አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት
;
;
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ


እስክንድር በምልክት አሳየው ። በዚያ ሁሉ ጠጪ መሐል ሁለት እጁን እኪሱ አድርጎ ፡ ሁሉንም በንቀት ዐይን እየተመለከተ ነበር ወደ ሽንት ቤቱ የሔደው ።

“ ቢራዋ ሥራዋን እየሠራች ነው ” አለ እስክንድር የአቤል አረማመድ እያየ ።

“ ግን ምን ይሻለዋል ?” አለ ሳምሶን " በአቤል ሁኔታ በማዘን ' “ አሁን በማዕረግ የሚመረቅ ይመስልሃል ? ” እስክንድር ገርሞት ሣቀ ። የሳምሶን ጥያቄ ግን ከቅን
መንፈስ የመነጨ ነበር ። አቤል የሚወደውም የሚያከብረውም በማዕረግ ተማሪነቱ ነው ። የአቤል የማዕረግ ተማሪነት በዩኒቨርስቲው ውስጥ በብዙ ተማሪዎች ዘንድ ይታወቃል
እንደ እስክንድር ጠጋ ብለው የማያውቁት አሁንም የዓመቱ የፕሬዚዳንት የከፍተኛ የማዕረግ ሽልማት ከአቤል እጅ አይወጣም የሚል ግምት አላቸው ። ሳምሶንም የመኝታ ክፍል ጓደኛው ቢሆንም ቅሉ በትምህርት ያን ያህል መድከሙን አያውቅም ነበር ።

“ እውነቴን ኮ ነው ። ምን ያሥቅሃል ?”

ማዕረጉ ቀርቶ በዚህ ዓመት መመረቁ ራሱ ነው እኔን የሚያጠራጥረኝ” አለው እስክንድር " በኀዘን ስሜት ፊቱ
ተለዋውጦ።

“ ያሳዝናል ! ግን ምን ታረገዋለህ! ” አለና ሳምሶን "ቢራውን ከጠርሙሱ ውስጥ እየጨለጠ ፥ “ በነገራችን ላይ መውደቂያችንን እናዘጋጅ እንጂ ! መቼም ዛሬ ወደ ካምፓስ አንገባም” አለው ።

እስክንድር የሳምሶን ሐሳብ ገባሁ ፤አንድ ሴሚስተር ሙሉ ታፍኖ የቆየ ስሜቴ ተነሣ ነገር ግን ኪሱ አስተ ማማኝ አልነበረም ።

“ እኔጋ በቂ ገንዘብ የለማ ! ” አለው ልመና በተቀላቀለበት ድምፅ ከልብ ተዝናንቶ ።

አቤልም እሺ የሚል አይመስለኝም ። ከአሁን በፊት ውጭ እድሮ አያውቅም ።
“ ምን ትቀልዳለህ ? ጭራሽ ? እምልህ ...”
“ አዎ ፡ ከእኔ ጋር ስንተዋወቅ ይኸው አራት ዓመት አለን አንድ ቀንም ኣድርጎት አያውቅም ።

እንግዲያው ዛሬ ድንግሉን ማስወሰድ አለብን ? ”አለ ሳምሶን ተንኮልም የፍቅር ስሜትም እየተሰማው ።

“ እዩዬ ! ተው እባክህ ! ” አለ እስክንድር ' በተዘበራረቀ ስሜት ።

“ ምናለበት ? አንተ ደሞ ! እንዲያውም ሴት ከቀመሰ የዐይኑ ፍቅር ይለቀው ይሆናል ። ገንዘብ እንደሆን እኔ ይዣለሁ ብዬሃለሁ ።

እስክንድር የሳምሶን ሁኔታ ራሱ እንግዳ ሆነበት ። ሳምሶን አብዛኛውን ጊዜ በኪሱ በርካታ ገንዘብ ይይዛል ። ወላጆቹ ደኅና ገቢ አላቸው ። አባቱ በአንድ ኢንተርናሽናል ድርጅት ውስጥ በጥሩ ደመወዝ ይሠራሉ ። በእናቱ ስም ደግሞ
መስጊድ አካባቢ የሰዓት መሸጫ ሱቅ አላቸው ። ወላጆቹ ለሳምሰን በወር ተቆራጭ ካደረጉለት ሃምሳ ብር ሌላ
ሊጠይቃቸው ብቅ ባለ ቁጥር አንድ ወይም ሁለት ባለ አሥር ኖት ሳያሽጉት አይመለስም ። ታዲያ ሳምሶን ይህን ሁሉ ገንዘብ ሲይዝ " ለመጠጥ ማጥፋት አይወድም። የሱ ገንዘብ የሚያልቀው በምግብ ነው ። መብላት ፡ ስፖርት መሥራት ግንባታ ብቻ ! በዩኒቨርስቲው አቅራቢያ ካሉት ምግብ ቤት ባለቤቶች ውስጥ እሱን የማያዉቅ የለም ። ዛሬ ገንዘቡን ለመጠጥና ለሴት ለማውጣት መዘጋጀቱ ነው እስክንድርን ያስገረመ።

“ እንዴት ነው ? ዛሬ ግንባታው ቀርቶ ለማፍረስ ነው መሰል የታጠቅከው ” አለው እስክንድር እየሣቀ ።

“አንዳንዴ ያስፈልጋል እባክህ ! ”
አሳላፊዋ አራት ጠርሙስ ቢራ ይዛ መጣች አንዱ ለራስዋ መሆኑ ነው ።

ቢራ እዚሁ ጓዳ መጥመቅ ጀመራችሁ እንዴ ? "
አላት እስክንድር ፡ ከታዘዘች መዘግየቷን ለመጠቆም ።

“ ቆየሁ እንዴ?አንድ ሰካራም ይዞ ሲነተርከኝ ነው” አለች ፥ ቢራውን እየከፈተች ።

“ አንቺው መጠጥ አቅርበሽለት አንቺው፡ሰካራም ትይዋለሽ ? በይ ነይ በይ ” አለና ሳምሶን ፡ ዳሌዋ ላይ ቸብ አደረጋት ቸብታው ጠንከር ያለ ስለ ነበር ዳሌዋን ለበለባት።

“ እንደዬ ! ታዲያ ዱላው ምንድነው ? ” አለች ተቆጥታ ዳሌዋን በእጅዋ እያሻሸች

ዝም በይና ቁጭ በይ ! ከፈለግኩ ጥርስሽን ነው የማረግፈው አላት ሳምሶን እንደ ልማዱ ።

እስክንድር ነገሩ ማየሉን ሲያይ ተደናገጠ

“ ኧረ እባክህ ! የማነህ ሒድና የሚስትህን ጥርስ አውልቅ " የእኔን የብርቅነሽን አይደለም። ስለ ቢራው እንደሆን ኬረዳሽ ! ” ብላው የከፈተችውን ቢራ ጥላ ተነሣች ብርቅነሽ አምርራ ልትሔድ ስትል'እስክንድር እጅዋን
ይዞ አባብሎ አስቀመጣት ።

“ አንቺ ደሞ እረፊ እንግዲህ ። እሱ ለጠዋታ ያህል ነው የነካሽ
እየተመናቀረች ከሳምሶን ርቃ እስክንድር ጎን ተቀምጠች ። ሳምሶንም ጥርሱን እያንቀጫቀጨባት ነበር ። በማይ
ረባ ነገር ተለካክፈው የጎሪጥ መተያየታቸው እስክንድርን
አስገረመው ።

“ ሁለታችሁም ዕረፉ ፡ ይሄ ቡና ቤት ነው በሰላም ጠጥተን መጫወት ነው የምንፈልገው ”አላቸው : ከግንባሩ ኮስተር ብሎ ፥ ግን በሆዱ እየሣቀ ።

የእስክንድር ሐሳብ እነሱጋ ረግቶ አልቆየም ። በድንገት አንድ ሐሳብ አእምሮውን ወጋው ።አቤል ወደ ሽንት
ቤት ከሔደ ቆይቷል ፤ግን አልተመለሰም ። እስክንድር ልቡ መጥፎ ነገር ጠረጠረና ድንገት ከተቀመጠበት ተነሣ ።

ምነው ?” አለው ሳምሶንም ፡ በሁኔታው ተደናግጦ ።

“ ምንም አይደለም ፥ መጣሁ ” ብሎ እስክንድር ወደ ሽንት ቤቱ ሄደ ። አቅለሽልሾት ይሆናል በሚል ግምት ሳምሶን ነገሩን ቸል አለው ።

እስክንድር ከመጸዳጃ ቤቱ አጠገብ ሲደርስ አቤል እጁን በኪሱ እንዳደረገ ግድግዳ ተደግፎ ቆሞ ነፋስ ሲቀበል አገኘው። ዐይኑ በርበሬ መስሏል ።አላፊ አግዳሚውን በንቀት ዐይን ነው የሚመለከተው።

ቴክሱ ምነው ? ”አለው እስክንድር ፥ ደህና መሆኑን ካረጋገጠ በኋላ"

“ ወረፋ ሆኖብኝ ነው እባክህ ! ”

“ የሽንት ወረፋ ? በል እንግዲህ ጠብቅ ። ምን ታረገዋለህ ? ” ብሎት እስንድርን ወደ መጣበት ተመለሰ ።አቤል አንድ አደጋ ደርሶቀታል የሚል ሥጋት ስለ ነበር፡ በሰላም በማግኘቱ ልቡ ተረጋጋ ። ምንጊዜም አያምነውም አንድ ቀን በራሱ ላይ የሞት ቅጣት ይፈርዳል የሚል ፍራቻ አለው።

ወደ መቀመጫው ሲምለስ ብርቅነሽና ሳምሶን ተስማተው ጎን ለጎን ተቀምጠው ሲያወሩ አገኛቸው ።

ታረቃችሁ እንዴ ? ”

“ ዱሮስ መች ተጣላን ? አንተ ደሞ ” አለችና ብርቅነሽ ጠየቀችው፡ ፡

ቀድሞውንም ጸበኞች የሚገባበዙት መሐላቸው ገላጋይ ሲኖር ነው ። ብቻቸውን ሲሆኑ አንደኛው ዐቅሙን
ዐውቆ ወይም ጥቅሙን ከጉዳቱ አመዛዝኖ ጸባዩን ያሳምራል ? አለ እስክንድር በልቡ ።

“ ያንን ነገር “ኮ ለብርቅነሽ ነገርኳት” አለው ሳምሶን' ዓይኑን እስክንድር ላይ ተክሎ "

የቱን ነግር ? ”

የአቤልን ነዋ ! በቃ እሷ ይዛው ትደር ።

ሳምሶን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መሆናቸውን አጫውቷት ከዚያው ቡና ቤት መኝታ እንድትይዝ ገንዘብም
ሰጥቷታል ።

“ አንተ ዛሬ የልጁን ድንግል ለማስወሰድ ታጥቀህ ተነሥተሃል ማለት ነው? ” አለ እስክንድር ጉጉቱ አስገርሞት እየሣቀ ።

“መሆን አለበት ብዬሃለሁ ። አድቬንቸር ነው
“ አንቺስ ? በነገሩ ተስማማሽ ? ” አላት እስክንድር ፊቱን ወደ ብርቅነሽ መልሶ።

ውይ በደስታ ነዋ ! እንዲያም ድንግል ወንድ ደርሶኝ አያውቅም ። ዕድሌ ሆኖ የተፈተነ ብቻ ነው የሚደርሰኝ።

ስትናገር ሣቅ ሃቅ ስለምትል የቀልዷን ይመስላል እንጂ ብርቅነሽ የምትናገረው የልቧን ነበር ። ወሲብ ጀማሪ ደርሷት
አያውቅም ። የልጅነት ባሏም ቢሆን ሁለተኛ ሚስቱ ነበረች ።ቡና ቤቱ ውስጥ የሥራ ጓደኞቾ፥ “ ዛሬ የአንዱን ጀማሪ ድንግል ወሰድን ” እያሉ ሲያወሩ ትቀናለች በዚህ ወሬ የተካነችው የቡና ቤቱ ባለቤት ነች የጥንት ዝናዋን ስታወራ ይሄ አርዕስት
👍1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#ድርሰት_በትክክል_ገና


በድንገት የተከሰተው አደጋ ክፉኛ ስላስደነገጠው ሻምበል ብሩክ ቀን እረፍት፤ ሌት እንቅልፍ፤ የሚባል ነገር አጥቶ እንደዚሁ በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ከረመ፡፡ ለዚሁ ጉዳይ ሲልም ከመስሪያ ቤቱ የአስራ አምስት ቀን ፈቃድ ወሰደ፡፡ በዚህ ፈቃድ በወሰደበት ጊዜው
ውስጥ ደግሞ ብዙ መሯሯጥ ይጠበቅበታል፡፡መጀመሪያ ሆስፒታል የተኛች እናቷን ማረጋጋት አለበት :: ከዚያም ለወንድሟ በቂና አሳማኝ ምክንያት መስጠት ይጠበቅበታል ይህንን ሁሉ ሲያደርግ በሀሳብ የምትረዳውና ! አብራው የምትሯሯጠው! አዜብ ብቻ ነች፡፡ አዜብ ስለደረሰው አደጋ የትህትና አክስት እንዲያውቁት ፈልጋ ነበር፡፡

