አስታርቂኝ
አስታርቂኝ ድንግል ማርያም /2/
ከልጅሽ /3/ ከመድኃኔዓለም
አስታርቂኝ ኃጢአትን ሰርቼ
አስታርቂኝ ጫካ ውስጥ ቆሜአለው
አስታርቂኝ ሥራዬ አሳፍሮኝ
አስታርቂኝ ዘወትር አነባለው
አስታርቂኝ ልጄ አዳም ብሎ
አስታርቂኝ አምላኬ ሲጠራ
አስታርቂኝ እነሆኝ ለማለት
አስታርቂኝ አንደበቴ ፈራ
አዝ ------------
አስታርቂኝ ሀብትን ተካፍዬ
አስታርቂኝ ከገዛ አባቴ
አስታርቂኝ ከቤቴ ኮበለልኩ
አስታርቂኝ ይሻለኛል ብዬ
አስታርቂኝ ገፍቼ ወጥቼ
አስታርቂኝ የቤቴን ገበታ
አስታርቂኝ ልበላ ተመኘሁ
አስታርቂኝ የእንስሳት ገፈራ
አዝ---------
አስታርቂኝ ወደ አባቴ ልሂድ
አስታርቂኝ አሁን ተነሥቼ
አስታርቂኝ ይቅርታ ልጠይቅ
አስታርቂኝ እግሩ ስር ወድቄ
አስታርቂኝ ልጅነቴ ቀርቶ
አስታርቂኝ አድርገኝ ባርያህ
አስታርቂኝ ከሞያተኞችህ
አስታርቂኝ እንደ አንዱ ቆጥረህ
አዝ ------
አስታርቂኝ ገና ሩቅ ሳለው
አስታርቂኝ አባቴ አይቶኝ
አስታርቂኝ ወደእኔ ሮጦ
አስታርቂኝ አቅፎ ነው የሳመኝ
አስታርቂኝ ጠፍቶ የነበረው
አስታርቂኝ ተገኘልኝ አለ
አስታርቂኝ ሞቶ የነበረው
አስታርቂኝ ደግሞ ሕያው ሆነ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
አስታርቂኝ ድንግል ማርያም /2/
ከልጅሽ /3/ ከመድኃኔዓለም
አስታርቂኝ ኃጢአትን ሰርቼ
አስታርቂኝ ጫካ ውስጥ ቆሜአለው
አስታርቂኝ ሥራዬ አሳፍሮኝ
አስታርቂኝ ዘወትር አነባለው
አስታርቂኝ ልጄ አዳም ብሎ
አስታርቂኝ አምላኬ ሲጠራ
አስታርቂኝ እነሆኝ ለማለት
አስታርቂኝ አንደበቴ ፈራ
አዝ ------------
አስታርቂኝ ሀብትን ተካፍዬ
አስታርቂኝ ከገዛ አባቴ
አስታርቂኝ ከቤቴ ኮበለልኩ
አስታርቂኝ ይሻለኛል ብዬ
አስታርቂኝ ገፍቼ ወጥቼ
አስታርቂኝ የቤቴን ገበታ
አስታርቂኝ ልበላ ተመኘሁ
አስታርቂኝ የእንስሳት ገፈራ
አዝ---------
አስታርቂኝ ወደ አባቴ ልሂድ
አስታርቂኝ አሁን ተነሥቼ
አስታርቂኝ ይቅርታ ልጠይቅ
አስታርቂኝ እግሩ ስር ወድቄ
አስታርቂኝ ልጅነቴ ቀርቶ
አስታርቂኝ አድርገኝ ባርያህ
አስታርቂኝ ከሞያተኞችህ
አስታርቂኝ እንደ አንዱ ቆጥረህ
አዝ ------
አስታርቂኝ ገና ሩቅ ሳለው
አስታርቂኝ አባቴ አይቶኝ
አስታርቂኝ ወደእኔ ሮጦ
አስታርቂኝ አቅፎ ነው የሳመኝ
አስታርቂኝ ጠፍቶ የነበረው
አስታርቂኝ ተገኘልኝ አለ
አስታርቂኝ ሞቶ የነበረው
አስታርቂኝ ደግሞ ሕያው ሆነ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
🌍 እመቤታችን አለም ሳይፈጠር በአምላክ ኅሊና ታስባ ትኖር ነበር 🌍
@And_Haymanot
በመጀመርያ ጊዜውን ባርኮና ቀድሶ ለዚህ ያደረሰን ለልዑል እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን እንዲሁም የፅድቃችን ምክንያት ለሆነችው ቅድስት ድንግል ማርያም ክብርና ምስጋና ይድረሳት
አሜን።
ምንጭ ትምህርተ ተዋህዶ ከሚለው አፕሊኬሽን የተወሰደ።
እመቤታችን አለም ሳይፈጠር በአምላክ ህሊና ታስባ ትኖር ነበር!!!
ይህንን ቅዱስ ቃል ስንናገር ተረፈ ሉተራውያን ለምን ይሆን ያዙኝ
ልቀቁኝ የሚሉት ???
.
.
.
[ መቅድመ ተኣምረ ማርያም ]
እግዚአብሔር አለምን ከመፍጠሩ በፊት ስለሚፈጥረው አለም አያውቅም ነበርን ???
የአለምንስ ፍፃሜ አያውቅምን ???
የእግዚአብሔርን ፍፁም አዋቂነት የሚያምን ሁሉ አያውቅም ሊል
አይችልም።
ራሱ ጌታችንና መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ስጋዌው ንጉሡም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል፦ እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ። ( ማቴዎስ 25 ቁጥር 34 )
በዚህ ትምህርቱ አለም ሳይፈጠር እመቤታችን በመታሰቧ ብቻ ሳይሆን ከእርሷ ሰው ሁኖ ዓለምን ማዳኑ በእለተ ምፅአትም በቀኙ የሚቆሙትና በግራ የሚቆሙት ሁሉ መታወቃቸው ተፅፏል።
አለም ሳይፈጠር ስሉስ ቅዱስ በፈቃ ድ አንድ መሆናቸውና የአካላዊ ቃል ከእመቤታችን ሰው መሆኑ መታወቁ ብቻ ሳይሆን በሰው ድህነትም ስላሴ መደሰታቸው ለማስረዳት ጌታችን
መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
፤ አባት ሆይ፥ በእኔ እንዳለህ እኔም በአንተ፥ እነርሱ ደግሞ በእኛ
አንድ ይሆኑ ዘንድ እለምናለሁ። ( ዮሐንስ ምዕ 17 ከቁጥር 20-21 )
ይህ ንግግር አካላዊ ቃል በተዋህዶ ሰው በመሆኑ ሰውን መውደዱን አብ ቅድመ ስጋዌ በስጋዌ መደሰቱን ለመግለፅ
የተነገረ ነው።
እመቤታችን በአምላክ ህሊና ታስባ ትኖር ነበር የሚለውም ስጋዌው አለም ይታወቃል ከእመቤታችን ከስጋዋ ስጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው መሆኑ መታወቁም እርሷ አለም ሳይፈጠር
ተመርጣለች ታውቃለች ለዚህም ታስባ ትኖር ነበር ማለት ነው። በሌላ መልኩ ደግሞ ይህን በዚህ መልክ የአምላክ ሰው መሆን መታወቁ ትክክል ነው ነገር ግን እመቤታችን ገና ሳትወለድ
እንዴት ልትታወቅ ትችላለች ?
የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ ፦
፤ ያልተሠራ አካሌን ዓይኖችህ አዩኝ፤ የተፈጠሩ ቀኖቼ ሁሉ አንድ ስንኳ ሳይኖር በመጽሐፍህ ተጻፉ። ( መዝሙር ምዕ 139 ቁጥር
16 ) በማለት የማያዳግም ምላሽ ሰጥቶናል። ቅዱሱ ወደፊት የሚመጣው ነገር ከመኖሩ በፊት አንድስ እንኳ
ሳይቀር በመፀሀፍ ቀድሞ መፃፉን ከነገረን ስለ እመቤታችን እንዲህ መባሉ ከቅዱስ መፀሀፍ ልዩነት እንደሌለው ያሳየናል። አንዳንዶቹ ደግሞ የእግዚአብሔርን አዋቂነት ቢያምኑም
እመቤታችን ብቻዋን አታውቅም የሚል መከራከሪያን ያመጣሉ ይህ ንግግራቸውም እራሳቸው ለእመቤታችን ያላቸው አመለካከት ወይም ያሳየናል እንጅ አይናቸውን ጨፍነው መካድ
የሚፈልጉ መሆናቸውን የቅዱሳት መፀሀፍት እውቀታቸውን
ሊያሳይ አይችልም። እግዚአብሔር ሁሉንም ያውቃል ስለሁሉም ግን አልተናገረም አልተፃፈም ትንቢት የተነገረላቸው ወይም በስራቸው
እግዚአብሔርን ምን ያህል ደስ እንደሚያሰኙት እርሱ ያወቃቸው
ብቻ ናቸው።
🔍 ነብዩ ኤርሚያስን ፦ በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማኅፀንም ሳትወጣ
ቀድሼሃለሁ፥ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ። ( ኤርምያስ ምዕ 1 ቁጥር 5 ) ይህ ማለት ግን እግዚአብሔር ሌሎቹን በእናታቸው ማህፀን
አያውቃቸውም ሳይወለዱና አድገው የሚሆኑትን ሳይሆኑ
አስቀድሞ አያውቅም ማለት አይደለም ቅዱስ ዳዊት ፦
💠 መዝሙር ምዕ 22 ቁጥር 10 ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ። ( መዝሙር
ምዕ 22 ቁጥር 10 ) እንዳለ ሁላችንንም አስቀድሞ ያውቀናል። ነብየ እግዚአብሔር ኤርሚያስ የተናገረው ግን በተለየ ሁኔታ ትንቢት የተነገረላቸው ሰወች አስቀድሞ የሚሆኑትና ቅድስናቸው የታወቀላቸው መሆኑን መናገር ነው። ለአህዛብም ነብይ አድርጌሀለሁ ያለው ገና ሳይወለድ ነው።
ነብይነትን ተሽሞ ወይም ተቀብቶ በምድር ላይ ከመጣ በኋላ
አይደለም። ነገር ግን ከተወለደና ካደገ በኋላ የሚደርስበት መዓረግና
ቅድስና አስቀድሞ ( ቀድሞ ) የሚታወቅ መሆኑን መናገሩ ነው።
💠 ቅዱስ ጳውሎስ ለጢሞቲወስ ሲፅፍለት ፦.ጢሞቴዎስ ልጄ ሆይ፥ አስቀድሞ ስለ አንተ እንደ ተነገረው ትንቢት፥ በእርሱ መልካም ጦርነት ትዋጋ ዘንድ ይህችን ትእዛዝ አደራ እሰጥሃለሁ፤
( 1ኛ ጢሞቴዎስ ምዕ 1 ቁጥር 18 )
ያለው በጢሞቲወስ በስም ተጠቅሶ ትንቢት ተነግሮለት አይደለም።
ነገር ግን ስለ ሐዲስ ኪዳን ካህናትና ሐዋርያት የተነገረው ለእርሱ የተነገረ መሆኑ የታወቀ በመሆኑ ነው።
ሥጋዌውን ዓለም ሳይፈጠር እግዚአብሔር ያውቀዋል ፣
ያስበዋል ማለትም እመቤታችን ታስባ ትኖር ነበር ማለት ነው።
።።።።።።።///።።።።።።
#በዓለም_ሳይፈጠር_በፊቱ_ቅዱሳንና_ነውር_የሌለን_በፍቅር_እንሆን_ዘንድ_በክርስቶስ_መረጠን ። ( ኤፌ ምዕ 1 ከቁጥር 4 እስከ 14 )
እመቤታችን አለም ሳይፈጠር በአምላክ ኅሊና ታስባ ትኖር ነበር የሚለው የተኣምረ ማርያም መቅድም ምንም አይነት ሕፀፅ የለውም መፀሐፍ ቅዱስም ይደግፈዋል።
።።።።።።።///።።።።።።።።
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ይቅር ባይነት
የእናታችን የድንግል ማርያም አማላጂነት
የቅዱሳን ፀሎት የመልዐክት ፈጣን ተራዳኢነት ከምናምነው ጋር
ይሁንልን አሜን።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
በመጀመርያ ጊዜውን ባርኮና ቀድሶ ለዚህ ያደረሰን ለልዑል እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን እንዲሁም የፅድቃችን ምክንያት ለሆነችው ቅድስት ድንግል ማርያም ክብርና ምስጋና ይድረሳት
አሜን።
ምንጭ ትምህርተ ተዋህዶ ከሚለው አፕሊኬሽን የተወሰደ።
እመቤታችን አለም ሳይፈጠር በአምላክ ህሊና ታስባ ትኖር ነበር!!!
ይህንን ቅዱስ ቃል ስንናገር ተረፈ ሉተራውያን ለምን ይሆን ያዙኝ
ልቀቁኝ የሚሉት ???
.
.
.
[ መቅድመ ተኣምረ ማርያም ]
እግዚአብሔር አለምን ከመፍጠሩ በፊት ስለሚፈጥረው አለም አያውቅም ነበርን ???
የአለምንስ ፍፃሜ አያውቅምን ???
የእግዚአብሔርን ፍፁም አዋቂነት የሚያምን ሁሉ አያውቅም ሊል
አይችልም።
ራሱ ጌታችንና መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ስጋዌው ንጉሡም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል፦ እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ። ( ማቴዎስ 25 ቁጥር 34 )
በዚህ ትምህርቱ አለም ሳይፈጠር እመቤታችን በመታሰቧ ብቻ ሳይሆን ከእርሷ ሰው ሁኖ ዓለምን ማዳኑ በእለተ ምፅአትም በቀኙ የሚቆሙትና በግራ የሚቆሙት ሁሉ መታወቃቸው ተፅፏል።
አለም ሳይፈጠር ስሉስ ቅዱስ በፈቃ ድ አንድ መሆናቸውና የአካላዊ ቃል ከእመቤታችን ሰው መሆኑ መታወቁ ብቻ ሳይሆን በሰው ድህነትም ስላሴ መደሰታቸው ለማስረዳት ጌታችን
መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
፤ አባት ሆይ፥ በእኔ እንዳለህ እኔም በአንተ፥ እነርሱ ደግሞ በእኛ
አንድ ይሆኑ ዘንድ እለምናለሁ። ( ዮሐንስ ምዕ 17 ከቁጥር 20-21 )
ይህ ንግግር አካላዊ ቃል በተዋህዶ ሰው በመሆኑ ሰውን መውደዱን አብ ቅድመ ስጋዌ በስጋዌ መደሰቱን ለመግለፅ
የተነገረ ነው።
እመቤታችን በአምላክ ህሊና ታስባ ትኖር ነበር የሚለውም ስጋዌው አለም ይታወቃል ከእመቤታችን ከስጋዋ ስጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው መሆኑ መታወቁም እርሷ አለም ሳይፈጠር
ተመርጣለች ታውቃለች ለዚህም ታስባ ትኖር ነበር ማለት ነው። በሌላ መልኩ ደግሞ ይህን በዚህ መልክ የአምላክ ሰው መሆን መታወቁ ትክክል ነው ነገር ግን እመቤታችን ገና ሳትወለድ
እንዴት ልትታወቅ ትችላለች ?
የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ ፦
፤ ያልተሠራ አካሌን ዓይኖችህ አዩኝ፤ የተፈጠሩ ቀኖቼ ሁሉ አንድ ስንኳ ሳይኖር በመጽሐፍህ ተጻፉ። ( መዝሙር ምዕ 139 ቁጥር
16 ) በማለት የማያዳግም ምላሽ ሰጥቶናል። ቅዱሱ ወደፊት የሚመጣው ነገር ከመኖሩ በፊት አንድስ እንኳ
ሳይቀር በመፀሀፍ ቀድሞ መፃፉን ከነገረን ስለ እመቤታችን እንዲህ መባሉ ከቅዱስ መፀሀፍ ልዩነት እንደሌለው ያሳየናል። አንዳንዶቹ ደግሞ የእግዚአብሔርን አዋቂነት ቢያምኑም
እመቤታችን ብቻዋን አታውቅም የሚል መከራከሪያን ያመጣሉ ይህ ንግግራቸውም እራሳቸው ለእመቤታችን ያላቸው አመለካከት ወይም ያሳየናል እንጅ አይናቸውን ጨፍነው መካድ
የሚፈልጉ መሆናቸውን የቅዱሳት መፀሀፍት እውቀታቸውን
ሊያሳይ አይችልም። እግዚአብሔር ሁሉንም ያውቃል ስለሁሉም ግን አልተናገረም አልተፃፈም ትንቢት የተነገረላቸው ወይም በስራቸው
እግዚአብሔርን ምን ያህል ደስ እንደሚያሰኙት እርሱ ያወቃቸው
ብቻ ናቸው።
🔍 ነብዩ ኤርሚያስን ፦ በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማኅፀንም ሳትወጣ
ቀድሼሃለሁ፥ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ። ( ኤርምያስ ምዕ 1 ቁጥር 5 ) ይህ ማለት ግን እግዚአብሔር ሌሎቹን በእናታቸው ማህፀን
አያውቃቸውም ሳይወለዱና አድገው የሚሆኑትን ሳይሆኑ
አስቀድሞ አያውቅም ማለት አይደለም ቅዱስ ዳዊት ፦
💠 መዝሙር ምዕ 22 ቁጥር 10 ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ። ( መዝሙር
ምዕ 22 ቁጥር 10 ) እንዳለ ሁላችንንም አስቀድሞ ያውቀናል። ነብየ እግዚአብሔር ኤርሚያስ የተናገረው ግን በተለየ ሁኔታ ትንቢት የተነገረላቸው ሰወች አስቀድሞ የሚሆኑትና ቅድስናቸው የታወቀላቸው መሆኑን መናገር ነው። ለአህዛብም ነብይ አድርጌሀለሁ ያለው ገና ሳይወለድ ነው።
ነብይነትን ተሽሞ ወይም ተቀብቶ በምድር ላይ ከመጣ በኋላ
አይደለም። ነገር ግን ከተወለደና ካደገ በኋላ የሚደርስበት መዓረግና
ቅድስና አስቀድሞ ( ቀድሞ ) የሚታወቅ መሆኑን መናገሩ ነው።
💠 ቅዱስ ጳውሎስ ለጢሞቲወስ ሲፅፍለት ፦.ጢሞቴዎስ ልጄ ሆይ፥ አስቀድሞ ስለ አንተ እንደ ተነገረው ትንቢት፥ በእርሱ መልካም ጦርነት ትዋጋ ዘንድ ይህችን ትእዛዝ አደራ እሰጥሃለሁ፤
( 1ኛ ጢሞቴዎስ ምዕ 1 ቁጥር 18 )
ያለው በጢሞቲወስ በስም ተጠቅሶ ትንቢት ተነግሮለት አይደለም።
ነገር ግን ስለ ሐዲስ ኪዳን ካህናትና ሐዋርያት የተነገረው ለእርሱ የተነገረ መሆኑ የታወቀ በመሆኑ ነው።
ሥጋዌውን ዓለም ሳይፈጠር እግዚአብሔር ያውቀዋል ፣
ያስበዋል ማለትም እመቤታችን ታስባ ትኖር ነበር ማለት ነው።
።።።።።።።///።።።።።።
#በዓለም_ሳይፈጠር_በፊቱ_ቅዱሳንና_ነውር_የሌለን_በፍቅር_እንሆን_ዘንድ_በክርስቶስ_መረጠን ። ( ኤፌ ምዕ 1 ከቁጥር 4 እስከ 14 )
እመቤታችን አለም ሳይፈጠር በአምላክ ኅሊና ታስባ ትኖር ነበር የሚለው የተኣምረ ማርያም መቅድም ምንም አይነት ሕፀፅ የለውም መፀሐፍ ቅዱስም ይደግፈዋል።
።።።።።።።///።።።።።።።።
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ይቅር ባይነት
የእናታችን የድንግል ማርያም አማላጂነት
የቅዱሳን ፀሎት የመልዐክት ፈጣን ተራዳኢነት ከምናምነው ጋር
ይሁንልን አሜን።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
🌍 እመቤታችን አለም ሳይፈጠር በአምላክ ኅሊና ታስባ ትኖር ነበር 🌍
@And_Haymanot
በመጀመርያ ጊዜውን ባርኮና ቀድሶ ለዚህ ያደረሰን ለልዑል እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን እንዲሁም የፅድቃችን ምክንያት ለሆነችው ቅድስት ድንግል ማርያም ክብርና ምስጋና ይድረሳት
አሜን።
ምንጭ ትምህርተ ተዋህዶ ከሚለው አፕሊኬሽን የተወሰደ።
እመቤታችን አለም ሳይፈጠር በአምላክ ህሊና ታስባ ትኖር ነበር!!!
ይህንን ቅዱስ ቃል ስንናገር ተረፈ ሉተራውያን ለምን ይሆን ያዙኝ
ልቀቁኝ የሚሉት ???
.
.
.
[ መቅድመ ተኣምረ ማርያም ]
እግዚአብሔር አለምን ከመፍጠሩ በፊት ስለሚፈጥረው አለም አያውቅም ነበርን ???
የአለምንስ ፍፃሜ አያውቅምን ???
የእግዚአብሔርን ፍፁም አዋቂነት የሚያምን ሁሉ አያውቅም ሊል
አይችልም።
ራሱ ጌታችንና መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ስጋዌው ንጉሡም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል፦ እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ። ( ማቴዎስ 25 ቁጥር 34 )
በዚህ ትምህርቱ አለም ሳይፈጠር እመቤታችን በመታሰቧ ብቻ ሳይሆን ከእርሷ ሰው ሁኖ ዓለምን ማዳኑ በእለተ ምፅአትም በቀኙ የሚቆሙትና በግራ የሚቆሙት ሁሉ መታወቃቸው ተፅፏል።
አለም ሳይፈጠር ስሉስ ቅዱስ በፈቃ ድ አንድ መሆናቸውና የአካላዊ ቃል ከእመቤታችን ሰው መሆኑ መታወቁ ብቻ ሳይሆን በሰው ድህነትም ስላሴ መደሰታቸው ለማስረዳት ጌታችን
መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
፤ አባት ሆይ፥ በእኔ እንዳለህ እኔም በአንተ፥ እነርሱ ደግሞ በእኛ
አንድ ይሆኑ ዘንድ እለምናለሁ። ( ዮሐንስ ምዕ 17 ከቁጥር 20-21 )
ይህ ንግግር አካላዊ ቃል በተዋህዶ ሰው በመሆኑ ሰውን መውደዱን አብ ቅድመ ስጋዌ በስጋዌ መደሰቱን ለመግለፅ
የተነገረ ነው።
እመቤታችን በአምላክ ህሊና ታስባ ትኖር ነበር የሚለውም ስጋዌው አለም ይታወቃል ከእመቤታችን ከስጋዋ ስጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው መሆኑ መታወቁም እርሷ አለም ሳይፈጠር
ተመርጣለች ታውቃለች ለዚህም ታስባ ትኖር ነበር ማለት ነው። በሌላ መልኩ ደግሞ ይህን በዚህ መልክ የአምላክ ሰው መሆን መታወቁ ትክክል ነው ነገር ግን እመቤታችን ገና ሳትወለድ
እንዴት ልትታወቅ ትችላለች ?
የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ ፦
፤ ያልተሠራ አካሌን ዓይኖችህ አዩኝ፤ የተፈጠሩ ቀኖቼ ሁሉ አንድ ስንኳ ሳይኖር በመጽሐፍህ ተጻፉ። ( መዝሙር ምዕ 139 ቁጥር
16 ) በማለት የማያዳግም ምላሽ ሰጥቶናል። ቅዱሱ ወደፊት የሚመጣው ነገር ከመኖሩ በፊት አንድስ እንኳ
ሳይቀር በመፀሀፍ ቀድሞ መፃፉን ከነገረን ስለ እመቤታችን እንዲህ መባሉ ከቅዱስ መፀሀፍ ልዩነት እንደሌለው ያሳየናል። አንዳንዶቹ ደግሞ የእግዚአብሔርን አዋቂነት ቢያምኑም
እመቤታችን ብቻዋን አታውቅም የሚል መከራከሪያን ያመጣሉ ይህ ንግግራቸውም እራሳቸው ለእመቤታችን ያላቸው አመለካከት ወይም ያሳየናል እንጅ አይናቸውን ጨፍነው መካድ
የሚፈልጉ መሆናቸውን የቅዱሳት መፀሀፍት እውቀታቸውን
ሊያሳይ አይችልም። እግዚአብሔር ሁሉንም ያውቃል ስለሁሉም ግን አልተናገረም አልተፃፈም ትንቢት የተነገረላቸው ወይም በስራቸው
እግዚአብሔርን ምን ያህል ደስ እንደሚያሰኙት እርሱ ያወቃቸው
ብቻ ናቸው።
🔍 ነብዩ ኤርሚያስን ፦ በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማኅፀንም ሳትወጣ
ቀድሼሃለሁ፥ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ። ( ኤርምያስ ምዕ 1 ቁጥር 5 ) ይህ ማለት ግን እግዚአብሔር ሌሎቹን በእናታቸው ማህፀን
አያውቃቸውም ሳይወለዱና አድገው የሚሆኑትን ሳይሆኑ
አስቀድሞ አያውቅም ማለት አይደለም ቅዱስ ዳዊት ፦
💠 መዝሙር ምዕ 22 ቁጥር 10 ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ። ( መዝሙር
ምዕ 22 ቁጥር 10 ) እንዳለ ሁላችንንም አስቀድሞ ያውቀናል። ነብየ እግዚአብሔር ኤርሚያስ የተናገረው ግን በተለየ ሁኔታ ትንቢት የተነገረላቸው ሰወች አስቀድሞ የሚሆኑትና ቅድስናቸው የታወቀላቸው መሆኑን መናገር ነው። ለአህዛብም ነብይ አድርጌሀለሁ ያለው ገና ሳይወለድ ነው።
ነብይነትን ተሽሞ ወይም ተቀብቶ በምድር ላይ ከመጣ በኋላ
አይደለም። ነገር ግን ከተወለደና ካደገ በኋላ የሚደርስበት መዓረግና
ቅድስና አስቀድሞ ( ቀድሞ ) የሚታወቅ መሆኑን መናገሩ ነው።
💠 ቅዱስ ጳውሎስ ለጢሞቲወስ ሲፅፍለት ፦.ጢሞቴዎስ ልጄ ሆይ፥ አስቀድሞ ስለ አንተ እንደ ተነገረው ትንቢት፥ በእርሱ መልካም ጦርነት ትዋጋ ዘንድ ይህችን ትእዛዝ አደራ እሰጥሃለሁ፤
( 1ኛ ጢሞቴዎስ ምዕ 1 ቁጥር 18 )
ያለው በጢሞቲወስ በስም ተጠቅሶ ትንቢት ተነግሮለት አይደለም።
ነገር ግን ስለ ሐዲስ ኪዳን ካህናትና ሐዋርያት የተነገረው ለእርሱ የተነገረ መሆኑ የታወቀ በመሆኑ ነው።
ሥጋዌውን ዓለም ሳይፈጠር እግዚአብሔር ያውቀዋል ፣
ያስበዋል ማለትም እመቤታችን ታስባ ትኖር ነበር ማለት ነው።
።።።።።።።///።።።።።።
#በዓለም_ሳይፈጠር_በፊቱ_ቅዱሳንና_ነውር_የሌለን_በፍቅር_እንሆን_ዘንድ_በክርስቶስ_መረጠን ። ( ኤፌ ምዕ 1 ከቁጥር 4 እስከ 14 )
እመቤታችን አለም ሳይፈጠር በአምላክ ኅሊና ታስባ ትኖር ነበር የሚለው የተኣምረ ማርያም መቅድም ምንም አይነት ሕፀፅ የለውም መፀሐፍ ቅዱስም ይደግፈዋል።
።።።።።።።///።።።።።።።።
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ይቅር ባይነት
የእናታችን የድንግል ማርያም አማላጂነት
የቅዱሳን ፀሎት የመልዐክት ፈጣን ተራዳኢነት ከምናምነው ጋር
ይሁንልን አሜን።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
በመጀመርያ ጊዜውን ባርኮና ቀድሶ ለዚህ ያደረሰን ለልዑል እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን እንዲሁም የፅድቃችን ምክንያት ለሆነችው ቅድስት ድንግል ማርያም ክብርና ምስጋና ይድረሳት
አሜን።
ምንጭ ትምህርተ ተዋህዶ ከሚለው አፕሊኬሽን የተወሰደ።
እመቤታችን አለም ሳይፈጠር በአምላክ ህሊና ታስባ ትኖር ነበር!!!
ይህንን ቅዱስ ቃል ስንናገር ተረፈ ሉተራውያን ለምን ይሆን ያዙኝ
ልቀቁኝ የሚሉት ???
.
.
.
[ መቅድመ ተኣምረ ማርያም ]
እግዚአብሔር አለምን ከመፍጠሩ በፊት ስለሚፈጥረው አለም አያውቅም ነበርን ???
የአለምንስ ፍፃሜ አያውቅምን ???
የእግዚአብሔርን ፍፁም አዋቂነት የሚያምን ሁሉ አያውቅም ሊል
አይችልም።
ራሱ ጌታችንና መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ስጋዌው ንጉሡም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል፦ እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ። ( ማቴዎስ 25 ቁጥር 34 )
በዚህ ትምህርቱ አለም ሳይፈጠር እመቤታችን በመታሰቧ ብቻ ሳይሆን ከእርሷ ሰው ሁኖ ዓለምን ማዳኑ በእለተ ምፅአትም በቀኙ የሚቆሙትና በግራ የሚቆሙት ሁሉ መታወቃቸው ተፅፏል።
አለም ሳይፈጠር ስሉስ ቅዱስ በፈቃ ድ አንድ መሆናቸውና የአካላዊ ቃል ከእመቤታችን ሰው መሆኑ መታወቁ ብቻ ሳይሆን በሰው ድህነትም ስላሴ መደሰታቸው ለማስረዳት ጌታችን
መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
፤ አባት ሆይ፥ በእኔ እንዳለህ እኔም በአንተ፥ እነርሱ ደግሞ በእኛ
አንድ ይሆኑ ዘንድ እለምናለሁ። ( ዮሐንስ ምዕ 17 ከቁጥር 20-21 )
ይህ ንግግር አካላዊ ቃል በተዋህዶ ሰው በመሆኑ ሰውን መውደዱን አብ ቅድመ ስጋዌ በስጋዌ መደሰቱን ለመግለፅ
የተነገረ ነው።
እመቤታችን በአምላክ ህሊና ታስባ ትኖር ነበር የሚለውም ስጋዌው አለም ይታወቃል ከእመቤታችን ከስጋዋ ስጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው መሆኑ መታወቁም እርሷ አለም ሳይፈጠር
ተመርጣለች ታውቃለች ለዚህም ታስባ ትኖር ነበር ማለት ነው። በሌላ መልኩ ደግሞ ይህን በዚህ መልክ የአምላክ ሰው መሆን መታወቁ ትክክል ነው ነገር ግን እመቤታችን ገና ሳትወለድ
እንዴት ልትታወቅ ትችላለች ?
የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ ፦
፤ ያልተሠራ አካሌን ዓይኖችህ አዩኝ፤ የተፈጠሩ ቀኖቼ ሁሉ አንድ ስንኳ ሳይኖር በመጽሐፍህ ተጻፉ። ( መዝሙር ምዕ 139 ቁጥር
16 ) በማለት የማያዳግም ምላሽ ሰጥቶናል። ቅዱሱ ወደፊት የሚመጣው ነገር ከመኖሩ በፊት አንድስ እንኳ
ሳይቀር በመፀሀፍ ቀድሞ መፃፉን ከነገረን ስለ እመቤታችን እንዲህ መባሉ ከቅዱስ መፀሀፍ ልዩነት እንደሌለው ያሳየናል። አንዳንዶቹ ደግሞ የእግዚአብሔርን አዋቂነት ቢያምኑም
እመቤታችን ብቻዋን አታውቅም የሚል መከራከሪያን ያመጣሉ ይህ ንግግራቸውም እራሳቸው ለእመቤታችን ያላቸው አመለካከት ወይም ያሳየናል እንጅ አይናቸውን ጨፍነው መካድ
የሚፈልጉ መሆናቸውን የቅዱሳት መፀሀፍት እውቀታቸውን
ሊያሳይ አይችልም። እግዚአብሔር ሁሉንም ያውቃል ስለሁሉም ግን አልተናገረም አልተፃፈም ትንቢት የተነገረላቸው ወይም በስራቸው
እግዚአብሔርን ምን ያህል ደስ እንደሚያሰኙት እርሱ ያወቃቸው
ብቻ ናቸው።
🔍 ነብዩ ኤርሚያስን ፦ በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማኅፀንም ሳትወጣ
ቀድሼሃለሁ፥ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ። ( ኤርምያስ ምዕ 1 ቁጥር 5 ) ይህ ማለት ግን እግዚአብሔር ሌሎቹን በእናታቸው ማህፀን
አያውቃቸውም ሳይወለዱና አድገው የሚሆኑትን ሳይሆኑ
አስቀድሞ አያውቅም ማለት አይደለም ቅዱስ ዳዊት ፦
💠 መዝሙር ምዕ 22 ቁጥር 10 ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ። ( መዝሙር
ምዕ 22 ቁጥር 10 ) እንዳለ ሁላችንንም አስቀድሞ ያውቀናል። ነብየ እግዚአብሔር ኤርሚያስ የተናገረው ግን በተለየ ሁኔታ ትንቢት የተነገረላቸው ሰወች አስቀድሞ የሚሆኑትና ቅድስናቸው የታወቀላቸው መሆኑን መናገር ነው። ለአህዛብም ነብይ አድርጌሀለሁ ያለው ገና ሳይወለድ ነው።
ነብይነትን ተሽሞ ወይም ተቀብቶ በምድር ላይ ከመጣ በኋላ
አይደለም። ነገር ግን ከተወለደና ካደገ በኋላ የሚደርስበት መዓረግና
ቅድስና አስቀድሞ ( ቀድሞ ) የሚታወቅ መሆኑን መናገሩ ነው።
💠 ቅዱስ ጳውሎስ ለጢሞቲወስ ሲፅፍለት ፦.ጢሞቴዎስ ልጄ ሆይ፥ አስቀድሞ ስለ አንተ እንደ ተነገረው ትንቢት፥ በእርሱ መልካም ጦርነት ትዋጋ ዘንድ ይህችን ትእዛዝ አደራ እሰጥሃለሁ፤
( 1ኛ ጢሞቴዎስ ምዕ 1 ቁጥር 18 )
ያለው በጢሞቲወስ በስም ተጠቅሶ ትንቢት ተነግሮለት አይደለም።
ነገር ግን ስለ ሐዲስ ኪዳን ካህናትና ሐዋርያት የተነገረው ለእርሱ የተነገረ መሆኑ የታወቀ በመሆኑ ነው።
ሥጋዌውን ዓለም ሳይፈጠር እግዚአብሔር ያውቀዋል ፣
ያስበዋል ማለትም እመቤታችን ታስባ ትኖር ነበር ማለት ነው።
።።።።።።።///።።።።።።
#በዓለም_ሳይፈጠር_በፊቱ_ቅዱሳንና_ነውር_የሌለን_በፍቅር_እንሆን_ዘንድ_በክርስቶስ_መረጠን ። ( ኤፌ ምዕ 1 ከቁጥር 4 እስከ 14 )
እመቤታችን አለም ሳይፈጠር በአምላክ ኅሊና ታስባ ትኖር ነበር የሚለው የተኣምረ ማርያም መቅድም ምንም አይነት ሕፀፅ የለውም መፀሐፍ ቅዱስም ይደግፈዋል።
።።።።።።።///።።።።።።።።
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ይቅር ባይነት
የእናታችን የድንግል ማርያም አማላጂነት
የቅዱሳን ፀሎት የመልዐክት ፈጣን ተራዳኢነት ከምናምነው ጋር
ይሁንልን አሜን።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ክርስቶስ
✞ "ክርስቶስ" የሚለው አጠራር ሥረ መሠረቱ ጽርዕ (ግሪክ) ነው። ቅቡዕ (የተቀባ) የሚል ትርጉም አለው። ከዚህ ጋር ተያይዞ በክርስቶስ ያመኑ፡ ማኅተመ መንፈስ ቅዱስን እንዲያገኙ የሚቀቡት "Chrism" (ቅባት) ወይም ሜሮን ይቀባሉ፤ ሥርዓቱም "Chrismation" (ምሥጢረ ሜሮን) ይባላል። በክርስቶስ ያመኑ ምሥጢሩ ሲፈጸምላቸው "ቅቡዓን" (በመንፈስ ቅዱስ የተቀቡ) መባላቸውን እናስተውላለን።.. እርሱን በጸጋ መስለው ወደሚኖሩበት ሃይማኖት ስለገቡ፤ እርሱ ወልድ ሲባል፡ እነሱም ውሉድ ይባላሉ፤ እርሱ ቅቡዕ ሲባል እነሱም ቅቡዓን (ክርስቶሳውያን) ይባላሉ።.. "ርኢኬ ዘከመ ያስተባዝኅ ክርስትናሆሙ በከመ ክርስቶስ ውእቱ፡ ወይሰምዮሙ መሲሓውያነ በከመ መሲሕ ውእቱ፤ እርሱ ክርስቶስ እንደሆነ የክርስቲያንን መጠሪያቸውን እንዳባዛ ተመልከት፡ እርሱም መሲሕ እንደሆነ መሲሓውያን ይላቸዋል" (መጽ. ምሥ. ንባብ ዘበዓለ ሃምሳ ቁ. 65) በማለት ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ሰግላዊ እንደተናገረ።.. ወደ ዋናው ርእሰ ጉዳያችን እንመለስ።
"ክርስቶስ" የሚለው የወልደ እግዚአብሔር ስም፤ ራሱ ወልድ ለአድኅኖተ ዓለም ከሁለት ባሕርያት በፍጹም ተዋሕዶ አንድ ባሕርይ ሆኖ ሲገለጥ የተሰጠው ስም ነው። ክርስቶስ (ቅቡዕ) የቃልነቱ ብቻ ስም አይደለም፤ የትስብእቱ ብቻ ስም አይደለም። በተዋሕዶ ሰው ሲሆን የተሰጠው ስም ነው እንጂ። ከሥጋዌ በፊት ክርስቶስ አልተባለም። "ወእነግር አነሂ ከመ ኢመፍትው እስምዮ ለቃለ እግዚአብሔር ክርስቶስ ዘእንበለ ትስብእት፡ ወኢለትስብእት ዘእንበለ መለኮት፤ ክርስቶስሃ ይሰመይ። ወእምቅድመ ትሥጉት አልቦ ዘይሰምዮ በዝንቱ ስም ለቃለ እግዚአብሔር ክርስቶስ" (የ ማቴ 1፡ 16 አንድምታ ትርጓሜ) ተብሎ እንደተነገረ።
ቅብዓት ማለትም ክብር (መክበር) ማለት ነው። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ቅቡዕ (የከበረ፤ ክብር ያገኘ) መባሉ በትስብእቱ (በሥጋው) ነው እንጂ በቃልነቱ አይደለም። ከላይ የጠቀስነው ወንጌል ትርጉም ክፍል ላይ "ወዝ ስም ክርስቶስ ወፍካሬሁ ቅብዓት ምስለ አምጣነ ትስብእቱ ረከቦ ለዋሕድ" በማለት ይገልጸዋል። በዚሁ መረዳት ያለብን ነገር ጌታ ሲቀባም፡ ሲዋሐድም አንድ ጊዜ ነው፤ የቅጽበተ ዓይን ያህል እንኳ የጊዜ ልዩነት አለመኖሩን ነው።
በመዝሙር መጽሐፍ "አፍቀርከ ጽድቀ ወዐመፃ ጸላእከ፤ በእንተዝ ቀብዐከ እግዚአብሔር አምላክከ" (መዝ 44) ተብሎ የተነገረውን እንመልከት። ጽድቅን (ሰው መሆንን) ወደድህ፡ ዐመፃን (ሰው አለመሆንን) ጠላህ፤ ስለዚህም እግዚአብሔር (እግዚአብሔርነትህ) በተዋሕዶ አከበረህ (አዋሐደህ) ብለን እንረዳዋለን። እግዚአብሔር ቀባህ፡ እግዚአብሔርነትህ ቀባህ ቢባል ምሥጢሩ አንድ ነው። በሥላሴ ያለች የአክባሪነት ሥልጣን አንዲት ናትና። ስለ ክርስቶስ ትንሣኤ ስንናገር "እግዚአብሔር አስነሳው"፣ "እግዚአብሔርነቱ አስነሳው"፣ "በራሱ ሥልጣን (ሀይል) ተነሳ" ብንል ምንም ልዩነት እንደሌለው ሁሉ። ... ስለዚህም ስለ ክርስቶስ "ለሊሁ ቀባዒ፡ ወለሊሁ ተቀባዒ" (ራሱ አክባሪ፡ ራሱ ከባሪ) ተብሎ ይነገራል።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
✞ "ክርስቶስ" የሚለው አጠራር ሥረ መሠረቱ ጽርዕ (ግሪክ) ነው። ቅቡዕ (የተቀባ) የሚል ትርጉም አለው። ከዚህ ጋር ተያይዞ በክርስቶስ ያመኑ፡ ማኅተመ መንፈስ ቅዱስን እንዲያገኙ የሚቀቡት "Chrism" (ቅባት) ወይም ሜሮን ይቀባሉ፤ ሥርዓቱም "Chrismation" (ምሥጢረ ሜሮን) ይባላል። በክርስቶስ ያመኑ ምሥጢሩ ሲፈጸምላቸው "ቅቡዓን" (በመንፈስ ቅዱስ የተቀቡ) መባላቸውን እናስተውላለን።.. እርሱን በጸጋ መስለው ወደሚኖሩበት ሃይማኖት ስለገቡ፤ እርሱ ወልድ ሲባል፡ እነሱም ውሉድ ይባላሉ፤ እርሱ ቅቡዕ ሲባል እነሱም ቅቡዓን (ክርስቶሳውያን) ይባላሉ።.. "ርኢኬ ዘከመ ያስተባዝኅ ክርስትናሆሙ በከመ ክርስቶስ ውእቱ፡ ወይሰምዮሙ መሲሓውያነ በከመ መሲሕ ውእቱ፤ እርሱ ክርስቶስ እንደሆነ የክርስቲያንን መጠሪያቸውን እንዳባዛ ተመልከት፡ እርሱም መሲሕ እንደሆነ መሲሓውያን ይላቸዋል" (መጽ. ምሥ. ንባብ ዘበዓለ ሃምሳ ቁ. 65) በማለት ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ሰግላዊ እንደተናገረ።.. ወደ ዋናው ርእሰ ጉዳያችን እንመለስ።
"ክርስቶስ" የሚለው የወልደ እግዚአብሔር ስም፤ ራሱ ወልድ ለአድኅኖተ ዓለም ከሁለት ባሕርያት በፍጹም ተዋሕዶ አንድ ባሕርይ ሆኖ ሲገለጥ የተሰጠው ስም ነው። ክርስቶስ (ቅቡዕ) የቃልነቱ ብቻ ስም አይደለም፤ የትስብእቱ ብቻ ስም አይደለም። በተዋሕዶ ሰው ሲሆን የተሰጠው ስም ነው እንጂ። ከሥጋዌ በፊት ክርስቶስ አልተባለም። "ወእነግር አነሂ ከመ ኢመፍትው እስምዮ ለቃለ እግዚአብሔር ክርስቶስ ዘእንበለ ትስብእት፡ ወኢለትስብእት ዘእንበለ መለኮት፤ ክርስቶስሃ ይሰመይ። ወእምቅድመ ትሥጉት አልቦ ዘይሰምዮ በዝንቱ ስም ለቃለ እግዚአብሔር ክርስቶስ" (የ ማቴ 1፡ 16 አንድምታ ትርጓሜ) ተብሎ እንደተነገረ።
ቅብዓት ማለትም ክብር (መክበር) ማለት ነው። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ቅቡዕ (የከበረ፤ ክብር ያገኘ) መባሉ በትስብእቱ (በሥጋው) ነው እንጂ በቃልነቱ አይደለም። ከላይ የጠቀስነው ወንጌል ትርጉም ክፍል ላይ "ወዝ ስም ክርስቶስ ወፍካሬሁ ቅብዓት ምስለ አምጣነ ትስብእቱ ረከቦ ለዋሕድ" በማለት ይገልጸዋል። በዚሁ መረዳት ያለብን ነገር ጌታ ሲቀባም፡ ሲዋሐድም አንድ ጊዜ ነው፤ የቅጽበተ ዓይን ያህል እንኳ የጊዜ ልዩነት አለመኖሩን ነው።
በመዝሙር መጽሐፍ "አፍቀርከ ጽድቀ ወዐመፃ ጸላእከ፤ በእንተዝ ቀብዐከ እግዚአብሔር አምላክከ" (መዝ 44) ተብሎ የተነገረውን እንመልከት። ጽድቅን (ሰው መሆንን) ወደድህ፡ ዐመፃን (ሰው አለመሆንን) ጠላህ፤ ስለዚህም እግዚአብሔር (እግዚአብሔርነትህ) በተዋሕዶ አከበረህ (አዋሐደህ) ብለን እንረዳዋለን። እግዚአብሔር ቀባህ፡ እግዚአብሔርነትህ ቀባህ ቢባል ምሥጢሩ አንድ ነው። በሥላሴ ያለች የአክባሪነት ሥልጣን አንዲት ናትና። ስለ ክርስቶስ ትንሣኤ ስንናገር "እግዚአብሔር አስነሳው"፣ "እግዚአብሔርነቱ አስነሳው"፣ "በራሱ ሥልጣን (ሀይል) ተነሳ" ብንል ምንም ልዩነት እንደሌለው ሁሉ። ... ስለዚህም ስለ ክርስቶስ "ለሊሁ ቀባዒ፡ ወለሊሁ ተቀባዒ" (ራሱ አክባሪ፡ ራሱ ከባሪ) ተብሎ ይነገራል።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ቤተ ክርስቲያን: አገር አቀፍ የሰላም እና ስብከተ ወንጌል ስምሪት ልታካሒድ ነው
@And_Haymanot
• ሥልጠናን፣ሕዝባዊ ውይይትንና ዕቅበተ እምነትን ያካተተ ስምሪት ነው፤
• እስከ ታኅሣሥ መጨረሻ ድረስ፣52 አህጉረ ስብከትን ለማዳረስ ታቅዷል፤
• በወቅቱ ፈተናዎች፥የካህናትና የወጣቶች መብትና ግዴታ ላይ ያተኩራል፤
• በሰማዕትነትና በሚዲያ አጠቃቀም ረገድ ኦርቶዶክሳዊውን ወጣት ያነቃል፤
*
• ከ9ሚ. ብር በላይ በጀት ተመድቧል፤250 ጠቅላላ ልኡካን ይሳማሩበታል፤
• በእያንዳንዱ ስምሪት በሊቀ ጳጳስ የሚመሩ 5፣ 5 ልኡካን ይሳተፉበታል፤
• ዓላማውን የሚያስፋፉ ንኡሳን ኮሚቴዎች በየአህጉረ ስብከቱ ይቋቁማሉ፤
• ካህናትና ምእመናን ከአቀባበል ጀምሮ በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቧል፤
*
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት፣ ከነገ በስቲያ ኀሙስ፣ ታኅሣሥ 4 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ለአንድ ወር ያህል የሚዘልቅ የአገራዊ ሰላም እና የስብከተ ወንጌል ስምሪት ሊያካሔድ ነው፡፡
በአገራችን አንዳንድ አካባቢዎች እየታየ ያለውና በቀላሉ የሚገታ የማይመስለው የሰላም ዕጦት ችግር ያሳሰበው ቅዱስ ሲኖዶስ፣ ባለፈው ጥቅምት 14 ቀን 2011 ዓ.ም. ባካሔደው የምልዓተ ጉባኤ ስብሰባው ባስተላለፈው መመሪያ መሠረት የተዘጋጀው ስምሪቱ፣ ቤተ ክርስቲያናችን በሰላም ዕጦት የሚገጥማትን ተግዳሮት የምትቋቋምበትና ለአገራዊ ዕርቅና ለሕዝብ አንድነት መጠበቅ ያላትን ታሪካዊና ብሔራዊ ሚና የምትወጣበት እንደኾነ ተገልጿል፡፡
