይላል።ወላልቀን ስላደርን፣ መነሳት አቅቶን ስንንከባለል አምስት ሰዓት ተኩል ድረስ ቆየን፡፡ የረሃብ ስሜቱ ሲጠናብን ምግብ ፍለጋ ወጣን፡፡ ምግቡ
በጣም ይጣፍጣል፡፡ተርበን ነበር፡፡ ከበላን በኋላ ድካሙ የባዕ ተጫጫነን፡፡ከትናንት ጀምሮ እረስተነው ወደ ነበረው ወደየ ራሳችን የሃሳብ ዓለም ተመለስን፡፡

“ዛሬም ወደ ቤት አትሸኘኝም?” አለችኝ ሃናን፡፡

“እህ እ! እንዲህ ገድለሽኝ፣ በምን አቅሜ ነው የምሸኝሽ...?” አልኳት ፈገግ ብዬ፡፡

“ኪ.ኪ...ኪ...፣ ጭራሽ እኔ ገዳይ? አላስተረፍከኝም እኮ፣ አውሬ!” የድካም ሳቅ እየሳቀች፡፡
👍4
#የታካሚው_ማስታወሻ


#ክፍል_አስራ_አራት


#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)


አሁኑኑ መጀመር አለብኝ፤ እንደዋሸኋት ማወቅ የለባትም፡፡ ደስተኛ አድርጋኛለች፡፡ ላጣት ላስቀይማት አልፈልግም፡፡

“እኔ ምልህ ሃብትሽ...፣”

“ወዬ ያቤዝ፡፡”

“ባለፈው ስለ ዶሮ እርባታ ስራ አዋጭነት ስታወሩ ሰምቼ ነበር፡፡”

“አዎ፣ ምነው?”

“እኔም የራሴን ስራ መጀመር እያሰብኩ ነበር፡፡ አዋጭ ከሆነ አግዛችሁኝ እሱን ለምን አልጀምርም?”

“ጥሩ ሃሳብ ነው። ምን ችግር አለው ታዲያ? እናግዝሃለና፡፡ያውም በደስታ!”

ስራውን ለመጀመር ወሰንኩ፡፡ ቤት ኪራይ እንዲፈልጉልኝ ለነአሌክስ ነገርኳቸው፡፡፡ አዳሬ አድካሚ ስለነበር ሳላመሽ ወደ ክፍሌ ገባሁ፡፡ አልጋ ውስጥ ገብቼም የዶሮ እርባታውን ለመጀመር ሚያስፈልገኝን ገንዘብ በግምት አሰላለሁ፡፡ ስራው ገንዘብ ያስፈልገዋል
የቀረኝ ደግሞ ብዙም አያወላዳም፡፡ ከቤት ኪራይ ሌላ፣ እቃዎችን ጨምሮ
ሌላ ወጪዎች ይኖራሉ፡፡ ገንዘብ ያንሰኛል፡፡ ልበደረው የምችለው ሰው
ደግሞ የለም፡፡ መኪናዬን መሸጥ አለብኝ፡፡ ማሂ ቀድማኝ ደወለች፡፡ አንተ
በቃ ሰው ትዝም አይልህም?' ብላ ወቀሰችኝ፡፡ ለማስተባበል ሞከርኩ፡፡

የሰው ልጅ የህይወት ገመድ ግሩም ነው፣ እጅግም ውስብስብ፡፡ ህይወት ግን መኖር ሰልችቶኝ፣ ፍላጎቴ ጭላንጭል ብቻ ነበረች፡፡ እንደሚበራ ሻማ አይደለችም፡፡ ጭላንጭሉን በቀላሉ እፍ ብሎ ማጥፋት
አልተቻለኝም፡፡ ውስጤ ጨልሞ አስጨናቂና አስፈሪ ሃሳቦችን ብቻ
እንዳላመዠኩ፣ መኖር ከንቱ ልፋት ብሎ ጭንቅላቴ እየነዘነዘ ሰላም እንዳልነሳኝ፣ አሁን ደግሞ ይኸዉ፣ ቀኑንም ለሊቱን ከአንዲት ሴት ጋር የመኖርን አጓጊነት ያሳስበኛል፡፡ መኖርን ያጓጓኛል፡፡ የህይወቴን ገመድ ለመቀጠል ዶሮ እርባታ ስራ ለመጀመር እባዝናለሁ፡፡

ከሃኒ ጋር ጥሩ ተግባባን፡፡ በየቀኑ እንደዋወላለን፡፡ ባጋጣሚ ብንገናኝም፣ ሁለታችንም ሰው ተርበናል፡፡ ከነ አሌክስ ጋር አስተዋወኳት፡፡ እነሱም ወደዋታል። ቆንጅዬና ምርጥ ልጅ ናት፣አፍሰሃል ተባልኩ፡፡ በህይወቴ አዲስ እንደተወለደ ከእርሷ ጋር ማደርገው ሁሉ ብርቅና ልዩ ሆነብኝ፡፡ በየቀኑ በሚባል ሁኔታ እንገናኛለን፡፡ ስሜቴ እሷን ባየ ቁጥር ይለኮሳል፡፡ እናብዳለን፡፡ ዛሬ ግን፣ እንደከዚህ ቀደሙ ወደ አልጋ አልሮጥንም፡፡ ድሪም ላንድ ሪዞርት ሄደን ተቀመጥን፡፡ቢራችንን እየጠጣን፣ የረጋውን የቢሾፍቱን ሃይቅ ቁልቁል
እየተመከለከትን ከሃይቁ የሚነሳውን ገራም ንፋስ እየተቀበልን እንጨዋወታለን፡፡

“እኔ የምልህ ያቤዝ፣ ልነግርህ የምፈልገው ነገር አለኝ፡፡”

ስለኬ ጠራ፡፡ አሌክስ ነው፡፡ አነሳሁትና ሃኒ እንዳትሰማኝ ተነስቼ፣ ከእርሷ እራቅ ብዬ ማናገር ጀመርኩ፤ ለስራው ሚሆን ቤት
እንዳገኙልኝ፣ ኪራዩ በወር አራት ሺህ ብር እንደሆነ እና የስድስት ወር ቅድመ ክፍያ እንደሚፈልጉ፣ ከሃብትሽ ጋር ሄደው እንዳዩት፣ ፅድት ያለ ቤት እንደሆነና እንደወደዱት፣ ቶሎ ሄጄ እንዳየውና እንድከራየው ሲነግረኝ፣ ገንዘቡ በጣም ብዙ እንደሆነና ይህን ሚያህል ገንዘብ
እንደሌለኝ ነግሬው ስልኩን ዘጋሁት፡፡ ስመለስ፣

