♥ #ቅዱስ_ዲዮስቆሮስ_ሊቅ ♥
ይህ አባት የተዋሕዶ ሃይማኖታችን ምሰሶ ነው:: በ5ኛው መቶ ክ/ዘ በግብጽ ተወልዶ አድጐ: በልጅነቱ
መጻሕፍትን ተምሮ: የምናኔ ሕይወትን መርጧል::
ቆይቶም የታላቁ ሊቅ #ቅዱስ_ቄርሎስ ረድእ ሆኖ
ተምሯል: አገልግሎታል::
+በጉባኤ #ኤፌሶን ጊዜም ቅዱስ ቄርሎስን ተከትሎ
ሒዶ ተሳትፏል:: በ444 ዓ/ም ታላቁን ሊቅ ተክቶ
የእስክንድርያ 25ኛ ፓትርያርክ ሆኖ ተሹሟል:: ለ7
ዓመታትም መጽሐፈ ቅዳሴውን (እምቅድመ ዓለምን)
ጨምሮ ብዙ ድርሰቶችን ደርሷል:: በመልካም እረኝነትም
ሕዝቡን ጠብቋል::
✝ዘመነ ሰማዕታትን ተከትሎ የመጣው የመናፍቃን ዘመን
ሲሆን ለ150 ዓመታት ያህል መናፍቃን እንደ አሸን
ፈልተዋል:: በዚያው ልክ ከዋክብት ቅዱሳን ሊቃውንት
ነበሩና በየጊዜው ጉባኤያትን እየሠሩ: መናፍቃንን
አሳፍረዋል:: ምዕመናንንም አጽንተዋል::
✝በ451 ዓ/ም የተፈጸመው ድርጊት ግን ዛሬም ድረስ
ጠባሳው የሚለቅ አልሆነም:: ንጉሡ መርቅያንና ዻዻሱ
ልዮን የንስጥሮስን ትምሕርት አለባብሰው ሊያስተምሩ
ሲሞክሩ ግጭት በመፈጠሩ ቤተ ክርስቲያን ለመጀመሪያ
ጊዜ ወደ 2 ተከፈለች::
✝በጉባኤው የነበሩ 636 ዻዻሳት ስቃይና ሞትን ፈርተው
በኑፋቄ መጽሐፍ ላይ በመፈረማቸው
"መለካውያን" (ከእግዚአብሔር ይልቅ ለንጉሥ
የሚታዘዙ) ተባሉ:: ጉባኤውም "ጉባኤ
ከለባት" (የውሾች ስብሰባ): "ጉባኤ አብዳን" (የሰነፎች
ጉባኤ) ተብሏል::
✝ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ግን "በኑፋቄው ላይ አልፈርምም"
ከማለቱ አልፎ መናፍቃኑን አወገዛቸው:: በዚህ ምክንያት
ወደ ጋግራ ደሴት ከ7 ደቀ መዛሙርቱ ጋር አሳደዱት::
በዚያም ለ3 ዓመታት ቆይቶ በ454 ዓ/ም ዐረፈ::
✝ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ከማረፉ በፊት በተሰደደባት ደሴተ
#ጋግራ ለ3 ዓመታት ብዙ መከራ ከመናፍቃን ደርሶበታል:: እርሱ ግን በትእግስቱና በትምሕርቱ
ብዙዎችን ወደ ሃይማኖት መልሷል:: ቤተ ክርስቲያን እርሱን 'አበ ተዋሕዶ' (የተዋሕዶ
እምነት አባትና አርበኛ) ትለዋለች:: የተነጨ ጺሙ:
የረገፉ ጥርሶቹና የፈሰሰ ደሙ ዛሬም ድረስ ትልቅ ምስክርና የሃይማኖት ፍሬ ነውና::
"ያስተጻንዕ ህየ እለ ኀለዉ ደቂቀ:
ዘተነጽየ እምነ ጽሕሙ ወእም አስናኒሁ ዘወድቀ: ፍሬ ሃይማኖቱ ፈነወ ብሔረ ርሑቀ" እንዲል::
