የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC
9.67K subscribers
9.58K photos
133 videos
1 file
1.55K links
ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው።

"ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።
Download Telegram
#በቢሊግራሀም_ኢቫንጀሊስቲክ_አሶሴሽን_የሚመራው_ኦፕሬሽን_ክሪስማስ_ቻይልድ ኦሲሲ ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር በጋራ በመሆን ለአራት መቶ ሰማኒያ ልጆች ስጦታን አበረከተ።
👍2
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC
#በቢሊግራሀም_ኢቫንጀሊስቲክ_አሶሴሽን_የሚመራው_ኦፕሬሽን_ክሪስማስ_ቻይልድ ኦሲሲ ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር በጋራ በመሆን ለአራት መቶ ሰማኒያ ልጆች ስጦታን አበረከተ።
የቢሊግራሀም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን አንድ ክንፍ የሆነው ኦፕሬሽን ክሪስማስ ቻልይድ ኦሲሲ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለያየ ችግር ውስጥ ለሚያልፉ ልጆች ስጦታን በመስጠት ወንጌል ለማድረስ የሚሰራ አገልግሎት ነው።
ይህም አገልግሎት ከኢትዮጵያ ወንጌል አምኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር በመተባበር የካቲት 27 እና 28 በቻይና ካምፕ አከባቢ በሚገኙ የቃለ ሕይወት እና መካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያኖች ላይ በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ለ480 ልጆች ስጦታ የመስጠት መርሃ ግብር አካሂዷል።
ኦሲሲ ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር በጥምረት ሲሰራ ይሄ የመጀመሪያው ጊዜ አይደለም። ከዚህ በፊት ለ50 የቤተ ክርስቲያን መሪዎች እና ለ200 የልጆች አገልጋዮች ግንዛቤን የመፍጠሪያ ስልጠና በኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል አማካኝነት አካሂዶ ነበር።
የካቲት 27 እና 28 ሀሙስ እና አርብ ላይ በተካሄደው ለልጆች ስጦታ የመስጠት መርሃ ግብር ላይ ኦሲሲን በመወከል ትልቅ ሚና የተጫወቱትን ፖል የተሰኙ የኦሲሲ ተወካይ ሲሆኑ በመርሃ ግብሩ ላይ ለልጆች ስጦታውን ለመስጠት የፍራንክሊንግ ግራሀም ልጅ የሆኑት ኤድዋርድ ግራሃም ተገኝተው ነበር።
አብረዋቸው የመጡት የቡድን አባላትም ለልጆች የእግዚአብሔርን ቃል አካፍለዋል።
በልጆች ላይ ከፍተኛ የደስታን ስሜት በፈጠረው ፕሮግራም ላይ የቤተ ክርስቲያን መሪዎች እና የልጆች አገልጋዮች ተገኝተዋል።
በኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የውጭ ግኑኝነት ሀላፊ የሆኑት መጋቢ አሸብርም ይህንን መርሃ ግብር አስመልክቶ ይሄ ገና ጅማሬው ነው በማለት ተናግረዋል።
መረጃውን ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የውጪ ግንኙነት መምሪያ አገኘነው።
9👍1
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC
#የኢትዮጵያ_ወንጌል_አማኞች_አብያተ_ክርስቲያናት_ካውንስል_ከቢሊ_ግራሀም_ኢቫንጀልስቲክ_አሶሴሽን_ጋር_በጋራ_በመሆን_ያዘጋጀው_መለኮታዊ_ጉብኝት_ለኢትዮጵያ_የተሰኘው_መረሃ_ግብር_በታላቅ_ድምቀት_ተጠናቀቀ፡፡
የካቲት 29 እና 30 ቀን 2017 ዓ.ም መለኮታዊ ጉብኝት በኢትዮጵያ" የጸሎትና ምስጋና መርሃ ግብር በኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካዉንስል እና በቢሊ ግራሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን ጋር ትብብር በተዘጋጀው በዚህ መርሃ ግብር ላይ ፤ የሬቨረንድ ቢሊ ግራሃም ልጅ ፍራንክሊን ቢሊ ግራሃም ያገለገሉ ሲሆን የጸሎትና እና የዝማሬ መርሃ ግብሮችም ተከናውኗል፡፡

መለኮታዊ ጉብኝት በኢትዮጵያ የጸሎትና ምስጋና መርሃ ግብር ላይ በርካታ ቁጥር ያለቸው ሰዎች ወደ አግዚአብሔር መንግስት ተጨምረዋል፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘ


ከ320 ሺህ በላይ ሰው መስቀል አደባባይ የእግዚአብሔርን ቃል ለመስማት በመገኘቱ የተሰማኝን ትልቅ ደስታ እገልጻለው ሲሉ ፍራንክሊን ግርሃም ።

ፍራንክሊን ግርሃም ከየመስቀል አደባባይ የማጠቃለያ አገልግሎታቸው በኋላ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክታቸው “ወንጌል ሃይል አለው። ዛሬ ንሰሃ በመግባት ኢየሱስ ክርስቶስን ለመከተል ስለ ወሰኑ ሰዎች ጌታን እናመሰግናለን።