“ይቅርታ ስላቋረጥኩሽ ሃን፡፡”

“አይ ችግር የለውም፡፡ የሆነ ልነግርህ ምፈልገው ነገር ነበረኝ፤” በቀዘቀዘ ድምፅ፡፡

“ታዲያ ምንችግር አለው፣ ንገሪኛ፡፡”

“ስሜ ሃናን አይደለም፡፡ ማሂ ነው፤” ብላኝ አትኩራ ተመለከተችኝ፡፡

አልመለስኩላትም፡፡ የስም መመሳሰሉ አስደንግጦኝ ዝም አልኩኝ፡፡

“ስለዋሸሁህ በጣም ይቅርታ! ሌላም የዋሸሁህ ነገር አለ፡፡”


“ምንድን ነው?” ውስጤን ፍራት ወረረኝ፡፡ ማላቃትን ልጅ ነው እንዴ የወደድኩት ብዬ አሰብኩ፡፡ መጥፎ ነገር እንዳይሆን
ተመኘሁ፡፡

“ፊልም ነው ምሰራው ያልኩህ...”

“እና ምንድን ነው የምትሰሪው...?”

“አሜሪካ ነበርኩኝ፤ አሁን ትቼው መጥቼ ነው::”

“ለምንድን ነው ትተሽው የመጣሽው..?

“ከዚህ ስሄድም ሳልፈልገው፣ በድንገት ነው የሄድኩት፡፡ የአዋላጅ ነርስ ነኝ፤ እዚህ ደስተኛ ነበርኩ፡፡ ውጪ ስለመሄድ አስቤም፣ ጓጉቼም አላውቅም፡፡ ፍቅረኛ ነበረኝ፡፡ እርሱ ደግሞ በተቃራኒው፣ ህልሙ አሜሪካ ነበረች፡፡ እዚህ እየኖረ ነበር ማለት ይከብዳል፡፡ ፌርማታ ጋር ቁጭ ብሎ ባስ እነደሚጠብቅ ሰው፣ አሜሪካ እስኪሄድ ሲጠባበቅ ነበር፡፡ አሜሪካ ለመሄድ ያልሞከረው ነገር የለም፡፡ አንድ ዓመት ላይ ዲቪ ሲከፈት፣
አብረን እንሙላ አለኝ፡፡ ሞልቼ አላውቅም፣ ትዝም አይለኝ ነበር፡፡ እንደባልና ሚስት ሞላን፣ ባጋጣሚ ደረስን፡፡ ብዙ ሰው እንድለኛ ነሽ አለኝ፡፡ እልል ተባለ። በተለይ ነርስ መሆኔ ብዙ እንደሚጠቅመኝ ነገሩኝ፡፡ፕሮሰሱን ጨርሰን አሜሪካ ገባን፡፡

እንደሄድን ከጓደኛዬ ቀድሜ እኔ ቶሎ ስራ አገኘሁ፡፡ ካሊፎርኒያ ውስጥ የሚገኝ አንድ ሆስፒታል፡፡ ጓደኛዬም ብዙም አልቆየም፣ ሌላ ስቴት ላይ ስራ አገኘ፡፡ አንድ መጋዘን ውስጥ ተቆጣጣሪ ሆኖ ተቀጠረ፡፡ በመጀመሪያ ሁሉ ነገር ደስ ብሎኝ ነበር፡፡ የሆስፒታሉ ንፅህና፣
አደረጃጀት፣ የህክምና መሳሪያዎች፣ ክፍያው፣ ብቻ ሁሉም ነገር በጣም ደስ አለኝ፡፡ ከተወሰነ ግዜ በኋላ፣ እርሱም ቢዚ እየሆነ፣ መገናኘት እየከበደ፣ ይናፍቀኝ ጀመር፡፡ እርሱ፣ በትርፍ ሰዓቱ ሌላ ተጨማሪ ስራ መስራት ሲጀመር፣ የምንገናኝበት ጊዜ በጣም ቀነሰ፡፡ ከሳምንታት ወደ ወራት ረዘመ:: ሲደውልልኝም፣ ከድምፁ የምሰማው ናፈቆት ሳይሆን ድካምና መሰልቸት ሆነ፡፡ ለእኔ ቦታ እንደሌለው እየተሰማኝ መጣ፡፡ ብዙ እንጨቃጨቅ፤ እንጣላ ጀመርን፡፡ አትወደኝም እለዋለሁ፤ አትረጂኝም፤
ይለኛል። ሲኒማ እንኳ ከሰው ጋር መግባት ናፈቀኝ፡፡ ማውቃቸው ሰዎች ጋር ደውዬ ሲኒማ እንግባ ስላቸው፣ እስቲ ፕሮግራም ልይ ይሉና፣
(Next Month the last Sundayi am free, we can meet and do it)
የሚቀጥለው ወር የመጨረሻው እሁድ እረፍት ነኝ፣ መገናኝት እንችላለን
ይሉኛል፡፡

እኔ ደግሞ ሰው ነው የራበኝ፡፡ እረሃብ ደግሞ ግዜ አይሰጥም፡፡ሰው ስናፈቀኝ በሁለት ወር ሰው ማግኘት ሰለቸኝ፡፡ ስሜት አልባ በሆኑ፣ በቁሳዊ ነገሮች በሚደሰቱ ሰዎች ብቻ የተከበብኩ ያህል ተሰማኝ፡፡ ጓደኛዬ ከኔ ይልቅ፣ ፍቅር ያለውጠ ለዳላር ሆኖ ተሰማኝ፡፡ ሁሉም machine
people, with machine brain and machine hearts መስለው ታዩኝ፡፡
የሰው ተፈጥሮ የሌላቸው በውስጣቸው፣ የሰው ፍቅር ርሀብ ማይሰማቸው፣ ዓለምን አስደናቂ፣ ግሩምና ሳቢ የሚደርጓት ቁሶች
ሳይሆኑ፣ ሰውና ተፈጥሮ እንደሆኑ ያልገባቸው ሮሆቦት ሆኑብኝ፡፡ በሰው
መሀል ሆኜ ሰው እራበኝ፡፡ ጥዬው መጣሁ፡፡”

በትካዜ ስሜት ውስጥ ሆና አወራችኝ፡፡ ለጥቂት ደቂቃዎች ዝም አለች፡፡ ደስተኛ ትመስለኝ ነበር፣ ንፁህ ያልደማ ልብ ያላት። ከትረካዋ እርሷም ቁስለኛ እንደሆነች ተረዳሁ፡፡ ላቋርጣት አልፈለኩም፡፡ይውጣላት፡፡ ትተንፍስ ብዬ፣ ዝም አልኳት፡፡ ቀጠለች፡፡

