የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC
9.69K subscribers
9.51K photos
133 videos
1 file
1.55K links
ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው።

"ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።
Download Telegram
በክርስቲያን ሴሚናሪ ላይ ለሁለተኛ ጊዜ ጥቃት መድረሱን ተከትሎ በናይጄሪያ የሚገኙ ጳጳስ መንግስት እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ አቀረቡ።
በናይጄርያ የሚገኙ ጳጳስ የሚመሩት ሴሚናሪ ላይ በ10 ወራት ውስጥ ሁለት ጊዜ ጥቃት ለመድረሱ የመንግስት ጠንካራ እርምጃ አለመውስድ አስተጽዖ አድርጓል በማለት ተናግረዋል። ታጣቂዎች ለሁለተኛ ጊዜ ባደረሱት ጥቃት የሴሚናሪው ጥበቃ የተገደለ ሲሆን 3 አዳጊ ወጣት የሆኑ ተማሪዎች ደግሞ ታግተው ተወስደዋል።
ጥቃቱም የተፈጸመው በባለፈው ሳምንት በማዕከላዊ ናይጄሪያ እዶ ግዛት ፤ ኢማኩላቴ ኮንሴፕሽን ማይነር ሴሚናሪ ነበር። ጳጳስ ገብሬል ዱኒያ ለቸርች ኢን ኒድ (Church in need) እንደተናገሩት ብዛት ያላቸው ታጣቂዎች ወደ ሴሚናሪው የመጡ ሲሆን የሴሚናሪው ጥበቃዎችም እነርሱን ለመከላከል አልቻሉም።
በጊዜውም ከሲቪል ጥበቃ ድርጅት ለሴሚናሪው የተመደበው ክርስቶፈር የተሰኘ ጥበቃ መገደሉን ተናግረዋል።
ከዛም ባለፈ እድሚያቸው ከ14 እስከ 17 የሆኑ ሶስት ተማሪዎች መታገታቸውን ጳጳሱ አስታወቀዋል።”የመንግስት አካላት ጥበቃ እንዲያደርጉ ያሳወቅን ቢሆንም ምንም አይነት ጠንከር ያለ እርምጃ እስከ አሁን አላስተዋንም።” ያሉት ጳጳሱ “ችግሩ ከአቅማችን በላይ ስለሆነ ሁሉም ሰው እንደያግዘን እና እንዲጸልይልን እናሳስባለን።” በማለት ተናግረዋል።
ከአጋቾቹ ጋር በመካከለኛ ሰዎች አማካኝነት ንግግር የተደረገ ቢሆንም ማገቱ እንዳይቀጥል ለታገቱ ሰዎች ክፍያ ከፍሎ ማስለቀቅ ተግባራዊ እንዳይደረግ የሴሚናሪው ፖሊሲ ይከለከላል።

ጳጳሱም እንደዚህ አይነት ጥቃቶች የሴሚናሪውን ቦታ ለመንጠቅ እና ክርስቲያኖችን ከዚያ ቦታ ለማስለቀቅ ያለሙ ሊሆን ይቻላሉ የሚል ስጋት እንዳላቸው ተናግረዋል።

መረጃውን ከፕሪሚየር ክርስቲያን ኒውስ አገኘነው።

ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፤ አማኑኤል ዴቢሶ
4
ሐምሌ 26 2017 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ “ለኢየሱስ” በሚል ርዕስ ሊዘጋጅ የታሰበውን የአምልኮ ድግስ አስመልክቶ ሐምሌ 11 2017 ዓ.ም በሳሮማሪያ ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጠ።


