ሀ. መልካም እንናገር ወይንም ዝም እንበል፡-
ኢማሙ-ሻፊዒይ (ረሒመሁላህ) የሐዲሡን መልክት ሲናገሩ እንዲህ አሉ፡- "መናገር የፈለገ እንደሆን ቀድሞ ያስብበት፡፡ ጉዳት እንደሌለው ከታየው ይናገረው፡፡ ጉዳት እንዳለው ካወቀ ወይም ከተጠራጠረ ይተወው" ከሰዎች አንደበት የሚወጡ ቃላት በጠቅላላ ይጻፋል (በዕብደት፣በልጅነት፣በዕንቅልፍ ምክንያት የሆኑት ብቻ ሲቀሩ)፡- "ከቃል አንድንም አይናገርም ከርሱ ዘንድ(ቃሉን ለመመዝገብ)ዝግጁ የሆኑ መላእክት ያሉ ቢሆን እንጅ።" (ሱረቱ ቃፍ 18)፡፡ "የእነዚያን አላህ ድኻ ነዉ፥ እኛ ግን ከበርቴዎች ነን ያሉትን ሰዎች ቃል አላህ በእርግጥ ሰማ፤ ያንን ያሉትንና ነቢያትን ያለ ሕግ መግደላቸዉን በእርግጥ እንጽፋለን፤ የእሳትንም ስቃይ ቅመሱ እንላቸዋለን።" (ሱረቱ አለ-ዒምራን 181)፡፡ "በናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትሆኑ፤ የተከበሩ ጸሐፊዎች የሆኑ፤ (ተጠባባቂዎች)" (ሱረቱል ኢንፊጣር 10-11)፡፡
ስለሆነም የምናነገረውን እንጠንቀቅ፡፡ ወይ ሊጠቅመን ወይም ሊጎዳን መሆኑ እስካልቀረ የሚበጀንን መምረጥ ብልኅነት ነው፡፡ ከተናገርን ጌታችንን የሚያስደስት፣ ሰዎችን የሚጠቅምና በሚዛናችን ላይ የሚቀርልንን እንምረጥ፡፡ መልካም ንግግር አስተዋይ ስብዕናን እንጂ ወጪን አይጠይቅምና፡-
አቢ ሁረይራህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደነገረን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "ጸሐይ በምትወጣበት ቀን ሁሉ እያንዳንዱ የሰውነት መገጣጠሚያ ሶደቃ አለበት፡፡ በሁለት ሰዎች መሐል በትክክል መፍረድ ሶደቃ ነው፣ ሰውየውን በመጓጓዣው ላይ እቃውን እንዲጭን ብታግዘው ሶደቃ ነው፣ #መልካም_ንግግር ሶደቃ ነው፣ ወደ ሶላት የምታደርገውው እንቅስቃሴም ሶደቃ ነው፣ የሚያስቸግር ነገር ከመንገድ ማንሳትህም ሶደቃ ነው" (ቡኻሪና ሙስሊም)፡፡
አቢ-ሙሳ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ አለ፡- "የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሆይ! ከሙስሊሞች መሐል በላጩ ማነው? ስላቸው፡ እሳቸውም፡- ‹‹ሙስሊሞች ከምላሱና ከእጁ የተረፉበት ሰው ነው›› ብለው መለሱልኝ" (ቡኻሪና ሙስሊም)፡፡
ሰህል ኢብኑ-ሰዕድ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደተናገረው የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "በሁለቱ አጥንቶቹ መሐል ያለውን (ምላሱን) እና በእግሮቹ መሐል ያለውን (ብልቱን) ለመጠበቅ ቃል ለሚገባልኝ ሰው ጀነትን ዋስ እሆነዋለሁ" (ቡኻሪና ሙስሊም)፡፡
አላህ ካልወፈቀንና መልካም ነገርን መናገር ካልቻልን ዝም እንበል፡፡ ዝምታም በራሱ ኸይር ነውና!! ዐብዱላህ ኢብኑ-ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንደተናገሩት የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- " ‹‹ዝም ያለ ሰው ነጃ ወጣ (ዳነ)›› እሳቸውም በጣም ዝምተኛና ሳቃቸውም መጠነኛ ነበር" (አሕመድ 9/196)፡፡ የምንናገረውን ነገር ቀድመን ሳናውቅ ከተናገርን አደጋው የከፋ ይሆናልና ቆጠብ እንበል፡-