“ለእኔ ህይወት ቁስ አይደለም፣ ማፍቀር ነው! To live is love”! ከጓደኛዬ ተጣላን፡፡ የአሜሪካ ኑሮ በእኔ ዕይን፣ እድሜህን ለመቼ እንደሆነ ለማይታውቀው ነገ ቁስ እየሰበሰብክ፣ ዛሬህን የምታባክንበት ህይወት ነው፡፡ የእኔ ሀገር እዛ አይደለም! ወሰንኩ፡፡ ግን፣ ከባድ ውሳኔ፡፡ብነግራቸው፣ ባስረዳቸው ሚረዳኝ አጣሁ፡፡ ጭራሽ እንደ እብድ ቆጠሩኝ፡፡ጥዬው መጣሁ፡፡ ከመጣሁ አስር ወር አለፈኝ፡፡ እዚህ ስራ ለመጀመር
ወስኜ ነው የተመለስኩት፡፡ ውሳኔዬ ማንንም ደስተኛ አላደረገም፡፡ቤተሰብ፣ ጎሮቤት፣ ጓደኛ፡፡ ሁሉም በእራሳቸው ምኞት፣ ለክተው እያሰቡና እየመዘኑ ስህተት ነሽ ይሉኛል፡፡ ሊመክሩኝ፣ ሊያሳምኑኝ ይጨቀጭቁኛል
👍5
#የታካሚው_ማስታወሻ


#ክፍል_አስራ_አምስት


#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ(MD)

ባለፈው ስናወራ፣ ሰው ሞልቶ፣ ሰው ሲጠፋ ምን ይደረግ ስትለኝ፣እንደኔው ሰው እንደራበህ ተሰማኝ፡፡ ሁሉም እንዲሆን በደስታ ፈቀድኩልህ፡፡ እንዲህ እንግባባለን ብዬ ስላልገመትኩ የውሸት ስምና ስራ ፈጥሬ ተዋወኩህ፡፡ ለዛ ነበር የዋሸሁህ፡፡” ዝም አልኳት፡፡

“በቃ ይሄው ነው፤” አለችኝ፡፡

“አንድ ነገር ልንገርሽ”

“እሺ ንገረኝ፡፡"

“ስለዋሸሽኝ አልተቀየምኩሽም፡፡ ግን እኔ ካሁን በኋላም ቢሆን፣ሃኒ ብዬ ነው ምጠራሽ፡፡ ማሂ ሚባል ስም ቆሌዬ አይወደውም፡፡”

“ኪ.ኪ.ኪ...፣ እሺ ባክህ፣ ባለ ቆሌ፣ አንተ ደስ እንዳለህ ጥራኝ፡፡” በአንዴ ፊቷ ከትካዜ ተላቀቀ፡፡ጥብቅ አድርጌ አቀፍኳትና “ሃኒዬ፣ ያደረግሺው ሁላ፣ ትክክል ነው፡፡ ትክክለኛ ውሳኔ ነው የወሰንሽው፡፡ ህይወት አንዴ ናት፡፡
አትደገምም፡፡ የአዕምሮ ደስታን፣የመንፈስ እርካታን የማይፈጥሩልሽን ቁሶች ስትሰበስቢ፣ ነብስሽ የምትሻውን ሳታገኚና ሳታጣጥሚ ለመሞት፣መኖር የለብሽም፡፡ ሚዛኑን መጠበቅ አስፈላጊ ነው!መኪና፣ ቤትና፣ሌሎች ቁሶች፣ ቋሚ ደስታ ሚፈጥሩ ሚመስሏቸው፣ እነርሱ ሳይገባቸው ሊያስረዱሽ የሚሞክሩ፣ ስላላዩት ሀገር የሚያወሩሽ፣ ሳይደርሱበት በርቀት እያዩ፣ በምኞት እረሀብ የሚቃጠሉና የሚቃዡ ናቸው፡፡ ተያቸው፡፡ ግራ ገብቷቸው ነው፣ ግራ ሚያጋቡሽ፡፡ እርሻቸው።” ፊቷ ላይ የደስታ ብርሃን
መፈንጠቅ ጀመረ፡፡

ጭምቅ አድርጋ አቀፈችኝ፡፡ “ያቡዬ ስለተረዳኸኝ በጣም አመሰግናለሁ!! አንተ ትክክል ነሽ፣ ያልከኝ የመጀመሪያው ሰው ነህ።እራሴን መጠራጠር ጀምሬ ነበር፡፡ ከረጅም ጊዜ በኋላ ትክክል እንደሆንኩ
እንዲሰማኝ አደረከኝ፡፡ ካገኘሁህ ቀን ጀምሮ ጥሩ እንዲስማኝ አድርገኸኛል። እወድሃለው፡፡”

ግንባሯን ሳምኳትና፣ “ደስተኛ እንደሆንሽ ስለነገርሽኝ፣አመሰግናለሁ፡፡ እኔም፣ በህይወቴ ተሰምቶኝ የማላውቀውን ደስታ
ሰጥተሽኛል፡፡ አንቺ በጣም ልዩ ሴት ነሽ፡፡ ስላንቺ በደንብ አስብያለሁ፡፡እንደዚህ አይነት ስሜት ተሰምቶኝ አያውቅም፣ የልቤ ንግስት አንጓነሽ፡፡ መቼም በምንም ምክንያት ላጣሽ አልፈልግም፡፡ ከአሁን በኋላ ሁሌም፣ በሁሉም ነገር አብሬሽ ነኝ፡፡ አንቺን ለማስደሰት ምንም አደርጋለሁ፡፡ ምንም!፡፡ አንቺ ለእኔ ልዩ ስጦታዬ ነሽ፡፡ ቀኑ ሲደርስ፣እኔም እንዳንቺ ሙሉ ታሪኬን እነግርሻለሁ። እስከዛው ግን እጅግ በጣም እወድሻለሁ፡፡” እንደዚህ የውስጥ ስሜታችንን ስናወራ አምሽተን ሸኘኋት፡፡

ከሃኒ ጋር በተደጋጋሚ እንገናኛለን፡፡ ሲከፋት፣ ሚረዳት ስታጣ እኔ ጋር ትደውላለች፡፡ የሙያ ፍቃዷ ስለተቃጠለ፣ ስራ መጀመር ከብዷታል፡፡ ቤተሰብ ደግሞ፣ በስራ መፍታቷ አመካኝቶ ያንገበግቧታል።ውሳኔዋ ስህተት እንደነበር እንድታምን በአሽሙር ይወጓታል፡፡ ተከፍታ መጥታ እኔ ጋር አምሽታ ሁሉን እረስታ ወደቤቷ ትመለሳለች። እኔም በእርሷ በጣም ደስተኛ ሆኛለሁ። የእኔ መኖር የሚጠቅመው፣ሚያስፈልገው ህይወት አገኘሁ፡፡ ተደስታ ስትሄድ ማላውቀው ደስታ ውስጤን ይሰማኛል። ስለሷ ማሰብ የህይወቴ ዋና ክፍል ሆኗል፡፡

