የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ክልሎች ጠቅላላ ጉባኤያት በመካሄድ ላይ መሆናቸው ተገለጸ።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ክልሎች ካለፈው ሐምሌ ወር ጀምሮ ጠቅላላ ጉባኤያቸውን በማካሄድ ላይ የሚገኙ ሲሆን ባሳለፍነው ሳምንት ነሃሴ 2 እና 3/2017 ዓ.ም ጉባኤዎቹ በመካከለኛው ስምጥ ሸለቆ ክልል፤ ሐዋሳ ክልል፤ ዲላና አካባቢው ክልል፤ በንሳ ዳዬ ጊዜያዊ ክልል፤ በሻኪሶ ጊዜያዊ ክልል እና ጅዳ ቆርኬ ጊዜያዊ ክልሎች ተካሂደዋል። በእነዚህ ጠቅላላ ጉባኤዎች በክልሎቹ ስር ከሚገኙ አጥቢያዎች የተወከሉ መሪዎችና አገልጋዮች ተገኝተዋል።
በጠቅላላ ጉባኤው የ2017 ዓ.ም ሪፖርትና የ2018 በጀት አመት እቅድ ሲቀርብ አዳዲስ የመሪዎች ምርጫና ሹመት እንዲሁም በታማኝነት መዋጮአቸውን ለሚከፍሉ አጥቢያዎች የእውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቷል።
በመጨረሻም በተጠናቀቀው የበጀት አመት እድገት ያሳዩ 18 ስርጭት ጣቢዎች ለጉባኤያቱ ቀርበው ወደ አጥቢያነት አንዲያድጉ መሪዎቹ አጽድቀዋል።
መረጃውን ከቤተ ክርስቲያኒቱ የፌስቡክ ገጽ ላይ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ክልሎች ካለፈው ሐምሌ ወር ጀምሮ ጠቅላላ ጉባኤያቸውን በማካሄድ ላይ የሚገኙ ሲሆን ባሳለፍነው ሳምንት ነሃሴ 2 እና 3/2017 ዓ.ም ጉባኤዎቹ በመካከለኛው ስምጥ ሸለቆ ክልል፤ ሐዋሳ ክልል፤ ዲላና አካባቢው ክልል፤ በንሳ ዳዬ ጊዜያዊ ክልል፤ በሻኪሶ ጊዜያዊ ክልል እና ጅዳ ቆርኬ ጊዜያዊ ክልሎች ተካሂደዋል። በእነዚህ ጠቅላላ ጉባኤዎች በክልሎቹ ስር ከሚገኙ አጥቢያዎች የተወከሉ መሪዎችና አገልጋዮች ተገኝተዋል።
በጠቅላላ ጉባኤው የ2017 ዓ.ም ሪፖርትና የ2018 በጀት አመት እቅድ ሲቀርብ አዳዲስ የመሪዎች ምርጫና ሹመት እንዲሁም በታማኝነት መዋጮአቸውን ለሚከፍሉ አጥቢያዎች የእውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቷል።
በመጨረሻም በተጠናቀቀው የበጀት አመት እድገት ያሳዩ 18 ስርጭት ጣቢዎች ለጉባኤያቱ ቀርበው ወደ አጥቢያነት አንዲያድጉ መሪዎቹ አጽድቀዋል።
መረጃውን ከቤተ ክርስቲያኒቱ የፌስቡክ ገጽ ላይ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
❤1🙏1
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ዋናው ቢሮ አገልጋዮችና ሰራተኞች ቤተክርስቲያኒቱ ከነሃሴ 1-11/2017 ዓ.ም ያወጀችውን ሀገር አቀፍ ጾምና ጸሎት ተከትሎ በዋናው ቢሮ በሚገኘው የመሰብሰቢያ አዳራሽ የእግዚአብሔርን ፊት መፈለግ ጀምረዋል።
በምድራችን ኢትዮጵያ ሰላም ላይ ትኩረቱን ባደረገው በዚህ ጾምና ጸሎት ጉባኤው በንስሀ እና ምልጃ ልምናውን ለእግዚአብሔር አቅርቧል።
"በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢፈግሉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።" 2ኛ ዜና 7÷14
መረጃውን ከቤተ ክርስቲያኒቱ የፌስቡክ ገጽ ላይ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
በምድራችን ኢትዮጵያ ሰላም ላይ ትኩረቱን ባደረገው በዚህ ጾምና ጸሎት ጉባኤው በንስሀ እና ምልጃ ልምናውን ለእግዚአብሔር አቅርቧል።
"በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢፈግሉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።" 2ኛ ዜና 7÷14
መረጃውን ከቤተ ክርስቲያኒቱ የፌስቡክ ገጽ ላይ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
❤10
የኢት./ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ በልጆችና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ አዘጋጅነት ወጣቶችን ለመሪነት የማሳደግ ስልጠና በጉዲና ቱምሳ ሁለንተናዊ የስልጠና ማዕከል ተካሄደ።
