♥ እንኩዋን ለታላላቁ ቅዱሳን #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት:
#ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ እና #ቅዱስ_ቶማስ_ዘመርዓስ
ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ♥
ቅዱስ #ተክለ_ሃይማኖት ሐዋርያዊ "*+ #ልደት
መልካም ዛፍ
መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ: #
ጸጋ_ዘአብ ካህኑና #እግዚእ_ኃረያ ናቸው:: እርሱ በክህነቱ:
እርሷ በደግነቷ: በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ
ፍሬን ሰጥቷቸዋል:: +በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ
ቢደርስባቸው #ቅዱስ_ሚካኤል: ጸጋ ዘአብን ከሞት: እግዚእ
ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል::
በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል:: +አቡነ ተክለ
ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24, በ1206 (1196) ሲሆን
የተወለዱት ታሕሳስ 24, በ1207 (1197) ዓ/ም ነው::
በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል:: ቤታቸውም
በበረከት ሞልቷል:: #ዕድገት =>የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው
"#ፍሥሃ_ጽዮን" ይሰኛል:: ይሕንን ስም ይዘው: አባታቸው ጸጋ
ዘአብን ተከትለው አድገዋል:: በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን
(ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል:: በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ
አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁና ከወቅቱ ዻዻስ #አባ_
ጌርሎስ ተቀብለዋል:: #መጠራት =>አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮን
ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ
ተሰማ:: የክብር ባለቤት #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ አእላፍ
መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ::
+የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ: "ከዛሬ ጀምሮ
ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን:: አራዊትን
ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ
በግርማ ዐረገ:: ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ
ሰዓትን አላጠፉም:: ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ
ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ:: #አገልግሎት
=>ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል
አገልግሎትን ጀመሩ:: በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (#
ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው
አጠመቁ:: ያንጊዜ #ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት:: 1.ዮዲት
(ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ
አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል: ወይም በባዕድ
አምልኮ ተጠምዷል:: 2.ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት
ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር:: +ግማሹ ሃገር በጨለመበት
ወቅት የደረሱት #ሐዲስ_ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት
ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ::
ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን
(ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል:: #ገዳማዊ ሕይወት =>ቅዱስ
ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው
ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል:: እርሳቸው ከሁሉ
የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል::
+እነዚህም በአቡነ #በጸሎተ_ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት:
በአቡነ #ኢየሱስ_ሞዐ_ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ
ዳሞ ከአቡነ #ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26
ዓመታት አገልግለዋል:: +በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ
በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ #ዞረሬ ተመልሰው በአንዲት በዓት
ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም
6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል:: #
ስድስት ክንፍ =>ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ
ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት
መካናት ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ #እሥራኤል የገቡት
በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ
ነበር:: +የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት #አባ_ሚካኤል ጋርም
ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ
በሁዋላ ነው:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ
ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ
እንባቸው ይፈስ ነበር:: +ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው
ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ:-
¤በቤተ መቅደስ ብስራቱን ¤በቤተ ልሔም ልደቱን ¤በቤተ ዮሴፍ
ግዝረቱን ¤በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን ¤በቤተ አልዓዛር
ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር:: +የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል
ወደሆነው #ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ
ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን
ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ:: በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ
#እመቤታችን_ድንግል_ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን
ወደሰማይ አሳረገቻቸው:: +በዚያም:- ¤የብርሃን ዐይን
ተቀብለው ¤6 ክንፍ አብቅለው ¤የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
¤ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው ¤ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም
ተደምረው ¤ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
¤"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ
ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል:: #ተአምራት
=>የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው::
*ሙት አንስተዋል *ድውያንን ፈውሰዋል *አጋንንትን አሳደዋል
*እሳትን ጨብጠዋል *በክንፍ በረዋል *ደመናን ዙፋን
አድርገዋል:: +ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን
መሥርተዋል:: በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት
አብረው ኑረዋል:: በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና:: #ዕረፍት
=>ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን
ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: አእላፍ ፍሬን አፍርተው:
በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24,
በ1306 (1296) ዓ/ም ዐርፈዋል:: ጌታ: ድንግል ማርያምና
ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል:: 10 ትውልድ
የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል::
#ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ እና #ቅዱስ_ቶማስ_ዘመርዓስ
ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ♥
ቅዱስ #ተክለ_ሃይማኖት ሐዋርያዊ "*+ #ልደት
መልካም ዛፍ
መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ: #
ጸጋ_ዘአብ ካህኑና #እግዚእ_ኃረያ ናቸው:: እርሱ በክህነቱ:
እርሷ በደግነቷ: በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ
ፍሬን ሰጥቷቸዋል:: +በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ
ቢደርስባቸው #ቅዱስ_ሚካኤል: ጸጋ ዘአብን ከሞት: እግዚእ
ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል::
በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል:: +አቡነ ተክለ
ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24, በ1206 (1196) ሲሆን
የተወለዱት ታሕሳስ 24, በ1207 (1197) ዓ/ም ነው::
በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል:: ቤታቸውም
በበረከት ሞልቷል:: #ዕድገት =>የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው
"#ፍሥሃ_ጽዮን" ይሰኛል:: ይሕንን ስም ይዘው: አባታቸው ጸጋ
ዘአብን ተከትለው አድገዋል:: በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን
(ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል:: በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ
አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁና ከወቅቱ ዻዻስ #አባ_
ጌርሎስ ተቀብለዋል:: #መጠራት =>አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮን
ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ
ተሰማ:: የክብር ባለቤት #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ አእላፍ
መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ::
+የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ: "ከዛሬ ጀምሮ
ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን:: አራዊትን
ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ
በግርማ ዐረገ:: ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ
ሰዓትን አላጠፉም:: ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ
ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ:: #አገልግሎት
=>ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል
አገልግሎትን ጀመሩ:: በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (#
ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው
አጠመቁ:: ያንጊዜ #ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት:: 1.ዮዲት
(ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ
አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል: ወይም በባዕድ
አምልኮ ተጠምዷል:: 2.ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት
ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር:: +ግማሹ ሃገር በጨለመበት
ወቅት የደረሱት #ሐዲስ_ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት
ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ::
ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን
(ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል:: #ገዳማዊ ሕይወት =>ቅዱስ
ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው
ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል:: እርሳቸው ከሁሉ
የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል::
+እነዚህም በአቡነ #በጸሎተ_ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት:
በአቡነ #ኢየሱስ_ሞዐ_ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ
ዳሞ ከአቡነ #ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26
ዓመታት አገልግለዋል:: +በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ
በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ #ዞረሬ ተመልሰው በአንዲት በዓት
ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም
6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል:: #
ስድስት ክንፍ =>ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ
ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት
መካናት ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ #እሥራኤል የገቡት
በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ
ነበር:: +የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት #አባ_ሚካኤል ጋርም
ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ
በሁዋላ ነው:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ
ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ
እንባቸው ይፈስ ነበር:: +ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው
ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ:-
¤በቤተ መቅደስ ብስራቱን ¤በቤተ ልሔም ልደቱን ¤በቤተ ዮሴፍ
ግዝረቱን ¤በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን ¤በቤተ አልዓዛር
ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር:: +የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል
ወደሆነው #ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ
ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን
ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ:: በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ
#እመቤታችን_ድንግል_ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን
ወደሰማይ አሳረገቻቸው:: +በዚያም:- ¤የብርሃን ዐይን
ተቀብለው ¤6 ክንፍ አብቅለው ¤የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
¤ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው ¤ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም
ተደምረው ¤ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
¤"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ
ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል:: #ተአምራት
=>የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው::
*ሙት አንስተዋል *ድውያንን ፈውሰዋል *አጋንንትን አሳደዋል
*እሳትን ጨብጠዋል *በክንፍ በረዋል *ደመናን ዙፋን
አድርገዋል:: +ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን
መሥርተዋል:: በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት
አብረው ኑረዋል:: በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና:: #ዕረፍት
=>ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን
ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: አእላፍ ፍሬን አፍርተው:
በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24,
በ1306 (1296) ዓ/ም ዐርፈዋል:: ጌታ: ድንግል ማርያምና
ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል:: 10 ትውልድ
የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል::
♥ቅዱስ #ቶማስ_ዘመርዓስ♥
ቅዱስ ቶማስ "መርዓስ" በምትባል ሃገር የፈለቀ
¤የንጋት ኮከብ
¤ጻድቅ
¤ገዳማዊ
¤ዻዻስ
¤ሐዋርያ
¤ሰማዕትና ሊቅ ነው:: የዚህን ቅዱስ ተጋድሎ እንደ እኔ ያለ
ሰው አይቻለውም:: የእርሱ ሕይወት
ክርስትና ምን እንደ ሆነ ያሳያል::
#ቅዱስ_ቶማስ:-
¤ከልጅነቱ ቅዱሳት መጻሕፍትን የተማረ
¤ገና በወጣትነቱ መንኖ ገዳም የኖረ
¤መርዓስ በምትባል ሃገር ዽዽስና ተሹሞ በእረኝነት ያገለገለ
¤በሐዋርያዊ አገልግሎት ብዙ አሕዛብን ወደ ክርስትና የመለሰ
¤በዘመነ ሰማዕታት ብዙ መከራን የተቀበለ አባት ነው::
+ጨካኞቹ ቅዱሱን ለ22 ዓመታት አካሉን እየቆራረጡ
ለጣዖታቸው ያጥኑ ስለ ነበር 2 እግሮቹ: 2 እጆቹ: 2 ጀሮዎቹ: 2
አፍንጫዎቹ: 2 ዐይኖቹ: ሁሉ አልነበሩም:: ነገር ግን እንዲህም
ሆኖ አልሞተም ነበር::
+በመጨረሻም በዘመነ መናፍቃን አርዮስን ካወገዙት 318ቱ
ሊቃውንት እንዳንዱ ተቆጥሯል:: ቅዱስ ቶማስ ዽዽስና በተሾመ
በ40 ዓመቱ በዚህች ቀን ዐርፏል:: የጻድቃንን: የሰማዕታትን:
የሐዋርያትንና ሊቃውንትን አክሊልም ተቀብሏል::
♥አምላከ ቅዱሳን በወዳጆቹ ምልጃ ክብራቸውን ያድለን::
በረከታቸውም በዝቶ ይደርብን::♥
ቅዱስ ቶማስ "መርዓስ" በምትባል ሃገር የፈለቀ
¤የንጋት ኮከብ
¤ጻድቅ
¤ገዳማዊ
¤ዻዻስ
¤ሐዋርያ
¤ሰማዕትና ሊቅ ነው:: የዚህን ቅዱስ ተጋድሎ እንደ እኔ ያለ
ሰው አይቻለውም:: የእርሱ ሕይወት
ክርስትና ምን እንደ ሆነ ያሳያል::
#ቅዱስ_ቶማስ:-
¤ከልጅነቱ ቅዱሳት መጻሕፍትን የተማረ
¤ገና በወጣትነቱ መንኖ ገዳም የኖረ
¤መርዓስ በምትባል ሃገር ዽዽስና ተሹሞ በእረኝነት ያገለገለ
¤በሐዋርያዊ አገልግሎት ብዙ አሕዛብን ወደ ክርስትና የመለሰ
¤በዘመነ ሰማዕታት ብዙ መከራን የተቀበለ አባት ነው::
+ጨካኞቹ ቅዱሱን ለ22 ዓመታት አካሉን እየቆራረጡ
ለጣዖታቸው ያጥኑ ስለ ነበር 2 እግሮቹ: 2 እጆቹ: 2 ጀሮዎቹ: 2
