♥ቅዱስ ብስንድዮስ ጻድቅ ♥
ቅዱስ_ብስንድዮስ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ድንቅ ሥራ
ከሠሩት እንደ አንዱ ሆኖ ይዘከራል:: ቅዱሱ ግብፃዊ
ሲሆን በልጅነቱ ወደ ትምሕርት ቤት ገብቶ ቅዱሳት
መጻሕፍትን ተምሯል:: የሚገርመው የብሉይም ሆነ
የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትን በሙሉ ያጠናቸው በቃሉ ነበር::
በርግጥ ይሕንን ማድረግ የቻሉ በርካታ የሃገራችን
ሊቃውንት ዘንድሮም አሉ:: ልዩነቱ ግን ወዲህ ነው:: ቅዱስ
ብስንድዮስ መጻሕፍቱን ያጠናቸው ለሕይወት እንጂ ለእውቀት አልነበረምና ሁሌም ነግቶ እስከሚመሽ እያንዳንዱን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል እያጣጣመ ይጸልይ ነበር:: ይሕንን ሲያደርግ ደግሞ
ባጭር ታጥቆ:
ጫማውን አውልቆ:
በባዶ ሆዱ ቁሞ ነው::
ታዲያ እያንዳንዱን የመጽሐፍ ክፍል ሲጸልይ #ነቢይ
ቢሆን #ሐዋርያ ወደ እርሱ ይወርድለት ነበር:: ለምሳሌ
#ዘፍጥረትን ሲጸልይ ሊቀ ነቢያት #ሙሴ ይመጣና ከፊቱ ተቀምጦ ይሰማዋል:: #ትንቢተ_ኢሳይያስ ላይ ሲደርስ
#ኢሳይያስ : #ወንጌለ_ማቴዎስ ላይ ሲደርስ
#ቅዱስ_ማቴዎስ ይመጡና ደስ እያላቸው ያደምጡት
ነበር:: አንዱ ነቢይ: ወይ ሐዋርያ ሲወጣ ቅዱስ ብስንድዮስን
ባርኮ ሌላኛውን ተክቶ ነው:: በዚህ ምክንያት የቅዱሱ ሕይወት በምድር እያለ ሰማያዊ ሆነ:
81ዱን አሥራው መጻሕፍት የጻፉ ቅዱሳንን ለማየት በቃ:
በእጆቻቸውም ተባረከ::
የቅዱስ ብስንድዮስ ቀጣይ የሕይወቱ ተግባር ብሕትውና
ሆነ:: ዓለምንና ግሳንግሷን ትቶም ወደ በርሃ መነነ::
በአጽንዖ በዓት: በጾምና በጸሎት:
በትሕርምት ተጋደለ:: በየደረሰበት ቦታ ሁሉ እግዚአብሔር
በእጆቹ ድንቅ ተአምር ይሠራ ነበር:: ብዙ ድውያንን ፈወሰ:
አጋንንትንም ከአካባቢው አሳደደ::
በነዚህ ሁሉ ጊዜያት ግን ስዕለት ስላለበት ሴቶችን ላለማየት ይጠነቀቅ ነበር:: በሆድ ሕመም ትሰቃይ የነበረችና ጥሪቷን በመድኃኒት የጨረሰች አንዲት ሴት ስለ ቅዱሱ ዝና ትሰማለች:: ችግሩ ግን እርሱ ከውዳሴ ከንቱና
ከሴት የሚርቅ ነውና እንዴት ብላ ታግኘው? አንድ ቀን ከበዓቱ አካባቢ ተደብቃ ውላ ሲመጣ የልብሶቹን ዘርፍ ለመንካት በእምነት አሰበች:: ልክ ከበዓቱ ሲዘልቅ # ስሉጥ (ፈጣን) ነበርና ገና እንዳያት ሩጦ አመለጣት:: እንዳትከተለው ድውይ ናትና
አልቻለችም::አዝና ዝቅ ስትል ግን የረገጠውን ኮቲ ተመለከተች:: በፍጹም ልቧ : በእምነት "የጻድቁ አምላክ ማረኝ" ብላ ከአፈሩ ቆንጥራ በላች:: ደቂቃ አልቆየችም:: ፈጥና ከደዌዋ ዳነች:: እንደ እንቦሳ እየዘለለች ወደ ከተማ ሔዳ ተአምሩን ተናገረች:: ከእነዚህ ዘመናት በሁዋላ በእግዚአብሔር ፈቃድ
#ቅፍጥ (Qift) በምትባል ሃገር ዽዽስናን (እረኝነትን) ተሹሟል:: ወደ ከተማ ሲገባ የቀደመ ተጋድሎውን ቸል አላለም:: ይልቁኑ ይተጋ ነበር እንጂ:: ከብቃት መዓርግ