ከእርሷ ጋር መኖርን ያጓጓኛል። አሁን መኖር አለብኝ፡፡ህይወቴን ሙሉ እርሷን ደስተኛ እያደረኩ መኖር እፈልጋለሁ፡፡ የሃኒ
ተስፋዋ፣ መከታዋ እኔ ነኝ፡፡ በየቀኑ ከምትነግረኝ ብሶት ልገላግላት ምችለው እኔ ብቻ ነኝ፡፡ ሆቴል ቁጭ ብዬ፣ ገቢ የሌለው ወጪ ብቻ የሆነ፣ ተስፋ የቆረጠ ሰው ንሮዬን አብቅቼ፣ ሰው ሆኜ ለእርሷም
ለመትረፍ በፍጥነት ስራ መጀመር አለብኝ፡፡ የዶሮ እርባታውን ስራ
ማፍጠን አለብኝ፡፡ መነሻ ስንት ብር ያስፈልገኝ ይሆን? አሌክስ ባለፈው
የነገረኝ የቤት ኪራይ ውድ ነው፡፡ ሌላስ የምን ወጪ አለ? ሃብታሙን ደውዬ ያለበት ቦታ ሄጄ አገኘሁት፡፡ ጭንቅላቴ ወር ሙሉ ሲያንቀላፋ ከርሞ፣ አሁን ያጣድፈኝ ጀመር፡፡ እንዳገኘሁት በቀጥታ ወደ ጉዳዩ
ገባሁ፡፡

“ሃብትሽ ያን ጉዳይ ዝም አላችሁኝ እኮ፡”
“የቱን ነው ያቤዝ?”

“የዶሮ ስራውን ነዋ፡፡ ጭራሽ በኛ ጣለው ብላችሁ ዝም አላችሁኝኮ፡፡”

“እ...፣ እሱንማ አንተው ነህ ዝም ያልከው፡፡ ባለፈው አሌክስ ቤት አገኘን ሲልህ፣ ሄደህ እንኳ አላይ ስትል የተውከው መሰለን፡፡”

“እሱኮ ውድ ሆኖብኝ ነው ሃብትሽዬ፡፡”

እሺ፣ ምን አይነት ዶሮ ነው ማርባት ምትፈልገው?”

“ማለት? ዶሮ ነዋ፡፡ ዶሮ ምን አይነት አለው?”

“አለው እንጂ ፤ የስጋ ዶሮ ነው፣ ወይስ የእንቁላል ማርባት ምትፈልገው?”

“እንደዛ ሚባል ነገርም አለ እንዴ? ሃብትሽዬ እኔ ምንም እውቀቱ የለኝም፡፡ ሚሻለውን እናተ ምረጡልኝ፡፡ ፕሊስ ሃብትሽ.”

“እኔ የእንቁላል ዶሮ ብትጀምር እመክርሃለው። ምክንያቱም፣ የእንቁላል ገበያ አመቱን ሙሉ አለ፡፡ ያ ደግሞ፣ አመቱን ሙሉ በወጥነት የሆነ ያህል ቢሆንም ገቢ አለህ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ፣ እንደቤት ኪራይና ሌሎች የወር ወጪዎችን ሊሸፍንልህ ይችላል፡፡ ያው ትንሽ በዛ ሚለው የምግብ ወጪያቸው ነው፣ እሱን ፈልጎ ከአቅራቢ መግዛት ነው፡፡ የስጋዎቹን ካረባህ፣ ምታገኘው ገቢ በአመት በተወሰነ ግዜ በአል ጠብቀህ
ብቻ ነው፡፡ ደግሞ ስንት ለፍተህ፣ በሽታ አንድ ነገር ቢያደርጋቸው፣እንዳትነሳ ሆነህ ትጎዳለህ፡፡” አለኝ፡፡

“እውነትህን ነው ሃብትሽ፤ የእንቁላል ይሻለኛል፡፡ አሌክስ ጋር ደውልለትና እረከስ ያለ ቤት ቶሎ ይፈልግልኝ፡፡ ምንም ስራ ሳልጀምር እጄ ላይ ያለው ብር ሊያልቅኮ ነው፡፡ በናትህ ሃብትሽ ቅበሩኝ፡፡” ተጣድፌ አጣደፍኩት፡፡

አሌክስን ደወለለትና፤ ይዤው ቤት ፍለጋ ከከተማው ጫፍ እስከ ጫፍ መዞር ጀመርን፡፡ በሁለት ቀን ከተማ ውስጥ ያሉትን ሰፈሮች አካለልናቸው፡፡ ቤት ውድ ነው፡፡ ለንግድ ሲሆን ደግሞ፣ ከስድስት ወር በታች ቅድመ ክፍያ አይቀበሉም፡፡ በመጨረሻም፣ በወር ሁለት ሺህ ብር
ለስድስት ወር አስራ ሁለት ሺህ ብር ከፍለን ተከራየን፡፡ ቤቱ ባለ ሶስት ክፍል ሲሆን፣ አንዱ እንደመጋዘን ሰፊና አራት መአዘን ነው፡፡ እሱን አናፂ ቀጥረን በስስ ሽቦ ወደ ስምንት የዶሮ መኖሪያ ክፍሎች ቀየርነው፡፡ተስፋ ቢስና ስልቹ የነበርኩት ልጅ፣ እነ ሃብትሽና አሌክስ እስኪሰለቹኝ፣
ጉዳዬን ሳልቋጭ ማይደክመኝ ተስፈኛ ሆንኩ፡፡ እንቁላል ጣይ ጫጩት በርካሽ ገዝቼ ከመጠበቅ አንድ መቶ እንቁላል ለመጣል የደረሱ ዶሮዎችን መርጬ ገዛሁና ስራ ጀመርኩ፡፡ ለአልጋ በየቀኑ የማወጣውን ወጪ ለመቆጠብ፣ አንዱን ክፍል ፍራሽና ብርድ ልብስ ገዝቼ መኖሪያዬ አደረኩት። ሃኒ ምግብ ማብሰያ እቃዎች ገዝታ፣ እቤት እየተመላለሰች
ታበስልልኝ ጀመር፡፡ በዛውም፣ እቤት ያስከፏትን ብሶቷን ስትነግረኝ አምሽታ እራት አብልታኝ ትሄዳለች፡፡

