Forwarded from ፩ ሃይማኖት
እምነትህን በሥራ አሳይ
@And_Haymanot
ያዕ 2፥14-26
14 ወንድሞቼ ሆይ፥ እምነት አለኝ የሚል፥ ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል? እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን?
15 ወንድም ወይም እኅት ራቁታቸውን ቢሆኑ የዕለት ምግብንም ቢያጡ፥
16 ከእናንተ አንዱም። በደኅና ሂዱ፥ እሳት ሙቁ፥ ጥገቡም ቢላቸው ለሰውነት ግን የሚያስፈልጉትን ባትሰጡአቸው ምን ይጠቅማቸዋል?
17 እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው።
18 ነገር ግን አንድ ሰው። አንተ እምነት አለህ እኔም ሥራ አለኝ፤ እምነትህን ከሥራህ ለይተህ አሳየኝ፥ እኔም እምነቴን በሥራዬ አሳይሃለሁ ይላል።
19 እግዚአብሔር አንድ እንደ ሆነ አንተ ታምናለህ፤ መልካም ታደርጋለህ፤ አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል።
20 አንተ ከንቱ ሰው፥ እምነት ከሥራ ተለይቶ የሞተ መሆኑን ልታውቅ ትወዳለህን?
21 አባታችን አብርሃም ልጁን ይስሐቅን በመሠዊያው ባቀረበ ጊዜ በሥራ የጸደቀ አልነበረምን?
22 እምነት ከሥራው ጋር አብሮ ያደርግ እንደ ነበረ፥ በሥራም እምነት እንደ ተፈጸመ ትመለከታለህን?
23 መጽሐፍም። አብርሃምም እግዚአብሔርን አመነ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት ያለው ተፈጸመ፤ የእግዚአብሔርም ወዳጅ ተባለ።
24 ሰው በእምነት ብቻ ሳይሆን በሥራ እንዲጸድቅ ታያላችሁ።
25 እንደዚሁም ጋለሞታይቱ ረዓብ ደግሞ መልእክተኞቹን ተቀብላ በሌላ መንገድ በሰደደቻቸው ጊዜ በሥራ አልጸደቀችምን?
26 ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደ ሆነ እንዲሁ ደግሞ ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ ነው።
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
@And_Haymanot @And_Haymanot
@And_Haymanot @And_Haymanot
@And_Haymanot @And_Haymanot
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
@And_Haymanot
ያዕ 2፥14-26
14 ወንድሞቼ ሆይ፥ እምነት አለኝ የሚል፥ ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል? እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን?
15 ወንድም ወይም እኅት ራቁታቸውን ቢሆኑ የዕለት ምግብንም ቢያጡ፥
16 ከእናንተ አንዱም። በደኅና ሂዱ፥ እሳት ሙቁ፥ ጥገቡም ቢላቸው ለሰውነት ግን የሚያስፈልጉትን ባትሰጡአቸው ምን ይጠቅማቸዋል?
17 እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው።
18 ነገር ግን አንድ ሰው። አንተ እምነት አለህ እኔም ሥራ አለኝ፤ እምነትህን ከሥራህ ለይተህ አሳየኝ፥ እኔም እምነቴን በሥራዬ አሳይሃለሁ ይላል።
19 እግዚአብሔር አንድ እንደ ሆነ አንተ ታምናለህ፤ መልካም ታደርጋለህ፤ አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል።
20 አንተ ከንቱ ሰው፥ እምነት ከሥራ ተለይቶ የሞተ መሆኑን ልታውቅ ትወዳለህን?
21 አባታችን አብርሃም ልጁን ይስሐቅን በመሠዊያው ባቀረበ ጊዜ በሥራ የጸደቀ አልነበረምን?
22 እምነት ከሥራው ጋር አብሮ ያደርግ እንደ ነበረ፥ በሥራም እምነት እንደ ተፈጸመ ትመለከታለህን?
23 መጽሐፍም። አብርሃምም እግዚአብሔርን አመነ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት ያለው ተፈጸመ፤ የእግዚአብሔርም ወዳጅ ተባለ።
24 ሰው በእምነት ብቻ ሳይሆን በሥራ እንዲጸድቅ ታያላችሁ።
25 እንደዚሁም ጋለሞታይቱ ረዓብ ደግሞ መልእክተኞቹን ተቀብላ በሌላ መንገድ በሰደደቻቸው ጊዜ በሥራ አልጸደቀችምን?
26 ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደ ሆነ እንዲሁ ደግሞ ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ ነው።
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
@And_Haymanot @And_Haymanot
@And_Haymanot @And_Haymanot
@And_Haymanot @And_Haymanot
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
በምስለ ፍቁር ወልዳ ሥዕል አድህኖ ከእመቤታችን በስተግራ የሚሳለው የማን ሥዕለ አድህኖ ነው
Anonymous Quiz
11%
ሀ, ቅዱስ ፋኑኤል
62%
ለ,ቅዱስ ገብርኤል
20%
ሐ, ቅዱስ ሚካኤል
8%
መ, ቅዱስ ሩፋኤል
✞በኢያሪኮ መንገድ✞
በኢያሪኮ መንገድ ጌታ እንተ ስታልፍ
ግፍያ ሆኖ ሳለ ስደነቃቀፍ
የዳዊት ልጅ ማረኝ ብዬ ተማጸነኩኝ
ዓይኔንም ፈወስከኝ ዛሬ ማየት ቻልኩኝ
አንተን እንዳላይህ ቁመቴ አጠረብኝ
ከፊትህ እየሮጥኩኝ እዛፍ ላይ ወጣሁኝ
ጌታ ሆይ ጠራኸኝ ዘኬዎስ ሆይ አልከኝ
በቤቴ ልትገባ ፈቃድህ ሆነልኝ(፪)
ሐሴትም ሆነልኝ በጣምም ደስ አለኝ
አንተን በእንግድነት በቤቴ ተቀበልኩኝ
ኃጢአቴን ሁል በአንተ ፊት ጥያለሁ
ሐብቴን እከፍል ዘንድ እንዲገባ አውቃለሁ
ሐብቴን እሰጥህ ዘንድ እንዲገባ አውቃለሁ
የክፋትን ገንዘብ መሰብሰብን ትቼ
አንተን ልከተልህ ሁሉን ረስቼ
ኑሮዬንም ባርከው የሕይወት ዘመኔን
መርጫለሁ አንተን በቤትህ መኖሬን
መርጫለሁ አንተን በቤትህ ማደጌን
ዘማሪ
ቀሲስ ወንድወሰን በቀለ
ሉቃ፲፱፥፩-፲
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@And_Haymanot
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
በኢያሪኮ መንገድ ጌታ እንተ ስታልፍ
ግፍያ ሆኖ ሳለ ስደነቃቀፍ
የዳዊት ልጅ ማረኝ ብዬ ተማጸነኩኝ
ዓይኔንም ፈወስከኝ ዛሬ ማየት ቻልኩኝ
አንተን እንዳላይህ ቁመቴ አጠረብኝ
ከፊትህ እየሮጥኩኝ እዛፍ ላይ ወጣሁኝ
ጌታ ሆይ ጠራኸኝ ዘኬዎስ ሆይ አልከኝ
በቤቴ ልትገባ ፈቃድህ ሆነልኝ(፪)
ሐሴትም ሆነልኝ በጣምም ደስ አለኝ
አንተን በእንግድነት በቤቴ ተቀበልኩኝ
ኃጢአቴን ሁል በአንተ ፊት ጥያለሁ
ሐብቴን እከፍል ዘንድ እንዲገባ አውቃለሁ
ሐብቴን እሰጥህ ዘንድ እንዲገባ አውቃለሁ
የክፋትን ገንዘብ መሰብሰብን ትቼ
አንተን ልከተልህ ሁሉን ረስቼ
ኑሮዬንም ባርከው የሕይወት ዘመኔን
መርጫለሁ አንተን በቤትህ መኖሬን
መርጫለሁ አንተን በቤትህ ማደጌን
ዘማሪ
ቀሲስ ወንድወሰን በቀለ
ሉቃ፲፱፥፩-፲
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@And_Haymanot
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
፩ ሃይማኖት የሁላችን ቻናል
እንደተለመደው በቅርቡ ጠንከር ባሉ ርእሶች ለመመለስ በዝግጅት ላይ ነው ከጎናችን በጸሎት እና በሃሳብ ላላችሁ ሁሉ ምስጋናችን የላቀ ነውና አሁንም ቀጥሉበት ለማለት እንወዳለን @And_Haymanot_bot ላይ
ሃሳባችሁን አድርሱ ቦቱ ላይ መፈሳዊ ጥያቄ የምጠይቁን ከብዛት አንጻር ነውና በዚህ አጋጣሚ ታገሱን ለማለት እንወዳለን
ኦርቶዶክስ መልስ አላት።
@And_Haymaot
እንደተለመደው በቅርቡ ጠንከር ባሉ ርእሶች ለመመለስ በዝግጅት ላይ ነው ከጎናችን በጸሎት እና በሃሳብ ላላችሁ ሁሉ ምስጋናችን የላቀ ነውና አሁንም ቀጥሉበት ለማለት እንወዳለን @And_Haymanot_bot ላይ
ሃሳባችሁን አድርሱ ቦቱ ላይ መፈሳዊ ጥያቄ የምጠይቁን ከብዛት አንጻር ነውና በዚህ አጋጣሚ ታገሱን ለማለት እንወዳለን
ኦርቶዶክስ መልስ አላት።
@And_Haymaot
ስለ ንጉሥ ቴዎድሮስ መምጣት
