፩ ሃይማኖት
👉 ዕራየ ማርያም ላይ የተወሰኑ የብሔር ስም እየጠራ ገነት አይገቡም ይላል ለሚሉት የመናፍቅ ፓስተር መልስ በዘማርያም ዘለቀ 👉 በግእዝ ሸ የምትባላዋ ፊደል እንደሌለች ያቃሉ? በብሔር ሥም ለመበጥበት ለተነሡት ልብ ይሥጥልን Share @And_Haymanot
👉 ዕራየ ማርያም ላይ የተወሰኑ የብሔር ስም እየጠራ ገነት አይገቡም ይላል ለሚሉት የመናፍቅ ፓስተር መልስ
👆👆 Sizu ከፍ ላለባችሁ በሚቀንሥ Size በድጋሚ እቀርባለን
👆👆 Sizu ከፍ ላለባችሁ በሚቀንሥ Size በድጋሚ እቀርባለን
Encoderbot file id45033 16k
👉 ዕራየ ማርያም ላይ የተወሰኑ የብሔር ስም እየጠራ ገነት አይገቡም ይላል ለሚሉት የመናፍቅ ፓስተር የተሠጠ መልስ
በዘማርያም ዘለቀ
በብሔር ሥም ለመበጥበት ለተነሡት ልብ ይሥጥልን
Size 2.2
Share @And_Haymanot
በዘማርያም ዘለቀ
በብሔር ሥም ለመበጥበት ለተነሡት ልብ ይሥጥልን
Size 2.2
Share @And_Haymanot
በ2011 ወደ ዩኒቨርሲቲ ለምትጓዙ ሁሉ ኑ ልጆቼ እግዚአብሔርን መፍራት አስተምራችኋለው ትላለች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በግቢ ጉባኤ በሚሠጡ ልዩ ልዩ ትምህርቶች ለነፍሳችሁም ስንቅ ሰንቁ... ዩኒቨርሲቲ ላወቀበት ገዳም ነውና በሁለት በኩል የተሳለ ሰይፍ ትሆኑ ዘንድ እንመኛለን
መልካም የትምህርትና የአገልግልግሎት ዘመን ይሁንላችሁ
@And_Haymanot
በዚህ አመት ወደ ከፍተኛ ተቋም ለተሻገሩ ተማሪዎች ሼር በማድረግ ወደቤቱ እንጥራቸው
፩ ሃይማኖት
@And_Haymanot
መልካም የትምህርትና የአገልግልግሎት ዘመን ይሁንላችሁ
@And_Haymanot
በዚህ አመት ወደ ከፍተኛ ተቋም ለተሻገሩ ተማሪዎች ሼር በማድረግ ወደቤቱ እንጥራቸው
፩ ሃይማኖት
@And_Haymanot
የላሊበላ ጉዳይ
ኢትዮጵያን ስሟን ከሚያስጠሯት ታሪካዊ ቅርሶች መካከል:የቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያና አንዱ ነው። በዓለማችን ቀልብን በመሳቡ በርካታ የዓለም የመረጃ
አውታራት ብዙ ዘግበውለታል ብዙም ጽፈውለታል። ይሁን እንጂ ይህ ታሪክ በዘመናችን ተጎድቶ ያለ ጠጋኝ መኖሩ እጅግ ልብ ይነካል። በተለያዩ ጊዜያት ለቅርሱ ጥበቃ ተብሎ መጠለያ ቢሰራ ችግሩን አባባሰው እንጅ አልቀረፈውም።
በቅርቡ ከአመት በፊት ጉዳዩ ተነስቶ በአዲስ አበባ ኮሚቴ
ተቋቁሞ ከኢትዮጵያ ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር ወደ ሥራ ለመግባት ውይይት በመደረጉ ተስፋ ሰንቀን ነበር። ጉዳዩ ከተስፋ የዘለለ ባለመሆኑ ዛሬ የላሊበላ ህዝብ ለአቤቱታ ወጥቷል። ከዚህ በፊትም በሬዎቻችንን ሸጠን እንጠግነዋለን ብሎ ቆርጦ ቢነሳም ሰሚ አላገኘም።
ይህ ጉዳይ የማይመለከተው ኢትዮጵያዊ የለም፡፡ በመሆኑም
ለጉዳዩ ቅርብ አካላት ቤተ ክህነት፣ቱሪዝም ቢሮ፣የቅርስ ጥበቃ ቢሮ፣ ዩኔስኮ ትኩረት እንዲሰጡት ማድረግ ያሻል። ይህ ካልሆነ ከሀገረ ስብከቱ ጋር በመሆን እኛ ማድረግ ያለብንን ድርሻ ተወጥተን መንከብከብ ይኖርብናል። በቅርብ ቀን የሃገረ ስብከቱን ሊቀ ጳጳስ አነጋግሬ መረጃውን ለማድረስ እሞክራለሁ።
መ/ር ንዋይ ካሳሁን
@And_Haymanot
ኢትዮጵያን ስሟን ከሚያስጠሯት ታሪካዊ ቅርሶች መካከል:የቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያና አንዱ ነው። በዓለማችን ቀልብን በመሳቡ በርካታ የዓለም የመረጃ
አውታራት ብዙ ዘግበውለታል ብዙም ጽፈውለታል። ይሁን እንጂ ይህ ታሪክ በዘመናችን ተጎድቶ ያለ ጠጋኝ መኖሩ እጅግ ልብ ይነካል። በተለያዩ ጊዜያት ለቅርሱ ጥበቃ ተብሎ መጠለያ ቢሰራ ችግሩን አባባሰው እንጅ አልቀረፈውም።
በቅርቡ ከአመት በፊት ጉዳዩ ተነስቶ በአዲስ አበባ ኮሚቴ
ተቋቁሞ ከኢትዮጵያ ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር ወደ ሥራ ለመግባት ውይይት በመደረጉ ተስፋ ሰንቀን ነበር። ጉዳዩ ከተስፋ የዘለለ ባለመሆኑ ዛሬ የላሊበላ ህዝብ ለአቤቱታ ወጥቷል። ከዚህ በፊትም በሬዎቻችንን ሸጠን እንጠግነዋለን ብሎ ቆርጦ ቢነሳም ሰሚ አላገኘም።
ይህ ጉዳይ የማይመለከተው ኢትዮጵያዊ የለም፡፡ በመሆኑም
ለጉዳዩ ቅርብ አካላት ቤተ ክህነት፣ቱሪዝም ቢሮ፣የቅርስ ጥበቃ ቢሮ፣ ዩኔስኮ ትኩረት እንዲሰጡት ማድረግ ያሻል። ይህ ካልሆነ ከሀገረ ስብከቱ ጋር በመሆን እኛ ማድረግ ያለብንን ድርሻ ተወጥተን መንከብከብ ይኖርብናል። በቅርብ ቀን የሃገረ ስብከቱን ሊቀ ጳጳስ አነጋግሬ መረጃውን ለማድረስ እሞክራለሁ።
መ/ር ንዋይ ካሳሁን
@And_Haymanot
ጽኑ ሰማዕት
ጽኑ ሰማዕት የእምነት አርበኛ
አርሴማ ነይ ነይ ወደኛ
------------------------------
ነይ ነይ ቅዱስ አትናትዮስ
›› ›› በስዕለት ያገኙሽ
›› ›› ብሉይን ከሀዲስ
›› ›› ጠንቅቀሽ የተማርሽ
›› ›› በፍፁም ትህትና
›› ›› በጸሎት የተጋሽ
›› ›› አርሴማ ልዩ ነሽ
›› ›› አምላክ የመረጠሸ
-------------------------------
ነይ ነይ ውበትም ሀሰት ነው
›› ›› ደም ግባትም ከንቱ
›› ›› ንብረት ትዳር ሁሉ
›› ›› አላፊ ውዕቱ
›› ›› ንግስት መባልን
›› ›› በፍጹም ሳትሻ
›› ›› አለምን በመናቅ
›› ›› ገባች ወደዋሻ
-------------------------------------
ነይ ነይ አረመኔው ድርጣድስ
›› ›› ቢያሰቃይሽም
›› ›› ውበቴ ክርስቶስ
›› ›› ነው ብለሽ ሰበክሽ
›› ›› አንገትሽን ለሰይፍ
›› ›› አሳልፈሽ ሰጠሸ
›› ›› ክብርሽም ተገልጾ
›› ›› ለአለም አበራሽ
---------------------------------
ነይ ነይ አርአያ ልትሆኝን
›› ›› ለእኛ ለሁላችን
›› ›› ፈፅመሽ አሳየሽ
›› ›› ታላቅ ተጋድሎሽን
›› ›› ይህን አለም ድል መንሳት
›› ›› አቅቶናል እና
›› ›› አርሴማ አትለይን
›› ›› በእምነት እንድንጸና
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ጽኑ ሰማዕት የእምነት አርበኛ
አርሴማ ነይ ነይ ወደኛ
------------------------------
ነይ ነይ ቅዱስ አትናትዮስ
›› ›› በስዕለት ያገኙሽ
›› ›› ብሉይን ከሀዲስ
›› ›› ጠንቅቀሽ የተማርሽ
›› ›› በፍፁም ትህትና
›› ›› በጸሎት የተጋሽ
›› ›› አርሴማ ልዩ ነሽ
›› ›› አምላክ የመረጠሸ
-------------------------------
ነይ ነይ ውበትም ሀሰት ነው
›› ›› ደም ግባትም ከንቱ
›› ›› ንብረት ትዳር ሁሉ
›› ›› አላፊ ውዕቱ
›› ›› ንግስት መባልን
›› ›› በፍጹም ሳትሻ
›› ›› አለምን በመናቅ
›› ›› ገባች ወደዋሻ
-------------------------------------
ነይ ነይ አረመኔው ድርጣድስ
›› ›› ቢያሰቃይሽም
›› ›› ውበቴ ክርስቶስ
›› ›› ነው ብለሽ ሰበክሽ
›› ›› አንገትሽን ለሰይፍ
›› ›› አሳልፈሽ ሰጠሸ
›› ›› ክብርሽም ተገልጾ
›› ›› ለአለም አበራሽ
---------------------------------
ነይ ነይ አርአያ ልትሆኝን
›› ›› ለእኛ ለሁላችን
›› ›› ፈፅመሽ አሳየሽ
›› ›› ታላቅ ተጋድሎሽን
›› ›› ይህን አለም ድል መንሳት
›› ›› አቅቶናል እና
›› ›› አርሴማ አትለይን
›› ›› በእምነት እንድንጸና
@And_Haymanot
@And_Haymanot
በፍጥነት ሼር እናድርግ 🙏
ባህርዳር ስቴድየም የሚገባ መልዕክቱን ያድርስ
ላልይበላን መታደግ እንደሚገባን ዛሬ ኬኒያን ከኢትዮጵያ ጋር ያገናኘው ግዙፉ የባህርዳር ስታዲየም ህዝቡ ብሶቱን ሊያሰማ ይገባል! ተስፋ እናደርጋለን
ይህ ህዝብ መልዕክቱን ለዩኔስኮ ማድረሻ መንገዱ ይህ እና ይህ ብቻ ነው! እግዚአብሔር ይመስገን በእምነቱ እና በሃገሩ የማይደራደረው ጨዋ ህዝብ ይህንን ጩኸት ለማስተጋባት እንቅስቃሴዎችን እንደጀመረ በወሬ ደረጃ እየተሰማም ነው!
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ባህርዳር ስቴድየም የሚገባ መልዕክቱን ያድርስ
ላልይበላን መታደግ እንደሚገባን ዛሬ ኬኒያን ከኢትዮጵያ ጋር ያገናኘው ግዙፉ የባህርዳር ስታዲየም ህዝቡ ብሶቱን ሊያሰማ ይገባል! ተስፋ እናደርጋለን
ይህ ህዝብ መልዕክቱን ለዩኔስኮ ማድረሻ መንገዱ ይህ እና ይህ ብቻ ነው! እግዚአብሔር ይመስገን በእምነቱ እና በሃገሩ የማይደራደረው ጨዋ ህዝብ ይህንን ጩኸት ለማስተጋባት እንቅስቃሴዎችን እንደጀመረ በወሬ ደረጃ እየተሰማም ነው!
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ኢትዮጵያ ሰላምሽ ይብዛ
ተጠለይ በእግዚአብሔር ታዛ
ከሚራራልን ፍቅር ከሆነው
ዘላቂ ሰላም ከእግዚአብሔር ነው
ይህን እወቂ ይህን ተረጂ
በልብሽ ጉልበት ለርሱ ስገጂ
አዝ ❖ ❖ ❖
በሠይፍ ያልቃሉ ሠይፍ የሚያነሱ
የሚራራልን ሲፈርድ ንጉሱ
በቀል የርሡ ነው አይደለም ያንቺ
በጸጋው ታጥረሽ በጸሎት በርቺ
አዝ ❖ ❖ ❖
ይህ ውጣ ውረድ ይህጉስቁልናው
በእግዚአብሔር ነው መከራ ማብቂያው
ሰላም ይሁን ሲል ይሆናል ሰላም
ያሳየሽውን ፍቅር አይረሳም
አዝ ❖ ❖ ❖
ማራት ኢትዮጵያን ማራት ሀገሬን
በየሔድኩበት መጠሪያ ስሜን
ይብቃት ሌሊቱ ይውጣላት ፀሃይ
አሁን ይዘርጋ እጅህ ከሰማይ
አዝ ❖ ❖ ❖
እንድትፈራርስ ጠላት ሸምቋል
ብርቱዉን ጉልበት ከአፈር ደባልቋል
ይህን ግፍ አስብ ዘንበል በልላት
ካንተ በስተቀር መሔጃ የላት
❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖
ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
@And_Haymanot
ተጠለይ በእግዚአብሔር ታዛ
ከሚራራልን ፍቅር ከሆነው
ዘላቂ ሰላም ከእግዚአብሔር ነው
ይህን እወቂ ይህን ተረጂ
በልብሽ ጉልበት ለርሱ ስገጂ
አዝ ❖ ❖ ❖
በሠይፍ ያልቃሉ ሠይፍ የሚያነሱ
የሚራራልን ሲፈርድ ንጉሱ
በቀል የርሡ ነው አይደለም ያንቺ
በጸጋው ታጥረሽ በጸሎት በርቺ
አዝ ❖ ❖ ❖
ይህ ውጣ ውረድ ይህጉስቁልናው
በእግዚአብሔር ነው መከራ ማብቂያው
ሰላም ይሁን ሲል ይሆናል ሰላም
ያሳየሽውን ፍቅር አይረሳም
አዝ ❖ ❖ ❖
ማራት ኢትዮጵያን ማራት ሀገሬን
በየሔድኩበት መጠሪያ ስሜን
ይብቃት ሌሊቱ ይውጣላት ፀሃይ
አሁን ይዘርጋ እጅህ ከሰማይ
አዝ ❖ ❖ ❖
እንድትፈራርስ ጠላት ሸምቋል
ብርቱዉን ጉልበት ከአፈር ደባልቋል
ይህን ግፍ አስብ ዘንበል በልላት
ካንተ በስተቀር መሔጃ የላት
❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖
ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
@And_Haymanot
"ኦርቶዶክስ መሆን እፈልጋለሁ!"