አፍንጫዎቹ: 2 ዐይኖቹ: ሁሉ አልነበሩም:: ነገር ግን እንዲህም
ሆኖ አልሞተም ነበር::
+በመጨረሻም በዘመነ መናፍቃን አርዮስን ካወገዙት 318ቱ
ሊቃውንት እንዳንዱ ተቆጥሯል:: ቅዱስ ቶማስ ዽዽስና በተሾመ
በ40 ዓመቱ በዚህች ቀን ዐርፏል:: የጻድቃንን: የሰማዕታትን:
የሐዋርያትንና ሊቃውንትን አክሊልም ተቀብሏል::
♥አምላከ ቅዱሳን በወዳጆቹ ምልጃ ክብራቸውን ያድለን::
በረከታቸውም በዝቶ ይደርብን::♥
💚💛እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ዓመታዊ የተአምር በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። 💛❤️
✝ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ✝
#ቅዱስ_ቶማስ_ሐዋርያ
ከ12ቱ ቅዱሳን ሐዋርያት አንዱ የሆነው ቅዱስ ቶማስ ብዙ መከራን በማሳለፉና የጌታችንን ጐን በመዳሰሱ ይታወቃል::
ቅዱስ ቶማስ እንደ ሌሎቹ ሐዋርያት በእሥራኤል ተወልዶ በዚያውም በሥርዓተ ኦሪት አድጐ ገና በወጣትነቱ የሰዱቃውያንን ማሕበር ተቀላቅሏል:: ሰዱቃውያን ሰው ከሞተ በሁዋላ አይነሳም (አልቦ ትንሳኤ) የሚሉ ናቸው:: መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማስተማር ሲጀምር ግን ቅዱስ ቶማስ ከነበረበት ማሕበር ወጥቶ ጌታችንን ተከተለ:: ጌታችንም ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ይሆን ዘንድ ሾመው:: የቀደመ ስሙ "ዲዲሞስ" ሲሆን ጌታችን "ቶማስ" ብሎታል::
ቅዱስ ቶማስ ጌታ አልዓዛርን ለማስነሳት በሔደ ጊዜ ሌሎች ሐዋርያት ጌታን "አይሁድ ይገድሉሃል ቅር" ሲሉት እርሱ ግን "እንሒድና አብረን እንሙት" ሲል ፍቅሩን አሳይቷል:: (ዮሐ. 11:16)
ጌታችን ትንሳኤውን ለደቀ መዛሙርቱ በገለጠ ጊዜ ያልነበረው ቶማስ ካላየሁ አላምንም አለ:: ምክንያቱም:-
1.ለጌታችን ከነበረው ፍቅር የተነሳ እውነት አልመስልህ ቢለው::
2.አንድም ሌሎቹ ሐዋርያት "ትንሳኤውን አየን" እያሉ ሲያስተምሩ እኔ ግን "ሰማሁ" ብየ ማስተማሬ ነው ብሎ በማሰቡ ነበር::
ለጊዜው ጌታ ተገልጾ ቢገስጸው "እግዚእየ ወአምላኪየ (ጌታየና አምላኬ)" ብሎ ፍጹም ሃይማኖቱን ገልጿል:: ለፍጻሜው ግን የጌታችንን ጎን (መለኮትን) ይዳስስ ዘንድ ባለቤቱ እንዳደለው ያጠይቃል:: መለኮትን የዳሰሰች ይሕቺ ቅድስት እጁ ዛሬም ድረስ ሕያው ናት:: በሕንድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥም በክብር ተቀምጣለች::
ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው ሐገረ ስብከት ሲከፋፈሉ ለቅዱስ ቶማስ ሕንድና በዙሪያዋ ያሉ ሃገራት ደረሱት:: ከዚህ በሁዋላ ነው እንግዲህ ዘርዝረን የማንጨርሰውን ተጋድሎ የፈጸመው:: ቅዱሱ በነበረው ፍጹም ትጋት አባቶቻችን "ዘአሠርገዋ ለብሔረ ሕንደኬ (ሕንድን በወንጌል ያስጌጣት)" ሲሉ ያከብሩታል::
ቅዱስ ቶማስ ንጉሥ ሉክዮስንና የሃገሩን ሕዝብ ለማሳመን በችንካር መሬት ላይ ወጥረው ቆዳውን ገፈውታል:: ቆዳውንም እንደ ገና ሰፍተው: አሸዋ ሞልተው አሸክመውታል:: በየመንገዱ የተገፈፈ ገላውን ጨው ቢቀቡት በጎች መጥተው ግጠው በልተውታል:: በዚሕ ምክንያት:-
"ኩሉ የአኪ እንዘ የአኪ ዘመኑ::
አባግዒሁ ለቶማስ እስመ አራዊተ ኮኑ::" ብለዋል ሊቃውንቱ::
በሁዋላ ግን ከፎቅ ወድቃ የሞተችውን የንጉሡን ሚስት በተገፈፈ ቆዳው በማዳኑ ሁሉም አምነው ተጠምቀዋል::
ቅዱሱ ሐዋርያ ልክ እንደ ቅዱስ ዻውሎስ አንዳንዴ በፈሊጥ: ሌላ ጊዜም በመከራ ለወንጌልና ለቤተ ክርስቲያን ተጋድሏል:: ያለ ማቁዋረጥም ከሕንድ እስከ ሃገራችን ኢትዮዽያ ድረስ ለ38 ዓመታት ወንጌልን ሰብኩዋል::
በመጨረሻም በ72 ዓ/ም በሰማዕትነት አርፏል:: መቃብሩና ቅድስት እጁ ዛሬ ድረስ ሕንድ ውስጥ አሉ:: ከኘሮቴስታንቶች በቀር መላው ዓለም ያከብረዋል::
✝ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ✝
#ቅዱስ_ቶማስ_ሐዋርያ
ከ12ቱ ቅዱሳን ሐዋርያት አንዱ የሆነው ቅዱስ ቶማስ ብዙ መከራን በማሳለፉና የጌታችንን ጐን በመዳሰሱ ይታወቃል::
ቅዱስ ቶማስ እንደ ሌሎቹ ሐዋርያት በእሥራኤል ተወልዶ በዚያውም በሥርዓተ ኦሪት አድጐ ገና በወጣትነቱ የሰዱቃውያንን ማሕበር ተቀላቅሏል:: ሰዱቃውያን ሰው ከሞተ በሁዋላ አይነሳም (አልቦ ትንሳኤ) የሚሉ ናቸው:: መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማስተማር ሲጀምር ግን ቅዱስ ቶማስ ከነበረበት ማሕበር ወጥቶ ጌታችንን ተከተለ:: ጌታችንም ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ይሆን ዘንድ ሾመው:: የቀደመ ስሙ "ዲዲሞስ" ሲሆን ጌታችን "ቶማስ" ብሎታል::
ቅዱስ ቶማስ ጌታ አልዓዛርን ለማስነሳት በሔደ ጊዜ ሌሎች ሐዋርያት ጌታን "አይሁድ ይገድሉሃል ቅር" ሲሉት እርሱ ግን "እንሒድና አብረን እንሙት" ሲል ፍቅሩን አሳይቷል:: (ዮሐ. 11:16)
ጌታችን ትንሳኤውን ለደቀ መዛሙርቱ በገለጠ ጊዜ ያልነበረው ቶማስ ካላየሁ አላምንም አለ:: ምክንያቱም:-
1.ለጌታችን ከነበረው ፍቅር የተነሳ እውነት አልመስልህ ቢለው::
2.አንድም ሌሎቹ ሐዋርያት "ትንሳኤውን አየን" እያሉ ሲያስተምሩ እኔ ግን "ሰማሁ" ብየ ማስተማሬ ነው ብሎ በማሰቡ ነበር::
ለጊዜው ጌታ ተገልጾ ቢገስጸው "እግዚእየ ወአምላኪየ (ጌታየና አምላኬ)" ብሎ ፍጹም ሃይማኖቱን ገልጿል:: ለፍጻሜው ግን የጌታችንን ጎን (መለኮትን) ይዳስስ ዘንድ ባለቤቱ እንዳደለው ያጠይቃል:: መለኮትን የዳሰሰች ይሕቺ ቅድስት እጁ ዛሬም ድረስ ሕያው ናት:: በሕንድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥም በክብር ተቀምጣለች::
ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው ሐገረ ስብከት ሲከፋፈሉ ለቅዱስ ቶማስ ሕንድና በዙሪያዋ ያሉ ሃገራት ደረሱት:: ከዚህ በሁዋላ ነው እንግዲህ ዘርዝረን የማንጨርሰውን ተጋድሎ የፈጸመው:: ቅዱሱ በነበረው ፍጹም ትጋት አባቶቻችን "ዘአሠርገዋ ለብሔረ ሕንደኬ (ሕንድን በወንጌል ያስጌጣት)" ሲሉ ያከብሩታል::
ቅዱስ ቶማስ ንጉሥ ሉክዮስንና የሃገሩን ሕዝብ ለማሳመን በችንካር መሬት ላይ ወጥረው ቆዳውን ገፈውታል:: ቆዳውንም እንደ ገና ሰፍተው: አሸዋ ሞልተው አሸክመውታል:: በየመንገዱ የተገፈፈ ገላውን ጨው ቢቀቡት በጎች መጥተው ግጠው በልተውታል:: በዚሕ ምክንያት:-
"ኩሉ የአኪ እንዘ የአኪ ዘመኑ::
አባግዒሁ ለቶማስ እስመ አራዊተ ኮኑ::" ብለዋል ሊቃውንቱ::
በሁዋላ ግን ከፎቅ ወድቃ የሞተችውን የንጉሡን ሚስት በተገፈፈ ቆዳው በማዳኑ ሁሉም አምነው ተጠምቀዋል::
ቅዱሱ ሐዋርያ ልክ እንደ ቅዱስ ዻውሎስ አንዳንዴ በፈሊጥ: ሌላ ጊዜም በመከራ ለወንጌልና ለቤተ ክርስቲያን ተጋድሏል:: ያለ ማቁዋረጥም ከሕንድ እስከ ሃገራችን ኢትዮዽያ ድረስ ለ38 ዓመታት ወንጌልን ሰብኩዋል::
በመጨረሻም በ72 ዓ/ም በሰማዕትነት አርፏል:: መቃብሩና ቅድስት እጁ ዛሬ ድረስ ሕንድ ውስጥ አሉ:: ከኘሮቴስታንቶች በቀር መላው ዓለም ያከብረዋል::
💚💛 #ቅዱስ_ቶማስ💛❤️
@senkesar
✞ ለነፍስ ማረፊያ የሚጠቅማትን ሰማያዊ ቤተ-መንግስት የገነባ ኢንጅነር!
