#ቀን_ስድስት ፮/6 ቅዳሜ
" ሙሴም በምድረ በዳ እባብን እንደ ሰቀለ እንዲሁ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ የሰው ልጅ ይሰቀል ይገባዋል።"
(የዮሐንስ ወንጌል 3:14-15)
እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን ጊዜ ህዝቡን ከስጋ ሞት ሊያድን ሙሴን የነሀሱን እባብ በመስቀል ላይ እንዲሰቅል አደረገ ፡፡ ያንን የተሰቀለ እባብ ያየ ሁላ ከስጋዉ ሞት ይድን ነበር ፡፡ በእርግጥ በመስቀል ላይ የተሰቀለዉ እባብ የሚወክለዉ እርግማንንን ሀጢያትን ክፋትን በደልን ነበር ፡፡
በሚሻለዉ በአዲሱ ኪዳን ግን እግዚአብሔር ህዝቡን ከስጋዊ ሞት ሳይሆን ከስጋ ሞት ከሚከፋዉ ዘላለማዊ ሞት ሊያድን አንድያ ልጁን በመስቀል ላይ እንዲሞት ወሰነ ፡፡ ኃጢያት የማያዉቀዉንም ቅዱስ ልጁን በመስቀል ላይ ስለሁላችን በደል ኃጢያት አርጎ ስለኛ ክፋት እኛን ለማዳን ሰቀለዉ ፡፡
ማጣቀሻ
(ኦሪት ዘኍልቍ ምዕራፍ 21)
6፤ እግዚአብሔርም በሕዝቡ ላይ እባቦችን ሰደደ፥ ሕዝቡንም ነደፉ፤ ከእስራኤልም ብዙ ሰዎች ሞቱ።
7፤ ሕዝቡም ወደ ሙሴ መጥተው። በእግዚአብሔርና በአንተ ላይ ስለ ተናገርን በድለናል፤ እባቦችን ከእኛ ያርቅልን ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸልይልን አሉት።
8፤ ሙሴም ስለ ሕዝቡ ጸለየ። እግዚአብሔርም ሙሴን። እባብን ሠርተህ በዓላማ ላይ ስቀል፤ የተነደፈውም ሁሉ ሲያያት በሕይወት ይኖራል አለው።
9፤ ሙሴም የናሱን እባብ ሠርቶ በዓላማ ላይ ሰቀለ፤ እባብም የነደፈችው ሰው ሁሉ የናሱን እባብ ባየ ጊዜ ዳነ።
2ኛ ወደ ቆሮንቶስ 5:21
እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው።
መልካም ቀን!
" ሙሴም በምድረ በዳ እባብን እንደ ሰቀለ እንዲሁ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ የሰው ልጅ ይሰቀል ይገባዋል።"
(የዮሐንስ ወንጌል 3:14-15)
እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን ጊዜ ህዝቡን ከስጋ ሞት ሊያድን ሙሴን የነሀሱን እባብ በመስቀል ላይ እንዲሰቅል አደረገ ፡፡ ያንን የተሰቀለ እባብ ያየ ሁላ ከስጋዉ ሞት ይድን ነበር ፡፡ በእርግጥ በመስቀል ላይ የተሰቀለዉ እባብ የሚወክለዉ እርግማንንን ሀጢያትን ክፋትን በደልን ነበር ፡፡
በሚሻለዉ በአዲሱ ኪዳን ግን እግዚአብሔር ህዝቡን ከስጋዊ ሞት ሳይሆን ከስጋ ሞት ከሚከፋዉ ዘላለማዊ ሞት ሊያድን አንድያ ልጁን በመስቀል ላይ እንዲሞት ወሰነ ፡፡ ኃጢያት የማያዉቀዉንም ቅዱስ ልጁን በመስቀል ላይ ስለሁላችን በደል ኃጢያት አርጎ ስለኛ ክፋት እኛን ለማዳን ሰቀለዉ ፡፡
ማጣቀሻ
(ኦሪት ዘኍልቍ ምዕራፍ 21)
6፤ እግዚአብሔርም በሕዝቡ ላይ እባቦችን ሰደደ፥ ሕዝቡንም ነደፉ፤ ከእስራኤልም ብዙ ሰዎች ሞቱ።
7፤ ሕዝቡም ወደ ሙሴ መጥተው። በእግዚአብሔርና በአንተ ላይ ስለ ተናገርን በድለናል፤ እባቦችን ከእኛ ያርቅልን ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸልይልን አሉት።
8፤ ሙሴም ስለ ሕዝቡ ጸለየ። እግዚአብሔርም ሙሴን። እባብን ሠርተህ በዓላማ ላይ ስቀል፤ የተነደፈውም ሁሉ ሲያያት በሕይወት ይኖራል አለው።
9፤ ሙሴም የናሱን እባብ ሠርቶ በዓላማ ላይ ሰቀለ፤ እባብም የነደፈችው ሰው ሁሉ የናሱን እባብ ባየ ጊዜ ዳነ።
2ኛ ወደ ቆሮንቶስ 5:21
እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው።
መልካም ቀን!