ያለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት የሚያርግ
ጸሎት እንደሌለ ያውቃሉ?
@And_Haymanot
ብዙ የተሐድሶ መናፍቃን ያለ እመቤታችን አማላጅነት የሚያርግ ጸሎት እንደሌለ ማመን ሲከብዳቸው ይስተዋላል፡፡ አንዳንዶቹ ያለ እመቤታችን አማላጅነት የሚያርግ ጸሎት የለም የሚለው
የሆነ አባት በሆነ ግዜ የተናገረው በቅዱሳት መጻሕፍት ያልተመዘገበ አድርገው ይናገራሉ፡፡
የዚህ ዓለም ሰዎች የእግዚአብሔር መንፈሳዊ ጸጋ ርቋቸው፤በመንፈስ ድህነት ውስጥ ሲማቅቁ የሰው ልጅ መንፈሳዊ ሀብቱ ተራቁቶ ነዳይ ሆኖ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስን በቀጥታ ከባሕርይ አባቱ ከእግዚአብሔር አብ መቀበል ሲያቅታቸው፤ በመንፈሳዊነት በበለጸገችው፤ ጸጋን በተመላች
በእመቤታችን በኩል እግዚአብሔር አንድያ ልጁ ሰጠ፤ ዓለምም
ከእመቤታችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አገኘ፡፡ ሊቁ ቅዱስ አውግስጢኖስ(St. Augustine) "The world being
unworthy to receive the Son of God directly from the hands of the Father, he gave his Son to Mary for the world to receive him from her." እንዲል፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ(Saint John Eudes) እንደተናገረው "ለኢየሱስ ክርስቶስ እናት ፍቅር የሌለው ሰው እውነተኛ ክርስቲያን አይደለም- A man is no true Christian if he has no devotion to the Mother of Jesus Christ."
እንዳለው የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ፍቅር እጥብ፣ ጥርግ፤ ሙልጭ አድርገው ከልባቸው ያወጡ መናፍቃን ዳሩ ግን ክርስቲያን ነን የሚሉ ሐሰተኞች ናቸው፡፡ ስለ ጌታችን
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆን ስናነሳ የግድ ስለ እመቤታችን ማንሳት ይጠይቃል፡፡
ነገረ ማርያም የነገረ ሥጋዌ መቅድም ነውና፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጆችን ለማዳን ሰው ሲሆን በእመቤታችን በኩል ብቻ ነውና፡፡ ለዚህም አይደል! ቅዱስ ሊውስ(Saint Louis Marie de Montfort) "The Son of God became man for our salvation but only in Mary and through Mary." በማለት
የተናገረው፡፡ እንዳውም ከኢትዮጵያውያን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የውጭ
ሀገር ሊቃውንትም ስለ እመቤታችን ግልጽ ባለ መልኩ ከተናገሩት መካከል ቅዱስ ጀርማነስ ዘቁስጥንጥንያ(Saint
Germanus of Constantinople) ስለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሲናገር "ድንግል ሆይ ያለ አንቺ ከክፉ ሁሉ ማንም ማምለጥ አይችልም፤ ድንግል እናት ሆይ! ማንም ምሕረት ቢያገኝ ባንቺ በኩል ነው፤ ምልዕተ ጸጋ፣ ምልዕተ ክብር;
- "There is no one, O Most Holy Mary, who can know God except through thee, no one who can be saved or redeemed but through thee, O Mother of God, no one who can be delivered from dangers but through thee, O Virgin Mother,
no one who obtains mercy but through thee, O Filled- Will – All – Grace!" ብሏል፡፡
እንዳውም ሊቁ ቅዱስ አንሴለም የተባለ አንድ ሊቀ ጳጳስ (Saint Anselm, Archbishop & Doctor of the Church) የተባለ አባት "ያለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
ውዴታና ጥበቃ አንዲት ነፍስ አትድንም፡፡" ብሏል፡፡ "It is impossible to save one’s soul without devotion to
Mary and without her protection." ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ኬሊዶነስ ለተባለ ቄስ በላከው መልእክቱ ላይ (St. Gregory Nazinzen,Letter to Cledonius the priest) ደግሞ ማንም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ወላዲተ አምላክ የማይላት ያ ሰው ስለ ነገረ
እግዚአብሔርም ባእድ ነው ሲል ተናግሯል፡፡ "If anyone does not believe that Holy Mary is the Mother of God, such a one is a stranger to the Godhead."
በመጽሐፈ ቅዳሴ አንድምታ ላይም ሰራኤ ካህን መሥዋዕቱን፣ዕጣኑን፣ ማኅቶቱን(መብራቱን) ና አገልጋዮቹን ሲባርክ ያለውን ክፍል ያለውን ሲተረጉም "አልቦ ጸሎት ወአልቦ ትንባሌ እንበሌኪ
ማርያም ዘየዓርግ ሉዓሌ- እመቤቴ ማርያም ሆይ ምንም ዓይነት ጸሎትም ሆነ ልመና ያለ አንቺ አማላጅነት አያርግም፡፡" አባ ጽጌ ድንግል በማኅሌተ ጽጌ ድርሰታቸው የጠቀሱትን በማንሳት ያለ እመቤታችን አማላጅነት የሚያርግ ጸሎትም ሆነ ልመና የለም ይላል፡፡
ይኼ ማለት አንድ ኦርቶዶክሳዊ የተዋሕዶ ክርስቲያን በጸሎቱ የእመቤታችን አማላጅነት በማቃለል ቢጸልይ ጸሎቱ ግዱፉ(የተተወ) ይሆናል፤ ስለሆነም አይድንም ማለት ነው፡፡ ያለ
እመቤታችን አማላጅነት ሲልኮ እመቤታችን አማላጅ ናት፤ እግዚአብሔር ደግሞ ተማላጅ ነው ማለት ነው፡፡ የእመቤታችን ወላዲተ አምላክነት፤ አማላጅነት በአጠቃላይ ነገረ ማርያም
ደግሞ ዶግማ እንጂ ቀኖና አይደለም፡፡ የእመቤታችን ወላዲተ አምላክነት፤ አማላጅነት ወዘተ …በማመን እግዚአብሔርን ቢለምን እመቤታችን ለፍጡራን ሁሉ ለማማለድ የፈጠነች ናትና ትራዳዋለች፡፡ ጸሎቱም ዉኩፍ(ተቀባይነት ያለው) ይሆናል፤
አምላከ ቅዱሳን አምላካችን እግዚአብሔርም ጻሕቀ ልቡናውን
(የልቡናውን መሻት) ይፈጽምለታል፡፡ ለዚህም ነው ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ(St. Basil the Great) እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በእግዚአብሔር ዘንድ ስላላት ድንቅ
ተሰሚነት ሲናገር "O sinner, be not discouraged, but have recourse to Mary in all you necessities. Call her to your assistance, for such is the divine Will that she should help in every kind of necessity."
ለዚህም አይደል ኢትዮጵያውያን መጋብያነ ምሥጢር ሊቃውንተ
ቤተ ክርስቲያን "የእናት ልመና አንገት አያስቀልስ፤ ፊት አያስመልስ" የሚሉት?!!
by Zemaryam zeleke
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ጸሎት እንደሌለ ያውቃሉ?
@And_Haymanot
ብዙ የተሐድሶ መናፍቃን ያለ እመቤታችን አማላጅነት የሚያርግ ጸሎት እንደሌለ ማመን ሲከብዳቸው ይስተዋላል፡፡ አንዳንዶቹ ያለ እመቤታችን አማላጅነት የሚያርግ ጸሎት የለም የሚለው
የሆነ አባት በሆነ ግዜ የተናገረው በቅዱሳት መጻሕፍት ያልተመዘገበ አድርገው ይናገራሉ፡፡
የዚህ ዓለም ሰዎች የእግዚአብሔር መንፈሳዊ ጸጋ ርቋቸው፤በመንፈስ ድህነት ውስጥ ሲማቅቁ የሰው ልጅ መንፈሳዊ ሀብቱ ተራቁቶ ነዳይ ሆኖ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስን በቀጥታ ከባሕርይ አባቱ ከእግዚአብሔር አብ መቀበል ሲያቅታቸው፤ በመንፈሳዊነት በበለጸገችው፤ ጸጋን በተመላች
በእመቤታችን በኩል እግዚአብሔር አንድያ ልጁ ሰጠ፤ ዓለምም
ከእመቤታችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አገኘ፡፡ ሊቁ ቅዱስ አውግስጢኖስ(St. Augustine) "The world being
unworthy to receive the Son of God directly from the hands of the Father, he gave his Son to Mary for the world to receive him from her." እንዲል፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ(Saint John Eudes) እንደተናገረው "ለኢየሱስ ክርስቶስ እናት ፍቅር የሌለው ሰው እውነተኛ ክርስቲያን አይደለም- A man is no true Christian if he has no devotion to the Mother of Jesus Christ."
እንዳለው የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ፍቅር እጥብ፣ ጥርግ፤ ሙልጭ አድርገው ከልባቸው ያወጡ መናፍቃን ዳሩ ግን ክርስቲያን ነን የሚሉ ሐሰተኞች ናቸው፡፡ ስለ ጌታችን
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆን ስናነሳ የግድ ስለ እመቤታችን ማንሳት ይጠይቃል፡፡
ነገረ ማርያም የነገረ ሥጋዌ መቅድም ነውና፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጆችን ለማዳን ሰው ሲሆን በእመቤታችን በኩል ብቻ ነውና፡፡ ለዚህም አይደል! ቅዱስ ሊውስ(Saint Louis Marie de Montfort) "The Son of God became man for our salvation but only in Mary and through Mary." በማለት
የተናገረው፡፡ እንዳውም ከኢትዮጵያውያን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የውጭ
ሀገር ሊቃውንትም ስለ እመቤታችን ግልጽ ባለ መልኩ ከተናገሩት መካከል ቅዱስ ጀርማነስ ዘቁስጥንጥንያ(Saint
Germanus of Constantinople) ስለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሲናገር "ድንግል ሆይ ያለ አንቺ ከክፉ ሁሉ ማንም ማምለጥ አይችልም፤ ድንግል እናት ሆይ! ማንም ምሕረት ቢያገኝ ባንቺ በኩል ነው፤ ምልዕተ ጸጋ፣ ምልዕተ ክብር;
- "There is no one, O Most Holy Mary, who can know God except through thee, no one who can be saved or redeemed but through thee, O Mother of God, no one who can be delivered from dangers but through thee, O Virgin Mother,
no one who obtains mercy but through thee, O Filled- Will – All – Grace!" ብሏል፡፡
እንዳውም ሊቁ ቅዱስ አንሴለም የተባለ አንድ ሊቀ ጳጳስ (Saint Anselm, Archbishop & Doctor of the Church) የተባለ አባት "ያለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
ውዴታና ጥበቃ አንዲት ነፍስ አትድንም፡፡" ብሏል፡፡ "It is impossible to save one’s soul without devotion to
Mary and without her protection." ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ኬሊዶነስ ለተባለ ቄስ በላከው መልእክቱ ላይ (St. Gregory Nazinzen,Letter to Cledonius the priest) ደግሞ ማንም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ወላዲተ አምላክ የማይላት ያ ሰው ስለ ነገረ
እግዚአብሔርም ባእድ ነው ሲል ተናግሯል፡፡ "If anyone does not believe that Holy Mary is the Mother of God, such a one is a stranger to the Godhead."