ሐዋርያው ቶማስ ትንሳዔ ሙታን የለም ብለው ከሚያምኑ ከሰዱቃዊያን ወገን ነው፡፡ ሰዱቃዊያን በዘመነ ሥጋዌ በአይሁድ መካከል ከሚገኙት ትላልቅ ቡድኖች መካከል አንዱ ነው፡፡ ቀደም ሲል በፖለቲካው ውስጥ ከፍያለ ቦታ በመያዛቸው ሃብታሞች እንዲሁም የመሬት ባለአባቶች ነበሩ፡፡ በአይሁድ ሸንጎ ውስጥም ከፈሪሳዊያን ያልተናነሰ ቦታ ነበራቸው፡፡ ሐዋ 23፡6- 10 በትንሳዔ ሙታን ካለማመናቸው ባሻገር የኦሪትን መጽሐፍ ብቻ የሚቀበሉ ቀጥታ ትርጉምን የሚከተሉ ነበሩ፡፡ ሐዋርያው ቶማስም ከሰዱቃዊያን ወገን በመሆኑ ነበር ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞት መነሳቱን አሥሩ ሐዋርያት ሲነግሩት " የችንካሩን ምልክት በእጆቼ ካላየሁ ፣ ጣቴንም በችንካሩ ምልክት ካላገባሁ ፣ እጄንም በጎኑ ካላስገባሁ አላምንም " ያለው። ዮሐ 20 : 25 በኃላ ግን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቶማስ በእምነቱ እንዲጠነክር አስቀድሞ አሥሩ ባሉበት እንደተገለጠ ሁሉ ዳግመኛ ቶማስ ባለበት በዝግ ቤት ውስጥ ተገልጦ ቶማስ ያለው ሁሉ እንዲፈጸምለት አደረገ ፤ ቶማስም " ጌታዬ አምላኬ " ብሎ አምኖ መስክሯል።
፠፠፠፠፠፠
ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ከሐዋርያት ሁሉ ርቆ ወደ ምሥራቅ የተጓዘ ሐዋርያ ነው ፤ በቅድሚያ ወደ ፐርሺያ (ያሁኗ ኢራን ስትሆን በዚህች ሀገር ኢትዮጲያዊው ጃንደረባ ‹ባኮስ› ወንጌልን አስተምሯል፡፡ በኮስ በሐዋርያው በፊልጶስ እጅ አምኖ ከተጠመቀ በኋላ በመጀመርያ ወደ ሀገሩ ተመልሶ ወንጌልን በመስበክ ንግስተ ሕንደኬ የቤተ-መንግስተ ሰዎች እና ሌሎች ሰዎች ከተጠመቁ በኋላ ወደ የመን ቀጥሎም ወደ ፐርሽያ ከዛ ወደ ሕንድ ተጉዞ በእነዚህ አከባቢ ወንጌልን አስተምሯል፡፡ የመጨረሻ ሀገረ ስብከቱ በጥንቷ ታፕሮባና በዛሬዋ ሲሎን በምትባለው ደሴት ሲሆን በዚህም ወንጌልን ሲያስተምር ቆይቶ በአረማዊያን እጅ በሰማዕትነት አርፏል፡፡) ከፐርሽያም ቀጥሎ ወደ ሕንድ ተጉዟል ፣ ቅዱስ ቶማስ ሕንድ የደረሰው በ46 ዓ.ም አካባቢ ነው።
፠፠፠፠፠፠
ቶማስ ወንጌልን በፐርሽያ ሰብኮ ወደ ሕንድ ለመውረድ ሲፈልግ አንድ ከንጉስ ዘንድ የተላከ ነጋዴ ከመንገድ ላይ ያገኘዋል፡፡ ነጋዴው ቶማስ ከኢየሩሳሌም መምጣቱን ሲሰማ እጅግ በጣም ደስ ይለዋል፡፡ ወደ ቶማስም ቀርቦ ከንጉስ ዘንድ እንደተላከ እና ንጉሱ የጠቢቡ ሰለሞንን አይነት ቤተ መንግስት ማሰራት እንደሚፈልግ ለዚህም ሃሳቡ ከኢየሩሳሌም የመጣ ጎበዝ ኢንጅነር እንደሚፈልግ አጫወተው ቶማስም የነጋዴውን ነገር ካዳመጠ በኋላ ሞያው እንደሆነ በዛም ይተዳደር እንደ ነበር ገልጾለት አብረው ወደ ንጉሱ አቀኑ፡፡ ንጉሱም በሰማው ነገር ተደስቶ ቶማስን አስከትሎ ቤተ-መንግስቱን ሊገነባበት ወዳሰበው ሳይት አመሩ በዚህም ስለግንባታው ከተወያዩ በኋላ ቶማስ እንዴት መሆን እንዳለበት ዲዛይኑን ለንጉሱ አስረዳው ንጉሱም በፕላኑ ተደስቶ ውሉን ከቶማስ ጋር ተዋዋለ፡፡ በትዕዛዙ መሰረት አስፈላጊውን ፈንድ ከንጉሱ ተለቆለት ወደ ሳይቱ ተመለሰ፡፡
❖ @senkesar ❖
ቶማስ ግን በተቀበለው ገንዘብ እንኳን ቤተ-ንግስት መሬት አላስቆፈረም፡፡ በሞያው ኢንጅነር ቢሆንም ጌታ ድንጋይ ለመገንባት ሳይሆን የሰውን ልብ ለመገንባት መርጦታል፡፡ ልክ ቅዱስ ጴጥሮስን አሳን ሳይሆን ሰው እምታጠም ድአደርግሀለው ብሎ ለትልቅ ክብር እንደጠራው ቶማስ ሰማያዊ ቤተ-መንግስት ለመገንባት የተመረጠ ሐዋርያ በሆኑ ከንጉሱ የተቀበለውን ገንዘብ የድሆችን ቤት በመስራት የተራቡትን በማብላት የተጠሙትን በማጠጣት የታመሙትን በመፈወስ ላይ አዋለው፡፡ ንጉሱ ግንባታው ምን ላይ እንደደረሰ ለማየት ሲመጣ ቤተ-መንግስት አይደለም ከዛፎቹ ውጪ ከፍ ብሎ የሚታይ ነገር አጣ፡፡ ኢ/ር ቶመስ በድሆች መንደር የተራቡትን በማብላት የተጠሙትን በማጠጣት የታመሙትን በመፈወስ ላይ እንደሚገኝ ሰማ አስጠርቶ ጠየቀው