የመጀመርያው ክፍል
ጥንተ ነገሩ "ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፥ በዚያን ጊዜም
መጨረሻው ይመጣል።" ማቴ.24፥14 የሚለው ገጸ ንባብ ሲኾን የመንግሥት ወንጌል ማለት ጌትነቱን የምትናገር ወንጌል በ፬ቱ ማዕዘን ትነገራለች። በእስላም ቤት ስንኳ ሳይቀር ትገኛለች
የሚል አንድምታ አለው። ትርጓሜውም ይኼን በታሪክ ሲያትተው፦ በሀገራችን ቴዎድሮስ በሀገራቸው ዮሐንስ የሚባል ይነግሣል፤ የእኛም ሂዶ ያም መጥቶ በእስክንድርያ ሦስት ቀን ይዋጋሉ።
አራቱ ሊቃነ ጳጳሳት የክርስቲያን ደም ለምን ይፈሳል? መሥዋዕት ሰውተን በመሥዋዕቱ ምልክት የታየለት ሃይማኖት ይጽና ይሏቸዋል። ኹሉም በያሉበት መሥዋዕት ያቀርባሉ። የእስክንድርያ
ሊቀ ጳጳሳት በሰዋው "አነ ውእቱ ክርስቶስ - እኔ ክርስቶስ ነኝ።" ብሎ በርግብ አምሳል ወርዶ ይመሰክራል። ከዚህ በኋላ በሃይማኖት አንድ ይኾናሉ፤ በግቢ ይገናኛሉ። እንደዚህ የሚል ከምን አለ ቢሉ ከገድለ ፊቅጦር ከራእየ ሲኖዳ።" [የማቴዎስ
ወንጌል 24፥14 አንድምታ]
➻ ይኽ ኾኖ ሳለ "ቴዎድሮስ" የሚለውን ስምም ለኦርቶዶክሳዊት የተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊያስተዋውቁ የሚሞክሩ አሉ። በቅዱሳት መጻሕፍት ከብዙ ጥቂቱን እንምዘዝ፦ የወርቃማ ዘመን ወርቃማ ደራሲ ጻድቅ ባሕታዊ አባ
ጊዮርጊስ ዘጋሥጫን ዘርዐ ያዕቆብ በድርሰቱ ሲመስለው ቴዎድሮስ ደግሞ በሕይወት መስሎታል። "ወበአሐቲ መዋዕል ተስዕሎ አሐዱ መስፍን ዘስሙ ቴዎድሮስ ዘይሰመይ ካዕበ ሊቀ ሐራ በእንተ ሃይማኖት ርትዕት ወደረሰ ሎቱ መጽሐፍ ዘይሰመይ ፍካሬ ሃይማኖት።" [ገድለ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ] እንዲል።
➾ ዐጼ ቴዎድሮስ አባ ጊዮርጊስን ከወኅኒ ቤት አውጥቶ በጥንቱ ቦታ አስቀምጦታል። ቴዎድሮስ የሚባል ሰማዕትም አለ። "የምሥራቃዊው
ቴዎድሮስና የሠራዊት አለቃ ቴዎድሮስ የገላውዴዎስ የፊቅጦር በረከት እንዲያርፍብኝ ለምኝልኝ።" [መጽሐፈ አርጋኖን ዘእሑድ ምዕራፍ ፰፥፮] ዳግመኛም "ሮማዊ ቴዎድሮስ የሚባል የሮም ሰው ነበር።" [ድርሳነ ገብርኤል፤ ስንክሳር ዘወርኀ መስከረም 28] እንዳለ። ቴዎድሮስ የሚባልም ኤጲስ ቆጶስ አለ። "ኃጥእት ስለምትኾን ስለዚች ስለ እኅታቸው ያጥን ዘንድ የቸርነት መገኛ ወደምትኾን እመቤታችንም ይለምንላት ዘንድ ቴዎድሮስ ለሚባል
ኤጲስ ቆጶስ ሰጡት።" [ተኣምረ ማርያም፤ ተኣምር 53፥43]
የሰማዕቷ የቅድስት አርሴማ አባትም ቴዎድሮስ ነው የሚባለው።
ቴዎድሮስ የሚባል መነኵሴም አለ። "በአንዲት ቀንም ስሙ ቴዎድሮስ የሚባል መነኵሴ ከእርሷ ዘንድ እንግድነት አደረ።" [ስንክሳር ዘወርኀ መስከረም ፲] ቴዎድሮስ የሚባል ሊቀ ካህናትም አለ። "የዚህ አባት ወላጅ
አባቱ በእስክንድርያ አገር ሊቀ ካህናት ነው፤ ስሙም ቴዎድሮስ ነው።" [ስንክሳር ዘወርኀ ኅዳር 29]
የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት የነበረ ቴዎድሮስ የተባለም አባት ነበረ። "በዚችም ዕለት የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት ቴዎድሮስ አረፈ።"[ስንክሳር ዘወርኀ የካቲት ፯]
በቁሙ ቴዎድሮስ የሚባል ንጉሥም ይንገስ ወይም ቴዎድሮስ ማለት የስሙ ትርጓሜ ውኂብ እምእግዚአብሔር|
ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠ| ማለት ነውና ከእግዚአብሔር ዘንድ የኾነ ለኢትዮጵያ የሰላም ጊዜ ይመጣ ይኾን? ብሎ በንስሓ በውዳሴ ማርያም፥ በመዝሙረ ዳዊት ደጊም በጸሎት ዘወትር
ተግተን ዘመነ ፍቅር ወሰላም እንዲመጣ ብንጸና እውነትም ቴዎድሮስ|ዘመነ ሰላም| ይመጣል። ድርጊት ትንቢትን
ይስበዋልና።
➸ ኹለት ዓይነት ትንቢት አለ፦...
፩. በነገሮች የሚወሰን
፪. በነገሮች የማይወሰን የግድ የሚፈጸም ትንቢት(Unconditio
nal Prophecy)
....
........ይቀጥላል
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
የመጀመርያው ክፍል
ጥንተ ነገሩ "ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፥ በዚያን ጊዜም
መጨረሻው ይመጣል።" ማቴ.24፥14 የሚለው ገጸ ንባብ ሲኾን የመንግሥት ወንጌል ማለት ጌትነቱን የምትናገር ወንጌል በ፬ቱ ማዕዘን ትነገራለች። በእስላም ቤት ስንኳ ሳይቀር ትገኛለች
የሚል አንድምታ አለው። ትርጓሜውም ይኼን በታሪክ ሲያትተው፦ በሀገራችን ቴዎድሮስ በሀገራቸው ዮሐንስ የሚባል ይነግሣል፤ የእኛም ሂዶ ያም መጥቶ በእስክንድርያ ሦስት ቀን ይዋጋሉ።
አራቱ ሊቃነ ጳጳሳት የክርስቲያን ደም ለምን ይፈሳል? መሥዋዕት ሰውተን በመሥዋዕቱ ምልክት የታየለት ሃይማኖት ይጽና ይሏቸዋል። ኹሉም በያሉበት መሥዋዕት ያቀርባሉ። የእስክንድርያ
ሊቀ ጳጳሳት በሰዋው "አነ ውእቱ ክርስቶስ - እኔ ክርስቶስ ነኝ።" ብሎ በርግብ አምሳል ወርዶ ይመሰክራል። ከዚህ በኋላ በሃይማኖት አንድ ይኾናሉ፤ በግቢ ይገናኛሉ። እንደዚህ የሚል ከምን አለ ቢሉ ከገድለ ፊቅጦር ከራእየ ሲኖዳ።" [የማቴዎስ
ወንጌል 24፥14 አንድምታ]
➻ ይኽ ኾኖ ሳለ "ቴዎድሮስ" የሚለውን ስምም ለኦርቶዶክሳዊት የተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊያስተዋውቁ የሚሞክሩ አሉ። በቅዱሳት መጻሕፍት ከብዙ ጥቂቱን እንምዘዝ፦ የወርቃማ ዘመን ወርቃማ ደራሲ ጻድቅ ባሕታዊ አባ
ጊዮርጊስ ዘጋሥጫን ዘርዐ ያዕቆብ በድርሰቱ ሲመስለው ቴዎድሮስ ደግሞ በሕይወት መስሎታል። "ወበአሐቲ መዋዕል ተስዕሎ አሐዱ መስፍን ዘስሙ ቴዎድሮስ ዘይሰመይ ካዕበ ሊቀ ሐራ በእንተ ሃይማኖት ርትዕት ወደረሰ ሎቱ መጽሐፍ ዘይሰመይ ፍካሬ ሃይማኖት።" [ገድለ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ] እንዲል።
➾ ዐጼ ቴዎድሮስ አባ ጊዮርጊስን ከወኅኒ ቤት አውጥቶ በጥንቱ ቦታ አስቀምጦታል። ቴዎድሮስ የሚባል ሰማዕትም አለ። "የምሥራቃዊው
ቴዎድሮስና የሠራዊት አለቃ ቴዎድሮስ የገላውዴዎስ የፊቅጦር በረከት እንዲያርፍብኝ ለምኝልኝ።" [መጽሐፈ አርጋኖን ዘእሑድ ምዕራፍ ፰፥፮] ዳግመኛም "ሮማዊ ቴዎድሮስ የሚባል የሮም ሰው ነበር።" [ድርሳነ ገብርኤል፤ ስንክሳር ዘወርኀ መስከረም 28] እንዳለ። ቴዎድሮስ የሚባልም ኤጲስ ቆጶስ አለ። "ኃጥእት ስለምትኾን ስለዚች ስለ እኅታቸው ያጥን ዘንድ የቸርነት መገኛ ወደምትኾን እመቤታችንም ይለምንላት ዘንድ ቴዎድሮስ ለሚባል
ኤጲስ ቆጶስ ሰጡት።" [ተኣምረ ማርያም፤ ተኣምር 53፥43]
የሰማዕቷ የቅድስት አርሴማ አባትም ቴዎድሮስ ነው የሚባለው።
ቴዎድሮስ የሚባል መነኵሴም አለ። "በአንዲት ቀንም ስሙ ቴዎድሮስ የሚባል መነኵሴ ከእርሷ ዘንድ እንግድነት አደረ።" [ስንክሳር ዘወርኀ መስከረም ፲] ቴዎድሮስ የሚባል ሊቀ ካህናትም አለ። "የዚህ አባት ወላጅ
አባቱ በእስክንድርያ አገር ሊቀ ካህናት ነው፤ ስሙም ቴዎድሮስ ነው።" [ስንክሳር ዘወርኀ ኅዳር 29]
የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት የነበረ ቴዎድሮስ የተባለም አባት ነበረ። "በዚችም ዕለት የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት ቴዎድሮስ አረፈ።"[ስንክሳር ዘወርኀ የካቲት ፯]
በቁሙ ቴዎድሮስ የሚባል ንጉሥም ይንገስ ወይም ቴዎድሮስ ማለት የስሙ ትርጓሜ ውኂብ እምእግዚአብሔር|
ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠ| ማለት ነውና ከእግዚአብሔር ዘንድ የኾነ ለኢትዮጵያ የሰላም ጊዜ ይመጣ ይኾን? ብሎ በንስሓ በውዳሴ ማርያም፥ በመዝሙረ ዳዊት ደጊም በጸሎት ዘወትር
ተግተን ዘመነ ፍቅር ወሰላም እንዲመጣ ብንጸና እውነትም ቴዎድሮስ|ዘመነ ሰላም| ይመጣል። ድርጊት ትንቢትን
ይስበዋልና።
➸ ኹለት ዓይነት ትንቢት አለ፦...