በመጽሐፈ ቅዳሴ አንድምታ ላይም ሰራኤ ካህን መሥዋዕቱን፣ዕጣኑን፣ ማኅቶቱን(መብራቱን) ና አገልጋዮቹን ሲባርክ ያለውን ክፍል ያለውን ሲተረጉም "አልቦ ጸሎት ወአልቦ ትንባሌ እንበሌኪ
ማርያም ዘየዓርግ ሉዓሌ- እመቤቴ ማርያም ሆይ ምንም ዓይነት ጸሎትም ሆነ ልመና ያለ አንቺ አማላጅነት አያርግም፡፡" አባ ጽጌ ድንግል በማኅሌተ ጽጌ ድርሰታቸው የጠቀሱትን በማንሳት ያለ እመቤታችን አማላጅነት የሚያርግ ጸሎትም ሆነ ልመና የለም ይላል፡፡
ይኼ ማለት አንድ ኦርቶዶክሳዊ የተዋሕዶ ክርስቲያን በጸሎቱ የእመቤታችን አማላጅነት በማቃለል ቢጸልይ ጸሎቱ ግዱፉ(የተተወ) ይሆናል፤ ስለሆነም አይድንም ማለት ነው፡፡ ያለ
እመቤታችን አማላጅነት ሲልኮ እመቤታችን አማላጅ ናት፤ እግዚአብሔር ደግሞ ተማላጅ ነው ማለት ነው፡፡ የእመቤታችን ወላዲተ አምላክነት፤ አማላጅነት በአጠቃላይ ነገረ ማርያም
ደግሞ ዶግማ እንጂ ቀኖና አይደለም፡፡ የእመቤታችን ወላዲተ አምላክነት፤ አማላጅነት ወዘተ …በማመን እግዚአብሔርን ቢለምን እመቤታችን ለፍጡራን ሁሉ ለማማለድ የፈጠነች ናትና ትራዳዋለች፡፡ ጸሎቱም ዉኩፍ(ተቀባይነት ያለው) ይሆናል፤
አምላከ ቅዱሳን አምላካችን እግዚአብሔርም ጻሕቀ ልቡናውን
(የልቡናውን መሻት) ይፈጽምለታል፡፡ ለዚህም ነው ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ(St. Basil the Great) እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በእግዚአብሔር ዘንድ ስላላት ድንቅ
ተሰሚነት ሲናገር "O sinner, be not discouraged, but have recourse to Mary in all you necessities. Call her to your assistance, for such is the divine Will that she should help in every kind of necessity."
ለዚህም አይደል ኢትዮጵያውያን መጋብያነ ምሥጢር ሊቃውንተ
ቤተ ክርስቲያን "የእናት ልመና አንገት አያስቀልስ፤ ፊት አያስመልስ" የሚሉት?!!
by Zemaryam zeleke
@And_Haymanot
@And_Haymanot
መሠረተ ያሬድ ሰ/ት/ቤት ዘአሣሣ:
†††አውጣኝ አውጣኝ†††
በብፁዕ አቡነ ሰላማ /የቀድሞ የባሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ/
@Meserete_Yared_Asasa
✍ በአንድ ዱር ጫካ ውስጥ አንበሳ በጣም ተርቦ አቤቱ ፈጣሪዬ የእለት ምግቤን ስጠኝ አብላኝ አብላኝ እያለ ይፀልያል ዱክላም ተራራው ጫፍ ላይ ሆኖ አንበሳውን አይቶ በመፍራት አቤቱ ፈጣሪዬ ከዚህ ጩኸት አውጣኝ አውጣኝ እያለ እየፀለየ ሁለቱም ይሮጣሉ አንበሳው አብላኝ ዱክላው አውጣኝ በማለት ሲሣደዱ በመሐል ጠግቦ የተኛን ዓሣማ አንበሳው ያገኘዋል አንበሳውም ተመስገን ጌታዬ ብሎ ያን አሣማ በላው ይባላል።
@Meserete_Yared_Asasa
❖ እንግዲህ ከዚህ ምሣሌ ልንወስድ የሚገባን አንበሣም አብላኝ ብሎ ፀሎት በማድረሱ ምግቡን እንዳገኘና ዱኩላም አውጣኝ ብሎ በማለቱ ፀልዮ ከፈተና እንደወጣ እንመለከታለን ነገር ግን ፀሎት ሣያደርግ እንደበላ ጠግቦ የተኛው ዓሣማ እንደተበላ ተገንዝበናል እኛም ዛሬ እንደዚህ ዓሣማ በሰይጣን ዲያብሎስ ከመዋጣችን አስቀድሞ ብርቱ ፀሎት ያስፈልገናል።
#አውጣኝ_ያለው_ወጣ_አብላኝ_ያለው_በላ
#ተኝቶ_ያለው_ዓሣማ_ተበላ
ምንጭ፦ የአቡነ ሰላማ መጽሐፈ ታሪክ ከነትምህርታቸው ገጽ 50-51
@Meserete_Yared_Asasa
@Meserete_Yared_Asasa
†††አውጣኝ አውጣኝ†††
በብፁዕ አቡነ ሰላማ /የቀድሞ የባሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ/
@Meserete_Yared_Asasa
✍ በአንድ ዱር ጫካ ውስጥ አንበሳ በጣም ተርቦ አቤቱ ፈጣሪዬ የእለት ምግቤን ስጠኝ አብላኝ አብላኝ እያለ ይፀልያል ዱክላም ተራራው ጫፍ ላይ ሆኖ አንበሳውን አይቶ በመፍራት አቤቱ ፈጣሪዬ ከዚህ ጩኸት አውጣኝ አውጣኝ እያለ እየፀለየ ሁለቱም ይሮጣሉ አንበሳው አብላኝ ዱክላው አውጣኝ በማለት ሲሣደዱ በመሐል ጠግቦ የተኛን ዓሣማ አንበሳው ያገኘዋል አንበሳውም ተመስገን ጌታዬ ብሎ ያን አሣማ በላው ይባላል።
@Meserete_Yared_Asasa
❖ እንግዲህ ከዚህ ምሣሌ ልንወስድ የሚገባን አንበሣም አብላኝ ብሎ ፀሎት በማድረሱ ምግቡን እንዳገኘና ዱኩላም አውጣኝ ብሎ በማለቱ ፀልዮ ከፈተና እንደወጣ እንመለከታለን ነገር ግን ፀሎት ሣያደርግ እንደበላ ጠግቦ የተኛው ዓሣማ እንደተበላ ተገንዝበናል እኛም ዛሬ እንደዚህ ዓሣማ በሰይጣን ዲያብሎስ ከመዋጣችን አስቀድሞ ብርቱ ፀሎት ያስፈልገናል።
#አውጣኝ_ያለው_ወጣ_አብላኝ_ያለው_በላ
#ተኝቶ_ያለው_ዓሣማ_ተበላ
ምንጭ፦ የአቡነ ሰላማ መጽሐፈ ታሪክ ከነትምህርታቸው ገጽ 50-51
@Meserete_Yared_Asasa
@Meserete_Yared_Asasa
✍ "ማርያም የሐናን ወተት እየጠባሽ ወደ ቤተ መቅደስ በገባሽ ጊዜ ያገኘሽ ብቸኝነት ያሳዝነኛል፤ ዳግመኛም በደመና የሚመላለስ ደመናን የሚረግጥ የእሳት አበባ ፋኑኤል ከጓደኞቹ መላእክት ጋር መናን እየመገበሽ በንጽሕና የማደግሽ ተአምር ደስ ያሰኘኛል፡፡"
# አባ_ጽጌ_ድንግል
@Meserete_Yared_Asasa
@Meserete_Yared_Asasa
# አባ_ጽጌ_ድንግል
@Meserete_Yared_Asasa
@Meserete_Yared_Asasa
ኢያቄም ወሐና እናት አባትሽ
ቤተ እግዚአብሔር ወስደው ስዕለት የሰጡሽ
መና ከሰማያት የወረደልሽ
ፍጹም ድንግል የሆንሽ ማርያም አንቺ ነሽ
ኦ /፬/ እመ ክርስቶስ ማርያም አንቺ ነሽ
ኦ /፬/ ወላዲተ አምላክ ድንግል አንቺ ነሽ
@Meserete_Yared_Asasa
✍ እንኳን ለበዓታ ማርያም ወርሃዊ በዓል አደረሰን!!! አደረሳችው!!!
@Meserete_Yared_Asasa
@Meserete_Yared_Asasa
ቤተ እግዚአብሔር ወስደው ስዕለት የሰጡሽ
መና ከሰማያት የወረደልሽ
ፍጹም ድንግል የሆንሽ ማርያም አንቺ ነሽ
ኦ /፬/ እመ ክርስቶስ ማርያም አንቺ ነሽ
ኦ /፬/ ወላዲተ አምላክ ድንግል አንቺ ነሽ
@Meserete_Yared_Asasa
✍ እንኳን ለበዓታ ማርያም ወርሃዊ በዓል አደረሰን!!! አደረሳችው!!!
