የቱ ጋር?
(ቶማስ አድማሱ)
ከአድዋ በፊት ያው ከድሉም ኋላ
ላንድ የዝና ታሪክ ላንድ የጋራ ጥላ
እንዴት ታጣ መላ?
እንደ ሰው ወደታች ያወረደን ማነው?
ከአድዋ ኋላ የቱ ጋር ነው የቆምነው?
*
እጃችን ማሸነፍ ረስቶ
ልባችን ወኔ ተነስቶ
ነፍሳችን ሃቅ እውነት ስቶ!
በካቻምና ታሪክ ዜማ
ልብ ባይን ሲደማ።
እዚያ ጋር ነው የቆምን እግር በእግር ሲወጋ?
ባንዲራ ላብ ማበስ ትቶ እግር ጠልፎ ሲያዋጋ፡፡
አያምም??
/ያማል/
ጎን ላይ እንደመወጋት
ተሰቅሎ በችንካር ቅጣት
ሆምጣጤ ከከርቤ ቅንጣት
ከሰፍነግ ላይ እንደመጋት፡፡
እሳት ላይ እንደቆመ እግር
እንደ ሰፋ የአራሽ ድግር
ያሸነፉት ሲያሸንፍ የጣሉት መልሶ ሲጥል
ሲያቃጥል!!!
*
“መንገዳችን ያሳዝናል”
የምንሄደው ያሰጋናል
አሁን ደሞ እንዲህ ሆነናል
/እንዲህ/
ይሁዳን እያሞገሱ ከዮሐንስ ጋር መጣለት
እዚህ በርባንን መስደብ በዚያ በኩል መስቀል መጥላት
በጉን ወዶ ተንከባክቦ ምን ይሉታል መጠየፍ ላት??
***
የጣልናቸው እየጣሉን
ያዘልናቸው እየጠሉን
እውነት?
አፈር አፈርን በላ?
ድንጋይ ድንጋይ ላይ ሰላ?
የቱ ጋር ነው የቆምን ከአድዋ ኋላ??
#ቶማስአድማሱ #ግጥምሲጥም #ጥበብበአደባባይ #ግጥማዊቅዳሜ
#ThomasAdmasu #tba #tibebbeqdebabay #digitalartfestival #artinaddis #gitemsitem
(ቶማስ አድማሱ)
ከአድዋ በፊት ያው ከድሉም ኋላ
ላንድ የዝና ታሪክ ላንድ የጋራ ጥላ
እንዴት ታጣ መላ?
እንደ ሰው ወደታች ያወረደን ማነው?
ከአድዋ ኋላ የቱ ጋር ነው የቆምነው?
*
እጃችን ማሸነፍ ረስቶ
ልባችን ወኔ ተነስቶ
ነፍሳችን ሃቅ እውነት ስቶ!
በካቻምና ታሪክ ዜማ
ልብ ባይን ሲደማ።
እዚያ ጋር ነው የቆምን እግር በእግር ሲወጋ?
ባንዲራ ላብ ማበስ ትቶ እግር ጠልፎ ሲያዋጋ፡፡
አያምም??
/ያማል/
ጎን ላይ እንደመወጋት
ተሰቅሎ በችንካር ቅጣት
ሆምጣጤ ከከርቤ ቅንጣት
ከሰፍነግ ላይ እንደመጋት፡፡
እሳት ላይ እንደቆመ እግር
እንደ ሰፋ የአራሽ ድግር
ያሸነፉት ሲያሸንፍ የጣሉት መልሶ ሲጥል
ሲያቃጥል!!!
*
“መንገዳችን ያሳዝናል”
የምንሄደው ያሰጋናል
አሁን ደሞ እንዲህ ሆነናል
/እንዲህ/
ይሁዳን እያሞገሱ ከዮሐንስ ጋር መጣለት
እዚህ በርባንን መስደብ በዚያ በኩል መስቀል መጥላት
በጉን ወዶ ተንከባክቦ ምን ይሉታል መጠየፍ ላት??
***
የጣልናቸው እየጣሉን
ያዘልናቸው እየጠሉን
እውነት?
አፈር አፈርን በላ?
ድንጋይ ድንጋይ ላይ ሰላ?
የቱ ጋር ነው የቆምን ከአድዋ ኋላ??