፩. በነገሮች የሚወሰን
፪. በነገሮች የማይወሰን የግድ የሚፈጸም ትንቢት(Unconditio
nal Prophecy)
....
........ይቀጥላል
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ስለ ንጉሥ ቴዎድሮስ መምጣት
፨፨፨፨፨፨፨፨
.........የቀጠለ
➸ ኹለት ዓይነት ትንቢት አለ፦
፩. በነገሮች የሚወሰን ትንቢት(Conditional Prophecy)፦
ለምሳሌ፦ "እሺ ብትሉ ለእኔም ብትታዘዙ፥ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤ እምቢ ብትሉ ግን ብታምፁም፥ ሰይፍ ይበላችኋል፤ የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሮአልና።" ኢሳ.1፥19-20 የሚለው ተፈጻሚ የሚኾነው እኛ ተኣዛዚ ኾነን እሺ ካልን ብቻ በረከተ ምድር እንበላለን። ካልኾንን በረከተ ምድርን አንበላም።
የሚወሰነው በምንሰጠው ግብረ መልስ ነው። "አባትህንና እናትህን አክብር፤ እግዚአብሔር አምላክህ በሚሰጥህ ምድር ዕድሜህ እንዲረዝም።" ዘጸ. 20፥12 "ዕድሜ የሚረዝመው" እናት አባታችን ካከበርን ነው፤ ካላከበርን ያጥራል። ተፈጻሚነቱ የሚወሰነው በእኛ ድርጊት ነው።
፪. በነገሮች የማይወሰን የግድ የሚፈጸም ትንቢት(Unconditional Prophecy) ደግሞ አለ። ለምሳሌ፦ ምጽአት ክርስቶስ እኛ ጻድቅም ኾንን ኃጥእ የማይቀር የግድ የሚፈጸም ትንቢት ነው። ሊቁ አባ ገ/ኪዳን እንዳስተማሩንም ምጽኣተ ቴዎድሮስ
በተመለከተ የጥንት ብራና መጽሐፍ የሚለው "እኛ በንስሓ ከተመለስን ነው" ደገኛ ንጉሥ በሀገራችን የሚነግሠው
ብለዋል። ይኼ ማለት አምላከ ቅዱሳን አምላካችን እግዚአብሔር በፍጹም ንስሓ መመለሳችንን አይቶ ቴዎድሮስ
የሚባል ንጉሥ ሊነግሥ ይችላል አሊያም እንደ ስሙ ትርጓሜ ዘመነ ሰላም|ቴዎድሮስን| ያሳየናል ማለት ነው። በአጭር ቃል እንደ አባ ገ/ኪዳን ገለጻ ምጽኣተ ቴዎድሮስ በነገሮች የሚወሰን
ትንቢት(Conditional Prophecy) ውስጥ የሚመደብ ነው።
➻ ይኼን የመጻሕፍት አስረጅ አክብረን ሳንነቅፍ ዳሩ ግን የቴዎድሮስ መምጣት ብርቅም ድንቅም አርጎ አለመናገር
ይገባል። ከድኅነተ ሥጋ ድኅነተ ነፍስ ይበልጣልና።
➾ በጠበል ከሥጋ በሽታችን ብንፈወስ መልካም ነው፤ባንፈወስም ንስሓ ገብተን ሕገ ወንጌለን ብንፈጽም በምሕረተ ክርስቶስ እንድናለን ብለን ተስፋ እናደርጋለን። ነገር ግን በጠበል ከሥጋ በሽታ ተፈውሰን ዳሩ ግን ንስሓ ካልገባንና ሕገ ወንጌል ካለፈጸምን አንድንም። የሥጋ በሽታ ፈውስ ለምድራዊ ኑሯችን እንጂ ለሰማያዊ ሕይወታችን ዋስትና አይኾንም። ከምጽኣተ ቴዎድሮስ ይልቅ ምጽኣተ ክርስቶስን ነቅተን፥ ተገተን በእጅጉ መዘጋጀት ይጠቅማል። ምክንያቱም፦
፩. ንጉሥ ቴዎድሮስ ፍጡር፥ መድኅነ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን የነገሥት ንጉሥ ፈጣሪ ነው።
፪. በቁሙ ቴዎድሮስ የሚባል ንጉሥ ላይመጣ ይችላል። መድኅነ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ግን እሱ ባወቀ ቀን መምጣቱ ግድ ነው። "ዳግመኛም በሕያዋንና በሙታን ሊፈርድ ይመጣል።"[ጸሎተ ሃይማኖት] እንዲል።
፫. ቴዎድሮስ ቢመጣ ጊዜያዊ ዘመነ ሰላም ሊያመጣ ሊነግስ ነው፤ ጌታችን ሲመጣ ግን ዘላለማዊ ሰላም ሊሰጠን ለጻድቃን ሊፈርድላቸው ለኃጥኣን ሊፈርድባቸው ነው።
፬. ቴዎድሮስ ቢመጣ ዓለምን ሊያሳልፍ አይደለም። መድኅነ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለምን ሊያሳልፍ ነው።
፭. ቴዎድሮስ ቢመጣ ጊዜያዊ ንጉሠ ኀላፊት ምድር ቢኾን ነው፤ መድኅነ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ዘላለማዊ ንጉሠ ሰማይ ወምድር ነው። "እነሆም፥ ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ።" ማቴ.12፥41 እንዲል።
➻ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራችን |የማርያም መቀነት| ሰንደቅ ዓላማችን ዓለምን ዳግም በንፍር ውሀ እንደማያጠፋት ለኖኅ ቃል ኪዳን መግባቱን የሚያሳይ ዓርማችን እንጂ ከዘላለም የሞት ፍርድ ግን አያድንም። በኦርቶዶክሳዊት የተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አራት ነገሮች አሉ።
፩. ፈጽሞ እንዳንፈጽማቸው የተከለከሉ አሉ። ለምሳሌ፦ ኃጢኣትና ክፉ እኵያት ኹሉም።
፪. እንድንፈጽማቸው የታዘዙም አሉ። ለአብነትም ሕገ ወንጌልን
መፈጸም።
፫. ተፈቅደው ግን የማይበረታቱ አሉ። ለምሳሌ፦ የሚያሰክር መጠጥ ፈጽሞ አይከለክልም፥ ግና የሚያሰክር መጠጥ
አይበረታታም። የማይጠጣ የተሻለ አደረገ እንጂ።
፫. ብንፈጽማቸው፥ ባንፈጽማቸውም የማያስተቹ አሉ። ለምሳሌ፦ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ነጠላ፥ አልባሳት ብንለብስም ባንለብስም ከወቀሳ ከከሰሳ አያደርስም። አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ ዓላማ
እንጂ ዶግማም ሥርዐትም አይደለማ። ለዚህም ነው 'ንጉሥ ቴዎድሮስ ይመጣል በሚል አረንጓዴ ቢጫ ቀይ በሩ ላይ ያደረገ ይድናል' የሚል ፈጠራ እብለት ነው የምንል። የኢትዮጵያ ሰንደቅ
ዓለማ እንጂ በራሱ ሃይማኖት አይደለማ። ሰንደቅ ዓላማችን ክብራችን ነው እናክብረው ማለት እየተቻለ Code እየሰጡ፥ በሥዕለ ቅዱሳን ተሸፍነው፥ 'ባንዲራ ሰቅላችሁ ጠብቁ ድኅነታችሁ ነው' ማለቱ ለምን አስፈለገ? ትንቢተ ኢሳይያስ ላይ "ደሴቶች ሆይ፥ ስሙኝ፥ እናንተም በሩቅ ያላችሁ አሕዛብ፥ አድምጡ፤ እግዚአብሔር ከማኅፀን
ጠርቶኛል፥ ከእናቴም ሆድ ጀምሮ ስሜን አንሥቶአል፤" ኢሳ.49፥1የሚለውኮ ስለ ቴዎድሮስ ሳይኾን ደሴት በውሀ፥ ውሀ
በደሴት እንዲከበብ ሰባ ዘመን በመከራ የተከበባችሁ እስራኤል ስሙኝ። አሕዛብ አድምጡኝ፤ በእናቴ ማኅፀን ስሜን ኢሳይያስ አለኝ፤ አንድም ከእናቴ ማኅፀን ከተወለድሁ በኋላ ኢሳይያስ ብሎ
ስም አወጣልኝ ለማለት ነው። "አፌንም እንደ ተሳለ ሰይፍ አድርጎአል፥" ሲል አንደበቴ እንደ ተሳለ ምላጭ አደረገው ማለት ኦሪትን እንዳስተምር አደረገኝ ሲለን እንጂ ስለ ምጽኣተ ቴዎድሮስ
አይናገርም። "የተቀላቀለ እንዳይኾን እንለይ" እንዳለ ደራሲ [ቅዳሴ ማርያም]
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
፨፨፨፨፨፨፨፨
.........የቀጠለ
➸ ኹለት ዓይነት ትንቢት አለ፦
፩. በነገሮች የሚወሰን ትንቢት(Conditional Prophecy)፦
ለምሳሌ፦ "እሺ ብትሉ ለእኔም ብትታዘዙ፥ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤ እምቢ ብትሉ ግን ብታምፁም፥ ሰይፍ ይበላችኋል፤ የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሮአልና።" ኢሳ.1፥19-20 የሚለው ተፈጻሚ የሚኾነው እኛ ተኣዛዚ ኾነን እሺ ካልን ብቻ በረከተ ምድር እንበላለን። ካልኾንን በረከተ ምድርን አንበላም።
የሚወሰነው በምንሰጠው ግብረ መልስ ነው። "አባትህንና እናትህን አክብር፤ እግዚአብሔር አምላክህ በሚሰጥህ ምድር ዕድሜህ እንዲረዝም።" ዘጸ. 20፥12 "ዕድሜ የሚረዝመው" እናት አባታችን ካከበርን ነው፤ ካላከበርን ያጥራል። ተፈጻሚነቱ የሚወሰነው በእኛ ድርጊት ነው።
፪. በነገሮች የማይወሰን የግድ የሚፈጸም ትንቢት(Unconditional Prophecy) ደግሞ አለ። ለምሳሌ፦ ምጽአት ክርስቶስ እኛ ጻድቅም ኾንን ኃጥእ የማይቀር የግድ የሚፈጸም ትንቢት ነው። ሊቁ አባ ገ/ኪዳን እንዳስተማሩንም ምጽኣተ ቴዎድሮስ
በተመለከተ የጥንት ብራና መጽሐፍ የሚለው "እኛ በንስሓ ከተመለስን ነው" ደገኛ ንጉሥ በሀገራችን የሚነግሠው
ብለዋል። ይኼ ማለት አምላከ ቅዱሳን አምላካችን እግዚአብሔር በፍጹም ንስሓ መመለሳችንን አይቶ ቴዎድሮስ
የሚባል ንጉሥ ሊነግሥ ይችላል አሊያም እንደ ስሙ ትርጓሜ ዘመነ ሰላም|ቴዎድሮስን| ያሳየናል ማለት ነው። በአጭር ቃል እንደ አባ ገ/ኪዳን ገለጻ ምጽኣተ ቴዎድሮስ በነገሮች የሚወሰን