@Meserete_Yared_Asasa
@Meserete_Yared_Asasa
በሳውላ ማረሚያ ቤት የሚገኙ 35 ፕሮቴስታንት የነበሩ የሕግ ታራሚዎች ተዋሕዶን ተቀብለው ሥርዓተ ጥምቀታቸው በቅዱስ እስጢፋኖስ ክብረ በዓል ተፈፆሞላቸዋል።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
#update የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነ ምህረት አንድነት ገዳም ሙዚየምን ዛሬ አስመረቀ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ፥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅርሶችን ጠብቃና ተንከባክባ እዚህ አድርሳለች ብለዋል። አሁን ያለው ትውልድ ተንከባክቦ የመጠበቅና ለትውልድ የማስተላለፍ ሃላፊነት አለበት ሲሉም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ቅርስና ጥናት ጥበቃ ባለስልጣን ዳሬክተር አቶ ዮናስ ደስታ በበኩላቸው፥ ሙዝየሙን ለማዘመንና ወደ ዲጅታል ላይብረሪ ለማሳደግ በቀጣይ እንደሚሰራ ገልፀዋል። በሐመረ ኖኅ ሙዚየም ውስጥ የኢትጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የታሪክ ጉዞና የገዳማት ታሪክ በከፊል የሚያሳዩ እንዲሁም በርካታ ንዋየ ቅድሳት፣ መጽሀፍት፣ አልባሳትና የተለያዩ ረጅም እድሜን ያስቆጠሩ መገልገያ ቁሳቁሶች ይገኛሉ።
Via FBC
@And_Haymanot
@And_Haymanot
Via FBC
@And_Haymanot
@And_Haymanot
"በዓለ ጥምቀት"
@And_Haymanot
ክፍል ፩
☞1. ትርጉም
ጥምቀት በጽርዕ ቋንቋ ኤጲፋኒ፣ በግእዝ አስተርእዮ፣ በአማርኛ
መገለጥ ፡ይባላል። ቃሉ በቀጥታ ሲተረጎም በውኃ ውስጥ ገብቶ መውጣት፣ መነከር፣ መዘፈቅ፣ መጥለቅ ማለት ነው። በምሥጢረ ትርጉሙ ግን ጥምቀት ከሰባቱ ምጥጢራተ ቤተ
ክርስቲያን /ጥምቀት፣ ሜሮን፣ ቁርባን፣ ንስሐ፣ ክህነት፣ ተክሊለና ቀንዲል/ አንዱና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኒቆዲሞስ በዮሐንስ ወንጌል በምዕራፍ 3 ቁጥር 5 ላይ “… ሰው ከውኃና
ከመንፈስ ቅዱስ ካልተወለደ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም”ብሎ እንደተናገረው ከውኃና ከመንፈስ ተወልደን የሥላሴን ልጅነት የምናገኝበት፣ መንግሥተ ሰማያት
የምንገባበት፣ ኃጢአታችን የሚደመሰስበትና ድኅነትን
የምናገኝበት ዐቢይ ምሥጢር ነው። ጥምቀት በምሥጢረ ሥላሴና በምሥጢረ ሥጋዌ አምኖ ለሚቀበለው ሰው ሁሉ ለኃጢአት መደምሰሻ፣ ከሥላሴ የጸጋ ልጅነት ለመቀበልና
የእግዚአብሔርን መንግሥት ለመውረስ የተሰጠ ልዩ የሕይወት መንገድ ነው።
☞2. አመጣጥ
የምሥጢረ ጥምቀት መሥራቹ ራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ነገር ግን ከጌታችን ጥምቀት በፊት
አይሁድ ለመንጻትና ለኃጢአት ሥርየት /ይቅርታ/ የሚጠመቁት ጥምቀት ነበራቸው። ይኸውም እግዚአብሔር በረድኤት በሚገለጥባቸው የተቀደሱ ዕለታትና ቦታዎች ሁሉ ሰውነትንና
ልብስን ማጠብ፣ የእግዚአብሔር ቤት መገልገያ የሆኑ ዕቃዎችን ሁሉ ማጠብ ማንጻት ሥርዓትና ልምድ ነበር። የእግዚአብሔር ፈቃድ ያለበት አሠራር ነበር። ወደ ቤተ እግዚአብሔርም
ከመቅረባቸውና ለተቀደሰው አገልግሎት ከመግባታቸው አስቀድመው እግሮቻቸውንና እጆቸቸውን የመታጠብ ግዴታም ነበራቸው፡ ሰውነታቸውን የመታጠብ ግዴታም ነበራቸው።
ሰውነታቸውን ከአፍአዊ /ከውጫዊ/ እድፍ በማጠብና ንጹሕ በማድረግ በባሕርዩ ንጹሕና ቅዱስ በሆነው አምላክ ፊት ውስጣዊ ሕይወትን ንጹሕ አድርጎ የመቅረብን ሥርዓትና ምሥጢር የሚያመለክት ልማድ ነበር፦ “አሮንና ልጆቹንም ወደ መገናኛቸው ድንኳን ታቀርባቸዋለህ፤ በውኃም ታጥባቸዋለህ፣
ሙሴም አሮንና ልጆቹን አቀረበ። በውኃም አጠባቸው” /ዘዳ 29፡
4፤ ዘሌ 8፡6/። ዮሐንስ በዮርዳኖስ በኢየሩሳሌም ይሁዳ አውራጃዎች ከጌታ
ቀደም ብሎ ተልኮ “መንግሥተ ሰማያት በልጅነት፣ ልጅነት በእምትና በጥምቀት ልትሰጠ ቀርባለችና ንስሐ ግቡ፣ ከኃጢአትና ከበደል ተመለሱ” እያለ ለኃጢአት ሥርየት ለንስሐ ያጠምቅ ነበር። ብዙ ሰዎችም ኃጢአታቸውን እየተናዘዙ ከሱ ይጠመቁ ነበር። በብሉየ ኪዳን ዘመን በርከት ያሉ የጥምቀት
ምሳሌዎችን እናገኛለን። ከእነዚህ ውስጥ የተወሰኑትን ለመመልከት፦
✞ 1ኛ) አብርሃም ዮርዳኖስን ተሻግሮ ወደ መልከ ጼዴቅ መሄዱ የጥምቀት ምሳሌ ነው። አብርሃም የምዕመናን፣ መልከ ጼዴቅም የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌዎች ናቸው። /ዘፍ 14፡17/
✞ 2ኛ) ኢዮብ በዮርዳኖስ ተጠምቆ ከደዌው ተፈውሷል። ይህም ምእመናን ተጠምቀው ከደዌ ሥጋ ከደዌ ነፍስ የመፈወሳቸው / ከመርገመ ሥጋ ከመርገመ ነፍስ/ የመዳናቸው ምሳሌ ነው።
✞ 3ኛ) ንዕማን ሶርያዊ ተጠምቆ ከለምጹ ድኗል። /2ኛ ነገ 5፡14/። ይኸውኛውም ምእመናን ተጠምቀው ከመርገመ ሥጋ
ከመርገመ ነፍስ የመዳናቸው ምሳሌ ነው።
✞ 4ኛ) የኖኅ መርከብ የጥምቀት ምሳሌ ነው። /ዘፍ 6፡13/። ይህንንም ሐዋርያው ቅዱስ ጥሮስ “ጥቂቶች ማለት ስምንት ነፍስ በውኃ የዳኑበት መርከብ ሲዘጋጅ የእግዚአብሔር ትዕግሥት በኖኅ ዘመን በቆየ ጊዜ ደግሞ አልታዘዙም። ይህም ውኃ
ጥምቀት ምሳሌው ሆኖ አሁን ያድነናል። የሰውነትን እድፍ ማስወገድ አይደለም፣ ለእግዚአብሔር የበጎ ኅሊና ልማድ ነው
እንጂ።” ሲል ተርጉሞታል። /1ኛ ጴጥ 3፡20/
✞ 5ኛ) እሥራኤል በደመና ተጋርደው ቀይ ባሕርን መሻገራቸው የጥምቀት ምሳሌ ነው። /ዘፀ 13፡21/ ። ይኽንንም ሓዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “አባቶቻችን ሁሉ ከደመና በታች ነበሩ። ሁሉም
ሙሴን ይተባበሩ ዘንድ በደመናና በባሕር ተጠመቁ” ሲል ተርጉሞታል። /1ቆሮ 10፡2/
✞ 6ኛ) አብርሃም ሕግ ሆኖ የተሰጠው ግዝረት የጥምቀት ምሳሌ ነው። አብርሃም ካረጀ በኋላ ቢገረዝም ልጆቹ ግን በተወለዱ በስምንተኛው ቀን እንዲገረዙ እግዚአበሔር አዝዞ ነበር። /ዘፍ 17፡9/። ይኽንንም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “በእጅ ባልተደረገ
መገረዝ በእርሱ ሆናችሁ ደግሞ ተገረዛችሁ” ሲል ተርጉሞታል። /ቆላ 1፡11/። እንግዲህ ጥምቀት የግዝረት
ምሳሌ በመሆኑ በኦሪቱ ዘምን ቀን ተወስኖ ሕፃናቱ ይገረዙ እንደ ነበረ በአዲስ ኪዳንም ተወስኖ ሕፃናት ወንዶች በተወለዱ በአርባኛው ቀን፣ ሴቶቹ ደግሞ በተወለዱ በስማንያኛው ቀን
ይጠመቃሉ። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጠመቀው በ5531 ዓመተ ዓለም፣
በዘመነ ሉቃስ፣ ማክሰኞ ጥር 11 ቀን ኬሊቱ በ10ኛው ሰዓት ነበር፡ /ፍት ነገ አንቀጽ 19፤ ዲድስቅ 29፤ ተረፈ ቄርሰሎስ/ በተጠመቀ ጊዜ 30 ዓመት ከ13 ቀን ነበር። /ሉቃ 3፡23/
ለመሆኑ ጌታችን ለምን በ30 ዓመቱ ተጠመቀ? በብሉይ ኪዳን ሥርዓትና ልማድ ካህናት ለቤተ እግዚአብሔር
ተልዕኮና መንፈሳዊ አገልግሎት ከ30 ዓመት ዕድሜ በፊት አደባባይ አይወጡም ነበር። እጅግ አስፈላጊ እንኳ ቢሆን ከ20 እና 25 ዓመት አስቀድሞ ለአገልግሎት መሰየም ለማድ
አልነበረም። የቤተ እግዚአብሔር አገልጋዮች በዕድሜና በዕውቀት የበሰሉ፣ በጠባይና በሥራ ልምድ የተፈተኑ፣ ተልእኮአቸውን በብቃት ለመወጣት በተገልጋዩ ሕዝብ ዘንድ
የተመሰከረላቸው መሆን ነበረባቸው። /ዘኁ 4፡3፤ 1ኛ ዜና መዋ. 23፡24፤ ዕዝ 3፡8፤ 1ኛ ጢሞ 3፡6-10/ ያንን ሥርዓት ለመፈጸም ጌታችን የተጠመቀውና ለትምህርተ ወንጌል የተገለጠው በ30 ዓመቱ ነበር። ዮሐንስ መጥምቅም
የጌታን መምጣት ለማወጅ በዮርዳኖስ ይሁዳ ምድረ በዳዎች ወጥቶ የታየው ከ30 ዓመት ዕድሜው በኋላ ነው።
ሌላው ዐቢይ ምክንያት የሰው ሁሉ መጀመሪያ አዳም የ30 ዓመት ጎልማሳ ሆኖ ተፈጥሮ በ40 ቀን ተሰጥቶት ያስወሰደውን ልጅነቱን ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ለማስመስከር የአዳም ልጆችን
የዕዳ ደብዳቤ ለመደምሰስና በስሕተት የጠፋውን የልጅነት ክብር ለመመለስ ነው። ጌታ ተጠምቆ ከውኃው ከወጣ በኋላ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ወርዶ በራሱ ለይ በማረፉ አብ በደመና
“ይህ ልጄ ነው” ብሎ ሲመሰክርለት የምሥጢረ ሥላሴ አንድነትና ሦስትነት በጉልህ ተረጋግጧል። /ማቴ 3፡16/
ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክ ሲሆን በአገልጋዩ በቅዱስ ዮሐንስ እጅ ይጠመቅ ዘንድ በፍጹም ትህትና ከገሊላ ወደ ዮረዳኖስ መጣ። ይህንንም ያደረገልን አብነት
ሊሆነን ነው። ምክንያቱም ጌታችን ቅዱስ ዮሐንስን “መጥተህ አጥምቀኝ” ብሎት ቢሆን ኖሮ ነገ ተነጎዲያ ነገሥታቱና መኳንንቱ ካህናቱን “መጥታችሁ አጥምቁን” ባሉ ነበር። ስለዚህ እንዲህ
እንዳይሆን ነው ጌታችን “ጌታ” ሲሆን በባሪያዬ እጅ እንደተጠመቅሁ እናንተም ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄዳችሁ በካህናት
