ስንክሳር
7.32K subscribers
825 photos
4 videos
37 files
237 links
በስንክሳር channal ስንክሳሩ ተገልጦ ቅዱሳን ይዘከራሉ፣ ወቅቱን የጠበቁ መረጃዎችን ያገኛሉ፡፡ ይከታተሉን!
Download Telegram
#አቡነ_ሰላማ_ካልዕ
እኒህ ታላቅ ደግ ሰው የነበሩት በሃገራችን ኢትዮዽያ ከ1340
እስከ 1380 ዓ/ም ነው:: በትውልድ ግብጻዊ ቢሆኑም
ለኢትዮዽያ ቤተ ክርስቲያን ብዙ ውለታን ውለዋል:: በዘመኑ
ዻዻስ ሁነው ቢመጡም እንደ ሌሎቹ ዻዻሳት በቤተ መንግስት
አካባቢ ሥራ ፈትተው መቀመጥን አልፈለጉም::
ወዲያው እንደ መጡ የግዕዝ ልሳንን ልቅም አድርገው
ተማሩ:: ቀጥለው ኢትዮዽያውያን ሊቃውንትን ሰብስበው
ቅዱሳት መጻሕፍትን ይተረጉሙ ገቡ:: አሥራው መጻሕፍትን
(81ዱን) ጨምሮ ብዙ መሠረታዊ መጻሕፍትን መተርጐም
ችለዋል::
ይህም ሥራ አድካሚ በመሆኑ ከ30 ዓመታት በላይ ጊዜን
ወስዷል:: ከተረጐሟቸው መጻሕፍትም:-
* #ስንክሳር
* #ግብረ_ሕማማት
* #ላሃ_ማርያም
* #ፊልክስዩስ (መጽሐፈ መነኮሳት)
* #መጽሐፈ_ግንዘት
*ድርሳን ዘቅዱስ #ያዕቆብ_ዘሥሩግ . . . ይጠቀሳሉ::
#አቡነ_ሰላማ በስብከተ ወንጌል አገልግሎታቸውና በገዳማዊ
ሕይወታቸው ይታወቁ ነበር:: በተጨማሪም በየቦታው እየዞሩ
ይናዝዙ: ያጠምቁም ነበር:: በወቅቱ ልክ እንደ ስማቸው ሰላም
እንዲሰፍን ይተጉ ነበር:: መሣፍንቱን: ነገሥታቱን እያስታረቁ
ለቤተ ክርስቲያን በአንድነት እንዲቆሙ አድርገዋል::
ጻድቁ አቡነ ፊልዾስን ጨምሮ ቅዱሳንን ገንዘውም ቀብረዋል::
በቀደመ ስማቸው #አባ_ፊቅጦር የሚባሉት ካልዕ (2ኛው)
ሰላማ በ1380 ዓ/ም ከ40 ዓመታት ትጋት በሁዋላ ዐርፈዋል::
ሲጠሩም:-
* #መተርጉም (መጻሕፍትን የተረጐሙ)
* #ብርሃነ_አዜብ (የኢትዮዽያ ብርሃን)
* #መጋቤ_ሃይማኖት ተብለው ነው::
✿አምላከ ቅዱሳን ወዳጆቹን እንዳጸናቸው ያጽናን::
ከበረከታቸውም ያድለን::
💚💛#አቡነ_ሰላማ_ከሣቴ_ብርሃን💛❤️
ቅዱሱ በትውልዳቸው ግሪካዊ ቢሆኑም ሶርያ
አካባቢ እንዳደጉ ይታመናል:: በቀደመ ስማቸው ፍሬምናጦስ
የሚባሉት አቡነ ሰላማ ወደ ኢትዮዽያ የመጡት በአደጋ
ምክንያት (በድንገት) ቢመስልም ውስጡ ግን ፈቃደ
እግዚአብሔር ነበረበት::
በድንበር ጠባቂዎች (በአደጋ ጣዮች) ከባልንጀራቸው
ኤዴስዮስ ጋር ተይዘው ወደ አክሱም የመጡት በንጉሥ ታዜር
(አይዛና) እና በሚስቱ ሶፍያ (አሕየዋ) ዘመን ነው:: ጊዜው
በውል ባይታወቅም በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው::
ፍሬምናጦስ ምንም የመጡበት ዓላማ ስብከተ ወንጌል
ባይሆንም በአክሱም ቤተ መንግስት አካባቢ ይሰበኩ ነበር::
ያን ጊዜ በጃንደረባው ቅዱስ ባኮስ የተቀጣጠለው የክርስትና
ችቦ ውስጥ ውስጡን በሃገሪቱ ነበረና ፍሬምናጦስ
አልተቸገሩም:: በተለይ ሕጻናቱን (ኢዛናና ሳይዛናን) ገና
ከልጅነት ስላስተማሯቸው ነገሮች የተሳኩ ሆኑ::
ልክ ንጉሥ ታዜር እንደ ሞተ ሁለቱ ሕጻናት በመንበሩ