@And_Hymanot
ሚጢጢዬዋ ሰባኪ ቦታው ሐዋሳ ነው። ባለፈው ወር ከአንድም ኹለት ጊዜ ወደ ሐዋሳ ለአገልግሎት ሔጄ ነበር። ኹሌም ወደ ሐዋሳ ስሔድ አንድ አስገራሚ ነገርን መስማትን ጆሮዬ ለምዷል። ከመልመድም አልፎ ይናፍቅ ጀምሯል። ለዚያም ነው አሁን ከሐዋሳ በ25 ደቂቃ መንገድ ርቀት ተጎራብታ ወደ ምትገኘው ሻሸመኔ እየሔድኩ ይህ ታሪክ የታወሰኝ። ለነገሩ ሻሸመኔም ብዙ ታሪክ የተሠራባት ቦታ ስለሆነች ለአንድ አዲስ ድንቃይ ታሪክ ጆሮዬ ሳይቋምጥ አይቀርም።
የሐዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም መዋዕለ
ሕፃናትና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት አለው። በዚህ ትምህርት ቤት ውስጥ ኦርቶዶክሳውያንም ሆኑ የሌሎች አብያተ እምነት አማኞች ይማሩበታል።
ሕፃናቱ ሰኞ ጠዋት ሲገናኙ ታዲያ የቅዳሜና እሑድ ውሏቸውን እየተሻሙ ለጓደኞቻቸው ይተርካሉ። አንዱ ከአንዷ እምቦቀቅላ አፍ ነጥቆ ያወራል፤ ሌላኛዋም እንዲሁ። ዘወትር ሰኞ
ከሚተርኩት ቁምነገር መካከል ታዲያ "እኔ ትላንት ቆረብኩ" የሚለው የማይቀር ነበር። አንዷ ይህን ካለች 'እኔም' 'እኔም' የሚሉ ቀልጣፋና ኮልታፋ ኦርቶዶክሳውያን አፎች ያጅቧታል። ቁርባንን የማያውቁ ሌሎች ኮልታፎች ግራ ይገባቸዋል። ቁርባንን ከማያውቁ
ኮልታፋ አፎች አንዱ የሚጡ ነው።
ሚጡ ከፕሮቴስታንት ወላጆች ተገኝታ በእናትና አባቷ ምርጫ ፕሮቴስታንት የኾነች እምቦቀቅላ ናት። ዘወትር ሰኞ ኦርቶዶክሳውያን ጓደኞቿ
መቁረባቸውን በነገሯት ቁጥር ታዲያ ትቆጭ ኖሯል። አንድ ቀን ሰኞ አንዲት ሚጢጢ የክፍል ጓደኛዋ ከእናትና አባቷ ጋር አስቀድሳ መቁረቧንና በሰንበት ትምህርት ቤት የተማረችውን በመዝሙር እያጀበች ስታወራና የውሎዋን ቅድስና በመንገር እንቁልልጭ ስትል የሚጡ የመቁረብ ፍላጎት ከአቅሟ በላይ ሆነ።
አንገቷን ቀለስ አድርጋ የሥረኛው ከንፈሯን እንደ ማኩረፍ ባለ መለማመጥ አሞጥሙጣ ዐይኗን በተቻለ መጠን በምስኪን አተያይ አሠልጥናና ዕምባዋም ቀሮ ወደ ቆረበችው ጓደኛዋ ሔደችና
"በናትሽ እ... እኔንም እ... እ.. አቁርቢኝ" ብላ ግጥም አድርጋ ሳመቻት። ጓደኛዋ ግን "አንቺ መቁረብ አትችዪም" አለች።
"ለምን?" በሚጡ ግራ ዐይን የሞላው ዕንባ የመሬት ስበት መኖሩን አረጋገጠ።
"አንቺ ኦርቶዶክስ አይደለሽማ..."
"መቁረብ እፈልጋለሁ" ሚጡ ሊያለቅስ አምስት ጉዳይ በሆነው ድምጸት አሞሸች። ጓደኞቿ ሳቁ፤ "መቁረብ እፈልጋለሁ" ክፍሉ በሳቅ ተሞላ።
ሚጡም ሳቃቸው የዐይን ሚጥሚጣ ሆነባት፤ እንባዋ ጎረፈ፤ በሳቅ የታጀበ የልቅሶ ወላፈን 'ሚስ' ባረፈደችበት ክፍል ውስጥ ተቀጣጠለ። የሚጡ ልቅሶ ካንጀት ነበርና ከሳቁ ድምቀት
ይልቅ መጉላት ጀመረ። ጓደኞቿ መሳቅ ትተው ማባበል ጀመሩ። ከልብ መሻት የፈለቀች አንዲት ልቅሶ የእልፎችን ሳቅ አሸነፈች። ተቆጣጠረቻቸው። በልቅሶ የተጨመቀው ዐይን ያወጣው ዕንባ በሳቅ የተጨመቁ ዐይኖች ያፈለቁትን ዕንባ ዋጣቸው፤ የተገኘን ውኃ ኹሉ
በጉልበቱ የዝናብ እንደሚያስመስል እንደ ደራሽ ጎርፍ በሳቅ የተገኘው ዕንባ ኹሉ በሚጡ ዕንባ ጉልበት እንደዚያ ኾነ...
"መቁረብ እፈልጋለሁ" አሁን ሳቅ የለም - ማባበል ብቻ እንጂ። 'አይዞሽ በቃ' እያሉ ከልብ የሚያባብሉ ከንፈሮች ጉንጮቿ ላይም ያርፉ ነበር። ሚጡ ቤት ስትገባ እንደውዳሴ ማርያም ቀኑን ሙሉ ስትደግመው የነበረውን ሐረግ
ደገመችው፦ "መቁረብ እፈልጋለሁ"
ወላጆቿ ግራ ገባቸው። ቀልድም መሰላቸው። ለማረሳሳትም ሞከሩ። ሚጡ ግን ያነሣሣት መንፈስ ቅዱስ ነውና ዝም ልትል አንደበቷ
አልታዘዘላትም። "መቁረብ እፈልጋለሁ!"
አንደበቷ ብቻ ሳይሆን አካሏ በሙሉ በዚህ ፍላጎቷ ተቃኘ። ዐይኗ በዕንባ መቁረብን ለመነ። ጆሮዋ ሌላ ነገር መስማትን ናቀ፤ አፎች ኹሉ
'እናቆርብሻለን' የሚል የምሥራችን
እንዲዘምሩም ተመኘ። እግሯ ቤተ ክርስቲያን እንጂ የትም የማይሔድ ኾነ። አፍንጫዋ የጸሎት፣ የምልጃ ዕጣንን መዓዛ እንጂ ሌላ ሽታ ከረፋው። እጇ ከቆረበች በኋላ ነጠላዋን አፈፍ
አድርጎ ጸበል እስክትጠጣ አፏ ላይ ሊጫን ፣ አፏን ሊሸፍን ጓጓ - ጓደኞቿ እንደነገሯት - እንደዚያ። አንገቷ ካለ ክር መራቆቱ አሳፈረው። ግንባሯ መስቀል መሳለምን፣ ከንፈሯ ሥዕለ ማርያምን መሳምን ተመኙ። ጸጉሯ በሻሽ ተሸፍኖ፣ ትከሻዋም ነጠላ ተጣፍቶለት መዝሙር
ማጥናትና ሰኞ ስትመጣ ከጓደኞቿ ጋር መዘመር የዘወትር ኅልሟ ሆነ። የሰውነት አካሏ ባጠቃላይ ኦርቶዶክሳዊነትን ሻተ፤ ጌታ የለኮሰው፣ ሐዋርያት ያቀጣጠሉት የሃይማኖት እሳት በማዕከለ ሰብእናዋ ተንቦገቦገ። (ሉቃ. 12፡49)። የሚጡ ኹለመና እንዲህ አለ፦ "መቁረብ እፈልጋለሁ፣ ኦርቶዶክስ መሆን
እፈልጋለሁ!" ይህ የሚጡ ልምምጥ ቃል ብቻ አይደለም
- በዕንባ የተለወሰ ንጹህ ጩኸት እንጂ። ንግግር ብቻ አይደለም - ከደመና በላይ የሚወጣ ልመና እንጂ። ዝርው ድምጽ ብቻ አይደለም
- ሳይበተን የሚያርግ ጸሎት እንጂ።
...እናም ወደላይ ወጣ። ከፍ ከፍ አለና ራማን አንኳኳ። ቅዱስ ገብርኤልም አስተናገደው። የሚጡ ሰሞንኛ ውትወታ ግራ ያጋባቸው ወላጆቿ ከእሑዶች በአንዱ ሚጡን ይዘው ወደ ገዳሙ ሰንበት ትምህርት ቤት መጡ። ሚጡ
ዛሬ ነፍሷን አታውቅም። በወላጆቿ ተይዛ ልክ እንደጓደኞቿ ወደ ቤተ ክርስቲያን መጣች። ኹሉነገሯ ጥርስ ሆኗል። ሰኞ ደርሶ ትምህርት ቤት የምታወራው፣ የምትፈጥረው የትረካ ድባብ
በሰንበቱ ታያት። ወላጆቿ የሆነውን ኹሉ ለሰንበት ትምህርት ቤቱ መምህራን ነግረው "እባካችሁ ሚጡ እንድትቆርብ አድርጉልን" አሉ። ሚጡም "መቁረብ እፈልጋለው!" አለች በጥዑም
አንደበቷ። መምህራኑ ግን አንድ ሰው ለመቁረብ የሚያስፈልገውን ትምህርት መማር እንደሚቀድምና ወላጆቿም በቁርባን ጊዜ በመቅደስ መቆየት እንደማይችሉ አስረዷቸው።
ሚጡም የዚያኑ ቀን እንደማትቆርብ ተረዳችው። አንድ ነገር ግን ገብቷታል - ኦርቶዶክስ ካልሆነች በገዳሙ መቁረብ እንደማትችል። ስለዚህ ድምጿን ከፍ አድርጋ "ኦርቶዶክስ መሆን እፈልጋለሁ" አለች። ወላጆቿ ደንግጠው ተያዩ። በድምጿ ውስጥ ያለው ቆራጥነት እናትና
አባቷን ለመተው እንኳን ደግማ የማታስብ አስመስሏታል።
መምህራኑ ሚጡንም ወላጆቿንም አረጋግተው ክትትላቸውን ቀጠሉ። የደብሩ ካህናትም ጉዳዩን ሥራቸው አደረጉት። ከዕለታት ለሚጡ በተቀደሰች አንዲት እሑድ
እንዲህ ኾነ....
የሚጡ ወላጆች ከመምህራኑ እንደተነገራቸው ቅዳሴ ሳይጀመር በሌሊት የገዳሙ ግቢ ውስጥ
ተገኙ። መምህራኑ እየመሯቸው ወደ ክርስትና ቤት ሔዱ....
ከቆይታ በኋላ ወጥተው ወደ ቤተ መቅደስ ገቡ። ሚጡ የአንድ ሰውን እጅ ይዛ የቤተ መቅደሱ በር ጋር ደረሱ። እንደተማረችው ጫማዋን አውልቃ ተሳለመች፤ ወደ ውስጥ ገባች። አብረዋት ያሉትም ገቡ። ወላጆቿም
ከመግባት አልተከለከሉም። "ፃዑ ንዑሰ ክርስቲያን" ተባለ። ወላጆቿ ግን
አልወጡም። ልዑካኑ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ይዘው ከመቅደስ በክብር ወደ ቅድስቱ ተገለጡ። እንደተለመደው ብዙ ቆራቢያን ተሰለፉ። ሚጡም ሰልፉን ከሠሩት ተነሣህያን ጋር
በመኾን ከበረች። ከትምህርት ቤት ጓደኞቿ መካከል በወላጆቻቸው
ታጅበውሊቆርቡ የተሰለፉም አሉ። ዛሬ ግን ለመጀመሪያ ጊዜ በሚጡ ተበለጡ። በርግጥ ሚጡ በልጅነት ጥምቀት ከብራ፣ በምሥጢረ ሜሮን መንፈስ ቅዱስን ተቀብላ ለመጀመሪያ ጊዜ ለመቁረብ መቅረቧ ነው። ጓደኞቿ ግን
ደጋግመው በሥጋ ወደሙ ከብረዋል። ግን ኹሉም ብቻቸውን ናቸው።
ሚጡ ሥጋ ወደሙን ተቀብላ በነጠላዋ አፏን ሸፍና ስትመለስ በጓደኞቿ ላይ ብልጫዋ ተገለጠ። ኹለት ረጃጅም ሰዎች ከኋላዋ እርሷን ተከትለው ተጠምቀውና ቆርበው አፋቸውን
ይዘው ተከተሏት - እናትና አባቷ። የጓደኞቿ ወላጆች ልጆቻቸውን
@And_Hymanot
ሚጢጢዬዋ ሰባኪ ቦታው ሐዋሳ ነው። ባለፈው ወር ከአንድም ኹለት ጊዜ ወደ ሐዋሳ ለአገልግሎት ሔጄ ነበር። ኹሌም ወደ ሐዋሳ ስሔድ አንድ አስገራሚ ነገርን መስማትን ጆሮዬ ለምዷል። ከመልመድም አልፎ ይናፍቅ ጀምሯል። ለዚያም ነው አሁን ከሐዋሳ በ25 ደቂቃ መንገድ ርቀት ተጎራብታ ወደ ምትገኘው ሻሸመኔ እየሔድኩ ይህ ታሪክ የታወሰኝ። ለነገሩ ሻሸመኔም ብዙ ታሪክ የተሠራባት ቦታ ስለሆነች ለአንድ አዲስ ድንቃይ ታሪክ ጆሮዬ ሳይቋምጥ አይቀርም።
የሐዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም መዋዕለ
ሕፃናትና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት አለው። በዚህ ትምህርት ቤት ውስጥ ኦርቶዶክሳውያንም ሆኑ የሌሎች አብያተ እምነት አማኞች ይማሩበታል።
ሕፃናቱ ሰኞ ጠዋት ሲገናኙ ታዲያ የቅዳሜና እሑድ ውሏቸውን እየተሻሙ ለጓደኞቻቸው ይተርካሉ። አንዱ ከአንዷ እምቦቀቅላ አፍ ነጥቆ ያወራል፤ ሌላኛዋም እንዲሁ። ዘወትር ሰኞ
ከሚተርኩት ቁምነገር መካከል ታዲያ "እኔ ትላንት ቆረብኩ" የሚለው የማይቀር ነበር። አንዷ ይህን ካለች 'እኔም' 'እኔም' የሚሉ ቀልጣፋና ኮልታፋ ኦርቶዶክሳውያን አፎች ያጅቧታል። ቁርባንን የማያውቁ ሌሎች ኮልታፎች ግራ ይገባቸዋል። ቁርባንን ከማያውቁ
ኮልታፋ አፎች አንዱ የሚጡ ነው።
ሚጡ ከፕሮቴስታንት ወላጆች ተገኝታ በእናትና አባቷ ምርጫ ፕሮቴስታንት የኾነች እምቦቀቅላ ናት። ዘወትር ሰኞ ኦርቶዶክሳውያን ጓደኞቿ
መቁረባቸውን በነገሯት ቁጥር ታዲያ ትቆጭ ኖሯል። አንድ ቀን ሰኞ አንዲት ሚጢጢ የክፍል ጓደኛዋ ከእናትና አባቷ ጋር አስቀድሳ መቁረቧንና በሰንበት ትምህርት ቤት የተማረችውን በመዝሙር እያጀበች ስታወራና የውሎዋን ቅድስና በመንገር እንቁልልጭ ስትል የሚጡ የመቁረብ ፍላጎት ከአቅሟ በላይ ሆነ።
አንገቷን ቀለስ አድርጋ የሥረኛው ከንፈሯን እንደ ማኩረፍ ባለ መለማመጥ አሞጥሙጣ ዐይኗን በተቻለ መጠን በምስኪን አተያይ አሠልጥናና ዕምባዋም ቀሮ ወደ ቆረበችው ጓደኛዋ ሔደችና
"በናትሽ እ... እኔንም እ... እ.. አቁርቢኝ" ብላ ግጥም አድርጋ ሳመቻት። ጓደኛዋ ግን "አንቺ መቁረብ አትችዪም" አለች።
"ለምን?" በሚጡ ግራ ዐይን የሞላው ዕንባ የመሬት ስበት መኖሩን አረጋገጠ።
"አንቺ ኦርቶዶክስ አይደለሽማ..."