ትንቢት(Conditional Prophecy) ውስጥ የሚመደብ ነው።
➻ ይኼን የመጻሕፍት አስረጅ አክብረን ሳንነቅፍ ዳሩ ግን የቴዎድሮስ መምጣት ብርቅም ድንቅም አርጎ አለመናገር
ይገባል። ከድኅነተ ሥጋ ድኅነተ ነፍስ ይበልጣልና።
➾ በጠበል ከሥጋ በሽታችን ብንፈወስ መልካም ነው፤ባንፈወስም ንስሓ ገብተን ሕገ ወንጌለን ብንፈጽም በምሕረተ ክርስቶስ እንድናለን ብለን ተስፋ እናደርጋለን። ነገር ግን በጠበል ከሥጋ በሽታ ተፈውሰን ዳሩ ግን ንስሓ ካልገባንና ሕገ ወንጌል ካለፈጸምን አንድንም። የሥጋ በሽታ ፈውስ ለምድራዊ ኑሯችን እንጂ ለሰማያዊ ሕይወታችን ዋስትና አይኾንም። ከምጽኣተ ቴዎድሮስ ይልቅ ምጽኣተ ክርስቶስን ነቅተን፥ ተገተን በእጅጉ መዘጋጀት ይጠቅማል። ምክንያቱም፦
፩. ንጉሥ ቴዎድሮስ ፍጡር፥ መድኅነ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን የነገሥት ንጉሥ ፈጣሪ ነው።
፪. በቁሙ ቴዎድሮስ የሚባል ንጉሥ ላይመጣ ይችላል። መድኅነ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ግን እሱ ባወቀ ቀን መምጣቱ ግድ ነው። "ዳግመኛም በሕያዋንና በሙታን ሊፈርድ ይመጣል።"[ጸሎተ ሃይማኖት] እንዲል።
፫. ቴዎድሮስ ቢመጣ ጊዜያዊ ዘመነ ሰላም ሊያመጣ ሊነግስ ነው፤ ጌታችን ሲመጣ ግን ዘላለማዊ ሰላም ሊሰጠን ለጻድቃን ሊፈርድላቸው ለኃጥኣን ሊፈርድባቸው ነው።
፬. ቴዎድሮስ ቢመጣ ዓለምን ሊያሳልፍ አይደለም። መድኅነ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለምን ሊያሳልፍ ነው።
፭. ቴዎድሮስ ቢመጣ ጊዜያዊ ንጉሠ ኀላፊት ምድር ቢኾን ነው፤ መድኅነ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ዘላለማዊ ንጉሠ ሰማይ ወምድር ነው። "እነሆም፥ ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ።" ማቴ.12፥41 እንዲል።
➻ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራችን |የማርያም መቀነት| ሰንደቅ ዓላማችን ዓለምን ዳግም በንፍር ውሀ እንደማያጠፋት ለኖኅ ቃል ኪዳን መግባቱን የሚያሳይ ዓርማችን እንጂ ከዘላለም የሞት ፍርድ ግን አያድንም። በኦርቶዶክሳዊት የተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አራት ነገሮች አሉ።
፩. ፈጽሞ እንዳንፈጽማቸው የተከለከሉ አሉ። ለምሳሌ፦ ኃጢኣትና ክፉ እኵያት ኹሉም።
፪. እንድንፈጽማቸው የታዘዙም አሉ። ለአብነትም ሕገ ወንጌልን
መፈጸም።
፫. ተፈቅደው ግን የማይበረታቱ አሉ። ለምሳሌ፦ የሚያሰክር መጠጥ ፈጽሞ አይከለክልም፥ ግና የሚያሰክር መጠጥ
አይበረታታም። የማይጠጣ የተሻለ አደረገ እንጂ።
፫. ብንፈጽማቸው፥ ባንፈጽማቸውም የማያስተቹ አሉ። ለምሳሌ፦ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ነጠላ፥ አልባሳት ብንለብስም ባንለብስም ከወቀሳ ከከሰሳ አያደርስም። አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ ዓላማ
እንጂ ዶግማም ሥርዐትም አይደለማ። ለዚህም ነው 'ንጉሥ ቴዎድሮስ ይመጣል በሚል አረንጓዴ ቢጫ ቀይ በሩ ላይ ያደረገ ይድናል' የሚል ፈጠራ እብለት ነው የምንል። የኢትዮጵያ ሰንደቅ
ዓለማ እንጂ በራሱ ሃይማኖት አይደለማ። ሰንደቅ ዓላማችን ክብራችን ነው እናክብረው ማለት እየተቻለ Code እየሰጡ፥ በሥዕለ ቅዱሳን ተሸፍነው፥ 'ባንዲራ ሰቅላችሁ ጠብቁ ድኅነታችሁ ነው' ማለቱ ለምን አስፈለገ? ትንቢተ ኢሳይያስ ላይ "ደሴቶች ሆይ፥ ስሙኝ፥ እናንተም በሩቅ ያላችሁ አሕዛብ፥ አድምጡ፤ እግዚአብሔር ከማኅፀን
ጠርቶኛል፥ ከእናቴም ሆድ ጀምሮ ስሜን አንሥቶአል፤" ኢሳ.49፥1የሚለውኮ ስለ ቴዎድሮስ ሳይኾን ደሴት በውሀ፥ ውሀ
በደሴት እንዲከበብ ሰባ ዘመን በመከራ የተከበባችሁ እስራኤል ስሙኝ። አሕዛብ አድምጡኝ፤ በእናቴ ማኅፀን ስሜን ኢሳይያስ አለኝ፤ አንድም ከእናቴ ማኅፀን ከተወለድሁ በኋላ ኢሳይያስ ብሎ
ስም አወጣልኝ ለማለት ነው። "አፌንም እንደ ተሳለ ሰይፍ አድርጎአል፥" ሲል አንደበቴ እንደ ተሳለ ምላጭ አደረገው ማለት ኦሪትን እንዳስተምር አደረገኝ ሲለን እንጂ ስለ ምጽኣተ ቴዎድሮስ
አይናገርም። "የተቀላቀለ እንዳይኾን እንለይ" እንዳለ ደራሲ [ቅዳሴ ማርያም]
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
አዎን አቤቱ አንተ ለዘላለም ልዑል ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ ሁሉን የምትገዛ ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ ሁሉን የምታድን ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ ሁሉን የምትመግብ ነህ
አዎን አቤቱ አንተ የፍጥረታት ጌታ ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ በእውነት የምትፈቀር ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ ሁሉን አሳልፈህ የምትኖር የዘላለም አምላክ
ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ አልፋ እና ኦሜጋ ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ አባታችን ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ የነፍስ የሥጋችን መመኪያ ነህ!
አዎን አቤቱ ፈጣሪያችን ነህ!
አዎን አቤቱ የምንገዛልህ የምናመልክህ የምንሰግድልህ
የምናመሰግንህ ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ ንጉሰ ነገሥት ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ የጌቶች ጌታ ነህ!
"አንተ ብቻ እግዚአብሔር ነህ፤ ሰማዩንና የሰማያት ሰማይን ሠራዊታቸውንም ሁሉ፥ ምድሩንና በእርስዋ ላይ ያሉትን ሁሉ፥ ባሕሮቹንና በእነርሱ ውስጥ ያለውን ሁሉ፥ ፈጥረሃል፥ ሁሉንም ሕያው አድርገኸዋል፤ የሰማዩም ሠራዊት ለአንተ ይሰግዳሉ።
" (መጽሐፈ ነሀምያ 9:6)
"አቤቱ፥ በጽዮን ለአንተ ምስጋና ይገባል፥ ለአንተም ጸሎት ይቀርባል።ሥጋ ሁሉ ጸሎትን ወደምትሰማ ወደ አንተ ይመጣል። መዝ 65፡1-2
" በምድር ያሉ ሁሉ ለአንተ ይሰግዳሉ፥ ለአንተም ይዘምራሉ፥ ለስምህም ይዘምራሉ።" (መዝሙረ ዳዊት 66:4)
ክብርና ግርማ በፊቱ፥ ኃይልና ደስታ በስፍራው ውስጥ ናቸው። የአሕዛብ ወገኖች ለእግዚአብሔር አምጡ፥ ክብርንና ኃይልን ለእግዚአብሔር አምጡ። ለስሙ የሚገባ ክብርን ለእግዚአብሔር አምጡ፤ ቍርባንን ይዛችሁ በፊቱ ግቡ፤ በቅድስናው ስፍራ
ለእግዚአብሔር ስገዱ። መፅ. ዜና. ቀዳማዊ 16፡27-29
፩ ኃይማኖት
@And_Haymanot
አዎን አቤቱ አንተ ሁሉን የምትገዛ ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ ሁሉን የምታድን ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ ሁሉን የምትመግብ ነህ
አዎን አቤቱ አንተ የፍጥረታት ጌታ ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ በእውነት የምትፈቀር ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ ሁሉን አሳልፈህ የምትኖር የዘላለም አምላክ
ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ አልፋ እና ኦሜጋ ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ አባታችን ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ የነፍስ የሥጋችን መመኪያ ነህ!
አዎን አቤቱ ፈጣሪያችን ነህ!
አዎን አቤቱ የምንገዛልህ የምናመልክህ የምንሰግድልህ
የምናመሰግንህ ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ ንጉሰ ነገሥት ነህ!
አዎን አቤቱ አንተ የጌቶች ጌታ ነህ!