ኢየሱስም እንዲህ አለ፤ “ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ በእኔ የሚያምን ቢሞት እንኳን በሕይወት ይኖራል፤ በእኔ የሚኖር፣ የሚያምንብኝም ከቶ አይሞትም”
ዮሐንስ 11፥25-26

ለዚህ ፕሮግራም መሳካት ትልቅ አስተዋጾ ላደረጉ ፣ለጸለዩ ወዳጆቼ እና አብያተ ክርቲያናት በሙሉ ትልቅ ምስጋና አለኝ። አብያተ ክርስቲያናት በእግዚአብሔር ቃል እየጸናችሁ፡ የምትሰሩትን የደቀ መዝሙር ማፈራት ስራ እግዚአብሔር ይባርክ።

ዛሬ በነበረን የዝማሪው ጊዜ በርካታ ዘማሪዎች በዝማሬ እና አምልኮ ከቀትር በኋላ እስከ ምሽት ድረስ በጥሩ ሁኔታ አገልግለዋል። መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ መርሃ ግብር ላይ ለተሳፋችሁ በሙሉ አመሰግናለሁ።” ብለዋል።
#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ - https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦ https://tttttt.me/EGBCC
tiktok :- https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!
👍19
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንሰል መገለጫ ሰጠ።

ከቅርብ ዓመታት ጀምሮ ወደ ምድራችን የሚመጡ የንስሐ ግቡ ሐልዕክቶች ሰለሆኑ ባላፈው ዓመት ታላቅ የአገራዊ ንስሃ ጊዜን በአደባባይ አከናውነናል። ይህንን ንስሃ መቀጠል ስለታመነበት የአገራዊ ንስሃ የሚያስተባብር ግብረ ኃይል በወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ይሁንታ ተቋቁሞ ተግባሮቹን በተሻለ መንገድ ለመወጣት በመሥራት ላይ ይገኛል።

ስለዚህ ፦

1.ከሚያዝያ 6 እስከ 11/2017 ዓ.ም ከሰኞ- ቅዳሜ በሉት የህማማቱ ሳምንት በመላው አገሪቱ ባሉ ማህበር ምዕመናን ቢቻልም በከተሞች አመቺ በሆኑ በተመረጡ አብያተክርስቲያናት በአንድነት በመሰባሰብ የኑዛዜና የንስሐ ቀናቶች እንዲሆኑ።

2. ከሚያዝያ 19 እስከ ግንቦት 17/2017 ዓ.ም ባሉት ሳምንታት ኑዛዜ ያደረግንባቸው ጉዳዮችን ወደ ፍሬ እንዲመጡ በየአጥቢያው የንስሐ አቅጣጫዎች የትምህርት እና ንስሃውን ከሕይወት ጋር የምሰናዛምድባቸው ጊዜያቶች እንዲሆኑ።

3.ግንቦት 24 ቀን 2017ዓ.ም በሁሉም ከተሞችና አካባቢዎች የማጠቃለያ የንሰሐ ጊዜ መሪዎች በየክልሎቻቸው የካውንስል እና የኀብረቶች አደረጃጀቶች እንዲያደርጉና በአዲስ አበባ ለሚካሄደው ለአገር አቀፉ የማጠቃለያ የንስሐ ጊዜ ከልሉን የሚወክሉ መሪዎችን ወክለውና በክልሉ ቤተክርስቲያን መለኮታዊ ሥልጣን ጸልየውላቸው ወደ አዲስ አበባ እንዲልኩ።

4.ከግንቦት 25 አስከ 27 2017 ዓ.ም ለሦስት ቀናት ከመላው ኢትዮጵያ ክልሎች እና ከዲያስፖራ በክልሎች ቤተክርስቲያን መለኮታዊ ሰልጣን በሚወከሉ መሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ ማጠቃለያውን በተወከሉ መሪዎች የንስሐ ጊዜ በማድረግ የንሰሐ ማጠቃለያ እንዲሆን ታቅዷል።

በመላው ኢትዮጵያ እና በውጭ ሀገር የምትኖሩ የወንጌላውያን አማኞች ሁሉ በዚህ በወጣው ፕሮግራም መስረት አሰተባባሪ ግብር ኃይል በልዩ ልዩ መገናኛ ዘዴዎች በሚያሰራጫቸው የንስሐ አቅጣጫዎች እና የኑዛዜ የጸሎት ርዕሶች አየታገዛቸሁ የንስሐ ጊዜውን አብረን በጋራ እንድናከናውን ጥሪዬን አቀርባለሁ።

“ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ጕበኞችን በቅጥርሽ ላይ አቁሜአለሁ፤ ቀንና ሌሊት ከቶ ዝም አይሉም፤ እናንተ እግዚአብሔርን የምታሳስቡ፥ ኢየሩሳሌምን እስኪያጸና በምድርም ላይ ምስጋና እስኪያደርጋት ድረስ አትረፉ ለእርሱም ዕረፍት አትስጡ።”ትንቢተ ኢሳይያስ 62፥6-7

ልዑል አግዚአብሔር አገራችንን ኢትዮጵያን ይባርክ!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ከርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ

መጋቢት 3/2017 ዓ.ም #ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ - https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦ https://tttttt.me/EGBCC
tiktok :- https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!
🙏10👍53🔥2