"አይሆንም ትርፉ ማስደንገጥ ብቻ ነው የሚሆነው፡፡ እነሱ ካወቁ ወሬው መዛመቱና፤ እናትዋ ጆሮ መድረሱ የማይቀር ስለሚሆን፤ በሚስጥር ቢያዝ ይሻላል” በማለት የተከራከረው ሻምበል
ነው፡፡ሻምበል ለእናቷ የሚሰጠው ምክንያት አሳማኝ እንዲሆን ሀሳብ
ሲያወጣና፧ ሲያወርድ፤ አዜብም እንደዚሁ ያሳምናታል ብላ ያሰበችውን ምክንያት ስትደረድር፤ ቆዩና ሁለቱም ይሆናል ባሉት ሃሳብ ላይ በጋራ ከተስማሙ በኋላ፤ ይህንኑ ሊያስረዳ ወደ የካቲት አስራ
ሁለት ሆስፒታል አቀና፡፡ ትህትና ከእናትዋ ጋር በአይነ ስጋ ከተገናኙ ሶስት ቀን ሆኗቸዋል፡፡ አንዱአለምም ድምጹ ከጠፋ ሳምንት አልፎታል፡፡በነገሩ እናት ግራ ተጋብታለች፡፡
"ልጆቼን ምን ነካብኝ?" በሚል ጭንቀት ተውጣለች፡፡ትናንትና ሆስፒታል መጥታ ያስተዳደረቻት ሰራተኛዋ ነበረች፡፡ ትህትና ከቤት ያለማደሯን ብቻ ነው የነገረቻት፡፡ በሽታዋን ማዳመጡን ትታ ልጆችዋን
እያብሰለሰለች፤ በሀሳብ እንደተዋጠች ነበር ሻምበል ብሩክ የደረሰው፡፡ብሩክን ስታየው በደስታ ልቧ ቀጥ አለች ::
"ትህትናዬስ ብሩኬ?" ከኪሱ አውጥቶ ይሰጣት ይመስል በጉጉት አይን አይኑን እያየች ጠየቀቸው፡፡ ሻምበል ብሩክ እንደማፈር ብሎ ሳቅ አለና፤ ተቅለሰለሰ፡፡ ለዘዴው...
“ምነው ብሩኬ በደህና ነው?" ከሁኔታው የከፋ ችግር እንደሌለ ተረድታለች፡፡
“ምንም ችግር የለም እማማ፡፡ ምን የኛ የወጣቶች ነገር...
የሚያሰጋ ነገር ያለመኖሩን ከሁኔታው ብትገነዘብም ምክንያቱን ለማወቅ
ቸኮለች፡፡
"ምንድነው እሱ ታዲያ?
ትህትና ምንም እንኳ እጮኛዬ ብትሆንም፤ ከትዳር በፊት እርግዝና ማለት፤ ትንሽ ያልተለመደ ስለሆነ... አንጠልጥሎ ተወው። ነገሩ ገባት
ከዚያ በላይ ልታስጨንቀው አልፈለገችም እሱ ግን ቀጠለ "ከጋብቻ በፊት ልጅ መውለድ የቤተሰብን ክብር መንካት ነው የሚል እምነት አላት፡፡ ተመካከርንና ማህጸኗ እንዲጠረግላት አደረግን፡፡ አሁን
ራስ ደስታ ሆስፒታል ትንሸ እረፍት ትውለድ ስላሉኝ አስተኝቻታለሁ።"አለና አጭር ድራማውን አጠናቀቀ፡፡ እናት የልጇን አቋም በእርግጥ ታውቀዋለች፡፡
አባቷ ያሳደጋትም በዚያ እምነት ጸንታ
እንድትኖር ነውና፤ በወሰደችው እርምጃ የተቃወሞ ድምጽ አላሰማችም፡፡
ነገሩን ውስጥ ውስጡን ስታብላላ ቆየችና......
“ሻምበል አደራህን! ትሁቴ ህጻን ልጅ ናት።እንደታላቅ ወንድም ተንከባከባት፡፡ እሷ ምኑንም የማታውቅ አንድ ፍሬ
ልጅ ናት፡፡ ለመጠንቀቁም ቢሆን አንተ ትሻላለህ፡፡ እሷ ምኑን ታውቀዋለች ብለህ
ነው?" የአሁኑ ስህተት እንዳይደገምና፤ በሌላ ጊዜ ተጨማሪ ጉዳት
እንዳይደርስባት፤ ሻምበል ሃላፊነቱን እንዲወጣ በማሳሰብ፤ አደራዋን
አጠበቀች፡፡ እሱም ትህትና ከሆስፒታል እንደወጣች ይዟት እንደሚመጣ
ቃል ገባላት፡፡ በመጠኑም ቢሆን ልቧ ትንሽ እረፍት አገኘ፡፡
“የአንዱአለሜ ወሬስ ? ምነው ጭልጥ ብሎ ጠፋ?" አከታትላ ጠየቀችው፡፡
“እኔ ራሴ ካገኘሁት ሳምንት ሆኖኛል እማማ፡፡ ለፈተናው ዝግጅት ሸፍቷል፡፡ ዘንድሮ አንደኛ ካልወጣሁ ሰው አይደለሁም ሲል የፎከረውን ለመፈፀም ቆርጦ መነሳቱን ትህትና ነግራኛለች። ምንም አያስቡ፤ ፈተናውን እንደጨረሰ እንዲመጣ እነግረዋለሁ።” ምክንያቱ
ብዙ ባይዋጥላትም የሻምበልን የማፅናኛ ቃል ከማዳመጥ በስተቀር አማራጭ አልነበራትም፡፡ዝም አለች፡፡ ከዚያም ሻምበል በግማሽ ልቡ ሆኖ፤ የሆነ ያልሆነውን፤ ሲያወራት ከቆየ በኋላ፤ ተሰናብቷት ወደ ትህትና ሩጫውን ቀጠለ....
ትህትና የቀዶ ህክምና ከተደረገላት በኋላ በአንደኛ ማእረግ እንድትተኛ ያደረገው ሻምበል ብሩክ ነው፡፡ ሻምበል አስፈላጊውን ክፍያ በመፈጸም ንጽህናው በተጠበቀና፤ ተጨማሪ በሽተኛ በሌለበት
አንደኛ ማእረግ ውስጥ እንድትተኛ የፈለገበት ዋናው ምክንያት፤
በሚተኙ በሽተኞች ስቃይ ተጨማሪ የአእምሮ መረበሽ ሊደርስባት ይችላል በሚል ፍራቻ ነው፡፡
ለቀዶ ጥገናው የተወጋችው ማደንዘዣ ስራውን በማጠናቀቁ ለአስቸኳይ ህክምናው በተሰጣት በሀያ አራት ሰአት ውስጥ ከሰመመናዊ እንቅልፉ ነቃችና አይኗን ገለጥ አደረገችው፡፡ ጣሪያውን ተመለከተች፡፡ ዙሪያዋን ቃኘች
የት እንዳለች፤ ምን እንደሆነች፤ በፍጹም
አታውቀውም፡፡ የተወጋችው የእንቅልፍ
መርፌ ፤ በጥይት የቆሰለው ሰውነቷና
እንደ ጉድ የፈሰሰው ደሟ መላ
አካሏን ድቅቅ አድርጐታል፡፡ከግራ ጆሮዋ ጀምሮ ፊቷ በአጠቃላይ በፋሻ ተሸፍኗል፡፡በክንዷ ላይ የተሰካውን ግሉኮስ ተመለከተችው፡፡ ጠብ ጠብ... እያለ
ይወርዳል። እንደገና አይኗን ጨፈነች፡፡ትንሽ ቆየችና መልሳ ገለጠችው::
እንደገና በሀሳብ ባህር ውስጥ ገባች፡፡ ምን ነበር የሆነው ? የት ነው ያለችው? እዚህ ለምን መጣች? እሷ ማን ነች? ቆይ .. ቆ ይ.. ምን ነበር የሆነው ? የሆነ
ነገር ብዥ ፧ ብዥ አለባት እንዴ ?..
መርካቶ ውስጥ እንደሻውን... ከዚያ በኋላ እራሷን... እንዴ?
ምንድነው ነገሩ? እሷ ሞታለች አይደለም እንዴ? በሰማይ ቤት ነው ወይንስ በምድር ላይ ያለችው? በዚያች በተሰናበተቻት ምድር ላይ? በፍጹም ሊሆን አይችልም! እንቆቅልሹም ሊገባት አልቻለም፡፡ ከዚያም ፊት ለፊትዋ የተቀመጡትን ሰዎች ትኩር ብላ ተመለከተቻቸው፡፡
ብዥ ፤ ብ ዥ ፤አሉባት አላወቀቻቸውም :: እነሱ በሀዘን ተውጠው አይን አይኗን ይመለከቷታል፡፡ እንደገና ትኩር ብላ ከመታሸግ በተረፈው በቀኝ አይኗ አየቻቸው፡፡ አሁንም አላወቀቻቸውም፡፡ እንቅስቃሴ የላትም፡፡እዚያ ከፊት ለፊቷ ሆነው በሀዘን ኩርምት ጭብጥ ብለው የተቀመጡትን ሰዎች በድጋሜ በጥንቃቄ ተመለከተቻቸው፡፡ የሆነ ምስል መጣላት፡፡
የምታውቀው ምስል በርቀት የምታውቀው ምስል.. አዎን
ታውቃቸዋለች እንጂ !! እንዴ..? በሚገባ ታውቃቸዋለች :: ቀስ ብላ በለሆሳስ ተጣራች "ብ..ሩ. ኬ..... አ . ዜ. ቢ . ና
እህህህ....." በዚህ ጊዜ አዜብ ቀስ ብላ ተነሳችና ሄዳ አጠገቧ ቆመች፡፡ ብሩክም አዜብን ተከትሎ ወደ አልጋው ተጠጋ፡፡ሻምበል እንደዚያ ሆና ሊያያት አልቻለም :: እንባው አመለጠውና ቀስ ብሎ ጉንጮቹን
እያቋረጠ ፈሰሰ፡፡
“እ ማ ዬ...ደ ህ...ና. ነች? ..አ.ን.ዱ.ዬስ..?"
"ሁለቱም በጣም ደህና ናቸው፡፡ ስለ እነሱ ምንም አታስቢ፡፡ እኛ አለን፡፡ አሁን ዋናው ማሰብ ያለብሽ ስለራስሽ ጤንነት ብቻ ነው እሺ?” አዜብ ነበረች፡፡
“እ..ሺ በደከመ ድምጽ፡፡
“ትሁት አዜብ የምትልሽን ስሚያት፡፡ስለ እማማ ምንም የሚያስጨንቅሽ ነገር የለም፡፡እሳቸው አንቺ ስለጠፋሽባቸው ነው ትንሽ ያሰቡት እንጂ በጣም ደህና ናቸው፡፡ ቶሎ ድነሽ ሄደሽ እንዲያዩሽ
በሃሳብና በጭንቀት ራስሽን መጉዳት የለብሽም፡፡ እሺ? አንዱ አለምም ድኗል ማለት ይቻላል፡፡ሰሞኑን መጥቶ ይጠይቅሻል እሺ?” ጉንጮቿን
እየዳበሰ፡፡
እሺ” አለች በድጋሜ፡፡ በዚያው ድክምክም ባለ ድምጿ። አሉኝ የምትላቸውና የምትተማመንባቸው ሁለቱ ጓደኞቿ፤ ደራሾቿ ፤ በዚህ በክፉ ቀን እንኳ ከጐኗ
👍1
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

....በለሃጩ አጨማለቃት፡፡ራቁት ገላውን እራቁት ገላዋ ላይ እንደቁንቡርስ አንደባለለው፤ መላ ፊቷን በሚርገበገብ ከንፈሩና በምላሱ አልኮሰኮሰው፤ እጆቿንና እግሮቿን ከአልጋው ጠርዞች ጋር እንደተጠፈሩ አፍዋ በቡትቶ ታጭቆ እንደተጎስጎስ በተንጋለለችበት ጥያፌዋን፣ ምሬቷን ሰውነቷን እያወራጨች አሳየችው፡፡

ግድ አልነበረውም...

በከርዳዳ ጺም የተሸፈነ ፊቱን ከፊቷ ላይ አንስቶ እስረኛው ምርኮኛው በሆነው ከስሩ በተንጋለለላት ገላዋ ላይ አንቀዋለሰው፣ አይን አዋጅ ሆነበት:: ..በደመነፍስ ያዳብሳት ጀመር፡፡ በል..በል የሚለውን ግፊት፤

ሂድ..ሂድ የሚለውን ስካር ሩጥ..ሩጥ የሚለውን እብደት ጥድፊያ አምቆ
መቆየቱ ጣፋጭ የስቃይ ስሜት ፈጠረለት፡፡ ከረሜላውን ከአፉ ከትቶ
ኮረሻሽሞ ጎረዳድሞ ከመዋጡ በፊት፣ የጎረሰውን ከረሜላ እየመላለሰ በመዳፉ
ላያ እየተፋ በስስት በስቃይ ስሜት እያየ ቀስቃዩ በሰቀቀኑ እንደሚደሰት ህፃን
የጓጓለትን የተንቀዋለለለትን ገላዋን ከስሩ አጋድሞ ተሰቃየ ለራቁት ገላዋ
ሳሳለት፡፡

ፂማም ፊቱን ወደ ደረቷ አስጠግቶ በጡቶቿ መሃል ወደቀ፡፡ሳያጎረድማት መጠጣት፤ ሳይኮረሽማት ላሳት፤ መልሶ ከአፉ አውጥቶ ተመለከታት::አውሬ ሆነች፡፡ ጥላቻዋ እየጨመረ. ምሬታ እየኮረረ. እልኋ እየጋመ በመጣ ቁጥር የልቡ ምት እየጨመረና ትንፋሹ እየተፋጀ መጣ ሰውነቱ በላብ አሙለጨለጨ ፊቱን ከጡቶቿ መሃል አውጥቶ ቁልቁል
አዘገመ...

ወገቧን ሰብቃ ሰደበችው ፧ ሽንጧን እያላጋች ረገመችው፧ ጭኖቿን
እያማታች ተፋችው

ደስታው ወሰን አጣ…

ጎንበስ ብሎ የሚወራጭ . አካሏን በለሀጩ በራሱ ከንፈሮቹ ተረከበው:: እንደ እንፋሎት የሚጋረፍ፡ ትንፋሹ ለስላሳ ቆዳዋን ፈጃት ፡ ለበለባት:: ህሊናቸውን መሳት የጀመሩ ደዳራ ጣቶቹ የሴት አካልዋን በጭካኔ አፍረጠረጡት፡፡

በሩ ተበረገደ፡፡

በጉልበቶቿ መሃል እንደተንበረከከ በድንጋጤ ፊቱን ወደጀርባው መነጨቀው የተመለከተውን አልወደደውም፡፡ በር ላይ በድን ይመስል የተገተረው ሰው የሚያየውን ትርዒት ለመረዳት ጊዜ ፈጀበት:: የሚመለከተው እየተገለጸለት ሲሄድ በእልህ ይንቀጠቀጥ ጀመር፡፡

“ጠርጥሬሃለሁ! አንት ውሻ ጠርጥሬሃለሁ!” አለ ማርቆስ በሩን
ለቅቆ ወደ ክፍሉ ከመግባቱ በፊት ከኮቱ ስር ሽጉጡን ላጥ አድርጎ አቀባብሎ
እላይዋ ላይ በተከመረባት ሰው ላይ እየደገነ። “እንዳትነቃነቅ... ከዚያ አልጋ
ላይ ለመውረድ ሞክርና እንደ ውሻ እገድልሃለሁ!” አለ ማርቆስ ሽጉጠን
እንደደገነ ወደ ስልኩ እያመራ፡፡ “ትንሽ ተነቃነቅና ምክንያት ስጠኝ ግንድህን አጋድምሃለሁ!” በቀኝ የያዘውን ሬድዮ ወደ አፉ ኣስጠግቶ ተናገረ።
“ሃሎ… ቆንጆዎቹ ቡድን ለ... አስቸኳይ ነው... ዜሮ አራት” ለጥቂት ደቂቃዎች ዝም አለ፡፡ “ቁጥር አንድ ጋር አገናኝኝ፡፡” የሬዲዮ መገናኛውን በግራው እንደጨበጠ በቀኙ የያዘውን ሽጉጥ እላይዋ ላይ በተከመረው ሰው
ላይ ደግኖ ተጠባበቀ፡፡ “ሃሎ …ዜሮ አራት በፍጥነት እፈልግሃለሁ… እዚሁ
ድረስ… ሌላ ሰው አይደለም አንተ ራስህ ተገኝታህ መመልከት አለብህ።”
አነጋግሮ ሊያበቃ ስልኩን ዘግቶ ሽጉጡን ወደፊት ኣስቀድሞ ወደ አልጋው
ተጠጋ፡፡

“ጉድህን እናየዋለን” አለ ማርቆስ ጺማሙን ሰውዬ በጥላቻ
እየተመለከተ፡፡

“ይቅርታ አድርግልኝ ማርቆስ፡፡ ሌላው ይቅር ልብሴን ልልበስ፡፡” አለ ሰውየው በጭኖቿ መሃል እራቁቱን እንደተንበረከከ በልምምጥ ፊት ማርቆስን እየተመለከተው፡፡

“ከማነው ሃጢያታችንን የምንሸሽገው? ለዓመታት አንዳችን የአንዳችንን ሃጢያት እንዳናይ የገዛ ሃጢያታችን እንዳይታይ ፊታችንን ስንመላለስ ቆይተናል፡፡ ከአሁን ወዲያ ግን ገበናችን መገለጥ አለበት፡፡
ከኃጢያታችን እራቁታችንን መተያየት አለብን። : እውነት ተሽፋፍና ተጀቧቡና አትኖርም፡፡ እራቁቷን ነው የምታምር፡፡” በዕልህ ተንቀጠቀጠ፡፡
“እራቁቷን!”