"መቁረብ እፈልጋለሁ" ሚጡ ሊያለቅስ አምስት ጉዳይ በሆነው ድምጸት አሞሸች። ጓደኞቿ ሳቁ፤ "መቁረብ እፈልጋለሁ" ክፍሉ በሳቅ ተሞላ።
ሚጡም ሳቃቸው የዐይን ሚጥሚጣ ሆነባት፤ እንባዋ ጎረፈ፤ በሳቅ የታጀበ የልቅሶ ወላፈን 'ሚስ' ባረፈደችበት ክፍል ውስጥ ተቀጣጠለ። የሚጡ ልቅሶ ካንጀት ነበርና ከሳቁ ድምቀት
ይልቅ መጉላት ጀመረ። ጓደኞቿ መሳቅ ትተው ማባበል ጀመሩ። ከልብ መሻት የፈለቀች አንዲት ልቅሶ የእልፎችን ሳቅ አሸነፈች። ተቆጣጠረቻቸው። በልቅሶ የተጨመቀው ዐይን ያወጣው ዕንባ በሳቅ የተጨመቁ ዐይኖች ያፈለቁትን ዕንባ ዋጣቸው፤ የተገኘን ውኃ ኹሉ
በጉልበቱ የዝናብ እንደሚያስመስል እንደ ደራሽ ጎርፍ በሳቅ የተገኘው ዕንባ ኹሉ በሚጡ ዕንባ ጉልበት እንደዚያ ኾነ...
"መቁረብ እፈልጋለሁ" አሁን ሳቅ የለም - ማባበል ብቻ እንጂ። 'አይዞሽ በቃ' እያሉ ከልብ የሚያባብሉ ከንፈሮች ጉንጮቿ ላይም ያርፉ ነበር። ሚጡ ቤት ስትገባ እንደውዳሴ ማርያም ቀኑን ሙሉ ስትደግመው የነበረውን ሐረግ
ደገመችው፦ "መቁረብ እፈልጋለሁ"
ወላጆቿ ግራ ገባቸው። ቀልድም መሰላቸው። ለማረሳሳትም ሞከሩ። ሚጡ ግን ያነሣሣት መንፈስ ቅዱስ ነውና ዝም ልትል አንደበቷ
አልታዘዘላትም። "መቁረብ እፈልጋለሁ!"
አንደበቷ ብቻ ሳይሆን አካሏ በሙሉ በዚህ ፍላጎቷ ተቃኘ። ዐይኗ በዕንባ መቁረብን ለመነ። ጆሮዋ ሌላ ነገር መስማትን ናቀ፤ አፎች ኹሉ
'እናቆርብሻለን' የሚል የምሥራችን
እንዲዘምሩም ተመኘ። እግሯ ቤተ ክርስቲያን እንጂ የትም የማይሔድ ኾነ። አፍንጫዋ የጸሎት፣ የምልጃ ዕጣንን መዓዛ እንጂ ሌላ ሽታ ከረፋው። እጇ ከቆረበች በኋላ ነጠላዋን አፈፍ
አድርጎ ጸበል እስክትጠጣ አፏ ላይ ሊጫን ፣ አፏን ሊሸፍን ጓጓ - ጓደኞቿ እንደነገሯት - እንደዚያ። አንገቷ ካለ ክር መራቆቱ አሳፈረው። ግንባሯ መስቀል መሳለምን፣ ከንፈሯ ሥዕለ ማርያምን መሳምን ተመኙ። ጸጉሯ በሻሽ ተሸፍኖ፣ ትከሻዋም ነጠላ ተጣፍቶለት መዝሙር
ማጥናትና ሰኞ ስትመጣ ከጓደኞቿ ጋር መዘመር የዘወትር ኅልሟ ሆነ። የሰውነት አካሏ ባጠቃላይ ኦርቶዶክሳዊነትን ሻተ፤ ጌታ የለኮሰው፣ ሐዋርያት ያቀጣጠሉት የሃይማኖት እሳት በማዕከለ ሰብእናዋ ተንቦገቦገ። (ሉቃ. 12፡49)። የሚጡ ኹለመና እንዲህ አለ፦ "መቁረብ እፈልጋለሁ፣ ኦርቶዶክስ መሆን
እፈልጋለሁ!" ይህ የሚጡ ልምምጥ ቃል ብቻ አይደለም
- በዕንባ የተለወሰ ንጹህ ጩኸት እንጂ። ንግግር ብቻ አይደለም - ከደመና በላይ የሚወጣ ልመና እንጂ። ዝርው ድምጽ ብቻ አይደለም
- ሳይበተን የሚያርግ ጸሎት እንጂ።
...እናም ወደላይ ወጣ። ከፍ ከፍ አለና ራማን አንኳኳ። ቅዱስ ገብርኤልም አስተናገደው። የሚጡ ሰሞንኛ ውትወታ ግራ ያጋባቸው ወላጆቿ ከእሑዶች በአንዱ ሚጡን ይዘው ወደ ገዳሙ ሰንበት ትምህርት ቤት መጡ። ሚጡ
ዛሬ ነፍሷን አታውቅም። በወላጆቿ ተይዛ ልክ እንደጓደኞቿ ወደ ቤተ ክርስቲያን መጣች። ኹሉነገሯ ጥርስ ሆኗል። ሰኞ ደርሶ ትምህርት ቤት የምታወራው፣ የምትፈጥረው የትረካ ድባብ
በሰንበቱ ታያት። ወላጆቿ የሆነውን ኹሉ ለሰንበት ትምህርት ቤቱ መምህራን ነግረው "እባካችሁ ሚጡ እንድትቆርብ አድርጉልን" አሉ። ሚጡም "መቁረብ እፈልጋለው!" አለች በጥዑም
አንደበቷ። መምህራኑ ግን አንድ ሰው ለመቁረብ የሚያስፈልገውን ትምህርት መማር እንደሚቀድምና ወላጆቿም በቁርባን ጊዜ በመቅደስ መቆየት እንደማይችሉ አስረዷቸው።
ሚጡም የዚያኑ ቀን እንደማትቆርብ ተረዳችው። አንድ ነገር ግን ገብቷታል - ኦርቶዶክስ ካልሆነች በገዳሙ መቁረብ እንደማትችል። ስለዚህ ድምጿን ከፍ አድርጋ "ኦርቶዶክስ መሆን እፈልጋለሁ" አለች። ወላጆቿ ደንግጠው ተያዩ። በድምጿ ውስጥ ያለው ቆራጥነት እናትና
አባቷን ለመተው እንኳን ደግማ የማታስብ አስመስሏታል።
መምህራኑ ሚጡንም ወላጆቿንም አረጋግተው ክትትላቸውን ቀጠሉ። የደብሩ ካህናትም ጉዳዩን ሥራቸው አደረጉት። ከዕለታት ለሚጡ በተቀደሰች አንዲት እሑድ
እንዲህ ኾነ....
የሚጡ ወላጆች ከመምህራኑ እንደተነገራቸው ቅዳሴ ሳይጀመር በሌሊት የገዳሙ ግቢ ውስጥ
ተገኙ። መምህራኑ እየመሯቸው ወደ ክርስትና ቤት ሔዱ....
ከቆይታ በኋላ ወጥተው ወደ ቤተ መቅደስ ገቡ። ሚጡ የአንድ ሰውን እጅ ይዛ የቤተ መቅደሱ በር ጋር ደረሱ። እንደተማረችው ጫማዋን አውልቃ ተሳለመች፤ ወደ ውስጥ ገባች። አብረዋት ያሉትም ገቡ። ወላጆቿም
ከመግባት አልተከለከሉም። "ፃዑ ንዑሰ ክርስቲያን" ተባለ። ወላጆቿ ግን
አልወጡም። ልዑካኑ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ይዘው ከመቅደስ በክብር ወደ ቅድስቱ ተገለጡ። እንደተለመደው ብዙ ቆራቢያን ተሰለፉ። ሚጡም ሰልፉን ከሠሩት ተነሣህያን ጋር
በመኾን ከበረች። ከትምህርት ቤት ጓደኞቿ መካከል በወላጆቻቸው
ታጅበውሊቆርቡ የተሰለፉም አሉ። ዛሬ ግን ለመጀመሪያ ጊዜ በሚጡ ተበለጡ። በርግጥ ሚጡ በልጅነት ጥምቀት ከብራ፣ በምሥጢረ ሜሮን መንፈስ ቅዱስን ተቀብላ ለመጀመሪያ ጊዜ ለመቁረብ መቅረቧ ነው። ጓደኞቿ ግን
ደጋግመው በሥጋ ወደሙ ከብረዋል። ግን ኹሉም ብቻቸውን ናቸው።
ሚጡ ሥጋ ወደሙን ተቀብላ በነጠላዋ አፏን ሸፍና ስትመለስ በጓደኞቿ ላይ ብልጫዋ ተገለጠ። ኹለት ረጃጅም ሰዎች ከኋላዋ እርሷን ተከትለው ተጠምቀውና ቆርበው አፋቸውን
ይዘው ተከተሏት - እናትና አባቷ። የጓደኞቿ ወላጆች ልጆቻቸውን
"ኦርቶዶክስ መሆን እፈልጋለሁ!"
....Cont
- እናትና አባቷ። የጓደኞቿ ወላጆች ልጆቻቸውን አቆረቡ። የእርሷ ወላጆች ግን እርሷን ቆርበው አቆረቡ። ለካስ "ኦርቶዶክስ መሆን እፈልጋለሁ - መቁረብ እፈልጋለሁ"
የሚለው ንግግር ወደ ወላጆቿም ተጋብቶ ኖሯል
- ይኸው በልጃቸው ተሰብከው ከልጃቸው ጋር ከበሩ - በምድርም በሰማይም ደስታ ሆነ። አንዳንድ ጊዜ ልጅም ለእናቷ ምጥን ታስተምራለች። ሚጡ ለእናትና አባቷ ምጥ
የሆነባቸውን ኦርቶዶክሳዊነት አስተማረች።
በቀጣዩ ቀን ሰኞ ሚጡ ትምህርት ቤት ስትሔድ ምን ብላ ገድሏን እንደምትተርክ ብንሰማ... አቤት...
አፎች ኹሉ ጆሮ ኾነው ሲያዳምጧት፣
በተቃራኒው የእርሷ ኹለመና አፍ ሲሆን... "እየውላችሁ.... እ.... እ..." ስትል በተራዋ ሌሎችን ስታጓጓ....
አቤት..... መቼስ እግዚአብሔር በጥበቡ እንደጠራት ከነቤተሰቧ ይጠብቅልን፣ ያጽናልን እንጂ ምን ይባላል! የሚጡን ዕንባ ያበሰ ቅዱስ ገብርኤል የእኛንም
ዕንባ በምልጃው ያብስልን!
©ዘሕሊና
@And_Hymanot
@And_Hymanot
....Cont
- እናትና አባቷ። የጓደኞቿ ወላጆች ልጆቻቸውን አቆረቡ። የእርሷ ወላጆች ግን እርሷን ቆርበው አቆረቡ። ለካስ "ኦርቶዶክስ መሆን እፈልጋለሁ - መቁረብ እፈልጋለሁ"
የሚለው ንግግር ወደ ወላጆቿም ተጋብቶ ኖሯል
- ይኸው በልጃቸው ተሰብከው ከልጃቸው ጋር ከበሩ - በምድርም በሰማይም ደስታ ሆነ። አንዳንድ ጊዜ ልጅም ለእናቷ ምጥን ታስተምራለች። ሚጡ ለእናትና አባቷ ምጥ
የሆነባቸውን ኦርቶዶክሳዊነት አስተማረች።
በቀጣዩ ቀን ሰኞ ሚጡ ትምህርት ቤት ስትሔድ ምን ብላ ገድሏን እንደምትተርክ ብንሰማ... አቤት...
አፎች ኹሉ ጆሮ ኾነው ሲያዳምጧት፣
በተቃራኒው የእርሷ ኹለመና አፍ ሲሆን... "እየውላችሁ.... እ.... እ..." ስትል በተራዋ ሌሎችን ስታጓጓ....
