ከገነት በተሰደደ ጊዜ #የአዳም ተስፋ አንቺ ነሽ፡፡ በግፍ የተገደለ #የአቤል የውሃቱ አንቺ
ነሽ፡፡ #የሴት ቸርነት አንቺ ነሽ፡፡ #የሄኖክ ሥራዎቹ ከክፉ ጥፋት የዳነባት #የኖህ መርከብ
#የሴም ቡራኬው ዕድል ፈንታውም አንቺ ነሽ፡፡
# የአብርሃም እንግድነት #የይስሃቅ መዓዛ #የያዕቆብም መሰላል አንቺ ነሽ፡፡
#ዮሴፍንም የምታረጋጊው አንቺ ነሽ፡፡
#የሙሴ ጽላት #ጳጦስ የተባለች የሲና ዕፅ በካህን #አሮን ልብስ የነበረች ጸናጽል
ዳግመኛም የበቀለች እና ያበበች ያፈራችም በትር አንቺ ነሽ፡፡ #የኢያሱ የምስክሩ ሐወልት
#የጌድዮን ፀምር #የሳሙኤል የሽቱ ሙዳይ እና የዘይት ቀንድ አንቺ
ነሽ፡፡ የተመካባት #የዕሴይ ሥር #የአሚናዳብ ሠረገላ #የዳዊት መሰንቆ #የሰሎሞንም
አክሊል አንቺ ነሽ፡፡ የታጠረች ተክል የተዘጋች የውሃ ምንጭ አንቺ ነሽ፡፡ #የኤልያስ የወርቅ
መሶብ #የኤልሳዕ ጋን አንቺ ነሽ፡፡ #ኢሳይያስ ፅንስን ከድንግልና ጋር የተናገረልሽ #ዳንኤልም ያለሩካቤ መውለድን የተናገረልሽ አንቺ ነሽ፡፡ #ፋራን የምትባል #የዕንባቆም
ተራራ የተዘጋች #የሕዝቅኤል ምስራቅ የቤቴ-ልሔም ሕግ መውጫ #ኤፍራታ የምትባል
ምድር አንቺ ነሽ፡፡ #የሲሎንዲስ ዕፀ ሕይወት #የናሆምንም ቁስል የምታድን #የዘካርያስ
ደስታው #የሚልክያስ ንፅሕት አዳራሽ አንቺ ነሽ፡፡
ነሽ፡፡ #የሴት ቸርነት አንቺ ነሽ፡፡ #የሄኖክ ሥራዎቹ ከክፉ ጥፋት የዳነባት #የኖህ መርከብ
#የሴም ቡራኬው ዕድል ፈንታውም አንቺ ነሽ፡፡
# የአብርሃም እንግድነት #የይስሃቅ መዓዛ #የያዕቆብም መሰላል አንቺ ነሽ፡፡
#ዮሴፍንም የምታረጋጊው አንቺ ነሽ፡፡
#የሙሴ ጽላት #ጳጦስ የተባለች የሲና ዕፅ በካህን #አሮን ልብስ የነበረች ጸናጽል
ዳግመኛም የበቀለች እና ያበበች ያፈራችም በትር አንቺ ነሽ፡፡ #የኢያሱ የምስክሩ ሐወልት
#የጌድዮን ፀምር #የሳሙኤል የሽቱ ሙዳይ እና የዘይት ቀንድ አንቺ
ነሽ፡፡ የተመካባት #የዕሴይ ሥር #የአሚናዳብ ሠረገላ #የዳዊት መሰንቆ #የሰሎሞንም
አክሊል አንቺ ነሽ፡፡ የታጠረች ተክል የተዘጋች የውሃ ምንጭ አንቺ ነሽ፡፡ #የኤልያስ የወርቅ
መሶብ #የኤልሳዕ ጋን አንቺ ነሽ፡፡ #ኢሳይያስ ፅንስን ከድንግልና ጋር የተናገረልሽ #ዳንኤልም ያለሩካቤ መውለድን የተናገረልሽ አንቺ ነሽ፡፡ #ፋራን የምትባል #የዕንባቆም
ተራራ የተዘጋች #የሕዝቅኤል ምስራቅ የቤቴ-ልሔም ሕግ መውጫ #ኤፍራታ የምትባል
ምድር አንቺ ነሽ፡፡ #የሲሎንዲስ ዕፀ ሕይወት #የናሆምንም ቁስል የምታድን #የዘካርያስ
ደስታው #የሚልክያስ ንፅሕት አዳራሽ አንቺ ነሽ፡፡
♥ እንኩዋን ለእመቤታችን
#ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ የጽንሰት በዓል
በሰላም አደረሳችሁ♥
✝ቁጽረታ ( #ጽንሰታ ) ለማርያም✝
ይህችን ዕለት አበው ሊቃውንት "ጥንተ
መድኃኒት_የድኅነት መነሻ ቀን" ሲሉ ይጠሯታል:: ስለ ምን
ነው ቢሉ:- ለዓለም ድኅነት ምክንያት የሆነች የአምላክ እናቱ
የተጸነሰችበት ዕለት በመሆኑ ነው:: አንድም ከአዳም ስሕተት
በሁዋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተጸነሰች የመጀመሪያ ሰው እርሷ
ናትና እንዲህ ይላሉ::
"ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ
እማሕጸን ቅዱስ::"
" #ድንግል_ሆይ ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው:
የተወለድሽበት ማሕጸንም ቅዱስ
ነው::" ( መጽሐፈ_ሰዓታት , ኢሳ. 1:9, መኃ. 4)
ይሕች ዕለት ለኢያቄምና ለሐና ብቻ ሳይሆን ለፍጥረት ሁሉ
የተስፋ ድኅነት ቀን ናትና ሐሴትን ልናደርግ ይገባል::
የእመቤታችን መጸነስስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
ከነገደ #ይሁዳ የሚወለድ #ቅዱስ_ኢያቄም የሚባል ደግ
ሰው ከነገደ #ሌዊ ( #አሮን ) የተወለደች #ሐና የምትባል ደግ
ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ
ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች "ልጅ የላችሁም" በሚል
ይናቁ ነበር::
ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን "ኅጡአ በረከት-ከጸጋ
#እግዚአብሔር የራቀ" ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና
ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ
አረጁ:: እነሱ ግን የሚያመልኩት #የአብርሃምና_ሣራን
አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::
የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን
አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር
ሲጫወቱ የተመለከተች #ቅድስት_ሐና ፈጽማ አለቀሰች::
"እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ
የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ
ፈጥረሃታልን?" ብላ አዘነች::
ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ
ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን
2ቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- #ነጭ_ርግብ ሰማያትን
ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ
አየ::እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ
ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም
ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው "ፈቃደ
እግዚአብሔር ይሁን" አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ
እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::
በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7)
#መልአከ_ብሥራት_ቅዱስ_ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ
እነርሱ ወረደ:: "ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ
የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ" ብሏቸው ተሠወራቸው::
እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::
እንደ ሥርዓቱም በዚህች ቀን አብረው አድረው
#እመ_ብርሃን ተጸነሰች::
" #ኦ_ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ
¤ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ
አይደለም" እንዳለ ሊቁ:: ( #ቅዳሴ_ማርያም )
#ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ የጽንሰት በዓል
በሰላም አደረሳችሁ♥
✝ቁጽረታ ( #ጽንሰታ ) ለማርያም✝
ይህችን ዕለት አበው ሊቃውንት "ጥንተ
መድኃኒት_የድኅነት መነሻ ቀን" ሲሉ ይጠሯታል:: ስለ ምን
ነው ቢሉ:- ለዓለም ድኅነት ምክንያት የሆነች የአምላክ እናቱ
የተጸነሰችበት ዕለት በመሆኑ ነው:: አንድም ከአዳም ስሕተት
በሁዋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተጸነሰች የመጀመሪያ ሰው እርሷ
ናትና እንዲህ ይላሉ::
"ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ
እማሕጸን ቅዱስ::"
" #ድንግል_ሆይ ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው:
የተወለድሽበት ማሕጸንም ቅዱስ
ነው::" ( መጽሐፈ_ሰዓታት , ኢሳ. 1:9, መኃ. 4)
ይሕች ዕለት ለኢያቄምና ለሐና ብቻ ሳይሆን ለፍጥረት ሁሉ
የተስፋ ድኅነት ቀን ናትና ሐሴትን ልናደርግ ይገባል::
የእመቤታችን መጸነስስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
ከነገደ #ይሁዳ የሚወለድ #ቅዱስ_ኢያቄም የሚባል ደግ
ሰው ከነገደ #ሌዊ ( #አሮን ) የተወለደች #ሐና የምትባል ደግ
ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ
ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች "ልጅ የላችሁም" በሚል
ይናቁ ነበር::
ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን "ኅጡአ በረከት-ከጸጋ
#እግዚአብሔር የራቀ" ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና
ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ
አረጁ:: እነሱ ግን የሚያመልኩት #የአብርሃምና_ሣራን
አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::
የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን
አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር
ሲጫወቱ የተመለከተች #ቅድስት_ሐና ፈጽማ አለቀሰች::
"እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ
የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ
ፈጥረሃታልን?" ብላ አዘነች::
ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ
ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን
2ቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- #ነጭ_ርግብ ሰማያትን
ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ
አየ::እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ
ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም
ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው "ፈቃደ
እግዚአብሔር ይሁን" አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ
እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::
በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7)
#መልአከ_ብሥራት_ቅዱስ_ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ
እነርሱ ወረደ:: "ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ
የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ" ብሏቸው ተሠወራቸው::
እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::
እንደ ሥርዓቱም በዚህች ቀን አብረው አድረው
#እመ_ብርሃን ተጸነሰች::
" #ኦ_ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ
¤ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ
አይደለም" እንዳለ ሊቁ:: ( #ቅዳሴ_ማርያም )
♥ቅድስት ኤልሳቤጥ ♥
በወንጌላዊው የተመሰገነች እናታችን ቅድስት
ኤልሳቤጥ ትውልዷ ከነገደ #ሌዊ ነው:: ሐረገ ሙላዷም
ከቅዱስ #አሮን_ካህን ወገን ይመዘዛል:: ከአሮን በቴክታና
በጥሪቃ ወርዶ #ሔርሜላ ላይ ይደርሳል::
✝ይህቺ ሔርሜላ የምትባል ደግ ሴት #ማጣት ("ጣ"
ጠብቆ ይነበብ) የሚባል የተባረከ ሰው አግብታ 3
ቡሩካት ልጆችን ወለደች:: የመጀመሪያዋን 'ማርያም'
አሏት:: እርሷ ቅድስት ሰሎሜን ወለደች:: ሁለተኛዋን
'ሶፍያ' አሏት:: እርሷ ደግሞ ቅድስት ኤልሳቤጥን
ወለደች::
✝ሦስተኛዋ ግን የተለየች ናት:: 'ሐና' ብለው ሰየሟት::
እርሷም የሰማይና የምድር ንግሥት የሆነችውን ድንግል
ማርያምን ወለደች:: በዚህም መሠረት ድንግል ማርያም:
ቅድስት ኤልሳቤጥና ቅድስት ሰሎሜ የእህትማማች
ልጆች ናቸው::
✝ቅድስት ኤልሳቤጥ እድሜዋ በደረሰ ጊዜ ስም አጠራሩ
የከበረ: ደግ ካህን ለሆነ: ቅዱስ #ዘካርያስ አጋቧት::
እርሷ የሊቀ ካህናቱ ሚስት ናትና ክብሯ ከፍ ያለ ነበር::
ምንም ልጅ ባይኖራትም ዘወትር በጸሎትና በጾም:
ምጽዋትንም በማዘውተር: ነዳያንንም በማሰብ የምትኖር
እናትም ነበረች::
ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የነዘካርያስን
ቤተሰብ ያህል ክብሩ የተገለጠለት ፍጡር ይኖራል ብሎ
መናገሩ ይከብዳል:: ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጀመረው
በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ሲል
አጽፎታል::
"ዘካርያስ ካህኑና ቅድስት ኤልሳቤጥ በሰውና
በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ"
ይላቸዋል:: (ሉቃ. 1:6)
✝የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ
መኖር ምን ይረቅ?