እጅ ተጠመቁ ሲል ነው። ቅደስ ዮሐንስ ጌታችን በእርሱ እጅ ለመጠመቅ ወደ እርሱ በመጣ ጊዜ “እኔ ባሪያህ በአንተ በጌታዬ እጅ ልጠመቅ ያስፈልገኛል እንጂ አንተ በእኔ በባሪያህ እጅ
ትጠመቅ ዘንድ እንዴት ወደ እኔ ትመጣለህ?” አለው። ጌታችንም
መልሶ “አሁንስ ፍቀድልኝ፣ እንግዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና /ትንቢተ ነቢያትን እንዲህ ልንፈጽም ያስፈልጋል/”
አለው። በዚህን ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ ጌታችንን አጠመቀው። በዚህም “መጥምቀ መለኮት” ተብሎ የቅዱስ ዮሐንስ ገናንነቱ ይነገራል፣...👇👇👇
@And_Haymanot
ክፍል ፩
☞1. ትርጉም
ጥምቀት በጽርዕ ቋንቋ ኤጲፋኒ፣ በግእዝ አስተርእዮ፣ በአማርኛ
መገለጥ ፡ይባላል። ቃሉ በቀጥታ ሲተረጎም በውኃ ውስጥ ገብቶ መውጣት፣ መነከር፣ መዘፈቅ፣ መጥለቅ ማለት ነው። በምሥጢረ ትርጉሙ ግን ጥምቀት ከሰባቱ ምጥጢራተ ቤተ
ክርስቲያን /ጥምቀት፣ ሜሮን፣ ቁርባን፣ ንስሐ፣ ክህነት፣ ተክሊለና ቀንዲል/ አንዱና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኒቆዲሞስ በዮሐንስ ወንጌል በምዕራፍ 3 ቁጥር 5 ላይ “… ሰው ከውኃና
ከመንፈስ ቅዱስ ካልተወለደ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም”ብሎ እንደተናገረው ከውኃና ከመንፈስ ተወልደን የሥላሴን ልጅነት የምናገኝበት፣ መንግሥተ ሰማያት
የምንገባበት፣ ኃጢአታችን የሚደመሰስበትና ድኅነትን
የምናገኝበት ዐቢይ ምሥጢር ነው። ጥምቀት በምሥጢረ ሥላሴና በምሥጢረ ሥጋዌ አምኖ ለሚቀበለው ሰው ሁሉ ለኃጢአት መደምሰሻ፣ ከሥላሴ የጸጋ ልጅነት ለመቀበልና
የእግዚአብሔርን መንግሥት ለመውረስ የተሰጠ ልዩ የሕይወት መንገድ ነው።
☞2. አመጣጥ
የምሥጢረ ጥምቀት መሥራቹ ራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ነገር ግን ከጌታችን ጥምቀት በፊት
አይሁድ ለመንጻትና ለኃጢአት ሥርየት /ይቅርታ/ የሚጠመቁት ጥምቀት ነበራቸው። ይኸውም እግዚአብሔር በረድኤት በሚገለጥባቸው የተቀደሱ ዕለታትና ቦታዎች ሁሉ ሰውነትንና
ልብስን ማጠብ፣ የእግዚአብሔር ቤት መገልገያ የሆኑ ዕቃዎችን ሁሉ ማጠብ ማንጻት ሥርዓትና ልምድ ነበር። የእግዚአብሔር ፈቃድ ያለበት አሠራር ነበር። ወደ ቤተ እግዚአብሔርም
ከመቅረባቸውና ለተቀደሰው አገልግሎት ከመግባታቸው አስቀድመው እግሮቻቸውንና እጆቸቸውን የመታጠብ ግዴታም ነበራቸው፡ ሰውነታቸውን የመታጠብ ግዴታም ነበራቸው።
ሰውነታቸውን ከአፍአዊ /ከውጫዊ/ እድፍ በማጠብና ንጹሕ በማድረግ በባሕርዩ ንጹሕና ቅዱስ በሆነው አምላክ ፊት ውስጣዊ ሕይወትን ንጹሕ አድርጎ የመቅረብን ሥርዓትና ምሥጢር የሚያመለክት ልማድ ነበር፦ “አሮንና ልጆቹንም ወደ መገናኛቸው ድንኳን ታቀርባቸዋለህ፤ በውኃም ታጥባቸዋለህ፣
ሙሴም አሮንና ልጆቹን አቀረበ። በውኃም አጠባቸው” /ዘዳ 29፡
4፤ ዘሌ 8፡6/። ዮሐንስ በዮርዳኖስ በኢየሩሳሌም ይሁዳ አውራጃዎች ከጌታ
ቀደም ብሎ ተልኮ “መንግሥተ ሰማያት በልጅነት፣ ልጅነት በእምትና በጥምቀት ልትሰጠ ቀርባለችና ንስሐ ግቡ፣ ከኃጢአትና ከበደል ተመለሱ” እያለ ለኃጢአት ሥርየት ለንስሐ ያጠምቅ ነበር። ብዙ ሰዎችም ኃጢአታቸውን እየተናዘዙ ከሱ ይጠመቁ ነበር። በብሉየ ኪዳን ዘመን በርከት ያሉ የጥምቀት
ምሳሌዎችን እናገኛለን። ከእነዚህ ውስጥ የተወሰኑትን ለመመልከት፦
✞ 1ኛ) አብርሃም ዮርዳኖስን ተሻግሮ ወደ መልከ ጼዴቅ መሄዱ የጥምቀት ምሳሌ ነው። አብርሃም የምዕመናን፣ መልከ ጼዴቅም የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌዎች ናቸው። /ዘፍ 14፡17/
✞ 2ኛ) ኢዮብ በዮርዳኖስ ተጠምቆ ከደዌው ተፈውሷል። ይህም ምእመናን ተጠምቀው ከደዌ ሥጋ ከደዌ ነፍስ የመፈወሳቸው / ከመርገመ ሥጋ ከመርገመ ነፍስ/ የመዳናቸው ምሳሌ ነው።
✞ 3ኛ) ንዕማን ሶርያዊ ተጠምቆ ከለምጹ ድኗል። /2ኛ ነገ 5፡14/። ይኸውኛውም ምእመናን ተጠምቀው ከመርገመ ሥጋ
ከመርገመ ነፍስ የመዳናቸው ምሳሌ ነው።
✞ 4ኛ) የኖኅ መርከብ የጥምቀት ምሳሌ ነው። /ዘፍ 6፡13/። ይህንንም ሐዋርያው ቅዱስ ጥሮስ “ጥቂቶች ማለት ስምንት ነፍስ በውኃ የዳኑበት መርከብ ሲዘጋጅ የእግዚአብሔር ትዕግሥት በኖኅ ዘመን በቆየ ጊዜ ደግሞ አልታዘዙም። ይህም ውኃ
ጥምቀት ምሳሌው ሆኖ አሁን ያድነናል። የሰውነትን እድፍ ማስወገድ አይደለም፣ ለእግዚአብሔር የበጎ ኅሊና ልማድ ነው
እንጂ።” ሲል ተርጉሞታል። /1ኛ ጴጥ 3፡20/
✞ 5ኛ) እሥራኤል በደመና ተጋርደው ቀይ ባሕርን መሻገራቸው የጥምቀት ምሳሌ ነው። /ዘፀ 13፡21/ ። ይኽንንም ሓዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “አባቶቻችን ሁሉ ከደመና በታች ነበሩ። ሁሉም
ሙሴን ይተባበሩ ዘንድ በደመናና በባሕር ተጠመቁ” ሲል ተርጉሞታል። /1ቆሮ 10፡2/
✞ 6ኛ) አብርሃም ሕግ ሆኖ የተሰጠው ግዝረት የጥምቀት ምሳሌ ነው። አብርሃም ካረጀ በኋላ ቢገረዝም ልጆቹ ግን በተወለዱ በስምንተኛው ቀን እንዲገረዙ እግዚአበሔር አዝዞ ነበር። /ዘፍ 17፡9/። ይኽንንም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “በእጅ ባልተደረገ
መገረዝ በእርሱ ሆናችሁ ደግሞ ተገረዛችሁ” ሲል ተርጉሞታል። /ቆላ 1፡11/። እንግዲህ ጥምቀት የግዝረት
ምሳሌ በመሆኑ በኦሪቱ ዘምን ቀን ተወስኖ ሕፃናቱ ይገረዙ እንደ ነበረ በአዲስ ኪዳንም ተወስኖ ሕፃናት ወንዶች በተወለዱ በአርባኛው ቀን፣ ሴቶቹ ደግሞ በተወለዱ በስማንያኛው ቀን
ይጠመቃሉ። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጠመቀው በ5531 ዓመተ ዓለም፣
በዘመነ ሉቃስ፣ ማክሰኞ ጥር 11 ቀን ኬሊቱ በ10ኛው ሰዓት ነበር፡ /ፍት ነገ አንቀጽ 19፤ ዲድስቅ 29፤ ተረፈ ቄርሰሎስ/ በተጠመቀ ጊዜ 30 ዓመት ከ13 ቀን ነበር። /ሉቃ 3፡23/
ለመሆኑ ጌታችን ለምን በ30 ዓመቱ ተጠመቀ? በብሉይ ኪዳን ሥርዓትና ልማድ ካህናት ለቤተ እግዚአብሔር
ተልዕኮና መንፈሳዊ አገልግሎት ከ30 ዓመት ዕድሜ በፊት አደባባይ አይወጡም ነበር። እጅግ አስፈላጊ እንኳ ቢሆን ከ20 እና 25 ዓመት አስቀድሞ ለአገልግሎት መሰየም ለማድ
አልነበረም። የቤተ እግዚአብሔር አገልጋዮች በዕድሜና በዕውቀት የበሰሉ፣ በጠባይና በሥራ ልምድ የተፈተኑ፣ ተልእኮአቸውን በብቃት ለመወጣት በተገልጋዩ ሕዝብ ዘንድ
የተመሰከረላቸው መሆን ነበረባቸው። /ዘኁ 4፡3፤ 1ኛ ዜና መዋ. 23፡24፤ ዕዝ 3፡8፤ 1ኛ ጢሞ 3፡6-10/ ያንን ሥርዓት ለመፈጸም ጌታችን የተጠመቀውና ለትምህርተ ወንጌል የተገለጠው በ30 ዓመቱ ነበር። ዮሐንስ መጥምቅም
የጌታን መምጣት ለማወጅ በዮርዳኖስ ይሁዳ ምድረ በዳዎች ወጥቶ የታየው ከ30 ዓመት ዕድሜው በኋላ ነው።
ሌላው ዐቢይ ምክንያት የሰው ሁሉ መጀመሪያ አዳም የ30 ዓመት ጎልማሳ ሆኖ ተፈጥሮ በ40 ቀን ተሰጥቶት ያስወሰደውን ልጅነቱን ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ለማስመስከር የአዳም ልጆችን
የዕዳ ደብዳቤ ለመደምሰስና በስሕተት የጠፋውን የልጅነት ክብር ለመመለስ ነው። ጌታ ተጠምቆ ከውኃው ከወጣ በኋላ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ወርዶ በራሱ ለይ በማረፉ አብ በደመና
“ይህ ልጄ ነው” ብሎ ሲመሰክርለት የምሥጢረ ሥላሴ አንድነትና ሦስትነት በጉልህ ተረጋግጧል። /ማቴ 3፡16/
ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክ ሲሆን በአገልጋዩ በቅዱስ ዮሐንስ እጅ ይጠመቅ ዘንድ በፍጹም ትህትና ከገሊላ ወደ ዮረዳኖስ መጣ። ይህንንም ያደረገልን አብነት
ሊሆነን ነው። ምክንያቱም ጌታችን ቅዱስ ዮሐንስን “መጥተህ አጥምቀኝ” ብሎት ቢሆን ኖሮ ነገ ተነጎዲያ ነገሥታቱና መኳንንቱ ካህናቱን “መጥታችሁ አጥምቁን” ባሉ ነበር። ስለዚህ እንዲህ
እንዳይሆን ነው ጌታችን “ጌታ” ሲሆን በባሪያዬ እጅ እንደተጠመቅሁ እናንተም ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄዳችሁ በካህናት
እጅ ተጠመቁ ሲል ነው። ቅደስ ዮሐንስ ጌታችን በእርሱ እጅ ለመጠመቅ ወደ እርሱ በመጣ ጊዜ “እኔ ባሪያህ በአንተ በጌታዬ እጅ ልጠመቅ ያስፈልገኛል እንጂ አንተ በእኔ በባሪያህ እጅ
ትጠመቅ ዘንድ እንዴት ወደ እኔ ትመጣለህ?” አለው። ጌታችንም
መልሶ “አሁንስ ፍቀድልኝ፣ እንግዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና /ትንቢተ ነቢያትን እንዲህ ልንፈጽም ያስፈልጋል/”
አለው። በዚህን ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ ጌታችንን አጠመቀው። በዚህም “መጥምቀ መለኮት” ተብሎ የቅዱስ ዮሐንስ ገናንነቱ ይነገራል፣...👇👇👇
👆👆👆በዓለ ጥምቀት...