አቢ ሁረይራህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ሲሉ ሰማ፡- "አንድ አላህ ባሪያ አንዲትን ቃል ጥሩ ይሁን መጥፎ ሳያስተውል ይናገርና በሷ ሰበብ ወደ እሳት ምስራቁና ምእራቡ ከሚራራቀው የበለጠ ይጣላል" (ቡኻሪና ሙስሊም)፡፡
ዐብዱላህ ኢብኑ-ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንደተናገሩት የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "አላህን ከማውሳት ውጭ በሆነ ነገር ላይ ንግግር አታብዙ፡፡ አላህን ከማውሳት ውጭ የሆነ ንግግር ማብዛት የልብ ድርቀት ነው፡፡ ልበ ደረቅ ሰው ደግሞ ከአላህ (ራሕመት) የራቀ ነው" (ቲርሚዚይ)፡፡
ዑቅበተ ኢብኑ-ዓሚር (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ አለ፡- "የአላህ መልክተኛ ሆይ! መዳን እንዴት ነው? ስላቸው፡ እሳቸውም፡- ‹‹ምላስህን ተቆጣጠር፣ ቤትህ ይስፋህ፣ ለኃጢአትህ አልቅስ›› አሉኝ" (ቲርሚዚይ)፡፡
ለ. ጎረቤት እናክብር፡-
ጎረቤት የሚባለው ማነው ማነው? የሚለውን ጉዳይ የኢስላም ሊቃውንቶች የገለጹበት መንገድ ያስደነግጣል፡፡ እኛ ጎረቤት ብለን የምንገምተው ከቤታችን ቀጥሎ ያሉት ከ1-4 ቤቶች ላይ ብቻ የተገደበ አድርገን ነበር፡፡ ሐሰኑል በስሪ ረሒመሁላህ) ስለ ጎረቤት ተጠይቀው ሲመልሱ ግን እንዲህ ነበር ያሉት፡- ‹‹ከፊት ለፊቱ እስከ አርባ ቤት ድረስ፣ ከኋላው እስከ አርባ ቤት ድረስ፣ ከቀኝ ጎኑ እስከ አርባ ቤት ድረስ፣ ከግራ ጎኑ እስከ አርባ ቤት ድረስ ያለው ነው›› ብለው መለሱ (ቡኻሪይ አደቡል-ሙፍረድ 109)፡፡ ወይንም ደግሞ እንደ አካባቢው ባሕል መታየት ስላለበት ያ አካባቢ ጎረቤት ብሎ የሚጠራውን ሁሉ ያካተተ በሚለው መጓዙም መልካም ነው፡ ወላሁ አዕለም፡፡ ጎረቤት ሶስት አይነት ነው፡- 1. በኛ ላይ ሶስት ሐቅ (መብት) ያለው፡- 2. በኛ ላይ ሁለት ሐቅ ያለው፡- 3. በኛ ላይ አንድ ሐቅ ያለው፡-
የመጀመሪያው አይነት ጎረቤት፡- ሙስሊምና የስጋ ዘመዳችን የሆነ ነው፡፡ እሱ ከጉርብትናም በተጨማሪ የዝምድና ሐቅ እንዲሁም የእስልምና ሐቅ አለው፡፡
ሁለተኛው ጎረቤት ደግሞ የስጋ ዝምድና የሌለን ሙስሊም ጎረቤት ነው፡፡ እሱ ደግሞ ከጉርብትናው ጋር የኢስላም ሐቅ አለው፡፡
ሶስተኛው ጎረቤት ደግሞ ሙስሊም ያልሆነና የስጋ ዝምድናም የሌለን ሲሆን፡ እሱም የጉርብትና ሐቅ አለው፡፡ ለጎረቤታችን መጥፎ ከመስራት መቆጠብ ጀምሮ መልካም ነገር እስከ-ማድረግ ያለው አላህ የሚደው ነገር ነው፡፡ ጌታ አላህም በቅዱስ ቃሉ እንዲህ ያዘናል፡-
"አላህን ተገዙ፤ በርሱም ምንንም አታጋሩ በወላጆችና በቅርብ ዝምድና ባለቤትም፣ በየቲሞች፣ በምስኪኖችም፣ በቅርብ ጎረቤትም፣ በጎን ባልደረባም፣ በመንገደኛም፣ እጆቻችሁም ንብረት ባደረጓቸው (ባሮች)፣ መልካምን (ሥሩ)፤ አላህ ኩራተኛ ጉረኛ የኾነን ሰው አይወድም።" (ሱረቱ-ኒሳእ 36)፡፡