አቤት..... መቼስ እግዚአብሔር በጥበቡ እንደጠራት ከነቤተሰቧ ይጠብቅልን፣ ያጽናልን እንጂ ምን ይባላል! የሚጡን ዕንባ ያበሰ ቅዱስ ገብርኤል የእኛንም
ዕንባ በምልጃው ያብስልን!
©ዘሕሊና
@And_Hymanot
@And_Hymanot
ተአምረ ማርያም ላይ ከተሃድሶ መናፍቃን ጥያቄዎች አንዱ
☞ ጥያቄ. ነፍሳትን በበላው በበላኤ ሰብ ታሪክ ላይ።
☞ መልስ፦ የብላዔ ሰብዕ 78 ነፍስ አጥፍቶ መማሩ በማቴ10:42
"በደቀ መዝሙር ስም ቀዝቃዛ ዉሃ ቢጠጣ እውነት እላችኋለሁ
ዋጋው አይጠፋበትም" በሚለው አምላካዊ ቃል መሰረት ነው::
ተአምረ ማርያም እንደሚነግረን ስምዖን የተባለው ይህ ሰው ብዙ ነፍስ ካጠፋ በሗላ ንስሓ ገባ ተጸጸተ ልክ በቀኝ እንደተሰቀለው ወንበዴ::
በወንጌሉ መሰረት ለድሀ ከደቀመዛሙርት ሁሉ ከፍጥረት
ሁሉ በከበረችው በእመቤታችን ስም ቀዝቃዛ ዉሀ ለድሀ አጠጣ:: እመቤታችም በወንጌሉ መሰረት ማርለኝ አለችው ማረላት:: በቀኝ የተሰቀለ ከብላዔ ሰብዕ (ከዚህ ሰብ በላ) የበለጠ ይሥራ አይሥራ እኛ አናዉቅም::
ቃል ኪዳን ሲሰጥ ክርስቶስ ገደብ አላስቀመጠም (ይህንን ያህል
የገደለ አልምርም የሚል የለ)::
በደቀ መዝሙር ስም ያጠጣ አለ እንጂ:: ስለዚህ የወንበዴውን መዳንም እየተጠራጠሩ በወንጌል አምናለሁ ማለት አይቻልም:: በወንጌል ተጽፎ ነው እንጂ በቀኝ የተሰቀለው ታሪክ በተአምረ
ማርያም ቢጻፍ ኖሮ አይቀበሉትም ነበር::
በመጨረሻም መናፍቃን ከተለያዩ ገድላት፣ድርሳናት፣ተአምራት በመጥቀስ ምዕመንን ለማሰናከል ይኳትናሉና።
በተቻለ መጠን አይታለሉላቸው። ምንም እንኳን ገድሉ ተአምሩ ለማመን ከባድ ቢሆንም ክርስቲያኖች ነንና ከዚህም በላይ እንደሚደረግ እንወቅ!
ጌታ ያለውም ይህንኑ ነው።በእኔ የሚያምን ከዚህ በላይ ያደርጋል
ተብሎ ተፅፋልና!!!..... ሌሎች ጥያቄዎችን እንመለስበታለን ይቆየን
@And_Haymanot
@And_Haymanot
☞ ጥያቄ. ነፍሳትን በበላው በበላኤ ሰብ ታሪክ ላይ።
☞ መልስ፦ የብላዔ ሰብዕ 78 ነፍስ አጥፍቶ መማሩ በማቴ10:42
"በደቀ መዝሙር ስም ቀዝቃዛ ዉሃ ቢጠጣ እውነት እላችኋለሁ
ዋጋው አይጠፋበትም" በሚለው አምላካዊ ቃል መሰረት ነው::
ተአምረ ማርያም እንደሚነግረን ስምዖን የተባለው ይህ ሰው ብዙ ነፍስ ካጠፋ በሗላ ንስሓ ገባ ተጸጸተ ልክ በቀኝ እንደተሰቀለው ወንበዴ::
በወንጌሉ መሰረት ለድሀ ከደቀመዛሙርት ሁሉ ከፍጥረት
ሁሉ በከበረችው በእመቤታችን ስም ቀዝቃዛ ዉሀ ለድሀ አጠጣ:: እመቤታችም በወንጌሉ መሰረት ማርለኝ አለችው ማረላት:: በቀኝ የተሰቀለ ከብላዔ ሰብዕ (ከዚህ ሰብ በላ) የበለጠ ይሥራ አይሥራ እኛ አናዉቅም::
ቃል ኪዳን ሲሰጥ ክርስቶስ ገደብ አላስቀመጠም (ይህንን ያህል
የገደለ አልምርም የሚል የለ)::
በደቀ መዝሙር ስም ያጠጣ አለ እንጂ:: ስለዚህ የወንበዴውን መዳንም እየተጠራጠሩ በወንጌል አምናለሁ ማለት አይቻልም:: በወንጌል ተጽፎ ነው እንጂ በቀኝ የተሰቀለው ታሪክ በተአምረ
ማርያም ቢጻፍ ኖሮ አይቀበሉትም ነበር::
በመጨረሻም መናፍቃን ከተለያዩ ገድላት፣ድርሳናት፣ተአምራት በመጥቀስ ምዕመንን ለማሰናከል ይኳትናሉና።
በተቻለ መጠን አይታለሉላቸው። ምንም እንኳን ገድሉ ተአምሩ ለማመን ከባድ ቢሆንም ክርስቲያኖች ነንና ከዚህም በላይ እንደሚደረግ እንወቅ!
ጌታ ያለውም ይህንኑ ነው።በእኔ የሚያምን ከዚህ በላይ ያደርጋል
ተብሎ ተፅፋልና!!!..... ሌሎች ጥያቄዎችን እንመለስበታለን ይቆየን
@And_Haymanot
@And_Haymanot
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ 31 አጀንዳዎችን በማጽደቅ
መወያየቱን ቀጥሏል
• ከተደጋጋሚ ጥሪ በኋላ በምልዓተ ጉባኤው የተገኙትን ብፁዕ
አቡነ ኤዎስጣቴዎስን በይቅርታ ተቀብሏል፤የሀገረ ስብከት ምደባ
ይሰጣቸዋል፤
• የአእላፋት ድምፅ የካህናትና የምእመናን ተናሥኦት ኅብረት
ተወካዮች፣በመሪ ዕቅድ ትግበራና የምእመናነ ከፍተኛ ተሳትፎ
የቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ ለውጥ እንቅስቃሴያቸውን
ቀርበው እንደሚያስረዱ ይጠበቃል፤
***
ከትላንት በስቲያ የተጀመረውና ሦስተኛ ቀኑን የያዘው፣ የቅዱስ
ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ፣ 31 አጀንዳዎችን በማጽደቅ ስብሰባውን
ቀጥሏል፤ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስን የመክፈቻ
ንግግር ካደመጠ በኋላ የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ
መንፈሳዊ ጉባኤ 37ኛ ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ የአቋም
መግለጫና የውሳኔ ሐሳብ ላይ በመወያየት አጽድቋል፡፡
ከ27 ዓመታት በኋላ በተመለሰው ሲኖዶሳዊ አንድነት፣ የአህጉረ
ስብከት ድልደላ እና የብፁዓን አባቶች ምደባ ማካሔድን
በተመለከተ በአጀንዳ ተ.ቁ(3) በመያዝ፣ የድልደላና ምደባ
ምክረ ሐሳቦችን ተቀብሏል፤ ጉዳዩን አደራጅተው ለምልዓተ
ጉባኤው የሚያቀርቡ የብፁዓን አባቶች ኮሚቴም ሠይሟል፤
በድልደላው፣ ከሀገር ውስጥም ኾነ ከውጭ በተደራራቢነት
የተያዙት አህጉረ ስብከት ተነጣጥለው ምደባ
እንደሚካሔድባቸው፤አዲስና ተጨማሪ የአህጉረ ስብከት
አደረጃጀትም እንደሚኖር ይጠበቃል፡፡
ከቀረቡትም ምክረ ሐሳቦች ውስጥ፤ ከሀገር ውስጥ
በተደራራቢነት የተያዙ 8 አህጉረ ስብከት ራሳቸውን ችለው
ብፁዓን አባቶች እንዲመደቡባቸው፤ የሰሜን አሜሪካ አህጉረ
ስብከት ለ9፣ የካናዳ ሀገረ ስብከት ለ3፣ የአውሮጳ አህጉረ
ስብከት ለ4፣ የአፍሪቃ አህጉረ ስብከት ለ3፣ የአውስትራልያ ሀገረ
ስብከት ለ3 ተከፍለው ብፁዓን አባቶች እንዲመደቡባቸው
የሚጠይቀው ይገኝበታል፡፡
በአሁኑ ምልዓተ ጉባኤ የተገኙት የቀድሞው የካሊፎርኒያ ሀገረ
ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ፣ ከ2003 ዓ.ም.
ጀምሮ ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ በተላለፉላቸው ተደጋጋሚ
ጥሪዎች መሠረት ያልቀረቡበትን ምክንያትና በአንዳንድ ወገኖች
ስለሚነሡባቸው ክሦችም ተጠይቀዋል፡፡ ክሦቹን
በተመለከተ፣“ግለሰቦች ስማቸውን ለማጥፋት የሸረቡት ሤራ
ነው፤” በማለት አስረድተዋል፡፡ ከፍተኛ ትምህርታቸውን
እየተከታተሉ እንደነበርና ለመመለስ የማይችሉበት ኹኔታ
እንዳጋጠማቸው የጠቀሱት ብፁዕነታቸው፣ ቅዱስ ሲኖዶሱን
ይቅርታ ጠይቀዋል፤ የሀገረ ስብከት ምደባ እንዲሰጣቸውም
አመልክተዋል፡፡ ይቅርታቸውን የተቀበለው ምልዓተ ጉባኤው፣
በቃል ያስረዱትን በጽሑፍ ሲያቀርቡ ምደባው እንዲሰጣቸው
ተስማምቷል፡፡
ምልዓተ ጉባኤው፣ በትላንት የቀትር በፊት ውሎው፣ በተ.ቁ(11)
አጀንዳው፥ አቤቱታ ስለቀረቡባቸው አህጉረ ስብከት ማለትም፦
• የሻሻመኔ ምእመናን የሀገረ ስብከት ጥያቄ፣
• የምሥራቅ ጎጃም ካህናትና ምእመናን በሊቀ ጳጳሱ ላይ
ስላቀረቡት አቤቱታ፣
• የአዊ ዞን ምእመናን በብፁዕ አባ ቶማስ ላይ ስላቀረቡት
አቤቱታ፤
• የደቡብ እና ሰሜን ጎንደር አህጉረ ስብከት፣
• የካፋ፣ የምዕራብ ወለጋ አህጉረ ስብከት፣
• የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት እና የደብረ ምጥማቅ ሰዓሊተ
ምሕረት ቅድስት ማርያም ካቴድራል ምእመናን አቤቱታዎች ላይ
መወያየት ጀምሯል፡፡
የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ካህናትና ምእመናን ሊቀ ጳጳሱ
ብፁዕ አባ ማርቆስ እንዲነሡላቸው ከ2004 ዓ.ም. ጀምሮ
ሲያቀርቡ የቆዩትን አቤቱታዎችና ራሳቸውም ምልዓተ ጉባኤውን
መጠየቃቸውን ተከትሎ ከሀገረ ስብከቱ እንዲነሡ ወስኗል፡፡
ችግሩ በአፋጣኝ ሳይፈታ ዓመታትን በማስቆጠሩና በሀገረ ስብከቱ
ምእመናን መካከል ልዩነት በመፍጠሩ አንድነቱን ለመጠበቅ
የሚያስችሉ የስብከተ ወንጌልና አስተዳደራዊ ሥራዎች
እንዲከናወኑ ምልዓተ ጉባኤው አሳስቧል፡፡ በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ
ስብከት ሥር ያለውና በሀገረ ስብከት ራስን የመቻል ጥያቄ
ያቀረቡት የምዕራብ አርሲ(የሻሸመኔ) ምእመናን የዓመታት
አቤቱታ፣ሊቀ ጳጳሱ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስም ባቀረቡት
የመፍትሔ ሐሳብ እልባት ይሰጠዋል፤ተብሏል፡፡
ከምልዓተ ጉባኤው ሌሎች ዐበይት አጀንዳዎች መካከል፡-
• ስለ ቤተ ክርስቲያን መሪ ዕቅድ እና ኹለንተናዊ ጉዳዮች
የተካሔደው ጥናት፣
• ሀገራዊ ሰላምና ዓለም አቀፍ የስብከተ ወንጌል ሥምሪትን
በተመለከተ፣
• በሕገ ቤተ ክርስቲያኑ ዝርዝር ደንብ እንዲወጣላቸው ስለተባሉ
ጉዳዮች፣
• የአእላፋት ድምፅ የካህናትና ምእመናን ኅብረት ተወካዮች፡-
በመሪ ዕቅድ ትግበራና ከፍተኛ የምእመናን ተሳትፎ የቤተ
ክርስቲያን አስተዳደራዊ ለውጥን በተመለከተ ስላቀረቡት ጥያቄ፤
• የፀረ ተሐድሶ እንቅስቃሴ ሀገር አቀፍ ሪፖርት፣
• የቤተ ክርስቲያኒቱን ሚዲያ በተመለከተ፣
• የላሊበላ አብያተ መቃድስ፣ የአኵስም ሙዝየም እና
የኢየሩሳሌም ገዳማት ችግሮች፣
• ከኤርትራ ኦርቶዶክስ የሰሜን አሜሪካ እና የአውሮፓ ሀገረ
ስብከት ስለተጻፈ ደብዳቤ፣
• ስለ አእምሯዊ ንብረት ሀብት የቀረበ ጥናት፣
• ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ችግርንና አዲስ አበባን በተመለከተ፣
• እነ አባ ገዳ ተሾመ ያቀረቡት አቤቱታ፣
• የውጭ ጉዳይ መምሪያ በውስጥና በውጭ እንዲደራጅ
ስለማድረግ፣
• የቤተ ክርስቲያኒቱን የትምህርት ተቋማት በተመለከተ፣
• የሰላም እና አንድነት ጉባኤ አደረጃጀት፣
• የቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ እና የአባቶች ማረፊያ
ሕንፃ ግንባታ የሚሉት ይገኙባቸዋል፡፡
ምንጭ ፡- ሐራ ዘተዋህዶ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
መወያየቱን ቀጥሏል
• ከተደጋጋሚ ጥሪ በኋላ በምልዓተ ጉባኤው የተገኙትን ብፁዕ
አቡነ ኤዎስጣቴዎስን በይቅርታ ተቀብሏል፤የሀገረ ስብከት ምደባ
ይሰጣቸዋል፤
• የአእላፋት ድምፅ የካህናትና የምእመናን ተናሥኦት ኅብረት
ተወካዮች፣በመሪ ዕቅድ ትግበራና የምእመናነ ከፍተኛ ተሳትፎ
የቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ ለውጥ እንቅስቃሴያቸውን
ቀርበው እንደሚያስረዱ ይጠበቃል፤
***
ከትላንት በስቲያ የተጀመረውና ሦስተኛ ቀኑን የያዘው፣ የቅዱስ
ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ፣ 31 አጀንዳዎችን በማጽደቅ ስብሰባውን
ቀጥሏል፤ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስን የመክፈቻ
ንግግር ካደመጠ በኋላ የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ
መንፈሳዊ ጉባኤ 37ኛ ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ የአቋም
መግለጫና የውሳኔ ሐሳብ ላይ በመወያየት አጽድቋል፡፡
ከ27 ዓመታት በኋላ በተመለሰው ሲኖዶሳዊ አንድነት፣ የአህጉረ
ስብከት ድልደላ እና የብፁዓን አባቶች ምደባ ማካሔድን
በተመለከተ በአጀንዳ ተ.ቁ(3) በመያዝ፣ የድልደላና ምደባ
ምክረ ሐሳቦችን ተቀብሏል፤ ጉዳዩን አደራጅተው ለምልዓተ
ጉባኤው የሚያቀርቡ የብፁዓን አባቶች ኮሚቴም ሠይሟል፤
በድልደላው፣ ከሀገር ውስጥም ኾነ ከውጭ በተደራራቢነት
የተያዙት አህጉረ ስብከት ተነጣጥለው ምደባ
እንደሚካሔድባቸው፤አዲስና ተጨማሪ የአህጉረ ስብከት
አደረጃጀትም እንደሚኖር ይጠበቃል፡፡
ከቀረቡትም ምክረ ሐሳቦች ውስጥ፤ ከሀገር ውስጥ
በተደራራቢነት የተያዙ 8 አህጉረ ስብከት ራሳቸውን ችለው
ብፁዓን አባቶች እንዲመደቡባቸው፤ የሰሜን አሜሪካ አህጉረ
ስብከት ለ9፣ የካናዳ ሀገረ ስብከት ለ3፣ የአውሮጳ አህጉረ
ስብከት ለ4፣ የአፍሪቃ አህጉረ ስብከት ለ3፣ የአውስትራልያ ሀገረ
ስብከት ለ3 ተከፍለው ብፁዓን አባቶች እንዲመደቡባቸው
የሚጠይቀው ይገኝበታል፡፡
በአሁኑ ምልዓተ ጉባኤ የተገኙት የቀድሞው የካሊፎርኒያ ሀገረ
ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ፣ ከ2003 ዓ.ም.