‹‹ የታል ቤተ-መንግስቴ? ››
ቶማስ መለሰ ‹‹ በሚገባ ተሰርቶ ተጠናቋል ›› ንጉሱም ግራ በመጋባት ስሜት ‹‹ የታል የሚታየኝ?›› በዚህ ጊዜ ቶማስ ትልቁ ስራውን ገለጠ ‹‹ በእርግጥ በምድር ላይ የድንጋይ ቤተ መንግስት ላያዩ ይችላሉ እኔ ግን በሰማይ እርሶ ካሰቡት በላይ ቤተ-መንግስት ሰርቼሎታለው፡፡›› ንጉሱ በንዴት እሚያደርገውን አጣ እዛው ፍርዱን አስተላለፈ ‹‹ እጅ እና እግሩን ቆረጣችሁ ግደሉልኝ›› ንጉስ ተደመጠ ፍረዱ እስኪፈጸም ቶማስ በወይኒ ተጣለ፡፡ በዚህ ጊዜ የንጉሱ ወንድም በድንገተኛ በሽታ ሞተ ንጉሱ ተጠራ ተለቀሰ መላዕክት የልዑሉን ነፍሱን አጅበው ወደ ሰማይ አወጧት ‹‹ ከአብያተ መንግስታቱ ትኖሪበት ዘንድ ያማረሽን ምረጪ›› ተባለች ካሉት እሚያምረውን መረጠች ይሔ ያንቺ አይደለም ቶማስ ለውንድምሽ የሰራው ሰማያዊ ቤተ- መንግስት ነው ተባለች በዚህ ጊዜ የልዑሉ ነፍስ ከስጋው ተዋህዳ ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሳ ሁሉም ለቅሶውን አቆመ ልዑሉም የተመለከተውን መሰከረ ንጉሱም ቶማስ ላይ ስላደረሰው መከራ አለቀሰ ከእስር አስፈትቶም የሰማያዊ ቤተ-መንግስት መገንባቱን እንዲቀጥልለት ከቶማስ ጋር ውሉን አደሰ ሌሎች ባለሃብቶችም የንጉሱን አሰረ ፍኖት ተከትለው ‹የሰማይ ቤተ- መንግስት› መገንባትን ጀመሩ፡፡
❖ @senkesar ❖
ሐዋርያው ከዛም በመቀጠል ከማላባር ጀምሮ እስከ ቻይና በመዝለቅ ወንጌልን ሰብኳል ። በመጨረሻም በ66 ዓ.ም በሚላፖር ከተማ የሚገኙ አምላክያነ ጣኦት ቆዳውን ገፈው በቆዳው ስልቻ በመሥራት በሰውነቱ ላይ ጨው ነስንሰው በቆዳው አሸዋ በመሙላት አሸክመው በአሰቃቂ ሁኔታ እንደገደሉት ታሪኩ ይመሰክራል፡፡ ከዛም ፍልሰተ አጽሙ ከሚላፖር ወደ ኤዴሳ ተዛውሯል፡፡
ኤዴሳ ያሁኗ ታነሻ ኢስያ ፣ ዑር ናት ይህችን ሀገር ካነሳን አይቀር ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊን እናንሳ ቅዱስ ኤፍሬም በ393 ዓ.ም የነጽቢን ከተማ በወራሪዎች እጅ ስትወድቅ ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር ወደዚህች ሀገር ተሰዷል፡፡ ይህች ቦታ ቅዱስ ኤፍሬም ከመናፍቃን ጋር የተጋደለባት ፣ አብዛኞቹን ክህደት ትምህርቶች የሞገተበት ፣ አብዛኞቹን መጽሐፍት ያዘጋጀባት ቦታ ናት፡፡ ይህ ታላቅ አባት ‹ አቤቱ የጸጋህን ማዕበል ግታልኝ › እስከሚል ድረስ ድረሳናትን ደርሷል፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ 370 ዓ.ም ሐምሌ 15 አርፏል፡፡ በታላቅ አባትነቱም ሶሪያዊያን ‹ ጥዑመ ልሳን ፣ መምህረ ዓለም ፣ ዓምደ ቤተ-ክርስቲያን በማለት ይጠሩታል፡፡ በቁጥር ስንክሳራችን ሲገልፀው 14 ሺህ ድርሳናትን እና ተግሳጻትን መድረሱን ያስቀምጣል) ለእኔ ሐዋርያት ላይ ከደረሱት ስቃዮች የሐዋርያው ቶማስ ስቃይ የከፋ ነው የጽናቱን ቅንጣት በልባችን በአማልጅነቱ ያኑርልን፡፡ ግንቦት 26 መታሰቢያው ነው፡፡
ምንጭ፡- ስለ 12ቱ ሐዋርያት በዚሁ በቻናላችን ስም ካዘጋጀነው ጽሑፍ
@senkesar
@senkesar
✞ ለነፍስ ማረፊያ የሚጠቅማትን ሰማያዊ ቤተ-መንግስት የገነባ ኢንጅነር!