ጌታችንም በባርያው እጅ በመጠመቁ ፍፁም
ትኅትናው ይነገርለታል። ጌታችን በዮርዳኖስ የተጠመቀው ልጅነትን የምታሰጥ ጥምቀትን ባርኮ ቀድሶ ሊሰጠን እንጂ ክብር እንዲሆነው አይደለም። ምክንያቱም እርሱ እከብር አይል ክቡር፣ እጸድቅ አይል ጻድቅ
ነውና። ቅዱስ ዮሐንስ ጌታችንን ምን እያለ እንደሚያጠምቅ አልገባውም
ነበር፡ በዚህም ምከንያት ጌታችንን “ጌታ ሆይ ሌላውን በአንተ ስም በባሕርይ አባትህ በአብ ስም፣ በባሕርይ ሕይወትህ በመንፈስ ቅዱሰ ስም አጠምቃለሁ። አንተንስ የማጠምቀው
በማን ነው?” ብሎ ጠየቀው። ጌታችንም “ወልዱ ለቡሩክ ከሣቴ ብርሃን ተሣሃለነ እግዚኦ፣ አንተ ካህኑ ለዓለም በከመ ሢመቱ ለመልከጼዴቅ፣ የቡሩክ አብ ልጅ ቡሩክ ወልድ ብርሃንን የምትገልጥ ይቅር በለን። እንደ መልከጼዴቅ ክህነት አንተ
ለዘለዓለም ካህን ነህ” እያልክ አጥምቀኝ ብሎታል። ጌታችን በተጠመቀ ጊዜ ምሥጢረ ሥላሴ ተገልጧል። መንፈስ
ቅዱስ በተለየ አካሉ በርግብ አምሳል ወረደ፤ አብም በተለየ አካሉ በደመና ሆኖ በማዕከለ ዮርዳኖስ የቆመውን ኢየሱስ
ክርስቶስን መለኮትን ከሥጋ ሳይለያይ አንድ አድርጎ “የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት” አለ። ምክንያቱም በተለየ አካሉ ሰው ሆኖ በዮርዳኖስ የቆመው ኢየሲስ ክርስቶስ በተዋሕዶ አንድ
አካል አንድ ባሕርይ ሆኖአልና። ተገልጦ የማያውቅ ምሥጢር ተገልጧል። የመንግሥተ ሰማያት በር ይከፈትላችኋል ማለት ነው።
ለመሆኑ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀትን ለምን በዮርዳኖስ አደረገው? ይቆየን ...
ጌታችንም በባርያው እጅ በመጠመቁ ፍፁም
ትኅትናው ይነገርለታል። ጌታችን በዮርዳኖስ የተጠመቀው ልጅነትን የምታሰጥ ጥምቀትን ባርኮ ቀድሶ ሊሰጠን እንጂ ክብር እንዲሆነው አይደለም። ምክንያቱም እርሱ እከብር አይል ክቡር፣ እጸድቅ አይል ጻድቅ
ነውና። ቅዱስ ዮሐንስ ጌታችንን ምን እያለ እንደሚያጠምቅ አልገባውም
ነበር፡ በዚህም ምከንያት ጌታችንን “ጌታ ሆይ ሌላውን በአንተ ስም በባሕርይ አባትህ በአብ ስም፣ በባሕርይ ሕይወትህ በመንፈስ ቅዱሰ ስም አጠምቃለሁ። አንተንስ የማጠምቀው
በማን ነው?” ብሎ ጠየቀው። ጌታችንም “ወልዱ ለቡሩክ ከሣቴ ብርሃን ተሣሃለነ እግዚኦ፣ አንተ ካህኑ ለዓለም በከመ ሢመቱ ለመልከጼዴቅ፣ የቡሩክ አብ ልጅ ቡሩክ ወልድ ብርሃንን የምትገልጥ ይቅር በለን። እንደ መልከጼዴቅ ክህነት አንተ
ለዘለዓለም ካህን ነህ” እያልክ አጥምቀኝ ብሎታል። ጌታችን በተጠመቀ ጊዜ ምሥጢረ ሥላሴ ተገልጧል። መንፈስ
ቅዱስ በተለየ አካሉ በርግብ አምሳል ወረደ፤ አብም በተለየ አካሉ በደመና ሆኖ በማዕከለ ዮርዳኖስ የቆመውን ኢየሱስ
ክርስቶስን መለኮትን ከሥጋ ሳይለያይ አንድ አድርጎ “የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት” አለ። ምክንያቱም በተለየ አካሉ ሰው ሆኖ በዮርዳኖስ የቆመው ኢየሲስ ክርስቶስ በተዋሕዶ አንድ
አካል አንድ ባሕርይ ሆኖአልና። ተገልጦ የማያውቅ ምሥጢር ተገልጧል። የመንግሥተ ሰማያት በር ይከፈትላችኋል ማለት ነው።
ለመሆኑ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀትን ለምን በዮርዳኖስ አደረገው? ይቆየን ...
በዓለ ጥምቀት
ክፍል ፪
ለመሆኑ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀትን ለምን በዮርዳኖስ አደረገው?
@And_Haymanot
በኢየሩሳሌም አካባቢ ብዙ ወንዞች፣ ኩሬዎችና ሐይቆች መኖራቸው የታወቀ ነው። ጌታ ጥምቀቱን ዮርዳኖስ ያደረገው ስለዚሁ አስቀድሞ የተነገረው ትንቢት መፈጸሙን ለማረጋገጥ
ነው፦ “ባሕር አይታ ሸሸች፣ ዮርዳኖስም ወደ ኋላዋ ተመለሰች፣ አንተስ ዮርዳኖእስ ወደ ኋላ የተመለስኸው ምን ሆነሃል? አቤቱ ውኈች ዐዩህ፤ ዐይተውም ፈሩህ /ጥልቆችም ተነዋወጡ፤ ውኈችም ጮሁ” /መዝ 113/114፡3-4፣ 76፡16/
ከዚህም ጋር ከላይ ምንጩ አንድ የሆነው ዮርዳኖስ ዝቅ ብሎ አንደሚገናኘ በግዝረትና በቁልፊት /በመገዘርና ባለመገዘር/ ተለያይተው የነበሩ ሕዝበና አሕዛብ መላው የአዳም ልጆች በጌታ
ጥምቀት አንድ መሆናቸውን የሚገለጽ ትርጉም አለው፡፤ እሥራኤል ዮርዳኖስን ተሻግረው ምድረ ርስት ገብተዋል። ያመኑ የተጠመቁ ምእመናንም በጥምቀት ገነት መንግሥተ ሰማያትን
ይወርሳሉ። /ዮሐ 21፡15/ ከላይ የቀረቡት ታሪኮች ለመረዳት እንደምንችለው ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጠመቀው በዮሐንስ እጅ ነው። ለምን?
ቅዱስ ዮሐንስ በኃጢአት የተዳደፉት ሁሉ ንስሐ ገብተው የተዘጋጀላቸውን መንግሥት ወራሾች ይሆኑ ዘንድ “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ” እያለ ሲሰብክ ነበር። ይህ
“መንግሥተ ሰማያት በልጅነት፤ ልጅነት ደግሞ በሃይማኖት ልትሰጥ ቀርባለችና ከኃጢአት ተለይታችሁ፣ ከበደል ርቃችሁ
ቅረቡ” ማለት ነው። በነቢያት እንደተነገረውም “ የእግዚአብሔርን መንገድ አዘጋጁ፣ ጥርጊያውንም አቅኑ” እያለ ድምጹን አሰምቶ ሰብኳል። ምሥጢሩንም በመጣ ጊዜ ተራራውና
ኮረበታው ተንዶ፣ ጎድጓዳው ተመልቶ፣ ሥሩ ተነቅሎ፣ ደንጊያው ተለቅሞ ለፈረስ ለሰረገላ እንዲመች ተደልድሎ እንደሚቆይ ሁሉ እናንተም የእግዚአብሔር ማደሪያ የሆነውን ሰውነታችሁን ከኃጢአታችሁ ንጹሕ አድርጋችሁ ጠብቁ ማለት ነው።
ቅዱስ ዮሐንስ ከንስሐው ስበከት በተጨማሪም ዘመን የማይቆጠርለት ሲሆን ሥጋን በመለበሱ ዘመን ተቆጥሮለት ከእርሱ በኋላ ስድስት ወር ዘግይቶ ስለሚመጣው ስለ ኢየሱስ
ክርስቶስ ማንነትም ሰብኳል፦“እኔስ ለንስሐ በውኃ አተምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል። እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል፤ መንሹም በእጁ ነው። አውድማውንም ስንዴውንም በጎተረው ይከታል፤ ፈጽሞ ያጠራል፤
ሰንዴወንም በጎተራው ይከታል፤ ገለባውን ግን በማይጠፋ እሳት ያቃጥለዋል። /ማቴ 3፡11፤ ዮሐ 1፡26/
“እኔ ክርስቶስ አይደለሁም፤ ነገር ግን ከእርሱ በፊት ተልኬአለሁ እንዳልሁ ራሳችሁ ትመሰክሩልኛላችሁ። ሙሽራዪቱ ያለችው.እርሱ ሙሽራ ነው። ቆሞ የሚሰማው ሚዜው ግን በሙሽራው
ድምጽ እጅግ ደስ ይለዋል፡ እንግዲህ ይህ ደስታዬ ተፈጸመ። እርሱ ሊልቅ እኔ ግን ላንስ ያስፈልጋል፡ ከላየ የሚመጣው ከሁሉ በላየ ነው፤ ከምድር የሚሆነው የምድር ነው፣ የምድርንም ይናገራል። ከሰማይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው… አባት /አብ/ልጁን /ወልድን/ ይወዳል፡፤ ሁሉንም በእጁ ሰጥቶታል። በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን
የእግዚአብሔር ቁጣ በርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም” /ዮሐ 3፡28/።
በዚህ ስብከቱና ምስክርነቱ የተነሣ ጌታ በዮሐንስ እጅ ተጠመቀ። ከዚህም ጋር ጌታ ዮሐንስ ወዳለበት ኺዶ ተጠመቀ እንጂ ዮሐንስ ወደእርሱ እንዲመጣ አላደረገም። ይህም በዚህ ዓለም
ሀብት ሥልጣን ያላቸው ሰዎች ሁሉ ካህናትን በየቤታችን እየመጣችሁ አጥምቁን የማለት ልምድ እንዳይኖር ሥርዓት.መወሰኑንና ጌታ መምህረ ትሕትና መሆኑን የሚያመለክት ነው።
☞ 3. የበዓሉ አከባበር
ይህ የዓለም መድኃኒት የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት መታሰቢያ በዓል በመላው ዓለም በክርስቲያኖች ይከበራል። በዓሉ የሚከበርበት መሠረታዊ መልአክት ተመሳሳይ ቢሆንም የአከባበሩ ይዘት ፣ ሥርዓትና ትውፊት እንደየሀገሩ ባሕልና እንደየአብያተ ክርስቲያናቱ እምነትና
ሥረዓት የተለያየ መልክ አለው። የጥምቀት በዓል በኢትዮጰያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በዓመታት ዑደት ከሚከበሩት ዐበይት በዓላት አንዱ ነው።
በአዳምና ሔዋን ሰብአዊ ተፈጥሮ አንድ ለሆነው ሰው ሁሉ ድኅንነተ የሰውን ሥጋ ዋሕዶ በተገለጠው በኢየሱስ ክርስቶስ
ደም የታነጸችው አሐቲ ቤተ ክርስቲያን በሰዎች የተለያየ አመለካከትና የእምነት ትርጉም ዛሬ በየአህጉሩና በየጎጡ
ተከፋፈላ በብዙ ስሞች ብትጠራም የጥንተ ክረስትናውን መሠረት ሳትለቅ፣ ከቀደምት አበው በተላለፈወ እምነትና ሥርዓት ጸንታ የመትጓዘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን
የጥቀትን በዓል የምታስበውና የምታከብረው በሌሎቸ ዘንድ በማንኛውም ቤተ ክርስቲያን በማይታይ ከፍተኛ መንፈሳዊ ትውፊትና ሥርዓት ነው፡፤ በተለይ ጌታችን በፈለገ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ እጅ ሊጠመቅ፣ ዮሐንስ ጌታን ሊያጠምቅ ወደ ዮርዳኖስ
እንደወረዱ ቤተ ክርስቲያን ታቦቷን ከመንበሯ አውጥታ ወደ ውኃ
ምንጮች /ወንዞች/ በመሄድ በልዩ መንፈሳዊ ሥርዓት ታከብራለች። ተከታዮቿ ምእመናንም /ሕዝበ ክርስቲያኑም/ ከታቦታቱ ጋር በየአካባቢአቸው አብረው በመውጣት ለዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ያላቸውን እምነት፣ ፍቅርና አክብሮት
በጋለ መንፈስ እየገለጡ በዓሉን በደማቅ ሥነ ሥርዓት ያከብራሉ፡፤ ለኢትዮጰያ ቤተ ክርስቲያን ልዩ የሆነውን ይህን ሥነ
በዓል ለመመልከት ከዓለም ዙሪያ የሚሰበሰቡ ሀገር ጎብኚዎች
ብዙዎች ናቸው።
✍ ሐመር ፲፩ኛ ዓመት፣ ቁ. ፮፤ ጥር - የካቲት ፲፱፻፺፮ ዓ.ም.