"አንተ ብቻ እግዚአብሔር ነህ፤ ሰማዩንና የሰማያት ሰማይን ሠራዊታቸውንም ሁሉ፥ ምድሩንና በእርስዋ ላይ ያሉትን ሁሉ፥ ባሕሮቹንና በእነርሱ ውስጥ ያለውን ሁሉ፥ ፈጥረሃል፥ ሁሉንም ሕያው አድርገኸዋል፤ የሰማዩም ሠራዊት ለአንተ ይሰግዳሉ።
" (መጽሐፈ ነሀምያ 9:6)
"አቤቱ፥ በጽዮን ለአንተ ምስጋና ይገባል፥ ለአንተም ጸሎት ይቀርባል።ሥጋ ሁሉ ጸሎትን ወደምትሰማ ወደ አንተ ይመጣል። መዝ 65፡1-2
" በምድር ያሉ ሁሉ ለአንተ ይሰግዳሉ፥ ለአንተም ይዘምራሉ፥ ለስምህም ይዘምራሉ።" (መዝሙረ ዳዊት 66:4)
ክብርና ግርማ በፊቱ፥ ኃይልና ደስታ በስፍራው ውስጥ ናቸው። የአሕዛብ ወገኖች ለእግዚአብሔር አምጡ፥ ክብርንና ኃይልን ለእግዚአብሔር አምጡ። ለስሙ የሚገባ ክብርን ለእግዚአብሔር አምጡ፤ ቍርባንን ይዛችሁ በፊቱ ግቡ፤ በቅድስናው ስፍራ
ለእግዚአብሔር ስገዱ። መፅ. ዜና. ቀዳማዊ 16፡27-29
፩ ኃይማኖት
@And_Haymanot
"ወዳጄ ሆይ ሮማውያን ወታደሮች ጎንጉነው በጌታችን እራስ ላይ እሾህ እዳቀዳጁት ባሰብህ ጊዜ እጅግ ማዘንህ አይቀርም ። ሆኖም አንተም እሾህ የተባለውን አንድ ኃጢአት በሰራህ ቁጥር በጌታችን ላይ የተደፉትን እሾኾች ቁጥር እንደጨመርህ አስብ ።በፈጣሪ የማያምኑት ሮማውያን ወታደሮች ከጎነጎኑት እሾኽ በላይ የጌታችንን እራስ የበለጠ ዘልቆ የሚወጋው ደሙን አፍስሶ ያዳነን እኛ ክርስቲያኖች በኃጢአታችን የምንጎነጉነው የእሾኽ አክሊል ነው ።{ስለመተላለፋችን የቆሰለው አምላክ በመተላለፋችንም ይቆስላል ።!}
{በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን ከሚለው ርዕስ የተወሰደ )
@And_Haymanot
[ ሕማማት]
{በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ}
{በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን ከሚለው ርዕስ የተወሰደ )
@And_Haymanot
[ ሕማማት]
{በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ}
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
ጴጥሮስን ለታላቅ ንስሐ የቀሰቀሰው የዶሮ ጩኸት ነበር
... ‹የዶሮ ጩኸት ጴጥሮስን ለንስሐ አበቃው› የሚለው ታሪክ ከዶሮ ጩኸት አልፎ እልፍ ሰባኪያን ‹ንስሐ ግቡ› እያሉ ሲጮኹ እየሰማን ምንም ለማይመስለን ለእኛ ለልበ ደንዳኖቹ መልእክቱ ምን ይሆን?
የዶሮዎቹን ጩኸት ሰምቶ በመመለስ ፈንታ የዶሮዎቹን የአጯጯህ ስልት እያወዳደርን ሰባኪያን ለምናማርጥ ለእኛ መልእክቱ በእርግጥ ምን ይሆን?
በእርግጥ የዶሮውም እድል የሚያስቀና ነው፡፡
አንድ ጊዜ ጮኾ የወደቀውን ጴጥሮስ እንዲነሣ መቀስቀስ መቻሉ የታደለ ሰባኪ ያደርገዋል፡፡
ብዙ ጊዜ ስንጮኽ ውለን አንድ ሰው ለንስሐ ማብቃት ላልቻልን ሰባኪያን ይህ ዶሮ ምንኛ የሚያስቀና ነው?
ለነገሩ በልማዱ ዶሮ ጮኾ ሌሎቹን ከማስነሣቱ በፊት እሱ ተነሥቶ ክንፉን እያርገበገበ ከፍ ከፍ ይላል፡፡
እኛ ግን ራሳችን በኃጢአት ተኝተን ሌላውን ለንስሐ ለመቀስቀስ የምንሞክር እንቅልፋም ዶሮዎች ስለሆንን በጩኸታችን የረበሽነው እንጂ የቀሰቀስነው ሰው የለም፡፡
"ሕማማት" ከተሰኘው ከዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ መጽሐፍ የተወሰደ
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
@And_Haymanot @And_Haymanot
@And_Haymanot @And_Haymanot
@And_Haymanot @And_Haymanot
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
... ‹የዶሮ ጩኸት ጴጥሮስን ለንስሐ አበቃው› የሚለው ታሪክ ከዶሮ ጩኸት አልፎ እልፍ ሰባኪያን ‹ንስሐ ግቡ› እያሉ ሲጮኹ እየሰማን ምንም ለማይመስለን ለእኛ ለልበ ደንዳኖቹ መልእክቱ ምን ይሆን?
የዶሮዎቹን ጩኸት ሰምቶ በመመለስ ፈንታ የዶሮዎቹን የአጯጯህ ስልት እያወዳደርን ሰባኪያን ለምናማርጥ ለእኛ መልእክቱ በእርግጥ ምን ይሆን?
በእርግጥ የዶሮውም እድል የሚያስቀና ነው፡፡
አንድ ጊዜ ጮኾ የወደቀውን ጴጥሮስ እንዲነሣ መቀስቀስ መቻሉ የታደለ ሰባኪ ያደርገዋል፡፡
ብዙ ጊዜ ስንጮኽ ውለን አንድ ሰው ለንስሐ ማብቃት ላልቻልን ሰባኪያን ይህ ዶሮ ምንኛ የሚያስቀና ነው?
ለነገሩ በልማዱ ዶሮ ጮኾ ሌሎቹን ከማስነሣቱ በፊት እሱ ተነሥቶ ክንፉን እያርገበገበ ከፍ ከፍ ይላል፡፡
እኛ ግን ራሳችን በኃጢአት ተኝተን ሌላውን ለንስሐ ለመቀስቀስ የምንሞክር እንቅልፋም ዶሮዎች ስለሆንን በጩኸታችን የረበሽነው እንጂ የቀሰቀስነው ሰው የለም፡፡
"ሕማማት" ከተሰኘው ከዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ መጽሐፍ የተወሰደ
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
@And_Haymanot @And_Haymanot
@And_Haymanot @And_Haymanot
@And_Haymanot @And_Haymanot
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
👍1
ይህ ሳምንት ከሰርከ ሆሳዕና እስከ ትንሣኤ ያሉትን ቀናት ያካትታል
✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥
❖ የጌታን መከራ እንግልት መሰቀል መሞት መቀበር የምናስብበት ነው፤ ለእኛ ሲል የተቀበላቸውን 13ቱ ሕማማተ መስቀል በማሰብ በልቅሶ በስግደት በጸሎት ልናሳልፈው ይገባል
❖ በዚህ ሳምንት ሊሰሩ ያልተፈቀዱ በርካታ ናቸው፤ በመስቀል መባረክ ማማተብ መሳቅ መሳሳም ከሴት ጋር መገናኘት ኑዛዜ መፈጸም ፈጽሞ የተከለከለ ሲሆን የ5500ው የጨለማ ዘመን መታሰቢያ በመሆኑ መንበሩ በጥቁር ልብስ ይሸፈናል ካሕናትም ጥቁር ይለብሳሉ
❖ በዚህ ሳምንት ለሞተ ጸሎተ ፍትሐት አይጸለይለትም ክርስትናም እንዲሁ አይፈጸምም፤ እግዚአብሔር ይፍታህ አይባልም ሳምንቱ የሚታሰበው ሕማሙን ሞቱን በማሰብና በስግደት ነው
❖ የግዝት በዓላት እንኳ ይሰገድባቸዋል፤ የዚህ ሳምንት ጾም የቻለ ሁለት ሁለት ቀን ያልቻለ እስከ ጀንበር ግባት ድረስ ነው፤ ምግቡም ቆሎ ዳቦ
የላመ የጣመ ያልሆነ ደረቁን በበርበሬ ነው መጠጡም ንጹህ ውኃ ነው
❖ ጠጅ ያንቆረቆረ ጮማ የቆረጠ እድል ፈንታው ጽዋእ ተርታው በጌታ ሞት ከተደሰቱት ከአይሁድ ጋር ነው፤ ጸሎቱ ውዳሴ ማርያም አንቀጸ ብርሃን መልክአ ሕማማት መዝሙረ ዳዊት ነው፤ የቅዱሳን መልክአ መልክእ ይጸለይም
❖ የጾሙ ሥርዓት ምን ይመስላል ካሉ ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15
📌 ቁጥር 578
❖ በሊህ በስድስቱ ቀኖች (በሰሙነ ሕማማት) ከቂጣ ከጨው ከውኃ ብቻ በቀር አይብሉባቸው፤ በሊህ ቀኖች ከወይን ከሥጋ ተለዩ የኀዘን ቀኖች ናቸውና የደስታ ቀኖች አይደሉም
❖ ዓርብንና ቅዳሜን ግን ሁለቱንም በአንድነት ጹሟቸው፤ #የሚችል እስከ ሌሊቱ ዶሮ ጩኸት ጊዜ ድረስ ምንም ምን አይቅመስባቸው ሰውየውም ሁለቱን ቀኖች በአንድነት መጾም ባይቻለው ግን የቅዳሜን ጾም ይጹም
📌 ቁጥር 590
❖ ካህን ሰሙነ ሕማማትን ቀንና ሌሊቱን ሳያስተካክል አስቀድሞ ቢያውል ይሻር፤ ከሕማማት ቀጥላ ከምትሆን ከቅዳሜ ስዑር በቀር እሑድንና ቅዳሜን የጾመ ካህን ቢኖር ይሻር
📌 ቁጥር 593
❖ ከካህናት ወገን ማንም ቢሆን በአርባ ጾም
በዓርብና በረቡዕም ጾም ወይን መጠጣት አይገባውም ወደ መዋት (ውሽባ ቤት) አይግባ፤ በዐቢይ ጾም ወራት ሰው ከሚስቱ ጋር አይተኛ
📌 ቁጥር 597
❖ ሴቶችም ጌጣቸውን ይተው፤ ሁሉም ለእያንዳንዱ በአርባ ጾምና በሰሙነ ሕማማት መጠበቅ ይገባዋል ድኅነታችንና የኃጢአታችን ሥርየት በእነርሱ ነውና
❖ ይኸውም ሥራ አንዱስ እንኳ በአርባ ጾም ወራት በምንጣፍ ፈጽሞ እንዳይገናኝ ከጋብቻ
ሕግ የወጣ ነው
❖ ክብርት በምትሆን በሕማማት ወራት ይህችን
ኃጢአት የሚሠራት ሰው ወዮለት፤ በአርባ ጾም በተድላ በደስታ ፈቃዳችንን ካደረግን ትንሣኤውን ባየን ጊዜ ተድላ ደስታችን ወዴት አለ ?