“ማርቆስ ልብህ ይራራ… ሁላችን እንሳሳታለን… ማረኝ፡”

"ማነው አውሬ… ለተናካሽ እውሬ የሚራራ? ቀሚሷን ገልበው እርቃኗን አንጋለው ለሚያረክሷት፣ ጭኖቿን በርግደው ሴትነቷን አጋልጠው ለባእድ
ለሚሽጧት አፍሪካ ርህራሄ አይኖራትም፡፡ ምህረት ምንድነው? በየዋህነት ለቸረቸራችሁ፣ በልበ ገርነቷ ለሽረሞጣችሁ፣ በድንግልናዋ ላቃጠራችሁ ምህረት ምንድነው? አፍሪካ መቼ ነው ቀሚሷን ዝቅ የምታደርግ፣ ጭኖቿን የምትሰበስብ፣ እፍረቷን የምትሸፍን? እናንተ ስትጠረጉ ብቻ ነው! ምህረት አያሻም! ራቁታችንን መተያየት አለብን!”

የክፍሉ በር ከጀርባው ሲበረገድ የተንበረከከው ጺማም ሰው ዓይኖቹን ጨፈነ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የቢሮውን በር በርግዶ ሲገባ ብርጋድየር ጀኔራሉ ከጠረጴዛው ጀርባ እንደተቀመጠ አፍጥጦ ተመለከተው፡፡
“ያዝነው!” አለ ማርቆስ ትንፍስ ትንፍስ እያል፡፡
“ናትናኤልን?” አለ ጀኔራሉ የሰማውን ለማረጋገጥ፡፡
“አዎ፡፡” አለ ማርቆስ ጭንቅላቱን ነቅንቆ ፀጉሩን እየደባበሰ፡፡
“ብታምነኝም ባታምነኝም እራሴን እስከምጠላ ተስፋ ቆርጬ ነበር፡፡”

“እንዴት ያዝስከው? ማለቴ የት?” አለ ጀኔራሉ ማርቆስን ተቀመጥ ሳይለው በቆመበት እንዳፈጠጠበት፡፡

“ባቡር ላይ፡፡” አለ ማርቆስ ወደፊት ተራምዶ ወንበር ላይ እየተቀመጠ፡፡ “ዛሬ ማታ ወደ ድሬዳዋ ለመሄድ ባቡር ላይ ሲሳፈር እዛ የመደብኳቸው ሁለት ሠራተኞቼ አይተውት አብረውት ተሳፍረዋል፡፡”

“ወደ ድሬዳዋ ተሳፍራል ነው የምትለኝ? ያዝኩት ያልከኝ መስሎኝ ነበር'ኮ፡፡” አለ ጀኔሪሉ ፊቱን አኮሳትሮ “መከታተሉ ምንድነው ትርጉሙ ለምን ቀጥታ አላስወገድከውም? "

“አታስብ... ከአዲስ አበባ እስከ ድሬዳዋ ያሉትን ጣቢያዎች በሙሉ በሰዎቻችን ሸኛቸዋለሁ፡፡”

“ባበሩ ሳያነሳ ለምን አልያዝከውም
“ጀኔራል ሰውየው ትኬት ሲቆርጥ ሰዎቻችን አላዩትም፡፡ ምናልባት
በሌላ ሰው እስቆርጦም ሊሆን ይችላል:: ድንገት ባቡር ላይ ሲሳፈር ያዩ ሠራተኞቼ ምርጫ ስላልነበራቸt ስልክ ደውለው ሲያስታወቀኝ ባበር ጣቢያ ውስጥ አስወጋጅ ሃያል ስላልነበረ ተከትለውት እንዲሳፈሩ አዘዝኳቸው።

ታዲያ ምኑን ነው ያዝኩት የምትለኝ?”

“ከዚህ ወድያ ሊያመልጥ አይችልም:: በየትኛውም ጣበያ ቢወርድ
ከማንም ጋር ከመገናኘቱ በፊት እንዲያስወግዱት ትዕዛዝ አስተላልፌአለሁ::”አለ ማርቆስ በፍጹም እርጋታ:: “በየጣብያው የሚጠባበቁት ሰዎች አሉ።

“አንተ ራስህ ለምን ድሬዳዋ በረህ አትጠብቀውም? የምልህ ይህን
ሰው አደገኛ ነው ጀኔራሉ ተረበሸ… “አንተ ራስህ ቀድመህ ብትጠበቀው
እመርጣለሁ:::”
“አንድ ሄሊኮፕተር እዛጋጅቼ እየተጠባበቅሁ ነው… ቀጥታ ወደ
ድሬዳዋ እንዳልበር ምናልባት በመሃል ሊወርድ ስለሚችል ባቡሩ እያንዳንዱን
ጣቢያ ሲያልፍ፡-የጣቢያው ያሉ ሰዎች የሬድዮ መልዕክት እያስተላለፉልኝ
እየጠበቅሁ ነው::”

“የት ነው ያለው ኣሁን?” አላ ጀኔራሉ በጉጉት፡፡
“ባቡሩ ናዝሬትን ማለፉን :: እንዳረጋገጥኩ ነው ወዳንተ የመጣሁት:: አላ ማርቆስ፡፡

ማርቆስ!” አለ ጀኔራሉ ፊቱ በጭንቀት ተወሮ፡፡ “ይህ አካሄድህ አላማረኝም እንበልና ይህ ሰው በሁለት ጣቢያዎች መሃል ከባቡሩ ቢዘል ምን ልታደርግ ነው? ከቦታው ላይ ምን ያህል ዘግይተህ እንደምትደርስ አታውቅም?”

“አብረውት የተሳፈሩት ሰዎች የነፍስ ወከፍ መሳሪያ የታወቁ ናቸው፡፡”

“የነፍስ ወከፍ መሣሪያ ይታጠቁ እንጂ ለዚህ ሥራ የሰለጠነና የተዘጋጁ አይመስሉኝም። ተራ የክትትል አባላት ናቸው… አይደለም?” አለ ጀኔራሉ ጠረጴዛውን ቡጢ ደልቆ፡፡

“እርግጥ የክትትል ሠራተኞች ናቸው ግን”

ማርቆስ! ማርቆስ! ምን እየሰራህ ነው?
👍3
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው


“ተቀመጪ እባክሽን” አላት ወፍራሙ የግል መርማሪ ዴሪክ ዊሊያምስ
በአንድ እጁ የእንኳን ደህና መጣሽን አቀባበል፣ በሌላኛውም እጁ ደግሞ
እንድትቀመጥ እየጋበዛት፡፡ ቆዳ ወንበሩ ላይ ያሉትን ወረቀቶችም ጠርጎ አነሳላት።

“የዛሬው ውሎሽ እንዴት ነበር ዶክተር ሮበርትስ?” ብሎ ደስ በሚል ስሜት ጠየቃት። ቅድም በስልክ ካወራት በኋላ ጥሩ ስሜት ውስጥ ነው የሚገኘው።

“በእርግጥ ውሎዬ አድካሚ ነበር” ብላ ኒኪ እውነቱን ነግራው ጣቶቿን ሞዠቀች። “በእውነቱ ሁለቱን ታካሚዎቼን እንደማላድናቸው ዛሬ ላይ ለማወቅ ችያለሁ።” ብላ መለስችለት፡፡ ለምን እንደሆነ ባይገባትም ከዴሪክ ዊሊያምስ የሆነ ነገሩ የደህንነት ስሜት እንዲሰማት ያደርጋታል፡፡ ማለትም ሌሎች እሷን ለማማለል የሚፈልጉ ሰዎች ከሚያደርጉት እንክብካቤ በተለየ መልኩ ቅልል ይላታል፡፡

“ሁለት ብቻ? ዕድለኛ ሰው ነሽ ባክሽ፡፡” ብሎ ወደ ጉዳያቸው ከመግባታቸው በፊት ዴስኩን ነፃ አደረገ፡፡ “ባይገርምሽ ሁሉም ደምበኞቼ ከብዙ ጊዜ አስቀድመው ነው ነገሮች የተዘበራረቀባቸው። አንቺን ሳይጨምር
ማለቴ ነው እንግዲህ።” ብሎ ከቀለደ በኋላ ፈገግ ሲል ኒኪም ፈገግ አለች፡፡

“እሺ ያገኘኸው አዲስ ነገር ምንድነው?” ኒኪ በጉጉት ተሞልታ “ስለ ባሌ ውሽማ ቢሆን ደግሞ ደስ ይለኛል” አለችው።

“ስለ እሷ አይደለም፡፡ ይቅርታ” ብሎ ሲመልስላት በጉጉት ተሞልቶ
የነበረው የኒኪ ፊት ዳመነ፡፡

“አሁን ገና አይደለም እንዴ ምርመራውን የጀመርነው? እመኚኝ የጣውንትሽን ጉዳይ በቅርቡ እንቋጨዋለን። ዛሬ ላንቺ የምነግርሽ ነገር” ብሎ በኩራት ተሞልቶ ከተመለከታት በኋላ “በእውነት እንደ ጅማሬ በጣም ቆንጆ የሆነ ነገር ነው ብዬ አስባለሁ።” አላት፡፡

“እሺ እስቲ አስገርመኝ” አለችው ኒኪ የሚነግራትን ነገር ለማወቅ ጓጉታ፡፡

ዴሪክ ዊሊያምስ ጉሮሮውን አጥርቶ “አንቺ የሰጠሺኝን ነገሮችን በደንብ
አድርጌ ካነበብኩኝ በኋላ ጉዳዩን ከትሬይ ሬይሞንድ ለመጀመር ውሳኔ ላይ
ደረስኩኝ”

በዚሁ መሰረት ወደ ዌስትሞንት ሄዶ ምርመራውን ለመጀመር ሲል መርማሪ ፖሊስ ጆንሰንን እንዳገኘው፣ ጆንስን በዚያ ዘረኛ አመለካከቱን በሚያሳይ ሁኔታ የሬይሞንድን ቤተሰቦችም ሆነ በዙሪያቸው የሚገኙ የአደንዛዥ
ዕፅ አዘዋዋሪዎችን በጣም ተጭኖ
መረጃ እንዲነግሩት የጠየቃቸው መሆኑን እና ይሁን እንጂ ምንም ዓይነት መረጃ ሳያገኝ እንደሄደ፣ ይሄ ደግሞ ለእሱ ጥሩ ዕድልን እንዳመቻቸለት ካስረዳት በኋላ
ሲቪል መስሎ በመቅረብ መረጃዎችን እንዲሰጡት ሲጠይቃቸው ዕፅ
አዘዋዋሪዎቹ ልባቸውን ከፍተው መረጃዎቹን ወደሱ እንዳፈሰሱለት
ተረከላት፡፡ ኒኪ የዊሊያምስን ትረካ በጥሞና እያዳመጠችው ነበር፡፡ ዊሊያምስ ትረካውን አቋረጠና

“ትሬይ አደንዛዥ ዕፅ መጠቀሙን ያቆመው ባለቤትሽን አግኝቶ ከታከመ
በኋላ ነበር። ማለቴ ሁለት ዓመት አልፎታል አይደል?” ሲል ጠየቃት፡፡”

“አዎ ልክ ነህ። በዶውግ እገዛ የተነሳ ነው ዕፁን መጠቀሙን ያቆመው::”
ብላ መለሰችለት፡፡

“ልክ ብለሻል” ብሎ ዊሊያምስ በመቀጠልም “ግን ነገሮች እንደዚህ በቀላሉ የሚተው አይደሉም። መጠቀም ከማቆሙ በፊት ትሬይ በተለይ የ ሄሮይን
አደንዛዥ ዕፅን ያዘዋውር ነበር፡፡ በመጨረሻ ላይ ግን አዲስ የዲስሞርፊን
አይነት አደንዛዥ ዕፅን ማዘዋወር ጀመረ። ዕፁ በተጠቃሚዎቹ ላይ አደገኛ
አካላዊ እና አዕምሮአዊ ችግርን የሚያደርስ ነው። ተጠቃሚዎቹ ክሮክዲልዐብለው ነው የሚጠሩት” አላት፡፡

“ይህንን አደንዛዥ ዕፅ አውቀዋለሁ፡፡ የዶውግ ጓደኛ የሆነው ሀዶን ዶፎ
ወደ እነርሱ ክሊኒክ ለመታከም የሚመጡት ተጠቃሚዎች የሚወስዱት
ይህንን ዕፅ እንደሆነ እና አደንዛዥ ዕፁንም ሩሲያውያን እንደሚያመርቱት
ጭምር አጫውቶኛል።” አለችው ኒኪ፡፡
“ልክ ነሽ” አለና ኒኪ ስለ አደንዛዥ ዕፁ በማወቋ ትንሽ ተገረመ፡፡ “ትሬይ ለአንድ የሜክሲኮ አደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪ ነበር ይሠራ የነበረው። የአደንዛዥ ዕፁንም ገበያ ከሩሲያኖቹ ጋር እየተፎካከረ እንዲቀጥል አድርጎላቸው ነበር።
እነዚህ አብሯቸው ይሰራ የነበሩት ሰዎች አዲስ ህይወት መጀመሪያ ስለሚባል ነገር መስማት አይፈልጉም፡፡ እንዲያውም እሱ ሥራውንዐእንዲያቋርጥ በፍፁም የሚፈልጉ ሰዎች አይደሉም::”ፀ

“ግን እኮ እሱ እነዚህን ነገሮች ትቶ አዲስ ህይወት ጀምሯል እኮ!”ብላ ኒኪ ሙግቷን ቀጠለች እና “ዶውግ ከሱስ እንዲፈወስ ካደረገው በኋላ ትሬይ በሙሉ ተለውጧል። እኔም ቢሮዬ ውስጥ ሥራ ሰጠሁት።ትሬይ በየቀኑ ሰዓቱን አክብሮ በመገኘት ሥራውን በብቃት ሲወጣም ነበር”

“ይህ ቀን ቀን አንቺ ቢሮ ውስጥ ሲሰራ የነበረው ሥራው ነው፡፡” አላት፡፡እና ዊልያምስ በመቀጠልም “ባለቤትሽ የአደንዛዥ ዕፅ ሱሰኛን ከሱሱ በደንብ
አድርጎ እንዲላቀቅ የሚያደርግ ትልቅ ባለሙያ እንደሆነ አምናለሁ፡፡ ነገር
ግን የናርኮቲክ ቢዝነሱን አስመልክቶ ብዙ የሚያውቅ አይመስለኝም፤ ሌላኛው
ትሬይን ቀጥሮ የሚያሰራው ሜክሲኳዊ የአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪ አለቃው
ስም ካርሎስ ዲ ላ ሮዛ ይባላል” አላት እና ኒኪን ቀጥ ብሎ እየተመለከተ

ስሙን ስትሰማ ፊቷ ላይ ለውጥ እንዳመጣ ለማጣራት ቢሞክርም ፊትዋ
ላይ የተለየ ነገር ማንበብ አልቻለም። ምክንያቱም ትሬይ ከጀርባ ሆኖ
አደንዛዥ ዕፅ ያዘዋውር ነበር የሚለው ሃሳብ በጣም አስደንግጧት ነበር፡፡

እና ይሄ ያልከው ሰው ነው ትሬይን የገደለው? ወይም ያስገደለው ብለህ
ታስባለህ?”