ስምሪቱ፥ የሥልጠና፣ የሕዝባዊ ውይይትና የዕቅበተ እምነት መርሐ ግብሮችን ማካተቱ ተጠቅሷል፡፡ ካህናትን በሚያሳትፈው ሥልጠና፦ የካህናት ድርሻ በሀገር ሰላም፣ የካህናት መብት እና ግዴታ፣ የካህናት ኖላዊነት(እረኝነት)፣ የካህናት መሪነት እና ዕቅበተ እምነት በሚሉ ርእሰ ጉዳዮች ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ እንደሚሠራ ተጠቁሟል፤ የኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች መብት እና ግዴታ፣ ወጣትነት እና ሰማዕትነት፣ ወጣትነት እና ወቅታዊ ፈተናዎች እንዲሁም መንፈሳዊ ወጣት እና የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም በሚሉ ርእሶችም የሰንበት ት/ቤት እና የአካባቢ ወጣቶችን የሚያነቁና የሚያስገነዝቡ ዐውደ ትምህርቶች መዘጋጀታቸው ተገልጿል፡፡
በአገር ሰላም እና በሕዝብ አንድነት ጉዳዮች ላይ የሚያተኩሩት የውይይት መርሐ ግብሮች፣ ከቤተ ክርስቲያን ምእመናን ውጭ የኾኑ ዜጎች የሚሳተፉበት ሕዝባዊ አቀራረብና ይዘት እንዳላቸው ታውቋል፡፡
በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ሰብሳቢነት የተቋቋመውና 6 ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትን ጨምሮ ከጠቅላይ ጽ/ቤቱ መምሪያዎችና ድርጅቶች፣ ከሰንበት ት/ቤቶች አገር አቀፍ አንድነት፣ከማኅበረ ቅዱሳን፣ ከነገ መለኰት ምሩቃን ማኅበር እና ሌሎች መንፈሳውያን ማኅበራት እንዲሁም ከመንፈሳውያን ኮሌጆች ተውጣጥቶ የተቋቋመና 15 ጠቅላላ አባላትን ያቀፈ የሥራ አስፈጻሚ ዐቢይ ኮሚቴ፣ በአምስት ንኡሳን ኮሚቴዎች በመደራጀት፥ ተሳታፊ ልኡካንን የመመልመል፣ የስምሪት ቦታዎችን የመለየትና አስፈላጊውን በጀት አጥንቶ የማቅረብ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱ ተነግሯል፡፡
250 ጠቅላላ ልኡካን የሚሳተፉበት ይኸው መርሐ ግብር፣ 52 የሀገር ውስጥ አህጉረ ስብከትን እንደሚሸፍንና ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ወጪ የተደረገ 9 ሚሊዮን ብር የማስፈጸሚያ በጀት እንደተመደበለት ታውቋል፡፡ እያንዳንዱ ስምሪት 5፣ 5 ልኡካን የሚይዝና በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራ እንደሚኾን ተጠቅሷል፡፡ ስምሪቱን በአህጉረ ስብከት ደረጃ የሚያቀናጁ፣ ሥልጠናውንና ውይይቱን እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ የሚያስፋፉ የማኅበረ ካህናት፣ የማኅበረ ምእመናን፣ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች፣ የማኅበራት ተወካዮች፣ የመንግሥት አካላትና የአገር ሽማግሌዎች ንኡሳን ኮሚቴዎች በየክፍሎቹ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት መሪነት ይቋቋማሉ፤ ተብሏል፡፡
ካህናት፣ ምእመናንና ወጣቶች፣ ለልኡካኑ አቀባበል ከማድረግ ጀምሮ የአካባቢያቸውን ችግሮች በማሳወቅ፣ በመወያየትና መፍትሔ በማስቀመጥ በሥልጠናውም በሕዝባዊ ውይይቱም በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቧል፡፡
ከነገ በስቲያ በይፋ የሚጀመረው የሀገራዊ ሰላምና ስብከተ ወንጌል ስምሪት ቀዳሚ ተሳታፊ ልኡካን፣ በነገው ዕለት በሥራ አስፈጻሚ ዐቢይ ኮሚቴው የተዘጋጀ ገለጻ/ኦሪየንቴሽን/ በጠቅላይ ጽ/ቤቱ እንደሚሰጣቸው ታውቋል፡፡ ጠቅላላ የስምሪት መርሐ ግብሩን እስከ ታኅሣሥ 26 ድረስ በማጠናቀቅ፣ በውጭ አህጉረ ስብከት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለመቀጠል መታቀዱ ተጠቁሟል፡፡
ምንጭ፦ ሐራ ዘተዋዶ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
• ሥልጠናን፣ሕዝባዊ ውይይትንና ዕቅበተ እምነትን ያካተተ ስምሪት ነው፤
• እስከ ታኅሣሥ መጨረሻ ድረስ፣52 አህጉረ ስብከትን ለማዳረስ ታቅዷል፤
• በወቅቱ ፈተናዎች፥የካህናትና የወጣቶች መብትና ግዴታ ላይ ያተኩራል፤
• በሰማዕትነትና በሚዲያ አጠቃቀም ረገድ ኦርቶዶክሳዊውን ወጣት ያነቃል፤
*
• ከ9ሚ. ብር በላይ በጀት ተመድቧል፤250 ጠቅላላ ልኡካን ይሳማሩበታል፤
• በእያንዳንዱ ስምሪት በሊቀ ጳጳስ የሚመሩ 5፣ 5 ልኡካን ይሳተፉበታል፤
• ዓላማውን የሚያስፋፉ ንኡሳን ኮሚቴዎች በየአህጉረ ስብከቱ ይቋቁማሉ፤
• ካህናትና ምእመናን ከአቀባበል ጀምሮ በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቧል፤
*
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት፣ ከነገ በስቲያ ኀሙስ፣ ታኅሣሥ 4 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ለአንድ ወር ያህል የሚዘልቅ የአገራዊ ሰላም እና የስብከተ ወንጌል ስምሪት ሊያካሔድ ነው፡፡
በአገራችን አንዳንድ አካባቢዎች እየታየ ያለውና በቀላሉ የሚገታ የማይመስለው የሰላም ዕጦት ችግር ያሳሰበው ቅዱስ ሲኖዶስ፣ ባለፈው ጥቅምት 14 ቀን 2011 ዓ.ም. ባካሔደው የምልዓተ ጉባኤ ስብሰባው ባስተላለፈው መመሪያ መሠረት የተዘጋጀው ስምሪቱ፣ ቤተ ክርስቲያናችን በሰላም ዕጦት የሚገጥማትን ተግዳሮት የምትቋቋምበትና ለአገራዊ ዕርቅና ለሕዝብ አንድነት መጠበቅ ያላትን ታሪካዊና ብሔራዊ ሚና የምትወጣበት እንደኾነ ተገልጿል፡፡
ስምሪቱ፥ የሥልጠና፣ የሕዝባዊ ውይይትና የዕቅበተ እምነት መርሐ ግብሮችን ማካተቱ ተጠቅሷል፡፡ ካህናትን በሚያሳትፈው ሥልጠና፦ የካህናት ድርሻ በሀገር ሰላም፣ የካህናት መብት እና ግዴታ፣ የካህናት ኖላዊነት(እረኝነት)፣ የካህናት መሪነት እና ዕቅበተ እምነት በሚሉ ርእሰ ጉዳዮች ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ እንደሚሠራ ተጠቁሟል፤ የኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች መብት እና ግዴታ፣ ወጣትነት እና ሰማዕትነት፣ ወጣትነት እና ወቅታዊ ፈተናዎች እንዲሁም መንፈሳዊ ወጣት እና የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም በሚሉ ርእሶችም የሰንበት ት/ቤት እና የአካባቢ ወጣቶችን የሚያነቁና የሚያስገነዝቡ ዐውደ ትምህርቶች መዘጋጀታቸው ተገልጿል፡፡
በአገር ሰላም እና በሕዝብ አንድነት ጉዳዮች ላይ የሚያተኩሩት የውይይት መርሐ ግብሮች፣ ከቤተ ክርስቲያን ምእመናን ውጭ የኾኑ ዜጎች የሚሳተፉበት ሕዝባዊ አቀራረብና ይዘት እንዳላቸው ታውቋል፡፡
በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ሰብሳቢነት የተቋቋመውና 6 ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትን ጨምሮ ከጠቅላይ ጽ/ቤቱ መምሪያዎችና ድርጅቶች፣ ከሰንበት ት/ቤቶች አገር አቀፍ አንድነት፣ከማኅበረ ቅዱሳን፣ ከነገ መለኰት ምሩቃን ማኅበር እና ሌሎች መንፈሳውያን ማኅበራት እንዲሁም ከመንፈሳውያን ኮሌጆች ተውጣጥቶ የተቋቋመና 15 ጠቅላላ አባላትን ያቀፈ የሥራ አስፈጻሚ ዐቢይ ኮሚቴ፣ በአምስት ንኡሳን ኮሚቴዎች በመደራጀት፥ ተሳታፊ ልኡካንን የመመልመል፣ የስምሪት ቦታዎችን የመለየትና አስፈላጊውን በጀት አጥንቶ የማቅረብ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱ ተነግሯል፡፡
250 ጠቅላላ ልኡካን የሚሳተፉበት ይኸው መርሐ ግብር፣ 52 የሀገር ውስጥ አህጉረ ስብከትን እንደሚሸፍንና ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ወጪ የተደረገ 9 ሚሊዮን ብር የማስፈጸሚያ በጀት እንደተመደበለት ታውቋል፡፡ እያንዳንዱ ስምሪት 5፣ 5 ልኡካን የሚይዝና በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራ እንደሚኾን ተጠቅሷል፡፡ ስምሪቱን በአህጉረ ስብከት ደረጃ የሚያቀናጁ፣ ሥልጠናውንና ውይይቱን እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ የሚያስፋፉ የማኅበረ ካህናት፣ የማኅበረ ምእመናን፣ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች፣ የማኅበራት ተወካዮች፣ የመንግሥት አካላትና የአገር ሽማግሌዎች ንኡሳን ኮሚቴዎች በየክፍሎቹ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት መሪነት ይቋቋማሉ፤ ተብሏል፡፡
ካህናት፣ ምእመናንና ወጣቶች፣ ለልኡካኑ አቀባበል ከማድረግ ጀምሮ የአካባቢያቸውን ችግሮች በማሳወቅ፣ በመወያየትና መፍትሔ በማስቀመጥ በሥልጠናውም በሕዝባዊ ውይይቱም በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቧል፡፡
ከነገ በስቲያ በይፋ የሚጀመረው የሀገራዊ ሰላምና ስብከተ ወንጌል ስምሪት ቀዳሚ ተሳታፊ ልኡካን፣ በነገው ዕለት በሥራ አስፈጻሚ ዐቢይ ኮሚቴው የተዘጋጀ ገለጻ/ኦሪየንቴሽን/ በጠቅላይ ጽ/ቤቱ እንደሚሰጣቸው ታውቋል፡፡ ጠቅላላ የስምሪት መርሐ ግብሩን እስከ ታኅሣሥ 26 ድረስ በማጠናቀቅ፣ በውጭ አህጉረ ስብከት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለመቀጠል መታቀዱ ተጠቁሟል፡፡
ምንጭ፦ ሐራ ዘተዋዶ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ሳታቋርጡ ጸልዩ
"ሥራ የሚሠራ ሰው ቀኑን ሙሉ በጸሎት ተፀምዶ መዋል አይችልም አትበለኝ፤ ይችላል። በጸሎት የሚያስፈልገው
ድምፅ ሳይኾን አሳብ ነው፤ እጅ ሳይኾን እደ ልቦናን ማንሣት ነው። ይህን ለማድረግ ደግሞ ቦታም ጊዜም
አይገድብህም። በጉልበትህ ባትንበረከክ፣ ደረትህንም ባትደቃ እንኳ መንፈስህ ትጉ ከኾነ ጸሎትህ ሥልጡን
ነው።"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ -
(አምስቱ የንስሐ መንገዶች መጽሐፍ ገጽ 32 -
#በገብረ_እግዚአብሔር_ኪደ የተተረጎመ)
@And_Haymanot
@And_Haymanot
"ሥራ የሚሠራ ሰው ቀኑን ሙሉ በጸሎት ተፀምዶ መዋል አይችልም አትበለኝ፤ ይችላል። በጸሎት የሚያስፈልገው
ድምፅ ሳይኾን አሳብ ነው፤ እጅ ሳይኾን እደ ልቦናን ማንሣት ነው። ይህን ለማድረግ ደግሞ ቦታም ጊዜም
አይገድብህም። በጉልበትህ ባትንበረከክ፣ ደረትህንም ባትደቃ እንኳ መንፈስህ ትጉ ከኾነ ጸሎትህ ሥልጡን
ነው።"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ -
(አምስቱ የንስሐ መንገዶች መጽሐፍ ገጽ 32 -
#በገብረ_እግዚአብሔር_ኪደ የተተረጎመ)
@And_Haymanot
@And_Haymanot
✞ እንስሳት ከአምላክ ጋር ቀጥተኛ የሆነ ግንኙነት እንዳላቸው ያውቃሉ? ✞
@And_Haymanot
እንስሳት ተንኮለኞች አይደሉም፡፡ በዘፈቀደ የሚንቀሳቀሱ ይምሰሉ እንጂ አንዳንዴ ከሰው የሚሻሉበት አጋጣሚ አይጠፋም፡፡ አይዋሹም፡፡ አያታልሉም፡፡
የአምላካቸውን ህልውናም አይክዱም፡፡ ለዚህም ይመስላል አምላክ በእነርሱ
በኩል ጥበቡን የሚገልጸው፡፡ በአገራችንም ሆነ በሌሎች ቦታዎች ታዲያ ሰው በማይታዘዝበት ዘመን ቅዱሳን እንስሳትንም ሆነ ነፍሳትን ሲያዙ ማየት አዲስ አይደለም፡፡
እንደ ንቡ ሚካኤል ባሉ ቦታዎችም እንስሳት እና ነፍሳት የአምላክን
ጥበብና ቸርነት ሲገልፁ ይታያሉ፡፡
.
