♥እንኳዋን ለሐዋርያው "ቅዱስ ናትናኤል" ዓመታዊ
የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ♥
+✝ቅዱስ ናትናኤል ✝+
በቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት ከቅዱሳን ሐዋርያት
መካከል ዘግይቶ ሰማዕትነትን የተቀበለ ይህ ቅዱስ ሐዋርያ
ነው:: ቅዱሱ ሐዋርያ የተወለደው ከእሥራኤላውያን ወላጆቹ
ጌታችን በተወለደበት ዘመን አካባቢ ነው:: ይህ በምን
ይታወቃል ቢሉ እርሱ ሕጻን እያለ ሔሮድስ 144,000
ሕጻናትን ሲፈጅ እርሱ ግን በእግዚአብሔር ጥበብ ተርፏል::
እናቱ በቅርጫት ውስጥ አድርጋ የበለስ ዛፍ ላይ አስቀምጣው ተደብቃ ታጠባው ነበር::
ለሐዋርያው ወላጆቹ ያወጡለት ስም #ስምዖን ሲሆን
ጌታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ደግሞ #ናትናኤል ብሎታል::
በባልንጀሮቹ ሐዋርያት ደግሞ የቃናው ስምዖን (ገሊላ ቃና
አካባቢ ስላደገ) አንዳንዴም #ቀናተኛው ስምዖን ይሉት ነበር::
ምሑረ ኦሪት ነበርና ዘወትር ለሕግ ይቀና ነበር:: በገሊላ ቃና
ሰርግ የደገሰው #ዶኪማስ የቅዱስ ናትናኤል የአጎት ልጅ
ነው:: ጌታና ደቀ መዛሙርቱን ዶኪማስ የጠራበት አንዱ
ምክንያትም ይሔው ነው::ቅዱስ ናትናኤል ኦሪትን #ከገማልያል ተምሮ : ከበለስ ቁጭ
ብሎ ይተክዝ ነበር:: "መሲሕ ምነው ቀረህ?" እያለም ይተክዝ
ነበር:: ማዕምረ ኅቡዓት አምላካችን ክርስቶስ ይህንን አውቆ
#በፊልዾስ አማካኝነት ጠርቶታል::
ናትናኤል ለጊዜው ተከራክሮ ነበር:: በሁዋላ ግን የጌታችንን
ማንነት በደቂቃዎች ተረድቶ አምኗል:: ጌታችንም "ክዳት
ሽንገላ በልቡ ውስጥ የሌለበት ንጹሕ እሥራኤላዊ" ሲል
አመስግኖታል::
ሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል ከጌታችን እግር ሥር ምስጢረ
መንግስተ ሰማያትን ተምሮ: በጸጋ መንፈስ ቅዱስም ሰክሮ:
ብዙ አሕዛብን ከጨለማ (ጣኦት አምልኮ) ወደ ብርሃን (አሚነ
ክርስቶስ) መልሷል::
እጅግ ብዙ መከራንም ተቀብሏል::
የጌታችን ወንድም የተባለ #ቅዱስ_ያዕቆብ በአይሁድ
ከተገደለ በሁዋላም ቅዱስ ናትናኤል የኢየሩሳሌም 2ኛ
ኤዺስ ቆዾስ ሆኖ አገልግሏል:: ከአይሁድም ዘንድ ብዙ መከራ
ደርሶበታል:: በመጨረሻም በዚህች ዕለት በሰማዕትነት
አልፏል:: በገድለ ሐዋርያት ላይ እንደተጠቀሰው ቅዱሱ
ሰማዕት የሆነው በ150 ዓመቱ ነው:: ያ ማለት ደግሞ
ከሐዋርያት አባቶች በመጨረሻ ያረፈው እርሱ ነው ያሰኛል::
የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ♥
+✝ቅዱስ ናትናኤል ✝+
በቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት ከቅዱሳን ሐዋርያት
መካከል ዘግይቶ ሰማዕትነትን የተቀበለ ይህ ቅዱስ ሐዋርያ
ነው:: ቅዱሱ ሐዋርያ የተወለደው ከእሥራኤላውያን ወላጆቹ
ጌታችን በተወለደበት ዘመን አካባቢ ነው:: ይህ በምን
ይታወቃል ቢሉ እርሱ ሕጻን እያለ ሔሮድስ 144,000
ሕጻናትን ሲፈጅ እርሱ ግን በእግዚአብሔር ጥበብ ተርፏል::
እናቱ በቅርጫት ውስጥ አድርጋ የበለስ ዛፍ ላይ አስቀምጣው ተደብቃ ታጠባው ነበር::
ለሐዋርያው ወላጆቹ ያወጡለት ስም #ስምዖን ሲሆን
ጌታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ደግሞ #ናትናኤል ብሎታል::
በባልንጀሮቹ ሐዋርያት ደግሞ የቃናው ስምዖን (ገሊላ ቃና
አካባቢ ስላደገ) አንዳንዴም #ቀናተኛው ስምዖን ይሉት ነበር::
ምሑረ ኦሪት ነበርና ዘወትር ለሕግ ይቀና ነበር:: በገሊላ ቃና
ሰርግ የደገሰው #ዶኪማስ የቅዱስ ናትናኤል የአጎት ልጅ
ነው:: ጌታና ደቀ መዛሙርቱን ዶኪማስ የጠራበት አንዱ
ምክንያትም ይሔው ነው::ቅዱስ ናትናኤል ኦሪትን #ከገማልያል ተምሮ : ከበለስ ቁጭ
ብሎ ይተክዝ ነበር:: "መሲሕ ምነው ቀረህ?" እያለም ይተክዝ
ነበር:: ማዕምረ ኅቡዓት አምላካችን ክርስቶስ ይህንን አውቆ
#በፊልዾስ አማካኝነት ጠርቶታል::
ናትናኤል ለጊዜው ተከራክሮ ነበር:: በሁዋላ ግን የጌታችንን
ማንነት በደቂቃዎች ተረድቶ አምኗል:: ጌታችንም "ክዳት
ሽንገላ በልቡ ውስጥ የሌለበት ንጹሕ እሥራኤላዊ" ሲል
አመስግኖታል::
ሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል ከጌታችን እግር ሥር ምስጢረ
መንግስተ ሰማያትን ተምሮ: በጸጋ መንፈስ ቅዱስም ሰክሮ:
ብዙ አሕዛብን ከጨለማ (ጣኦት አምልኮ) ወደ ብርሃን (አሚነ
ክርስቶስ) መልሷል::
እጅግ ብዙ መከራንም ተቀብሏል::
የጌታችን ወንድም የተባለ #ቅዱስ_ያዕቆብ በአይሁድ
ከተገደለ በሁዋላም ቅዱስ ናትናኤል የኢየሩሳሌም 2ኛ
ኤዺስ ቆዾስ ሆኖ አገልግሏል:: ከአይሁድም ዘንድ ብዙ መከራ
ደርሶበታል:: በመጨረሻም በዚህች ዕለት በሰማዕትነት
አልፏል:: በገድለ ሐዋርያት ላይ እንደተጠቀሰው ቅዱሱ
ሰማዕት የሆነው በ150 ዓመቱ ነው:: ያ ማለት ደግሞ
ከሐዋርያት አባቶች በመጨረሻ ያረፈው እርሱ ነው ያሰኛል::