♥#አባታችን_ቅዱስ_አብርሃም♥
#የሃይማኖት-የደግነት-የምጽዋት-የፍቅር አባት የሆነው
#አብርሃም ደጉ በዚህች ቀን ይታሠባል:: በቤተ ክርስቲያን
ትውፊት መሠረት የአብርሃም አባቱ ታራ ጣዖትን ይጠርብና
ይሸጥ ነበር:: ሽጦ ገንዘብ የሚያመጣለት ደግሞ ልጁ
አብርሃም ነበር::
በዚያ ወራት አብርሃም እውነተኛውን አምላክ ፍለጋ ገብቶ
ነበር:: አንድ ቀን ጣዖቱን ሊሸጥ ወደ ገበያ እየሔደ
የተሸከመውን እንጨት ይመራመረው ገባ:: "አሁን ይሔ ምኑ
ነው አምላክ!" እያለም ያደንቅ ገባ:: መንገድ ላይም ደክሞት
ካረፈበት "ለምን አልጠይቀውም" በሚል አናገረው::
"እርቦኛል አብላኝ" አለው:: መልስ የለም:: "እሺ አጠጣኝ"
አለው:: አሁንም ያው ነው:: "ባይሆን እሺ አጫውተኝ" አለው::
ጣዖቱ ተራ እንጨት ነውና መልሱ ዝምታ ነበር:: ከዚያ ተነስቶ
ወደ ገበያው ሲደርስ "ዐይን እያለው የማያይ: ጀሮ እያለው
የማይሰማ አምላክ የሚገዛ" እያለ ይጮህ ጀመር::
ይህን ሲሰሙ አንዳንዶቹ "የታራ ልጅ አብዶ" ሲሉ ሌሎቹ
ደግሞ "እሱ ያቀለለውን ማን ይገዛዋል" ብለውት ሔደዋል::
ከገበያ ሲመለስም ጣዖቱን ተመልክቶ አብርሃም እንዲህ አለ::
"አንተ ቀድሞውን በዕለተ ሠሉስ የተፈጠርክ ዕፅ ነህ" ብሎ
ሰባበረው::
ወደ ቤቱ ሲመለስም ሁሉንም ጣዖታት ሠባበራቸው:: ይህ
የተደረገው ከ2,000 ዓመታት በፊት በዚህች ቀን ነው::
የመንግስተ ሰማያት አበጋዝ: የእግዚአብሔር ወዳጅ አባታችን
አብርሃም በመጨረሻው በውሃ: በነፋስ: በእሳትና በፀሐይ
ተመራምሮ ፈጣሪውን አግኝቷል::
#የሃይማኖት-የደግነት-የምጽዋት-የፍቅር አባት የሆነው
#አብርሃም ደጉ በዚህች ቀን ይታሠባል:: በቤተ ክርስቲያን
ትውፊት መሠረት የአብርሃም አባቱ ታራ ጣዖትን ይጠርብና
ይሸጥ ነበር:: ሽጦ ገንዘብ የሚያመጣለት ደግሞ ልጁ
አብርሃም ነበር::
በዚያ ወራት አብርሃም እውነተኛውን አምላክ ፍለጋ ገብቶ
ነበር:: አንድ ቀን ጣዖቱን ሊሸጥ ወደ ገበያ እየሔደ
የተሸከመውን እንጨት ይመራመረው ገባ:: "አሁን ይሔ ምኑ
ነው አምላክ!" እያለም ያደንቅ ገባ:: መንገድ ላይም ደክሞት
ካረፈበት "ለምን አልጠይቀውም" በሚል አናገረው::
"እርቦኛል አብላኝ" አለው:: መልስ የለም:: "እሺ አጠጣኝ"
አለው:: አሁንም ያው ነው:: "ባይሆን እሺ አጫውተኝ" አለው::
ጣዖቱ ተራ እንጨት ነውና መልሱ ዝምታ ነበር:: ከዚያ ተነስቶ
ወደ ገበያው ሲደርስ "ዐይን እያለው የማያይ: ጀሮ እያለው
የማይሰማ አምላክ የሚገዛ" እያለ ይጮህ ጀመር::
ይህን ሲሰሙ አንዳንዶቹ "የታራ ልጅ አብዶ" ሲሉ ሌሎቹ
ደግሞ "እሱ ያቀለለውን ማን ይገዛዋል" ብለውት ሔደዋል::
ከገበያ ሲመለስም ጣዖቱን ተመልክቶ አብርሃም እንዲህ አለ::
"አንተ ቀድሞውን በዕለተ ሠሉስ የተፈጠርክ ዕፅ ነህ" ብሎ
ሰባበረው::
ወደ ቤቱ ሲመለስም ሁሉንም ጣዖታት ሠባበራቸው:: ይህ
የተደረገው ከ2,000 ዓመታት በፊት በዚህች ቀን ነው::
የመንግስተ ሰማያት አበጋዝ: የእግዚአብሔር ወዳጅ አባታችን
አብርሃም በመጨረሻው በውሃ: በነፋስ: በእሳትና በፀሐይ
ተመራምሮ ፈጣሪውን አግኝቷል::