ስንክሳር
7.32K subscribers
825 photos
4 videos
37 files
237 links
በስንክሳር channal ስንክሳሩ ተገልጦ ቅዱሳን ይዘከራሉ፣ ወቅቱን የጠበቁ መረጃዎችን ያገኛሉ፡፡ ይከታተሉን!
Download Telegram
እንኩዋን ለታላላቁ ቅዱሳን #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት:
#ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ እና #ቅዱስ_ቶማስ_ዘመርዓስ
ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ
ቅዱስ #ተክለ_ሃይማኖት ሐዋርያዊ "*+ #ልደት
መልካም ዛፍ
መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ: #
ጸጋ_ዘአብ ካህኑና #እግዚእ_ኃረያ ናቸው:: እርሱ በክህነቱ:
እርሷ በደግነቷ: በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ
ፍሬን ሰጥቷቸዋል:: +በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ
ቢደርስባቸው #ቅዱስ_ሚካኤል: ጸጋ ዘአብን ከሞት: እግዚእ
ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል::
በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል:: +አቡነ ተክለ
ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24, በ1206 (1196) ሲሆን
የተወለዱት ታሕሳስ 24, በ1207 (1197) ዓ/ም ነው::
በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል:: ቤታቸውም
በበረከት ሞልቷል:: #ዕድገት =>የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው
"#ፍሥሃ_ጽዮን" ይሰኛል:: ይሕንን ስም ይዘው: አባታቸው ጸጋ
ዘአብን ተከትለው አድገዋል:: በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን
(ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል:: በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ
አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁና ከወቅቱ ዻዻስ #አባ_
ጌርሎስ ተቀብለዋል:: #መጠራት =>አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮን
ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ
ተሰማ:: የክብር ባለቤት #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ አእላፍ
መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ::
+የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ: "ከዛሬ ጀምሮ
ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን:: አራዊትን
ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ
በግርማ ዐረገ:: ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ
ሰዓትን አላጠፉም:: ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ
ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ:: #አገልግሎት
=>ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል
አገልግሎትን ጀመሩ:: በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (#
ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው
አጠመቁ:: ያንጊዜ #ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት:: 1.ዮዲት
(ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ
አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል: ወይም በባዕድ
አምልኮ ተጠምዷል:: 2.ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት
ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር:: +ግማሹ ሃገር በጨለመበት
ወቅት የደረሱት #ሐዲስ_ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት
ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ::
ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን
(ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል:: #ገዳማዊ ሕይወት =>ቅዱስ
ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው
ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል:: እርሳቸው ከሁሉ
የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል::
+እነዚህም በአቡነ #በጸሎተ_ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት:
በአቡነ #ኢየሱስ_ሞዐ_ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ
ዳሞ ከአቡነ #ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26
ዓመታት አገልግለዋል:: +በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ
በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ #ዞረሬ ተመልሰው በአንዲት በዓት
ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም
6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል:: #
ስድስት ክንፍ =>ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ
ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት
መካናት ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ #እሥራኤል የገቡት
በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ
ነበር:: +የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት #አባ_ሚካኤል ጋርም
ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ
በሁዋላ ነው:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ
ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ
እንባቸው ይፈስ ነበር:: +ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው
ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ:-
¤በቤተ መቅደስ ብስራቱን ¤በቤተ ልሔም ልደቱን ¤በቤተ ዮሴፍ
ግዝረቱን ¤በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን ¤በቤተ አልዓዛር
ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር:: +የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል
ወደሆነው #ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ
ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን
ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ:: በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ
#እመቤታችን_ድንግል_ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን
ወደሰማይ አሳረገቻቸው:: +በዚያም:- ¤የብርሃን ዐይን
ተቀብለው ¤6 ክንፍ አብቅለው ¤የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
¤ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው ¤ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም
ተደምረው ¤ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
¤"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ
ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል:: #ተአምራት
=>የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው::
*ሙት አንስተዋል *ድውያንን ፈውሰዋል *አጋንንትን አሳደዋል
*እሳትን ጨብጠዋል *በክንፍ በረዋል *ደመናን ዙፋን
አድርገዋል:: +ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን
መሥርተዋል:: በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት
አብረው ኑረዋል:: በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና:: #ዕረፍት
=>ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን
ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: አእላፍ ፍሬን አፍርተው:
በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24,
በ1306 (1296) ዓ/ም ዐርፈዋል:: ጌታ: ድንግል ማርያምና
ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል:: 10 ትውልድ
የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል::
💚💛 አባ ፊልዾስ ዘደብረ ሊባኖስ 💛
ታላቁ ኢትዮዽያዊ ጻድቅ: ሐዋርያና ሰማዕት #አቡነ_ፊልዾስ የጻድቁ #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት ደቀ መዝሙር ሲሆኑ የተወለዱት በምድረ ሽዋ በ1266 ዓ/ም ነው:: ከልጅነታቸው ጀምረው ምሥጢር ተመራማሪና መጻሕፍትን መርማሪ የነበሩት ጻድቁ የመነኑት ገና በ15 ዓመታቸው ነበር::