“ይህንን እንኳ በእርግጠኝነት ልመልስልሽ ያስቸግረኛል ግን ሊሆን የማይችልበት ምክንያት የለም ብዬ እገምታለሁ፡፡ በተለይ ደግሞ አንቺ እንደነገርሽኝ ከሆነ ትሬይ ይህንን ስራውን ለማቆም ሙከራ ካደረገ ሊያስገድሉት ይችላል እላለሁ፡፡ ዴላ ሮዛ ዌስት ሞንት ውስጥ በጣም ትልቅ አሳ ሊሆን ይችላል” ብሎ ዊልያምስ ገለፃውን በመቀጠልም “ነገር ግን በአለም ዙሪያ ከሚገኙ ታላላቅ አደንዛዥ እጽ አምራቾች እና አዘዋዋሪዎች አንጻር ሲታይ እሱ ትንሽዬ የጥብስ አሳ ነው፡፡”

“የ ዴ ላ ሮዛ አለቃ እጅግ በጣም አደገኛ ሰው ነው፡፡ እዚህ ላይ ነው እንግዲህ ነገሩ ገራሚ ነገር የሚታይበት፡፡” አላት፡፡
“የዚህ እጅግ በጣም አደገኛ አለቃ ስም ማን ይባላል?” ብላ ኒኪ ጠየቀች፡፡

“ዶክተር ሮበርትስ ብታምኚኝም ባታምኚኝም ይህንን ሰው በሆነ መልኩ
የምታውቂው ሰው ነው፡፡ ሉዊስ ዶሚኒኩ ሮድሪጌዝ ይባላል።” ኒኪም ግንባርዋን ቋጥራ ስሙን የት እንደምታውቀው እያሰበች ቆየች።

“አኔ ቤታማን የምትባለው የአንቺ ታካሚ የዚህ ሰው ሚስት ናት” ካላት በኋላ ዊልያሚስ ላፕቶፑን አዙሮ የጎግል ኢሜጅ ላይ ያገኘውን የአንድ መልከ መልካም ዳር ዳሩ ላይ ሽበት ጣል ጣል ያደረገበት ጥቁር ሉጫ ጸጉር እና ጠንቃቃ አይኖች ያሉትን የላቲን ተወላጅ ፎቶ አሳያት፡፡
ኒኪም ግራ እንደተጋባች “ሚስተር ዊልያምስ የተሳሳትክ ይመስለኛል
ወይንም ደግሞ እንድትሳሳት ሆነሃል የአኔ ባለቤት እኮ የሪል እስቴቶችን
ገንብቶ የሚሸጥ የቢዝነስ ሰው ነው፡፡” አለችው፡፡

“ዴሪክ ብለሽ ጥሪኝ እባክሽን” ብሎ አስታወሳት እና በመቀጠልም “ምንም
ነገር አልተሳሳትኩም ሉዊስ ሮድሪጌዝ አኔ ቤታማንን ያገባት የዛሬ ስምንት አመት ኮስታሪካ ውስጥ ቀለል ባለ ሰርግ ነው ካላመንሽኝ የምስክር ወረቀታቸውን ኮፒ ላሳይሽ እችላለሁ እኔ ይህ ጉዳይ የሳበኝ ከዚህ በፊት ከሉዊስ ሮድሪጌዝ ጋር የሚገናኝ ስራ ሰርቼ ስለነበር ነው ጉዳዩም አንዲት ሜክሲኮ ውስጥ የጠፋች ወጣት ሴትን አስመልክቶ ነው፡፡ በይፋ ባይሆንም ሁሉም ሰዎች ወጣቷ ልጅ በሰው እንደተገደለች
👍61
#የወዲያነሽ


#ክፍል__ሰላሳ_ስድስት


#ድርሰት_በሐይለመለኮት_መዋል


....እናቴ አዘኔታ በሚታየበት ፊት ወደ እኔ መለስ አለችና ሞኝነትህ፣ ሞኝነትህ ነው ልጄ! 'አይዞሽ ግድ የለሽም' ብለህ ይዘሃት ና፡፡ እኔ እናትህ አሳምሬ እቀበልልሃለሁ። አትፍሪ! አትፍሪ ነዪና እንታረቅ፣ ከእንግዲህ ወዲያ እኔና አንቺ እናትና ልጅ ነን፣ ልጄ ልጄ ብላሻለች” ብለህ አሳምረህ ንገርልኝ በማለት ያን በውስጤ ሲገላበጥ የዋለ ሥጋትና የመንፈስ ሽብር ገደለችልኝ
እናቴ ጋሻዬነህን ፍለጋ መልከት መልከት ስትል እንቅልፉ ሊጥለው ሲያንጎላጅ
አየችውና «አፈር በበላሁት! ልጄን! ልጄን! ያቺ እናትህ እንኳን አላየች!» ብላ
ካነሣችው በኋላ እግሩን እያንዘላዘለች ወደ የውብነሽ መኝታ ቤት ይዛው ገባች::
የእናቴ እግር ወጣ እንዳለ የውብነሽ ድንገት ብድግ ብላ አለቀ! ጨብጠኝ
ወዳ አይምሰልህ የግዷን ነው» ብላ ደስታዋን ገለጸችልኝ።

«አዎ ከእንግዲህ ደግሞ አንድ አስቸጋሪና የለየለት ግብግብ ብቻ ይቀረኛል» ብዬ መለስኩላት

የወዲያነሽ ምነው ቆየህ? ና እንጂ ጌታነህ! ቁርጤን ልወቅ? የምትል
መሰለኝ፡፡ ሰዓቴን ብመለከት ዐሥራ ሁለት ሰዓት አልፏል። እናቴ ከተቀመጠች
በኋላ ጥያቄና መልስ ቀጠለ። ከመጠን በላይ ተዝናናሁ፡፡ መላ አካላቴ
ተንፈላሰሰ፡፡ የወዲያነሽን ሥቃይና መከራ ባጭር ባጭሩ አንዲትም ሳላስቀርና
ሳልዘነጋ እንደ ተረት ነጋሪ አሳምሬ ወጣሁላት። የእኔንም ልፋትና ውጣውረድ
ሁሉ ገለጽኩላት፡፡ ንግግሬን እንደ ጀመርኩ ፊቷ ትንሽ በትንሽ ጠወለገ፡፡ እንባዋ
እየተሽቀዳደመ ሲወርድ ማዘንና መፀፀቷ ገባኝ። የእናቴ ርኅራኄና ገራገርነት እንደ ኮረብታ ጎልቶ ታየኝ፡፡ በኀዘን ጠውልጎ በእንባ የራሰውን ጉንጯን በማየቴ
በጣም ረካሁ፡፡ በሕዝብ ኃይል ሥልጣን እንደ ያዘ መንግሥት ደስ አለኝ።
የወዲያነሽም ድል ስታደርግ ወለል ብሎ ታየኝ፡፡

«አሠቃይቻታለሁ በቁሟ ቀብሪያታለሁ» አለችና ልቅሶዋን ቀጠለች።
«ያለፈው አልፏል ከነገ ጀምሮ ታርቃችሁ ተፋቀሩ እንጂ እሷ በበኩሏ ሁለንም
ነገር ይቅር ብላ ትታዋለች በጣም እኮ ነው የምትወድሽ» ብዬ ትካዜዋን ለማቅለል ሞከርኩ፡፡ ሙሉ ፈገግታዋ ሳይመለስ ለመሄድ ተነሣሁ፡፡ «ጋሻዬን አምጪልኝ የውብነሽ!» አልኳት፡፡

«አንት ጨምላቃ ጨመለቅ! እኔ እጅ ገብቶ ነው የምትወስደው?ባይሆን እንኳ ዋንየዋ ከመጣች በኋላ የሆነው ይሆናል!» ብላ ቱግ አለች። ልቤ ጮቤ ረገጠች፡፡ ተደሰትኩ እንጂ አልከፋኝም፡፡ የወሬ ሠንጋ ጥለን ስናወራርድ ሁለት ሰዓት ተኩል አለፈ። የውብነሽን ለብቻዋ ጠርቼ «ነገ አራት ሰዓት እንድትመጪ» አልኳትና «ደኅና እደሩ» ብዩ ወጣሁ፡፡

የቤቴን አጥር ግቢ ከፍቼ ስገባ የወዲያነሽ ጋቢዋን ለብሳና የሰበሰቡን አግዳሚ ተደግፋ ስትጠብቀኝ ደረስኩ እንደ ወትሮዋ ነቃ መብላት ስላልተቀበለችኝ
አእምሮዋ በሐሳብ ጉልበቷ በመቆም እንደ ተዳከሙ ገባኝ። እጅዋን ያዝ አድርጌ ዐይን ዐይኗን እያየሁ አመሸው እንዴ የወዲያ ደስ ይበልሽ! ደስ ብሎኛል
የሄድኩበት ጉዳይ ተሳክቷል» አልኩና በምሽቱ አየር የቀዘቀዙ ጉንጮቿን ሳምኳቸው፡፡

«እንኳን ደኅና መጣህ? እንኳን ደስ ያለህ? ጋሻዬስ? ከእጅህ ላይ ሳጣው ጊዜ አፌ ተሳሰረ» አለችና በልከኛው የመብራት ውጋጋን ውስጥ ትክ ብላ ተመለከተችኝ፡፡ ተያይዘን ከገባን በኋላ እንዴት ብዬ ልግለጽልሽ? እናቴ በጣም ተደሰተች። ምነው የዛሬዋ ዕለት የሁለትና የሦስት ቀን ያህል በረዘመች ! ስለ አንቺና እኔም አንዳችም ሳላስቀርና ሳልደብቅ ነገርኳት። በጸጸት ተቃጥላ እንባ በእንባ ሆነች። ርኅራኄዋንና የእናትነት ልባዊ ፍቅሯን ለማግኘት ችያለሁ፡፡በመጨረሻ ግን ጋሻነህን ልውሰድ ብዬ ብጠይቅ አፈን አስያዘችኝ፡፡ «እሷን እዚህ ይዘህ መጥተህ ይቅርታ አድርጊልኝ ብዬ ሳንታረቅና እንደ እናትና ልጅ ሳንሳሳም፣ ልጅ የሚሉ ነገር አልሰጥም ብላ ማለች» ብዪ ጋሻዬነህ የቀረበትን ምክንያት አብራራሁላት፡፡

የወዲያነሽ እውነት ስላልመሰላት «መቼ ሥራ አጡና! እንኳን ጥራትና አምጣት ሊሉህ ይቅርና ይህንኑ ዐይኗን እንዳታሳየኝ ብለውህ ይሆናል፡፡ ያንተን ሥራ መች አጣኋትና! ታዝናለች፣ ይከፋታል ብለህ ነው:: አትጨነቅ ቢከፋኝስ ምን እንዳላመጣ ነው? አጀብ እቴ ! ያም ሆነ ይህ እንኳን ደስ ያለህ» ብላ አሻግራ ስትመለከት «አምጪ እጅሽን፣ የወዲያነሽ ሙች! » ብዩ ለእውነተኛነቴ ማረጋገጫ እንዲሆን እጅዋን ስቢ ጠፋሁት፡፡

ከጥቂት ቆይታ በኋላ ራት አቀረበች። ሆዴ በቀኑ ምግብ ደስታና ፈንጠዝያ በመጎሰሩ ምንም አላሰኘኝም፡፡ የወዲያነሽ «በቃኝ! በቃኝ!» እስከምትል ማጉረስ በመቻሌ እንደገና ደግሞ አጋጣሚው አስደሰተኝ። ከራት በኋላ ከቀኑ ወሬ ውስጥ ቀነጫጭቤ አወራሁላት። በጥርጣሬና በሥጋት ታፍኖ የነበረው አእምሮዋ ገለጥለጥ ስሳለላት ጥርጣሬዋ ከላይዋ ላይ በንኖ ጠፋ፡፡

«እኔ በበኩሌ ቂም የሚሉ ነገር አልያዝኩም፡፡ ላንተ ስል ሁሉንም ነገር ትቼዋለሁ፡፡ የፈራሁትና የሠጋሁት አሻፈረኝ ይላሉ ብዬ ነው እንጂ፣ እሺ ካሉንማ ምን ቆርጦኝ። ጫማቸው ላይ ወድቄ ይቅርታ አድርጉለኝ ብላቸው ምን ነውር አለበትና ነው?» በማለት እቅጩን ነግራኝ ወደ መኝታ ቤት ገባች። መላ ሰውነቴ ጥርስ አውጥቶ ሣቀ፡፡ ተከትያት ገባሁ። ምንጊዜም ከዚያ ቀደም ወስዶኝ በማያውቅ ሁኔታ እንቅልፌን ስለጥጥ አደርኩ፡፡ እውነተኛ ፍቅርና የሕሊና ጸጥታ ምንኛ ሰላም ይሰጣሉ!
የወዲያነሽ ቀኝ እጅዋን በብርድ ልብስ ውስጥ አሾልካ ግንባሬን
እየዳበሰች «እንዴ? የዛሬውስ እንቅልፍ ለብቻው ነው፣ ለጤና ያድርግልህ» ብላ በማያስደነግጥ ሁኔታ ባትቀሰቅሰኝ ኖሮ ተኝቼ አረፍድ ነበር። ከአንገቴ ቀና
ብዬ «ረፍዷል እንዴ? ስንት ሰዓት ሆነ?» አልኳት፡፡ ሰዓቷን አየት አድርጋ «ሦስት ሰዓት ከሐያ አምስት» ብላኝ ሄደች።

በመስኮቱ በኩል የገባው የረፋዷ ፀሐይ ጮራ ክፍሉን አወግጎታል።
ተጣጥቤና ለባብሼ ለመቀመጥ ቸኮልኩ፡ ሠራተኛይቱ ያመጣችልኝ ሽግ ያል ውሃ ደህና አዝናናኝ፡፡ ጊዜው በመገሥገሡ ተደሰትኩ በእናቴ ፊት «የሚያስከብረኝን» ልብስ ለብሼ ስጨርስ አራት ሰዓት ተኩል አለፈ፡፡

የወዲያነሽ ከፊት ለፊቴ ቆም አለችና ምን ዓይነት ልብስ ልልበስ? እስኪ ንገረኝ?» ብላ ዐይኖቼን በዐይኖቿ አቆላመጠቻቸው ደረቷ ላይ ዠቅ
ያለውን ሐብልና መስቀል እየተመለከትኩ «መጨነቅና መጠበብ አያስፈልግም የአንቺ መጎናፀፊያና ግርማ ሞገስሽ የሰው ልጅነትሽ ብቻ ነው። የሐር ድርብና የወርቅ ቁርጥራጭ አይደለም፡፡ ይህን የአጣና ያአገኘ የመለያ ምልክት በግብግብ
እናስወግደዋለን። ደስ ያለሽን ልበሽ?» አልኳት። ባለ ወይን ጠጅ ጥለት ኩታና ቀሚስ ለብሳ፣ ተረከዘ
አጭር ጫማ ተጫምታ ጸጉሯን በቀላሉ ጎነጎነችው፡፡

ምንም እንኳ ቀደም ሲል በሕወይቷ ላይ በደረሰው ተደጋጋሚ ችግርና የሕሊና
ሥቃይ የተነሣ አካላቷ ሲፈካና ሲጠወልግ፣ ሲከሳና ሲኮስስ ቢኖርም፣ የወዲያነሽ በአሁኑ ጊዜ በምቹ ቦታ ላይ በቅላ በማለፊያ ዳስ ላይ እንደ ተንሰራፋች የወይን
ተክል ሐረግ ቀስ በቀስ አምሮባታል።