ከታች የሚታዩት በግሪክ አገር በተሰሎንቄ አቅራቢያ ከሚገኘው የኤቶስ ተራራ
(Mount Athos) የተገኙ ምስሎች ናቸው፡፡ ይህ ተራራ የብዙ ቅዱሳን መኖሪያ በመሆኑ በዓለም ይታወቃል፡፡ ታዲያ በዚህ አካባቢ የሚገኙ ንቦች በቅዱሳን ስዕላት ላይ ቀፎን ይሰራሉ፡፡ ሆኖም ግን በአርኪቴክት የተሰመረላቸው ይመስል የሚሰሩት በቅዱሳኑ ዙሪያ ለክተው ነው፡፡ በምንም ተዓምር የቅዱሱን/የቅድስቷን
ፊት ደግሞ አይነኩም፡፡
የእግዚአብሔር ሥራ አይደንቀም?
.
ምስሉን የሰጠኝን ወንድማችንን Carlito Frédéric Cadiou በክርስትና ስሙ
ገብረእግዚአብሔር ብላችሁ በጸሎት አስቡልኝ፡፡ እኔንም ወንድማችሁን
ገብረመስቀልን በጸሎታችሁ አስቡኝ ።
ይቆየን
Share
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
እንስሳት ተንኮለኞች አይደሉም፡፡ በዘፈቀደ የሚንቀሳቀሱ ይምሰሉ እንጂ አንዳንዴ ከሰው የሚሻሉበት አጋጣሚ አይጠፋም፡፡ አይዋሹም፡፡ አያታልሉም፡፡
የአምላካቸውን ህልውናም አይክዱም፡፡ ለዚህም ይመስላል አምላክ በእነርሱ
በኩል ጥበቡን የሚገልጸው፡፡ በአገራችንም ሆነ በሌሎች ቦታዎች ታዲያ ሰው በማይታዘዝበት ዘመን ቅዱሳን እንስሳትንም ሆነ ነፍሳትን ሲያዙ ማየት አዲስ አይደለም፡፡
እንደ ንቡ ሚካኤል ባሉ ቦታዎችም እንስሳት እና ነፍሳት የአምላክን
ጥበብና ቸርነት ሲገልፁ ይታያሉ፡፡
.
ከታች የሚታዩት በግሪክ አገር በተሰሎንቄ አቅራቢያ ከሚገኘው የኤቶስ ተራራ
(Mount Athos) የተገኙ ምስሎች ናቸው፡፡ ይህ ተራራ የብዙ ቅዱሳን መኖሪያ በመሆኑ በዓለም ይታወቃል፡፡ ታዲያ በዚህ አካባቢ የሚገኙ ንቦች በቅዱሳን ስዕላት ላይ ቀፎን ይሰራሉ፡፡ ሆኖም ግን በአርኪቴክት የተሰመረላቸው ይመስል የሚሰሩት በቅዱሳኑ ዙሪያ ለክተው ነው፡፡ በምንም ተዓምር የቅዱሱን/የቅድስቷን
ፊት ደግሞ አይነኩም፡፡
የእግዚአብሔር ሥራ አይደንቀም?
.
ምስሉን የሰጠኝን ወንድማችንን Carlito Frédéric Cadiou በክርስትና ስሙ
ገብረእግዚአብሔር ብላችሁ በጸሎት አስቡልኝ፡፡ እኔንም ወንድማችሁን
ገብረመስቀልን በጸሎታችሁ አስቡኝ ።
ይቆየን
Share
@And_Haymanot
@And_Haymanot
❖ "ጻድቅ በቀልን ባየ ጊዜ ደስ ይለዋል፤ በኃጢአተኛው ደምም እጁን ይታጠባል።"
መዝሙረ ዳዊት 58:10
ምን ለማለት ፈልጎ ነው?
መልስ፦ ንጉሥ ዳዊት የተናገረው ስለ ክርስቶስ ነው። ጻድቅ የተባለው እርሱ ነው (በእኛም "ጻድቀ ባሕርይ" መባሉን እናውቃለን)። እርሱም የሚበቀለው ኀጢአትን፣ ሞትን እና ዲያብሎስን ነው ይላል መጣፉ ... "በኀጢአተኛውም ደም እጁን ይታጠባል" ሲል ድል መንሳቱን መናገር ነው።[ምንጭ፦ Orthodox Study Bible]፥
@And_Haymanot
@And_Haymanot
መዝሙረ ዳዊት 58:10
ምን ለማለት ፈልጎ ነው?
መልስ፦ ንጉሥ ዳዊት የተናገረው ስለ ክርስቶስ ነው። ጻድቅ የተባለው እርሱ ነው (በእኛም "ጻድቀ ባሕርይ" መባሉን እናውቃለን)። እርሱም የሚበቀለው ኀጢአትን፣ ሞትን እና ዲያብሎስን ነው ይላል መጣፉ ... "በኀጢአተኛውም ደም እጁን ይታጠባል" ሲል ድል መንሳቱን መናገር ነው።[ምንጭ፦ Orthodox Study Bible]፥
@And_Haymanot
@And_Haymanot
🎄🎄 የገና ዛፍ 🎄🎄
☄ 🎉🎊🎁 🎁 🎁 💥🌲 ☄
የገና ዛፍ የባእድ አምልኮ ስርኣት ነውና ከሀገራችን በአፋጣኝ ልናስወግደው ይገባናል!!!
በምዕራቡ ዓለም የክረምቱ ወቅት በጣም አስቸጋሪ ነው። ዛፎች ሁሉ ቅጠሎቻቸው ይረግፋሉ። ልምላሜ አይታይባቸውም። ፅድ ግን በተፈጥሮው ይህን አስቸጋሪ ወቅት ተቋቁሞ የማለፍ ኃይል አለው። በመሆኑም ፅድ ክፉውን ዘመን /ክረምቱን/ ተቋቁሞ መልካሙ ዘመናቸው እስኪመጣላቸው ድረስ በልምላሜ ይቆይላቸዋል። ይህም ሳተርን /ደጉ አምላካቸው/ ከክፉው
አምላክ ለመሸሸግ በፅድ ውስጥ ተደብቆ ይኖራል ብለው ያመናሉ ምዕራባውያኑ። እናም ብራ ሲሆን /በእኛ መስከረም ጠባ እንደምንለው ነው/ የደጉን አምላክ ‹‹የእንኳን ደህና መጣህ›› በዓልን በድምቀት ያከብራሉ።
ተወዳጆች ሁላችንም ለቤተክስቲያናችን ዘብ እንቁም!! በየቤታችንም ገዝተን የምንጠቀም እንዲሁም በየሆቴሎች የሚደረገውንም ለሆቴሎቹ ማኔጀሮች
በትህትና በማግባባት የባህል ወረራው እና የባእድ አምልኮ ልምምዱ ባፋጣኝ እንዲቆም የበኩላችንን እንወጣ!!!!
ቱሪስቶች ቤታቸው እንዳሉ እንዲሰማቸው ለማድረግ ነው በምትል ማደንዘዣ እንዳታዘናጉን አደራ!! ቱሪስት የገዛ ቤቱን ስርኣት ለማየት አይመጣም!!! የሚመጣው የእኛን ስርኣት ለማየት እንጅ የራሱን ሀገር ስርኣት ለማየት አይደለም።
ባዕድ አምልኮ መሆኑን ተረድተን ይህን ከማድረግ እንቆጠብ፡፡
....ይቆየን [በዚሁ ርዕስ በስፋት እንመለሳለን]
Share በማድረግ ይህን ለምናውቃቸው እናሳውቅ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
☄ 🎉🎊🎁 🎁 🎁 💥🌲 ☄
የገና ዛፍ የባእድ አምልኮ ስርኣት ነውና ከሀገራችን በአፋጣኝ ልናስወግደው ይገባናል!!!
በምዕራቡ ዓለም የክረምቱ ወቅት በጣም አስቸጋሪ ነው። ዛፎች ሁሉ ቅጠሎቻቸው ይረግፋሉ። ልምላሜ አይታይባቸውም። ፅድ ግን በተፈጥሮው ይህን አስቸጋሪ ወቅት ተቋቁሞ የማለፍ ኃይል አለው። በመሆኑም ፅድ ክፉውን ዘመን /ክረምቱን/ ተቋቁሞ መልካሙ ዘመናቸው እስኪመጣላቸው ድረስ በልምላሜ ይቆይላቸዋል። ይህም ሳተርን /ደጉ አምላካቸው/ ከክፉው
አምላክ ለመሸሸግ በፅድ ውስጥ ተደብቆ ይኖራል ብለው ያመናሉ ምዕራባውያኑ። እናም ብራ ሲሆን /በእኛ መስከረም ጠባ እንደምንለው ነው/ የደጉን አምላክ ‹‹የእንኳን ደህና መጣህ›› በዓልን በድምቀት ያከብራሉ።
ተወዳጆች ሁላችንም ለቤተክስቲያናችን ዘብ እንቁም!! በየቤታችንም ገዝተን የምንጠቀም እንዲሁም በየሆቴሎች የሚደረገውንም ለሆቴሎቹ ማኔጀሮች
በትህትና በማግባባት የባህል ወረራው እና የባእድ አምልኮ ልምምዱ ባፋጣኝ እንዲቆም የበኩላችንን እንወጣ!!!!
ቱሪስቶች ቤታቸው እንዳሉ እንዲሰማቸው ለማድረግ ነው በምትል ማደንዘዣ እንዳታዘናጉን አደራ!! ቱሪስት የገዛ ቤቱን ስርኣት ለማየት አይመጣም!!! የሚመጣው የእኛን ስርኣት ለማየት እንጅ የራሱን ሀገር ስርኣት ለማየት አይደለም።
ባዕድ አምልኮ መሆኑን ተረድተን ይህን ከማድረግ እንቆጠብ፡፡
....ይቆየን [በዚሁ ርዕስ በስፋት እንመለሳለን]
Share በማድረግ ይህን ለምናውቃቸው እናሳውቅ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
"አንድ ነገር እንድታውቁልኝ እፈልጋለሁ ተመሳስለው የገቡ ቄስ መስለው፣መነኩሴ መስለው፣ ሰባኪ መስለው ስህተትን ለሚዘሩ መናፍቃን ቦታ የለኝም።
ካንሰርን ካልቆረጡት እንደ ማይድን ሁሉ እነዚህንም ቆርጠን እናስወግዳቸዋለን መቀሱ በእጄ ነው! ነገር ግን ንስሃ እንድትገቡ ቀድሜ እመክራችኋለው አባ ሄኖክ በሬ 24 ሰዓት ክፍት ነው።"
ብፁዕ አቡነ ሄኖክ በሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል ከተናገሩት የተወሰደ
14/04/2011
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ካንሰርን ካልቆረጡት እንደ ማይድን ሁሉ እነዚህንም ቆርጠን እናስወግዳቸዋለን መቀሱ በእጄ ነው! ነገር ግን ንስሃ እንድትገቡ ቀድሜ እመክራችኋለው አባ ሄኖክ በሬ 24 ሰዓት ክፍት ነው።"
ብፁዕ አቡነ ሄኖክ በሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል ከተናገሩት የተወሰደ
14/04/2011
@And_Haymanot
@And_Haymanot
☄🎄 የገና ዛፍ 🎄 ☄
☄ 🎉🎊 🎁 🎁 🌲 ☄
@And_Haymanot
🎄 የገና ዛፍ የነጮች የባዕድ አምልኮ መገለጫ መሆኑን ያውቃሉ? የገና ዛፍ ታሪክና አመጣጡ የገናን ዛፍ የት መጣውን /ምንጩን/ ስናጤነው ቅዱሳት
መጻሕፍት እንዲህ ይነግሩናል። በዞራስተርን የሁለት አማልክት
ዕምነት የሚያምኑት ምዕራባውያን አዲሱን ዓመታቸውን /2017/
ተቀብለዋል። በዞራስተርን የሁለት አማልክት ዕምነት መሠረት ክፉውና ደጉ የተባሉ ሁለት አማልክቶች አሉ። እንደ ዕምነቱ አስተሳሰብ ከሆነ እዚህ ምድር ላይ የሆነው እየሆነው ያለውና
የሚሆነውም ማንኛውም ነገር በሙሉ የሚከናወነው በእነዚህ በሁለቱ አማልክቶች ፉክክር ነው። ክፉው አምላክ ከሰለጠነ /የበላይ ከሆነ/ በምድር ላይ ክፉ የሆኑ ብዙ ነገሮች ይከሰታሉ። በተቃራኒው ደግሞ ደጉ አምላክ ከሰለጠነ በጎ ነገሮች ይከሰታሉ
ማለት ነው። ምዕራባውያኑ ታዲያ ደጉን አምላካቸውን ማለትም ጣዖታቸውን ሳተርን ብለው ይጠሩታል።
☄ በምዕራቡ ዓለም የክረምቱ ወቅት በጣም አስቸጋሪ ነው። ዛፎች ሁሉ ቅጠሎቻቸው ይረግፋሉ። ልምላሜ አይታይባቸውም። ፅድ 🎄 ግን በተፈጥሮው ይህን አስቸጋሪ ወቅት ተቋቁሞ የማለፍ ኃይል አለው። በመሆኑም ፅድ ክፉውን ዘመን /ክረምቱን/ ተቋቁሞ መልካሙ ዘመናቸው እስኪመጣላቸው ድረስ በልምላሜ ይቆይላቸዋል።
💫 ይህም ሳተርን /ደጉ አምላካቸው/ ከክፉው አምላክ ለመሸሸግ በፅድ ውስጥ ተደብቆ ይኖራል ብለው
ያመናሉ ምዕራባውያኑ። እናም ብራ ሲሆን /በእኛ መስከረም ጠባ
እንደምንለው ነው/ የደጉን አምላክ ‹‹የእንኳን ደህና መጣህ›› በዓልን በድምቀት ያከብራሉ። ምስጋና ለፅዱ ይሁንና ደጉ አምላካቸውን ደብቆ ስላቆየላቸው ባለውለታ ስለሆነ የደጉን አምላክ የእንኳን ደህና መጣህ በዓል
ሲያከብሩ ታዲያ ፅድን ለበዓላቸው ማድመቂያነት ይጠቀሙበት ነበር። ይኸው ትውፊታቸው ዛሬም ድረስ አለ። በአጭሩ ከጥንት ጀምሮ እነርሱ ይኽን በዓል የሚያከብሩት ሳተርን ለተባለው
ጣዖት /ደጉ አምላክ/ ያደርጉት የነበረው ሥርዓት ነው። በዚህ ዓይነት ሁኔታ ታላቁ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ክርስትናን በአዋጅ
ካስፋፋበት ጊዜ ጀምሮ በውጭው ዓለም ጥንት የነበሩ ብዙ ጣዖታዊ በዓላት ክርስቲያናዊ በዓል ሆነው አሁንም ድረስ በብዙ ሀገራት እየተከበሩ ይገኛሉ። /ነገር ግን ልደትንና ትንሣኤን ጨምሮ ሌሎችም በዓላት ቢሆኑ ሥርዓታቸውን በጠበቁ መልኩ የሚከበርባቸው አንዳንድ ሀገራት እንዳሉ የዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ
ለማስገንዘብ ይወዳል።/
☄ በአንድም ይሁን በሌላ ምክንያት በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ይኸው እስከዛሬ እኛም ይኽንኑ የባዕድና የጣኦት አምልኮ በዓላቸውን በእነሱው ልማድ መሠረት የፅድ የገና ዛፍ እየሠራን
ስናከብርላቸው ኖረናል። አባቶቻችን ሲናገሩ ‹‹እግዚአብሔር ዓለሙን ከፈጠረበት ጥበቡ ይልቅ ሰው ሆኖ ዓለሙን ያዳነበት ጥበቡ እጅግ ረቂቅና ጥልቅ ነው›› ይላሉ። እንዴት ደስ የሚል
አገላለፅ ነው!!! ታዲያ ምን ዋጋ አለው? አለመታደል ሆኖ ይሁን አሊያም አለማወቃችን ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋን ይግባውና እጅግ ድንቅ የሆነውን የጌታችንን የአምላካችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል ከእንደዚህ ዓይነቱ ምዕራባዊ የጣዖት በዓል ጋር ቀላቅለን እናከብራለን።
@And_Haymanot
👉 ይህ እጅግ አሳዘኝ ነገር ነው በእውነት! በአንድ ወቅት በምዕራባውያን የገና በዓል ሰሞን በ‹‹BBC channel 4›› ላይ የበዓል መርሀ ግብር /program/ ቀርቦ ነበር። በመርሀ ግብሩ ላይ የተለያዩ የዕምነት ድርጅቶች የበዓል
አከባበር፣ የጸሎትና የመዝሙር ሥርዓትና ሌሎችንም ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች ከቀረቡ በኋላ የመርሀ ግብሩ መሪ
በመጨረሻ እንዲህ ነው ያለው፡- “now let us see the real Christianity” ማለትም “አሁን እውነተኛውን የክርስትና
ሃይማኖት እንመልከት” በሚል መሸጋገሪያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ
ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን የበዓል አከባበር ስነ-ሥርዓት ማስተላለፍ ጀመረ። ካህናት አባቶች ወረብ ሲያቀርቡ፣ የቅዳሴውን ሥርዓት፣ መዝሙሩ ሲዘመር፤ ጧፉ እየበራ ወንጌሉ ሲነበብ፣ እጣኑ እየጤሰ ስብሐተ እግዚአብሔር ሲቀርብ......