#ቶማስአድማሱ #ግጥምሲጥም #ጥበብበአደባባይ #ግጥማዊቅዳሜ
#ThomasAdmasu #tba #tibebbeqdebabay #digitalartfestival #artinaddis #gitemsitem
እኔ ፀሐይ
እሰይ አደይ ፈነዳች፤
የመስከረም ፀሐይ ወጣች፤
አበባየሁ አሉ ልጆች፤
አበባ ያልያዙ እጆች፤
በምርቃት ሊወለዱ 30 እና 60 ጥጆች፤
ቀልዬ ከሶሪት ላባ፤
ካባቴ ገቦ ወጥቼ ከናቴ ማ'ጸን ስገባ፤
ይኸው መስከረም ጠባ።
እልል አበብሽ ብዬ
ለምለም አደይ ነቅዬ፤
እንግጫሽ አበባ፤አበባየሽ ለምለም
የመስከረም ጸሐይ ወጣች
ከእንዲህ ነጎድጓድ መፍራት በሰማይ ማማረር የለም።
በክረምት ጠል ርሶ፤ ሊመጣ ጸደይ ያማረ፤
በምርቃት ወንድ ሊሰጥ በሴት አካል ወንድ አደረ።
አበባ ነኝ እኔ አበባ
ከአድማስ ፀሐይ ሳትገባ
መታፈር በከንፈር ያልኩ ጥርሴ መንታ የሚያነባ
ቢጫነት በሆዴ ያለ ልቤ መዓት የሚያደባ፤
አበባ ነኝ እኔ አበባ።
ለወደድኩት የዓይን ጥም
ከካህን ማስር ምፈታ ከደብተራ ምጠመጥም
የጠላሁት የሚሰጥም
ለተናቀ ረባዳ
ለተከበረ ሰው ሜዳ።
አበባ ነኝ እኔ አበባ።
እሰይ አደይ ፈነዳች፤ ይኸው ጳጉሜ ከነዳች።
ከሰማይ ምንም ሳይጎድል ከመሬት ሳይጨምር አንዳች።
(ቶ)በምን አገባኝ ፍካሬ አክናፌን ስዘረጋጋ
(ማ) ነህ ብሎ ለሚያዛጋ
(ስ)ብዬ አፉን የማሲዝ የማልፈጥን የማልረጋ።
መሬት ቢጫ ስትለብስ። የአምናን መከራ አልፌ
እልል የምል ችቦ ወገብ ተደግፌ
ለከርሞ ትልሜን ለፍፌ
የሚል ግጥም ሳሰናዳ
እሰይ አደይ ፈነዳ::
#ቶማስአድማሱ #ግጥምሲጥም #ጥበብበአደባባይ #ግጥማዊቅዳሜ
#ThomasAdmasu #tba #tibebbeqdebabay #digitalartfestival #artinaddis #gitemsitem
እሰይ አደይ ፈነዳች፤
የመስከረም ፀሐይ ወጣች፤
አበባየሁ አሉ ልጆች፤
አበባ ያልያዙ እጆች፤
በምርቃት ሊወለዱ 30 እና 60 ጥጆች፤
ቀልዬ ከሶሪት ላባ፤
ካባቴ ገቦ ወጥቼ ከናቴ ማ'ጸን ስገባ፤
ይኸው መስከረም ጠባ።
እልል አበብሽ ብዬ
ለምለም አደይ ነቅዬ፤
እንግጫሽ አበባ፤አበባየሽ ለምለም
የመስከረም ጸሐይ ወጣች
ከእንዲህ ነጎድጓድ መፍራት በሰማይ ማማረር የለም።
በክረምት ጠል ርሶ፤ ሊመጣ ጸደይ ያማረ፤
በምርቃት ወንድ ሊሰጥ በሴት አካል ወንድ አደረ።
አበባ ነኝ እኔ አበባ
ከአድማስ ፀሐይ ሳትገባ
መታፈር በከንፈር ያልኩ ጥርሴ መንታ የሚያነባ
ቢጫነት በሆዴ ያለ ልቤ መዓት የሚያደባ፤
አበባ ነኝ እኔ አበባ።
ለወደድኩት የዓይን ጥም
ከካህን ማስር ምፈታ ከደብተራ ምጠመጥም
የጠላሁት የሚሰጥም
ለተናቀ ረባዳ
ለተከበረ ሰው ሜዳ።
አበባ ነኝ እኔ አበባ።
እሰይ አደይ ፈነዳች፤ ይኸው ጳጉሜ ከነዳች።
ከሰማይ ምንም ሳይጎድል ከመሬት ሳይጨምር አንዳች።
(ቶ)በምን አገባኝ ፍካሬ አክናፌን ስዘረጋጋ
(ማ) ነህ ብሎ ለሚያዛጋ
(ስ)ብዬ አፉን የማሲዝ የማልፈጥን የማልረጋ።
መሬት ቢጫ ስትለብስ። የአምናን መከራ አልፌ
እልል የምል ችቦ ወገብ ተደግፌ
ለከርሞ ትልሜን ለፍፌ
የሚል ግጥም ሳሰናዳ
እሰይ አደይ ፈነዳ::
#ቶማስአድማሱ #ግጥምሲጥም #ጥበብበአደባባይ #ግጥማዊቅዳሜ
#ThomasAdmasu #tba #tibebbeqdebabay #digitalartfestival #artinaddis #gitemsitem