ደርሷልና ሲቀድስ ጌታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስን በገሃድ
ያየው : ሠራዊተ መላእክትም ይከቡት ነበር:: ሕዝቡ ሊቆርቡ ሲመጡ የእያንዳንዱ ኃጢአት
በግንባራቸው ተጽፎ ይታየው ነበር:: የበቁትን እያቀበለ :
ያልበቁትን እየመከረና ንስሃ እየሰጠ ይመልሳቸዋል::
እንዲሕ በጽድቅ : በሐዋርያዊ አገልግሎትና በንጽሕና
ተመላልሶ ቅዱስ ብስንድዮስ በዚህች ቀን ዐርፏል:: ቅዱስ ብስንድዮስ ካረፈ በሁዋላ ደቀ መዝሙሩ ከመግነዙ ጥቂት ቆርጦ አስቀርቶ ብዙ ድውያንን
ፈውሶበታል::
♥ቸር አምላክ ለአባቶቻችን የሰጠውን ጸጋ ለእኛ
ለባሮቹም አይንሳን:: ከቅዱሱ በረከትም ያድለን::♥
ቅዱስ_ብስንድዮስ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ድንቅ ሥራ
ከሠሩት እንደ አንዱ ሆኖ ይዘከራል:: ቅዱሱ ግብፃዊ
ሲሆን በልጅነቱ ወደ ትምሕርት ቤት ገብቶ ቅዱሳት
መጻሕፍትን ተምሯል:: የሚገርመው የብሉይም ሆነ
የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትን በሙሉ ያጠናቸው በቃሉ ነበር::
በርግጥ ይሕንን ማድረግ የቻሉ በርካታ የሃገራችን
ሊቃውንት ዘንድሮም አሉ:: ልዩነቱ ግን ወዲህ ነው:: ቅዱስ
ብስንድዮስ መጻሕፍቱን ያጠናቸው ለሕይወት እንጂ ለእውቀት አልነበረምና ሁሌም ነግቶ እስከሚመሽ እያንዳንዱን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል እያጣጣመ ይጸልይ ነበር:: ይሕንን ሲያደርግ ደግሞ
ባጭር ታጥቆ:
ጫማውን አውልቆ:
በባዶ ሆዱ ቁሞ ነው::
ታዲያ እያንዳንዱን የመጽሐፍ ክፍል ሲጸልይ #ነቢይ
ቢሆን #ሐዋርያ ወደ እርሱ ይወርድለት ነበር:: ለምሳሌ
#ዘፍጥረትን ሲጸልይ ሊቀ ነቢያት #ሙሴ ይመጣና ከፊቱ ተቀምጦ ይሰማዋል:: #ትንቢተ_ኢሳይያስ ላይ ሲደርስ
#ኢሳይያስ : #ወንጌለ_ማቴዎስ ላይ ሲደርስ
#ቅዱስ_ማቴዎስ ይመጡና ደስ እያላቸው ያደምጡት
ነበር:: አንዱ ነቢይ: ወይ ሐዋርያ ሲወጣ ቅዱስ ብስንድዮስን
ባርኮ ሌላኛውን ተክቶ ነው:: በዚህ ምክንያት የቅዱሱ ሕይወት በምድር እያለ ሰማያዊ ሆነ:
81ዱን አሥራው መጻሕፍት የጻፉ ቅዱሳንን ለማየት በቃ:
በእጆቻቸውም ተባረከ::
የቅዱስ ብስንድዮስ ቀጣይ የሕይወቱ ተግባር ብሕትውና
ሆነ:: ዓለምንና ግሳንግሷን ትቶም ወደ በርሃ መነነ::
በአጽንዖ በዓት: በጾምና በጸሎት:
በትሕርምት ተጋደለ:: በየደረሰበት ቦታ ሁሉ እግዚአብሔር
በእጆቹ ድንቅ ተአምር ይሠራ ነበር:: ብዙ ድውያንን ፈወሰ:
አጋንንትንም ከአካባቢው አሳደደ::
በነዚህ ሁሉ ጊዜያት ግን ስዕለት ስላለበት ሴቶችን ላለማየት ይጠነቀቅ ነበር:: በሆድ ሕመም ትሰቃይ የነበረችና ጥሪቷን በመድኃኒት የጨረሰች አንዲት ሴት ስለ ቅዱሱ ዝና ትሰማለች:: ችግሩ ግን እርሱ ከውዳሴ ከንቱና
