✞ ✞ ✞ ✞ ነገረ ክርስቶስ ✞ ✞ ✞ ✞
(((((((((((ካለፈው የቀጠለ))))))))))))
#ስለ_እነርሱ_ሊያማልድ {ዕብ.፯፥፳፬}
@And_Haymanot
.....እርሱ ግን ለዘለዓለም የሚኖር ስለሆነ የማይለወጥ ክህነት አለው ፤ ስለ እነርሱ ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል ። ዕብ.፯፥፳፬
ስለ እነርሱ ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራል።
👉 ይህን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በመውሰድ አንዳንዶች ጌታችንን አሁንም አማላጅ አድርገው ሲናገሩ ይሰማሉ።
ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነቱ ይህ አይደለም። ጌታችን በመዋዕለ ሥጋዌው (ሰው ሆኖ በምድር ላይ) የማስታረቅን ሥራ ከራሱ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ፈጽሟል። ይህ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ያለ እውነታ ነው።
አሁንም አማላጅ ነው ማለት ግን ትልቅ ክህደት ነው። ለምሳሌ አምላካችን ጌታችን መድኀኒታችን ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌው ተርቧል ተጠምቷል ክብር ይግባውና በምድር ስለ ተራበ አሁንም ረሃብተኛ ስለ ተጠማ አሁንም ጥማተኛ ነው አንለውም። እንዲሁም በሥጋ የማስታረቅን ሥራ ስለ ሠራ አሁን አማላጅ አንለውም።
በመሠረቱ ይህንን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ከላይ ከዕብ.፯፥፲፩ ጀምሮ በደንብ ላስተዋለው ሰው አነጋገሩ በጣም ግልጽ ነው። ሐዋርያው የኦሪትና የሐዲስ ኪዳኑን ክህነት እያነጻጸረ ነው የጻፈው በሌዊ ክህነት ፍጹምነት እንዳልተገኘ የእነ አሮንም ሹመት እንዳለፈችና እንደ መልከ ጼዴቅ ሌላ ካህን ማስፈለጉን በዚህ ምክንያት በመልከ ጼዴቅ አምሳል ሌላ ካህን ከነገደ ይሁዳ መምጣቱንና ይህም በሊቀ ካህናችን በኢየሱስ ክርስቶስ መፈጸሙን ይናገራል።
ዕብ.፯፥፲፯ ላይም " እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘለዓለም ካህን አንተ ነህ " ሲል ያስምቀጠዋል ኦሪት ደካማ ስርዓት ስለነበረች ግዳጅዋን አልፈጸመችም ፍጹም የሰው ልጅ ድኅነት አልተገኘባትም ነበር ። ካህኑ ለኃጢአት ማስተስረያ እንስሳትን መስዋዕት አድርጎ የሚረጨው ደም የአዳምን የውርስ ኃጢዓት ሊያነጻ በፍጹም አልቻለም ነበርና በእሷ በኦሪት ፈንታ ወደ እግዚአብሔር የምንቀርብበት ተስፋ ገብቷል እያለ ነው ቅዱስ ጳውሎስ የሚያብራራው ።
ከታች ዝቅ ብሎ ዕብ.፯፥፳፬ ጀምሮ " እርሱ ግን ለዘለዓለም የሚኖር ስለሆነ የማይለወጥ ክህነት አለው ስለ እነርሱ ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል እንደዚህ ያለ ሊቀ ካህናት ይገባልና እርሱም እንደነዚያ(እንደ ኦሪቶቹ ) ሊቃነ ካህናት አስቀድሞ ስለ ራሱ ኃጢዓት በኋላም ስለ ሕዝቡ ኃጢዓት ዕለት ዕለት መስዋዕትን ሊያቀርብ አያስፈልገውም ራሱን ባቀረበ ጊዜ ይህን አንድ ጊዜ ፈጽሞ አድርጓልና " ( ዕብ.፯፥፳፯ ) ለነገሩ ይህ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል መናፍቃኑ ለምንፍቅና ትምህርታቸው እንዲመቻቸው " ስለ እነርሱ ሊያማልድ ዘወትር ይኖራል " ብለው ያጣሙት እንጂ ቆየት ብሎ በታተመው መጽሐፍ ቅዱስ ( 1960 ) ላይ ግን እንደዚህ አይደለም የተቀመጠው ትክክለኛው ቃል
"ክህነቱ አይሻርም ዘወትር በእርሱ በኩል ወደ እግዚአብሔር የሚቀርቡትን ሊያድናቸው ይቻለዋል ለዘለዓለም ሕያው ነውና ያስታርቃቸዋል" ነው የሚለው ዕብ.፯፥፳፬-፳፭ ይህስ ቢሆን ምን ማለት ነው ?
