#ዜና #ዘኦርቶዶክስ #ተዋህዶ #ዕለታዊ
ቅዱስ ሲኖዶስ ገራሚ ገራሚ ውሳኔዎች ማሳለፉን ቀጥሏል። በትላንትናው ዕለት ካሥተላለፋቸው ውሳኔዎችም
#1ኛ ) በትላንትና እለት የዘገብነውን የሻሸመኔ ምዕመናን ፦ ለመንፈሳዊ አገልግሎት እንዲያመቻቸው ያቀረቡትን የአዲስ አህጉረ ስብከት መቋቋም ፥ ተወያይቶ አፅድቆላቿል ። አዲሱ
የሻሸመኔ ሐገረ ስብከትም የምዕራብ አርሲ ሐገረ ስብከት ተብሎ
ተሰይሟል ። ሊቀ ጳጳስም በዚሁ ምልአተ ጉባኤ ይሾምለታል ።
#2ኛ ) የአዊ ምዕመናን እንባ መድኃኔአለም ያየው ይመስላል ።
ከአባ ማርቆስ ቀጥሎ ሁለተኛው ባለ ቅባት አባ ቶማስ በምዕመናኑ ላይ ያደረሱት የአስተዳደር በደል በአስቸኳይ
እንዲጣራ ኮሚቴ ተቋቁሟል ። ቀጣዩ ተነሺ እንደሚሆኑ ይጠበቃል ።
#3ኛ ) የከፋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጽኡ አቡነ ሕዝቅኤል ስራቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ፥ ከባድ ማሳሰቢያ ተሰጥቷቿል ።
# 4ኛ ) የአዲስ አበባ አህጉረ ስብከትን ለመንፈሳዊ አገልግሎት እና ለሐብት ቁጥጥር በሚያመች መልኩ ለ4 አህጉረ ስብከቶች የመክፈሉን ጉዳይ ተወያይቶ ውሳኔ ሊሰጥበት ቀጠሮ
አስቀምጧል ።
#5ኛ ) ባለፈው ሳምንት እንደገለጽነው በመላው ሐገሪቱ ሰላም ለማስጠበቅ ፥ ብጥብጥን ለማስወገድ ፥ የብጽአን አባቶች
#የሰላም #ሐዋሪያዊ #ተልዕኮ በቡድን በቡድን ሆኖ ስምሪት ለማድረግ ከስምምነት ተደርሷል ።
#6ኛ ) በምዕራብ ሐረርጌ ሐገረ ስብከት በታላቁ የአሰቦት ገዳም "የኦነግ " ታጣቂዎች ነን ባዮች በመነኮሳት ላይ ጉዳት እያደረሱ መሆኑን ተጠቁሟል ። የኦሮሚያ እና የፌደራል.መንግስት ባስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ መጠየቁ ።
#7ኛ ) የኢየሩሳሌም የዴር ሱልጣን ገዳም ፥ በግብጽ መነኮሳት
የማይገባቸውን እርስት የመጠየቅ ብጥብጥ ፥ የእስራኤል ፖሊስ
ጣልቃ ገብቶ ፥ ቀሳጢያንን የግብጽ መነኮሳት ማሰሩ። እርሱንም ተከትሎ የCoptic ቤተክርስቲያን ተጽኖ ለመፍጠር ዘመቻ መጀመሯ ።
#በቀጣይ #ቀናት #ውሎ
#1ኛ ) ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተክርስቲያኒቱን አንድነት ለማናጋት
ዘረኝነትን ወደ ቅድስት ቤተክርስቲያን ለማስገባት ለሚፈልጉ ቡድኖች የማያዳግም መልስ ይሰጣል ተብሎ ይጠብቃል
#2ኛ ) በቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት እና በጣና ገዳማት ላይ በተጋረጠው አደጋ ዙሪያ አስቸኳይ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል
#3ኛ ) የኢየሩሳሌምን የቅድስት ቤተክርስቲያን እርስቶች በሚገባ የሚያስጠብቅ የማያዳግም ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል ።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ቅዱስ ሲኖዶስ ገራሚ ገራሚ ውሳኔዎች ማሳለፉን ቀጥሏል። በትላንትናው ዕለት ካሥተላለፋቸው ውሳኔዎችም
