የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በአለም አቀፉ የሚሽን ማህበር ጉባኤ ላይ የእውቅና ሽልማት አገኘች።
በመካከለኛው አሜሪካ ሁንዱራስ እየተካሄደ በሚገኘውና ሁለተኛ ሳምንቱን በያዘው የአለም አቀፍ ሚሽን ማህበር (IMA) ጉባኤ እየተሳተፈች የምትገኘው የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በመድረኩ በወንጌል ተልዕኮ እያከናወነች ላለው እንቅስቃሴና ከአሞር ቪንቪንቴ ቤተክርስቲያን ጋር ላላት አጋርነት የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላታል።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን በመወከል በስፍራው የሚገኙት የቤተክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ ሽልማቱን ሲቀበሉ "ይህ እውቅና ክርስቶስን ለመስበክ እና መንግስቱን በማህበረሰቦች መካከል ለመገንባት ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያሳይ ግሩም ማስታወሻ ነው።" ሲሉ ገልጸዋል። ፕሬዚዳንቱ አክለውም አለም አቀፉ የሚሽን ማህበር ለወንጌል ስራ እንድንነቃቃ እያደረገ ስላለው አስተዋጽኦ አመሰግናለሁ ብለዋል።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በተለያየ አለም የሚገኙ አብያተክርስቲያናት በተካተቱበት አለም አቀፍ የሚሽን ማህበር (IMA) መስራች አባል መሆኗ ይታወቃል።
መረጃው የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
በመካከለኛው አሜሪካ ሁንዱራስ እየተካሄደ በሚገኘውና ሁለተኛ ሳምንቱን በያዘው የአለም አቀፍ ሚሽን ማህበር (IMA) ጉባኤ እየተሳተፈች የምትገኘው የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በመድረኩ በወንጌል ተልዕኮ እያከናወነች ላለው እንቅስቃሴና ከአሞር ቪንቪንቴ ቤተክርስቲያን ጋር ላላት አጋርነት የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላታል።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን በመወከል በስፍራው የሚገኙት የቤተክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ ሽልማቱን ሲቀበሉ "ይህ እውቅና ክርስቶስን ለመስበክ እና መንግስቱን በማህበረሰቦች መካከል ለመገንባት ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያሳይ ግሩም ማስታወሻ ነው።" ሲሉ ገልጸዋል። ፕሬዚዳንቱ አክለውም አለም አቀፉ የሚሽን ማህበር ለወንጌል ስራ እንድንነቃቃ እያደረገ ስላለው አስተዋጽኦ አመሰግናለሁ ብለዋል።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በተለያየ አለም የሚገኙ አብያተክርስቲያናት በተካተቱበት አለም አቀፍ የሚሽን ማህበር (IMA) መስራች አባል መሆኗ ይታወቃል።
መረጃው የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
❤3👍1
ቻይልድ ኢቫንጀሊዝም ፌሎሺፕ ለ10 ተከታታይ ቀናት ለታዳጊ ወጣቶች ስልጠና ሰጠ።
ቻይልድ ኢቫንጀሊዝም ፌሎሺፕ ከሚሰጣቸው ስልጠናዎች መካከል CYIA (Christian Youth In Action/የክርስቲያን ወጣት ታላቅ ስራ) አንዱ ሲሆን ይህ ስልጠና በክረምት ወራት ለ10 ተከታታይ ቀናት ለታዳጊ ወጣቶች የሚሰጥ ሲሆን በዚህ አመት ደብረዘይት በተካሄደው ስልጠና ላይ የሰለጠኑ ተማሪዎች ብዛት 104 መሆኑ ተግልጾዋል።
ከነዚህም መካከል 23 የሚሆኑ የአራተኛ ዓመት ተማሪዎች ተመርቀዋል። በዚህ የአስር ቀን ቆይታ ሰልጣኝ ተማሪዎች ለአምስት ቀናት ልጆችን በተለያዩ ቤተክርስቲያናት ላይ አስተምረዋል። እንዲሁም የጎዳና ላይ የወንጌል ስርጭት አድርገዋል።
በአጠቃላይ 3130 የሚሆኑ ልጆች ወንጌልን የሰሙ ሲሆን 590 የሚሆኑ ልጆች ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደግል አዳኛቸው አድርገው ተቀብለዋል።
በምርቃቱ ላይ ተማሪዎች በዚህ ስልጠና ሕይወታቸው እንዴት እንደተለወጠ ምስክርነት ሰጥተዋል።በተጨማሪም ወደ ሃገራቸውም ሄደው ወንጌልን በደንብ እንዲሰሩና እንዲያገለግሉ በቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የልጆች አገልግሎት መሪ በሆኑት ፓስተር ማርቆስ በፀሎት ተባርከው ተሸኝተዋል።