መጋቢ ትዝታው ሳሙኤል በጸሎት ባስጀመሩት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የአሮማ ቤተ ክርስቲያን መሪ የሆኑት መጋቢ በጋሻው ደሳለኝ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል።
በመክፈቻው ንግግራቸው ከዚህ በፊት መጋቢ ትዝታው ሳሙኤል የመዝሙር ግጥሞችን በማበርከት ሲያገለግሉ እንደቆዩ ተናግረዋል።
"መጋቢ ትዝታው ሳሙኤል ከዚህ ቀደም 'ሊነጋ ሲል ይጨልማል' ፣ 'መላክዕክቱ በፊቱ ይቆማሉ'፣ 'ስመሰክር' ፣ 'ማን ቀረ ከሜዳ' እና 'በማንም የማልቀይርህ' በሚሉት መዝሙሮቹ ይታወቃል። በአሁኑም ጊዜ ከ13 ዓመታት በኋላ በኢትዮጵያ ተገኝቶ ለኢየሱስ በሚል የመዝሙር ኮንሰርት አዘጋጅቷል። " ሲሉ ተደምጠዋል።


ዘማሪ ትዝታው ይሄ ጊዜ ለረዥም ጊዜ ሲጠብቁት የቆየ እንደሆነ ተናግረዋል።
በአምልኮ ድግሱ ላይም በሁሉም ስፍራ ያሉ ሰዎች መጥተው እንዲካፈሉ ጥሪ የተደረገ ሲሆን በጌታ ያመኑ ሰዎች የትንሳኤ ልጆች መሆናቸውን አስመልክቶ ነጭ ልብስ ለብሰው እንዲገኙ ጥሪ ተደርጓል።
ከዚህም ባለፈ ሐምሌ 26 2017 ዓ.ም በሚዘጋጀው የመዝሙር ኮንሰርት የጸሎት ፕሮግራሞች የሕይወት ምስክርነት የዝማሬ እና የአምልኮ ጊዜ ፣ የወንጌል አገልግሎት፣ የነፍሳት ጥሪ እንዲሁም ለምድራችን ጸሎት ይደረጋል ሲሉ አገራዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።


በስፍራው የተገኘችው ዘማሪ ዘርፌ ከበደ ወንጌል የሕይወታችን ክፍል ስለሆነ ለትውልድ እንዲደርስ በጽድቅ የተሞላ አገልግሎታችን ያስፈልጋል ስትል ገልጻለች።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፤ ቃልኪዳን እንዳለ
7👍1🔥1
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ክልሎች አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሄደ።

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በአሁን ሰዓት በመላው ሀገሪቱ 60 ክልሎች ያሏት ሲሆን እነዚህ ክልሎች በየአመቱ በስራቸው የሚገኙ አጥቢያ መሪዎችና አገልጋዮች የሚሳተፉበት ጉባኤ ያሰናዳሉ። በእነዚህ ጉባኤዎች ከመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ዋናው ቢሮ በተወከሉ ኃላፊዎች ትምህርቶች ሲሰጡ የክልሉ አመታዊ ሪፖርት ይደመጣል።

በዚህም መሠረት ባሳለፍነው ሳምንት የሻምቡ፣ ጃርቴ፣ ዶዮገና፣ ሆሳዕና፣ ሺንሺቾ፣ አርሲና ባሌ፣ አድአ ሊበን፣ አድአ በርጋ፣ ቡራዩ ወልመራ፣ የሜታ ሸኖ እና ወሌንሾ ቡታጅራ ክልሎች የክልል ጠቅላላ ጉባኤያቸውን አካሂደዋል።

በጉባኤያቸው በተለይ አዲስ በተሻሻለው የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ውስጠ ደንብ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐግብር ተከናውኗል።

መረጃው የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
4
ኪንግደም ፓሽን ሴሚናሪ የስነ መለኮት ትምህርት ቤት በነቀምትና መቱ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ።

ሐምሌ 12 ቀን 2017 ዓ.ም የኪንግደም ፓሽን ሴሚናሪ በወለጋና በኢሉ አባቦር በማስተርስ ፣ በዲግሪና በዲፕሎማ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በነቀምቴ ሁለገብ አደራሽ አስመርቋል። በዚሁ የምርቃት ስነ ስርዓት ላይም የኢትዮጵያ ወንጌላዊያን አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የምዕራብ ሪጅን ቦርድ ሰብሳቢ ቄስ ገመቹ አብዲሳ እና የነቀምቴ ከተማ ምክትል ከንቲባ ተመስገን ሚሬሳን ጨምሮ ፣ ተጋባዥ አገልጋዮች እና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።