ከሴት የሚርቅ ነውና እንዴት ብላ ታግኘው? አንድ ቀን ከበዓቱ አካባቢ ተደብቃ ውላ ሲመጣ የልብሶቹን ዘርፍ ለመንካት በእምነት አሰበች:: ልክ ከበዓቱ ሲዘልቅ # ስሉጥ (ፈጣን) ነበርና ገና እንዳያት ሩጦ አመለጣት:: እንዳትከተለው ድውይ ናትና
አልቻለችም::አዝና ዝቅ ስትል ግን የረገጠውን ኮቲ ተመለከተች:: በፍጹም ልቧ : በእምነት "የጻድቁ አምላክ ማረኝ" ብላ ከአፈሩ ቆንጥራ በላች:: ደቂቃ አልቆየችም:: ፈጥና ከደዌዋ ዳነች:: እንደ እንቦሳ እየዘለለች ወደ ከተማ ሔዳ ተአምሩን ተናገረች:: ከእነዚህ ዘመናት በሁዋላ በእግዚአብሔር ፈቃድ
#ቅፍጥ (Qift) በምትባል ሃገር ዽዽስናን (እረኝነትን) ተሹሟል:: ወደ ከተማ ሲገባ የቀደመ ተጋድሎውን ቸል አላለም:: ይልቁኑ ይተጋ ነበር እንጂ:: ከብቃት መዓርግ
ደርሷልና ሲቀድስ ጌታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስን በገሃድ
ያየው : ሠራዊተ መላእክትም ይከቡት ነበር:: ሕዝቡ ሊቆርቡ ሲመጡ የእያንዳንዱ ኃጢአት
በግንባራቸው ተጽፎ ይታየው ነበር:: የበቁትን እያቀበለ :
ያልበቁትን እየመከረና ንስሃ እየሰጠ ይመልሳቸዋል::
እንዲሕ በጽድቅ : በሐዋርያዊ አገልግሎትና በንጽሕና
ተመላልሶ ቅዱስ ብስንድዮስ በዚህች ቀን ዐርፏል:: ቅዱስ ብስንድዮስ ካረፈ በሁዋላ ደቀ መዝሙሩ ከመግነዙ ጥቂት ቆርጦ አስቀርቶ ብዙ ድውያንን
ፈውሶበታል::
♥ቸር አምላክ ለአባቶቻችን የሰጠውን ጸጋ ለእኛ
ለባሮቹም አይንሳን:: ከቅዱሱ በረከትም ያድለን::♥
💚💛ቅድስት አውፎምያ ሰማዕት💛❤️
እናታችን #ቅድስት_አውፎምያ (ስሟ አፎምያ አይደለም:: በስሕተት "ው" መካከል ላይ የገባች እንዳይመስልዎ:: እስመ ከመዝ ስማ-ስሟ እንዲሁ ነው የሚጠራው) በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ከነበሩ ወጣት ክርስቲያኖች አንዷ ናት:: ገና ከልጅነቷ ልቧ በፍቅረ ክርስቶስ የተነደፈ ነበር::
በዚህም ምክንያት ራሷን በጾምና በጸሎት ወስና ትኖር ነበር:: እድሜዋ ገና በአሥራዎቹ ቢሆንም በመንኖ ጥሪት መኖር ምርጫዋ ነበር:: ሊቃውንት አበው ከሰማዕትነቷ ደርበው "ጻድቅት አውፎምያ" እያሉም ይጠሯታል::
አንድ ቀን ግን መንገድ ወጥታ ነበርና ክርስቲያኖች ሲሰቃዩ ተመለከተች:: ምንም ጥፋት ሳይገኝባቸው ክርስቶስን ስላመለኩ ብቻ ይሙት በቃ ተፈርዶባቸው ሊገደሉ እየተወሰዱ ነበር:: አሕዛብ ግብራቸው የአውሬ ነውና ርሕራሔ የላቸውም:: ሰማዕታቱ ደማቸው በየመንገዱ እየፈሰሰ ጥቁር ሰንሰለት በአንገታቸው: በእጃቸውና በእግራቸው ላይ አድርገው ይጐትቷቸው ነበር::
ቅድስት አውፎምያ የተደረገውን ሁሉ ተመልክታ አምርራ አለቀሰች:: ፈጠን ብላም ወደ መኮንኑ ቀርባ ገሰጸችው::
"አንተ አእምሮ የጎደለህ! እንዴት ክርስቲያኖችን እንዲህ ታሰቃያለህ? አምላካቸው #ጌታ_ክርስቶስ ታጋሽ ባይሆን ኑሮ በቅጽበት ከገጸ ምድር ባጠፋህ ነበር" አለችው::