መረጃውን ከቻይልድ ኢቫንጀሊዝም ፌሎሺፕ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
ቻይልድ ኢቫንጀሊዝም ፌሎሺፕ ከሚሰጣቸው ስልጠናዎች መካከል CYIA (Christian Youth In Action/የክርስቲያን ወጣት ታላቅ ስራ) አንዱ ሲሆን ይህ ስልጠና በክረምት ወራት ለ10 ተከታታይ ቀናት ለታዳጊ ወጣቶች የሚሰጥ ሲሆን በዚህ አመት ደብረዘይት በተካሄደው ስልጠና ላይ የሰለጠኑ ተማሪዎች ብዛት 104 መሆኑ ተግልጾዋል።
ከነዚህም መካከል 23 የሚሆኑ የአራተኛ ዓመት ተማሪዎች ተመርቀዋል። በዚህ የአስር ቀን ቆይታ ሰልጣኝ ተማሪዎች ለአምስት ቀናት ልጆችን በተለያዩ ቤተክርስቲያናት ላይ አስተምረዋል። እንዲሁም የጎዳና ላይ የወንጌል ስርጭት አድርገዋል።
በአጠቃላይ 3130 የሚሆኑ ልጆች ወንጌልን የሰሙ ሲሆን 590 የሚሆኑ ልጆች ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደግል አዳኛቸው አድርገው ተቀብለዋል።
በምርቃቱ ላይ ተማሪዎች በዚህ ስልጠና ሕይወታቸው እንዴት እንደተለወጠ ምስክርነት ሰጥተዋል።በተጨማሪም ወደ ሃገራቸውም ሄደው ወንጌልን በደንብ እንዲሰሩና እንዲያገለግሉ በቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የልጆች አገልግሎት መሪ በሆኑት ፓስተር ማርቆስ በፀሎት ተባርከው ተሸኝተዋል።
መረጃውን ከቻይልድ ኢቫንጀሊዝም ፌሎሺፕ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
የኢቫንጀልየም ሚሸን ኢትዮጵያ ''ከቢጫ ወደ አረንጓዴ'' በሚል መርሐ ግብር በአዳማ የስልጠና እና የምክክር ጊዜ አደረገ።
ሐምሌ 14/2017 ዓ.ም በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ደቡብ አዳማ ክልል የኢቫንጀልየም ሚሺን ኢትዮጵያ በመሐል አዳማ አጥቢያ ከ44 አጥቢያ ከመጡ የሚሸኑ አገልጋዮች እና የቤተክርስቲያን መሪዎች ጋር የትምህርት እና የምክክር ጊዜ አካሄዷል።
ይህ መርሐ ግብር “ከቢጫ ወደ አረንጓዴ” በሚል ርዕሰ የተደረገ ሲሆን በዕለቱም መጋቢ ዳመነ ደጉ “የሙሴ መሪነት እና አገልግሎት በሚል የእግዚአብሔርን ቃል አስተምረዋል።
በመርሀግብሩ ላይም የክልሉ ዋና ጻሐፊ መጋቢ ሻሾ ቱሉ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ታሪክ በመጥቀስ “ወንጌል በሚሸነሪዎች አማካኝነት በብዙ ዋጋ መክፈል ወደ እኛ ዘመን መጥቶአልና እኛም ዋጋ ከፍለን እናገልግል።” ካሉ በኃላም “ እኛም ቤተክርስቲያናችንን እንወቅ” የሚል መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም የክልሉ የሚሸን አሰተባባሪ የሆኑት መጋቢ ብዙአየሁ ተሊላ “ከቢጫ ወደ አረንጓዴ” የሚለውን መርሐ ግብር እና በሚሸኑ በክልል እና በአጥቢያ ደረጃ እየተሰራ ስላለው ሰፊ የሆነ መንፈሳዊ እንቅስቃሴ ለጉባኤው ገለጻ ካደረጉ በኃላ በቀረበው መንፈሳዊ ጉዳዮች ላይ ምክክርና በቀጣይነት በተሻለ ሁኔታ ሊሰራበት የሚቻልበትን የስራ አቅጣጫ በማስቀመጥ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
ሐምሌ 14/2017 ዓ.ም በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ደቡብ አዳማ ክልል የኢቫንጀልየም ሚሺን ኢትዮጵያ በመሐል አዳማ አጥቢያ ከ44 አጥቢያ ከመጡ የሚሸኑ አገልጋዮች እና የቤተክርስቲያን መሪዎች ጋር የትምህርት እና የምክክር ጊዜ አካሄዷል።
ይህ መርሐ ግብር “ከቢጫ ወደ አረንጓዴ” በሚል ርዕሰ የተደረገ ሲሆን በዕለቱም መጋቢ ዳመነ ደጉ “የሙሴ መሪነት እና አገልግሎት በሚል የእግዚአብሔርን ቃል አስተምረዋል።
በመርሀግብሩ ላይም የክልሉ ዋና ጻሐፊ መጋቢ ሻሾ ቱሉ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ታሪክ በመጥቀስ “ወንጌል በሚሸነሪዎች አማካኝነት በብዙ ዋጋ መክፈል ወደ እኛ ዘመን መጥቶአልና እኛም ዋጋ ከፍለን እናገልግል።” ካሉ በኃላም “ እኛም ቤተክርስቲያናችንን እንወቅ” የሚል መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም የክልሉ የሚሸን አሰተባባሪ የሆኑት መጋቢ ብዙአየሁ ተሊላ “ከቢጫ ወደ አረንጓዴ” የሚለውን መርሐ ግብር እና በሚሸኑ በክልል እና በአጥቢያ ደረጃ እየተሰራ ስላለው ሰፊ የሆነ መንፈሳዊ እንቅስቃሴ ለጉባኤው ገለጻ ካደረጉ በኃላ በቀረበው መንፈሳዊ ጉዳዮች ላይ ምክክርና በቀጣይነት በተሻለ ሁኔታ ሊሰራበት የሚቻልበትን የስራ አቅጣጫ በማስቀመጥ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
❤2