የኢት./ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ በልጆችና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ አዘጋጅነት ወጣቶችን ለመሪነት የማሳደግ ስልጠና በጉዲና ቱምሳ ሁለንተናዊ የስልጠና ማዕከል ተካሂዷል፡፡
በስልጠናውም ከቤተክርስቲያኒቱ ሲኖዶሶች የተወጣጡ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተሮች እና አስተባባሪዎች እንዲሁም ከየሲኖዶሶች የተወከሉ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት በጎፈቃድ አምባሳደሮች ተሳትፈዋል።
የቤተክርስቲያኒቱ ፕረዝዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ በፕሮግራሙ በመገኘት በልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ተቀርጾ እየተሰራበት ያለውን ፓኬጅ ልጆች እና ወጣቶችን በሁለንተናዊ መልኩ ቀርጾ ለማሳደግ በጣም አስፈላጊ መሆኑን በማንሳት : ለስኬቱ የአገልግሎቱ መሪዎች እና አስተባባሪዎች እንዲሁም የአገልግሎቱ አምባሳደሮች በትጋት መስራት እንደሚጠበቅባቸው ምክር ለግሰዋል።
የቤተ ክርስቲያኒቱ የልጆችና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ወንድማገኝ ኡዴሳ በተለያየ የቤተክርስቲያኒቱ መዋቅር መምራት የሚችሉ ተተኪ ወጣት መሪዎችን ማፍራት የስልጠና አላማ እንዳሆነ ገልጸዋል።
በፕሮግራሙም እየተሰራበት ባለው ሁለንተናዊ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት ፓኬጅ ዙርያ ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን ; በተለያዩ ርዕሶች ዙርያም በተለያዩ የቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮች ትምህርቶች ተሰጥተዋል።
በመጨረሻም የምክክር ጊዜ ከተካሄደ በኃላ ፡ በስልጠና ለተሳተፉ አምባሳደሮች የምስክር ወረቀት እና የተለያዩ መንፈሳዊ መጽሐፍትን በመስጠት ተጠናቋል።
መረጃውን ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
የኢት./ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ በልጆችና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ አዘጋጅነት ወጣቶችን ለመሪነት የማሳደግ ስልጠና በጉዲና ቱምሳ ሁለንተናዊ የስልጠና ማዕከል ተካሂዷል፡፡
በስልጠናውም ከቤተክርስቲያኒቱ ሲኖዶሶች የተወጣጡ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተሮች እና አስተባባሪዎች እንዲሁም ከየሲኖዶሶች የተወከሉ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት በጎፈቃድ አምባሳደሮች ተሳትፈዋል።
የቤተክርስቲያኒቱ ፕረዝዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ በፕሮግራሙ በመገኘት በልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ተቀርጾ እየተሰራበት ያለውን ፓኬጅ ልጆች እና ወጣቶችን በሁለንተናዊ መልኩ ቀርጾ ለማሳደግ በጣም አስፈላጊ መሆኑን በማንሳት : ለስኬቱ የአገልግሎቱ መሪዎች እና አስተባባሪዎች እንዲሁም የአገልግሎቱ አምባሳደሮች በትጋት መስራት እንደሚጠበቅባቸው ምክር ለግሰዋል።
የቤተ ክርስቲያኒቱ የልጆችና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ወንድማገኝ ኡዴሳ በተለያየ የቤተክርስቲያኒቱ መዋቅር መምራት የሚችሉ ተተኪ ወጣት መሪዎችን ማፍራት የስልጠና አላማ እንዳሆነ ገልጸዋል።
በፕሮግራሙም እየተሰራበት ባለው ሁለንተናዊ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት ፓኬጅ ዙርያ ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን ; በተለያዩ ርዕሶች ዙርያም በተለያዩ የቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮች ትምህርቶች ተሰጥተዋል።
በመጨረሻም የምክክር ጊዜ ከተካሄደ በኃላ ፡ በስልጠና ለተሳተፉ አምባሳደሮች የምስክር ወረቀት እና የተለያዩ መንፈሳዊ መጽሐፍትን በመስጠት ተጠናቋል።
መረጃውን ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