"የቅርብ ጎረቤት" የተባለው ዝምድናም ያለውን ሲሆን "የጎን ባልደረባ" የተባለው ደግሞ ዝምድና የሌለውን ነው፡፡ ዐብዱላህ ኢብኑ-ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንደተናገሩት የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "ጂብሪል (ዐለይሂ ሰላም) በጎረቤት ሐቅ እኔን አደራ! እያለ ከማስታወስ አልተወገደም፡ ምናልባትም ጎረቤት ይወርሳል ብዬ እስካስብ ድረስ" (ቡኻሪና ሙስሊም)፡፡
ዐብዱላህ ኢብኑ-ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንደተናገሩት የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "ጎረቤቱ ተርቦ እያደረ እሱ የሚጠግብ ከሆነ ሙእሚን አይደለም" (ሲልሲለቱ-ሶሒሐህ 149)፡፡
የምእመናን እናት አዒሻህ (ረዲየላሁ ዐንሃ) እንዲህ አለች፡- "የአላህ መልክተኛን፡- እኔ ሁለት ጎረቤቶች አሉኝና ወደማንኛቸው ስጦታ ልጀምር? ስላቸው፡ እሳቸውም፡- ‹‹ላንቺ ቤት ቅርብ ከሆነው›› አሉኝ" (ቡኻሪይ)፡፡
አቢ ሁረይራህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "ሙስሊም ሴቶች ሆይ! ጎረቤት ጎረቤቷን ትንሽ ስጋ ባዘለ አጥንትም ቢሆን እንኳ እንዳትንቅ!" (ቡኻሪና ሙስሊም)፡፡
አቢ-ሹረይሕ (ረዲየላሁ ዐንሁ) የአላህ መልክተኛ እንዲህ ተናገሩ አለ፡- "‹‹በአላህ ይሁንብኝ አላመነም! በአላህ ይሁንብኝ አላመነም! በአላህ ይሁንብኝ አላመነም!›› የአላህ መልክተኛ ሆይ! ማነው ያላመነው? ሲባሉ፡ እሳቸውም፡- ‹‹ጎረቤቱ በንብረታቸው የማያምኑት ሰው›› ብለው መለሱ" (ቡኻሪና ሙስሊም)፡፡
ኢማሙ-ሻፊዒይ (ረሒመሁላህ) የሐዲሡን መልክት ሲናገሩ እንዲህ አሉ፡- "መናገር የፈለገ እንደሆን ቀድሞ ያስብበት፡፡ ጉዳት እንደሌለው ከታየው ይናገረው፡፡ ጉዳት እንዳለው ካወቀ ወይም ከተጠራጠረ ይተወው" ከሰዎች አንደበት የሚወጡ ቃላት በጠቅላላ ይጻፋል (በዕብደት፣በልጅነት፣በዕንቅልፍ ምክንያት የሆኑት ብቻ ሲቀሩ)፡- "ከቃል አንድንም አይናገርም ከርሱ ዘንድ(ቃሉን ለመመዝገብ)ዝግጁ የሆኑ መላእክት ያሉ ቢሆን እንጅ።" (ሱረቱ ቃፍ 18)፡፡ "የእነዚያን አላህ ድኻ ነዉ፥ እኛ ግን ከበርቴዎች ነን ያሉትን ሰዎች ቃል አላህ በእርግጥ ሰማ፤ ያንን ያሉትንና ነቢያትን ያለ ሕግ መግደላቸዉን በእርግጥ እንጽፋለን፤ የእሳትንም ስቃይ ቅመሱ እንላቸዋለን።" (ሱረቱ አለ-ዒምራን 181)፡፡ "በናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትሆኑ፤ የተከበሩ ጸሐፊዎች የሆኑ፤ (ተጠባባቂዎች)" (ሱረቱል ኢንፊጣር 10-11)፡፡
ስለሆነም የምናነገረውን እንጠንቀቅ፡፡ ወይ ሊጠቅመን ወይም ሊጎዳን መሆኑ እስካልቀረ የሚበጀንን መምረጥ ብልኅነት ነው፡፡ ከተናገርን ጌታችንን የሚያስደስት፣ ሰዎችን የሚጠቅምና በሚዛናችን ላይ የሚቀርልንን እንምረጥ፡፡ መልካም ንግግር አስተዋይ ስብዕናን እንጂ ወጪን አይጠይቅምና፡-