የችግርና የሠቀቀን ኑሮ ያሟሰሰው ለዛና ዛላዋ፣ ውበትና ደም ግባትዋ
እንደገና እንደ ሐምሌ ጎርፍ እየሞላ፣ እንደ መስከረም ወንዝ እየጠራ፣ እንደ ጥቅምት አዝመራ አሺቷል። ከአገርና ከሕዝብ መኻል በተለይ ተመርጣ የምትጠቀስ ልዩ ቆንጆ ባትሆንም የወዲያነሽ የምትኮክብ የውበት ጉልላት
ሆነች። ጠበብ ካለው ግንባሯ ግርጌ ከቅንድቦቿ ድባብ ሥር ያሉት ተንተግታጊ ውብ ዐይኖቿ ከሥጋ ቅምር ሳይሆን ከሚጨበጥ ንጥረ ብርሃን የተሠሩ መሰሉ፡፡
👍51
#የተወጋ_ልብ


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#ድርሰት_በትክክል_ገና


...ሁለት ዓመታት እንደ ዋዛ አለፉ። በነዚህ ሁለት አመታት ውስጥ የአማረችና የጌትነት ግንኙነት ደረጃ በውል አልታወቀም። አማረች በሁለተኛው አመት መጀመሪያ ላይ የእናቷን ቡናማ ቀለም ያላት ዳትሰን መኪና
ይዛ መምጣት ጀመረች። ይሄ ሁኔታ ደግሞ በመካከላቸው ያለውን ልዩነት ይበልጥ አጎላበትና ድህነቱ ተፅእኖ ያሳድርበት ጀመር፡፡ በልቡ የተሰማውን ስሜት በአንደበቱ ለመግፅ ከአቅም በላይ መንጠራራት እየመሰለው ፈራት፡ የግንኙነት ደረጃቸው እስከምን ድረስ እንደሆነ እሷ እንድትነግረው ፈለገ፡፡ እሷ ደግሞ ግፊቱ ከሱ እስከሚመጣ ድረስ ጠበቀችው፡፡
ሁለቱም ከሱ ይምጣ ከሷ ይምጣ ሲባባሉ ጊዜው ነጎደ። አማረች በቤት ውስጥ መነጫነጭ ጀመረች፡፡ እሷ ስትበሳጭ እናቷ አብረዋት ጭንቅ ጥብብ ይላሉ፡፡ “ምን ሆነሻል ልጄ?እስቲ የሆንሽውን ንገሪኝ?" ይሏታል።
ምክንያቱን እሷም በውል አታውቀውም፡፡ ይሄ ንጭንጫ ከጌትነት ጋር ስትገናኝ ድራሹ ይጠፋል፡፡ ደስተኛ ሆና አብራው ትቆያለች። ከሱ ስትለይ ደግሞ ያው ፀባይዋ ተመልሶ ይመጣል። ቀስ በቀስ ፍቅር እንደጀማመራት ተረዳች። ሲሽሻት በዘዴ የቀረበችው እሷ ትሁን እንጂ አፍ አውጥታ አፈቀርኩህ ብላ ለመጠየቅ ተቸገረች። ሴት ልጅ ለፍቅር ስትጠየቅ እንጂ ስትጠይቅ አልተለመደምና እንዴት አድርጋ ስሜቷን እንደምትገልጽለት
ከመጨነቅ የተነሳ የሌለባትን ፀባይ ማሳየት ጀመረች።

ዩኒቨርሲቲው ሊዘጋ ተቃርቧል። ጌትነትና አማረች ፈተና ጨርሰው
ውጤቱን በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡ ትምህርት ቤት ከተዘጋ ደግሞ በየቀኑ መገናኘት ሊቀር ነው። አልፎ አልፎ ስልክ መደዋወሉ ብቻ ብዙም ፋይዳ የለውም፡፡ በየግላቸው በናፍቆት ሲጠበሱ መክረማቸው ነው፡፡
ቢያንስ ዐይን ለዐይን እየተያዩ ረሃባቸውን ለመወጣት ሰበባቸው ትምህርት ቤት ነበረችና መዘጊያዋ ሲደርስ ሁለቱም ተጨነቁ፡፡ በተለይ አማረች ይሄው ለተወሰነ ጊዜ የመለያየቱ ነገር በይበልጥ አስጨንቋት ሙሉውን ሌሊት በሀሳብ ስትገላበጥ አነጋች፡፡ ጌትነትን ወኔ ለማላበስ ምን ማድረግ እንዳለባት ዕቅድ ስታወጣ ፕሮግራም ስትነድፍ አደረች።

"ጌትሽ ትምህርት ቤት ከመዘጋቱ በፊት በፈተና ሲጨነቅ የከረመ አእምሯችንን ትንሽ ለማዝናናት ወደ ላንጋኖ ብንሄድ ምን ይመስልሃል?' ከፊቷ ፈገግታ ባይጠፋም በልቧ እምቢ ብሎ እንዳያሳፍረኝ አምላኬ አደራህን እያለች ነበር፡፡

ያንን ከአማረች የተሰነዘረ የተቀደሰ ሃሳብ ሲሰማ የጌትነት ልብ በደስታ
ወከክ አለች። በተለይ የሀብታም ልጅ መሆኗን እየተረዳ ከመጣ በኋላ "እንድታስጠናኝ እንጂ እኩያህ ነኝ ወይ? እንዴት ያለአቅምህ ትንጠራራለህ? የሳቀና የተጫወተ ሁሉ አፈቀረ ማለት አይደለም የድሃ ልጅ!"ብላ ቅስሜን ብትሰብረውስ? የሚል ፍርሃት ሸምቅቆ ይዞት ነበር። ተንቀዥቅዦ ውርደት ከመቅመስ ይልቅ የሷን ፍላጎት ከሷ ከመጠበቅ ውጪ
አማራጭ የለውም ብሎ ወስኖ በነበረበት ሰዓት ይሄንን ሲመኘው የኖረውን ሰናይ ሃሳብ ስታቀርብለት አላንገራገረም፡፡

"ደስታውን አልችለውም አማረች ግን መቼ?" አላት፡፡ቅዳሜ ዕለት የዋና ልብስ እንዳትረሳ!... "
ቅዳሜ ከጠዋቱ ሁለት ስዓት ላይ ለገሀር እንዲጠብቃት ተቀጣጠሩ
ቅዳሜ ላንጋኖ ደርሰው ተዝናንተው በእለቱ ወደ አዲስ አበባ ሊመለሱ
እንደማይችሉ የታወቀ ነው። ነገሩ አዳር እንዳለበት በልቡ ገመተና ለማንኛውም ብሎ ለእህቱ ነገራት፡፡


"ዘይንዬ ነገ ወደ ላንጋኖ ሳልሄድ አልቀርም ምናልባት ካደርኩ ከጎረቤት የሚያስተዳድርሽ ሰው ልፈልግ?" አላት፡፡
"ወንድም ጋሼ ለምን አብሬህ አልሄድም?” አለችው፡፡ ደንገጥ አለ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ እህቱ ያቀረበችለትን ጥያቄ ላለመቀበልና ለመዋሸት ተገደደ::“ዘይንዬ ጉዞው ከመስሪያ ቤታችን ሰራተኞች ጋር ስለሆነ አይመችም::
በሌላ ጊዜ ፕሮግራም ይዘን እንሄዳለን እሺ?" አለና ተለማመጣት::"እሺ ወንድም ጋሼ ለእትዬ ጤናዳም እነግራቸውና ከሎሚ ጋር አብሬ አድራለሁ" የዕድሜ አቻ የጎረቤታቸውን ልጅ ማለቷ ነው፡፡

በከፍተኛ የንፋስ ሞገድ የታጀበ ውርጭ እንደ ጅራፍ እየተጋረፈ ይዘንባል። የብዙዎቹን ሰዎች ጃንጥላ የሚገለብጥ የሚያፏጭ ንፋስ ከታክሲ ላይ ወርዶ እየሮጠ ሄደና ከአንድ ህንፃ ስር ተጠለለ፡፡ ከቀጠሮው በፊት ስላሳ ደቂቃ ቀድሟል፡፡ የቀጠሮው ሰዓት ሊደርስ አምስት ደቂቃ ሲቀረው
ዐይኖቹን አሻግሮ ወረወረና ከወዲያ ማዶ ብቅ ባለችው ቡናማ ዳትሰን መኪና ላይ አሳረፋቸው። አማረች ከቀጠሮው በፊት አምስት ደቂቃ ቀደም ብላ መድረሷ ነበር። እየሮጠ ሄደ። ተገናኙ። ሞቅ ያለ ሰላምታ ተለዋወጡ። "ጎበዝ ሰዓት አክባሪ!" የጋቢናውን በር እየከፈተችለት በቀጠሮ አክባሪነቱ አድናቆቷን በፈገግታ ገለፀችለት፡፡

“አመሰግናለሁ" እሱም እየሳቀ ነበር፡፡ መቼም አማረች የጨዋታ ቅመም ነች፡፡ እንኳንስ ወደ ሽርሽር ቦታ ለመዝናናት እየሄዱ ይቅርና በአስጨናቂው ጥናት ላይም ቢሆን አፍ ታስከፍታለች። በተለይ የዛሬው ጉዞ የረጅም ጊዜ ጓደኝነታቸው ወደ ላቀ ደረጃ የሚሸጋገርበት አጋጣሚ ነውና
ፍፁም ነፃነት እንዲሰማው የተቻላትን ሁሉ ለማድረግ ወስናለች። ጉዞ ተጀመረና ቀስ እያሉ እየተዝናኑ አዋሳ ደረሱ። አዳር በቀለ ሞላ ሆቴል ነበር። ራታቸውን በልተው ሲጨዋወቱ አመሹ :: የተያዘው አልጋ
ሁለት ነው፡፡

“አንድ አልጋ ይበቃናል ለምን ለሁለት አልጋ ይከፈላል የሚል የተቀደሰ ሃሳብ ያቀረበ አልነበረም" መኝታ ክፍላቸው ጎን ለጎን ቢሆንም በመካከሉ የግንብ ግርዶሽ አለ፡፡ በይሉኝታና በፍራቻ ግርዶሽ ላይ የግንቡ ግርዶሽ ተጨምሮበት ለሊቱን ሙሉ ተለያይተው ማደራቸው ነው፡፡
የቅርብ ሩቅ... በመንፈስ እሱ ወደ እሷ እሷም ወደ እሱ እየሄዱ ቢፈላ
ለጉም ሃሳባቸውን በግልፅ አውጥተው መነጋገር አልቻሉምና መድረሻቸውን ያላወቁ መንታ መንገድ ላይ የቆሙ መንገደኞች ሆኑ። በስሜትዐረጅም ርቀት የተጓዙ ነገር ግን በይሉኝታ ልጓም ተሽብበው የተያዙ ተፈላላጊዎች። አማረች የዛሬው ግብዣዋ የሽርሽር ብቻ ሳይሆን የፍቅር ግብዣንም የሚያጠቃልል መሆኑን ከሁኔታዎች ይገነዘባል የሚል እምነት ነበራት፡፡ እሱ ደግሞ ይቺ ቆንጆ የሀብታም ቤተሰብ ልጅ በትምህርት ቤት ውስጥ በተመቻት ጊዜና ቦታ ሁሉ እየተገኘ የሚያስጠናትን እንደ ውለታ ቆጥራ ያንን ውለታ ለመክፈል የጋበዘችው እንጂ የፍቅር ግብዣ ጭምር መሆኑን አላወቀምና ፈራት፡፡ እሱ እንደሚያስበው በፍቅር አስባው ካልሆነ ሊያስቀይማት ሊጣላት ነው ማለት ነው፡፡ ይህንን ደግሞ
አልፈለገውም፡፡ ዐይኖቹ ያንን ልብ የሚያጠፋ ውበቷን በቅርበት እያስተዋሉ እንዲያደንቁ፣ ጆሮዎቹ ያንን የማይጠገብ ጨዋታዋን እንዲያደምጡ፣ አፍንጫው ያንን ጣፋጭ መአዛዋን ያለምንም ገደብ እያጣጣመ በሀሴት ይሞላ ዘንድ የተፈቀደለት ሰው ነውና ቢያንስ ቢያንስ ሌላው ባይሳካለት እንኳ እሷነቷን ጥሬ ጓደኛነቷን ላለማጣት ራሱን ቆጠበ፡፡ ሲያያት
ምራቁን የሚውጠው ወንድ ሁሉ ያልተፈቀደለትን እሱ ተፈቅዶለታል።
ይሄ ሁሉነቷ ገደብ ያልተደረገበት ሰው ነውና ከራሷ እስካልመጣ ድረስ ተሽቀዳድሞ ነገር ማበላሸት ይሆናል በሚል ፍራቻ ዝምታን መርጧል።
👍4
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ

...«እየው» አሉት ወደ ጆሮው ጠጋ በማለት «እሙዬን ራሴን አሞኛልና
መድሃኒት ግዢልኝ ብዬ ወደ ከተማ ልልካት ነው። እሷ ከሄደች በኋላ የምነግርህ ነገር አለኝ። በል ቶሎ ተኛ፡፡» አሉት እያዋከቡት።

“ምንድነው እሱ?» አላቸው አስራት ዓይኑን ዓይናቸው ላይ ትክል አደርጎ።
«ብኋላ እነግርህ የለ! አሁን ተኛ፣» አሉትና ወደ ጓዳ ገባ ብለው ጋቢ
አምጥተወ ሰጡት፡፡ በል ቶሎ በል!ካሉ በኋላ አሁንም ወደ ጆሮው ጠጋ ብለው «እሙዬ ምን ሆንክ ታለችህ ድንገት ቁርጠት ተነሳብኝ ብለህ ቅልስልስ እያልክ ንገራት።
አሉት ጣደፍ ጣደፍ እያሉ።
አስራት ግራ እየገባው ጋቢውን ለብሶ ቁጭ ብሎበት በነበረ መደብ ላይ ጥቅልል ብሎ ተኛ፡፡ በጆሮው ግን የእናቱን እንቅስቃሴ በጥንቃቄ ያዳምጣል፡፡
የሔዋን እናት የአስራትን አተኛኘት ካረጋገጡ በኋሳ ወደ ጓሮ ዞሩ። ልክ እንደ ታመሙ" ሁሉ ሰውነታቸውን ድክምም፤ ዓይናቸውን ቅዝዝ፣ ፊታቸውንም
ጭምድድ አድርገው ከሔዋን አጠገብ ደረሱና በቀስታ እየተቀመጡ «እንዴት ይሻለኛል
እሙዬ ስላልተቀሳቀስኩበት ነው መሰለኝ ይኸ ራሴ ተነሳና ይፈልጠኝ ጀመር ያንን ኪኒንና የምትሉትን ነገር ግዛልኝ ልለው ወደ ቤት ብገባ አስራቴ ደሞ ሆዴን አመመኝ ብሎ ተኝቶ አገኘሁት።
አሉና ኧረ እዲያ» በማለት ብስጭትና ምሬታቸውን ለመግለፅ ሞከሩ።

