♥#አቡነ_ሰላማ_ካልዕ♥
እኒህ ታላቅ ደግ ሰው የነበሩት በሃገራችን ኢትዮዽያ ከ1340
እስከ 1380 ዓ/ም ነው:: በትውልድ ግብጻዊ ቢሆኑም
ለኢትዮዽያ ቤተ ክርስቲያን ብዙ ውለታን ውለዋል:: በዘመኑ
ዻዻስ ሁነው ቢመጡም እንደ ሌሎቹ ዻዻሳት በቤተ መንግስት
አካባቢ ሥራ ፈትተው መቀመጥን አልፈለጉም::
ወዲያው እንደ መጡ የግዕዝ ልሳንን ልቅም አድርገው
ተማሩ:: ቀጥለው ኢትዮዽያውያን ሊቃውንትን ሰብስበው
ቅዱሳት መጻሕፍትን ይተረጉሙ ገቡ:: አሥራው መጻሕፍትን
(81ዱን) ጨምሮ ብዙ መሠረታዊ መጻሕፍትን መተርጐም
ችለዋል::
ይህም ሥራ አድካሚ በመሆኑ ከ30 ዓመታት በላይ ጊዜን
ወስዷል:: ከተረጐሟቸው መጻሕፍትም:-
* #ስንክሳር
* #ግብረ_ሕማማት
* #ላሃ_ማርያም
* #ፊልክስዩስ (መጽሐፈ መነኮሳት)
* #መጽሐፈ_ግንዘት
*ድርሳን ዘቅዱስ #ያዕቆብ_ዘሥሩግ . . . ይጠቀሳሉ::
#አቡነ_ሰላማ በስብከተ ወንጌል አገልግሎታቸውና በገዳማዊ
ሕይወታቸው ይታወቁ ነበር:: በተጨማሪም በየቦታው እየዞሩ
ይናዝዙ: ያጠምቁም ነበር:: በወቅቱ ልክ እንደ ስማቸው ሰላም
እንዲሰፍን ይተጉ ነበር:: መሣፍንቱን: ነገሥታቱን እያስታረቁ
ለቤተ ክርስቲያን በአንድነት እንዲቆሙ አድርገዋል::
ጻድቁ አቡነ ፊልዾስን ጨምሮ ቅዱሳንን ገንዘውም ቀብረዋል::
በቀደመ ስማቸው #አባ_ፊቅጦር የሚባሉት ካልዕ (2ኛው)
ሰላማ በ1380 ዓ/ም ከ40 ዓመታት ትጋት በሁዋላ ዐርፈዋል::
ሲጠሩም:-
* #መተርጉም (መጻሕፍትን የተረጐሙ)
* #ብርሃነ_አዜብ (የኢትዮዽያ ብርሃን)
* #መጋቤ_ሃይማኖት ተብለው ነው::
✿አምላከ ቅዱሳን ወዳጆቹን እንዳጸናቸው ያጽናን::
ከበረከታቸውም ያድለን::
እኒህ ታላቅ ደግ ሰው የነበሩት በሃገራችን ኢትዮዽያ ከ1340
እስከ 1380 ዓ/ም ነው:: በትውልድ ግብጻዊ ቢሆኑም
ለኢትዮዽያ ቤተ ክርስቲያን ብዙ ውለታን ውለዋል:: በዘመኑ
ዻዻስ ሁነው ቢመጡም እንደ ሌሎቹ ዻዻሳት በቤተ መንግስት
አካባቢ ሥራ ፈትተው መቀመጥን አልፈለጉም::
ወዲያው እንደ መጡ የግዕዝ ልሳንን ልቅም አድርገው
ተማሩ:: ቀጥለው ኢትዮዽያውያን ሊቃውንትን ሰብስበው
ቅዱሳት መጻሕፍትን ይተረጉሙ ገቡ:: አሥራው መጻሕፍትን
(81ዱን) ጨምሮ ብዙ መሠረታዊ መጻሕፍትን መተርጐም
ችለዋል::
ይህም ሥራ አድካሚ በመሆኑ ከ30 ዓመታት በላይ ጊዜን
ወስዷል:: ከተረጐሟቸው መጻሕፍትም:-
* #ስንክሳር
* #ግብረ_ሕማማት
* #ላሃ_ማርያም
* #ፊልክስዩስ (መጽሐፈ መነኮሳት)
* #መጽሐፈ_ግንዘት
*ድርሳን ዘቅዱስ #ያዕቆብ_ዘሥሩግ . . . ይጠቀሳሉ::
#አቡነ_ሰላማ በስብከተ ወንጌል አገልግሎታቸውና በገዳማዊ
ሕይወታቸው ይታወቁ ነበር:: በተጨማሪም በየቦታው እየዞሩ
ይናዝዙ: ያጠምቁም ነበር:: በወቅቱ ልክ እንደ ስማቸው ሰላም
እንዲሰፍን ይተጉ ነበር:: መሣፍንቱን: ነገሥታቱን እያስታረቁ
ለቤተ ክርስቲያን በአንድነት እንዲቆሙ አድርገዋል::
ጻድቁ አቡነ ፊልዾስን ጨምሮ ቅዱሳንን ገንዘውም ቀብረዋል::
በቀደመ ስማቸው #አባ_ፊቅጦር የሚባሉት ካልዕ (2ኛው)
ሰላማ በ1380 ዓ/ም ከ40 ዓመታት ትጋት በሁዋላ ዐርፈዋል::
ሲጠሩም:-
* #መተርጉም (መጻሕፍትን የተረጐሙ)
* #ብርሃነ_አዜብ (የኢትዮዽያ ብርሃን)
* #መጋቤ_ሃይማኖት ተብለው ነው::
✿አምላከ ቅዱሳን ወዳጆቹን እንዳጸናቸው ያጽናን::
ከበረከታቸውም ያድለን::