ይህ አባት የተዋሕዶ ሃይማኖታችን ምሰሶ ነው:: በ5ኛው መቶ ክ/ዘ በግብጽ ተወልዶ አድጐ: በልጅነቱ
መጻሕፍትን ተምሮ: የምናኔ ሕይወትን መርጧል::
ቆይቶም የታላቁ ሊቅ #ቅዱስ_ቄርሎስ ረድእ ሆኖ
ተምሯል: አገልግሎታል::
+በጉባኤ #ኤፌሶን ጊዜም ቅዱስ ቄርሎስን ተከትሎ
ሒዶ ተሳትፏል:: በ444 ዓ/ም ታላቁን ሊቅ ተክቶ
የእስክንድርያ 25ኛ ፓትርያርክ ሆኖ ተሹሟል:: ለ7
ዓመታትም መጽሐፈ ቅዳሴውን (እምቅድመ ዓለምን)
ጨምሮ ብዙ ድርሰቶችን ደርሷል:: በመልካም እረኝነትም
ሕዝቡን ጠብቋል::
✝ዘመነ ሰማዕታትን ተከትሎ የመጣው የመናፍቃን ዘመን
ሲሆን ለ150 ዓመታት ያህል መናፍቃን እንደ አሸን
ፈልተዋል:: በዚያው ልክ ከዋክብት ቅዱሳን ሊቃውንት
ነበሩና በየጊዜው ጉባኤያትን እየሠሩ: መናፍቃንን
አሳፍረዋል:: ምዕመናንንም አጽንተዋል::
✝በ451 ዓ/ም የተፈጸመው ድርጊት ግን ዛሬም ድረስ
ጠባሳው የሚለቅ አልሆነም:: ንጉሡ መርቅያንና ዻዻሱ
ልዮን የንስጥሮስን ትምሕርት አለባብሰው ሊያስተምሩ
ሲሞክሩ ግጭት በመፈጠሩ ቤተ ክርስቲያን ለመጀመሪያ
ጊዜ ወደ 2 ተከፈለች::
✝በጉባኤው የነበሩ 636 ዻዻሳት ስቃይና ሞትን ፈርተው
በኑፋቄ መጽሐፍ ላይ በመፈረማቸው
"መለካውያን" (ከእግዚአብሔር ይልቅ ለንጉሥ
የሚታዘዙ) ተባሉ:: ጉባኤውም "ጉባኤ
ከለባት" (የውሾች ስብሰባ): "ጉባኤ አብዳን" (የሰነፎች
ጉባኤ) ተብሏል::
✝ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ግን "በኑፋቄው ላይ አልፈርምም"
ከማለቱ አልፎ መናፍቃኑን አወገዛቸው:: በዚህ ምክንያት
ወደ ጋግራ ደሴት ከ7 ደቀ መዛሙርቱ ጋር አሳደዱት::
በዚያም ለ3 ዓመታት ቆይቶ በ454 ዓ/ም ዐረፈ::
✝ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ከማረፉ በፊት በተሰደደባት ደሴተ
#ጋግራ ለ3 ዓመታት ብዙ መከራ ከመናፍቃን ደርሶበታል:: እርሱ ግን በትእግስቱና በትምሕርቱ
ብዙዎችን ወደ ሃይማኖት መልሷል:: ቤተ ክርስቲያን እርሱን 'አበ ተዋሕዶ' (የተዋሕዶ
እምነት አባትና አርበኛ) ትለዋለች:: የተነጨ ጺሙ:
የረገፉ ጥርሶቹና የፈሰሰ ደሙ ዛሬም ድረስ ትልቅ ምስክርና የሃይማኖት ፍሬ ነውና::
"ያስተጻንዕ ህየ እለ ኀለዉ ደቂቀ:
ዘተነጽየ እምነ ጽሕሙ ወእም አስናኒሁ ዘወድቀ: ፍሬ ሃይማኖቱ ፈነወ ብሔረ ርሑቀ" እንዲል::