ሁሉንም በየተራ ማቅረብ ጀመረ። እናም እነርሱ ማለት ምዕራባውያን ስለ ዕምነት ጉዳይ እውነት የሆነውን ነገር ፍለጋ
ፊታቸውን ወደ እኛ ባዞሩበት ወቅት እኛ ደግሞ እውነተኛውን ማንነታችንን ባንጥልና የአጉል ባህል ተገዢዎች ባንሆን ብሎም በአምልኮ ጣኦታቸው ተሳታፊዎች ባንሆን መልካም ነው።
መልካም ነው ብቻም ሳይሆን መንፈሳዊና ሞራላዊ ግዴታዎችም አሉብን።
በእርግጥ እኛ የዚህ ዘመን ትውልዶች የግሎባላይዜሽን ጎርፍ ጠራርጎ የወሰደን ስለሆንንና ‹‹በጣም ስልጡኖችና ዘመናውያንም›› ስለሆንን ይህ ምን ማለት እንደሆነ ላይገባን
ይችላል፤ እንዲገባንም አንፈልግም፡፡
የሴቶቻችን እርቃን መሄድ፣ አካሎቻቸውን መነቀስና መበሳት፣ የወንዶች አለባበስና ፀጉር አቆራረጥ… እነዚህና ሌሎቹም ነገሮች በዘመናዊነት ሰበብ የመጡብን የዘመናዊ ቅኝ ግዛት ውጤቶች
ናቸው፡፡ በግል አዳኝ ‹‹ኢየሱሴ›› ስም ብዙኃኑን ሕዝባችንን ፈጣሪውን አስክደው አምላክ የለሽ አደረጉትና ለግሎባላይዜሽናቸው የተመቸ ዝርው ትውልድ ፈጠሩ፡፡ አሁንማ ጭራሽ ለይቶላቸው ‹‹church of Satan›› በማለት ‹የሰይጣን ቤተክርስቲያን› ከፍተው አባሎቻቸው በሆኑ ‹‹ታዋቂ የሂፖፕ›› አቀንቃኞቻቸው አማካኝነት የአባላቶቻቸውን ቁጥር ለመጨመር
እኛም ሀገር ብቅ ብለውልናል፡፡ ግብረ ሰዶማዊነት እንደግለሰብ ነፃነት አድርጋችሁ ካልተቀበላችሁ እርዳታ አንሰጣችሁምም ተባልን፡፡ እሺ እነዚህና ሌሎቹም አስከፊ ኃጢአቶቻቸውን
በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እንድንቀበል ቢያስገድዱንም
ቢያንስ እኛ በራሳችን ጊዜ ለምን የራሳችንን ባሕል ድምጥማጡን
በማጥፋት የእነርሱን ባሕል እንከተላለን? የዘመናዊነት መገለጫው የራስን ባሕልና እምነት በሌሎች መተካት ሆነ
እንዴ? ድሮ ቅኝ ቅዛት ተገዝተን ቢሆን ኖሮ ምንድን ነበር የምናጣው? ቀላል ነው መልሱ፡- የራስ ማንነት፣ እምነት፣ ባሕል፣ታሪክ…አይኖረንም ነበር፡፡ አሁን ታዲያ በዘመናዊው ቅኝ አገዛዝ ሥርዓት ምክንያት እነዚህን ነገሮች አላጣናቸውም ይሆን?
🙏 እንዲያው በመድኃኔዓለም! እባካችሁ ከፊት ለፊታችን በታላቅ ጉጉትና ተስፋ የምንጠብቀውን ከድቅድቅ ጨለማ ወጥተን ብርሃን ያገኘንበትን የአማኑኤልን የልደት በዓል የገናን ዛፍ በመጠቀም ከነጮቹ ባዕድና ጣኦት አምልኮ ጋር አንቀላቅለው፡፡ ልደቱን ቅድስት ቤተክርስቲያን እንደሚገባው አድርጋ ታከብረዋለችና እኛም ልጆቿ እንደሚገባው መጠን ልደቱን እናክብር፡፡ የገና ዛፍ የባዕድ አምልኮ መገለጫ ነው፡፡ ማህቶተ ቤተክርስቲያን ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ምንድን ነበር
ያለው! ‹‹ከማያምኑ ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመዱ፤ ጽድቅ ከዓመፅ ጋር ምን ተካፋይነት አለውና? ብርሃንም ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው? ክርስቶስስ ከቤልሆር ጋር ምን መስማማት አለው? ወይስ የሚያምን ከማያምን ጋር ምን ክፍል አለው?
የእግዚአብሔርን ታቦት በጣዖት ቤት ውስጥ የሚያኖር ማነው?
2ኛ ቆሮ 6፡14-16፡፡ “በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ” 2ኛ ቆሮ 13፡5፡፡ ተዘጋጀ በጀማል ሀሰን ዓሊ (ስመ ጥምቀቱ ገብረሥላሴ) የአባቶቻችን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር በሃይማኖታችንና በኦርቶዶክሳዊ ማንነታችን ያፅናን አሜን።
(የጽሑፉ ምንጮች፡- አናቆጸ ሲኦል በብርሃኑ ጐበና፤ ሐመር 5ኛ
ዓመት ቁ1፣ 1989 ዓ.ም
@And_Haymanot
@And_Haymanot
☄ 🎉🎊 🎁 🎁 🌲 ☄
@And_Haymanot
🎄 የገና ዛፍ የነጮች የባዕድ አምልኮ መገለጫ መሆኑን ያውቃሉ? የገና ዛፍ ታሪክና አመጣጡ የገናን ዛፍ የት መጣውን /ምንጩን/ ስናጤነው ቅዱሳት
መጻሕፍት እንዲህ ይነግሩናል። በዞራስተርን የሁለት አማልክት
ዕምነት የሚያምኑት ምዕራባውያን አዲሱን ዓመታቸውን /2017/
ተቀብለዋል። በዞራስተርን የሁለት አማልክት ዕምነት መሠረት ክፉውና ደጉ የተባሉ ሁለት አማልክቶች አሉ። እንደ ዕምነቱ አስተሳሰብ ከሆነ እዚህ ምድር ላይ የሆነው እየሆነው ያለውና
የሚሆነውም ማንኛውም ነገር በሙሉ የሚከናወነው በእነዚህ በሁለቱ አማልክቶች ፉክክር ነው። ክፉው አምላክ ከሰለጠነ /የበላይ ከሆነ/ በምድር ላይ ክፉ የሆኑ ብዙ ነገሮች ይከሰታሉ። በተቃራኒው ደግሞ ደጉ አምላክ ከሰለጠነ በጎ ነገሮች ይከሰታሉ
ማለት ነው። ምዕራባውያኑ ታዲያ ደጉን አምላካቸውን ማለትም ጣዖታቸውን ሳተርን ብለው ይጠሩታል።
☄ በምዕራቡ ዓለም የክረምቱ ወቅት በጣም አስቸጋሪ ነው። ዛፎች ሁሉ ቅጠሎቻቸው ይረግፋሉ። ልምላሜ አይታይባቸውም። ፅድ 🎄 ግን በተፈጥሮው ይህን አስቸጋሪ ወቅት ተቋቁሞ የማለፍ ኃይል አለው። በመሆኑም ፅድ ክፉውን ዘመን /ክረምቱን/ ተቋቁሞ መልካሙ ዘመናቸው እስኪመጣላቸው ድረስ በልምላሜ ይቆይላቸዋል።
💫 ይህም ሳተርን /ደጉ አምላካቸው/ ከክፉው አምላክ ለመሸሸግ በፅድ ውስጥ ተደብቆ ይኖራል ብለው
ያመናሉ ምዕራባውያኑ። እናም ብራ ሲሆን /በእኛ መስከረም ጠባ
እንደምንለው ነው/ የደጉን አምላክ ‹‹የእንኳን ደህና መጣህ›› በዓልን በድምቀት ያከብራሉ። ምስጋና ለፅዱ ይሁንና ደጉ አምላካቸውን ደብቆ ስላቆየላቸው ባለውለታ ስለሆነ የደጉን አምላክ የእንኳን ደህና መጣህ በዓል
ሲያከብሩ ታዲያ ፅድን ለበዓላቸው ማድመቂያነት ይጠቀሙበት ነበር። ይኸው ትውፊታቸው ዛሬም ድረስ አለ። በአጭሩ ከጥንት ጀምሮ እነርሱ ይኽን በዓል የሚያከብሩት ሳተርን ለተባለው
ጣዖት /ደጉ አምላክ/ ያደርጉት የነበረው ሥርዓት ነው። በዚህ ዓይነት ሁኔታ ታላቁ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ክርስትናን በአዋጅ
ካስፋፋበት ጊዜ ጀምሮ በውጭው ዓለም ጥንት የነበሩ ብዙ ጣዖታዊ በዓላት ክርስቲያናዊ በዓል ሆነው አሁንም ድረስ በብዙ ሀገራት እየተከበሩ ይገኛሉ። /ነገር ግን ልደትንና ትንሣኤን ጨምሮ ሌሎችም በዓላት ቢሆኑ ሥርዓታቸውን በጠበቁ መልኩ የሚከበርባቸው አንዳንድ ሀገራት እንዳሉ የዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ
ለማስገንዘብ ይወዳል።/
☄ በአንድም ይሁን በሌላ ምክንያት በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ይኸው እስከዛሬ እኛም ይኽንኑ የባዕድና የጣኦት አምልኮ በዓላቸውን በእነሱው ልማድ መሠረት የፅድ የገና ዛፍ እየሠራን
ስናከብርላቸው ኖረናል። አባቶቻችን ሲናገሩ ‹‹እግዚአብሔር ዓለሙን ከፈጠረበት ጥበቡ ይልቅ ሰው ሆኖ ዓለሙን ያዳነበት ጥበቡ እጅግ ረቂቅና ጥልቅ ነው›› ይላሉ። እንዴት ደስ የሚል
አገላለፅ ነው!!! ታዲያ ምን ዋጋ አለው? አለመታደል ሆኖ ይሁን አሊያም አለማወቃችን ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋን ይግባውና እጅግ ድንቅ የሆነውን የጌታችንን የአምላካችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል ከእንደዚህ ዓይነቱ ምዕራባዊ የጣዖት በዓል ጋር ቀላቅለን እናከብራለን።
@And_Haymanot
👉 ይህ እጅግ አሳዘኝ ነገር ነው በእውነት! በአንድ ወቅት በምዕራባውያን የገና በዓል ሰሞን በ‹‹BBC channel 4›› ላይ የበዓል መርሀ ግብር /program/ ቀርቦ ነበር። በመርሀ ግብሩ ላይ የተለያዩ የዕምነት ድርጅቶች የበዓል
አከባበር፣ የጸሎትና የመዝሙር ሥርዓትና ሌሎችንም ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች ከቀረቡ በኋላ የመርሀ ግብሩ መሪ
በመጨረሻ እንዲህ ነው ያለው፡- “now let us see the real Christianity” ማለትም “አሁን እውነተኛውን የክርስትና
ሃይማኖት እንመልከት” በሚል መሸጋገሪያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ
ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን የበዓል አከባበር ስነ-ሥርዓት ማስተላለፍ ጀመረ። ካህናት አባቶች ወረብ ሲያቀርቡ፣ የቅዳሴውን ሥርዓት፣ መዝሙሩ ሲዘመር፤ ጧፉ እየበራ ወንጌሉ ሲነበብ፣ እጣኑ እየጤሰ ስብሐተ እግዚአብሔር ሲቀርብ......