#በደብረ_ሊባኖስ በአሞክሮ ለ3 ዓመታት ቆይተው መንኩሰዋል:: ለ22 ዓመታትም የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ደቀ መዝሙር ሆነው አገልግለዋል:: አቡነ ተክለ ሃይማኖት በ1306 ዓ/ም ነሐሴ 24 ቀን ሲያርፉ የተተኩት አባ ኤልሳዕ ቢሆኑም ለ3 ወራት ቆይተው ዐርፈዋል::

በ1307 ዓ/ም አቡነ ፊልዾስ የደብረ ሊባኖስ አበ ምኔት (እጨጌ) ሁነዋል:: ገዳሙንም ለ28 ዓመታት መርተዋል:: ከዚያም በዘመነ አፄ ዓምደ ጽዮንና በአፄ ሰይፈ አርዕድ ብዙ ስደት: መከራ: እሥራትና ግርፋት ደርሶባቸዋል:: ምክንያቱ ደግሞ እውነትን መናገራቸውና ነገሥታቱን መገሰጻቸው ነበር:: በስደትም ለ6 ዓመታት ከ9 ወራት ቆይተዋል::

ሃገሪቱን በስብከተ ወንጌል ካበሩ #12ቱ_ንቡራነ_እድ አንዱ የሆኑት #እጨጌ አባ ፊልዾስ በተወለዱ በ74 ዓመት ከ9 ወራቸው በ1341 ዓ/ም ዐርፈዋል:: የተቀበሩት #በደብረ_ዕንቁ ሲሆን ካረፉ በ140 ዓመት #አቡነ_መርሐ_ክርስቶስ ዐጽማቸውን አፍልሰዋል::
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
ከቅዱሳኑ እንድራኒቆስ ወአትናስያ እና ከጻድቁ አቡነ ፊልዾስ በረከትን ይክፈለን::

@senkesar @senkesar
ባልንጀራህን አትቀየመው ።
ወኢትትቀየም ቢጸከ ⇨ ባልንጀራህን አትቀየም ⇨ be not angry with thy
neighbour" [ሢራ. ፳፰፥፯]
. እመቤታችን ያለ ምንም ነውር ፣ ሰይጣን ግን ያለ ምንም ክብር ሆነው ይኖራሉ።
. ቅዱሳን በሚደነቅ ንጽሕና እኛም በታላቅ ስንፍና የምንመላለስ ነን።
ነገር ግን ከበጎዎች ጥቂት ድክመት ከደካሞች ጥቂት በጎነት አይታጣም ።
ለዚህ ነው መጽሐፋችን ⇨ ፍጡር ከሆነ ከ #እመቤታችን በቀር ጥቂት ጽነት የሌለበት
የለም! ከነጭ ላም ከጉያዋ ከብሻሻዋ (ከብሽሽቷ) ቢፈልጉ ጥቂት ጥቁር እንዳይጠፋ፤
⇨ ፍጡርም ሆኖ ከ #ዲያብሎስ በቀር ጥቂት ቸርነት የሌለው የለምና! ከጥቁር ላም
ከጉያዋ ከብሻሻዋ ቢፈልጉ ጥቂት ነጭ እንዳይጠፋ፤
⇝ የኃጥኡ ምግባር ለጻድቁ ክብር ያበዛለታል የጻድቁም ክፋት በኃጥኡ ፍዳ የመጣበታልና