👉 ጌታችን ራሱ መስዋዕት አቅራቢ ራሱ መስዋዕት ራሱ መስዋዕት ተቀባይ ሆኖ አንድ ጊዜ ብቻ ራሱን ባቀረበው ለዘለዓለም ኃጢዓታችንን ያስተሰርይልናል።
አንድ ጊዜ በመስቀል ላይ ያፈሰሰው ደም ያለፈውንም ሆነ የሚመጣውን ትውልድ ለዘለዓለም ያስታርቀዋል እንጂ እንደ ኦሪቱ ስርዓት ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው " ዕለት ዕለት መስዋዕትን ሊያቀርብ አያስፈልገውም " ራሱን ባቀረበ ጊዜ ይህን አንድ ጊዜ ፈጽሞ አድርጓልና ስለዚህ እኛም ፍጹም ድኅነትን ያገኘነው አንድ ጊዜ በሠራልን የክህነት ሥራ ነው በመስቀሉ ደም ሰላም አድርጎ በምድራዊ ወይም በሰማያት ያሉትን ሁሉ ለራሱ እንዲያስታርቅ ፈቅዷል ቆላ.፩፥፲፱ ተብሎ እንደ ተጻፈ።
ይህን የሠራልን የክህነቱ ሥራው ነው ዘወትር ሲያስታርቀን የሚኖረው አሁንም ያማልደናል ካልን ግን ክርስቶስ ዕለት ዕለት ኃጢዓት በሠራን ቁጥር መሞት አለበት ማለት ነው። ምክንያቱም ዓለም ፍጹም ድኅነት ያገኘችው በእርሱ ሞት ብቻ ነውና ወይም በሌላ አገላለፅ እንዲህ ማለት
ለምሳሌ ቅዱስ ጴጥሮስ አንካሳውን ሰውዬ " በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሳና ተመላለሰ " ሲለው ተነሥቶ ተመላልሷል ጴጥሮስ " ተነሳና ተመላለሰ " ብሎ ሲናገር አንድ አንካሳ ብቻ ዳነ እንጂ ለዚህ አንካሳ የተነገረው ቃል በጴጥሮስ እጅ ለተፈወሱ ሌሎች ብዙ አንካሶች አልሠራም ማለትም ለሁሉም አንካሶች እንደገና ለእያንዳንዳቸው " ተነሳና ተመላለሰ " ተብሎ መነገር አለበት።
ይህ የሚያሳየው በፍጡራን አንድ ጊዜ የተነገረው ቃል ሥራ የሚሠራው አንድ ጊዜ ብቻ ነው ማለት ነው።
የፈጣሪ ቃል ግን እንደዚህ አይደለም ፈጣሪ አንድ ጊዜ የተናገረው ቃል ለዘለዓለም ጸንቶ ነው የሚኖረው
ለምሳሌ እግዚአብሔር ዓለሙን ሲፈጥር ይሁን ይሁን እያለ ነው የፈጠረው ስለዚህ ፍጥረት ሁሉ ይኸው አንድ ጊዜ በተናገረው ቃል እስከ ዕለተ ምፅዓት ሁኑ እንዳላቸው ሆነው ተገኝተዋል "ቀንና ሌሊት ይለዩ " ዘፍ.፩፥፲፬ ብሎ አንድ ጊዜ ብቻ በተናገረው ቃሉ ይኸው ቀንና ሌሊት እየተፈራረቁ ነው ይህም በፈጣሪ አንድ ጊዜ የተነገረው ቃል ዘለዓለማዊ ሥራ እንደሚሠራ ነው የሚያሳየን።
እናም " ለዘለዓለም ሕያው ነውና ያስታርቃቸዋል " ወይም መናፍቃኑ እንደሚሉት " ሲያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራል " ተብሎ ቢነገርም እንኳን ትርጉሙ ከዚህ ከላይ ካየነው የተለየ አይደለም " ራሱን መስዋዕት አድርጎ ባቀረበ ጊዜ ፈጽሞ አድርጓልና " እንደተባለው ጌታችንም " የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው " ብሎ ማስታረቅን ያጠቃለለበት ያው አንዴ የተናገረው የምልጃ ቃል ክርስቶስ ደጋግሞ ሳያማልድ የሚመጣውንም ሁሉንም ትውልድ የሚያስታርቅ ነው።
ተፈጸመ ያለውም ይህንኑ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታረቀበትን ሥራ ነው ያው አንድ ጊዜ በመስቀል ላይ የተነገረ ቃል የአምላክ ቃል ነውና ለዘወትር ይጸናል።