#1ኛ ) በትላንትና እለት የዘገብነውን የሻሸመኔ ምዕመናን ፦ ለመንፈሳዊ አገልግሎት እንዲያመቻቸው ያቀረቡትን የአዲስ አህጉረ ስብከት መቋቋም ፥ ተወያይቶ አፅድቆላቿል ። አዲሱ
የሻሸመኔ ሐገረ ስብከትም የምዕራብ አርሲ ሐገረ ስብከት ተብሎ
ተሰይሟል ። ሊቀ ጳጳስም በዚሁ ምልአተ ጉባኤ ይሾምለታል ።
#2ኛ ) የአዊ ምዕመናን እንባ መድኃኔአለም ያየው ይመስላል ።
ከአባ ማርቆስ ቀጥሎ ሁለተኛው ባለ ቅባት አባ ቶማስ በምዕመናኑ ላይ ያደረሱት የአስተዳደር በደል በአስቸኳይ
እንዲጣራ ኮሚቴ ተቋቁሟል ። ቀጣዩ ተነሺ እንደሚሆኑ ይጠበቃል ።
#3ኛ ) የከፋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጽኡ አቡነ ሕዝቅኤል ስራቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ፥ ከባድ ማሳሰቢያ ተሰጥቷቿል ።
# 4ኛ ) የአዲስ አበባ አህጉረ ስብከትን ለመንፈሳዊ አገልግሎት እና ለሐብት ቁጥጥር በሚያመች መልኩ ለ4 አህጉረ ስብከቶች የመክፈሉን ጉዳይ ተወያይቶ ውሳኔ ሊሰጥበት ቀጠሮ
አስቀምጧል ።
#5ኛ ) ባለፈው ሳምንት እንደገለጽነው በመላው ሐገሪቱ ሰላም ለማስጠበቅ ፥ ብጥብጥን ለማስወገድ ፥ የብጽአን አባቶች
#የሰላም #ሐዋሪያዊ #ተልዕኮ በቡድን በቡድን ሆኖ ስምሪት ለማድረግ ከስምምነት ተደርሷል ።
#6ኛ ) በምዕራብ ሐረርጌ ሐገረ ስብከት በታላቁ የአሰቦት ገዳም "የኦነግ " ታጣቂዎች ነን ባዮች በመነኮሳት ላይ ጉዳት እያደረሱ መሆኑን ተጠቁሟል ። የኦሮሚያ እና የፌደራል.መንግስት ባስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ መጠየቁ ።
#7ኛ ) የኢየሩሳሌም የዴር ሱልጣን ገዳም ፥ በግብጽ መነኮሳት
የማይገባቸውን እርስት የመጠየቅ ብጥብጥ ፥ የእስራኤል ፖሊስ
ጣልቃ ገብቶ ፥ ቀሳጢያንን የግብጽ መነኮሳት ማሰሩ። እርሱንም ተከትሎ የCoptic ቤተክርስቲያን ተጽኖ ለመፍጠር ዘመቻ መጀመሯ ።
#በቀጣይ #ቀናት #ውሎ
#1ኛ ) ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተክርስቲያኒቱን አንድነት ለማናጋት
ዘረኝነትን ወደ ቅድስት ቤተክርስቲያን ለማስገባት ለሚፈልጉ ቡድኖች የማያዳግም መልስ ይሰጣል ተብሎ ይጠብቃል
#2ኛ ) በቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት እና በጣና ገዳማት ላይ በተጋረጠው አደጋ ዙሪያ አስቸኳይ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል
#3ኛ ) የኢየሩሳሌምን የቅድስት ቤተክርስቲያን እርስቶች በሚገባ የሚያስጠብቅ የማያዳግም ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል ።
@And_Haymanot
@And_Haymanot