መልካም የጥምቀት በዓል።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ክፍል ፪
ለመሆኑ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀትን ለምን በዮርዳኖስ አደረገው?
@And_Haymanot
በኢየሩሳሌም አካባቢ ብዙ ወንዞች፣ ኩሬዎችና ሐይቆች መኖራቸው የታወቀ ነው። ጌታ ጥምቀቱን ዮርዳኖስ ያደረገው ስለዚሁ አስቀድሞ የተነገረው ትንቢት መፈጸሙን ለማረጋገጥ
ነው፦ “ባሕር አይታ ሸሸች፣ ዮርዳኖስም ወደ ኋላዋ ተመለሰች፣ አንተስ ዮርዳኖእስ ወደ ኋላ የተመለስኸው ምን ሆነሃል? አቤቱ ውኈች ዐዩህ፤ ዐይተውም ፈሩህ /ጥልቆችም ተነዋወጡ፤ ውኈችም ጮሁ” /መዝ 113/114፡3-4፣ 76፡16/
ከዚህም ጋር ከላይ ምንጩ አንድ የሆነው ዮርዳኖስ ዝቅ ብሎ አንደሚገናኘ በግዝረትና በቁልፊት /በመገዘርና ባለመገዘር/ ተለያይተው የነበሩ ሕዝበና አሕዛብ መላው የአዳም ልጆች በጌታ
ጥምቀት አንድ መሆናቸውን የሚገለጽ ትርጉም አለው፡፤ እሥራኤል ዮርዳኖስን ተሻግረው ምድረ ርስት ገብተዋል። ያመኑ የተጠመቁ ምእመናንም በጥምቀት ገነት መንግሥተ ሰማያትን
ይወርሳሉ። /ዮሐ 21፡15/ ከላይ የቀረቡት ታሪኮች ለመረዳት እንደምንችለው ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጠመቀው በዮሐንስ እጅ ነው። ለምን?
ቅዱስ ዮሐንስ በኃጢአት የተዳደፉት ሁሉ ንስሐ ገብተው የተዘጋጀላቸውን መንግሥት ወራሾች ይሆኑ ዘንድ “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ” እያለ ሲሰብክ ነበር። ይህ
“መንግሥተ ሰማያት በልጅነት፤ ልጅነት ደግሞ በሃይማኖት ልትሰጥ ቀርባለችና ከኃጢአት ተለይታችሁ፣ ከበደል ርቃችሁ
ቅረቡ” ማለት ነው። በነቢያት እንደተነገረውም “ የእግዚአብሔርን መንገድ አዘጋጁ፣ ጥርጊያውንም አቅኑ” እያለ ድምጹን አሰምቶ ሰብኳል። ምሥጢሩንም በመጣ ጊዜ ተራራውና
ኮረበታው ተንዶ፣ ጎድጓዳው ተመልቶ፣ ሥሩ ተነቅሎ፣ ደንጊያው ተለቅሞ ለፈረስ ለሰረገላ እንዲመች ተደልድሎ እንደሚቆይ ሁሉ እናንተም የእግዚአብሔር ማደሪያ የሆነውን ሰውነታችሁን ከኃጢአታችሁ ንጹሕ አድርጋችሁ ጠብቁ ማለት ነው።
ቅዱስ ዮሐንስ ከንስሐው ስበከት በተጨማሪም ዘመን የማይቆጠርለት ሲሆን ሥጋን በመለበሱ ዘመን ተቆጥሮለት ከእርሱ በኋላ ስድስት ወር ዘግይቶ ስለሚመጣው ስለ ኢየሱስ
ክርስቶስ ማንነትም ሰብኳል፦“እኔስ ለንስሐ በውኃ አተምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል። እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል፤ መንሹም በእጁ ነው። አውድማውንም ስንዴውንም በጎተረው ይከታል፤ ፈጽሞ ያጠራል፤
ሰንዴወንም በጎተራው ይከታል፤ ገለባውን ግን በማይጠፋ እሳት ያቃጥለዋል። /ማቴ 3፡11፤ ዮሐ 1፡26/
“እኔ ክርስቶስ አይደለሁም፤ ነገር ግን ከእርሱ በፊት ተልኬአለሁ እንዳልሁ ራሳችሁ ትመሰክሩልኛላችሁ። ሙሽራዪቱ ያለችው.እርሱ ሙሽራ ነው። ቆሞ የሚሰማው ሚዜው ግን በሙሽራው
ድምጽ እጅግ ደስ ይለዋል፡ እንግዲህ ይህ ደስታዬ ተፈጸመ። እርሱ ሊልቅ እኔ ግን ላንስ ያስፈልጋል፡ ከላየ የሚመጣው ከሁሉ በላየ ነው፤ ከምድር የሚሆነው የምድር ነው፣ የምድርንም ይናገራል። ከሰማይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው… አባት /አብ/ልጁን /ወልድን/ ይወዳል፡፤ ሁሉንም በእጁ ሰጥቶታል። በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን
የእግዚአብሔር ቁጣ በርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም” /ዮሐ 3፡28/።
በዚህ ስብከቱና ምስክርነቱ የተነሣ ጌታ በዮሐንስ እጅ ተጠመቀ። ከዚህም ጋር ጌታ ዮሐንስ ወዳለበት ኺዶ ተጠመቀ እንጂ ዮሐንስ ወደእርሱ እንዲመጣ አላደረገም። ይህም በዚህ ዓለም
ሀብት ሥልጣን ያላቸው ሰዎች ሁሉ ካህናትን በየቤታችን እየመጣችሁ አጥምቁን የማለት ልምድ እንዳይኖር ሥርዓት.መወሰኑንና ጌታ መምህረ ትሕትና መሆኑን የሚያመለክት ነው።
☞ 3. የበዓሉ አከባበር
ይህ የዓለም መድኃኒት የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት መታሰቢያ በዓል በመላው ዓለም በክርስቲያኖች ይከበራል። በዓሉ የሚከበርበት መሠረታዊ መልአክት ተመሳሳይ ቢሆንም የአከባበሩ ይዘት ፣ ሥርዓትና ትውፊት እንደየሀገሩ ባሕልና እንደየአብያተ ክርስቲያናቱ እምነትና
ሥረዓት የተለያየ መልክ አለው። የጥምቀት በዓል በኢትዮጰያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በዓመታት ዑደት ከሚከበሩት ዐበይት በዓላት አንዱ ነው።
በአዳምና ሔዋን ሰብአዊ ተፈጥሮ አንድ ለሆነው ሰው ሁሉ ድኅንነተ የሰውን ሥጋ ዋሕዶ በተገለጠው በኢየሱስ ክርስቶስ
ደም የታነጸችው አሐቲ ቤተ ክርስቲያን በሰዎች የተለያየ አመለካከትና የእምነት ትርጉም ዛሬ በየአህጉሩና በየጎጡ
ተከፋፈላ በብዙ ስሞች ብትጠራም የጥንተ ክረስትናውን መሠረት ሳትለቅ፣ ከቀደምት አበው በተላለፈወ እምነትና ሥርዓት ጸንታ የመትጓዘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን
የጥቀትን በዓል የምታስበውና የምታከብረው በሌሎቸ ዘንድ በማንኛውም ቤተ ክርስቲያን በማይታይ ከፍተኛ መንፈሳዊ ትውፊትና ሥርዓት ነው፡፤ በተለይ ጌታችን በፈለገ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ እጅ ሊጠመቅ፣ ዮሐንስ ጌታን ሊያጠምቅ ወደ ዮርዳኖስ
እንደወረዱ ቤተ ክርስቲያን ታቦቷን ከመንበሯ አውጥታ ወደ ውኃ
ምንጮች /ወንዞች/ በመሄድ በልዩ መንፈሳዊ ሥርዓት ታከብራለች። ተከታዮቿ ምእመናንም /ሕዝበ ክርስቲያኑም/ ከታቦታቱ ጋር በየአካባቢአቸው አብረው በመውጣት ለዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ያላቸውን እምነት፣ ፍቅርና አክብሮት
በጋለ መንፈስ እየገለጡ በዓሉን በደማቅ ሥነ ሥርዓት ያከብራሉ፡፤ ለኢትዮጰያ ቤተ ክርስቲያን ልዩ የሆነውን ይህን ሥነ
በዓል ለመመልከት ከዓለም ዙሪያ የሚሰበሰቡ ሀገር ጎብኚዎች
ብዙዎች ናቸው።
✍ ሐመር ፲፩ኛ ዓመት፣ ቁ. ፮፤ ጥር - የካቲት ፲፱፻፺፮ ዓ.ም.