ልክ እግዚአብሔር " ቀንና ሌሊት ይለዩ " ብሎ አንዴ በተናገረው ቃል መሠረት ቀንና ሌሊት እየተፈራረቁ እስከ ዕለተ ምፅዓት ድረስ እንደሚቆዩ ማለት ነው። ከዚህ ውጪ ግን ክርስቶስ ያን በሞቱ አንድ ጊዜ የፈጸመውን የማዳን የማስታረቅ ሥራ አሁንም ይሠራል ብሎ ማመን ከኑፋቄም በላይ ክህደት ነው የእግዚአብሔርንም ፍቅሩን አለማወቅም እኛም አልዳንም ክርስቶስም እንደ ገና መጥቶ መሞት አለበት ማለት ነው።
👉 በአጠቃላይ ሐዋርያት የክርስቶስን ስም ከምልጃ ጋር ቢጠቅሱም እንኳን እስካሁን ባየነው መልኩ ነው መታየት ያለበት ከዚህ ውጪ ግን ራሱ ጌታችን ለሐዋርያት በዚያች ቀን ( ከትንሳኤ በኋላ)
ዮሐ.፲፮፥፳፮ በስሜ ትለምናላችሁ እኔም ስለ እናንተ አብን አለምንም ብሏቸው እያለ " አይ አንተ ከትንሳኤ በኋላ ታማልዳለህ " ብለው አይቃወሙትም " ብትወዱኝ ትዕዛዜን ጠብቁ " ያላቸውን አምላክ ጠንቅቀው ያውቁታል ደግሞስ ቅዱስ ጳውሎስ
፪ቆሮ.፭፥፲፮-፲፰ " ክርስቶስ ከትንሳኤው በኋላ በሥጋው ወራት እንደምናውቀው ከእንግዲህ ወዲያ እኛም ሐዋርያቱ ብንሆን በሥጋ እንዳወቅነው አናውቀውም "በማለት ነው የጻፈው እንዲያውም እዚያው ላይ ቁጥር ፲፱ ጀምሮ " በእኛም የማስታረቅን ቃል አኖረ የማያስታርቅን ሥልጣን ለእኛ ሰጠን እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማለድ ዕወቁ
(((((((((((ካለፈው የቀጠለ))))))))))))
#ስለ_እነርሱ_ሊያማልድ {ዕብ.፯፥፳፬}
@And_Haymanot
.....እርሱ ግን ለዘለዓለም የሚኖር ስለሆነ የማይለወጥ ክህነት አለው ፤ ስለ እነርሱ ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል ። ዕብ.፯፥፳፬
ስለ እነርሱ ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራል።
👉 ይህን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በመውሰድ አንዳንዶች ጌታችንን አሁንም አማላጅ አድርገው ሲናገሩ ይሰማሉ።
ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነቱ ይህ አይደለም። ጌታችን በመዋዕለ ሥጋዌው (ሰው ሆኖ በምድር ላይ) የማስታረቅን ሥራ ከራሱ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ፈጽሟል። ይህ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ያለ እውነታ ነው።
አሁንም አማላጅ ነው ማለት ግን ትልቅ ክህደት ነው። ለምሳሌ አምላካችን ጌታችን መድኀኒታችን ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌው ተርቧል ተጠምቷል ክብር ይግባውና በምድር ስለ ተራበ አሁንም ረሃብተኛ ስለ ተጠማ አሁንም ጥማተኛ ነው አንለውም። እንዲሁም በሥጋ የማስታረቅን ሥራ ስለ ሠራ አሁን አማላጅ አንለውም።
በመሠረቱ ይህንን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ከላይ ከዕብ.፯፥፲፩ ጀምሮ በደንብ ላስተዋለው ሰው አነጋገሩ በጣም ግልጽ ነው። ሐዋርያው የኦሪትና የሐዲስ ኪዳኑን ክህነት እያነጻጸረ ነው የጻፈው በሌዊ ክህነት ፍጹምነት እንዳልተገኘ የእነ አሮንም ሹመት እንዳለፈችና እንደ መልከ ጼዴቅ ሌላ ካህን ማስፈለጉን በዚህ ምክንያት በመልከ ጼዴቅ አምሳል ሌላ ካህን ከነገደ ይሁዳ መምጣቱንና ይህም በሊቀ ካህናችን በኢየሱስ ክርስቶስ መፈጸሙን ይናገራል።