ሐዋርያው ቶማስ ትንሳዔ ሙታን የለም ብለው ከሚያምኑ ከሰዱቃዊያን ወገን ነው፡፡ ሰዱቃዊያን በዘመነ ሥጋዌ በአይሁድ መካከል ከሚገኙት ትላልቅ ቡድኖች መካከል አንዱ ነው፡፡ ቀደም ሲል በፖለቲካው ውስጥ ከፍያለ ቦታ በመያዛቸው ሃብታሞች እንዲሁም የመሬት ባለአባቶች ነበሩ፡፡ በአይሁድ ሸንጎ ውስጥም ከፈሪሳዊያን ያልተናነሰ ቦታ ነበራቸው፡፡ ሐዋ 23፡6- 10 በትንሳዔ ሙታን ካለማመናቸው ባሻገር የኦሪትን መጽሐፍ ብቻ የሚቀበሉ ቀጥታ ትርጉምን የሚከተሉ ነበሩ፡፡ ሐዋርያው ቶማስም ከሰዱቃዊያን ወገን በመሆኑ ነበር ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞት መነሳቱን አሥሩ ሐዋርያት ሲነግሩት " የችንካሩን ምልክት በእጆቼ ካላየሁ ፣ ጣቴንም በችንካሩ ምልክት ካላገባሁ ፣ እጄንም በጎኑ ካላስገባሁ አላምንም " ያለው። ዮሐ 20 : 25 በኃላ ግን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቶማስ በእምነቱ እንዲጠነክር አስቀድሞ አሥሩ ባሉበት እንደተገለጠ ሁሉ ዳግመኛ ቶማስ ባለበት በዝግ ቤት ውስጥ ተገልጦ ቶማስ ያለው ሁሉ እንዲፈጸምለት አደረገ ፤ ቶማስም " ጌታዬ አምላኬ " ብሎ አምኖ መስክሯል።
፠፠፠፠፠፠
ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ከሐዋርያት ሁሉ ርቆ ወደ ምሥራቅ የተጓዘ ሐዋርያ ነው ፤ በቅድሚያ ወደ ፐርሺያ (ያሁኗ ኢራን ስትሆን በዚህች ሀገር ኢትዮጲያዊው ጃንደረባ ‹ባኮስ› ወንጌልን አስተምሯል፡፡ በኮስ በሐዋርያው በፊልጶስ እጅ አምኖ ከተጠመቀ በኋላ በመጀመርያ ወደ ሀገሩ ተመልሶ ወንጌልን በመስበክ ንግስተ ሕንደኬ የቤተ-መንግስተ ሰዎች እና ሌሎች ሰዎች ከተጠመቁ በኋላ ወደ የመን ቀጥሎም ወደ ፐርሽያ ከዛ ወደ ሕንድ ተጉዞ በእነዚህ አከባቢ ወንጌልን አስተምሯል፡፡ የመጨረሻ ሀገረ ስብከቱ በጥንቷ ታፕሮባና በዛሬዋ ሲሎን በምትባለው ደሴት ሲሆን በዚህም ወንጌልን ሲያስተምር ቆይቶ በአረማዊያን እጅ በሰማዕትነት አርፏል፡፡) ከፐርሽያም ቀጥሎ ወደ ሕንድ ተጉዟል ፣ ቅዱስ ቶማስ ሕንድ የደረሰው በ46 ዓ.ም አካባቢ ነው።
፠፠፠፠፠፠
ቶማስ ወንጌልን በፐርሽያ ሰብኮ ወደ ሕንድ ለመውረድ ሲፈልግ አንድ ከንጉስ ዘንድ የተላከ ነጋዴ ከመንገድ ላይ ያገኘዋል፡፡ ነጋዴው ቶማስ ከኢየሩሳሌም መምጣቱን ሲሰማ እጅግ በጣም ደስ ይለዋል፡፡ ወደ ቶማስም ቀርቦ ከንጉስ ዘንድ እንደተላከ እና ንጉሱ የጠቢቡ ሰለሞንን አይነት ቤተ መንግስት ማሰራት እንደሚፈልግ ለዚህም ሃሳቡ ከኢየሩሳሌም የመጣ ጎበዝ ኢንጅነር እንደሚፈልግ አጫወተው ቶማስም የነጋዴውን ነገር ካዳመጠ በኋላ ሞያው እንደሆነ በዛም ይተዳደር እንደ ነበር ገልጾለት አብረው ወደ ንጉሱ አቀኑ፡፡ ንጉሱም በሰማው ነገር ተደስቶ ቶማስን አስከትሎ ቤተ-መንግስቱን ሊገነባበት ወዳሰበው ሳይት አመሩ በዚህም ስለግንባታው ከተወያዩ በኋላ ቶማስ እንዴት መሆን እንዳለበት ዲዛይኑን ለንጉሱ አስረዳው ንጉሱም በፕላኑ ተደስቶ ውሉን ከቶማስ ጋር ተዋዋለ፡፡ በትዕዛዙ መሰረት አስፈላጊውን ፈንድ ከንጉሱ ተለቆለት ወደ ሳይቱ ተመለሰ፡፡
❖ @senkesar ❖