ሴሚናሪው ለ8ኛ ዙር ብቁ ናቸው ብሎ ያሰባቸውን 96 ተማሪዎችን በይፋ ያስመረቀም ሲሆን ከነዚህም ውስጥ በማስተርስ 27 ተማሪዎችን እንዲሁም በዲግሪ 69 ተማሪዎችን ኮሌጁ አስመርቋል።

የኪንግደም ፓሽን ሴሚናሪ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት ፕሬዘዳንት በመሆን እያገለገሉ የሚገኙት ዶክተር ዘካሪያስ አዱኛ እንደተናገሩትም ሴሚናሪው ከዚህ ቀደም በእንግሊዝኛ በአማርኛና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች ብዙ ተማሪዎችን እያሰለጠነ ያፈራ እና እያፈራ እንደሚገኝ በመጥቀስ ብቁ የሆኑ አገልጋዮችን ለቤተክርስቲያንና ለእግዚአብሔር መንግስት እያበረከተ ያለ የስነ መለኮት ተቋም መሆኑንም አንስተው ለወደፊት ካምፓሶቹን በሁሉም ክልሎች እንደሚከፍትም ጠቅሰዋል።

በመርሀ ግብሩ ላይም የሴሚናሪው ፕርሪንሲፓል ዶክተር ጋዲሳ መንገሻ የእግዚአብሔርን ቃል ያካፈሉ ሲሆን በምርቃቱ ወቅትም የኪንግደም ፓሽን ሴሚናሪ ለቤተክርስቲያን አገልጋዮችን በማፍራት እየተጋ ያለ ተቋም መሆኑንም በማንሳት ከዲፕሎማ እስ ፒ ኤች ዲ ተማሪዎችን ተቀብሎ እያሰለጠኑ መሆናቸውንም ጠቅሷል።

በምረቃው መርሐግብሩ ላይ የተገኙት የክቡር እንግዶችም በነበረው መርሐግብሮች ደስተኛ እንደሆኑና ሴሚናሪው እየሰራ ያለ ስራዎችን በማድነቅ አበረታቷል። በዕለቱም የማዕረግ እና የፒኤችዲ ተመራቂ ተማሪዎችም በሴሚናሪው የነበራቸውን ቆይታ አስመልክቶም ደስተኞች እንደነበሩና ለወደፊቱም ከሴሚናሪው ጎን መሆናቸውን ተናግሯል።

በወንጌል ተልዕኮና ዓቃቤ እምነት ትምህርትቤትነት የሚታወቀው ኪንግደም ፓሽን ሴሚናሪ በአሁን ሰዓትም በሀገር ውስጥ ያሉትን 80 ካንፓሶች ጨምሮ ፣በምስራቅ አፍሪካ በ11 ካንፓሶች እና በኦለይን በመካከለኛው ምስራቅም ጭምር ተማሪዎችን እያሰለጠነ እንደሚገኝ ተነግሯል። ሴሚናሪው ከከተማ ወጣ ያሉ ቦታዎችን በመድረስና አብያተክርስትያንን ለታላቁ ተልዕኮና ለእቀበተ እምነት ስራም በማስታጠቅ እየሰራም ይገኛል።

በተጨማሪም ኪንግደም ፓሽን ሰሚናሪ በወንጌል አገልግሎት እድሜያቸውን ለጨረሱትና ለወንጌል ስራ ብዙ መስዋዕትነት በመክፈል ለወንጌል መስፋፋት ምክንያት ለሆኑት ለሶስት አባቶች ለመጋቢ ተፈራ ጎንፋ ከመሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን፣ ለመጋቢ ኩመራ ሊካሳ ከሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያንና ፣ለቄስ ታደሰ ከነቀምቴ መካነ ኢየሱስ እውቅና ሰጥቷል።



መረጃውን ኪንግደም ፓሽን ሰሚናሪ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ላይ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፤ ቤተልሔም ደረጄ
👍1