📌 ቁጥር 599
❖ በተባሕትዎ በትሕትና አርባ ቀን ጾምን ይጹሙ፤ ከጥሉላት መከልከል ይገባል፤ አያግቡም
📌 ቁጥር 600
❖ በሰሙነ ሕማማት ክርስትና ማንሣት ክህነት
መስጠት ለሞቱ ሰዎች መጸለይ አይገባም
❖ በእነዚህም ቀኖች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ፈጽሞ ማገልገል ይገባል እንጅ፤ በሰሙነ ሕማማት ስለሚሞቱት ሰዎች የሙታን ግንዘትና የሐዋርያት ሥራ ወንጌላት የሙታን ፍትሐት በሆሣዕና በዓል ቀን ይነበብ እንጅ
📌 ቁጥር 601
❖ በጸሎተ ሐሙስ ጸሎተ ተአምኆ እግዚአ ሕያዋን የቡራኬ ጸሎት አይባልም (አይጸለይም)
❖ ቅዳሜ ግን እግዚአ ሕያዋን ይባላል ፍትሐት ይፈታል፤ ከመሳለም በቀር ጸሎተ ዕጣንም ይጸለያል
❖ በዕለተ እሑድ ግንዘት ማድረግ በፋሲካ
ቀንም ማልቀስ አይገባም፤ ዳግመኛም በውስጧ በአርባ ጾም ከተድላ ከደስታ ወገን ምንም ማድረግ አይገባም
❖ መጋባት ክህነት መስጠት ክርስትና ማንሣት ከሹመትም ወገን ስለሚሞቱት ከመጸለይ በቀር ምንም ማድረግ አይገባም፤ ይሞታል ተብሎ ለሚያስፈራው ግን ጥምቀተ ክርስትና ይደረግለታል
📌 የተከለከሉ ነገሮች ምን ምን ናቸው ካሉ
፩. እጅ ተጨባብጦ ሰላምታ መባባል መሳሳም
፪. ሩካቤ ሥጋ ማድረግ
፫. መስቀል ማሳለም እና መሳለም
፬. ክርስትና ማስነሣት
፭. ለሙታን ፍትሐት ማድረግ
፮. ክህነት መስጠት
፯. የላመ የጣመ ምግብ መመገብ
፰. መሳቅ መጫዎት መጨፈር
፱. አብዝቶ ጠግቦ መመገብ
፲. መስከር ወዘተ ናቸው።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይቆየን !!!
✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥
💚 @And_haymanot 💚
💛 @And_haymanot 💛
❤️ @And_haymanot ❤️
✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥
❖ የጌታን መከራ እንግልት መሰቀል መሞት መቀበር የምናስብበት ነው፤ ለእኛ ሲል የተቀበላቸውን 13ቱ ሕማማተ መስቀል በማሰብ በልቅሶ በስግደት በጸሎት ልናሳልፈው ይገባል
❖ በዚህ ሳምንት ሊሰሩ ያልተፈቀዱ በርካታ ናቸው፤ በመስቀል መባረክ ማማተብ መሳቅ መሳሳም ከሴት ጋር መገናኘት ኑዛዜ መፈጸም ፈጽሞ የተከለከለ ሲሆን የ5500ው የጨለማ ዘመን መታሰቢያ በመሆኑ መንበሩ በጥቁር ልብስ ይሸፈናል ካሕናትም ጥቁር ይለብሳሉ
❖ በዚህ ሳምንት ለሞተ ጸሎተ ፍትሐት አይጸለይለትም ክርስትናም እንዲሁ አይፈጸምም፤ እግዚአብሔር ይፍታህ አይባልም ሳምንቱ የሚታሰበው ሕማሙን ሞቱን በማሰብና በስግደት ነው
❖ የግዝት በዓላት እንኳ ይሰገድባቸዋል፤ የዚህ ሳምንት ጾም የቻለ ሁለት ሁለት ቀን ያልቻለ እስከ ጀንበር ግባት ድረስ ነው፤ ምግቡም ቆሎ ዳቦ
የላመ የጣመ ያልሆነ ደረቁን በበርበሬ ነው መጠጡም ንጹህ ውኃ ነው
❖ ጠጅ ያንቆረቆረ ጮማ የቆረጠ እድል ፈንታው ጽዋእ ተርታው በጌታ ሞት ከተደሰቱት ከአይሁድ ጋር ነው፤ ጸሎቱ ውዳሴ ማርያም አንቀጸ ብርሃን መልክአ ሕማማት መዝሙረ ዳዊት ነው፤ የቅዱሳን መልክአ መልክእ ይጸለይም
❖ የጾሙ ሥርዓት ምን ይመስላል ካሉ ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15
📌 ቁጥር 578
❖ በሊህ በስድስቱ ቀኖች (በሰሙነ ሕማማት) ከቂጣ ከጨው ከውኃ ብቻ በቀር አይብሉባቸው፤ በሊህ ቀኖች ከወይን ከሥጋ ተለዩ የኀዘን ቀኖች ናቸውና የደስታ ቀኖች አይደሉም
❖ ዓርብንና ቅዳሜን ግን ሁለቱንም በአንድነት ጹሟቸው፤ #የሚችል እስከ ሌሊቱ ዶሮ ጩኸት ጊዜ ድረስ ምንም ምን አይቅመስባቸው ሰውየውም ሁለቱን ቀኖች በአንድነት መጾም ባይቻለው ግን የቅዳሜን ጾም ይጹም
📌 ቁጥር 590
❖ ካህን ሰሙነ ሕማማትን ቀንና ሌሊቱን ሳያስተካክል አስቀድሞ ቢያውል ይሻር፤ ከሕማማት ቀጥላ ከምትሆን ከቅዳሜ ስዑር በቀር እሑድንና ቅዳሜን የጾመ ካህን ቢኖር ይሻር
📌 ቁጥር 593
❖ ከካህናት ወገን ማንም ቢሆን በአርባ ጾም
በዓርብና በረቡዕም ጾም ወይን መጠጣት አይገባውም ወደ መዋት (ውሽባ ቤት) አይግባ፤ በዐቢይ ጾም ወራት ሰው ከሚስቱ ጋር አይተኛ
📌 ቁጥር 597
❖ ሴቶችም ጌጣቸውን ይተው፤ ሁሉም ለእያንዳንዱ በአርባ ጾምና በሰሙነ ሕማማት መጠበቅ ይገባዋል ድኅነታችንና የኃጢአታችን ሥርየት በእነርሱ ነውና
❖ ይኸውም ሥራ አንዱስ እንኳ በአርባ ጾም ወራት በምንጣፍ ፈጽሞ እንዳይገናኝ ከጋብቻ
ሕግ የወጣ ነው
❖ ክብርት በምትሆን በሕማማት ወራት ይህችን
ኃጢአት የሚሠራት ሰው ወዮለት፤ በአርባ ጾም በተድላ በደስታ ፈቃዳችንን ካደረግን ትንሣኤውን ባየን ጊዜ ተድላ ደስታችን ወዴት አለ ?
📌 ቁጥር 599
❖ በተባሕትዎ በትሕትና አርባ ቀን ጾምን ይጹሙ፤ ከጥሉላት መከልከል ይገባል፤ አያግቡም
📌 ቁጥር 600
❖ በሰሙነ ሕማማት ክርስትና ማንሣት ክህነት
መስጠት ለሞቱ ሰዎች መጸለይ አይገባም
❖ በእነዚህም ቀኖች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ፈጽሞ ማገልገል ይገባል እንጅ፤ በሰሙነ ሕማማት ስለሚሞቱት ሰዎች የሙታን ግንዘትና የሐዋርያት ሥራ ወንጌላት የሙታን ፍትሐት በሆሣዕና በዓል ቀን ይነበብ እንጅ
📌 ቁጥር 601
❖ በጸሎተ ሐሙስ ጸሎተ ተአምኆ እግዚአ ሕያዋን የቡራኬ ጸሎት አይባልም (አይጸለይም)
❖ ቅዳሜ ግን እግዚአ ሕያዋን ይባላል ፍትሐት ይፈታል፤ ከመሳለም በቀር ጸሎተ ዕጣንም ይጸለያል
❖ በዕለተ እሑድ ግንዘት ማድረግ በፋሲካ
ቀንም ማልቀስ አይገባም፤ ዳግመኛም በውስጧ በአርባ ጾም ከተድላ ከደስታ ወገን ምንም ማድረግ አይገባም
❖ መጋባት ክህነት መስጠት ክርስትና ማንሣት ከሹመትም ወገን ስለሚሞቱት ከመጸለይ በቀር ምንም ማድረግ አይገባም፤ ይሞታል ተብሎ ለሚያስፈራው ግን ጥምቀተ ክርስትና ይደረግለታል
📌 የተከለከሉ ነገሮች ምን ምን ናቸው ካሉ
፩. እጅ ተጨባብጦ ሰላምታ መባባል መሳሳም
፪. ሩካቤ ሥጋ ማድረግ
፫. መስቀል ማሳለም እና መሳለም
፬. ክርስትና ማስነሣት
፭. ለሙታን ፍትሐት ማድረግ
፮. ክህነት መስጠት
፯. የላመ የጣመ ምግብ መመገብ
፰. መሳቅ መጫዎት መጨፈር
፱. አብዝቶ ጠግቦ መመገብ
፲. መስከር ወዘተ ናቸው።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይቆየን !!!
✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥
💚 @And_haymanot 💚
💛 @And_haymanot 💛
❤️ @And_haymanot ❤️
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
ሳልፆም ሊፈሰክ ነው
አይ የኔ ነገር !