ሁሉንም በየተራ ማቅረብ ጀመረ። እናም እነርሱ ማለት ምዕራባውያን ስለ ዕምነት ጉዳይ እውነት የሆነውን ነገር ፍለጋ
ፊታቸውን ወደ እኛ ባዞሩበት ወቅት እኛ ደግሞ እውነተኛውን ማንነታችንን ባንጥልና የአጉል ባህል ተገዢዎች ባንሆን ብሎም በአምልኮ ጣኦታቸው ተሳታፊዎች ባንሆን መልካም ነው።
መልካም ነው ብቻም ሳይሆን መንፈሳዊና ሞራላዊ ግዴታዎችም አሉብን።
በእርግጥ እኛ የዚህ ዘመን ትውልዶች የግሎባላይዜሽን ጎርፍ ጠራርጎ የወሰደን ስለሆንንና ‹‹በጣም ስልጡኖችና ዘመናውያንም›› ስለሆንን ይህ ምን ማለት እንደሆነ ላይገባን
ይችላል፤ እንዲገባንም አንፈልግም፡፡
የሴቶቻችን እርቃን መሄድ፣ አካሎቻቸውን መነቀስና መበሳት፣ የወንዶች አለባበስና ፀጉር አቆራረጥ… እነዚህና ሌሎቹም ነገሮች በዘመናዊነት ሰበብ የመጡብን የዘመናዊ ቅኝ ግዛት ውጤቶች
ናቸው፡፡ በግል አዳኝ ‹‹ኢየሱሴ›› ስም ብዙኃኑን ሕዝባችንን ፈጣሪውን አስክደው አምላክ የለሽ አደረጉትና ለግሎባላይዜሽናቸው የተመቸ ዝርው ትውልድ ፈጠሩ፡፡ አሁንማ ጭራሽ ለይቶላቸው ‹‹church of Satan›› በማለት ‹የሰይጣን ቤተክርስቲያን› ከፍተው አባሎቻቸው በሆኑ ‹‹ታዋቂ የሂፖፕ›› አቀንቃኞቻቸው አማካኝነት የአባላቶቻቸውን ቁጥር ለመጨመር
እኛም ሀገር ብቅ ብለውልናል፡፡ ግብረ ሰዶማዊነት እንደግለሰብ ነፃነት አድርጋችሁ ካልተቀበላችሁ እርዳታ አንሰጣችሁምም ተባልን፡፡ እሺ እነዚህና ሌሎቹም አስከፊ ኃጢአቶቻቸውን
በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እንድንቀበል ቢያስገድዱንም
ቢያንስ እኛ በራሳችን ጊዜ ለምን የራሳችንን ባሕል ድምጥማጡን
በማጥፋት የእነርሱን ባሕል እንከተላለን? የዘመናዊነት መገለጫው የራስን ባሕልና እምነት በሌሎች መተካት ሆነ
እንዴ? ድሮ ቅኝ ቅዛት ተገዝተን ቢሆን ኖሮ ምንድን ነበር የምናጣው? ቀላል ነው መልሱ፡- የራስ ማንነት፣ እምነት፣ ባሕል፣ታሪክ…አይኖረንም ነበር፡፡ አሁን ታዲያ በዘመናዊው ቅኝ አገዛዝ ሥርዓት ምክንያት እነዚህን ነገሮች አላጣናቸውም ይሆን?
🙏 እንዲያው በመድኃኔዓለም! እባካችሁ ከፊት ለፊታችን በታላቅ ጉጉትና ተስፋ የምንጠብቀውን ከድቅድቅ ጨለማ ወጥተን ብርሃን ያገኘንበትን የአማኑኤልን የልደት በዓል የገናን ዛፍ በመጠቀም ከነጮቹ ባዕድና ጣኦት አምልኮ ጋር አንቀላቅለው፡፡ ልደቱን ቅድስት ቤተክርስቲያን እንደሚገባው አድርጋ ታከብረዋለችና እኛም ልጆቿ እንደሚገባው መጠን ልደቱን እናክብር፡፡ የገና ዛፍ የባዕድ አምልኮ መገለጫ ነው፡፡ ማህቶተ ቤተክርስቲያን ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ምንድን ነበር
ያለው! ‹‹ከማያምኑ ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመዱ፤ ጽድቅ ከዓመፅ ጋር ምን ተካፋይነት አለውና? ብርሃንም ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው? ክርስቶስስ ከቤልሆር ጋር ምን መስማማት አለው? ወይስ የሚያምን ከማያምን ጋር ምን ክፍል አለው?
የእግዚአብሔርን ታቦት በጣዖት ቤት ውስጥ የሚያኖር ማነው?
2ኛ ቆሮ 6፡14-16፡፡ “በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ” 2ኛ ቆሮ 13፡5፡፡ ተዘጋጀ በጀማል ሀሰን ዓሊ (ስመ ጥምቀቱ ገብረሥላሴ) የአባቶቻችን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር በሃይማኖታችንና በኦርቶዶክሳዊ ማንነታችን ያፅናን አሜን።
(የጽሑፉ ምንጮች፡- አናቆጸ ሲኦል በብርሃኑ ጐበና፤ ሐመር 5ኛ
ዓመት ቁ1፣ 1989 ዓ.ም
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ውርጃ
የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አስተምሮ
ምድሪቱ (የሴቲቱ ማኅፀን) ዘር ከዘራንባት በኃላ ፍሬ እንዳታፈራ የምናደርገው ስለ ምንድን ነው? ውርጃን የምናካሒደው ስለ ምንድን ነው? እናንተ ዘማውያን ሆይ! ዝሙት መፈጸማችሁ ሳይበቃ ሰውን መግደል ትጨምሩበታላችሁን? እንግዲህ ስካር እንደ ምን ሴተኛ አዳሪን እንደሚያደርግ፣ ሴተኛ አዳሪነትም ዘማዊ፣ ዝሙትም እንደ ምን ነፍሰ ገዳይ እንደሚያደርግ ታስተውላላችሁን?
ይህን ምን ብዬ እንደምጠራው አላውቅም ምክንያቱም ይህን ሕፃን ከተወለደ በኃላ ከቤት አስወጥተን አይደለም ያባረርነው፤ እንዳይወለድ ከለከልነው እንጂ ወዮ! ስለምን የእግዚአብሔርን ስጦታ ታቃልላላችሁ? ስለምን ሕጉን ትተላለፋላችሁ? ስለምን ርጉም የሆነን ግብር እንደ በረከት ትቆጥሩታላችሁ? ስለምን እግዚአብሔር ሰውን ለመፍጠር ያዘጋጀውን መንገድ መግደያ ታደርጉታላችሁ? ስለምን ልጅን አቅፋ እንድትስም የተፈጠረችውን ሴት ነፍሰ ገዳይ እንድትሆን ታደርጓታላችሁ? እህቴ ሆይ! ፍቅረ ንዋይ ዐይንሽን አሳውሮት፣ ዳግመኛም በፍትወት ከሚመስሉሽ ጋር ዝሙትን ለመሥራት ስትዪ ፍምን በራስሽ ላይ አታከማቺ ወንድሜ ሆይ! ምንም እንኳን ይህን አሰቃቂ ግድያ የምትፈጽመው እርሷ ብትሆንም አንተም ከእርሷ ጋር ተባባሪ ነህ። ✞
ምንጭ፦ ሰማዕትነት አያምልጣችው በገብረ እግዚአብሔር ኪደ ገፅ 53
@And_Haymanot
@And_Haymanot
የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አስተምሮ
ምድሪቱ (የሴቲቱ ማኅፀን) ዘር ከዘራንባት በኃላ ፍሬ እንዳታፈራ የምናደርገው ስለ ምንድን ነው? ውርጃን የምናካሒደው ስለ ምንድን ነው? እናንተ ዘማውያን ሆይ! ዝሙት መፈጸማችሁ ሳይበቃ ሰውን መግደል ትጨምሩበታላችሁን? እንግዲህ ስካር እንደ ምን ሴተኛ አዳሪን እንደሚያደርግ፣ ሴተኛ አዳሪነትም ዘማዊ፣ ዝሙትም እንደ ምን ነፍሰ ገዳይ እንደሚያደርግ ታስተውላላችሁን?
ይህን ምን ብዬ እንደምጠራው አላውቅም ምክንያቱም ይህን ሕፃን ከተወለደ በኃላ ከቤት አስወጥተን አይደለም ያባረርነው፤ እንዳይወለድ ከለከልነው እንጂ ወዮ! ስለምን የእግዚአብሔርን ስጦታ ታቃልላላችሁ? ስለምን ሕጉን ትተላለፋላችሁ? ስለምን ርጉም የሆነን ግብር እንደ በረከት ትቆጥሩታላችሁ? ስለምን እግዚአብሔር ሰውን ለመፍጠር ያዘጋጀውን መንገድ መግደያ ታደርጉታላችሁ? ስለምን ልጅን አቅፋ እንድትስም የተፈጠረችውን ሴት ነፍሰ ገዳይ እንድትሆን ታደርጓታላችሁ? እህቴ ሆይ! ፍቅረ ንዋይ ዐይንሽን አሳውሮት፣ ዳግመኛም በፍትወት ከሚመስሉሽ ጋር ዝሙትን ለመሥራት ስትዪ ፍምን በራስሽ ላይ አታከማቺ ወንድሜ ሆይ! ምንም እንኳን ይህን አሰቃቂ ግድያ የምትፈጽመው እርሷ ብትሆንም አንተም ከእርሷ ጋር ተባባሪ ነህ። ✞
ምንጭ፦ ሰማዕትነት አያምልጣችው በገብረ እግዚአብሔር ኪደ ገፅ 53
@And_Haymanot
@And_Haymanot
የኔ አባት…. ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት
@And_Haymanot
(ያንብቡ ለሌሎች ያጋሩ)
👉 የኔ አባት ብዙ ጊዜ ሳዮት የሰንበት ትምህርት ቤት ነገር የገባዎት አልመሰለኝም... መቼስ ከርሶ ባላውቅም ጥቂት ልበልዎት.. አደራ ያስተውሉኝ!
✍ ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የኔ አባት… እኛ ልጆችዎ ሰው የሆንበት ሥፍራ ነው። ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የኔ አባት… በፍቅር ወድቀን፣ በፍቅር ተነሥተን፣ በፍቅር ተርበን፣ በፍቅር በልተን፣ በፍቅር ተጣልተን፣ በፍቅር ታርቀን፣ በፍቅር ተኮራርፈን ፣ በፍቅር ተጨዋውተን፣ በፍቅር አልቅሰን፣ በፍቅር ስቀን፣ በፍቅር ኮርኩመን፣ በፍቅር ተኮርኩመን፣ በፍቅር ተፎካክረን፣ በፍቅር ተሸናንፈን፣ በፍቅር ተምረን፣ በፍቅር ተተራርበን፣ በፍቅር አጥፍተን፣ በፍቀር ታርመን እኛነታችን የተሠራበት ቦታ ነው፡፡ አባቴ ይሙቱ! … እኔ በርሶ ምዬ አልዋሽም፡፡
❖ ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የኔ አባት… በፍቅር ባሪያ የሆንበት፣ በፍቅርም ገዢ የሆንበት ቦታ ነው፡፡ አሽከርም ንጉሥም ሆነንበታል፤ አባቴ አሽከርና ንጉሥ በአንድ ጊዜ ሆነው ያውቃሉ? በፍቅር ባሪያም ገዢም ሆነውስ ያውቃሉ? በእውነት እንደዛ ከሆኑስ እርሶም ሰንበት ተማሪ ኖት ማለት ነው፡፡ ነቃሁቦት፤ ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የኔ አባት ልጅ ሳለን ሥራ አመራርን ያጠናንበት፣ የሕዝብ አስተዳደርን የተማርንበት ፣ በተለያየ ሙያ ስብጥር የተሰባጠርንበት፣ ለአረንጓዴ ልማት አትክልትን የተከልንበት፣ በሀገር ፍቅር የነደድንበት፣ በዕቅበተ እምነት የበለጸግንበት፣ በበጎ አድራጎት ስለ ወገን ማሰብን ያየንበት፣ ለሀገር ጥሩ ዜጋ መሆንን የቀሰምንበት ቦታ ነው፡፡
♦ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የኔ አባት… ካለዘር ክፍፍል የተፋቀርንበት፣ እገሌ ከዚህ ነው እገሌም ከዚያ ነው ያልተባለበት ሰሜንና ደቡብ፣ ምዕራብና ምስራቅ የሌለው ቦታ ነው፡፡ ሰንበት ተማሪ ሲሆኑ አባቴ… ብሔሮ ክርስትና፣ ቋንቋዎ ፍቅር ፣ ሀገርዎ በሰማይ ፣ ንጉሦ ክርስቶስ ይሆናል፡፡
✞ እመቤቴን! የኔ አባት… መቼስ ከእርሶ አናውቅም፣ እንደርሶ ሊቅም አይደለንም፣ ብሉዩን ከሐዲሱ ፣ ሊቃውንቱን ከመነኮሳቱም አናመሰጥር ይሆናል፤ ሰንበት ተማሪ ሲኮን ግን አባቴ… በሐዲስ ኪዳንና በብሉይ ኪዳን ያለው እንደ እሳት የሚንቀለቀል ፍቅረ ቤተ ክርስቲያን በውስጥዎ ይነዳል፡፡ ቤተ ክርቲያን ስትነካ አካሎ እንደተቆረጠ ያንገበግቦታል፤ ትምህርትዎን ሥራዎን እርግፍ አድርገው መፍትሔ ለመስጠት ይሮጣሉ፤…. ብቻ አባቴ ሰንበት ትምህርት ቤት የቅንዐተ ቤተ ክርስቲያን እሳት የሚንቦገቦግባት ምድጃ ናት፡፡
🔷 አባቴ… ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት፣ እርሶ የሚወዷቸው ትልቁ መምህር የተማሩበት ቦታ ነው፤ እርሶ የሚያከብሯቸው ትልቁ ሊቅም ማስተማርን የጀመሩበት ቦታ ነው፤ ያኔ ተኮለታትፈው ባያስተምሩን ኖሮ ዛሬ እርሶን የመሰለ አባት በተገኙበት ጉባኤ ለማስተማር መንፈሳዊ ልምድ አይኖራቸውም ነበር፡፡ እኛ አሜን ባንላቸው ኖሮ ዛሬ በሺ የሚቆጠር ምእመን አሜን አይላቸውም ነበር፡፡ ድንግልን! በዚህ ቅንጣት አልጠራጠርም፡፡
♠ ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የኔ አባት… የቤተ ክርስቲያን ጠላቶች የሆኑ ተኩላዎች እንደጉድ የሚፈሩት ቦታ ነው፤ የቤተ ክርስቲያን የቁርጥ ቀን ልጆች አሉበታ፤ አባቴ… ሰንበት ትምህርት ቤት እንደ ጳውሎስና እንደ ሲላስ ሲያገለግሉ የሚታሠሩበት ቦታ ነው፤ ያኔ የቤተ ክርስቲያን ጠላቶች የእግዚአብሔር ቅዱሳንን ነገር እየጠመዘዙ ከነገሥታት ጋር እንደሚያጣሉና በምድራዊ ፍርድ ቤት እንደሚገትሩ… በሰንበት ትምህርት ቤትም እንዲሁ ነው፤ ለሃይማኖት ሲቆረቆሩ የፓርቲ አባል የመንግሥት ጠላት ተደርገው ይከሰሳሉ፤ የቤተ ክርስቲያንን መዘረፍ ሲቃወሙ በዓለማዊ ፍርድ ቤት አሸብረዋል ተብለው ይገተራሉ፡፡
♣ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የኔ አባት ወንድምዎ በኃጢአት ሲወድቅ እንደእነ ቅዱስ መቃርዮስ የወንድሞን ነውር ለመሸፈን ቅርጫት የሚደፉበት ቦታም ነው፡፡ በየቦታው ሲናቁና ሲባረሩም በፍቅር ተመክረው የሚመለሱበት ገዳም ነው፡፡ በወጣትነት ብዙ እያጠፉ በብዙ የሚማሩበት ቦታም ነው፡፡
❤ አባቴ… እውነተኛ ወንድሞች አሉዎት? በሐዘንዎ ጊዜ ሳይለዮት ከልብ የሚያስተዛዝኖት፣ ማስተዛዘን ብቻም ሳይሆን በመንፈስ የሚያጸኑዎት… ወንድሞች አሎት? አብረው ውለው አብረው አድረው… እንግዳን አስተናግደው፣ ዕቃ አጥበው የሚያግዙዎትስ እኅቶች አሉዎት? በደስታዎ ጊዜ ከእርስዎ ጋር አብረው ከልብ የሚደሰቱ፣ ድግሶን ድግሳቸው አድርገው የሚንደፋደፉ ወዳጆች አሉዎት? እኚህ ከሌሉዎት የኔ አባት አንድ ነገር ጎሎታል ማለት ነው… ሰንበት ተማሪነት አልነካካዎትም ማለት ነው፡፡
💮 ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የኔ አባት አንድነትና ኅብረት አካል ነሥቶ የሚያዩበት ቦታ፤ አባቴ ይሙቱ እውነቴን ነው፡፡ አንድነትና ንጹህ ፍቅር በስምንተኛው ሺ ገዝፎ የሚታይበት ገነት ነው ሰንበት ትምህርት ቤት፡፡ ለዛ ነው እኮ አባቴ… ሰነፍ ሆነን እንኳን እንደ ብርቱ የምንታየው፣ ምንም ሳንደክምበት እንኳን አገልግሎታችንና ሐሳባችን የሚሞላው… ምንም ሳናውቅ እንኳን ከአዋቂዎች በላይ የምናገለግለው… አባቴ ይሙቱ… ይኸው በርሶ ምያለሁ… ይሄ ሁሉ ስለአንድነታችንና ስለፍቅራችን ነው፡፡ እንጂማ እኛ አኮ ባዶ ነን…፤ ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የኔ አባት… ባዶ ሳሉ ምሉዕ የሚሆኑባት ሥፍራ ነች፡፡
✅ስለዚህ አባቴ… ቢቻሎ እርሶም ሰንበት ተማሪ ይሁኑ፤ አባል ሆነው ይቀላቀሉን፤ ካልተቻሎም አባል የሚሆኑትን አይከልክሉ፡፡ ቢቻልዎት ሰንበት ትምህርት ቤትን ከልቦ ይደግፉ፤ ባለዎት ነገር ሁሉ ያበርቱ፡፡ ካልቻሉም አደራ አገልግሎቱን ከሚያደናቅፉት ፣ አባላትን ከሚያንገላቱት ጎን አይሁኑ፡፡ ቢቻልዎት ስለሰንበት ትምህርት ቤት መልካምነት ያውሩ፤ ባይቻልዎትም ዝም ይበሉ እንጂ ልጆችዎን አይሙ፡፡
ቢቻልዎት በጸሎትዎ ሰንበት ትምህርት ቤትን ያስቡ፤ ባይቻልዎትም ቢያንስ አይርገሙ፡፡
(በዲ/ን ሕሊና በለጠ)
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
(ያንብቡ ለሌሎች ያጋሩ)
👉 የኔ አባት ብዙ ጊዜ ሳዮት የሰንበት ትምህርት ቤት ነገር የገባዎት አልመሰለኝም... መቼስ ከርሶ ባላውቅም ጥቂት ልበልዎት.. አደራ ያስተውሉኝ!