ከሁለተኛው ሳምንት በኋላ፣ እጄ ላይ ገንዘብ ጨረስኩኝ፡፡የዶሮዎቹን ምግብና የእኔን የቀን ወጪ መሸፈን አቃተኝ፡፡ ለሃብትሽ ሳማክረው፣ ስራው ጥሩ ትርፍ የሚኖረው፣ አምስት መቶና ከዛ በላይ
እንቁላል ጣይ ዶሮዎች ሲኖር እንደሆነ ነገረኝ፡፡ እርሱ የነገረኝን ከማመንና ከመፈፀም፣ ወደ ፊት ከመሄድ ውጪ ምንም አማራጭ የለኝም፡፡ ያንን ለማድረግ ደግሞ መኪናዬን መሸጥ አለብኝ፡፡ ለመሸጥ ያላገባ ሳወጣ፣ እናቴ መኪና ልሽጥ እንደሆነ ጠርጥራ፤ 'ተው ልጄ ተው፣ ምን ሆንኩ ብለህ ነው ንብረት ምትሸጠው? ተው ንብረት ዝም ተብሎ አይሸጥም፡፡ ተው ልጄ፡፡" አለችኝ፡፡ ምክሯን ከቁብ ሳልቆጥረው፣ቆም ብዬ ሌላ አማራጭ እንኳ ለማየት ሳልሞክር መኪናዬን ሸጥኩኝ፡፡ተጨማሪ አራት መቶ እንቁላል መጣል የደረሱ ዶሮዎችንና ምግባቸውን በጅምላ ገዛሁ፡፡

አሁን በገንዘብ እጥረት ሚሰማኝ ስጋት ጠፋ፡፡ ኪሴ ወፍሯል፡፡ግን ገና ከቤት ለመውጣት ሳስብ፣ የታክሲ ጥበቃውና ፀሃዩን
👍1
#የታካሚው_ማስታወሻ


#ክፍል_አስራ_ስድስት


#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)

ጉዞ ወደ አርባምንጭ፤በጥዋት ተነስተን በሚኒ ባስ ተሳፍረን ጉዞ ጀመርን፡፡ሃኒ ከአዲስ አበባ ስንነሳ ጀምሮ መኪናው አልተመቻትም፤ ስትንቆራጠጥ ነው ሻሸመኔ ደረስን አደርን፡፡ ከሻሸመኔ ደግሞ ቅጥቅጥ አይሱዙ ተሳፍረን፣ በወላይታ
ሶዶ አድርገን፣ ጉዞ ወደ አርባ ምንጭ፡፡ መኪናው እላይ አድርሶ ያፈርጠናል፡፡ ደጋግሜ አይዞሽ እላታለሁ፡፡ በእርግጥ እንደዛ ከማለት ውጪ፣ ምንም ማድረግ ምችለው ነገርም የለም፡፡

“መዝናናት ሳይሆን መጉላላት ሆነብሽ?” አልኳት የሚሰማትን ማውቅ ፈልጌ፡፡

“ለምንድነው ግን፣ በቱር መኪና ያልመጣነው?” አለች፡፡

“አቅም ነዋ ሃኒዬ፣ አቅም..! በጣም ውድኮ ነው፡፡ በቀን ሁለት ሺህ አምስት መቶ ብር፣ አይከብድም...?”

“ኖ...! እንደሱ ሳይሆን፣ ኮስትር በጋራ ከሌላ ጎብኒዎች ጋር ሆነን ማለቴ ነው፡፡”

“እንደዛ አይነት ፓኬጅ ያለ አይመስለኝም፡፡ ሰምቼ አላውቅም፡፡
ሙሉ ኮስትር ግን ይባስ ውድ ነው፡፡”
“ለምን እንከራየዋለን? እንደኛ አርባ ምንጭን ለመጎብኘት የሚፈልጉ ተጓዦችን አሰባስቦ የሚሄድ፣ የአስጎብኚ ድርጅቱ ጋር ሁለት ትኬት ገዝተን ብንሄድ ነው ምልህ፡፡ እንደውም፣ አስጎብኚ ስለሚኖር ብዙ ነገሮችን ማየት እንችላለን፡፡”

“እንደምትዪው አይነት ጉዞ ሰምቼ አላውቅም፡፡ በአስጎብኚዎች የሚዘጋጅ፣ የግሩፕ የጉብኝት ጉዞ እድል ያለው፣ ወደ እስራኤልና ሲሸል ለማስጎብኘት ሲሆን፣እንጂ ሀገራችን አልተለመደም፡፡ ሀገራችንን ለማየት፣ ያለን አማራጭ፣ በቀን ሁለት ሺህ አምስት መቶ ብር ከፍሎ፣ ላንድክሩዘር መከራየት ይጠይቃል ወይም
እንደዚህ በተለመደው የህዝብ ትራንስፖርት ተሳፍረሽ፣ ለመዝናናት
እየተጉላላሽ መሄድ ነው፡፡ የግሩፕ ጉዞ ቢኖር ኖሮማ፣ይሄኔ ሀገሬን ከሰሜን እስከደቡብ፣ ከምስራቅ እስከምዕራብ ማየት እችል ነበር፡፡”

“እንዴ ይኼ እኮ አሪፍ ቢዝነስ ነው፡፡ እና ወደ አርባ ምንጭም ሆነ፣ ወደተለያዩ የሀገራችን ተፈጥሯዊና ባህላዊ መስህብ ያላቸውን ቦታዎች በተደራጀ መልኩ፣ ቅስቀሳ አድርገው፣ በተመጣጣኝ ዋጋ
የማስጎብኘት ስራ የሚሰሩ ድርጀቶች የሉም እያልከኝ ነው?”