ጀምሮ ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ በተላለፉላቸው ተደጋጋሚ
ጥሪዎች መሠረት ያልቀረቡበትን ምክንያትና በአንዳንድ ወገኖች
ስለሚነሡባቸው ክሦችም ተጠይቀዋል፡፡ ክሦቹን
በተመለከተ፣“ግለሰቦች ስማቸውን ለማጥፋት የሸረቡት ሤራ
ነው፤” በማለት አስረድተዋል፡፡ ከፍተኛ ትምህርታቸውን
እየተከታተሉ እንደነበርና ለመመለስ የማይችሉበት ኹኔታ
እንዳጋጠማቸው የጠቀሱት ብፁዕነታቸው፣ ቅዱስ ሲኖዶሱን
ይቅርታ ጠይቀዋል፤ የሀገረ ስብከት ምደባ እንዲሰጣቸውም
አመልክተዋል፡፡ ይቅርታቸውን የተቀበለው ምልዓተ ጉባኤው፣
በቃል ያስረዱትን በጽሑፍ ሲያቀርቡ ምደባው እንዲሰጣቸው
ተስማምቷል፡፡
ምልዓተ ጉባኤው፣ በትላንት የቀትር በፊት ውሎው፣ በተ.ቁ(11)
አጀንዳው፥ አቤቱታ ስለቀረቡባቸው አህጉረ ስብከት ማለትም፦
• የሻሻመኔ ምእመናን የሀገረ ስብከት ጥያቄ፣
• የምሥራቅ ጎጃም ካህናትና ምእመናን በሊቀ ጳጳሱ ላይ
ስላቀረቡት አቤቱታ፣
• የአዊ ዞን ምእመናን በብፁዕ አባ ቶማስ ላይ ስላቀረቡት
አቤቱታ፤
• የደቡብ እና ሰሜን ጎንደር አህጉረ ስብከት፣
• የካፋ፣ የምዕራብ ወለጋ አህጉረ ስብከት፣
• የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት እና የደብረ ምጥማቅ ሰዓሊተ
ምሕረት ቅድስት ማርያም ካቴድራል ምእመናን አቤቱታዎች ላይ
መወያየት ጀምሯል፡፡
የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ካህናትና ምእመናን ሊቀ ጳጳሱ
ብፁዕ አባ ማርቆስ እንዲነሡላቸው ከ2004 ዓ.ም. ጀምሮ
ሲያቀርቡ የቆዩትን አቤቱታዎችና ራሳቸውም ምልዓተ ጉባኤውን
መጠየቃቸውን ተከትሎ ከሀገረ ስብከቱ እንዲነሡ ወስኗል፡፡
ችግሩ በአፋጣኝ ሳይፈታ ዓመታትን በማስቆጠሩና በሀገረ ስብከቱ
ምእመናን መካከል ልዩነት በመፍጠሩ አንድነቱን ለመጠበቅ
የሚያስችሉ የስብከተ ወንጌልና አስተዳደራዊ ሥራዎች
እንዲከናወኑ ምልዓተ ጉባኤው አሳስቧል፡፡ በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ
ስብከት ሥር ያለውና በሀገረ ስብከት ራስን የመቻል ጥያቄ
ያቀረቡት የምዕራብ አርሲ(የሻሸመኔ) ምእመናን የዓመታት
አቤቱታ፣ሊቀ ጳጳሱ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስም ባቀረቡት
የመፍትሔ ሐሳብ እልባት ይሰጠዋል፤ተብሏል፡፡
ከምልዓተ ጉባኤው ሌሎች ዐበይት አጀንዳዎች መካከል፡-
• ስለ ቤተ ክርስቲያን መሪ ዕቅድ እና ኹለንተናዊ ጉዳዮች
የተካሔደው ጥናት፣
• ሀገራዊ ሰላምና ዓለም አቀፍ የስብከተ ወንጌል ሥምሪትን
በተመለከተ፣
• በሕገ ቤተ ክርስቲያኑ ዝርዝር ደንብ እንዲወጣላቸው ስለተባሉ
ጉዳዮች፣
• የአእላፋት ድምፅ የካህናትና ምእመናን ኅብረት ተወካዮች፡-
በመሪ ዕቅድ ትግበራና ከፍተኛ የምእመናን ተሳትፎ የቤተ
ክርስቲያን አስተዳደራዊ ለውጥን በተመለከተ ስላቀረቡት ጥያቄ፤
• የፀረ ተሐድሶ እንቅስቃሴ ሀገር አቀፍ ሪፖርት፣
• የቤተ ክርስቲያኒቱን ሚዲያ በተመለከተ፣
• የላሊበላ አብያተ መቃድስ፣ የአኵስም ሙዝየም እና
የኢየሩሳሌም ገዳማት ችግሮች፣
• ከኤርትራ ኦርቶዶክስ የሰሜን አሜሪካ እና የአውሮፓ ሀገረ
ስብከት ስለተጻፈ ደብዳቤ፣
• ስለ አእምሯዊ ንብረት ሀብት የቀረበ ጥናት፣
• ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ችግርንና አዲስ አበባን በተመለከተ፣
• እነ አባ ገዳ ተሾመ ያቀረቡት አቤቱታ፣
• የውጭ ጉዳይ መምሪያ በውስጥና በውጭ እንዲደራጅ
ስለማድረግ፣
• የቤተ ክርስቲያኒቱን የትምህርት ተቋማት በተመለከተ፣
• የሰላም እና አንድነት ጉባኤ አደረጃጀት፣
• የቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ እና የአባቶች ማረፊያ
ሕንፃ ግንባታ የሚሉት ይገኙባቸዋል፡፡
ምንጭ ፡- ሐራ ዘተዋህዶ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
#ዜና #ዘኦርቶዶክስ #ተዋህዶ #ዕለታዊ
ቅዱስ ሲኖዶስ ገራሚ ገራሚ ውሳኔዎች ማሳለፉን ቀጥሏል። በትላንትናው ዕለት ካሥተላለፋቸው ውሳኔዎችም
#1ኛ ) በትላንትና እለት የዘገብነውን የሻሸመኔ ምዕመናን ፦ ለመንፈሳዊ አገልግሎት እንዲያመቻቸው ያቀረቡትን የአዲስ አህጉረ ስብከት መቋቋም ፥ ተወያይቶ አፅድቆላቿል ። አዲሱ
የሻሸመኔ ሐገረ ስብከትም የምዕራብ አርሲ ሐገረ ስብከት ተብሎ
ተሰይሟል ። ሊቀ ጳጳስም በዚሁ ምልአተ ጉባኤ ይሾምለታል ።
#2ኛ ) የአዊ ምዕመናን እንባ መድኃኔአለም ያየው ይመስላል ።
ከአባ ማርቆስ ቀጥሎ ሁለተኛው ባለ ቅባት አባ ቶማስ በምዕመናኑ ላይ ያደረሱት የአስተዳደር በደል በአስቸኳይ
እንዲጣራ ኮሚቴ ተቋቁሟል ። ቀጣዩ ተነሺ እንደሚሆኑ ይጠበቃል ።
#3ኛ ) የከፋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጽኡ አቡነ ሕዝቅኤል ስራቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ፥ ከባድ ማሳሰቢያ ተሰጥቷቿል ።
# 4ኛ ) የአዲስ አበባ አህጉረ ስብከትን ለመንፈሳዊ አገልግሎት እና ለሐብት ቁጥጥር በሚያመች መልኩ ለ4 አህጉረ ስብከቶች የመክፈሉን ጉዳይ ተወያይቶ ውሳኔ ሊሰጥበት ቀጠሮ
አስቀምጧል ።
#5ኛ ) ባለፈው ሳምንት እንደገለጽነው በመላው ሐገሪቱ ሰላም ለማስጠበቅ ፥ ብጥብጥን ለማስወገድ ፥ የብጽአን አባቶች
#የሰላም #ሐዋሪያዊ #ተልዕኮ በቡድን በቡድን ሆኖ ስምሪት ለማድረግ ከስምምነት ተደርሷል ።
#6ኛ ) በምዕራብ ሐረርጌ ሐገረ ስብከት በታላቁ የአሰቦት ገዳም "የኦነግ " ታጣቂዎች ነን ባዮች በመነኮሳት ላይ ጉዳት እያደረሱ መሆኑን ተጠቁሟል ። የኦሮሚያ እና የፌደራል.መንግስት ባስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ መጠየቁ ።
#7ኛ ) የኢየሩሳሌም የዴር ሱልጣን ገዳም ፥ በግብጽ መነኮሳት
የማይገባቸውን እርስት የመጠየቅ ብጥብጥ ፥ የእስራኤል ፖሊስ
ጣልቃ ገብቶ ፥ ቀሳጢያንን የግብጽ መነኮሳት ማሰሩ። እርሱንም ተከትሎ የCoptic ቤተክርስቲያን ተጽኖ ለመፍጠር ዘመቻ መጀመሯ ።
#በቀጣይ #ቀናት #ውሎ
#1ኛ ) ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተክርስቲያኒቱን አንድነት ለማናጋት
ዘረኝነትን ወደ ቅድስት ቤተክርስቲያን ለማስገባት ለሚፈልጉ ቡድኖች የማያዳግም መልስ ይሰጣል ተብሎ ይጠብቃል
#2ኛ ) በቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት እና በጣና ገዳማት ላይ በተጋረጠው አደጋ ዙሪያ አስቸኳይ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል
#3ኛ ) የኢየሩሳሌምን የቅድስት ቤተክርስቲያን እርስቶች በሚገባ የሚያስጠብቅ የማያዳግም ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል ።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ቅዱስ ሲኖዶስ ገራሚ ገራሚ ውሳኔዎች ማሳለፉን ቀጥሏል። በትላንትናው ዕለት ካሥተላለፋቸው ውሳኔዎችም
#1ኛ ) በትላንትና እለት የዘገብነውን የሻሸመኔ ምዕመናን ፦ ለመንፈሳዊ አገልግሎት እንዲያመቻቸው ያቀረቡትን የአዲስ አህጉረ ስብከት መቋቋም ፥ ተወያይቶ አፅድቆላቿል ። አዲሱ
የሻሸመኔ ሐገረ ስብከትም የምዕራብ አርሲ ሐገረ ስብከት ተብሎ
ተሰይሟል ። ሊቀ ጳጳስም በዚሁ ምልአተ ጉባኤ ይሾምለታል ።
#2ኛ ) የአዊ ምዕመናን እንባ መድኃኔአለም ያየው ይመስላል ።
ከአባ ማርቆስ ቀጥሎ ሁለተኛው ባለ ቅባት አባ ቶማስ በምዕመናኑ ላይ ያደረሱት የአስተዳደር በደል በአስቸኳይ
እንዲጣራ ኮሚቴ ተቋቁሟል ። ቀጣዩ ተነሺ እንደሚሆኑ ይጠበቃል ።
#3ኛ ) የከፋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጽኡ አቡነ ሕዝቅኤል ስራቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ፥ ከባድ ማሳሰቢያ ተሰጥቷቿል ።
# 4ኛ ) የአዲስ አበባ አህጉረ ስብከትን ለመንፈሳዊ አገልግሎት እና ለሐብት ቁጥጥር በሚያመች መልኩ ለ4 አህጉረ ስብከቶች የመክፈሉን ጉዳይ ተወያይቶ ውሳኔ ሊሰጥበት ቀጠሮ
አስቀምጧል ።
#5ኛ ) ባለፈው ሳምንት እንደገለጽነው በመላው ሐገሪቱ ሰላም ለማስጠበቅ ፥ ብጥብጥን ለማስወገድ ፥ የብጽአን አባቶች
#የሰላም #ሐዋሪያዊ #ተልዕኮ በቡድን በቡድን ሆኖ ስምሪት ለማድረግ ከስምምነት ተደርሷል ።
#6ኛ ) በምዕራብ ሐረርጌ ሐገረ ስብከት በታላቁ የአሰቦት ገዳም "የኦነግ " ታጣቂዎች ነን ባዮች በመነኮሳት ላይ ጉዳት እያደረሱ መሆኑን ተጠቁሟል ። የኦሮሚያ እና የፌደራል.መንግስት ባስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ መጠየቁ ።
#7ኛ ) የኢየሩሳሌም የዴር ሱልጣን ገዳም ፥ በግብጽ መነኮሳት
የማይገባቸውን እርስት የመጠየቅ ብጥብጥ ፥ የእስራኤል ፖሊስ
ጣልቃ ገብቶ ፥ ቀሳጢያንን የግብጽ መነኮሳት ማሰሩ። እርሱንም ተከትሎ የCoptic ቤተክርስቲያን ተጽኖ ለመፍጠር ዘመቻ መጀመሯ ።
#በቀጣይ #ቀናት #ውሎ
#1ኛ ) ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተክርስቲያኒቱን አንድነት ለማናጋት
ዘረኝነትን ወደ ቅድስት ቤተክርስቲያን ለማስገባት ለሚፈልጉ ቡድኖች የማያዳግም መልስ ይሰጣል ተብሎ ይጠብቃል
#2ኛ ) በቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት እና በጣና ገዳማት ላይ በተጋረጠው አደጋ ዙሪያ አስቸኳይ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል
#3ኛ ) የኢየሩሳሌምን የቅድስት ቤተክርስቲያን እርስቶች በሚገባ የሚያስጠብቅ የማያዳግም ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል ።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ኢትዮጵያ እና የኤርትራ
✢~በታሪክ አጋጣሚ የተለያዩ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርስቲያናት ከ27 አመታት በኋላ በአንድ ቅዱስ ሲኖዶስ ሥር እንዲተዳደሩ ፥ ከኢትዮጵያ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ጥሪ ቀርበ ።
✢ ~ ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ለመጀመሪያ ጊዜ
በሶስት ፓትሪያኮች ልትመራ ትችላለች ።
✢ ~ ለ27 አመታት በታሪክ አጋጣሚ ፥ በተለያዩ ሲኖዶሶች ተከፋፍላ የቆየችው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ
ቤተክርስቲያን ፥ የመጀመሪያውን ወሳኝ አንድነት ከፈጠረች በኋላ ቀጣዩ አንድነት ከኤርትራ ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተከርስቲያን ጋር ለመፈጸም እንደታሰበ ብጽኡ ወቅዱስ ፓትሪያክ አቡነ
ማቲያስ በጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ንግግራቸው ገልጸዋል ።
✢ ~ ብጽኡ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ በንግግራቸው "ኢትዮጵያዊያን እና ኤርትራዊያን በታሪክ ና በሐይማኖት አንድ ህዝቦች ናቸው ብለዋል : አክለውም ለኢትዮጵያዊያን
ከኤርትራውያን በላይ ቅርብ ወንድም ለኤርትራውያንም ከኢትዮጵያውያን በላይ የሚቀርባቸው ወንድም የለም ብለዋል።"
✢~ በመጨረሻም ለኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እህት ቤተክርስቲያን የአንድነት ሲኖዶሳዊ አስተዳዳር ለመፍጠር ጥሪ
አቅርበዋል ።
✢ ~ ከኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ዘንድ በወርሃ
ሐምሌ 2010 ዓም የአንድነት እና የትብብር ጥሪ መቅረቡ
አይዘነጋም ።
✢~ የኤርትራ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትሪያክ ከግብጽ የማርቆስ መንበር ወደ ቀደመ ማንነቱ የአቡነ ተክለኃይማኖት
መንበር ይመለሳል ተብሎ ይጠበቃል።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
✢~በታሪክ አጋጣሚ የተለያዩ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርስቲያናት ከ27 አመታት በኋላ በአንድ ቅዱስ ሲኖዶስ ሥር እንዲተዳደሩ ፥ ከኢትዮጵያ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ጥሪ ቀርበ ።
✢ ~ ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ለመጀመሪያ ጊዜ
በሶስት ፓትሪያኮች ልትመራ ትችላለች ።
✢ ~ ለ27 አመታት በታሪክ አጋጣሚ ፥ በተለያዩ ሲኖዶሶች ተከፋፍላ የቆየችው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ
ቤተክርስቲያን ፥ የመጀመሪያውን ወሳኝ አንድነት ከፈጠረች በኋላ ቀጣዩ አንድነት ከኤርትራ ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተከርስቲያን ጋር ለመፈጸም እንደታሰበ ብጽኡ ወቅዱስ ፓትሪያክ አቡነ
ማቲያስ በጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ንግግራቸው ገልጸዋል ።
✢ ~ ብጽኡ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ በንግግራቸው "ኢትዮጵያዊያን እና ኤርትራዊያን በታሪክ ና በሐይማኖት አንድ ህዝቦች ናቸው ብለዋል : አክለውም ለኢትዮጵያዊያን
ከኤርትራውያን በላይ ቅርብ ወንድም ለኤርትራውያንም ከኢትዮጵያውያን በላይ የሚቀርባቸው ወንድም የለም ብለዋል።"
✢~ በመጨረሻም ለኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እህት ቤተክርስቲያን የአንድነት ሲኖዶሳዊ አስተዳዳር ለመፍጠር ጥሪ
አቅርበዋል ።
✢ ~ ከኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ዘንድ በወርሃ
ሐምሌ 2010 ዓም የአንድነት እና የትብብር ጥሪ መቅረቡ
አይዘነጋም ።
✢~ የኤርትራ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትሪያክ ከግብጽ የማርቆስ መንበር ወደ ቀደመ ማንነቱ የአቡነ ተክለኃይማኖት
መንበር ይመለሳል ተብሎ ይጠበቃል።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ቅዱስ ሲኖዶስ በሚያስደምም ውሳኔዎቹ ታጅቦ ቀጥሏል!
ጥቅምት 16/2011 ዓም
¶ ከእንግዲህ ሚስጥር ያላቸውን የቅድስት የቤተክርስቲያንን
የመዝሙር እቃዎች ከመርካቶ እየሸመቱ መለፋደድ አከተመ።
¶ ቅዱስ ሲኖዶስ ትላንት በቀጠለው ጉባኤው "የቅድስት ቤተክርስቲያንን ንዋየ ቅድሳት እና የመዝሙር እቃዎች
የባለቤትነትን መብት ከእንግዲህ በኋላ አስከብራለው " ብሏል።
¶ በትላንትናው እለት በቀጠለው በቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ፥ አጀንዳ ተራ ቁጥር 14 ላይ በተቀመጠው ርዕስ ማለትም በቅድስት ቤተክርስቲያኒቱ ንዋየ ቅድሳትና የመዝሙር እቃዎች ዙሪያ ተወያይቶ በቅርብ ቀናት ባለሙያ አስመድቦ በብሔራዊ ስነ አይምሯዊ ተቋም የባለቤትነት መብት (Patent Right ) እቀበላለው ብሏል ።
¶ ከዛ በኋላማ የ ተሃድሶ መናፍቅን እና መናፍቃን በማያገባቸው
ንብረቶቻችን ላይ መለፋደዳቸውን በህግ ያቆማሉ ።
እነ አዝማሪት ዘርፍሺዋም ወደ ለመዱት ፒያኗቸው እና ጃዛቸው ይመለሳሉ ማለት ነው ።
የእኛ ነው ዋሻው እምነቱ ፀበሉ ፥
አናፍርም ተምክህታችን ነው መስቀሉ ።
Share Share Share
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ጥቅምት 16/2011 ዓም
¶ ከእንግዲህ ሚስጥር ያላቸውን የቅድስት የቤተክርስቲያንን
የመዝሙር እቃዎች ከመርካቶ እየሸመቱ መለፋደድ አከተመ።
¶ ቅዱስ ሲኖዶስ ትላንት በቀጠለው ጉባኤው "የቅድስት ቤተክርስቲያንን ንዋየ ቅድሳት እና የመዝሙር እቃዎች
የባለቤትነትን መብት ከእንግዲህ በኋላ አስከብራለው " ብሏል።
¶ በትላንትናው እለት በቀጠለው በቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ፥ አጀንዳ ተራ ቁጥር 14 ላይ በተቀመጠው ርዕስ ማለትም በቅድስት ቤተክርስቲያኒቱ ንዋየ ቅድሳትና የመዝሙር እቃዎች ዙሪያ ተወያይቶ በቅርብ ቀናት ባለሙያ አስመድቦ በብሔራዊ ስነ አይምሯዊ ተቋም የባለቤትነት መብት (Patent Right ) እቀበላለው ብሏል ።
¶ ከዛ በኋላማ የ ተሃድሶ መናፍቅን እና መናፍቃን በማያገባቸው
ንብረቶቻችን ላይ መለፋደዳቸውን በህግ ያቆማሉ ።
እነ አዝማሪት ዘርፍሺዋም ወደ ለመዱት ፒያኗቸው እና ጃዛቸው ይመለሳሉ ማለት ነው ።
የእኛ ነው ዋሻው እምነቱ ፀበሉ ፥
አናፍርም ተምክህታችን ነው መስቀሉ ።
Share Share Share
@And_Haymanot
@And_Haymanot
'በሐዲስ ኪዳን ውግዘት
የሚባል የለም!' ለምትሉት፦
by Zemaryam zeleke
@And_Haymanot
✞ "...ለሰይጣን እንዲሰጥ ፍርዴ ነው።" [1ኛቆሮ.5፥5] ማለት ምን ማለት ነው?
❖ "መንፈሱ በጌታ በኢየሱስ ቀን ትድን ዘንድ እንደዚህ ያለው ለሥጋው ጥፋት ለሰይጣን እንዲሰጥ ፍርዴ ነው።" [1ኛቆሮ.5፥5]
ለሰይጣን አሳልፋችሁ ስጡት /መጥውዎ ለሰይጣን/(1ኛጢሞ.1፥20) ማለት፦ በተጨባጭ ኑፋቄ የተገኘበትን ሰው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት ሲያወግዙት አድሮበት የነበረ መንፈስ ቅዱስ ይለየዋል፥ መንፈስ ቅዱስም ከተለየው ማኅደር ያለኀዳሪ አያድርም ሰይጣን
ያድርበታልና ለሰይጣን አሳልፋችሁ ስጡት(መጥውዎ ለሰይጣን)አለ።
"ለሥጋው ጥፋት..." ከመ ይሥርዎ ሥጋሁ ሲል በሥጋው ያጠፋው ዘንድ ማለት ነው። "መንፈሱ በጌታ በኢየሱስ ቀን ትድን ዘንድ፦ ወትድኃን መንፈሱ በዕለተ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲል ደግሞ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚመጣበት ቀን በዕለተ ሞት በዕለተ ምጽአት ነፍሱ ትድን ዘንድ ማለት ነው። ይኼም ማለት ከሞተ ኃጢአቱን አይሠራውምና ኃጢአቱንም ካልሠራው ፍዳው ይቀርለታልና። አንድም በሱ ጥፋት የሌላው ነፍስ ትድን ዘንድ የእነረዓይትን (የኔፍሊሞች) ጥፋት ለእነኖኅ ለፈውሰ ነፍሶሙ ሥጋሆሙ(ለነፍስ ለሥጋቸው ፈውስ እንደሆነች) እንዳለ ኄኖክ።
❖ "ከእናንተም ጋር እንዳለሁ ሆኜ ይህን እንደዚህ በሠራው ላይ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሁን ፈርጄበታለሁ፤ እናንተና መንፈሴም ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ጋር
ተሰብስበን፥..." [1ኛ ቆሮ. 5፥4-5]
"በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሁን ፈርጄበታለሁ፤ አንገሊገክሙ በስመ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ።" የጌታችን
የኢየሱስ ክርስቶስን ስሙን ዳኛ አድርጋችሁ። "መንፈሴም" ወምስለ መንፈስየ ሲል ክታቤን ይዛችሁ
ማለቱ ነው።."ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ጋር ተሰብስበን" ምስለ
ኃይለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲል ደግሞ ቀሳውስትን ዲያቆናትን ሰብስባችሁ ማለቱ ነው።
"ለሰይጣን እንዲሰጥ፦ መጥውዎ ለሰይጣን" ማለት ለቀኖናው አሳልፋችሁ ስጡት ሲል ነው።
ቀኖናውን ሰይጣን አለው፥ በዚያ ወራት ሰይጣን መከራ የሚያጸናበት ስለኾነ።
"የሚያውኩአችሁ ይቆረጡ።" ገላ.5፥12 ርቱዕ ይንትጉ እለ የሐውኩክሙ፦ አገባብስ የሚያውኳችሁ(በክህደት፥ በጥርጣሬ) ሰዎች ከአንድነት ሊወጡ ይገባል ሲል ነው። "...በዚያች ሌሊት እንጀራን አንሥቶ አመሰገነ፥..." [1ኛቆሮ.11፥24] ወልደ እግዚአብሔር ሕያው ወልደ ማርያም ሥግው መድኅነ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ "ነሥአ
ኅብስተ አኰተ(እንጀራን(ዳቦን) አንሥቶ አመሰገነ) ሲል፦ ዳቦ አንሥቶ አባቱን አመሰገነ። ያንተ ሞት የዓለሙ ድኅነት፤
ያንተ ኃሣር የዓለሙ ክብር ይኹን ያልህ ብሎ አባቱን አመሰገነ ማለት ነው።
አንድም ሞቱን አመሰገነ፤ ብዙ ነቢያት ጻድቃን ቢሞቱ የነዚያ ሞት ዓለሙን አላዳነም የኔ ሞት ግን ዓለሙን አዳነ ብሎ ሞቱን አመሰገነ ማለት ነው።
አንድም መሥዋዕትነቱን አመሰገነ፤ ብዙ አልሕምት (ላሞች)፥ ብዙ አባግዕ(በጎች) ቢሠዉ የነዚያ መሥዋዕትነት
ለዓለም ጥቅም አልኾነም፤ የኔ መሥዋዕትነት ግን ለዓለሙ
ጥቅም ኾነ ብሎ መሥዋዕትነቱን አመሰገነ።
❖ "እንዲሁም ከእንጀራው ይብላ ከጽዋውም ይጠጣ፤" [1ኛቆሮ.11፥29]
✞ ሥጋውን ደሙን በመብል በመጠጥ ያደረገው በሌላ ያላደረገው ስለምን ነው ቢሉ መብል መጠጥ ያፋቅራል፤ ሥጋው
ደሙም ያፋቅራልና፤ አንድም የቀረው ከብት በአፍአ ይቀራል የበሉት የጠጡት ይዋሐዳል፤ በዚህ ምክንያት ተዋሕጃችሁ