✍ ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የኔ አባት… እኛ ልጆችዎ ሰው የሆንበት ሥፍራ ነው። ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የኔ አባት… በፍቅር ወድቀን፣ በፍቅር ተነሥተን፣ በፍቅር ተርበን፣ በፍቅር በልተን፣ በፍቅር ተጣልተን፣ በፍቅር ታርቀን፣ በፍቅር ተኮራርፈን ፣ በፍቅር ተጨዋውተን፣ በፍቅር አልቅሰን፣ በፍቅር ስቀን፣ በፍቅር ኮርኩመን፣ በፍቅር ተኮርኩመን፣ በፍቅር ተፎካክረን፣ በፍቅር ተሸናንፈን፣ በፍቅር ተምረን፣ በፍቅር ተተራርበን፣ በፍቅር አጥፍተን፣ በፍቀር ታርመን እኛነታችን የተሠራበት ቦታ ነው፡፡ አባቴ ይሙቱ! … እኔ በርሶ ምዬ አልዋሽም፡፡
❖ ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የኔ አባት… በፍቅር ባሪያ የሆንበት፣ በፍቅርም ገዢ የሆንበት ቦታ ነው፡፡ አሽከርም ንጉሥም ሆነንበታል፤ አባቴ አሽከርና ንጉሥ በአንድ ጊዜ ሆነው ያውቃሉ? በፍቅር ባሪያም ገዢም ሆነውስ ያውቃሉ? በእውነት እንደዛ ከሆኑስ እርሶም ሰንበት ተማሪ ኖት ማለት ነው፡፡ ነቃሁቦት፤ ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የኔ አባት ልጅ ሳለን ሥራ አመራርን ያጠናንበት፣ የሕዝብ አስተዳደርን የተማርንበት ፣ በተለያየ ሙያ ስብጥር የተሰባጠርንበት፣ ለአረንጓዴ ልማት አትክልትን የተከልንበት፣ በሀገር ፍቅር የነደድንበት፣ በዕቅበተ እምነት የበለጸግንበት፣ በበጎ አድራጎት ስለ ወገን ማሰብን ያየንበት፣ ለሀገር ጥሩ ዜጋ መሆንን የቀሰምንበት ቦታ ነው፡፡
♦ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የኔ አባት… ካለዘር ክፍፍል የተፋቀርንበት፣ እገሌ ከዚህ ነው እገሌም ከዚያ ነው ያልተባለበት ሰሜንና ደቡብ፣ ምዕራብና ምስራቅ የሌለው ቦታ ነው፡፡ ሰንበት ተማሪ ሲሆኑ አባቴ… ብሔሮ ክርስትና፣ ቋንቋዎ ፍቅር ፣ ሀገርዎ በሰማይ ፣ ንጉሦ ክርስቶስ ይሆናል፡፡
✞ እመቤቴን! የኔ አባት… መቼስ ከእርሶ አናውቅም፣ እንደርሶ ሊቅም አይደለንም፣ ብሉዩን ከሐዲሱ ፣ ሊቃውንቱን ከመነኮሳቱም አናመሰጥር ይሆናል፤ ሰንበት ተማሪ ሲኮን ግን አባቴ… በሐዲስ ኪዳንና በብሉይ ኪዳን ያለው እንደ እሳት የሚንቀለቀል ፍቅረ ቤተ ክርስቲያን በውስጥዎ ይነዳል፡፡ ቤተ ክርቲያን ስትነካ አካሎ እንደተቆረጠ ያንገበግቦታል፤ ትምህርትዎን ሥራዎን እርግፍ አድርገው መፍትሔ ለመስጠት ይሮጣሉ፤…. ብቻ አባቴ ሰንበት ትምህርት ቤት የቅንዐተ ቤተ ክርስቲያን እሳት የሚንቦገቦግባት ምድጃ ናት፡፡
🔷 አባቴ… ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት፣ እርሶ የሚወዷቸው ትልቁ መምህር የተማሩበት ቦታ ነው፤ እርሶ የሚያከብሯቸው ትልቁ ሊቅም ማስተማርን የጀመሩበት ቦታ ነው፤ ያኔ ተኮለታትፈው ባያስተምሩን ኖሮ ዛሬ እርሶን የመሰለ አባት በተገኙበት ጉባኤ ለማስተማር መንፈሳዊ ልምድ አይኖራቸውም ነበር፡፡ እኛ አሜን ባንላቸው ኖሮ ዛሬ በሺ የሚቆጠር ምእመን አሜን አይላቸውም ነበር፡፡ ድንግልን! በዚህ ቅንጣት አልጠራጠርም፡፡
♠ ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የኔ አባት… የቤተ ክርስቲያን ጠላቶች የሆኑ ተኩላዎች እንደጉድ የሚፈሩት ቦታ ነው፤ የቤተ ክርስቲያን የቁርጥ ቀን ልጆች አሉበታ፤ አባቴ… ሰንበት ትምህርት ቤት እንደ ጳውሎስና እንደ ሲላስ ሲያገለግሉ የሚታሠሩበት ቦታ ነው፤ ያኔ የቤተ ክርስቲያን ጠላቶች የእግዚአብሔር ቅዱሳንን ነገር እየጠመዘዙ ከነገሥታት ጋር እንደሚያጣሉና በምድራዊ ፍርድ ቤት እንደሚገትሩ… በሰንበት ትምህርት ቤትም እንዲሁ ነው፤ ለሃይማኖት ሲቆረቆሩ የፓርቲ አባል የመንግሥት ጠላት ተደርገው ይከሰሳሉ፤ የቤተ ክርስቲያንን መዘረፍ ሲቃወሙ በዓለማዊ ፍርድ ቤት አሸብረዋል ተብለው ይገተራሉ፡፡
♣ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የኔ አባት ወንድምዎ በኃጢአት ሲወድቅ እንደእነ ቅዱስ መቃርዮስ የወንድሞን ነውር ለመሸፈን ቅርጫት የሚደፉበት ቦታም ነው፡፡ በየቦታው ሲናቁና ሲባረሩም በፍቅር ተመክረው የሚመለሱበት ገዳም ነው፡፡ በወጣትነት ብዙ እያጠፉ በብዙ የሚማሩበት ቦታም ነው፡፡
❤ አባቴ… እውነተኛ ወንድሞች አሉዎት? በሐዘንዎ ጊዜ ሳይለዮት ከልብ የሚያስተዛዝኖት፣ ማስተዛዘን ብቻም ሳይሆን በመንፈስ የሚያጸኑዎት… ወንድሞች አሎት? አብረው ውለው አብረው አድረው… እንግዳን አስተናግደው፣ ዕቃ አጥበው የሚያግዙዎትስ እኅቶች አሉዎት? በደስታዎ ጊዜ ከእርስዎ ጋር አብረው ከልብ የሚደሰቱ፣ ድግሶን ድግሳቸው አድርገው የሚንደፋደፉ ወዳጆች አሉዎት? እኚህ ከሌሉዎት የኔ አባት አንድ ነገር ጎሎታል ማለት ነው… ሰንበት ተማሪነት አልነካካዎትም ማለት ነው፡፡
💮 ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የኔ አባት አንድነትና ኅብረት አካል ነሥቶ የሚያዩበት ቦታ፤ አባቴ ይሙቱ እውነቴን ነው፡፡ አንድነትና ንጹህ ፍቅር በስምንተኛው ሺ ገዝፎ የሚታይበት ገነት ነው ሰንበት ትምህርት ቤት፡፡ ለዛ ነው እኮ አባቴ… ሰነፍ ሆነን እንኳን እንደ ብርቱ የምንታየው፣ ምንም ሳንደክምበት እንኳን አገልግሎታችንና ሐሳባችን የሚሞላው… ምንም ሳናውቅ እንኳን ከአዋቂዎች በላይ የምናገለግለው… አባቴ ይሙቱ… ይኸው በርሶ ምያለሁ… ይሄ ሁሉ ስለአንድነታችንና ስለፍቅራችን ነው፡፡ እንጂማ እኛ አኮ ባዶ ነን…፤ ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የኔ አባት… ባዶ ሳሉ ምሉዕ የሚሆኑባት ሥፍራ ነች፡፡
✅ስለዚህ አባቴ… ቢቻሎ እርሶም ሰንበት ተማሪ ይሁኑ፤ አባል ሆነው ይቀላቀሉን፤ ካልተቻሎም አባል የሚሆኑትን አይከልክሉ፡፡ ቢቻልዎት ሰንበት ትምህርት ቤትን ከልቦ ይደግፉ፤ ባለዎት ነገር ሁሉ ያበርቱ፡፡ ካልቻሉም አደራ አገልግሎቱን ከሚያደናቅፉት ፣ አባላትን ከሚያንገላቱት ጎን አይሁኑ፡፡ ቢቻልዎት ስለሰንበት ትምህርት ቤት መልካምነት ያውሩ፤ ባይቻልዎትም ዝም ይበሉ እንጂ ልጆችዎን አይሙ፡፡
ቢቻልዎት በጸሎትዎ ሰንበት ትምህርት ቤትን ያስቡ፤ ባይቻልዎትም ቢያንስ አይርገሙ፡፡
(በዲ/ን ሕሊና በለጠ)
@And_Haymanot
@And_Haymanot
የነብያት ትንቢታቸው ኢየሱስ ክርስቶስ ተወለደ
"በጎል ሰከበ አፅርቅት ተጠብለለ
ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ"
በበረት ተኛ በጨርቅ ተጠቅለለ፡
የዓለም መድኃኒት ዛሬ ተወለደ
፩
ኃ
ይ
ማ
ኖ
ት
@And_Haymanot
" ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።"
(ኢሳ 7: 14)
" እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፥ ትርጓሜውም፦ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚል ነው።"
(ማቴ 1: 23)
" ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል ስሙም ድንቅ መካር" ኃያል "አምላክ" የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።"
(ኢሳ 9: 6
ጌ ታ ች ን
አ ም ላ ካ ች ን
መ ዳ ኒ ታ ች ን
ኢ
የ
ሱ
ስ
ክርስቶስ
የእናታችን
የቅድስት
ድንግል
ማሪያም
ል
ጅ
አ ማ ኑ ኤ ል
በቸርነቱ
ይ
ባ
ር
ከ
ን
የሰላም
የደስታ
የፍቅር
የበረከት
የአንድነት
በዓል
ይሁንልን
አሜን!!!
አሜን!!!
አሜን!!!
@And_Haymanot
@And_Haymanot
"በጎል ሰከበ አፅርቅት ተጠብለለ
ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ"
በበረት ተኛ በጨርቅ ተጠቅለለ፡
የዓለም መድኃኒት ዛሬ ተወለደ
፩
ኃ
ይ
ማ
ኖ
ት
@And_Haymanot
" ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።"
(ኢሳ 7: 14)
" እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፥ ትርጓሜውም፦ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚል ነው።"
(ማቴ 1: 23)
" ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል ስሙም ድንቅ መካር" ኃያል "አምላክ" የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።"
(ኢሳ 9: 6
ጌ ታ ች ን
አ ም ላ ካ ች ን
መ ዳ ኒ ታ ች ን
ኢ
የ
ሱ
ስ
ክርስቶስ
የእናታችን
የቅድስት
ድንግል
ማሪያም
ል
ጅ
አ ማ ኑ ኤ ል
በቸርነቱ
ይ
ባ
ር
ከ
ን
የሰላም
የደስታ
የፍቅር
የበረከት
የአንድነት
በዓል
ይሁንልን
አሜን!!!
አሜን!!!
አሜን!!!
@And_Haymanot
@And_Haymanot