እንደነ #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት
እንደነ #አቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ ያለ ቢሆንሳ ቢሉ ዝክራቸውን ለዘከረ ስማቸውን
ለጠራ ክብር ሲያሰጡ ይኖራሉ ይላል ፍትሕ መንፈሳዊ።(ፍትሐ ነገሥት ምዕ ፲ ቁ ፫፻፶፭
ትርጓሜ)
✧ መቼም #እኔ_ደካማ_ነኝ ! በሀገራችን እና በቤተክርስቲያናችን ላይ በዘመናችን
የመጣው ይኼ ፈተና በእኔ ምክንያት
① ነፍሴን በማጉደሌ፣ ② አምላኬን በመበደሌ እና ③ ባልንጀራዬን በማቃለሌ መሆኑን
አምናለሁ!
☞ለነፍሴ ድርሻዬን ለመወጣት እጥራለሁ!
☞ እግዚአብሔር ይቅር እንዲለኝ ለምኑልኝ (ክፍለ ሥላሴ) መቼም እርሱ እግዚአብሔር
ይቀየም ዘንድ እንደሰው አይደለምና በምሕረቱ እታመናለሁ ( ኢኮነ ከመ ዕጓለ መሕያው
ዘይትቄየም ዮዲ.፰ ፥፲፮)
☞ እናንተን ባልንጀሮቼን አልሜ ሰው ለመጉዳት አልያም ተሳስቼ ለመርዳት በጻፍኩት፣
በተናገርኩት ባደረኩትም ይቅር በሉኝ ከዚህ አልፎም ከእኔ በሚጠበቀውም መጠን
ድርሻዬን ሳልወጣ ሳልጽፍ፣ ሳልናገር እና ሳላደርግ በቀረሁትም ጭምር በእጅጉ ይቅርታ!
ሐሳቤን የበለጠ ያጠነክራል ብዬ ይኽን ከቅዱስ መጽሐፍ [የጠቢቡ ሢራክን ቃልና የሊቁን
የሕማማት ሰላምታ ክፍል] ለትምህርትና ለተማጽኖ አስቀምጬ ለ"ጥቂት" ጊዜ ልሰናበት።
“ አንተ ሰው ሆነህ እንዳንተ ያለውን ሰው ሳትቀየም እግዚአብሔርን እንዴት ይቅር
በለኝ ትለዋለህ? እንዳንተ ያለ ሰው ይቅር ሳትል ኃጢዓትህን ያስተሰርይልህ ዘንድ
እንግዲህ እንዴት ትለምነዋለህ ኃጢዓትህን አስበህ ጠብን ተዋት ሞትን አስበው
መቃብርንም አስበው ትእዛዙንም ጠብቅ፤ ሕጉን አስበህ ባልንጀራህን አትቀየም" ሢራ ፳፰፥
፪–፯
በከመ ልማድኪ በሊ ኀበ ወልድኪ ከሃሊ
.ኦ ርኅሩኅ ኢተበቃሊ
.ያጠፍኦኑ ለሥዕሉ ሠዓሊ ፦ ኪነተከ ዘትካት ኀሊ።
እንደዚህ በዪ እንደልማድሽ
. ሁሉን ወደሚችለው ልጅሽ
. የምትራራ ነህና የማትበቀል
. የእጅህን ድንቅ ሥራ ጠብቅ ፣ የቀደመውን ያንተን አምሳል
ሠዓሊ ሥዕሉን እንደምን ያጠፋል?!
‘እናታችን ድንግል’ ቂም ይዞ ከማይበቀለው ጽድቀ አሚንን ፣ ርትዓተ ልቡናን
ከሚያድለው ልጅሽ ይቅርታውን ይልክልን ዘንድ ለምኚልን!