“በእርግጥ፣ ይሄ አካሄድ ገዳማትን ለማስጎብኘት በየታክሲው፣በከተማዋ ግድግዳዎችና የስልክ ቋሚዎች ላይ በሚለጠፉ ቅስቀሳዎች፣ፍላጎቱ ያላቸውን ሰዎችን አሰባስበው በማደራጀት በተመጣጣኝ ዋጋ ጉብኝቶችን ሲያዘጋጁ አይቻለሁ፡፡ ነገር ግን ይህን አካሄድ፣ በጥቂቱ አዘምነው፣ ሀይማኖታዊ ላልሆኑትም ለሌሎች የሀገሪቱ መስህቦችን ለማስጎብኘት ብንጠቀምበት፣ ማህበረሰቡን በተመጣጣኝ ዋጋ የተለዩ የሀገራችንን መስህቦች ለማስጎብኘት እድል ይሰጣል፡፡ በሂደቱም፣ ለብዙ ሰዎች የስራ እድል ከመፍጠሩም በላይ፣ ለሀገራችን ኢኮኖሚ ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል፡፡ ነገርግን፣ ይህ የተለመደ ባለመሆኑ፣ ላሊበላን፣
አክሱምን፣ የጀጎል ግንብን፣ የባሌ ብሄራዊ ፓርክን፣ ነጭሳር ፓርክን
እና ሌሎች ልዩ እና ድንቅ የሆኑ የሀገራችን ውበቶችና ኩራቶች ከዜጎቻችን ይልቅ በውጪ ቱሪስቶች ይጎበኛሉ፡፡ ትውልዱም ሀገሩን የማወቅ እድል ስለሌለው፣ በሀገሩ መኩራት ሲገባው፣ ባለማወቁ ፀምክንያት ያፍርባታል፡፡”

“ይኸውልህ ያቡ፣ የህዝብ ትራንስፖርት ላይ ያለው ውጣ ውረድ አድካሚ እና የሚያጉላላ ከመሆኑም በተጨማሪ በየቦታው የሚገኙ መስህቦችን ቆም ብሎ ለማየት፣ ለማድነቅና ፎቶ ለማንሳት አይመችም፡፡በመሆኑም ጉብኝቱን የተሟላ እንዳይሆን ያደርጋል፡፡ እንደምትነግረኝ ከሆነ፣ የአስጎብኚ ድርጅቶች አደረጃጀት የውጪ ዜጎችንና ከፍተኛ የኑሮ ደረጃ ያላቸውን ሰዎች ብቻ ያማከለ ይመስላል፡፡ ይህም የመጎብኘት
ባህላችን ላይ ተፅዕኖ ያሳድራል፡፡ ጉብኝትን እንደቅንጦት እንዲቆጠር
ያደርጋል፡፡ እራስን አድሶ ለቀጣይ ስራ እራስን ከማዘጋጀትም በላይ፣
በመጎብኘት ውስጥ በጣም ብዙ አዲስ እውቀት፣ የፈጠራ ሀሳቦችና የልምድ ልውውጦች አሉ፡፡”

“ትክክል ብለሻል ሃኒዬ፡፡ እንደማህበረሰብ የመጎብኘት ባህላችን መሻሻል አለበት። እንዳልሺው መጎብኘት ከመዝናናት በዘለለ ብዙ ፋይዳዎች አሉት፡፡ አንዱ ማህበረሰብ ውስጥ ያየሽውን ባህልና እሴት ቀምረሽ፣ በህይወት ለሌሎች ችግሮችም እንደ መፍትሄ ልትጠቀሚበት
ትችያለሽ፡፡ ነገር ግን እንዳለ መታደል ሆኖ፣ በማህበረሰባችን መጎብኘትን
እንደቅንጦት፣ ለመጎብኘት የሚያወጣን ወጪ እንደ ማባከን የሚቆጥረው
ቁጥሩ ቀላል ሚባሉ አይደሉም፡፡”

እየተጫወትን ለመርሳት የመኪናውን እንግልት እንዲህ ሞከርን፡፡ ሲደክማት ጋደም እያለችብኝ፣ አስር ሰአት አርባ ምንጭ ከተማ ገባን፡፡ እንደደረስን ቱሪስት ሆቴል አልጋ ያዝን፡፡ ቢደክመንም፣ ሃኒ
ከተማውን ለማየት ካላት ጉጉት የተነሳ፣ ሳናርፍ ሻወር ወስደን ወጣን፡፡በቅርብ የተሰራ የውስጥ ለውስጥ መንገድ፣ ለከተማዋ አዲስ ውበት ሰጥቷል፡፡ አርባ ምንጭ ግርግር ያልበዛበት ደርባባ ከተማ ነች፡፡ በባጃጅ ተዘዋውረን ከተማዋን ለማየት ሞከርን፡፡ ከተማዋ ሁለት ጫፎች አሏት፡፡የዩኒቨርስቲውን መስፋፋት ተከትሎ የተመሰረተውና የቀደመው መንደር ደረጃውን በጠበቀ የአስፓልት መንገድ በቅርብ እንደተገናኘ ያስታውቃል፡፡
አስፓልቱ ሳይሰራ ከተማዋን አሰብኳት፡፡ የአባይና ጫሞ ትልልቅ ሀይቆች ሀገር፣ የነጭ ሳር ፓርክ፤ የአዞ ገበያ፣ የሙዝና የተለያዩ ፍራፍሬዎች፣ የቱሪስት መናኸሪያ ሀገር፣ አርባ ምንጭ የረባ የአስፓልት
መንገድ ለዓመታት ብርቋ ነበር፡፡

ለዐይን ያዝ ሲያደርግ ወክ እያደረግን ወደ ቱሪስት ሆቴል ተመለስን፡፡ ወደ ሆቴሉ እንደገባን ረሃብ ስሜት ተሰማኝ፡፡ እራት
ለመብላት ዞርዞር ብለን ቦታ መፈለግ ጀመርን፡፡ አንድ ጥግ ላይ ክፍት ቦታ አገኘንና ተቀመጥን፡፡ አስተናጋጅ እየጠበቅን፣ ግቢውን ቃኘነው፡፡

“ግማሽ በግማሽ ፈረንጅ አይደል እንዴ?” አለች ሃኒ፡፡

“ያው ቱሪስት ሆቴል አይደል፡፡”

“ኪ.ኪ.ኪ..፣ እና ለዛ ነው?”

ማለቴ አርባ ምንጭ እኮ ምድራዊ ገነት ናት፡፡” አስተናጋጁ መጥቶ “ምን ልታዘዝ!” አለን፡፡

“ምን እንብላ ሃኒዬ?”

“እንዴ! አርባ ምንጭ መጥተንማ፣ ከአሳ ውጪ መብላት...”

“እሺ! አንድ ለብለብ አንድ ጉላሽ ይሁን?”

“እሺ፣አሪፍ ነው፡፡”

“የሚጠጣ ሁለት ጊዮርጊስ ቢራ፡፡”

አስተናጋጁ እየተዋከበ ከአጠገባችን ሄደ፡፡ ግቢውን በዐይኔ ቃኘሁት፡፡ በግቢው የመዝናናት መንፈስ ሰፍኗል፡፡ ሰው ይበላል፤ ይጠጣል፡፡ ይጫወታል፡፡ ከሃኒ ጀርባ የተቀመጡ ሁለት ነጭ ሴቶችን አየሁ፡፡ ከኔ ትይዩ ያለችው ፈረንጅ
👍3
#የታካሚው_ማስታወሻ


#ክፍል_አስራ_ስምንት


#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)

“ምን እያደረክ ነው?” የሚል ድምፅ ሰምቼ ቀና ስል፣ ግዙፍ ቅልብ ጎረምሳ ፊትለፊቴ ቆሟል፡፡ ልቤ ፀጥ ልትልብኝ ነው፡፡

“ዕቃ ወድቆብኝ እየፈለኩ፡፡”

“መጀመሪውኑ ባጃጄ ውስጥ ምን ፈልገህ ገባህ ነው የምልህ?”