እኖራለሁ ሲል ነው። ያውስ ቢኾን በስንዴ በወይን ያደረገው በሌላ ያላደረገው ስለምን ነው ቢሉ፦ ትንቢቱ ምሳሌው ሊፈጸም።
፠ ትንቢት እምፍሬ ሥርናይ ወወይን ወቅብዕ በዝኀ/ከስንዴ ፍሬና
ከወይን ከዘይትም ይልቅ በዛ/ (መዝ.4፥7)።
ቀዳሜ ሕይወቱ ለሰብእ እክል ወማይ ወይን ወሥርናይ/ የሰው የፈቃዱ መጀመሪያ ውኃ እሳት ብረት ጨው እህል ስንዴ ማር ወተት የወይን ዘለላ ደም ዘይት ልብስ ነው/ ያለው ነው
(ሲራክ 39፥26።)
፠ ምሳሌም መልከ ጼዴቅ በስንዴ በወይን ያስታኩት ነበርና
ትንቢቱን አውቆ ተናግሯል፤ ምሳሌውንም እንጂ አውቆ አስደርጓል ፍጻሜው እንደምን ነው ቢሉ ስንዴ ስብ ይመስላል፤
ወይንም ደም ይመስላልና፤ በመሰለ ነገር ለመስጠት ስንዴ ልባም ሴት የያዘችው እንደኾነ ነውር የሌለበት የማይለወጥ
ይኾናል ነውር የሌለበት የማትለወጥ ሕግ ሠራሁላችሁ ሲል። ወይንም የጣሉት እንደኾነ ኃይል እየነሣ ይሔዳል፤ ኃይል የምትኾን ሕግ ሠራሁላችሁ ሲል።
❖ "ተወዳጆች ሆይ፥ራሳችሁ አትበቀሉ፥ ለቁጣው ፈንታ ስጡ እንጂ፤..." ሮሜ 12፥19 ወኢትትበቀሉ ለሊክሙ(እናንተ
እንበቀላለን አትበሉ)፤ አኀዊነ አኅልፍዋ ለመዓት(ወንድሞቻችን ቂምን አርቋት)። እንደ ዋርካ። ዋርካ በቡቃያነቷ ሳለች አንድ ብላቴና ነቅሎ ይጥላታል። ካደገች ከገነነች በኋላ ግን ብዙ ሰው፥ ብዙ ምሳር፥ ብዙ መጫኛ ታስፈልጋለች። ቂምም የዋለች ያደረች እንደኾነ ከቀቲል(ከመግደል) ታደርሳለች፤ ከቀቲልም ካደረሰች ፍዳዋ ይጸናልና።
አንድም ክህደትን ከናንተ አርቋት መዓተ አርዮስ እንዲል።
❖ "የዚች ዓለም ጥበብ በእግዚአብሔር ፊት ሞኝነት ነውና። እርሱ ጥበበኞችን በተንኰላቸው የሚይዝ፤..." [1ኛቆሮ.3፥19] ዘይእኅዞሙ ለጠቢባን ትምይንቶሙ/እርሱ ጥበበኞችን
በተንኰላቸው የሚይዝ/(ኢዮብ 5፥12-15) ማለት ፈላስፎችን
ከዕውቀት የሚገታቸው እናውቃለን ማለታቸው ነው ብሏልና። (ታሪክ) እንደ አንድ ፈላስፋ መምህር ውዳሴ ከንቱ ሽቶ ሙስና (መቃብር ፈርቶ) አርድእቶቹን ልጆቼ የሞትሁ እንደኾነ ሥጋዬን
አትቅበሩት አርዳችሁ ብሉት ጥበብ ይገለጥላችኋል አላቸው፤.ጥበብማ የሚገለጥልን ከኾነ እስኪሞት ምን ያጠባብቀናል ብለው አርደው ተቀራምተው ቀምሰውታልና እርሱ ጥበበኞችን በተንኰላቸው የሚይዝ አለ።
❖ "ደግሞም፦ ጌታ የጥበበኞችን አሳብ ከንቱ እንደ ሆነ ያውቃል ተብሎ ተጽፎአልና።"[1ኛ ቆሮ. 3፥20]
ዳግመኛ ጠቢባን ነን የሚሉ ሰዎች ጥበባቸው ከንቱ እንደ ኾነ እግዚአብሔር ያውቃል ብሎ መጽሐፍ እንደተናገረ። (ታሪክ) እንዳንድ ፈላስፋ በፍልስፍና ሲዞር ዕፀ ሕይወትን አገኘ ከሀገር
የኾነ እንደኾነ ከሰው ይተርፋል ብሎ በሸክላ ዘፍዝፎ ተሸክሞ ወደ በረሀ ሲሔድ ጌታ ምቀኝነት አይወድምና መልአክ ከላዩ ላይ ሰበረበት በኲል አካሉ ሲፈስ በኲሌታ አካሉ ሳይፈስበት ቀረ
የፈሰሰበት አካሉ ሕያው ኾኖ ያልፈሰሰበት አካሉ ሸቶ ተልቶ
በኃሣር የሚኖር ኾኗል። (ዜና እስክንድር)
☞ የዚህ ጽሑፍ ጸሐፊ በ Youtube በተለያዩ ርዕሶች
የሚሰጣቸውን መንፈሳዊ ትምህርቶችን Audio በሚከተለው
አድራሻ ይከታተሉ። https://www.youtube.com/channel/UCyW5pGARAaJt4HMNmtZsYGQ/videos?
view_as=subscriber
☞ Join @And_Haymanot
የሚባል የለም!' ለምትሉት፦
by Zemaryam zeleke
@And_Haymanot
✞ "...ለሰይጣን እንዲሰጥ ፍርዴ ነው።" [1ኛቆሮ.5፥5] ማለት ምን ማለት ነው?
❖ "መንፈሱ በጌታ በኢየሱስ ቀን ትድን ዘንድ እንደዚህ ያለው ለሥጋው ጥፋት ለሰይጣን እንዲሰጥ ፍርዴ ነው።" [1ኛቆሮ.5፥5]
ለሰይጣን አሳልፋችሁ ስጡት /መጥውዎ ለሰይጣን/(1ኛጢሞ.1፥20) ማለት፦ በተጨባጭ ኑፋቄ የተገኘበትን ሰው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት ሲያወግዙት አድሮበት የነበረ መንፈስ ቅዱስ ይለየዋል፥ መንፈስ ቅዱስም ከተለየው ማኅደር ያለኀዳሪ አያድርም ሰይጣን
ያድርበታልና ለሰይጣን አሳልፋችሁ ስጡት(መጥውዎ ለሰይጣን)አለ።
"ለሥጋው ጥፋት..." ከመ ይሥርዎ ሥጋሁ ሲል በሥጋው ያጠፋው ዘንድ ማለት ነው። "መንፈሱ በጌታ በኢየሱስ ቀን ትድን ዘንድ፦ ወትድኃን መንፈሱ በዕለተ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲል ደግሞ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚመጣበት ቀን በዕለተ ሞት በዕለተ ምጽአት ነፍሱ ትድን ዘንድ ማለት ነው። ይኼም ማለት ከሞተ ኃጢአቱን አይሠራውምና ኃጢአቱንም ካልሠራው ፍዳው ይቀርለታልና። አንድም በሱ ጥፋት የሌላው ነፍስ ትድን ዘንድ የእነረዓይትን (የኔፍሊሞች) ጥፋት ለእነኖኅ ለፈውሰ ነፍሶሙ ሥጋሆሙ(ለነፍስ ለሥጋቸው ፈውስ እንደሆነች) እንዳለ ኄኖክ።
❖ "ከእናንተም ጋር እንዳለሁ ሆኜ ይህን እንደዚህ በሠራው ላይ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሁን ፈርጄበታለሁ፤ እናንተና መንፈሴም ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ጋር
ተሰብስበን፥..." [1ኛ ቆሮ. 5፥4-5]
"በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሁን ፈርጄበታለሁ፤ አንገሊገክሙ በስመ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ።" የጌታችን
የኢየሱስ ክርስቶስን ስሙን ዳኛ አድርጋችሁ። "መንፈሴም" ወምስለ መንፈስየ ሲል ክታቤን ይዛችሁ
ማለቱ ነው።."ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ጋር ተሰብስበን" ምስለ
ኃይለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲል ደግሞ ቀሳውስትን ዲያቆናትን ሰብስባችሁ ማለቱ ነው።
"ለሰይጣን እንዲሰጥ፦ መጥውዎ ለሰይጣን" ማለት ለቀኖናው አሳልፋችሁ ስጡት ሲል ነው።
ቀኖናውን ሰይጣን አለው፥ በዚያ ወራት ሰይጣን መከራ የሚያጸናበት ስለኾነ።
"የሚያውኩአችሁ ይቆረጡ።" ገላ.5፥12 ርቱዕ ይንትጉ እለ የሐውኩክሙ፦ አገባብስ የሚያውኳችሁ(በክህደት፥ በጥርጣሬ) ሰዎች ከአንድነት ሊወጡ ይገባል ሲል ነው። "...በዚያች ሌሊት እንጀራን አንሥቶ አመሰገነ፥..." [1ኛቆሮ.11፥24] ወልደ እግዚአብሔር ሕያው ወልደ ማርያም ሥግው መድኅነ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ "ነሥአ
ኅብስተ አኰተ(እንጀራን(ዳቦን) አንሥቶ አመሰገነ) ሲል፦ ዳቦ አንሥቶ አባቱን አመሰገነ። ያንተ ሞት የዓለሙ ድኅነት፤
ያንተ ኃሣር የዓለሙ ክብር ይኹን ያልህ ብሎ አባቱን አመሰገነ ማለት ነው።
አንድም ሞቱን አመሰገነ፤ ብዙ ነቢያት ጻድቃን ቢሞቱ የነዚያ ሞት ዓለሙን አላዳነም የኔ ሞት ግን ዓለሙን አዳነ ብሎ ሞቱን አመሰገነ ማለት ነው።
አንድም መሥዋዕትነቱን አመሰገነ፤ ብዙ አልሕምት (ላሞች)፥ ብዙ አባግዕ(በጎች) ቢሠዉ የነዚያ መሥዋዕትነት
ለዓለም ጥቅም አልኾነም፤ የኔ መሥዋዕትነት ግን ለዓለሙ
ጥቅም ኾነ ብሎ መሥዋዕትነቱን አመሰገነ።
❖ "እንዲሁም ከእንጀራው ይብላ ከጽዋውም ይጠጣ፤" [1ኛቆሮ.11፥29]
✞ ሥጋውን ደሙን በመብል በመጠጥ ያደረገው በሌላ ያላደረገው ስለምን ነው ቢሉ መብል መጠጥ ያፋቅራል፤ ሥጋው
ደሙም ያፋቅራልና፤ አንድም የቀረው ከብት በአፍአ ይቀራል የበሉት የጠጡት ይዋሐዳል፤ በዚህ ምክንያት ተዋሕጃችሁ
እኖራለሁ ሲል ነው። ያውስ ቢኾን በስንዴ በወይን ያደረገው በሌላ ያላደረገው ስለምን ነው ቢሉ፦ ትንቢቱ ምሳሌው ሊፈጸም።
፠ ትንቢት እምፍሬ ሥርናይ ወወይን ወቅብዕ በዝኀ/ከስንዴ ፍሬና
ከወይን ከዘይትም ይልቅ በዛ/ (መዝ.4፥7)።
ቀዳሜ ሕይወቱ ለሰብእ እክል ወማይ ወይን ወሥርናይ/ የሰው የፈቃዱ መጀመሪያ ውኃ እሳት ብረት ጨው እህል ስንዴ ማር ወተት የወይን ዘለላ ደም ዘይት ልብስ ነው/ ያለው ነው
(ሲራክ 39፥26።)
፠ ምሳሌም መልከ ጼዴቅ በስንዴ በወይን ያስታኩት ነበርና
ትንቢቱን አውቆ ተናግሯል፤ ምሳሌውንም እንጂ አውቆ አስደርጓል ፍጻሜው እንደምን ነው ቢሉ ስንዴ ስብ ይመስላል፤
ወይንም ደም ይመስላልና፤ በመሰለ ነገር ለመስጠት ስንዴ ልባም ሴት የያዘችው እንደኾነ ነውር የሌለበት የማይለወጥ
ይኾናል ነውር የሌለበት የማትለወጥ ሕግ ሠራሁላችሁ ሲል። ወይንም የጣሉት እንደኾነ ኃይል እየነሣ ይሔዳል፤ ኃይል የምትኾን ሕግ ሠራሁላችሁ ሲል።
❖ "ተወዳጆች ሆይ፥ራሳችሁ አትበቀሉ፥ ለቁጣው ፈንታ ስጡ እንጂ፤..." ሮሜ 12፥19 ወኢትትበቀሉ ለሊክሙ(እናንተ
እንበቀላለን አትበሉ)፤ አኀዊነ አኅልፍዋ ለመዓት(ወንድሞቻችን ቂምን አርቋት)። እንደ ዋርካ። ዋርካ በቡቃያነቷ ሳለች አንድ ብላቴና ነቅሎ ይጥላታል። ካደገች ከገነነች በኋላ ግን ብዙ ሰው፥ ብዙ ምሳር፥ ብዙ መጫኛ ታስፈልጋለች። ቂምም የዋለች ያደረች እንደኾነ ከቀቲል(ከመግደል) ታደርሳለች፤ ከቀቲልም ካደረሰች ፍዳዋ ይጸናልና።
አንድም ክህደትን ከናንተ አርቋት መዓተ አርዮስ እንዲል።
❖ "የዚች ዓለም ጥበብ በእግዚአብሔር ፊት ሞኝነት ነውና። እርሱ ጥበበኞችን በተንኰላቸው የሚይዝ፤..." [1ኛቆሮ.3፥19] ዘይእኅዞሙ ለጠቢባን ትምይንቶሙ/እርሱ ጥበበኞችን
በተንኰላቸው የሚይዝ/(ኢዮብ 5፥12-15) ማለት ፈላስፎችን
ከዕውቀት የሚገታቸው እናውቃለን ማለታቸው ነው ብሏልና። (ታሪክ) እንደ አንድ ፈላስፋ መምህር ውዳሴ ከንቱ ሽቶ ሙስና (መቃብር ፈርቶ) አርድእቶቹን ልጆቼ የሞትሁ እንደኾነ ሥጋዬን
አትቅበሩት አርዳችሁ ብሉት ጥበብ ይገለጥላችኋል አላቸው፤.ጥበብማ የሚገለጥልን ከኾነ እስኪሞት ምን ያጠባብቀናል ብለው አርደው ተቀራምተው ቀምሰውታልና እርሱ ጥበበኞችን በተንኰላቸው የሚይዝ አለ።
❖ "ደግሞም፦ ጌታ የጥበበኞችን አሳብ ከንቱ እንደ ሆነ ያውቃል ተብሎ ተጽፎአልና።"[1ኛ ቆሮ. 3፥20]
ዳግመኛ ጠቢባን ነን የሚሉ ሰዎች ጥበባቸው ከንቱ እንደ ኾነ እግዚአብሔር ያውቃል ብሎ መጽሐፍ እንደተናገረ። (ታሪክ) እንዳንድ ፈላስፋ በፍልስፍና ሲዞር ዕፀ ሕይወትን አገኘ ከሀገር
የኾነ እንደኾነ ከሰው ይተርፋል ብሎ በሸክላ ዘፍዝፎ ተሸክሞ ወደ በረሀ ሲሔድ ጌታ ምቀኝነት አይወድምና መልአክ ከላዩ ላይ ሰበረበት በኲል አካሉ ሲፈስ በኲሌታ አካሉ ሳይፈስበት ቀረ
የፈሰሰበት አካሉ ሕያው ኾኖ ያልፈሰሰበት አካሉ ሸቶ ተልቶ
በኃሣር የሚኖር ኾኗል። (ዜና እስክንድር)
☞ የዚህ ጽሑፍ ጸሐፊ በ Youtube በተለያዩ ርዕሶች
የሚሰጣቸውን መንፈሳዊ ትምህርቶችን Audio በሚከተለው
አድራሻ ይከታተሉ። https://www.youtube.com/channel/UCyW5pGARAaJt4HMNmtZsYGQ/videos?
view_as=subscriber
☞ Join @And_Haymanot
እኔ እና እሱ.....