እርግጥ አልበላሁም ስጋም ሆነ ቅቤ
አልፆም አለኝ እንጂ አመፀኛ ልቤ
ካምናና ካቻምና የዘንድሮ ብሶ
መላ ማንነቴ በሀጢያት ተለውሶ
ስዋሽ ስቀጥፍ
ህግን ስተላለፍ
ስሰድብ ሳደማ
የሰው ስጋ ሳማ
ባይኔ ሳመነዝር
የሰው ሰው ሳማትር
ገላዬን_ሳራቁት
አዳምን/ሔዋንን ሳሳስት
ስረሳ ስቃይህን
መስቀል ህማምህን
ያን ሁሉ ግርፋት
ነብሴ ሳያስጨንቃት
አይ እኔ
በሀሰት ስመሰክር
በሀጢያት ስዳክር
ለማይሞላ ኑሮ
ሳልሻል ዘንድሮ
ፆሙ ተጋመሰ
ጊዜው ተጋመሰ
ጌታ ሆይ
አቤቱ አስበኝ
ለንሰሀ አብቃኝ
እስቲ የቀረውን ለበረከት በለው
አመፀኛ ልቤ ፆምህን ይፁመው
"ከደጀ ሰላሙ ከካህኑ እግር ስር
ንስሀዬን ልውሰድ ስለመስቀል ፍቅር" 🙏
================
ከናንተው የተላከ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
አይ የኔ ነገር !
እርግጥ አልበላሁም ስጋም ሆነ ቅቤ
አልፆም አለኝ እንጂ አመፀኛ ልቤ
ካምናና ካቻምና የዘንድሮ ብሶ
መላ ማንነቴ በሀጢያት ተለውሶ
ስዋሽ ስቀጥፍ
ህግን ስተላለፍ
ስሰድብ ሳደማ
የሰው ስጋ ሳማ
ባይኔ ሳመነዝር
የሰው ሰው ሳማትር
ገላዬን_ሳራቁት
አዳምን/ሔዋንን ሳሳስት
ስረሳ ስቃይህን
መስቀል ህማምህን
ያን ሁሉ ግርፋት
ነብሴ ሳያስጨንቃት
አይ እኔ
በሀሰት ስመሰክር
በሀጢያት ስዳክር
ለማይሞላ ኑሮ
ሳልሻል ዘንድሮ
ፆሙ ተጋመሰ
ጊዜው ተጋመሰ
ጌታ ሆይ
አቤቱ አስበኝ
ለንሰሀ አብቃኝ
እስቲ የቀረውን ለበረከት በለው
አመፀኛ ልቤ ፆምህን ይፁመው
"ከደጀ ሰላሙ ከካህኑ እግር ስር
ንስሀዬን ልውሰድ ስለመስቀል ፍቅር" 🙏
================
ከናንተው የተላከ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
👍1
ጉልባን
ጉልባን ከባቄላ ክክ፣ ከስንዴ ወይንም ከተፈተገ ገብስ ጋር አንድ ላይ ተቀቅሎ የሚዘጋጅና የጸሎተ ሐሙስ ዕለት የሚባላ ንፍሮ ነው፡፡
የጉልባን ትውፊት እስራኤላውያን ከግብፅ ተሰደው በሚወጡበት ጊዜ በችኮላ ስለነበር፤ አቡክተው ጋግረው መብላት ያለመቻላቸውን ሁኔታ ያመለክታል፡፡ ያን ጊዜ ያልቦካውን ሊጥ
እየጋገሩ ቂጣ መብላት፤ ንፍሮም ቀቅለው ስንቅ መያዝ ተግባራቸው ነበርና ይህን ለማሰብ በሰሙነ ሕማማት ቂጣና
ጉልባን በማዘጋጀት በዓሉ ይታሰባል፡፡
በጸሎተ ሐሙስ ይህንን መሠረት በማድረግ የሚዘጋጀው ጉልባን
አንዲህም ቂጣ ጨው በዛ ተደርጎ ይጨመርበታል፡፡ ጨው ውኃ የሚያስጠማ በመሆኑ የጌታን መጠማት ያስታውሳል፡፡ ይህ ትውፊታዊ ሥርዓት ከእስራኤላውያን የመጣ ሲሆን በኢትዮጵያም አብዛኛዎቹ የትውፊት ክንዋኔዎች የብሉይ ኪዳን መነሻ ስላላቸው ሥርዓቱ ዛሬም ይከበራል፡፡
በዲ/ን ቤርዜሊ ተስፋዬ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ጉልባን ከባቄላ ክክ፣ ከስንዴ ወይንም ከተፈተገ ገብስ ጋር አንድ ላይ ተቀቅሎ የሚዘጋጅና የጸሎተ ሐሙስ ዕለት የሚባላ ንፍሮ ነው፡፡
የጉልባን ትውፊት እስራኤላውያን ከግብፅ ተሰደው በሚወጡበት ጊዜ በችኮላ ስለነበር፤ አቡክተው ጋግረው መብላት ያለመቻላቸውን ሁኔታ ያመለክታል፡፡ ያን ጊዜ ያልቦካውን ሊጥ
እየጋገሩ ቂጣ መብላት፤ ንፍሮም ቀቅለው ስንቅ መያዝ ተግባራቸው ነበርና ይህን ለማሰብ በሰሙነ ሕማማት ቂጣና
ጉልባን በማዘጋጀት በዓሉ ይታሰባል፡፡
በጸሎተ ሐሙስ ይህንን መሠረት በማድረግ የሚዘጋጀው ጉልባን
አንዲህም ቂጣ ጨው በዛ ተደርጎ ይጨመርበታል፡፡ ጨው ውኃ የሚያስጠማ በመሆኑ የጌታን መጠማት ያስታውሳል፡፡ ይህ ትውፊታዊ ሥርዓት ከእስራኤላውያን የመጣ ሲሆን በኢትዮጵያም አብዛኛዎቹ የትውፊት ክንዋኔዎች የብሉይ ኪዳን መነሻ ስላላቸው ሥርዓቱ ዛሬም ይከበራል፡፡
በዲ/ን ቤርዜሊ ተስፋዬ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
+++ምን ሰጡህ ይሁዳ+++
ሙትን ልታስነሳ ድውይን ልትፈውስ
ሥልጣን ሰጥቶህ ነበር ኢየሱስ ክርስቶስ
ልታስር ልትፈታ በነፍስም በሥጋ
ሥልጣን ሰጥቶህ ነበር አልፋና ኦሜጋ
ምን ሰጡህ ይሁዳ አይሁድ ወገኖችህ
ለነርሱ አሳልፈህ ጌታህን የሰጠህ
ከሁሉ የሚበልጥ ሥልጣን ሰጥቶህ ሳለ
ብርን ለመቀበል ልብህ ተታለለ
ሰማይና ምድርን በቃሉ የፈጠረ
እንዴት በመቃብር ሶሥት ቀን አደረ
አንተ የሰጠኸው አሳልፈህ ለሞት
ሞትን ድል አድርጎ ተነሳ በሰንበት
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ሙትን ልታስነሳ ድውይን ልትፈውስ
ሥልጣን ሰጥቶህ ነበር ኢየሱስ ክርስቶስ
ልታስር ልትፈታ በነፍስም በሥጋ
ሥልጣን ሰጥቶህ ነበር አልፋና ኦሜጋ
ምን ሰጡህ ይሁዳ አይሁድ ወገኖችህ
ለነርሱ አሳልፈህ ጌታህን የሰጠህ
ከሁሉ የሚበልጥ ሥልጣን ሰጥቶህ ሳለ
ብርን ለመቀበል ልብህ ተታለለ
ሰማይና ምድርን በቃሉ የፈጠረ
እንዴት በመቃብር ሶሥት ቀን አደረ
አንተ የሰጠኸው አሳልፈህ ለሞት
ሞትን ድል አድርጎ ተነሳ በሰንበት
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
በግብረ ሕማማት ውስጥ የሚገኙ ባዕድ ቃላት
በግብረ ሕማማት ውስጥ ወደ ግእዝም ሆነ በኋላ ወደ አማርኛ ሳይተረጎሙ የተቀመጡ የዕብራይስጥ፣ የቅብጥ እና የግሪክ ቃላት ይገኛሉ፡፡ የእነዚህ ቃላት ትርጉም የሚከተለው ነው፡፡
🔔 ኪርያላይሶን
ቃሉ የግሪክ ሲሆን አጠራሩ «ኪርዬ ኤሌይሶን» ነው፡፡ «ኪርያ» ማለት «እግዝእትነ» ማለት ሲሆን «ኪርዬ» ማለት ደግሞ «እግዚኦ» ማለት ነው፡፡ ሲጠራም «ኪርዬ ኤሌይሶን» መባል
አለበት፡፡ ትርጉሙም «አቤቱ ማረን» ማለት ነው፡፡ «ኪርያላይሶን» የምንለው በተለምዶ ነው፡፡ ይኼውም ኪርዬ ከሚለው «ዬ» ኤላይሶን ከሚለው ደግሞ «ኤ» በመሳሳባቸው በአማርኛ «ያ»ን ፈጥረው ነው፡፡
🔔 ናይናን
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «መሐረነ፣ ማረን» ማለት ነው፡፡
🔔 እብኖዲ
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «አምላክ» ማለት ነው፡፡ «እብኖዲ ናይናን» ሲልም «አምላክ ሆይ ማረን» ማለቱ ነው
🔔 ታኦስ
የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «ጌታ፣ አምላክ» ማለት ነው፡፡ «ታኦስ ናይናን» ማለትም «ጌታ ሆይ ማረን» ማለት ነው፡፡
🔔 ማስያስ
የዕብራይስጥ ቃል ሲሆነ ትርጉሙ «መሲሕ» ማለት ነው፡፡ «ማስያስ ናይናን» ሲልም «መሲሕ ሆይ ማረን» ማለት ነው
🔔 ትስቡጣ
«ዴስፓታ» ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ደግ ገዥ ማለት ነው
🔔 አምነስቲቲ ሙኪርያቱ አንቲ ፋሲልያሱ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ
መንግሥትከ- አቤቱ በመንግሥትህ አስበኝ» ማለት ነው፡፡
🔔 አምንስቲቲ መዓግያ አንቲ ፋሲልያሱ
የቅብጥ ቃል ሲሆን «ተዘከረነ ኦ ቅዱስ በውስተ መንግሥትከ - ቅዱስ ሆይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው አምንስቲቲ ሙዳሱጣ አንቲ ፋሲልያሱ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚአ ኩሉ በውስተ መንግሥትከ- የሁሉ የበላይ የሆንክ ወይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው፡፡
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
በግብረ ሕማማት ውስጥ ወደ ግእዝም ሆነ በኋላ ወደ አማርኛ ሳይተረጎሙ የተቀመጡ የዕብራይስጥ፣ የቅብጥ እና የግሪክ ቃላት ይገኛሉ፡፡ የእነዚህ ቃላት ትርጉም የሚከተለው ነው፡፡
🔔 ኪርያላይሶን
ቃሉ የግሪክ ሲሆን አጠራሩ «ኪርዬ ኤሌይሶን» ነው፡፡ «ኪርያ» ማለት «እግዝእትነ» ማለት ሲሆን «ኪርዬ» ማለት ደግሞ «እግዚኦ» ማለት ነው፡፡ ሲጠራም «ኪርዬ ኤሌይሶን» መባል