“ባለ ባጃጁ አንተ ነህ? ጭፈራው ቤት ነበርን፡፡ ብጥብጥ ሲነሳ ኮንትራት ፈልገን ስንመጣ የለህም፡፡ እንድታደርሰን ቁጭ ብለን እየጠበቅንህ ነው፡፡” ብዬ፣ ከሾፌሩ ወንበር ላይ ቀስ ብዬ ጠጋ አልኩና
ቦታውን ለቀኩለት። ከኋላ ዞር ብሎ ሲመለከት ብቻዬን እንዳልሆንኩ
ተገነዘበ፤

“ወዴት ናችሁ?”

“ቱሪስት ሆቴል።”

“መቶ ብር ትከፍላላችሁ፡፡”

“ችግር የለውም፡፡” ኡፈይ አልኩ በውስጤ፡፡

ቁልፉን አውጥቶ ባጃጇን ለማስነሳት ሞከረ፣ ምንም ድምፅ የለም፡፡ ደጋግሞ ሞከረ፣ ምንም የለም፡፡ ደነገጥኩ፡፡ እኔ ስጎትት ወደ የነበረበት ጎንበስ ብሎ አየ፡፡ ላብ አጠመቀኝ፡፡ ስካሬ ብን ብሎ ጠፋ፡፡ ገመድ በጥሼ ይሆን እንዴ? የሆነ ነገር ነካካ፡፡ መልሶ ቁልፉን ሞከረ፡፡ ባጃጇ
ተረክ ብላ ተነሳች፡፡ ተመስገን...፣ ከግንባሬ ላይ ላቤን ጠራረኩ፡፡

እንግዶች ናችሁ?”

“አዎ፡፡”

“አርባ ምንጭ ሰላማዊ ከተማ ነች፡፡ የቅድሙ ፀብ አጋጣሚ ነው፡፡ በሴት ተጣልተው ነው፡፡ አትደንግጡ፡፡ እንደዚህ ተፈጥሮ አያውቅም፡፡ ዘና በሉ፡፡ ከፈለጋችሁኝ ስልኬን ውሰዱ፡፡”
“እሺ እናመሰግናለን፡፡ ስልክ ቁጥርህን ስጠን፤” አልኩት፡፡ሆቴላችን አድርሶን፣ ሂሳብ ከፍለን ቁጥሩን ተቀብለን ወረድን፡፡ ባጃጁ ከሄደ በኋላ፣ ሦስቱም ያደረኩትን እያስታወሱ፣ ያሽኩብኝ ጀመር፡፡

“ቆይ ባጃጇን ምን ልታደረጋት ፈልገህ ነው፣ እንደዛ የተንፈራፈርከው?” ከት... ከት... ከት

“በተለይ ባጃጇ በቁልፉ አልነሳም ስትልማ የደነገጥኩት ድንጋጤ... ” ከት... ከት ከት..

“ደግሞ እኮ ተው ሲባል አይሰማም፡፡” ከት ከት...

“እኔማ ይሄ ልጅ፣ ዛሬ እስር ቤት አሳደረን እያልኩ ነበር፡፡” ከት..ከት..

የሰራሁት የእብድ ስራ መልሶ እኔንም ያስቀኝ ጀመር፡፡

አብሪያቸው እስቃለሁ፡፡ እስኪደክማቸው፣ እንባ እሰኪወጣቸው ሳቁብኝ፡፡

“ኧረ ሰዓቱን እዩት፡፡ ከለሊቱ ስምንት ሰዓት አልፏልኮ፡፡” አልኩኝ እንደደከመው ሚስቁብኝን ለማስቆም፡፡ ወደ ክፍላችን ገባን፡፡ ልንተኛ ስል፣ ቅድም ከነጮ ጋር ባደረኩት የተሰማኝ ፀፀት ጠፍቶ፣ ስሜቴ.
እንደገና ሲያገረሽ ተሰማኝ፡፡ ምክንያት ፈልጌ መውጣት ፈለኩ፡፡ ምን ብዬ እወጣለሁ፡፡ ሽንት ቤቱ እዚሁ ነው፡፡ ሌላ ምን ምክንያት እፈጥራለሁ፡፡ ኢቫም እንደኔው እያሰበችኝ ነው ብዬ ገመትኩ፡፡ ጆሮዬን አቁሜ ውጪ ያለ የተለየ እንቅስቃሴ ማዳመጥ ጀመርኩ፡፡ በር ላይ የቆመ ሰው እንዳለ ይሰማኛል፡፡ ሃኒ ተኝታለች፡፡ ቀስ ብዬ ከአልጋ ውስጥ
ወጣሁ፡፡ ከአልጋው ብድግ ስል፧ “እንቅልፍ እንቢ አለህ እንዴ ያቡ”
አለች ሃኒ፡፡ አልተኛችም፡፤

“አይ ይሄን ቢራ ልፈን ሽንቴ..”

ለይስሙላ ሽንት ቤት ደርሼ ተመልሼ ተኛሁ፡፡ በንጋታው በጣም የድካም ስሜት ተሰማን፡፡ ከአልጋችን ላይ አርፍደን ተነሳን፡፡ ቁርስ እንደነገሩ ቀማመስን፡፡ ሁለታችንም የምግብ ፍላጎት አልነበረንም፡፡ ሃኒም ከኔ እኩል ድካም ተሰምቷታል፡፡ ከሰዓት በአብዛኛው እክፍላችን ተኝተን አሳለፍነው፡፡ አስራ ሁለት ሰዓት አካባቢ ተነስተን ከክፍላችን ወጣን፡፡

“ሃኒዬ እርቦኛል፡፡”

እኔም ልልህ ነበር፡፡ የሆነ ነገር እንብላ፡፡”

“ምን እንብላ?”

“አሳ እንዳይሆን እንጂ፣ የፈለገከውን፡፡”

“ከአሳ ውጪ እንዳላልሽ፣ ሰለቸሽ?”