@And_Haymanot
እኔ ለእግዚአብሔር የአምልኮ ስግደት ለቅዱሳኑ ደግሞ የክብር ስግደት እፈፅማለሁ! አንድ ሰው የሚከተለው ጥቅስ ጠቅሶ ስግደት መፈፀም ያለበት
ለእግዚአብሔር ብቻ ነው ምስጋናም እንዲሁ ብለኝ መንፈስ ቅዱስ እንደገለጠልኝ እንደሚከተለው እመልስለት ነበር። እሱና እኔ
እሱ=> እኔ ሕያው ነኝ ይላል ጌታ ጉልበት ሁሉ ለእኔ ይምበረከካል ምላስም ሁሉ እግዚአብሔርን ያመሰግናል ተብሎ
ተጽፏልና። ሮሜ 14:11
ስለዚህ ስግደትና ምስጋና ለጌታ ብቻ ነው የሚገባው።
እኔ=> የሮሜ መልእክትን የፃፈው ማን ነው?
እሱ=> እሱ የምያውቅ ከሆነ ቅዱስ ጳውሎስ ብሎ ይመልሳል።
እኔ=> ታድያ ቅዱስ ጳውሎስ ስግደት መፈፀም ያለበት ለጌታ ብቻ መሆኑን እያወቀ የወህኒ ቤት ጠባቂ ተደፍቶ ስሰግድለት ለምን ዝም አለው? ስግደት ለጌታ ብቻ ነውና ተነስ ለምን አላለውም? ሐዋ 16:29 ያንብቡት!
እሱ=> እሱ ምን ይለኝ እንደነበር እግዚአብሔር ይወቀው እኔ ግን ጥያቄየን እቀጥላለሁ።
እኔ=> በብሉይ ኪዳን በየቦታው ሰዎች ከእግዚአብሔር ውጭ ለፍጡራኖቹ ማለት ለቅዱሳን መላእክትና ቅዱሳን ሰዎች ሲሰግዱ የምናየው ለምንድነው? ዘፍ 19፡1 ኢያ 5:14 2 ነገ1:13 ዳን 2:46 ያ ስግደት ለእርሱ ብቻ የሚገባው ጌታ ያኔ ስላልነበረ ነውን? እንድያውም በአንተ አተረጓጎም ከእኔ በቀር ለሌላ አማልክት አትስገድ(ዘፀ 20) ሲል ለቅዱሳን መላእክትና ለቅዱሳን ሰዎች
ከሆነ ሰዎች ለቅዱሳን ተደፍተው ለምን ሰገዱ? ስግደታቸው በእግዚአብሔር ፍት ያልተወደደና ያልተፈቀደ ከነበረስ እስራኤላዊያን አሮን ላቆመላቸው ጣኦት በሰገዱ ግዜ የተቀሰፉ ሲሆን ለቅዱሳን ስሰግዱ እንኳን ሊቀስፋቸው ምንም
አልተናገራቸውም። ታድያ ለምን? ዘፀ 32:1-32 ከእኔ ውጭ ለማንም አትስገዱ ባለበት በብሉይ ዘመን ከእርሱ
ውጭ ለቅዱሳን ስግደት ከተፈፀመ እንደሱ ብሎ ባልተናገረበት በሐዲስ ኪዳን ስግደት ለቅዱሳን እንዴት አይገባም?? እንደሱ ሲል በብሉይ የተናገረው ቃሉ ለዘላለም የሚሰራ ሕያው መሆኑን ዘንግቼ አይደለሁም ይልቅ በብሉይ እና በሐዲስ እያልክ
ለያይተህ የምትቀበል ካንተ ጋራ እያወራሁ ስለሆነ ነው እንጂ።
እንዳንተ ስንፍና ብሄድ ግን በሐዲስ ኪዳን ከእኔ በቀር ለሌላ አትስገዱ ስላላለ ለድመት ብንሰግድም ችግር የለውም ቢል ልክ ነኝ። ባንተ ቋንቋ መናገሬ ነው። ግን ሎቱ ስብሐት ለእርሱ
የአምልኮ ለቅዱሳኑ ደግሞ የክብር ስግደት ከመፈፀም ውጭ ለማንም አልሰግድም።
እሱ=> እሱ በብሉይ ስግደት ይፈፀም ነበር በሐዲስ ግን አይፈቀድም እንዳይለኝ አስቀድሜ በሐድስ እንደተፈቀደ ስላሳየሁት(ሐዋ 16:29) ምን ይለኝ እንደነበረ አላውቅም።
መሄጃ ቢያጣ ኦህ ይቅርታ በቁርአን አልተፈቀደም ማለቴን ነው እንኳ ቢለኝ ዲያብሎስ ለአደም ባለመስገዱ መቀጣቱን ለመንገር ብዙ አይከብድም። ሱራት አል በቀራህ (2) የቀረን የምስጋና ጉዳይ ነው። እሱ መጀመርያ ላይ እንዳየነው ቃሉ <<ምላስም ሁሉ እግዚአብሔርን ያመሰግናል ተብሎ
ተፅፏልና>> ስለምል ምላስ ያለው ሁሉ ከእግዚአብሔር ውጭ ማንንም ማመስገን የለበትም ባይ ነው።
እኔ=> እንደምታወቀው <ምላስ ሁሉ> ሲል <ትውልድ ሁሉ> ማለቱ ነው። ለሁሉ ግልፅ የሆነ ነገር ስለሆነ አላማው ሌላ
ካልሆነ በስተቀር አይደለም ይለኛል ብየ አልጠብቅም። ታዲያ መፅሐፍ ቅዱስ ትውልድ ሁሉ ለማርያም ብፅዕት ይላታል
የሚለው ቃል አላነበብክምን ።
<< እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይለኛል። ሉቃ
1:48>>
እና መፅሐፍ ተሳስቷል ማለት ነው? ሐሰት
ወይስ ቅዱስ ሉቃስ ተሳስቶት ይሆን? ሐሰት
ሉቃስማ የፃፈው በመንፈስ ቅዱስ እንጂ ከራሱ አይደለም። ሐዋ 1:14 ሥራ 2
እንደሱ እንዳትል መፅሐፉ ቅዱስ ነው ብለህ ተሸክመኸዋል ከእነርሱ አንዱ የሉቃስ ነው። እለው ነበር እናንተም መንፈስ ቅዱስ በገለጠላችሁ መጠን ምን ትሉት እንደነበር በኮሜንት ያስቀምጡለት!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ዲያቆን ሓሰበላ ኣለማ ዘጉንዳጉንዶ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
እኔ ለእግዚአብሔር የአምልኮ ስግደት ለቅዱሳኑ ደግሞ የክብር ስግደት እፈፅማለሁ! አንድ ሰው የሚከተለው ጥቅስ ጠቅሶ ስግደት መፈፀም ያለበት
ለእግዚአብሔር ብቻ ነው ምስጋናም እንዲሁ ብለኝ መንፈስ ቅዱስ እንደገለጠልኝ እንደሚከተለው እመልስለት ነበር። እሱና እኔ
እሱ=> እኔ ሕያው ነኝ ይላል ጌታ ጉልበት ሁሉ ለእኔ ይምበረከካል ምላስም ሁሉ እግዚአብሔርን ያመሰግናል ተብሎ
ተጽፏልና። ሮሜ 14:11
ስለዚህ ስግደትና ምስጋና ለጌታ ብቻ ነው የሚገባው።
እኔ=> የሮሜ መልእክትን የፃፈው ማን ነው?
እሱ=> እሱ የምያውቅ ከሆነ ቅዱስ ጳውሎስ ብሎ ይመልሳል።
እኔ=> ታድያ ቅዱስ ጳውሎስ ስግደት መፈፀም ያለበት ለጌታ ብቻ መሆኑን እያወቀ የወህኒ ቤት ጠባቂ ተደፍቶ ስሰግድለት ለምን ዝም አለው? ስግደት ለጌታ ብቻ ነውና ተነስ ለምን አላለውም? ሐዋ 16:29 ያንብቡት!
እሱ=> እሱ ምን ይለኝ እንደነበር እግዚአብሔር ይወቀው እኔ ግን ጥያቄየን እቀጥላለሁ።
እኔ=> በብሉይ ኪዳን በየቦታው ሰዎች ከእግዚአብሔር ውጭ ለፍጡራኖቹ ማለት ለቅዱሳን መላእክትና ቅዱሳን ሰዎች ሲሰግዱ የምናየው ለምንድነው? ዘፍ 19፡1 ኢያ 5:14 2 ነገ1:13 ዳን 2:46 ያ ስግደት ለእርሱ ብቻ የሚገባው ጌታ ያኔ ስላልነበረ ነውን? እንድያውም በአንተ አተረጓጎም ከእኔ በቀር ለሌላ አማልክት አትስገድ(ዘፀ 20) ሲል ለቅዱሳን መላእክትና ለቅዱሳን ሰዎች
ከሆነ ሰዎች ለቅዱሳን ተደፍተው ለምን ሰገዱ? ስግደታቸው በእግዚአብሔር ፍት ያልተወደደና ያልተፈቀደ ከነበረስ እስራኤላዊያን አሮን ላቆመላቸው ጣኦት በሰገዱ ግዜ የተቀሰፉ ሲሆን ለቅዱሳን ስሰግዱ እንኳን ሊቀስፋቸው ምንም
አልተናገራቸውም። ታድያ ለምን? ዘፀ 32:1-32 ከእኔ ውጭ ለማንም አትስገዱ ባለበት በብሉይ ዘመን ከእርሱ
ውጭ ለቅዱሳን ስግደት ከተፈፀመ እንደሱ ብሎ ባልተናገረበት በሐዲስ ኪዳን ስግደት ለቅዱሳን እንዴት አይገባም?? እንደሱ ሲል በብሉይ የተናገረው ቃሉ ለዘላለም የሚሰራ ሕያው መሆኑን ዘንግቼ አይደለሁም ይልቅ በብሉይ እና በሐዲስ እያልክ
ለያይተህ የምትቀበል ካንተ ጋራ እያወራሁ ስለሆነ ነው እንጂ።
እንዳንተ ስንፍና ብሄድ ግን በሐዲስ ኪዳን ከእኔ በቀር ለሌላ አትስገዱ ስላላለ ለድመት ብንሰግድም ችግር የለውም ቢል ልክ ነኝ። ባንተ ቋንቋ መናገሬ ነው። ግን ሎቱ ስብሐት ለእርሱ
የአምልኮ ለቅዱሳኑ ደግሞ የክብር ስግደት ከመፈፀም ውጭ ለማንም አልሰግድም።
እሱ=> እሱ በብሉይ ስግደት ይፈፀም ነበር በሐዲስ ግን አይፈቀድም እንዳይለኝ አስቀድሜ በሐድስ እንደተፈቀደ ስላሳየሁት(ሐዋ 16:29) ምን ይለኝ እንደነበረ አላውቅም።
መሄጃ ቢያጣ ኦህ ይቅርታ በቁርአን አልተፈቀደም ማለቴን ነው እንኳ ቢለኝ ዲያብሎስ ለአደም ባለመስገዱ መቀጣቱን ለመንገር ብዙ አይከብድም። ሱራት አል በቀራህ (2) የቀረን የምስጋና ጉዳይ ነው። እሱ መጀመርያ ላይ እንዳየነው ቃሉ <<ምላስም ሁሉ እግዚአብሔርን ያመሰግናል ተብሎ
ተፅፏልና>> ስለምል ምላስ ያለው ሁሉ ከእግዚአብሔር ውጭ ማንንም ማመስገን የለበትም ባይ ነው።
እኔ=> እንደምታወቀው <ምላስ ሁሉ> ሲል <ትውልድ ሁሉ> ማለቱ ነው። ለሁሉ ግልፅ የሆነ ነገር ስለሆነ አላማው ሌላ
ካልሆነ በስተቀር አይደለም ይለኛል ብየ አልጠብቅም። ታዲያ መፅሐፍ ቅዱስ ትውልድ ሁሉ ለማርያም ብፅዕት ይላታል
የሚለው ቃል አላነበብክምን ።
<< እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይለኛል። ሉቃ
1:48>>
እና መፅሐፍ ተሳስቷል ማለት ነው? ሐሰት
ወይስ ቅዱስ ሉቃስ ተሳስቶት ይሆን? ሐሰት
ሉቃስማ የፃፈው በመንፈስ ቅዱስ እንጂ ከራሱ አይደለም። ሐዋ 1:14 ሥራ 2
እንደሱ እንዳትል መፅሐፉ ቅዱስ ነው ብለህ ተሸክመኸዋል ከእነርሱ አንዱ የሉቃስ ነው። እለው ነበር እናንተም መንፈስ ቅዱስ በገለጠላችሁ መጠን ምን ትሉት እንደነበር በኮሜንት ያስቀምጡለት!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ዲያቆን ሓሰበላ ኣለማ ዘጉንዳጉንዶ
@And_Haymanot
@And_Haymanot