በሀዋሳ ከተማ ወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ስር የባለአደራ ትውልድ የታዳጊ ወጣቶች አገልግሎት የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ አካሄዱ።
3 ሺህ የሚሆኑ የ2017 ዓ.ም ስልጠና ተሳታፊዎች ከ25 አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን የተውጣጡ የባለአደራ ትውልድ ሰልጣኝ ታዳጊ ወጣቶች በሀዋሳ ከተማ ጉዱማሌ ፓርክ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም አካሄደዋል።
በሲዳማ ክልል የምትገኝው የአማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን በሀዋሳ ከተማ በጉዱማሌ ፓርክ በመገኝት ከ3000ሺ በላይ በሚሆኑ የባላደራ ትውልድ ሰልጣኝ ታዳጊ ወጣቶችና የቤተክርስቲያኗ አገልጋዮች የአረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።
ወጣቶቹ ለነገ የቤተክርስቲያንን ፣የራስን ፣የቤተሰብንና የሀገርን አደራን የሚቀበል ሀላፊነቱን የሚወጣ ትውልድን ለማፍራት ከሀምሌ 7 እስከ ሀምሌ 12 ለአምስት ተከታታይ ቀናት “የባለአደራ ትውልድ” በሚል የራዕይ ቃል በቤተክርስቲያኗ ስልጠናም ሲወስዱ ቆይተዋል።
በእለቱ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የፅዳትና የወንጌል ስብከት በከተማዋ እግር ጉዞም አካሂደዋል።
የባላደራ ትውልድ የታዳጊ ወጣቶች ስልጠና ዋና አስተባባሪ መጋቢ ተክለአብ ማቴዎስ ስልጠናው 5ተኛ ዙር መሆኑን በመግለፅ በአመት ለሁለት ጊዜ እንደሚካሄድም ገልፀዋል።
የሀዋሳ አማኑኤል ህብረት መጋቢ የሆኑት መጋቢ ወንዶሰን ካሳ በእለቱ እንደተናገሩት “ስልጠናው እድሜያቸው ከ14 እስከ 18 ዕድሜ ክልል ያሉ ታዳጊዎች እንደሚሰጥ እና ቤተክርስቲያንም ሆነ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ስለሚያስፈልጋት ቤተክርስቲያንኗ ትውልድን የማዳን ፣የማብቃት፣የማፍራት ራዕይ ላይ ትኩረት ሰጥተን እየሰራንም ነው ።”ብለዋል።
መረጃውን አገልጋይ ፍፁም አዲሱ ከአማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን ሀዋሳ አደረሰን
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
3 ሺህ የሚሆኑ የ2017 ዓ.ም ስልጠና ተሳታፊዎች ከ25 አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን የተውጣጡ የባለአደራ ትውልድ ሰልጣኝ ታዳጊ ወጣቶች በሀዋሳ ከተማ ጉዱማሌ ፓርክ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም አካሄደዋል።
በሲዳማ ክልል የምትገኝው የአማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን በሀዋሳ ከተማ በጉዱማሌ ፓርክ በመገኝት ከ3000ሺ በላይ በሚሆኑ የባላደራ ትውልድ ሰልጣኝ ታዳጊ ወጣቶችና የቤተክርስቲያኗ አገልጋዮች የአረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።
ወጣቶቹ ለነገ የቤተክርስቲያንን ፣የራስን ፣የቤተሰብንና የሀገርን አደራን የሚቀበል ሀላፊነቱን የሚወጣ ትውልድን ለማፍራት ከሀምሌ 7 እስከ ሀምሌ 12 ለአምስት ተከታታይ ቀናት “የባለአደራ ትውልድ” በሚል የራዕይ ቃል በቤተክርስቲያኗ ስልጠናም ሲወስዱ ቆይተዋል።
በእለቱ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የፅዳትና የወንጌል ስብከት በከተማዋ እግር ጉዞም አካሂደዋል።
የባላደራ ትውልድ የታዳጊ ወጣቶች ስልጠና ዋና አስተባባሪ መጋቢ ተክለአብ ማቴዎስ ስልጠናው 5ተኛ ዙር መሆኑን በመግለፅ በአመት ለሁለት ጊዜ እንደሚካሄድም ገልፀዋል።
የሀዋሳ አማኑኤል ህብረት መጋቢ የሆኑት መጋቢ ወንዶሰን ካሳ በእለቱ እንደተናገሩት “ስልጠናው እድሜያቸው ከ14 እስከ 18 ዕድሜ ክልል ያሉ ታዳጊዎች እንደሚሰጥ እና ቤተክርስቲያንም ሆነ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ስለሚያስፈልጋት ቤተክርስቲያንኗ ትውልድን የማዳን ፣የማብቃት፣የማፍራት ራዕይ ላይ ትኩረት ሰጥተን እየሰራንም ነው ።”ብለዋል።
መረጃውን አገልጋይ ፍፁም አዲሱ ከአማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን ሀዋሳ አደረሰን
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
❤2