«አመመሽ እማ?» አለቻቸው ሔዋን ሁኔታቸውን ሰለል እያደረገች፡፡ብታይ ጦሩን ይዞ ሽቀሽቀኝ፡፡ አሏት ራሳቸውን በሁለት እጃቸው ይዘው
ወደ መሬት በማጎንበስ።
«ምን ዓይነት ኪኒን ይሆን?»
«ይኽ እምብሮ ነው ምንትስ የምትሉት!
«አስፕሪን ይሆናል::»
«ይሆናላ! እኔ አላቀው፡፡ እንዳንዴ ሲያመኝ ይኸው አስራቴ ነበር
የሚገዛልኝ። እንግዲህ አባታችሁ እስከሚመጣ ልጠብቅና የሚያውቀው ተሆነ ይገዛልኛላ::"» አሏት በግማሽ ልባቸው ወደ ሔዋን ወረቀቶች ዓየት እያረጉ፡፡
«እኔ እገዛልሻለሁ እማ!» አለቻቸው ሔዋን።
«አዬ...ልጄ! መንገዱ ይርቅሻል። የኛ ሰፈር ደሞ ገጠር አይሉት ከተማ አጉል ነው።ከሱቅ እስቲደርሱ ድረስ ያለው መንገድ መች ቀላል ነውና።ክ
«ግድየለም እማ! መግዣውን ስጪኝ፡፡» አለቻቸው።
«ተበረታሽ ደግ የኔ ልጅ!» ብለው ከተቀመጡበት ተነሱና ነይ ቤት
እሰጥሻለሁ፡፡» እያሉ ወደ ቤት አመሩ፡፡ አስራት ጥቅልል ብሎ እንደተኛ ነው፡፡
የእናቱንና የሔዋንን ወደ ቤት መግባት እውቆ የሚደረገውን ለመከታተል ጆሮውን አቁሞ ሳለ ሔዋን ተናገረችው።
«አመመህ እንዴ አስራት!»
«አረ ቁርጠት ሊገለኝ ነው፡፡» አላት ገልበጥበጥ እያለ።
የሔዋን እናት ፈጥነው ወደ ጓዳ ገብተዋል። «ቆይ ተኔ መድሃኒት
እንሰጥሀለን፡፡ እስከዚያው ቻለው፡፡» እያሉ ይዘው የመጡትን ገንዘብ ለሔዋን ሰጧት፡፡ ተቀብላቸው ከቤት ስትወጣ እስከ ውጭ ድረስ ሸኟት፡፡
ጥቂት ርምጃዎች እስክትራመድ ድረስ በዓይናቸው ሲከታተሏት ከቆዩ በኋላ ፊታቸውን ወደ ግቢው በር ምልስ አድርገው እስከ ቁርጭምጭሚታቸው ይደርስ
የነበረ የአበሻ ቀሚሳቸውን እስከ ጉልበታቸው ድረስ ሰቀሰቁና ወደ ቤት ሳይገቡ ወደ ጓሮ
በሚወሰደው መተላለፊያ መንገድ ሮጡ። ከቦታው ሲደርሱ የሔዋንን የወረቀት አቀማመጥ ልብ ብለው ተመለከቱ፣ወረቀቷን ሲመልሱ
አቀማመጡ እንዳይጠፋባቸው ተጠነቀቁ። ከዚያም የጻፈችባትን ወረቀት ከማስደገፊያዋ ደብተር
ውስጥ ቀስ ብለው መዝዘው አወጧትና አሁንም በሩጫ ወደ ቤት ገሰገሱ።
“እስቲ ተነስ እስራቴ! አሉት ቶሎ ቶሎ እየተነፈሱ።
አስራት ከተሸፈነበት ገለጥ ብሎ ከፊትለፊቱ የቆሙ እናቱንና በእጃቸው የያዝዋትን ወረቀት እየተመለከተ «ምንድነው?» ሲል ጠየቃቸው፡፡
«ቶሎ ተነስ! እሙዬ የጣፈችው ወረቀት ነው፡፡ ሳትመጣብን አንብበውና ከአስተቀመጠችበት ቦታ ልመልስ አሉት በተቻኮለ አነጋገር፡፡
አስራት ከተኛበት ቀና ብሎ ወሪቃቱን ተቀበለና አየት ሲያዩርግ ግጥም ደረድርበታለች፡፡ ከግጥሙ ዳርና ዳር ደግሞ የተለያዩ ቃላት ተሞነጫጭረውበታል።
አስቹ ሆዴ፣ የኔ ምስኪን.. ወዘተ የሚሉ፡፡ ወደ ዋናው ግጥም ከመግባቱ በፊት እነዚህን ቃላት አየት አየት ሲያደርግ ለካ ለሔዋን እናት ዘግይቶባቸው ኖሯል፡፡

“አንብበው እንጂ! አቃተህ እንዴ?» ሲሉ ጮሁበት፡፡ አስራት ግጥሞቹን ማንበብ ጀመረ።
እናቱም፣ ጀሮአቸውን አቁመው ያዳምጡ ጀመር።

«የኔ ሆድ አስቻለው አንተ የኔ ከርታታ!
ላመንከው ለመሞት የማታመነታ።
እመጣለሁ ብለህ ሄደህ እንደዋዛ፣
አንተም በዘያው ቀረህ የኔም አሳር በዛ፡፡
በእርግጥ ባትኖር እንጂ ፍጹም በሕይወት፣
አይጨክንም ነበር አስቹ የአንተ አንጀት።

የበላክን አውሬ ምነው ባገኘሁት፣
በውስጡ ባገኝክ እኔም በበላሁት።
ደምህን ከደሜ አጥንቴን ከአጥንትህ፤
አገናኝህ ነበር ነፍስ እንዲዘራብህ፡፡

የሳምከው ከንፈሬ ደርቋል እንደ ኩበት፤
እህል ውሃ ጠልቶ አንተ የሌለህበት፡፡

እንደው ሂጂ ሂጂ ብረሪ ይለኛል፣
እልም ያለው ገደል ባህሩ ይታየኛል።
ዛሬ ነገ አልኩ እንጂ ልቤ እየዋለለ፣
ስሜቴስ ይጮሀል በርቺ በርቺ እያለ።
ይጎነትለኛል የናፍቆት ሰቀቀን፣
አንተን ካላገኘሁ አይቀርም አንድ ቀን።»
«ኧ! ኧ! እስቲ እስቲ ድገመው!» አሉ የሔዋን እናት አሁንም ጆሮአቸውን ወደ አስራት ጣል አድርገው:: ዓይናቸው ፍጥጥ ማለት ጀምሯል፡፡
አስራት ቀስ ረጋ ብሎ ደግሞ አነበበላቸው: አንብቦ ከጨረሰም በኋላ እናቱ የሚሆኑትን ለማየት ቀና ብሎ በስጋት ዓይን ያያቸው ጀመር።
የሔዋን እናት ድንገት ጥርሳቸውን ግጥጥ፣ ፊታቸውን ክፍት አደረጉና
እንባቸውን እያዘሩ "እክክክክ..እክክክክ...እክክክክ" አሉ አንዳች የሀዘንና የስጋት
ስሜት ውስጣቸው ገብቶ በረብራቸውና፡፡ቀጠሉ አሁንም እጆቻቸውን በነጠላ ላይ ሸፍነው በወገባቸው ላይ በማሳረፍ ቀሚሳቸው በአየር ተንሳፎ
እስኪገለብ ድረስ በቆሙበት ላይ ወደ ግራ ቀኝ እየተወዛዙ «አንቲ» አሉ የጥሪ ያህል በረዘመ ድምፅ።
ሟቿን የአስቻለውን እናት መጥራታቸው ነው።«የጠጡት ጥዋ የለም? የካደሟት አድባር የለችም? የሳሙት ቤተክሲያን የለም፣? አረ አንድ በሉኝ! ኧረ በውቃቢዎ! ድረሱልኝ! ኧረ ልጆዎ ልጄን በላብኝ! ኧረ ልጄን አስመነነብኝ! ኧረ ምን አባቴን ልሁነው! እያሉ ዓይንና አፍንጫቸውን በነጠላቸው
እየጠራረጉ ልክ ሞታ ቀብረዋት ሀዘናቸው ገና እንዳልወጣላቸው አይነት ወያኔ ልጄን ወይኔ ልጄን እመዬ ምን ላርግሽ? እንደው ምን ልሁንልሽ? ልጄ! ልጄ! ልጄ! አሉ በተከታታይ።
“ምነው እማዬ! ምን ሆንሽ?» አላቸው አስራት ደንግጦ ።
በቃ እኮ እንግዲህ እኔም ልጄ በህይወት አለች ብዬ ተስፋ አላደርግም አንተም እህት አለችኝ ብለህ አታስብ! ልጂ ማምለጧ ነው። እሙዩ ተእንግዲህ ሰው አልሆነችም በቃ በቃ! በቃ በቃ! እህህህ።
«አረ ምንም አትሆን እማ»
«ኧረ ወዲያ አስራቴ በቃ ቁርጡን ነገረችን እኮ! በቃ ተናዘዘች እኮ!
«እሙዬ ገደል መግባቷ ነው እኮ! እ፤ህህህህህህ…"
«እንጠብቃታለና»
«አየየ... ጥበቃ! አየየ... ጥበቃ ዋልኝ! የሷ ነገር ተእንግዲህ ከበቃ
እኔም አብሬ ወደ ገደል ነው! እኔም ከእሷ ጋር ወደ ባህር ነው እህህህህህ» አስራት
👍8
#ምንትዋብ


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ

....“ግዝየ እኛ ነን።”

ጥላዬ፣ በወርቅ ያሸበረቀችው ቁስቋም ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ሲገባ በቤተክርስቲያኗ ውበት ተማረከ። በአጥሩ ግንብ ማማር ተደነቀ።ፀሐይዋ አለዚያን ቀን እንደዚያ አብርታ የማታውቅ መስላ ታየችው።ቆም ብሎ ሁሉን በዓይኑ ቃኘ።

ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ከሞተ በኋላ፣ ምንትዋብን የማግኘት ፍላጎቱ
ቢበረታም አስራ ዐራት ዓመት ሙሉ ቆርጦ አለመነሳቱ ኅሊናውን
ሲቆጠቁጠው ቆይቶ፣ የኢዮአስን ሞትና የመንግሥቱን ማብቃት ሲሰማ አላስችል ብሎት ወደ ጐንደር አቀና።

ከአብርሃም ቤት ወጥቶ ቁልቁል ሲወርድ፣ የተጫጫነው ትካዜ፣ ገና ከደብረ ወርቅ ሲነሳ ምንትዋብ ላይ የደረሰው ድርብ ሐዘን፣ የጐንደር መበጥበጥ፣ የሃገሩ መረበሽ የልብ ስብራት የፈጠረበት መሆኑ ቀርቶ ዛሬ ቁስቋም ግቢ ውስጥ ሲቆም፣ ድንገት ሰላምና መረጋጋት በማግኘቱ ያችን ሰዐት ለዘላለም ለማቆየት የፈለገ ይመስል እዚያው ያለበት ቦታ
ቆሞ ቀረ።

ውስጡ የተቀጣጠለው የተስፋ ስሜት ያቺ ደማቅ ፀሐይ ከረጨችው ብርሃን ጋር ተዋሕዶ ልቡን አሞቀው። ለጊዜው እዚያ ቦታ ላይ ለምን እንደተገኘ ረስቶ፣ ሄዶ መሳለም ብሎም ጸሎት ማድረስ እንዳለበት ዘንግቶ ከቆመበት አልንቀሳቀስ አለ። ቁስቋምን በምናቡ ብራና ላይ
ሣላት። ቀደም ብሎ ጐንደር እንዲመጣ በሮብዓም ግብዣ ሲቀርብለት አለመቀበሉ የሚያየው ውበትና ታሪክ ተካፋይ ሳያደርገው በመቅረቱ ተቆጨ። አንዲት መነኩሴ እጅ ሲነሱት ደንገጥ ብሎ ሰላምታ ሰጣቸው።
ምን ያህል ጊዜ እዚያ እንደቆመ ባያውቅም ወደ ቤተክርስቲያኗ በዝግታ አመራ። በወንዶቹ መግቢያ በኩል ሄዶ በሩን ተሳለመ። ቆም ብሎም
ዳዊቱን ከማኅደሩ አውጥቶ ደገመ።

ሲጨርስ፣ ዙርያውን ተመለከተ። ወደ ቤተመንግሥት የሚመራው
ሰው በዓይኑ ፈለግ ፈለግ አደረገ። ወደ መጣበት ሲመለስ፣ አንድ ቄስ
ከግቢ ሊወጡ ሲሉ አያቸውና “አባቴ!” ብሎ አስቆማቸው። እንዲባርኩት ከተጠጋቸው በኋላ፣ ወደ “እቴጌ ቤተመንግሥት በየት ነው ምሄድ?” ሲል ጠየቃቸው።

ቄሱም፣ “በዝያ በወንዶቹ መግቢያ በኩል ሲኸዱ ዘበኞቹን ያያሉ።
እነሱ ያሳይዎታል” ብለውት ተሰናበቱት።

ተመልሶ ወደ ቤተክርስቲያኒቱ ወንዶች መግቢያ አመራ። በስተጀርባ በኩል ቁልቁል ሲወርድ፣ ቄሱ እንዳሉት በግንብ የታጠረው በር ላይ ዘበኞች ቆመዋል። ትኩር ብለው ያዩታል። ራቅ ብሎ እጅ ነሳና፣ “እቴጌ
ዘንድ ጉዳይ ነበረኝ። ስሜ ሥሙር ነው። ኸነማይ ነው የመጣሁት።
የእቴጌ ዘመድ ነኝ።” ብሎ የያዘውን የተጠቀለለ ዕቃ አሳያቸው።

ዘበኞቹ፣ ጉዳዩ ምን እንደሆነ ደግመው ደጋግመው ከጠየቁት በኋላ፣እንዲጠብቅ ነግረውት አንደኛው ወደ ውስጥ ገባ። ጥቂት ቆይቶ አንድ ያደገደገ አስተናጋጅ መጥቶ ማን እንደሆነና ጉዳዩ ምን እንደሆነ አጥብቆ ከጠየቀው በኋላ ሄደ። ጥላዬ እንደገና ዘለግ ላለ ተጨማሪ ጊዜ ከጠበቀ በኋላ፣ አስተናጋጁ ተመልሶ መጥቶ እንዲከተለው በእጁ
ምልክት ሰጠው።

ግቢው ውስጥ ሲገባ፣ የምንትዋብ ቤተመንግሥት ከፊት ለፊቱ ገዝፎ ታየው። በስተቀኙ ያለው የጸሎት ቤቷን እያደነቀ ሲሄድ ግቢው ውስጥ ያለው የሰው ብዛትና ጫጫታ ገረመው። ሕፃናት ከወዲያ ወዲህ ይራወጣሉ። “ኸነዝኸህ ውስጥ የልዥ ልዧቿ አሉበት መቸም”
ብሎ ወደፊት ሲመለከት ወይዛዝርትና ባለሟሎች ከወዲያ ወዲህ ይዘዋወራሉ። አስተናጋጁ በዝምታ ሲመራው ድንገት ግዙፍ የሆነ ግንብ ሲያይ ዝናውን የሰማው “ሽናዋ” የግብር አዳራሽ መሆኑ ገባው።የግንቡ ማማር ከፀሐይዋ ብርሃን ጋር ተደምሮ ዓይኑን አጭበረበረው።ምንትዋብን ራሷን እንደዛ ገዝፋ ያያት መሰለው።