ለዚህ አንክሮ (አድናቆት) ይገባል! እሊህ ቅዱሳን ባልና
ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ
ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት
ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ 90 የዘካርያስ 100 ደግሞ
ደርሶ ነበር::
✝ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ
እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ ታላቅ ነቢይን
ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን
ላከላቸው:: ቅድስቲቷ መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው
ጸንሳ ለ6 ወራት ራሷን ሠወረች::
✝ #ድንግል_እመቤታችን ወደ እርሷ መጥታ 'ሰላም'
ባለቻት ጊዜ ምንም ያሳደገቻት ልጇ ማለት ብትሆን:
መንፈስ ቅዱስ ስለ ሞላባት እመ ብርሃንን
አመስግናታለች:: ቡርክት: ብጽእት: ከፍጥረተ ዓለሙ
የከበረች መሆኗንም መስክራለች:: በማሕጸኗ ያለ የ6 ወር ጽንስም የእመ አምላክን ድምጽ ቢሰማ በደስታ ዘሏል:: ለፈጣሪውም ስግደተ-ስባሔ
አቅርቧል:: ቅድስት ኤልሳቤጥ አክላም "ወምንትኑ አነ
ከመ ትምጽኢ ኀቤየ እሙ ለእግዚእየ-የጌታየ እናቱ ወደ
እኔ ትመጪ ዘንድ እንዴት ይገባኛል?" ስትል በትኅትና
ተናግራለች:: ከጌታ እናት ጋር ለ3 ወራት በአንድ ቤት ቆይታለች::
✝ ቅዱስ ዮሐንስ ከተወለደ 2 ዓመት ከ6 ወር በሆነው
ጊዜ ሰብአ ሰገል በመምጣታቸው በእሥራኤል ምድር
የሚገኙ ሕጻናትን ሔሮድስ ቁዝ አስፈጀ:: ትንሽ ቆይቶም
አይሁድ ለሔሮድስ ስለ ቅዱሱ ሕጻን ነገሩት:: "ሲጸነስ
የአባቱን አንደበት የዘጋ: ሲወለድ ደግሞ የከፈተ
'ዮሐንስ' የሚባል ሕጻን አለና እሱንም ግደል" አሉ::
✝እናቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ ይዛው ስትሸሽ ካህኑን
ዘካርያስን ግን በቤተ መቅደስ መካከል ገድለውታል::
አረጋይት ኤልሳቤጥም ሕጻኑን እያሳደገች በገዳመ ዚፋታ
ለ3 (5) ዓመታት ቆይታለች:: ቅዱስ ዮሐንስ 5 (7)
ዓመት ሲሞላው ግን እዚያው በበርሃ እናቱ ዐረፈች:: ከሰማይ
ዘካርያስና ስምዖን ወርደው
ቀበሯት:: #ኤልሳቤጥ ማለት 'እግዚአብሔር መሐላየ
ነው': አንድም 'የጌታ አገልጋይ' ማለት ነው::
በወንጌላዊው የተመሰገነች እናታችን ቅድስት
ኤልሳቤጥ ትውልዷ ከነገደ #ሌዊ ነው:: ሐረገ ሙላዷም
ከቅዱስ #አሮን_ካህን ወገን ይመዘዛል:: ከአሮን በቴክታና
በጥሪቃ ወርዶ #ሔርሜላ ላይ ይደርሳል::
✝ይህቺ ሔርሜላ የምትባል ደግ ሴት #ማጣት ("ጣ"
ጠብቆ ይነበብ) የሚባል የተባረከ ሰው አግብታ 3
ቡሩካት ልጆችን ወለደች:: የመጀመሪያዋን 'ማርያም'
አሏት:: እርሷ ቅድስት ሰሎሜን ወለደች:: ሁለተኛዋን
'ሶፍያ' አሏት:: እርሷ ደግሞ ቅድስት ኤልሳቤጥን
ወለደች::
✝ሦስተኛዋ ግን የተለየች ናት:: 'ሐና' ብለው ሰየሟት::
እርሷም የሰማይና የምድር ንግሥት የሆነችውን ድንግል
ማርያምን ወለደች:: በዚህም መሠረት ድንግል ማርያም:
ቅድስት ኤልሳቤጥና ቅድስት ሰሎሜ የእህትማማች
ልጆች ናቸው::
✝ቅድስት ኤልሳቤጥ እድሜዋ በደረሰ ጊዜ ስም አጠራሩ
የከበረ: ደግ ካህን ለሆነ: ቅዱስ #ዘካርያስ አጋቧት::
እርሷ የሊቀ ካህናቱ ሚስት ናትና ክብሯ ከፍ ያለ ነበር::
ምንም ልጅ ባይኖራትም ዘወትር በጸሎትና በጾም:
ምጽዋትንም በማዘውተር: ነዳያንንም በማሰብ የምትኖር
እናትም ነበረች::
ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የነዘካርያስን
ቤተሰብ ያህል ክብሩ የተገለጠለት ፍጡር ይኖራል ብሎ
መናገሩ ይከብዳል:: ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጀመረው
በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ሲል
አጽፎታል::
"ዘካርያስ ካህኑና ቅድስት ኤልሳቤጥ በሰውና
በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ"
ይላቸዋል:: (ሉቃ. 1:6)
✝የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ
መኖር ምን ይረቅ?