ቶማስ ግን በተቀበለው ገንዘብ እንኳን ቤተ-ንግስት መሬት አላስቆፈረም፡፡ በሞያው ኢንጅነር ቢሆንም ጌታ ድንጋይ ለመገንባት ሳይሆን የሰውን ልብ ለመገንባት መርጦታል፡፡ ልክ ቅዱስ ጴጥሮስን አሳን ሳይሆን ሰው እምታጠም ድአደርግሀለው ብሎ ለትልቅ ክብር እንደጠራው ቶማስ ሰማያዊ ቤተ-መንግስት ለመገንባት የተመረጠ ሐዋርያ በሆኑ ከንጉሱ የተቀበለውን ገንዘብ የድሆችን ቤት በመስራት የተራቡትን በማብላት የተጠሙትን በማጠጣት የታመሙትን በመፈወስ ላይ አዋለው፡፡ ንጉሱ ግንባታው ምን ላይ እንደደረሰ ለማየት ሲመጣ ቤተ-መንግስት አይደለም ከዛፎቹ ውጪ ከፍ ብሎ የሚታይ ነገር አጣ፡፡ ኢ/ር ቶመስ በድሆች መንደር የተራቡትን በማብላት የተጠሙትን በማጠጣት የታመሙትን በመፈወስ ላይ እንደሚገኝ ሰማ አስጠርቶ ጠየቀው
‹‹ የታል ቤተ-መንግስቴ? ››
ቶማስ መለሰ ‹‹ በሚገባ ተሰርቶ ተጠናቋል ›› ንጉሱም ግራ በመጋባት ስሜት ‹‹ የታል የሚታየኝ?›› በዚህ ጊዜ ቶማስ ትልቁ ስራውን ገለጠ ‹‹ በእርግጥ በምድር ላይ የድንጋይ ቤተ መንግስት ላያዩ ይችላሉ እኔ ግን በሰማይ እርሶ ካሰቡት በላይ ቤተ-መንግስት ሰርቼሎታለው፡፡›› ንጉሱ በንዴት እሚያደርገውን አጣ እዛው ፍርዱን አስተላለፈ ‹‹ እጅ እና እግሩን ቆረጣችሁ ግደሉልኝ›› ንጉስ ተደመጠ ፍረዱ እስኪፈጸም ቶማስ በወይኒ ተጣለ፡፡ በዚህ ጊዜ የንጉሱ ወንድም በድንገተኛ በሽታ ሞተ ንጉሱ ተጠራ ተለቀሰ መላዕክት የልዑሉን ነፍሱን አጅበው ወደ ሰማይ አወጧት ‹‹ ከአብያተ መንግስታቱ ትኖሪበት ዘንድ ያማረሽን ምረጪ›› ተባለች ካሉት እሚያምረውን መረጠች ይሔ ያንቺ አይደለም ቶማስ ለውንድምሽ የሰራው ሰማያዊ ቤተ- መንግስት ነው ተባለች በዚህ ጊዜ የልዑሉ ነፍስ ከስጋው ተዋህዳ ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሳ ሁሉም ለቅሶውን አቆመ ልዑሉም የተመለከተውን መሰከረ ንጉሱም ቶማስ ላይ ስላደረሰው መከራ አለቀሰ ከእስር አስፈትቶም የሰማያዊ ቤተ-መንግስት መገንባቱን እንዲቀጥልለት ከቶማስ ጋር ውሉን አደሰ ሌሎች ባለሃብቶችም የንጉሱን አሰረ ፍኖት ተከትለው ‹የሰማይ ቤተ- መንግስት› መገንባትን ጀመሩ፡፡
❖ @senkesar ❖
ሐዋርያው ከዛም በመቀጠል ከማላባር ጀምሮ እስከ ቻይና በመዝለቅ ወንጌልን ሰብኳል ። በመጨረሻም በ66 ዓ.ም በሚላፖር ከተማ የሚገኙ አምላክያነ ጣኦት ቆዳውን ገፈው በቆዳው ስልቻ በመሥራት በሰውነቱ ላይ ጨው ነስንሰው በቆዳው አሸዋ በመሙላት አሸክመው በአሰቃቂ ሁኔታ እንደገደሉት ታሪኩ ይመሰክራል፡፡ ከዛም ፍልሰተ አጽሙ ከሚላፖር ወደ ኤዴሳ ተዛውሯል፡፡
ኤዴሳ ያሁኗ ታነሻ ኢስያ ፣ ዑር ናት ይህችን ሀገር ካነሳን አይቀር ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊን እናንሳ ቅዱስ ኤፍሬም በ393 ዓ.ም የነጽቢን ከተማ በወራሪዎች እጅ ስትወድቅ ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር ወደዚህች ሀገር ተሰዷል፡፡ ይህች ቦታ ቅዱስ ኤፍሬም ከመናፍቃን ጋር የተጋደለባት ፣ አብዛኞቹን ክህደት ትምህርቶች የሞገተበት ፣ አብዛኞቹን መጽሐፍት ያዘጋጀባት ቦታ ናት፡፡ ይህ ታላቅ አባት ‹ አቤቱ የጸጋህን ማዕበል ግታልኝ › እስከሚል ድረስ ድረሳናትን ደርሷል፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ 370 ዓ.ም ሐምሌ 15 አርፏል፡፡ በታላቅ አባትነቱም ሶሪያዊያን ‹ ጥዑመ ልሳን ፣ መምህረ ዓለም ፣ ዓምደ ቤተ-ክርስቲያን በማለት ይጠሩታል፡፡ በቁጥር ስንክሳራችን ሲገልፀው 14 ሺህ ድርሳናትን እና ተግሳጻትን መድረሱን ያስቀምጣል) ለእኔ ሐዋርያት ላይ ከደረሱት ስቃዮች የሐዋርያው ቶማስ ስቃይ የከፋ ነው የጽናቱን ቅንጣት በልባችን በአማልጅነቱ ያኑርልን፡፡ ግንቦት 26 መታሰቢያው ነው፡፡
ምንጭ፡- ስለ 12ቱ ሐዋርያት በዚሁ በቻናላችን ስም ካዘጋጀነው ጽሑፍ
@senkesar