አለበት፡፡ ትርጉሙም «አቤቱ ማረን» ማለት ነው፡፡ «ኪርያላይሶን» የምንለው በተለምዶ ነው፡፡ ይኼውም ኪርዬ ከሚለው «ዬ» ኤላይሶን ከሚለው ደግሞ «ኤ» በመሳሳባቸው በአማርኛ «ያ»ን ፈጥረው ነው፡፡
🔔 ናይናን
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «መሐረነ፣ ማረን» ማለት ነው፡፡
🔔 እብኖዲ
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «አምላክ» ማለት ነው፡፡ «እብኖዲ ናይናን» ሲልም «አምላክ ሆይ ማረን» ማለቱ ነው
🔔 ታኦስ
የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «ጌታ፣ አምላክ» ማለት ነው፡፡ «ታኦስ ናይናን» ማለትም «ጌታ ሆይ ማረን» ማለት ነው፡፡
🔔 ማስያስ
የዕብራይስጥ ቃል ሲሆነ ትርጉሙ «መሲሕ» ማለት ነው፡፡ «ማስያስ ናይናን» ሲልም «መሲሕ ሆይ ማረን» ማለት ነው
🔔 ትስቡጣ
«ዴስፓታ» ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ደግ ገዥ ማለት ነው
🔔 አምነስቲቲ ሙኪርያቱ አንቲ ፋሲልያሱ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ
መንግሥትከ- አቤቱ በመንግሥትህ አስበኝ» ማለት ነው፡፡
🔔 አምንስቲቲ መዓግያ አንቲ ፋሲልያሱ
የቅብጥ ቃል ሲሆን «ተዘከረነ ኦ ቅዱስ በውስተ መንግሥትከ - ቅዱስ ሆይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው አምንስቲቲ ሙዳሱጣ አንቲ ፋሲልያሱ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚአ ኩሉ በውስተ መንግሥትከ- የሁሉ የበላይ የሆንክ ወይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው፡፡
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ሁሉን የያዘውን ያዙት
ሁሉን የሚገዛውን አሰሩት
በቁጣ ጎተቱት
በፍቅር ተከተላቸው
✥••┈┈┈••●◉✞◉●••┈┈┈••✥
መልካም የስቅለት በዓል ይሁንልህ/ሽ
_SHARE______
❤️ @And_haymanot ❤️
ሁሉን የሚገዛውን አሰሩት
በቁጣ ጎተቱት
በፍቅር ተከተላቸው
✥••┈┈┈••●◉✞◉●••┈┈┈••✥
መልካም የስቅለት በዓል ይሁንልህ/ሽ
_SHARE______
❤️ @And_haymanot ❤️
ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጋላችሁ ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም ። ሉቃ 24፥5
እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም በጤና አደረሰን ።
****
@And_Haymanot
እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም በጤና አደረሰን ።
****
@And_Haymanot
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
ለምን አንጾምም?
ተወዳጆች ሆይ የተሃድሶ መናፍቃን በዓለ ሃምሳን ለምን አትፆሙም ሲሉ ይደመጣሉ ከዛም አልፎ በዓቢይ ጾም የጾማችሁትን ለማካካስ ነው በማለት ይተቻሉ ቅድስት ቤተክርስቲያናችንስ ምን ትላለች?
ጥያቄ:- በበዓለ ሃምሳ ለምን አንጾምም?
በፍትሐ ነገሥት ላይ እንዲህ የሚል ትዕዛዝ አለ፦ "ዳግመኛ በየሳምንቱ ዓርብ እና ረቡዕን መጾም ነው፡፡ በዓለ ሃምሳ፣ የልደት እና የጥምቀት በዓል የተባበሩባቸው ጊዜ ካልሆነ በቀር" /ዐንቀጽ 15:566/።
"የዓርብን እና የረቡዕን ጾም ግን ከልደት፣ ከጥምቀት እና ከበዓለ ሃምሳ በቀር ዘወትር ይጹሙ" /ዐንቀጽ
15:603/። የዐቢይ ጾምን ፍቺ ተከትሎ ለ50 ቀናት የማንጾምበት ምክንያት
ብዙ ጥልቅ ምሥጢር ያለው ሥርዓተ ሃይማኖት ነው። በምሳሌ ለማስረዳትም ፦ ከትንሣኤ በፊት ያለውን አንድ ሳምንት ሰሙነ ሕማማት ብለን የምናስበው ዘመነ ኦሪት እንደሆነ በማሰብ ነው።
በዚኸ ሳምንት ከሌሎች ድርጊቶች በተጨማሪ መስቀል አንሳለምም። ይኸ የሆነበት ምክንያት በዘመነ ኦሪት መስቀል በክርስቶስ መለኮታዊ ደም ተባርኮ አልተሰጠም'ና ነው። ልክ
እንደዚሁ ከትንሣኤ ዕለት ጀምሮ አስከ በዓለ ጰራቂሊጦስ (አስከ የሐዋርያት ጾም መግቢያ ድረስ) ያሉት 50 ቀናት እንደ አንድ ቀን ነው የሚታዩት። ይህም ማለት ሰው ከትንሣኤ በኃላ ፍጹም
ያለ ድካም እንደሚኖር ለማስተማር ጾም እና የንስሐ ቀኖና አይሰጡም።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ተወዳጆች ሆይ የተሃድሶ መናፍቃን በዓለ ሃምሳን ለምን አትፆሙም ሲሉ ይደመጣሉ ከዛም አልፎ በዓቢይ ጾም የጾማችሁትን ለማካካስ ነው በማለት ይተቻሉ ቅድስት ቤተክርስቲያናችንስ ምን ትላለች?
ጥያቄ:- በበዓለ ሃምሳ ለምን አንጾምም?
በፍትሐ ነገሥት ላይ እንዲህ የሚል ትዕዛዝ አለ፦ "ዳግመኛ በየሳምንቱ ዓርብ እና ረቡዕን መጾም ነው፡፡ በዓለ ሃምሳ፣ የልደት እና የጥምቀት በዓል የተባበሩባቸው ጊዜ ካልሆነ በቀር" /ዐንቀጽ 15:566/።
"የዓርብን እና የረቡዕን ጾም ግን ከልደት፣ ከጥምቀት እና ከበዓለ ሃምሳ በቀር ዘወትር ይጹሙ" /ዐንቀጽ
15:603/። የዐቢይ ጾምን ፍቺ ተከትሎ ለ50 ቀናት የማንጾምበት ምክንያት
ብዙ ጥልቅ ምሥጢር ያለው ሥርዓተ ሃይማኖት ነው። በምሳሌ ለማስረዳትም ፦ ከትንሣኤ በፊት ያለውን አንድ ሳምንት ሰሙነ ሕማማት ብለን የምናስበው ዘመነ ኦሪት እንደሆነ በማሰብ ነው።
በዚኸ ሳምንት ከሌሎች ድርጊቶች በተጨማሪ መስቀል አንሳለምም። ይኸ የሆነበት ምክንያት በዘመነ ኦሪት መስቀል በክርስቶስ መለኮታዊ ደም ተባርኮ አልተሰጠም'ና ነው። ልክ
እንደዚሁ ከትንሣኤ ዕለት ጀምሮ አስከ በዓለ ጰራቂሊጦስ (አስከ የሐዋርያት ጾም መግቢያ ድረስ) ያሉት 50 ቀናት እንደ አንድ ቀን ነው የሚታዩት። ይህም ማለት ሰው ከትንሣኤ በኃላ ፍጹም
ያለ ድካም እንደሚኖር ለማስተማር ጾም እና የንስሐ ቀኖና አይሰጡም።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
አደባባያችንን አትንኩ!
ብፁዕ አቡነ ያሬድ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ። ብፁዕነታቸው ዛሬ ለአዲስ አበባ መስተዳድር የሰላምና ደኅንነት፡ቢሮ በጻፉት ደብዳቤ ሙስሊም ወንድሞቻችን ከዚህ ቀደም አፍጥርን በስታዲየም ሲያከብሩ መቆየታቸው እየታወቀ ዛሬ
በመስቀል አደባባይ እንዲከበር መፍቀድ ተከባብሮ የኖረውን ክርስቲያኑን እና ሙስሊሙን ማኅበረሰብ ወደ አላስፈላጊ ግጭት የሚገፋ ተግባር መሆኑን ፈቃድ ሰጭው አካል እንዲያጤነው አሳስበዋል። ሊቀ ጳጳሱ በደብዳቤያቸው ለሙስሊሙ ማኅበረሰብ ያላቸውን አክብሮት ገልጸው የአፍጥር ዝግጅቱም ሆነ ዒድ አልፈጥር በዓል ግን በተለመደው ስታዲዬም እንጂ በመስቀል
አደባባይ መከበር እንደሌለበት በአንክሮ አሳስበዋል።
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ብፁዕ አቡነ ያሬድ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ። ብፁዕነታቸው ዛሬ ለአዲስ አበባ መስተዳድር የሰላምና ደኅንነት፡ቢሮ በጻፉት ደብዳቤ ሙስሊም ወንድሞቻችን ከዚህ ቀደም አፍጥርን በስታዲየም ሲያከብሩ መቆየታቸው እየታወቀ ዛሬ
በመስቀል አደባባይ እንዲከበር መፍቀድ ተከባብሮ የኖረውን ክርስቲያኑን እና ሙስሊሙን ማኅበረሰብ ወደ አላስፈላጊ ግጭት የሚገፋ ተግባር መሆኑን ፈቃድ ሰጭው አካል እንዲያጤነው አሳስበዋል። ሊቀ ጳጳሱ በደብዳቤያቸው ለሙስሊሙ ማኅበረሰብ ያላቸውን አክብሮት ገልጸው የአፍጥር ዝግጅቱም ሆነ ዒድ አልፈጥር በዓል ግን በተለመደው ስታዲዬም እንጂ በመስቀል
አደባባይ መከበር እንደሌለበት በአንክሮ አሳስበዋል።
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot