የጽዮን ከተማ ሰራዊት የእየሱስ ክርስቶስ ወንጌል አገልግሎት ከኢትዮጵያ ወንጌልን አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካወንስል እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር "ነሐሴን ለወንጌል እንዋጀዋለን "በሚል መሪ ቃል የመክፈቻ መርሐግብር አካሄደ።
ነሐሴን ለወንጌል በሚል መሪ ቃል የአንድ ወር የዲጂታል የወንጌል ስርጭት ሊከናወን ነዉ።
የጽዮን ከተማ ሰራዊት የእየሱስ ክርስቶስ ወንጌል አገልግሎት ከኢትዮጵያ ወንጌልን አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካወንስል እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር "ነሐሴን ለወንጌል እንዋጀዋለን "በሚል መሪ ቃል የመክፈቻ መርሐግብር አካሂዷል።
የጽዮን ከተማ ሰራዊት የእየሱስ ክርስቶስ ወንጌል አገልግሎት ከኢትዮጵያ ወንጌልን አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካወንስል እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በነሐሴ ወር የ30 ቀን የዲጂታል የቀጥታ ወንጌል ተልእኮ ዘመቻን በተመለከተ የመክፈቻና የምክክር መርሐግብር ነው ያካሄደው።
የጽዮን ከተማ ሰራዊት የእየሱስ ኮርስቶስ ወንጌል አገልግሎት ከኢትዮጲያ ወንጌላዉያን አብያተ ክርስቲያናት ካዉንስል ጋር በመተባበር የተለያዮ ስራዋችን በመስራት ይታወቃል።
በዚህ በመጨረሻ እና በዲጂታል ዘመን የእየሱስ ክርስቶስን የመንግስቱን ወንጌል በተለያዮ የዲጂታል የሶሻል ሚዲያ ማሰራጫ መንገዶች ማለትም በ ፌስቡክ፣ በዮቲዮብ ፣ በኢንስታግራም፣በቲክቶክ ፣በኢሜል ፣በፖድካስቶች እና በሌሎች አማራጮች ሁሉ በቀጥታ ስርጭቶች መስመር ላይ ለ30 ቀን የሚቆይ መሆኑ ተገልጿል።
ሐምሌ 19/20017 ዓ.ም የፅዮን ከተማ ሰራዊት የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል አገልግሎት ቤ/ክ ከወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካዉንስል እና ከአባል ቤተዕምነቶች ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን ከነሐሴ 1 - 30 የሚኖረዉን የቀጥታ የዲጂታል ወንጌል ስርጭት ዘመቻ አስመልክቶ ከሚዲያ አካላት እና ከአብያተክርስቲያናት መሪዎች ጋር ራዕይ የማካፈልና የምክክር ፕሮግራም ተደርጓል ።
ለመረሃ ግብሩ በፀሎት ፣ በመዘምራን ፣ በክትትል እና በዲጂታል ቡድን የሚያገለግሉ ጨምሮ 7 ግብረሃይል የተዘጋጀ መሆኑን የቤተክርስቲያን መሪዎች በመድረኩ ጠቅሰዋል።
ምሽት ከ12:00 - 2:00 በሚኖረዉ የቀጥታ የወንጌል ስርጭት በአንድ ወር ዉስጥ ለ1 ሚሊዮን ሰዎች የምስራቹን ለመንገር እና 3ሺህ ነብሳት ጌታን እንደ ግል አዳኛቸዉ አድርገዉ እንዲቀበሉ ለመስራት እቅድ እንደተያዘ ተናግረዋል።
በአለም ዙሪያ ያሉ አንድ ሚሊዬን አዳዲስ ነፋሳት (ትዉልድን) በወንጌል በመድረስ ታላቁ ተልዕኳችንን ለመፈፀም የታለመ ራአይ መሆኑ ተነግሯል።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
ነሐሴን ለወንጌል በሚል መሪ ቃል የአንድ ወር የዲጂታል የወንጌል ስርጭት ሊከናወን ነዉ።
የጽዮን ከተማ ሰራዊት የእየሱስ ክርስቶስ ወንጌል አገልግሎት ከኢትዮጵያ ወንጌልን አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካወንስል እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር "ነሐሴን ለወንጌል እንዋጀዋለን "በሚል መሪ ቃል የመክፈቻ መርሐግብር አካሂዷል።
የጽዮን ከተማ ሰራዊት የእየሱስ ክርስቶስ ወንጌል አገልግሎት ከኢትዮጵያ ወንጌልን አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካወንስል እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በነሐሴ ወር የ30 ቀን የዲጂታል የቀጥታ ወንጌል ተልእኮ ዘመቻን በተመለከተ የመክፈቻና የምክክር መርሐግብር ነው ያካሄደው።
የጽዮን ከተማ ሰራዊት የእየሱስ ኮርስቶስ ወንጌል አገልግሎት ከኢትዮጲያ ወንጌላዉያን አብያተ ክርስቲያናት ካዉንስል ጋር በመተባበር የተለያዮ ስራዋችን በመስራት ይታወቃል።
በዚህ በመጨረሻ እና በዲጂታል ዘመን የእየሱስ ክርስቶስን የመንግስቱን ወንጌል በተለያዮ የዲጂታል የሶሻል ሚዲያ ማሰራጫ መንገዶች ማለትም በ ፌስቡክ፣ በዮቲዮብ ፣ በኢንስታግራም፣በቲክቶክ ፣በኢሜል ፣በፖድካስቶች እና በሌሎች አማራጮች ሁሉ በቀጥታ ስርጭቶች መስመር ላይ ለ30 ቀን የሚቆይ መሆኑ ተገልጿል።
ሐምሌ 19/20017 ዓ.ም የፅዮን ከተማ ሰራዊት የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል አገልግሎት ቤ/ክ ከወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካዉንስል እና ከአባል ቤተዕምነቶች ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን ከነሐሴ 1 - 30 የሚኖረዉን የቀጥታ የዲጂታል ወንጌል ስርጭት ዘመቻ አስመልክቶ ከሚዲያ አካላት እና ከአብያተክርስቲያናት መሪዎች ጋር ራዕይ የማካፈልና የምክክር ፕሮግራም ተደርጓል ።
ለመረሃ ግብሩ በፀሎት ፣ በመዘምራን ፣ በክትትል እና በዲጂታል ቡድን የሚያገለግሉ ጨምሮ 7 ግብረሃይል የተዘጋጀ መሆኑን የቤተክርስቲያን መሪዎች በመድረኩ ጠቅሰዋል።
ምሽት ከ12:00 - 2:00 በሚኖረዉ የቀጥታ የወንጌል ስርጭት በአንድ ወር ዉስጥ ለ1 ሚሊዮን ሰዎች የምስራቹን ለመንገር እና 3ሺህ ነብሳት ጌታን እንደ ግል አዳኛቸዉ አድርገዉ እንዲቀበሉ ለመስራት እቅድ እንደተያዘ ተናግረዋል።
በአለም ዙሪያ ያሉ አንድ ሚሊዬን አዳዲስ ነፋሳት (ትዉልድን) በወንጌል በመድረስ ታላቁ ተልዕኳችንን ለመፈፀም የታለመ ራአይ መሆኑ ተነግሯል።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
❤5
"በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል የሃይማኖት አባቶች የተሳተፉበት 7ኛዉ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር ተካሄደ።
በመርሃ ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሊድያ ግርማ ከዚህ ቀደም በነበሩት መረሃ ግብሮች 6 ሚሊዮን ችግኞች መትከላቸውን አንስተው ተክሎ ከመሄድ በዘለለ በመንከባከብ ለሚፈለገው ግብ ማድረስ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
ከተማችን አዲስ አበባ እንደስሟ ውብ ለማድረግ ሰላም በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በአረንጓዴ አሻራም ለማስዋብ ትልቁን አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ጠቁመው አሁንም የከተማችን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ ተግተን እንሰራለን ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ለሀገር ሰላም በጋራ የሚተጉ የሰላም አለኝታ የሆኑ የፀጥታ ኃይሎች አዲስ አበባን ውብና ጽዱ ለማድረግና አሻራቸውን ለማሳረፍ በስፍራው በመገኘታቸው ምስጋናቸው ያቀረቡት በመርሃ ግብሩ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ግርማ ሰይፍ ናቸው።
የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ባለፉት 6 ዓመታት በነበሩት የአርንጓዴ አሻራ የማኖር መረሃ ግብር አባል ቤተዕምነቶችን በማስተባበር በመዲናችን አዲስ አበባ ከ3 ሚሊዮን በላይ ችግኞች እንዲተከሉ ያደረገ ሲሆን በአንድ ጀምበር 700 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል በተዘጋጀው ሀገራዊ ንቅናቄ ሁሉም አባላት አሻራውን እንዲያኖር ጥሪ አቅርቧል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የውጪ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ መጋቢ አሸብር ከተማ፣የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሐፊን መጋቢ ታምራት አበጋዝን ጨምሮ የጉባኤው አባል ቤተዕምነት መሪዎች እና ክብርት ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሀላፊ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ጠ/መምሪያ ዋና አዛዥ ኮሚሽነር ጌቱ አርጋውን ሌሎች የጸጥታ እና የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
መረጃው የአዲስ አበባ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
በመርሃ ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሊድያ ግርማ ከዚህ ቀደም በነበሩት መረሃ ግብሮች 6 ሚሊዮን ችግኞች መትከላቸውን አንስተው ተክሎ ከመሄድ በዘለለ በመንከባከብ ለሚፈለገው ግብ ማድረስ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
ከተማችን አዲስ አበባ እንደስሟ ውብ ለማድረግ ሰላም በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በአረንጓዴ አሻራም ለማስዋብ ትልቁን አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ጠቁመው አሁንም የከተማችን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ ተግተን እንሰራለን ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ለሀገር ሰላም በጋራ የሚተጉ የሰላም አለኝታ የሆኑ የፀጥታ ኃይሎች አዲስ አበባን ውብና ጽዱ ለማድረግና አሻራቸውን ለማሳረፍ በስፍራው በመገኘታቸው ምስጋናቸው ያቀረቡት በመርሃ ግብሩ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ግርማ ሰይፍ ናቸው።
የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ባለፉት 6 ዓመታት በነበሩት የአርንጓዴ አሻራ የማኖር መረሃ ግብር አባል ቤተዕምነቶችን በማስተባበር በመዲናችን አዲስ አበባ ከ3 ሚሊዮን በላይ ችግኞች እንዲተከሉ ያደረገ ሲሆን በአንድ ጀምበር 700 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል በተዘጋጀው ሀገራዊ ንቅናቄ ሁሉም አባላት አሻራውን እንዲያኖር ጥሪ አቅርቧል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የውጪ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ መጋቢ አሸብር ከተማ፣የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሐፊን መጋቢ ታምራት አበጋዝን ጨምሮ የጉባኤው አባል ቤተዕምነት መሪዎች እና ክብርት ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሀላፊ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ጠ/መምሪያ ዋና አዛዥ ኮሚሽነር ጌቱ አርጋውን ሌሎች የጸጥታ እና የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
መረጃው የአዲስ አበባ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
❤1👍1