ስለ ምንትዋብ ሲያስብ፣ ምን እንደሚጠብቅ ማወቅ አልቻለም።
ልጄ ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ሞቶ፣ ቤተመንግሥት ሁለት ተከፍሎ ብሎም ፍርክስክሱ ወጥቶ፣ ወጣቱ ንጉሠ ነገሥት አድያም ሰገድ ኢዮአስ በሻሽ ታንቆ ተገድሎ፣ ሬሳው ጉድጓድ ውስጥ ተጥሎ፣ መሣፍንት በየበኩላቸው
ተቆራቁሰው፣ ሃገር ተተራምሶ፣ ወንድሟ ወልደልዑልና ዘመዶቿ አንድ በአንድ ሞተው፣ እሷ ቤተመንግሥቱን ጥላ ወጥታ ምን ልትመስል እንደምትችል መገመት ተሳነው። ቁስቋም ግቢ ውስጥ ሲገባ ተሰምቶት የነበረው የመንፈስ መነቃቃት ከውስጡ ሊተን ቃጣው።

አስተናጋጁ፣ በሽናዋ አዳራሽ በስተቀኝ በኩል ወዳለው እንቁላል
ግንብ ወደሚወስደው ደረጃ ሲወጣ ተከትሎት ወጣ። ቁና ቁና ተነፈሰ።ጉልበቱ ላለበት። ዕድሜው እንደገፋ ቢያውቅም አሁን በቅጽበት ጨምሮ የሸመገለ መሰለው። ደረጃውን ሲጨርሱ፣ ላብ አሰመጠው።በፍጥነት ግንባሩን ያራሰውን ላብ በኩታው ተም ተም አደረገው። እጁ
ውስጥ ሊንቆረቆር የሚታገለውን ላብ እጀ ጠባቡ ላይ ጠራረገው። በርላይ ሲደርሱ ቆም ብሎ ኩታውን አስተካከለ።
ግራና ቀኝ ያደገደጉ አስተናጋጆች ቆመዋል። አስተናጋጁ እርሱን
ለእነሱ አስረክቦ ወደኋላ ሲቀር፣ አንደኛው እልፍኝ አስከልካይ እጅ
ነስቶ “ይግቡ” አለና ቀደም ብሎ ገብቶ እጅ ነስቶ፣ “እቴጌ እንግዳው መጥተዋል” ብሎ አስቀደመው

ጥላዬ፣ ልቡ ከታች ምላሱ ካላይ ጉሮሮውን የዘጉበት መሰለው።

ምንትዋብ፣ ቀይ ከፋይ የለበሰ ሰፊ ወንበር ላይ ተቀምጣለች።
የለበሰችው ረጅምና ባለቀይ ጥበብ ቀሚስ ላይ የደረበችው በወርቅ ያጌጠው ሰማያዊ ካባ ልዩ ድምቀት ሰጥቷታል። ሹሩባዋ ላይ ሸብ ያደረገችው ነጭ ሐር ሻሽ ግርማ ሞገስ አክሎላቷል።

ጥላዬ፣ ልቡ ቷ አለበት፤ ሰውነቱ ራደ። ግርማ ሞገሷ አስፈራው።

ለጥ ብሎ እጅ ነሣ። ያ በር ላይ ሲደርስ ሊያጥለቀልቀው የቃጣው
ላብ ፊቱ ላይ ክልብስ አለበት።

“ይቀመጡ” ብላ፣ ፊት ለፊቷ ያለ ወንበር በእጇ አሳየችው።

በእጁ ግንባሩን አሻሽና በጨርቅ የተጠቀለለውን ብራና ከብብቱ
ስር አውጥቶ፣ የተሸፈነበትን ጨርቅ ከላዩ ላይ አንስቶ እንደገና ለጥ ብሎ እጅ ነሥቶ፣ ሲሰጣት ምንትዋብ ተቀበለችው። ዕንጨት ላይ የተወጠረውን ብራና ስታየው ከዓመታት በፊት መነኩሴው ይዘውት መጥተው የነበረው ዓይነት የራሷ ምስል ነው።

“እርስዎን ደሞ ማን ላከዎት?” አለችው።

“ማነም አላከኝ። ዛሬስ ራሴ መጣሁ።”

“ሥሙር ማለት እርስዎ ነዎት?”

“እርስዎ አያስታውሱኝም። ግዝየውም ርቋል። የባላምባራስ ሁነኝ ልዥ ... ጥላዬ ነኝ።”

“ባላምባራስ ሁነኝ የቋራው ... የሳቸው ልዥ ... ጥላዬ?” ብላ የሷ
ያልመሰላት ድምፅ ከውስጧ ሲወጣ ተሰማት።

“አዎ... የቋራው ... ጥላዬ።”

ምንትዋብ ደነገጠች፤ ምላሷ ተቆለፈ። ከጥቂት ዝምታ በኋላ
እንደምንም ብላ፣ “ኧረ... በቁስቋሟ ተቀመጥ እንጂ!” አለችው፣ ወንበር እያመለከተችው።

ተቀመጠ።

ሁለቱም በዝምታ ተያዩ።

“ለካንስ አንተ ኑረኻል ካንዴም ሁለቴ ምስል ስትልክ የነበርኸው።
ለመሆኑ እስተዛሬ የት ነበርህ?”

ጥላዬ ፈገግ ብሎ ዝም አለ። ከመምጣቱ በፊት ሊላት በሐሳቡ
ያወጣው ያወረደው፣ ያለመውና የተመኘው ሁሉ ከጭንቅላቱ ብን
ብሎ ጠፍቷል። የቀረው ዝምታ ብቻ ብዙ ሐሳቦችን፣ በርካታ
ትዝታዎችንና ስሜቶችን የያዘ ከንግግር የላቀ ዝምታ። ለዚህ ቀን
ምን ዓይነት ቃላት ይበቁ ነበር? በዚያ ሁሉ የሐሳብ ውዥንብር ውስጥ አንድ ነገር ከአእምሮው አልወጣ አለ ንግሥታዊ ግርማ ሞገሷ።አፍዝ አደንግዝ የያዘው ይመስል አፉ ተሳሰረ። ስትናገር ደንገጥ ብሎ መስማት ጀመረ።

“ዛዲያ እስተዛሬ እንደዝኽ መምጣት እየቻልህ ስለምን ይኸን ያህል ግዝየ ቆየህ? እኔኮ ኸቋራ ኸወጣሁ ዠምሮ የት እንደደረስህም አላውቅም
ነበረ። ቤተመንግሥት እኮ እንዲህ ኸዘመድ እንደልብ ሚያገናኝ ቦታ
ማዶል ። እንደዝህ ስጎዳ ስለምን አልጠየቅኸኝም?”
👍8
#ምንዱባን


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ


ዣቬር ምልክት ሲሰጣቸው ብዙ መሣሪያ የያዙ ፖሊሶች ከክፍሉ
ውስጥ ገቡ፡፡ ሽፍቶቹን ያዝዋቸው: ክፍሉ ውስጥ በርቶ የነበረው ሻማ
አንድ ብቻ ስለነበር ክፍሉ ውስጥ ሰው ሲበዛ ጊዜ ብዙ ጥላ በማጥለሉ እየጨለመ ሄደ።

«ሁሉንም በብረት ሰንሰለት እጆቻቸውን እሰሩ» በማለት ዣቬር አዘዘ

«በሉ ወደዚህ ኑ» የሚል ቀጭን የሴት ድምፅ ተሰማ፡፡ ሚስስ
ቴናድዬ ነበረች፡፡ ባልዋ ከለበሰችው ሰፊ ካባ ስር ተሸሽጓል፡፡

ጠንቀቅ በሉ!» ስትል በመጮህ ተናገረች::

ሽፍቶቹ በሙሉ ያለማንገራገር እጆቻቸውን ሰጥተው ሲጠፈሩ
በማየትዋ «ፈሪ ሁሉ!» ስትል አጉረመረመች፡፡

ዣቬር ፈገግ አለ፡፡ ሚስስ ቴናድዬ ወደነበረችበት አመራ፡፡

«አይጠጉኝ፧ ከዚህ ቶሎ ቢወጡ ይሻላል» ስትል በማንጓጠጥ
ተናገረች::«እምቢ ካሉ ዋጋዎን ነው የምሰጥዎት::»

«ደፋር» አለ ዣቬር፡፡ «እመቤቴ እንደ ወንድ ጢም አብቅለዋል፤ እኔ
ደግሞ እንደ ሴት ጥፍር አሳድጌአለሁ» ሲል አሾፈባት።

ዣቬር እየተጠጋት መጣ፡፡ አጠገብዋ አንዳንዴ ልጆችዋ አንዳንዴም ራስዋ የምትቀመጥበት ድንጋይ ነበር፡፡ ዘልላ ሄዳ ያንን ድንጋይ አነሳችና
ዣቬርን ለመምታት ወረወረችው:: ዣቬር ጎንበስ በማለት ራሱን አዳነ፡፡ድንጋዩ ከግድግዳ ጋር ሄዶ ተላተመ:: የግድግዳው ቀለም ፈራርሶ ወለሉን ሞላው:: ድንጋዩ ሲመለስ እየተንከባለለ ከዣቬር እግር ስር ደረሰ።

ዣቬር ወደ ባልና ሚስቱ ሄደ:: በአንድ እጁ የሴትዮዋን፤ በሌላ እጁ የወንዱን ትከሻ ጨምድዶ ያዘ፡፡

«መሣሪያ አምጡ» ሲል ጮኸ፡፡

ወዲያው የብረት ማሠሪያ መጥቶ ሁለቱ ሰዎች ተቀፈደዱ። የራስዋና
የባልዋ እጆች መቀፍደዳቸውን ባየች ጊዜ «ወይኔ ልጆቼ» በማለት ከጮኸች ኋላ ከመሬት ላይ ተዘረረች፡፡

«በእድላቸው ያድጋሉ» ሲል አፌዘባት::

ሦስቱ ፊታቸውን በከሰል ያጠቆሩና ሦስቱ ፊታቸውን በጨርቅ የሸፈኑ ሽፍቶች እጃቸው ታስሮ ቆመዋል::

«ፊታችሁን እንደሽፈናችሁ ቆዩ» አለ ዣቬር፡-

እያንዳንዳቸውን በስም እየጠራ አንዱን «እንደምን አመሸህ»፣ ሌላውን ጤና ይስጥልኝ»፤ ሌላውን ደግሞ «ብርቱም አልሰነበትክ» በማለት
ሰላምታ ከሰጣቸው በኋላ ገና ከክፍሉ ሲገባ አንገቱን ደፍቶ ቆሞ
የነበረው እስረኛ ታወሰው::
«እስረኛውን ፍቱት» ሲል አዘዘ፡፡ «ከዚህ ቤት ደግሞ አንድ ሰው .
እንዳይወጣ?»
ይህን እንደተናገረ ከወንበሩ ላይ ሄዶ ቁጭ አለ፡፡ ከኪሱ ወረቀትና
ብዕር አውጥቶ ከጠረጴዛው ላይ አስቀመጠ፡፡ ቀና ብሉ «እያየ እስረኛውን ወደዚህ አምጡት» አለ፡፡
ፖሊሶቹ በዓይን ፈለጉት::
«ምነው፤ ምን ያንቀረፍፋችኋል? የት አለ ሰውዬው?» ሲል
ጮኸባቸው::
እስረኛው አባባ ሸበቶ ከዚያ አልነበረም፧ ወጥቶ ሄዷል፡፡
በሩ ላይ ፖሊስ ቆሞአል፡፡ የነበሩበት ክፍል ፎቅ ቤት ነው:: ታዲያ የት ሄደ? መስኮቱ አጠገብ ፖሊስ አልነበረም:: ትርምሱ ሲበዛ ቀደም ሲል እነቴናድዬ ለማምለጫ ባዘጋጁት የገመድ መሰላል አድርጎ ሾልኮአል። የፖሊሶቹ ዓይን አርፎ የነበረው ሽፍቶቹ ላይ ነበር፡፡

«ጋኔላም!» አለ ዣቬር በጥርሶቹ መሀል፤ «ጥሩ ምስክር ይሆነን
ነበር፡፡»

በሚቀጥለው ቀን ማታ አንድ ልጅ በኃይል እያፏጨና እየዘመረ
በመንገድ ላይ ሲጓዝ ከአንድ ነገር ጋር ይጋጫል፡፡ የተጋጨው ከሴት ጋር ነበር፡፡ ለመውደቅ እንደ መንገዳገድ ይልና ወደኋላ ዞር ብሎ ይመለከታል::

«ምነው! ትልቅ ውሻ መስሎኝ ነበር፡፡»

አሮጊትዋ ገንፍላ ከተኛችበት ብድግ አለች፡፡

«የተረገምክ» አለች ፤ «ከድካም ብዛት ሰውነቴ ባይከዳኝ ምን
እንደማደርግህ አውቅ ነበር፡፡»
ልጁ ኣሁን ትንሽ ራቅ ብሎ ነበር የቆመው፡፡

«ፕስ... ፕስ...» በማለት ካሽሟጠጣት በኋላ «በካልቾ ማቅመሴ አልተሳሳትኩም ፤ አበጀሁ፤ አበጀሁ» ሲል ተናገራት፡፡
ሴትየዋ ከተቀመጠችበት ብድግ አለች፡፡ ልጁ ሮጦ ሸሽ፡፡ እርሱን ለመያዝ ስትሮጥ መብራት ከነበረበት ደረሰች፡፡ የፊትዋ መሸብሸብና የወገብዋ መጉበጥ በግልጽ ታየ:: ልጁ ራቅ ብሎ ቆሞ አጤናት።

«እኔ የምወደው መልክ የለሽም» ብሎአት እያዜመ መንገዱን ቀጠለ፡፡ የቤት ቁጥር 50-52 ስለደረሰ ቆመ፡፡ በሩ መቆለፉን ሲያይ በእርግጫ መታው
አመታቱ የልጅ ሳይሆን የአዋቂ ነበር፡፡ ለካስ መንገድ ተኝታ
ያያት ሴት ትከተለው ኖሮ ከነበረበት ደረሰች::

ምንድነው ነገሩ እባካችሁ? ያ ከበሩ ላይ የቆመው ማነው? የእግዜር ያለህ በሩን እየሰበሩት ነው፤ ሌቦች ከቤቴ ሊገቡ ነው» ስትል ጮኸች፡፡

ልጁ በር መደብደቡን ቀጠለ፡፡ ሴትዬዋ ትንፋሽ አጥሮአት መተንፈስዋ በግድ ሆነ፡፡

«የአሁነስ ዘረፋ ዓይን በዓይን ሆነ እንዴ?» ብላ ከጠየቀች በኋላ ልጁን አተኩራ ስትመለከተው ማን እንደሆነ አወቀችው፡፡

«እንዴ! ያ ርኩስ፤ ያ ሰይጣን ነው እንዴ!»

«ጉድ ፈላ! አሮጊትዋ ናትና» አለ ልጁ ወደኋላ እየሸሸ፡፡ «ዘመዶቼን
መጠየቅ መጥቼ እኮ ነው::»

«ከዚህ ማንም የለም፤ አንተ ጋኔል» አለች ሴትዬዋ ጥላቻዋን ከፊትዋ ላይ ለማሳየት እየሞከረች::

«አይ ምን ይላሉ እርስዎ ደግሞ፤ ታዲያ አባቴ የት ሄደ?»