በድፍረቷ የተገረመው መኮንኑ "አንቺስ ማንን ታመልኪያለሽ?" ሲል ጠየቃት:: እርሷም "ሰማይና ምድርን የፈጠረውን: ስለ እኛ ሲል በቀራንዮ አንባ የተሠዋውን #ኢየሱስ ክርስቶስን አመልካለሁ" ስትል መለሰችለት:: በዚያች ሰዓት የመኮንኑ ቁጣ በቅድስቷ ላይ ነደደ::
ነገር ግን ቁጣውን ከቁም ነገር አልቆጠረችውምና እንዲያሰቃዩዋት አዘዘ:: ወታደሮቹ ሥጋዋን በብዙ አሰቃዩ:: ብላቴናዋ አውፎምያ ግን ጽንዕት ናትና አልቻሏትም:: በመጨረሻ በእሳት ተቃጥላ ትሞት ዘንድ ተፈረደባት::
እሳቱ ከመሬት ከፍ ባለ ጊዜ ወደ ውስጥ ወረወሯት:: በእሳቱ መካከል ቁማ ለረዥም ጊዜ ጸለየች:: ከዚያም ነፍሷን አሳልፋ ሰጠች:: ምዕመናን በክብር ገንዘው ቀብረዋታል::
From dn yordanos abebe
@senkesar @senkesar
እናታችን #ቅድስት_አውፎምያ (ስሟ አፎምያ አይደለም:: በስሕተት "ው" መካከል ላይ የገባች እንዳይመስልዎ:: እስመ ከመዝ ስማ-ስሟ እንዲሁ ነው የሚጠራው) በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ከነበሩ ወጣት ክርስቲያኖች አንዷ ናት:: ገና ከልጅነቷ ልቧ በፍቅረ ክርስቶስ የተነደፈ ነበር::
በዚህም ምክንያት ራሷን በጾምና በጸሎት ወስና ትኖር ነበር:: እድሜዋ ገና በአሥራዎቹ ቢሆንም በመንኖ ጥሪት መኖር ምርጫዋ ነበር:: ሊቃውንት አበው ከሰማዕትነቷ ደርበው "ጻድቅት አውፎምያ" እያሉም ይጠሯታል::
አንድ ቀን ግን መንገድ ወጥታ ነበርና ክርስቲያኖች ሲሰቃዩ ተመለከተች:: ምንም ጥፋት ሳይገኝባቸው ክርስቶስን ስላመለኩ ብቻ ይሙት በቃ ተፈርዶባቸው ሊገደሉ እየተወሰዱ ነበር:: አሕዛብ ግብራቸው የአውሬ ነውና ርሕራሔ የላቸውም:: ሰማዕታቱ ደማቸው በየመንገዱ እየፈሰሰ ጥቁር ሰንሰለት በአንገታቸው: በእጃቸውና በእግራቸው ላይ አድርገው ይጐትቷቸው ነበር::
ቅድስት አውፎምያ የተደረገውን ሁሉ ተመልክታ አምርራ አለቀሰች:: ፈጠን ብላም ወደ መኮንኑ ቀርባ ገሰጸችው::
"አንተ አእምሮ የጎደለህ! እንዴት ክርስቲያኖችን እንዲህ ታሰቃያለህ? አምላካቸው #ጌታ_ክርስቶስ ታጋሽ ባይሆን ኑሮ በቅጽበት ከገጸ ምድር ባጠፋህ ነበር" አለችው::
በድፍረቷ የተገረመው መኮንኑ "አንቺስ ማንን ታመልኪያለሽ?" ሲል ጠየቃት:: እርሷም "ሰማይና ምድርን የፈጠረውን: ስለ እኛ ሲል በቀራንዮ አንባ የተሠዋውን #ኢየሱስ ክርስቶስን አመልካለሁ" ስትል መለሰችለት:: በዚያች ሰዓት የመኮንኑ ቁጣ በቅድስቷ ላይ ነደደ::
ነገር ግን ቁጣውን ከቁም ነገር አልቆጠረችውምና እንዲያሰቃዩዋት አዘዘ:: ወታደሮቹ ሥጋዋን በብዙ አሰቃዩ:: ብላቴናዋ አውፎምያ ግን ጽንዕት ናትና አልቻሏትም:: በመጨረሻ በእሳት ተቃጥላ ትሞት ዘንድ ተፈረደባት::
እሳቱ ከመሬት ከፍ ባለ ጊዜ ወደ ውስጥ ወረወሯት:: በእሳቱ መካከል ቁማ ለረዥም ጊዜ ጸለየች:: ከዚያም ነፍሷን አሳልፋ ሰጠች:: ምዕመናን በክብር ገንዘው ቀብረዋታል::
From dn yordanos abebe
@senkesar @senkesar