መልካም የጥምቀት በዓል።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
✞ ✞ ✞ ታቦት ✞ ✞ ✞
ተወዳጆች በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ እያልን ዛሬ በታቦት ዙርያ የሚጠየቁ ጥያቄዎችን ይዘን ቀርበናል
☞ ታቦትን ሌሎች ሃገራት እንዴት ይጠቀሙታል?Read more
☞"ታቦትና ኢየሱስ ክርስቶስ"
ታቦት በሐዲስ ኪዳን ለምን ያስፈልጋል?
አንዳንድ ሰዎች ‹‹የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታቦት ከኦሪቱ ጋር አይመሳሰልም!›› ብለው እንደ ትልቅ መከራከሪያ ሲያውጁ ማየት እጅግ ያስገርማል፡፡ አንዴ ‹ኦሪታዊት ነሽ› አንድ ጊዜ ደግሞ ‹‹ለምን እንደ ኦሪቱ አልሆንሽም›› ብሎ ንትርክ ግራ ያጋባል፡፡ አንዳንዶች ደግሞ "የቃልኪዳኑ ታቦት ብለው ከእንግዲህ አይሹትም ፣ አይደረግምም" የሚለውን በመጥቀስ የሐዲስ ኪዳነ ታቦትን ይቃወማሉ።...
Read more
☞ ታቦት ተሽሯል? Read more
☞ ይህ ሁሉ ታቦት ከየት መጣ? Read more
☞ የሐዲስ ኪዳን ታቦታችን ክርስቶስ ነው ሌላውን ሽሮታል? Read more
ተጨማሪ ለማንበብ ☞ ይህን ይጫኑ
ተወዳጆች በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ እያልን ዛሬ በታቦት ዙርያ የሚጠየቁ ጥያቄዎችን ይዘን ቀርበናል
☞ ታቦትን ሌሎች ሃገራት እንዴት ይጠቀሙታል?Read more
☞"ታቦትና ኢየሱስ ክርስቶስ"
ታቦት በሐዲስ ኪዳን ለምን ያስፈልጋል?
አንዳንድ ሰዎች ‹‹የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታቦት ከኦሪቱ ጋር አይመሳሰልም!›› ብለው እንደ ትልቅ መከራከሪያ ሲያውጁ ማየት እጅግ ያስገርማል፡፡ አንዴ ‹ኦሪታዊት ነሽ› አንድ ጊዜ ደግሞ ‹‹ለምን እንደ ኦሪቱ አልሆንሽም›› ብሎ ንትርክ ግራ ያጋባል፡፡ አንዳንዶች ደግሞ "የቃልኪዳኑ ታቦት ብለው ከእንግዲህ አይሹትም ፣ አይደረግምም" የሚለውን በመጥቀስ የሐዲስ ኪዳነ ታቦትን ይቃወማሉ።...
Read more
☞ ታቦት ተሽሯል? Read more
☞ ይህ ሁሉ ታቦት ከየት መጣ? Read more
☞ የሐዲስ ኪዳን ታቦታችን ክርስቶስ ነው ሌላውን ሽሮታል? Read more
ተጨማሪ ለማንበብ ☞ ይህን ይጫኑ
ትላንት ማታ ጨረቃ ላይ የጌታችንንና የመጥምቁን ሥዕል ያዩ ምእመናን (ለመዋሸት ምንም ምክንያት የሌላቸው ወንድሞች ሳይቀር) በደስታ ሲነግሩን ፎቶ ሲልኩልን አምሽተዋል። ነገሩን ለማጣራት መቼም "ጨረቃ ሆይ አንድ ጊዜ ድገሚው" ማለት አንችልም። ይህን አምኖ ፈጣሪን ማመስገን አያስነቅፍም። ያየውን የሚመሰክር ሰው ሲገጥመንም ዝም ብለን አንነቅፍም። ይሁንና "ላይሆን ይችላል ፣ በፎቶሾፕ የተሠራ ቢሆንስ" ወዘተ ብሎ መጠርጠርም (Sceptical መሆንም) በምልክት ማመን የእምነት መለኪያ ስላልሆነ አያስቀጣም። በሐሰት ምልክት ከመነዳትም ስለሚጠብቅ ጥሩ ነው። ደቀ መዛሙርቱም ክርስቶስን ተከትለውት ተአምር አዩ እንጂ ተአምር አይተው አልተከተሉትም።
ጨረቃን የፈጠረ ብለን የምናመልከው አምላክ በጨረቃ ላይ ምልክት ቢያሳየንም ባያሳየንም አምላክ ነው። እስከ ጨረቃ ድረስ የሚያይ ዓይናችንን እንደ ቴሌስኮፕ የገጠመው እርሱን በጨለማ የምታበራዋን ኳስ የፈጠራትን እርሱን ለማድነቅ በሚልየን የሚቆጠሩ ብዙ ምክንያቶች አሉን።
በጨረቃ ላይ በታየው ነገር ለየሰዉ የሚታየው ነገር እንደማንነቱ ነው። መንፈሳዊ ዓይን ያለው መንፈሳዊ ነገር ያያል። ሌላው ደግሞ ድራገን ፣ ጊንጥ ወዘተ አየሁ ሊል ይችላል። በሌላው ዓለም ዜና ማሠራጫዎችም የየራሱ ትንታኔ ተሠጥቶታል። ጥምቀትን ላከበረው ክርስቲያን ምእመን ግን መጥምቁ ዮሐንስ ጌታን ሲያጠምቅ ታይቶታል።
በአንድ ዩኒቨርሲቲ ጊቢ ተማሪዎች ማታ ወጥተው ሲዘምሩ አምሽተዋል። ወጣቶች በሌሊት ተነሥተው ወደ ጭፈራ ቤት ከመሔድ ይልቅ ፈጣሪን ሲያመሰግኑ ማደራቸው ራሱ ብቻውን ተአምር ነው። ጨረቃ ላይ ከታየው መሬት ላይ የታየው በለጠ ያሰኛል። ጨረቃ ላይ ፍጡር ካለ ወደ ምድር ቁልቁል እያየ ይኼን ዝማሬ ማድነቅ ይኖርበታል።
ከዚያ ውጪ እኛ ኦርቶዶክሳውያን መጥምቁ ዮሐንስን ግን ጨረቃ ላይ ካየነው ቆይተናል።
መጥምቁ ዮሐንስ ራሱ ጨረቃ ነው። ጨረቃ በጨለማ ያበራል ፣ ፀሐይ ሲወጣ ለፀሐይ ሥፍራውን ይለቅቃል። መጥምቁ በጨለማው የብሉይ ኪዳን ዘመን ካበሩ ነቢያት የመጨረሻውና ከሁሉ የሚበልጠው ነቢይ ነበር። "እርሱ የሚነድ መብራት ነበረ ፣ ጥቂት ዘመን በብርሃኑ ደስ ሊላችሁ ወደዳችሁ" እንደተባለ መጥምቁ ዮሐንስ በሌሊት ያበራ ጨረቃ ነበረ። (ዮሐ 5:35)
ፀሐይ ከወጣች በኋላ ጨረቃ ብርሃንዋ እንደማያስፈልግና ለፀሐይ ቦታዋን እንደምትለቅ መጥምቁ ዮሐንስም እውነተኛው ፀሐይ ክርስቶስ ሲመጣ "እርሱ ሊልቅ እኔ ላንስ ይገባኛል" ብሎ ሥፍራውን ለቀቀ። (ዮሐ 3:30)
ዮሐንስ በራእዩ ያያት ፀሐይን ተጎናፅፋ ፣ ዐሥራ ሁለት ከዋክብት ዘውድ የሆኑላት ፣ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች የሆነላት ሴትም በአንድ በኩል ሙሽራይቱ ቤተ ክርስቲያን ስትሆን በሌላ በኩል "ወንድ ልጅ ወለደች" የሚለው ቃል እንደሚያስገድደን ድንግል ማርያም ናት። ፀሐይ ክርስቶስን የተጎናጸፈችውም በማኅፀንዋ ማደሩ ከእርስዋ በመወለዱ ሲሆን ከዋክብቱም የከበቧት ሐዋርያት ነበሩ። ከእግሮችዋ በታች የሆነላት ጨረቃ ገና በእናቱ ማኅፀን እያለ የሰላምታዋን ድምፅ ሰምቶ የሰገደው መጥምቁ ዮሐንስ ነው።
ኦርቶዶክሳውያን መጥምቁ ዮሐንስን ጨረቃ ላይ ስናየው ቆይተናል። ጨረቃ ላይ ሥዕሉን ብናይም ባናይም ጨረቃን ባየን ቁጥር መጥምቁ ዮሐንስን ማሰባችን አይቀርም።
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጥር 13 2011 ዓ ም
ስቶክሆልም ስዊድን
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ጨረቃን የፈጠረ ብለን የምናመልከው አምላክ በጨረቃ ላይ ምልክት ቢያሳየንም ባያሳየንም አምላክ ነው። እስከ ጨረቃ ድረስ የሚያይ ዓይናችንን እንደ ቴሌስኮፕ የገጠመው እርሱን በጨለማ የምታበራዋን ኳስ የፈጠራትን እርሱን ለማድነቅ በሚልየን የሚቆጠሩ ብዙ ምክንያቶች አሉን።
በጨረቃ ላይ በታየው ነገር ለየሰዉ የሚታየው ነገር እንደማንነቱ ነው። መንፈሳዊ ዓይን ያለው መንፈሳዊ ነገር ያያል። ሌላው ደግሞ ድራገን ፣ ጊንጥ ወዘተ አየሁ ሊል ይችላል። በሌላው ዓለም ዜና ማሠራጫዎችም የየራሱ ትንታኔ ተሠጥቶታል። ጥምቀትን ላከበረው ክርስቲያን ምእመን ግን መጥምቁ ዮሐንስ ጌታን ሲያጠምቅ ታይቶታል።
በአንድ ዩኒቨርሲቲ ጊቢ ተማሪዎች ማታ ወጥተው ሲዘምሩ አምሽተዋል። ወጣቶች በሌሊት ተነሥተው ወደ ጭፈራ ቤት ከመሔድ ይልቅ ፈጣሪን ሲያመሰግኑ ማደራቸው ራሱ ብቻውን ተአምር ነው። ጨረቃ ላይ ከታየው መሬት ላይ የታየው በለጠ ያሰኛል። ጨረቃ ላይ ፍጡር ካለ ወደ ምድር ቁልቁል እያየ ይኼን ዝማሬ ማድነቅ ይኖርበታል።
ከዚያ ውጪ እኛ ኦርቶዶክሳውያን መጥምቁ ዮሐንስን ግን ጨረቃ ላይ ካየነው ቆይተናል።
መጥምቁ ዮሐንስ ራሱ ጨረቃ ነው። ጨረቃ በጨለማ ያበራል ፣ ፀሐይ ሲወጣ ለፀሐይ ሥፍራውን ይለቅቃል። መጥምቁ በጨለማው የብሉይ ኪዳን ዘመን ካበሩ ነቢያት የመጨረሻውና ከሁሉ የሚበልጠው ነቢይ ነበር። "እርሱ የሚነድ መብራት ነበረ ፣ ጥቂት ዘመን በብርሃኑ ደስ ሊላችሁ ወደዳችሁ" እንደተባለ መጥምቁ ዮሐንስ በሌሊት ያበራ ጨረቃ ነበረ። (ዮሐ 5:35)
ፀሐይ ከወጣች በኋላ ጨረቃ ብርሃንዋ እንደማያስፈልግና ለፀሐይ ቦታዋን እንደምትለቅ መጥምቁ ዮሐንስም እውነተኛው ፀሐይ ክርስቶስ ሲመጣ "እርሱ ሊልቅ እኔ ላንስ ይገባኛል" ብሎ ሥፍራውን ለቀቀ። (ዮሐ 3:30)
ዮሐንስ በራእዩ ያያት ፀሐይን ተጎናፅፋ ፣ ዐሥራ ሁለት ከዋክብት ዘውድ የሆኑላት ፣ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች የሆነላት ሴትም በአንድ በኩል ሙሽራይቱ ቤተ ክርስቲያን ስትሆን በሌላ በኩል "ወንድ ልጅ ወለደች" የሚለው ቃል እንደሚያስገድደን ድንግል ማርያም ናት። ፀሐይ ክርስቶስን የተጎናጸፈችውም በማኅፀንዋ ማደሩ ከእርስዋ በመወለዱ ሲሆን ከዋክብቱም የከበቧት ሐዋርያት ነበሩ። ከእግሮችዋ በታች የሆነላት ጨረቃ ገና በእናቱ ማኅፀን እያለ የሰላምታዋን ድምፅ ሰምቶ የሰገደው መጥምቁ ዮሐንስ ነው።