«ላ ፎርስ ከተባለ ሥፍራ፡፡»
«እናቴስ?»
«ሳን ላዛር፡፡»
«እሺ፧ እህቶቼስ?»
«ሌ ማደለኔ ሄደዋል፡፡»
ልጁ ጆሮውን አከክ እያደረገ ሴትዮዋን ቀና ብሎ አያት:: ሴትዮዋ እነቴናድዬ ይኖሩበት የነበረው ቤት ጠባቂ ነበረች፡፡

«እንዴት ይሆናል?» ሲል ራሱን ጠየቀ።

ከዚያም ፊቱን አዙሮ ቀደም ሲል ያዜመው የነበረውን ዜማ እያዜመ
መንገዱን ቀጠለ፡

ቅዱስ ዴኒስና ከፕሎሜ
ጎዳና ያስ ቤት

ኢፓኒን

ማሪየስ ባጠመደው ወጥመድ ፍርድ ሲገለባበጥ አየ:: የፖሊሱ
አዛዥ እስረኞቹን ይዞ ወጣ፡፡ ማሪየስም ከነበረበት ክፍል ወዲያው ሄደ፡፡ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ገደማ ሆኖአል፡፡ ወደ ጓደኛው ቤት አመራ፡፡ ከጓደኛ
ው ከኩርፌይራክ ቤት እንደደረሰም ከእርሱ ጋር ለማደር እንደመጣ ገለጸለት፡፡ ኩርፌይራክም ከመሬት ላይ ፍራሽ አነጠፈለት::

በሚቀጥለው ቀን በጠዋት ከቤቱ ተመልሶ ያለበትን ቤት ኪራይ
ክፍሎ ቤቱን ለቀቀ፡፡ እቃውን በጋሪ አስጭኖ ከኩርፌይራክ ሰፈር ሄደ፡፡

ዣቬር የልጁን ስም ረስቶ ከቤቱ አገኘው እንደሆነ ብሉ ቢመጣ
አጣው:: ማሪየስን ለማግኘት ብዙ ሞከረ ፤ ግን አልተሳካለትም:: ምናልባትም ልጁ የሚደርሰውን አደጋ ላለማየት ብሎ በመፍራት ከአገር የጠፋ መሰለው::

ማሪየስ ግን ባየውና በተሰጠው ፍርድ እጅግ ተረብሾ ነበር፡፡ ሁሉም
ነገር ጨለመበት:: የሚያየው የወደፊት ተስፋ ከፊቱ ራቀ፡፡ ልቡ የተሰቀለላት ልጅና አባትዋ ድንገት እንደ ብርሃን ብልጭታ ብቅ ብለው እንደገና ተሰወሩበት:: የእርሱ የወደፊት ተስፋ እነዚህ የማይታወቁ ፍጡሮች ነበሩ፡፡
ልቡ በልጅትዋ ፍቅር ታውሮአል፡፡ «ሂድና ፈልጋት» ብሎ ስሜቱን
ቢገፋፋውም ዓይኑ ማየት ስላልቻለ እንዲያው ዝም ብሎ መረበሽ፤ መጠበብ፤
መጨነቅ ሆነ፡፡ ቀቢጸ ተስፋ ተጠናወተው:: ተስፋ የተለየው ሕይወት ጨለማ ስለሆነ ፀሐይ ወጥቶ ሳለ ምድር ጨለመችበት:: ዓይኖቹ የፍቅር ረሃብተኞች ቢሆኑም ለማየት የፈለጉትን ባለማግኘታቸው ከማየት ተቆጠቡ::ጀሮዎቹ ለመስማት የፈለጉትን ድምፅ ባለመስማታቸው ሌላ ነገር ከመስማት አፈገፈጉ፡፡ ልቡ የፈለገውን ሳያገኝ ሲቀር የፍላጎቱ መጠንና ግለት እየጎላ
👍20
#ሳቤላ


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ

ሳምንቶች ሁለት ሦስቱ ሲያልፉ ጉዳዮች ደግሞ ከወደፊት ይልቅ የኋሊት
የሚሠግሡ መሰሉ የፍራንሲዝ ሌቪሰን ጉዳይ ፈቀቅ አልል አለ ባለ ዕዳዎቹም ፍንክች አላሉም ሰው እንዳያየው በሚስተር ካርላይል ዝግ ሠረገላ እየሆነ ሦስት ጊዜ ሌቪሰን ፖርክ ቢመላለስም ሰር ፒተርም እንደ ባለ ዕዳዎቹ ድርቅ አለ አንድ ጊዜ ለአንድ ዕዳ አንዲከፌል የሰጠውን ገንዘብ ለቪሰን ተቀብሎ ሳይከፍል ለራሱ
ማጥፋቱን ስለ ደረሰበት ፡ ሰር ፒተር በጣም ተናደደና ምንም ማድረግ እንደ ማይችል ነገረው " ሌቪሰን ወደ ነበረበት ወዶ አውሮፓ ከመመለስ በቀር ሌላ ተስፋ
እንደሌለው ተረዳ ።

ሰር ፒተርም የሱ ብጤ ከንቱዎች የተጠራቁሙበት እዚያው ስለሆነ፤ከሁሉ
ፍራንሲዝ ሌቪሰን የተሻለ የሚስማማው ወደዚያው ቢመለስ መሆኑን ነገረው
ሊሔድ ሲነሣ ሰር ፒተር የአንድ መቶ ፓውንድ ኖት አውጥቶ ወደሱ ሲመጣ ላወጣው ወጭ መተኪያ ብሎ ሰጠው ። አበሉንም እንደማያቋርጥበትም ገለጸለት ።

“ ዛሬ ከሰር ፒተር ጋር እንዴት ሆናችሁ ? አለው ሚስተር ካርላይል ማታ
ከራት ላይ እንደ ነበሩ ።

“ መቸም ምንም አይል” አለው ፍራንሲዝ ሌቪሰን ' “ ከሱ ጋር ምንም ያህል
ነገር አልፈጸምኩም " እነዚህ የዱሮ ሰዎች ጉዳዮችን ቶሎ አይቆርጡም " ጊዜ መውሰድ ደስ ይላቸዋል "

ከኢስት ሊን ለመውጣት ስለ አልፈለገና እውነቱን ቢናገር ደግሞ የማይሔድ
በት ምክንያት ስላልነበረው ያልሆነ መልስ ነገረው ።
በመሻሻል ፈንታ በፍጥነት እየባሰ የሔደው ደግሞ የሳቤላ ቅናት ነበር ። ባርባራን በየዕለቱ ከሚስተር ካርላይል ጋር ስትገናኝ ታያለች ካፒቴን ሌቪሰን ነገሩን እየተከታተለ የተመለከተውን እያጋነነ እየተነተነ ይነግራታል ። ሳቤላ በዚህ ጊዜ ራሷንና በዙሪያዋ ያሉትን ሁሉ ትጠላ ጀመር በባሏ ላይ አደገኛ የሆነ ጥላቻ ጠነሰሰች ጥንስሱም እየፈላ መጣ ካፒቴን ሌቪሰን ከሰር ፒተር ዘንድ በሔደበት
ቀን በሠረገላ ሆና በዌስት ሊን ስታልፍ ባሏና ባርባራ በጣም የጠበቀ ጫወታ እንደያዙ አገኘቻቸው " እነሱ ግን ሠረገላዋ ባጠገባቸው ዐልፎ ሲሔድ ልብ ብለው አላዩትም ።

በበነጋው ጧት የጆስቲስ ሔር ቤተሰብ ቁርስ ላይ እንደ ተቀመጡ ፖስተኛኛውን ሲመጣ አዩትና ባርባራ በመስኮቱ ዘልቃ አንድ ደብዳቤ ተቀበለችው "

“ ከማን የተላከ ነው ?” አላት አድራሻው ለሱ ባይሆንም የማንኛውንም ደብዳቤ ይዘት ለማወቅ ጉጉት የነበረው አባቷ ።

“ ከአን ነው ... አባባ” አለችው ደብዳቤውን ከጐኗ በማስቀመጥ "

“ ታዲያ ለምንና ምን ብላ እንደ ጻፈችው ከፍተሽ አታይውም ?”

“ እከፍተዋላሁ " ለእማማ ሻይ ልቀዳላት ብዬ ነው „”

ባርባራ ሻዩን ለናቷ ሰጥታ ፖስታውን ስትከፍተው፡አንዲት ትንሽ የታጠፈች
ወረቀት ከጭኗ ላይ ወደቀች : ደግነቱ ግን አባቷ ከቡናው ስኒ እንዳቀረቀረ ስለ ነበር ወረቀቲቱን አላያትም ሚስዝ ሔር ግን አይታ ነበር "

“ባርባራ አንድ ነገር ጣልሽ"

ባርባራም ወረቀቲቱን አይታ ስለ ነበር ቀስ አድርጋ ሳትታይ ያዘቻት ።
“ አንቺ የኔ ልጅ ኧረ አንድ ነገር ከጭንሽ ላይ ወይቀ ”
“አንቺ እናትሽን አትሰሚያትም እንዴ?

"ምንድነው የጣልሽው? አላት አባቷ"

ባርባራ ፊቷ በድንጋጤ እንደ ቀላ ከተቀመጠችበት ተነሣችና ልብሷን አራገፈች “ምንም ነገር የለም... አባባ ” አለችው " ከዚያ ከቦታዋ ተመልሳ ከተቀመጠች በኋላ እናቷን ዝም እንድትል በዐይኗ ገረመመቻት "

ባርባራ የእኅቷን ደብዳቤ አንብባ ማየት የሚፈልግ እንዲያየው ጠረጴዛው
ላይ አኖረችው ።

አባትየው ቶሎ አነሣና ከተመለከተው በኋላ እያልጐመጐመ ከጠረጴዛው ላይ
ጣለው "

“ ዱሮውንም ከአን ደብዳቤ ምንም አይገኝም ። እስኪ አንድ ስኒ ቡና ጨምሪልኝ ' ባርባራ ። ”

በመጨረሻ ዳኛው ቁርሱን በልቶ ካበቃ በኋላ ወደ አትክልቱ ቦታ ለመንሸራሸር ወጣ ። ሚስዝ ሔር ባርባራን ቀና ብላ አየቻት "

“ ልጄ ... ምን አድርጌሽ ነው እንደዚያ ተቆጥተሽ ያየሺኝ ? ከጭንሽ ላይ
የወደቀውስ ምን ነበር ? እኔማ ከአን ደብዳቤ የወደቀ መስሎኝ ነው ።

“ እሱስ ነው ፤ከአን ፖስታ ነው የወደቀው ። አባባ ግን ሁሉን ነገር እኔ ልየው እያለ መጠየቅ ይወዳል አን ለማንም ሳይሆን ለኔ ብቻ በተለየ ወረቀት አብራ ትጽፍልኛለች " ምናልባት ከዚህ አብራ ከአንድ ፖስታ ከምትልካቸው ትናንሽ ደብዳ
ቤዎች አንዱ ሊሆን ይችላል

“ ባርባራ አባትሽ ላንቺ የሚጻፉትን ደብዳቤዎች ማየት አይችልም የምት
ይው ደስ አይለኝም ።”

“ የምትይው እውነት ነው ... እማማ ። እሱ ግን ትንሽ ልብ ቢኖረው እኔና አንም ስለየግላችን የመጻጻፍ ነጻነት ሊኖረን እንደሚገባ ማወቅ አለበት " እሱ በሆነው ባልሆነው ጥልቅ ማለት አያስፈልገውም ነበር

ባርባራ ወድቃ የነበረችውን ወረቀት አውጥታ “እማማ ... ስለ ሪቻርድ
ነው” አለቻትና አነበበችላት
“ ከሪቻርድ ቀንም ስምም የሌለው ማስታወሻ ደረሰኝ እኔም በጽሑፉ ነው ያወቅሁት አሁን የተወለደችው ጨረቃ ስትደምቅ ስለሚመጣ ከአፅዱ እንድትጠብቂው ሲመጣ ምልክት ያሳይሻል” ይላል የአን ወረቀት "

ሚስዝ ሔር ፊቷን ለጥቂት ደቂቃዎች ሸፍና ቆየች።

ግን እኮ ... እማማ ለመምጣት ሙከራው ለሱ አደገኛ ነው'' አለቻት

“ በሕይወት መኖሩን ማወቅሳ ! ስለ አደጋው እስካሁን የጠበቀው አምላክ
ይጠብቀዋል ይልቅስ ልጄ
እሷን ወረቀት አጥፊያት ''

« በፊት አርኪባልድ ካርላይል ያንብበወና ኋላ አጠፋታለሁ "

“ እንግዲያውስ ዛሬ ፌልግሽ አሳይው።እሱን ካላጠፋሽ ልቤ አያርፍልም"

ባርባራ ሚስተር ካርላይልን ፍለጋ ወደ ዌስትሊን ብትዘልቅ ወደ ሊንበራ መጓዙን ሚስተር ዲል ነግራት ከዚያ ወደ ቤቷ ተመልሳ ሲያልፍ እንድታገኘው ከበር
ስትጠብቅ አመሸች " ሲቀር ጊዜ በሌላ በኩል አድርጐ ወደ ቤት ዐልፎ ይሆናል
በማለት ወደ ኢስት ሊን ሔደች " እዚያ ስትደርስ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተደወለ

ሚስተር ካርላይል አሁን ነጻ ነው ወይስ ሥራ ይዟል ?

«ሚስተር ካርላይል
አልገቡም እሜቴ ና ሚስ ካርላይልም ራት እየጠበቋቸው ነው ” አለና በሩን የከፈተው አሽከር እንድትገባ ጠየቃት " እሷ ግን ገብታ ለማነጋገር አላሰኛትም ነበርና ተመልሳ ሔደች "

በመስኮት ቁማ የባሏን መምጣት ስትጠብቅ የነበረችው ሳቤላ ባርባራን ወደ ቤት ስትመጣና ተመልሳ ስትወጣ አየቻት ወዲያው ደግሞ በሩን የከፈተላት አሽከር ሳቤላ ወደ ነበረችበት ክፍል ገባ
“ ያቺ ሚስ ሔር አይደለችም እንዴ ? አለችው " ናት . .
እመቤቴ ጌቶችን ነበር የፈለገች " እኔ እንኳን የእርስዎን መኖር ነግሬአት ነበር ግን ለመግባት አልፈለገችም :

ሳቤላ ምንም ሳትመልስ ዝም አለች " ፍራንሲዝ ሌቪሰን በአስተዛዛኝነት
መልኩ ሲያያት አየችው " እጆቿን እስኪያማት ድረስ እያፋተገች ወደ መስኮቱ ተመለሰች "

ባርባራ እያዘገመች ቁልቁል ስትወርድ ሚስተር ካርላይል ቶሎ ቶሎ እየተራመደ! አሻቅቦ ወደ ቤቱ ሲመጣ ተገናኙና ሲጨባበጡ ሳቤላ አየቻቸው "

“ ከቢሮህ መጥቸ አጣሁህ ፤ ይኸውልህ ይህ ወረቀት ከሪቻርድ ደረሰኝ "ብላ ያችን ቁራጭ ወረቀት ሰጠችው "

ሚስተር ካርላይል ወረቀቲቱን ተቀብሎ ሲያነብ ባርባራ ተጠግታ ስትመለከተው እነሱን ደግሞ በቅናት የተንገገበችው ሳቤላና በተንኮል የተመረዘው ካፕቴን ሌቪሰን በመስኮት ዘልቀው ከሩቅ ይመለከቷቸው ነበር ኮርኒሊያ ካርላይል
አየቻቸው
👍18