አቢ ሁረይራህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደነገረን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "ጸሐይ በምትወጣበት ቀን ሁሉ እያንዳንዱ የሰውነት መገጣጠሚያ ሶደቃ አለበት፡፡ በሁለት ሰዎች መሐል በትክክል መፍረድ ሶደቃ ነው፣ ሰውየውን በመጓጓዣው ላይ እቃውን እንዲጭን ብታግዘው ሶደቃ ነው፣ #መልካም_ንግግር ሶደቃ ነው፣ ወደ ሶላት የምታደርገውው እንቅስቃሴም ሶደቃ ነው፣ የሚያስቸግር ነገር ከመንገድ ማንሳትህም ሶደቃ ነው" (ቡኻሪና ሙስሊም)፡፡
አቢ-ሙሳ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ አለ፡- "የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሆይ! ከሙስሊሞች መሐል በላጩ ማነው? ስላቸው፡ እሳቸውም፡- ‹‹ሙስሊሞች ከምላሱና ከእጁ የተረፉበት ሰው ነው›› ብለው መለሱልኝ" (ቡኻሪና ሙስሊም)፡፡
ሰህል ኢብኑ-ሰዕድ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደተናገረው የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "በሁለቱ አጥንቶቹ መሐል ያለውን (ምላሱን) እና በእግሮቹ መሐል ያለውን (ብልቱን) ለመጠበቅ ቃል ለሚገባልኝ ሰው ጀነትን ዋስ እሆነዋለሁ" (ቡኻሪና ሙስሊም)፡፡
አላህ ካልወፈቀንና መልካም ነገርን መናገር ካልቻልን ዝም እንበል፡፡ ዝምታም በራሱ ኸይር ነውና!! ዐብዱላህ ኢብኑ-ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንደተናገሩት የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- " ‹‹ዝም ያለ ሰው ነጃ ወጣ (ዳነ)›› እሳቸውም በጣም ዝምተኛና ሳቃቸውም መጠነኛ ነበር" (አሕመድ 9/196)፡፡ የምንናገረውን ነገር ቀድመን ሳናውቅ ከተናገርን አደጋው የከፋ ይሆናልና ቆጠብ እንበል፡-
አቢ ሁረይራህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ሲሉ ሰማ፡- "አንድ አላህ ባሪያ አንዲትን ቃል ጥሩ ይሁን መጥፎ ሳያስተውል ይናገርና በሷ ሰበብ ወደ እሳት ምስራቁና ምእራቡ ከሚራራቀው የበለጠ ይጣላል" (ቡኻሪና ሙስሊም)፡፡
ዐብዱላህ ኢብኑ-ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንደተናገሩት የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "አላህን ከማውሳት ውጭ በሆነ ነገር ላይ ንግግር አታብዙ፡፡ አላህን ከማውሳት ውጭ የሆነ ንግግር ማብዛት የልብ ድርቀት ነው፡፡ ልበ ደረቅ ሰው ደግሞ ከአላህ (ራሕመት) የራቀ ነው" (ቲርሚዚይ)፡፡
ዑቅበተ ኢብኑ-ዓሚር (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ አለ፡- "የአላህ መልክተኛ ሆይ! መዳን እንዴት ነው? ስላቸው፡ እሳቸውም፡- ‹‹ምላስህን ተቆጣጠር፣ ቤትህ ይስፋህ፣ ለኃጢአትህ አልቅስ›› አሉኝ" (ቲርሚዚይ)፡፡
ለ. ጎረቤት እናክብር፡-