ተቀመጡ:: ፍሬምናጦስንም ወደ ግብፅ ዻዻስና ጥምቀት
ከመጻሕፍት ጋር እንዲመጣላቸው ላኩ:: ሐዋርያዊ ቅዱስ
አትናቴዎስም ፍሬምናጦስን "ሰላማ" ብሎ ሰይሞ : በዽዽስና
: በንዋየ ቅድሳትና በመጻሕፍት ሸልሞ መለሳቸው::
አቡነ ሰላማ ወደ ኢትዮዽያ እንደተመለሱ ከነገሥታቱ ጀምረው
ለሕዝቡ ጥምቀትን አደሉ:: ኢዛናና ሳይዛናም አብርሃ (አበራ)
እና አጽብሃ (አነጋ) ተብለው ስማቸው ተደነገለ:: ከዚያ
በሁዋላ ድንቅ በሚሆን አገልግሎት ነገሥታቱ : ዻዻሱ
ሰላማና ሊቀ ካህናቱ እንበረም ለክርስትና መስፋፋት በጋራ
ሠርተዋል::

የአቡነ ሰላማ ትሩፋቶች:-

1.ዽዽስናና ክህነትን ከእውነተኛ ምንጭ አምተዋል::
2.ክርስትናና ጥምቀትን በሃገራችን አስፋፍተዋል::
3.ቅዱሳት መጻሕፍትን ከውጭ ልሳኖች ተርጉመዋል::
4.ገዳማዊ ሕይወትን ጀምረዋል::
5.አብያተ ክርስቲያናትን አንጸዋል::
6.ግዕዝ ቋንቋን አሻሽለዋል::
ሀ.ከግራ ወደ ቀኝ እንዲፃፍ
ለ.እርባታ እንዲኖረው
ሐ.ከ"አበገደ" ወደ "ሀለሐመ" ቀይረዋል::
ባላቸው ንጹሕ የቅድስና ሕይወት ለሕዝቡ ምሳሌ ሆነዋ::
"ወበእንተዝ ተሰይመ ከሳቴ ብርሃን" እንዲል ገድላቸው
በነዚህ ምክንያቶች "ከሣቴ ብርሃን" (ብርሃንን የገለጠ) ሲባሉ
ይኖራሉ:: በመጨረሻም ከመልካሙ ገድል በሁዋላ በ352
ዓ/ም ዐርፈው ተቀብረዋል::
@dn yordanos
💚💛 አቡነ ሰላማ ካልዕ 💛❤️
እኒህ ታላቅ ደግ ሰው የነበሩት በሃገራችን ኢትዮዽያ ከ1340 እስከ 1380 ዓ/ም ነው:: በትውልድ ግብጻዊ ቢሆኑም ለኢትዮዽያ ቤተ ክርስቲያን ብዙ ውለታን ውለዋል::
በዘመኑ ዻዻስ ሁነው ቢመጡም እንደ ሌሎቹ ዻዻሳት በቤተ
መንግስት አካባቢ ሥራ ፈትተው መቀመጥን አልፈለጉም::
ወዲያው እንደ መጡ የግዕዝ ልሳንን ልቅም አድርገው
ተማሩ:: ቀጥለው ኢትዮዽያውያን ሊቃውንትን ሰብስበው
ቅዱሳት መጻሕፍትን ይተረጉሙ ገቡ:: አሥራው መጻሕፍትን
(81ዱን) ጨምሮ ብዙ መሠረታዊ መጻሕፍትን መተርጐም
ችለዋል::
ይህም ሥራ አድካሚ በመሆኑ ከ30 ዓመታት በላይ ጊዜን ወስዷል:: ከተረጐሟቸው መጻሕፍትም:-
* #ስንክሳር
* #ግብረ_ሕማማት
* #ላሃ_ማርያም
* #ፊልክስዩስ (መጽሐፈ መነኮሳት)
* #መጽሐፈ_ግንዘት
*ድርሳን ዘቅዱስ #ያዕቆብ_ዘሥሩግ . . . ይጠቀሳሉ::
#አቡነ_ሰላማ በስብከተ ወንጌል አገልግሎታቸውና
በገዳማዊ ሕይወታቸው ይታወቁ ነበር:: በተጨማሪም
በየቦታው እየዞሩ ይናዝዙ: ያጠምቁም ነበር:: በወቅቱ ልክ
እንደ ስማቸው ሰላም እንዲሰፍን ይተጉ ነበር:: መሣፍንቱን:
ነገሥታቱን እያስታረቁ ለቤተ ክርስቲያን በአንድነት እንዲቆሙ
አድርገዋል::
ጻድቁ አቡነ ፊልዾስን ጨምሮ ቅዱሳንን ገንዘውም
ቀብረዋል:: በቀደመ ስማቸው #አባ_ፊቅጦር የሚባሉት
ካልዕ (2ኛው) ሰላማ በ1380 ዓ/ም ከ40 ዓመታት ትጋት
በሁዋላ ዐርፈዋል:: ሲጠሩም:-
* #መተርጉም (መጻሕፍትን የተረጐሙ)
* #ብርሃነ_አዜብ (የኢትዮዽያ ብርሃን)
* #መጋቤ_ሃይማኖት ተብለው ነው::
🌼አምላከ ቅዱሳን ወዳጆቹን እንዳጸናቸው ያጽናን:: ከበረከታቸውም ያድለን::🌼