“ሳይሆን፣ ቅድመ ጥንቃቄ ነው፡፡”

ወጥተን ምሳችንን እንደነገሩ በላን፤ ቡና ጠጥተን ሰውነታችንን ለማፍታታት ከሆቴላችን ወጣን፡፡ ስለ ሀገሩ ለምነት እያወራን፣ በትናንትናው እብደት እየሳቅን፣ ነገ ነጭ ሳር ፓርክን ለማየት እያቀድን
የአርባ ምንጭን የምሽት ንፁህ አየር እየማግን፣ በእግራችን ብዙ
ተንቀሳቀስን፡፡
በንጋታው በጥዋት የበቀደሙ አስጎብኚ ድርጅት ጋር ሄድን፡፡

“ሄይ እንዴት ነህ አለቃ?" አልኩት፡፡

“አለሁ፤ አለሁ...፤ እንዴት ናችሁ ዘመዶች?"

“ይመስገነው! ይኸው ያንተ ናፍቆት መልሶ አመጣን”

“እንኳን ደህና መጣችሁ፡፡ ዛሬ ደግሞ ምን እንታዘዝ ” አለ እጆቹን እያሸሽ፡፡

ነጭ ሳር ፓርክን ማየት ፈልገን ነበር፡፡ እንዴት እንደከረመ ጠይቀነው እንምጣ?”

“ታዲያ ምን ችግር አለ፡፡ እንደ ንጉስ አስጎብኝተን እንመልሳችኋለን፡፡ በጀልባ ይሁንላችሁ በመኪና?”

“በጀልባ” አለች ሃኒ ከአፉ ነጥቃ፡፡

“በጀልባ፣ ሶስት ሺህ ብር ብቻ ያስከፍላችኋል፡፡”

እችን ትወዳለች.... እኛ አንተን ደንበኛ ብለን መርጠንህ ብንመጣ፣ ጭራሽ ታሰወድዳለህ?”

“እንደውም ደምበኝነታችሁን ብዬ ነው፡፡አልተወደደም፡፡”

“እንዴ! በጣም ውድ ነው እንጂ፣ በጣም!”
“እንደዛ ነው ዋጋው፡፡ ጀልባው አራት ሰው ነው የሚጭነው፡፡

ሁለት ሰው ካገኛችሁ ሂሳቡን ተካፍላችሁ መሄድ ትችላላችሁ፡፡”

“እኛ ሰው ከየት እናመጣለን? ባይሆን እሺ እሱን ፈልግ፡፡”

“እዛ ጋር የቆሙት ሁለቱ ነጮች፣ እንደናንተው ዋጋው በዛ ብለው ነው፣ ካልደበራችሁ አናግሯቸው፡፡” አለኝ ፈንጠር ብለው ወደ ቆሙ ሁለት ፈረንጆች እየጠቆመኝ፡፡ አውርቶ ሳይጨርስ፣ ቆመው ከነበሩት ፈረንጆች ወንድየው ወደኛ መምጣት ጀመረ፡፡ ሰላምታ
ሰጠንና፤

“ወደ ነጭ ሳር መሄድ ፈልጋችሁ ነው?” አለን በእግሊዝኛ፡፡

አዎ፡፡ ግን ዋጋው በዛብን፡፡”

“እኛም ዋጋው በዝቶብን ነው፡፡ ዋጋውን ተካፍለን አብረን ብንሄድ፣ ይስማማችኋል?”

“ጥሩ ነው፡፡ እንደዛ ይሻላል፡፡” አልኩ ሃኒን እያየሁ፡፡

መስማማቷን ጭንቅላቷን በመነቅነቅ ገለጠችልኝ፡፡

ሦስት ሺህ ብሩን እኩል አዋጥተን ትኬት ቆረጥን፡፡ ወደ ሀይቁ ለመሄድ፣ ከከተማ ለታክሲ አራት መቶ ብር ተጠየቅን፡፡ ፈረንጆቹ ቀድመው መረጃ ሰብስበዋል፡፡ በባጃጅ በሁለት መቶ ብር መሄድ
እንደሚቻል ነግረውን፣ ባጃጅ መጠበቅ ጀመርን፡፡ የከተማው ዋና መንገድ
ላይ ቆመን፣ ባጃጅ እየጠበቅን፣ በመንገድ ላይ ጫት እየቃሙ ሚያልፉ ወጣቶችን ፈረንጆቹ ተመልክተው፣

“ወጣቶቹ ሚበሉት ቅጠል ምንድን ነው?” ብለው ጠየቁ፡፡

“ጫት ይባላል፤” አልኳቸው፡፡

“ያለው ጥቅም ምንድን ነው?”

“ያነቃቃል፡፡ ደስተኛ ያደርጋል፡፡”

“እንዴት ያነቃቃል?” ሰውየው አጥብቆ ጠየቀኝ፡፡

“ማለት?”

“ውስጡ ያለው ንጥረ ቅመም ምንድን ነው? ሴሮቶኒን /የደስታ ንጥረ ቅመም/ አለው?”

“ስለ ሴሮቶኒን ንጥረ ቅመም ብዙም አላውቅም፡፡ ግን ካቲን የተባለ ቅመም አለው ሲባል ሰምቻለሁ፡፡”

በተባለው ዋጋ ወደ ሃይቁ የሚያደርሰን ባጃጅ አግኝተን ጉዟችንን ጀመርን፡፡ መንገዱ በጣም ቁልቁለታማ፣ ጥምዝምዝ የበዛው፣ ግማሽ ፒስታ በሚባል ደረጃ፣ የፈራረሰና ጠባብ መንገድ ነው፡፡ ወደ ሀይቁ ስንቀርብ፣ መንገዱ ጭራሽ ጭቃ የበዛው ረግረጋማ ሆነ፡፡ ከዚህ በፊት ሰምጠው የተያዙ ተሽከርካሪዎች ጎማ ቅርፅ ይታያል፡፡

“ሌላ የተሻለ አማራጭ መንገድ የለም?” አለች፤ አብራው ያለችው ፈረንጅ፡፡

አይመስለንም፤” አልኳት።

በጭቃው መንገድ ውስጥ ትንሽ እንደሄድን፣ ባጃጁ ቆመና እዚህ
ጋር ነው መውረጃው አለን ሹፌሩ፡፡ ሀይቁ በትልልቅ ዛፎች ተከቦ ይታያል፡፡ ወደ ፓርክ እየገባን እንደሆነ ሚያሳይ፣ አንዳችም ምልክት የለም፡፡ ሂሳብ ከፍለን ወረድን፡፡
“ምልክት ሚሆን መግቢያ በር የለውም እንዴ?” አለችኝ ሃኒ፡፡

“ሌላ መግቢያ ይኖረው ይሆናል፡፡”

“እንዴ፣ ቢኖረውስ፣ ቱሪስት ሚገባበት እስከሆነ ድረስ፣ ምልክት መኖር አለበት፡፡ በዛውም
👍1