ኦርቶዶክሳውያን መጥምቁ ዮሐንስን ጨረቃ ላይ ስናየው ቆይተናል። ጨረቃ ላይ ሥዕሉን ብናይም ባናይም ጨረቃን ባየን ቁጥር መጥምቁ ዮሐንስን ማሰባችን አይቀርም።
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጥር 13 2011 ዓ ም
ስቶክሆልም ስዊድን
@And_Haymanot
@And_Haymanot
💒 116ኛው የግብጽ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ በፓትርያርክነት ዘመናቸው ይቀመጡበት የነበረው በቅዱስ ማርቆስ ካቴድራል የሚገኝ አንድ ያረጀ ክፍል ነበረ። በዚህ ክፍል ሲኖሩ አንድ የካቶሊክ መነኩሴ ሊጎበኛቸው መጣ። የፓትርያርኩን ማረፊያ ቤት እና እቃዎቻቸውን ሲመለከት ለክብራቸው የሚመጥን ባለመሆኑ እጅግ ደነገጠ።
❖ መነኩሴው አቡነ ቄርሎስን እንዲህ ሲል ጠየቃቸው "እባክዎን በእንዲህ ያለ ቤት መኖር ለእርሶ የሚመጥን አይደለም። ፍቃድዎ ከሆነ እኔ ቤትዎን ላሳድስሎት እና አዳዲስ ምርጥ ዕቃዎችን ላስገባሎት?" የፓትርያርኩ ይህን ሲሰሙ ፈገግ ብለው በፍቅር አይን ከተመለከቱት በኋላ"የእኔ ልጅ በጣም አመሰግናለሁ! እርግጥ ነው ይህ ቤት በጣም የተጎሳቆለ ነው። እንደዚያም ሆኖ ግን ጌታ ከተወለደበት በረት ይሻላል!!" አሉት።
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
@And_Haymanot @And_Haymanot
@And_Haymanot @And_Haymanot
@And_Haymanot @And_Haymanot
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
❖ መነኩሴው አቡነ ቄርሎስን እንዲህ ሲል ጠየቃቸው "እባክዎን በእንዲህ ያለ ቤት መኖር ለእርሶ የሚመጥን አይደለም። ፍቃድዎ ከሆነ እኔ ቤትዎን ላሳድስሎት እና አዳዲስ ምርጥ ዕቃዎችን ላስገባሎት?" የፓትርያርኩ ይህን ሲሰሙ ፈገግ ብለው በፍቅር አይን ከተመለከቱት በኋላ"የእኔ ልጅ በጣም አመሰግናለሁ! እርግጥ ነው ይህ ቤት በጣም የተጎሳቆለ ነው። እንደዚያም ሆኖ ግን ጌታ ከተወለደበት በረት ይሻላል!!" አሉት።
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
@And_Haymanot @And_Haymanot
@And_Haymanot @And_Haymanot
@And_Haymanot @And_Haymanot
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
ድረስልን
በቃ ብሎን ጌታ ግፍ እና መከራ
ይላክልን አንተን እስቲ እኛን አብስራ ።
ዘመናችን ሆኗል እንደ ዓመተ ፍዳ
ድረስልን ማልደህ ገብርኤል ፈጣኑ ድሆቹን ተራዳ ።
[ዳንኤል ግርማ ]
@And_Haymanot
የመልአኩ ተራዳይነት አይለየን
መልካም ዕለተ ሰንበት
በቃ ብሎን ጌታ ግፍ እና መከራ
ይላክልን አንተን እስቲ እኛን አብስራ ።
ዘመናችን ሆኗል እንደ ዓመተ ፍዳ
ድረስልን ማልደህ ገብርኤል ፈጣኑ ድሆቹን ተራዳ ።
[ዳንኤል ግርማ ]
@And_Haymanot
የመልአኩ ተራዳይነት አይለየን
መልካም ዕለተ ሰንበት
አስተርእዮ ማርያም
፠★፠★፠★፠★፠★
:
ወር በገባ በ21ኛው ቀን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን
የምናስብት ቀን ነው፡፡ ለመሆኑ ምክንያቱ ምንድር ነው?
:
ምክንያቱ የእመቤታችንን በዓለ እረፍት የምናስብት በመሆኑ ነው
፡፡ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ሞትና ትንሣኤ
በነገረ ማርያም አበው እንደሚያስረዱት ዕረፍቷ በጥር 21
እሑድ ነው ።
:
ጥር 21 አስተርእዮ ማርያም ይባላል፡፡ አስተርእዮ ማለት
መታየት፣ መገለጥ ማለት ነው። ቃሉ አስተርአየ ታየ፡ ተገለጠ
ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ነው። ጌታችን መድኀኒታችን
ኢየሱስክርስቶስ በገባው ቃል ኪዳን መሠረት በሥጋ
የተገለጠበት(የታየበት) ፣አንድነት ሦስትነቱም የተገለጠበት ወቅት
በመሆኑ ከልደት በዓል እስከ ጥር መጨረሻ በሙሉ ዘመነ
አስተርእዮ በመባል ይታወቃል። የእመቤታችን በዓለ ዕረፍት
በዘመነ አስተርእዮ ውስጥ ስለሚከበር “አስተርእዮ
ማርያም”ተብሏል።
፡
የኃጥአንን ለቅሶና ሐዘን አይተሽ ስለእነርሱ ድኅነት(መዳን)
ዕረፍትሽን በሀሴት የተቀበልሽ እመቤታችን ሆይ ሐዋርያት
በሱባዔ ትንሣዔሽን ለማየት በቅተዋልና እኛም በዓለ ዕረፍትሽን
አክብረን ልጅሽ በሰጠሽ ቃል ኪዳን በቀኙ እንቆም ዘንድ
ለምኝልን። አሜን።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
፠★፠★፠★፠★፠★
:
ወር በገባ በ21ኛው ቀን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን
የምናስብት ቀን ነው፡፡ ለመሆኑ ምክንያቱ ምንድር ነው?
:
ምክንያቱ የእመቤታችንን በዓለ እረፍት የምናስብት በመሆኑ ነው
፡፡ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ሞትና ትንሣኤ
በነገረ ማርያም አበው እንደሚያስረዱት ዕረፍቷ በጥር 21
እሑድ ነው ።
:
ጥር 21 አስተርእዮ ማርያም ይባላል፡፡ አስተርእዮ ማለት
መታየት፣ መገለጥ ማለት ነው። ቃሉ አስተርአየ ታየ፡ ተገለጠ
ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ነው። ጌታችን መድኀኒታችን
ኢየሱስክርስቶስ በገባው ቃል ኪዳን መሠረት በሥጋ
የተገለጠበት(የታየበት) ፣አንድነት ሦስትነቱም የተገለጠበት ወቅት
በመሆኑ ከልደት በዓል እስከ ጥር መጨረሻ በሙሉ ዘመነ
አስተርእዮ በመባል ይታወቃል። የእመቤታችን በዓለ ዕረፍት
በዘመነ አስተርእዮ ውስጥ ስለሚከበር “አስተርእዮ
ማርያም”ተብሏል።
፡
የኃጥአንን ለቅሶና ሐዘን አይተሽ ስለእነርሱ ድኅነት(መዳን)
ዕረፍትሽን በሀሴት የተቀበልሽ እመቤታችን ሆይ ሐዋርያት
በሱባዔ ትንሣዔሽን ለማየት በቅተዋልና እኛም በዓለ ዕረፍትሽን
አክብረን ልጅሽ በሰጠሽ ቃል ኪዳን በቀኙ እንቆም ዘንድ
ለምኝልን። አሜን።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ዘርፌ አዳራሹን ብትቀላቀልም ኦርቶዶክስ ናት ብላችሁ ዛሬም ጥብቅና የምትቆሙላት ንስሃ ግቡ ንቁ ንቁ ንቁ ሰውን ሳይሆን አማኑኤልን ተከተሉ። እግዚአብሔር ሰውን ከመከተል ይጠብቀን ፣
ሁሉን ማድረግ የሚቻለው ጌታ ልብ ይስጣት
👍አሜን👍
@And_Haymanot
ሁሉን ማድረግ የሚቻለው ጌታ ልብ ይስጣት
👍አሜን👍
@And_Haymanot
"ወዳጄ ሆይ! ክርስቲያን ነህን? እንኪያስ በፍጹም ወንድምህን አትናቀው፡፡ እኅትህን አትናቃት፡፡ ምንም ይኹን ምን ሰውን አትናቅ፡፡ ይህ የምትንቀው ወንድም በተለይ ክርስቲያን ከኾነ
ክርስቶስን እየሰደብከው እንደኾነ አስተውል፡፡ #እንዴት? ያልከኝ እንደኾነ ይህ የምትንቀው ወንድምህ የክርስቶስ ሕዋስ (ብልት) ኾኗል፡፡ የክርስቶስ ሕዋስ ከኾነ ደግሞ እርሱን ናቅኸው ማለት
ክርስቶስን ናቅኸው ማለት ነውና ወንድምህን የምትንቅ ከኾነ በጲላጦስ አደባባይ ጌታን ከገረፉት፣ ዕራቁቱን ከሰቀሉት፣ሐሞትን ቀላቅለው ካጠጡት፣ በፊቱ ላይ ከተፉበት ሰዎች በምንም አትተናነስም፡፡ ስለዚህ ወንድምህን እኅትህን ከመናቅ ተጠንቀቅ፡፡”
~ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፥
ምንጭ፡- ሰማዕትነት አያምልጣችሁ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ክርስቶስን እየሰደብከው እንደኾነ አስተውል፡፡ #እንዴት? ያልከኝ እንደኾነ ይህ የምትንቀው ወንድምህ የክርስቶስ ሕዋስ (ብልት) ኾኗል፡፡ የክርስቶስ ሕዋስ ከኾነ ደግሞ እርሱን ናቅኸው ማለት
ክርስቶስን ናቅኸው ማለት ነውና ወንድምህን የምትንቅ ከኾነ በጲላጦስ አደባባይ ጌታን ከገረፉት፣ ዕራቁቱን ከሰቀሉት፣ሐሞትን ቀላቅለው ካጠጡት፣ በፊቱ ላይ ከተፉበት ሰዎች በምንም አትተናነስም፡፡ ስለዚህ ወንድምህን እኅትህን ከመናቅ ተጠንቀቅ፡፡”
~ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፥
ምንጭ፡- ሰማዕትነት አያምልጣችሁ
@And_Haymanot
@And_Haymanot