ዕብ.፯፥፲፯ ላይም " እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘለዓለም ካህን አንተ ነህ " ሲል ያስምቀጠዋል ኦሪት ደካማ ስርዓት ስለነበረች ግዳጅዋን አልፈጸመችም ፍጹም የሰው ልጅ ድኅነት አልተገኘባትም ነበር ። ካህኑ ለኃጢአት ማስተስረያ እንስሳትን መስዋዕት አድርጎ የሚረጨው ደም የአዳምን የውርስ ኃጢዓት ሊያነጻ በፍጹም አልቻለም ነበርና በእሷ በኦሪት ፈንታ ወደ እግዚአብሔር የምንቀርብበት ተስፋ ገብቷል እያለ ነው ቅዱስ ጳውሎስ የሚያብራራው ።
ከታች ዝቅ ብሎ ዕብ.፯፥፳፬ ጀምሮ " እርሱ ግን ለዘለዓለም የሚኖር ስለሆነ የማይለወጥ ክህነት አለው ስለ እነርሱ ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል እንደዚህ ያለ ሊቀ ካህናት ይገባልና እርሱም እንደነዚያ(እንደ ኦሪቶቹ ) ሊቃነ ካህናት አስቀድሞ ስለ ራሱ ኃጢዓት በኋላም ስለ ሕዝቡ ኃጢዓት ዕለት ዕለት መስዋዕትን ሊያቀርብ አያስፈልገውም ራሱን ባቀረበ ጊዜ ይህን አንድ ጊዜ ፈጽሞ አድርጓልና " ( ዕብ.፯፥፳፯ ) ለነገሩ ይህ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል መናፍቃኑ ለምንፍቅና ትምህርታቸው እንዲመቻቸው " ስለ እነርሱ ሊያማልድ ዘወትር ይኖራል " ብለው ያጣሙት እንጂ ቆየት ብሎ በታተመው መጽሐፍ ቅዱስ ( 1960 ) ላይ ግን እንደዚህ አይደለም የተቀመጠው ትክክለኛው ቃል
"ክህነቱ አይሻርም ዘወትር በእርሱ በኩል ወደ እግዚአብሔር የሚቀርቡትን ሊያድናቸው ይቻለዋል ለዘለዓለም ሕያው ነውና ያስታርቃቸዋል" ነው የሚለው ዕብ.፯፥፳፬-፳፭ ይህስ ቢሆን ምን ማለት ነው ?
👉 ጌታችን ራሱ መስዋዕት አቅራቢ ራሱ መስዋዕት ራሱ መስዋዕት ተቀባይ ሆኖ አንድ ጊዜ ብቻ ራሱን ባቀረበው ለዘለዓለም ኃጢዓታችንን ያስተሰርይልናል።
አንድ ጊዜ በመስቀል ላይ ያፈሰሰው ደም ያለፈውንም ሆነ የሚመጣውን ትውልድ ለዘለዓለም ያስታርቀዋል እንጂ እንደ ኦሪቱ ስርዓት ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው " ዕለት ዕለት መስዋዕትን ሊያቀርብ አያስፈልገውም " ራሱን ባቀረበ ጊዜ ይህን አንድ ጊዜ ፈጽሞ አድርጓልና ስለዚህ እኛም ፍጹም ድኅነትን ያገኘነው አንድ ጊዜ በሠራልን የክህነት ሥራ ነው በመስቀሉ ደም ሰላም አድርጎ በምድራዊ ወይም በሰማያት ያሉትን ሁሉ ለራሱ እንዲያስታርቅ ፈቅዷል ቆላ.፩፥፲፱ ተብሎ እንደ ተጻፈ።
ይህን የሠራልን የክህነቱ ሥራው ነው ዘወትር ሲያስታርቀን የሚኖረው አሁንም ያማልደናል ካልን ግን ክርስቶስ ዕለት ዕለት ኃጢዓት በሠራን ቁጥር መሞት አለበት ማለት ነው። ምክንያቱም ዓለም ፍጹም ድኅነት ያገኘችው በእርሱ ሞት ብቻ ነውና ወይም በሌላ አገላለፅ እንዲህ ማለት