ለዚህ አንክሮ (አድናቆት) ይገባል! እሊህ ቅዱሳን ባልና
ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ
ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት
ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ 90 የዘካርያስ 100 ደግሞ
ደርሶ ነበር::
✝ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ
እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ ታላቅ ነቢይን
ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን
ላከላቸው:: ቅድስቲቷ መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው
ጸንሳ ለ6 ወራት ራሷን ሠወረች::
✝ #ድንግል_እመቤታችን ወደ እርሷ መጥታ 'ሰላም'
ባለቻት ጊዜ ምንም ያሳደገቻት ልጇ ማለት ብትሆን:
መንፈስ ቅዱስ ስለ ሞላባት እመ ብርሃንን
አመስግናታለች:: ቡርክት: ብጽእት: ከፍጥረተ ዓለሙ
የከበረች መሆኗንም መስክራለች:: በማሕጸኗ ያለ የ6 ወር ጽንስም የእመ አምላክን ድምጽ ቢሰማ በደስታ ዘሏል:: ለፈጣሪውም ስግደተ-ስባሔ
አቅርቧል:: ቅድስት ኤልሳቤጥ አክላም "ወምንትኑ አነ
ከመ ትምጽኢ ኀቤየ እሙ ለእግዚእየ-የጌታየ እናቱ ወደ
እኔ ትመጪ ዘንድ እንዴት ይገባኛል?" ስትል በትኅትና
ተናግራለች:: ከጌታ እናት ጋር ለ3 ወራት በአንድ ቤት ቆይታለች::
✝ ቅዱስ ዮሐንስ ከተወለደ 2 ዓመት ከ6 ወር በሆነው
ጊዜ ሰብአ ሰገል በመምጣታቸው በእሥራኤል ምድር
የሚገኙ ሕጻናትን ሔሮድስ ቁዝ አስፈጀ:: ትንሽ ቆይቶም
አይሁድ ለሔሮድስ ስለ ቅዱሱ ሕጻን ነገሩት:: "ሲጸነስ
የአባቱን አንደበት የዘጋ: ሲወለድ ደግሞ የከፈተ
'ዮሐንስ' የሚባል ሕጻን አለና እሱንም ግደል" አሉ::
✝እናቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ ይዛው ስትሸሽ ካህኑን
ዘካርያስን ግን በቤተ መቅደስ መካከል ገድለውታል::
አረጋይት ኤልሳቤጥም ሕጻኑን እያሳደገች በገዳመ ዚፋታ
ለ3 (5) ዓመታት ቆይታለች:: ቅዱስ ዮሐንስ 5 (7)
ዓመት ሲሞላው ግን እዚያው በበርሃ እናቱ ዐረፈች:: ከሰማይ
ዘካርያስና ስምዖን ወርደው
ቀበሯት:: #ኤልሳቤጥ ማለት 'እግዚአብሔር መሐላየ
ነው': አንድም 'የጌታ አገልጋይ' ማለት ነው::