#ቅዱስ_ዑቲኮስ_ሐዋርያ
ቅዱሱ ሐዋርያ ጭራሽ ከነ ስማቸው እንኩዋ እየተዘነጉ
ከሔዱ #ሐዋርያት አንዱ ሲሆን ቁጥሩም ከ72ቱ #አርድእት
ነው:: በወጣትነት ዘመኑ የጌታችን ደቀ መዝሙር መሆንን
መርጦ ለ3 ዓመታት ከ3 ወራት ምሥጢረ ወንጌልን ጠንቅቆ
ተምሯል::
መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜም እንደ መጠኑ ተቀብሎ
ለአገልግሎት ወጥቷል:: በመጀመሪያ የወንጌላዊው ዮሐንስ
ተከታይ ሁኖ ብዙ ምሥጢራትን ተካፍሏል:: ቀጥሎም ቅዱስ
ዻውሎስን ተከትሎ ብዙ አሕጉራትን በስብከተ ወንጌል
አዳርሷል::
በመጨረሻም በእስያ አካባቢ ለብቻው ተጉዞ: ብዙ ነፍሳትን
ማርኮ: ጣዖታትን አጥፍቷል:: ስለዚህ ፈንታም በእሳት:
በስለትና በግርፋት ብዙ መከራዎችን አሳልፏል:: በዚህች
ቀንም በበጐው እርግና (ሽምግልና) ዐርፏል::
ቅዱሱ ሐዋርያ ጭራሽ ከነ ስማቸው እንኩዋ እየተዘነጉ
ከሔዱ #ሐዋርያት አንዱ ሲሆን ቁጥሩም ከ72ቱ #አርድእት
ነው:: በወጣትነት ዘመኑ የጌታችን ደቀ መዝሙር መሆንን
መርጦ ለ3 ዓመታት ከ3 ወራት ምሥጢረ ወንጌልን ጠንቅቆ
ተምሯል::
መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜም እንደ መጠኑ ተቀብሎ
ለአገልግሎት ወጥቷል:: በመጀመሪያ የወንጌላዊው ዮሐንስ
ተከታይ ሁኖ ብዙ ምሥጢራትን ተካፍሏል:: ቀጥሎም ቅዱስ
ዻውሎስን ተከትሎ ብዙ አሕጉራትን በስብከተ ወንጌል
አዳርሷል::
በመጨረሻም በእስያ አካባቢ ለብቻው ተጉዞ: ብዙ ነፍሳትን
ማርኮ: ጣዖታትን አጥፍቷል:: ስለዚህ ፈንታም በእሳት:
በስለትና በግርፋት ብዙ መከራዎችን አሳልፏል:: በዚህች
ቀንም በበጐው እርግና (ሽምግልና) ዐርፏል::