ለምሳሌ ቅዱስ ጴጥሮስ አንካሳውን ሰውዬ " በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሳና ተመላለሰ " ሲለው ተነሥቶ ተመላልሷል ጴጥሮስ " ተነሳና ተመላለሰ " ብሎ ሲናገር አንድ አንካሳ ብቻ ዳነ እንጂ ለዚህ አንካሳ የተነገረው ቃል በጴጥሮስ እጅ ለተፈወሱ ሌሎች ብዙ አንካሶች አልሠራም ማለትም ለሁሉም አንካሶች እንደገና ለእያንዳንዳቸው " ተነሳና ተመላለሰ " ተብሎ መነገር አለበት።
ይህ የሚያሳየው በፍጡራን አንድ ጊዜ የተነገረው ቃል ሥራ የሚሠራው አንድ ጊዜ ብቻ ነው ማለት ነው።
የፈጣሪ ቃል ግን እንደዚህ አይደለም ፈጣሪ አንድ ጊዜ የተናገረው ቃል ለዘለዓለም ጸንቶ ነው የሚኖረው
ለምሳሌ እግዚአብሔር ዓለሙን ሲፈጥር ይሁን ይሁን እያለ ነው የፈጠረው ስለዚህ ፍጥረት ሁሉ ይኸው አንድ ጊዜ በተናገረው ቃል እስከ ዕለተ ምፅዓት ሁኑ እንዳላቸው ሆነው ተገኝተዋል "ቀንና ሌሊት ይለዩ " ዘፍ.፩፥፲፬ ብሎ አንድ ጊዜ ብቻ በተናገረው ቃሉ ይኸው ቀንና ሌሊት እየተፈራረቁ ነው ይህም በፈጣሪ አንድ ጊዜ የተነገረው ቃል ዘለዓለማዊ ሥራ እንደሚሠራ ነው የሚያሳየን።
እናም " ለዘለዓለም ሕያው ነውና ያስታርቃቸዋል " ወይም መናፍቃኑ እንደሚሉት " ሲያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራል " ተብሎ ቢነገርም እንኳን ትርጉሙ ከዚህ ከላይ ካየነው የተለየ አይደለም " ራሱን መስዋዕት አድርጎ ባቀረበ ጊዜ ፈጽሞ አድርጓልና " እንደተባለው ጌታችንም " የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው " ብሎ ማስታረቅን ያጠቃለለበት ያው አንዴ የተናገረው የምልጃ ቃል ክርስቶስ ደጋግሞ ሳያማልድ የሚመጣውንም ሁሉንም ትውልድ የሚያስታርቅ ነው።
ተፈጸመ ያለውም ይህንኑ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታረቀበትን ሥራ ነው ያው አንድ ጊዜ በመስቀል ላይ የተነገረ ቃል የአምላክ ቃል ነውና ለዘወትር ይጸናል።
ልክ እግዚአብሔር " ቀንና ሌሊት ይለዩ " ብሎ አንዴ በተናገረው ቃል መሠረት ቀንና ሌሊት እየተፈራረቁ እስከ ዕለተ ምፅዓት ድረስ እንደሚቆዩ ማለት ነው። ከዚህ ውጪ ግን ክርስቶስ ያን በሞቱ አንድ ጊዜ የፈጸመውን የማዳን የማስታረቅ ሥራ አሁንም ይሠራል ብሎ ማመን ከኑፋቄም በላይ ክህደት ነው የእግዚአብሔርንም ፍቅሩን አለማወቅም እኛም አልዳንም ክርስቶስም እንደ ገና መጥቶ መሞት አለበት ማለት ነው።
👉 በአጠቃላይ ሐዋርያት የክርስቶስን ስም ከምልጃ ጋር ቢጠቅሱም እንኳን እስካሁን ባየነው መልኩ ነው መታየት ያለበት ከዚህ ውጪ ግን ራሱ ጌታችን ለሐዋርያት በዚያች ቀን ( ከትንሳኤ በኋላ)
ዮሐ.፲፮፥፳፮ በስሜ ትለምናላችሁ እኔም ስለ እናንተ አብን አለምንም ብሏቸው እያለ " አይ አንተ ከትንሳኤ በኋላ ታማልዳለህ " ብለው አይቃወሙትም " ብትወዱኝ ትዕዛዜን ጠብቁ " ያላቸውን አምላክ ጠንቅቀው ያውቁታል ደግሞስ ቅዱስ ጳውሎስ
፪ቆሮ.፭፥፲፮-፲፰ " ክርስቶስ ከትንሳኤው በኋላ በሥጋው ወራት እንደምናውቀው ከእንግዲህ ወዲያ እኛም ሐዋርያቱ ብንሆን በሥጋ እንዳወቅነው አናውቀውም "በማለት ነው የጻፈው እንዲያውም እዚያው ላይ ቁጥር ፲፱ ጀምሮ " በእኛም የማስታረቅን ቃል አኖረ የማያስታርቅን ሥልጣን ለእኛ ሰጠን እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማለድ ዕወቁ