ጎረቤት የሚባለው ማነው ማነው? የሚለውን ጉዳይ የኢስላም ሊቃውንቶች የገለጹበት መንገድ ያስደነግጣል፡፡ እኛ ጎረቤት ብለን የምንገምተው ከቤታችን ቀጥሎ ያሉት ከ1-4 ቤቶች ላይ ብቻ የተገደበ አድርገን ነበር፡፡ ሐሰኑል በስሪ ረሒመሁላህ) ስለ ጎረቤት ተጠይቀው ሲመልሱ ግን እንዲህ ነበር ያሉት፡- ‹‹ከፊት ለፊቱ እስከ አርባ ቤት ድረስ፣ ከኋላው እስከ አርባ ቤት ድረስ፣ ከቀኝ ጎኑ እስከ አርባ ቤት ድረስ፣ ከግራ ጎኑ እስከ አርባ ቤት ድረስ ያለው ነው›› ብለው መለሱ (ቡኻሪይ አደቡል-ሙፍረድ 109)፡፡ ወይንም ደግሞ እንደ አካባቢው ባሕል መታየት ስላለበት ያ አካባቢ ጎረቤት ብሎ የሚጠራውን ሁሉ ያካተተ በሚለው መጓዙም መልካም ነው፡ ወላሁ አዕለም፡፡ ጎረቤት ሶስት አይነት ነው፡- 1. በኛ ላይ ሶስት ሐቅ (መብት) ያለው፡- 2. በኛ ላይ ሁለት ሐቅ ያለው፡- 3. በኛ ላይ አንድ ሐቅ ያለው፡-
የመጀመሪያው አይነት ጎረቤት፡- ሙስሊምና የስጋ ዘመዳችን የሆነ ነው፡፡ እሱ ከጉርብትናም በተጨማሪ የዝምድና ሐቅ እንዲሁም የእስልምና ሐቅ አለው፡፡
ሁለተኛው ጎረቤት ደግሞ የስጋ ዝምድና የሌለን ሙስሊም ጎረቤት ነው፡፡ እሱ ደግሞ ከጉርብትናው ጋር የኢስላም ሐቅ አለው፡፡
ሶስተኛው ጎረቤት ደግሞ ሙስሊም ያልሆነና የስጋ ዝምድናም የሌለን ሲሆን፡ እሱም የጉርብትና ሐቅ አለው፡፡ ለጎረቤታችን መጥፎ ከመስራት መቆጠብ ጀምሮ መልካም ነገር እስከ-ማድረግ ያለው አላህ የሚደው ነገር ነው፡፡ ጌታ አላህም በቅዱስ ቃሉ እንዲህ ያዘናል፡-
"አላህን ተገዙ፤ በርሱም ምንንም አታጋሩ በወላጆችና በቅርብ ዝምድና ባለቤትም፣ በየቲሞች፣ በምስኪኖችም፣ በቅርብ ጎረቤትም፣ በጎን ባልደረባም፣ በመንገደኛም፣ እጆቻችሁም ንብረት ባደረጓቸው (ባሮች)፣ መልካምን (ሥሩ)፤ አላህ ኩራተኛ ጉረኛ የኾነን ሰው አይወድም።" (ሱረቱ-ኒሳእ 36)፡፡
"የቅርብ ጎረቤት" የተባለው ዝምድናም ያለውን ሲሆን "የጎን ባልደረባ" የተባለው ደግሞ ዝምድና የሌለውን ነው፡፡ ዐብዱላህ ኢብኑ-ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንደተናገሩት የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "ጂብሪል (ዐለይሂ ሰላም) በጎረቤት ሐቅ እኔን አደራ! እያለ ከማስታወስ አልተወገደም፡ ምናልባትም ጎረቤት ይወርሳል ብዬ እስካስብ ድረስ" (ቡኻሪና ሙስሊም)፡፡
ዐብዱላህ ኢብኑ-ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንደተናገሩት የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "ጎረቤቱ ተርቦ እያደረ እሱ የሚጠግብ ከሆነ ሙእሚን አይደለም" (ሲልሲለቱ-ሶሒሐህ 149)፡፡
የምእመናን እናት አዒሻህ (ረዲየላሁ ዐንሃ) እንዲህ አለች፡- "የአላህ መልክተኛን፡- እኔ ሁለት ጎረቤቶች አሉኝና ወደማንኛቸው ስጦታ ልጀምር? ስላቸው፡ እሳቸውም፡- ‹‹ላንቺ ቤት ቅርብ ከሆነው›› አሉኝ" (ቡኻሪይ)፡፡
አቢ ሁረይራህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "ሙስሊም ሴቶች ሆይ! ጎረቤት ጎረቤቷን ትንሽ ስጋ ባዘለ አጥንትም ቢሆን እንኳ እንዳትንቅ!" (ቡኻሪና ሙስሊም)፡፡
አቢ-ሹረይሕ (ረዲየላሁ ዐንሁ) የአላህ መልክተኛ እንዲህ ተናገሩ አለ፡- "‹‹በአላህ ይሁንብኝ አላመነም! በአላህ ይሁንብኝ አላመነም! በአላህ ይሁንብኝ አላመነም!›› የአላህ መልክተኛ ሆይ! ማነው ያላመነው? ሲባሉ፡ እሳቸውም፡- ‹‹ጎረቤቱ በንብረታቸው የማያምኑት ሰው›› ብለው መለሱ" (ቡኻሪና ሙስሊም)፡፡
👍2