የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን የደቡብ ምስራቅ አዲስ አበባና አካባቢው ክልል ጠቅላላ ጉባኤ በጾም ጸሎት ተጀመረ።
ነሐሴ አርብ 2/2017 ዓ.ም በ 22 ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን የደቡብ ምስራቅ አዲስ አበባና አካባቢው ክልል ጠቅላላ ጉባኤ በጾም ጸሎት ተጀምሯል።
የቀጠና ሁለት ሙሉ ወንጌል አጥቢያ B ኳየር በዝማሬ በማገልገል ጉባኤው እግዚአብሔርን አምልኮአል።
በመቀጠል በቤተ እምነቱ የቦርድ ስራ አስፈጻሚ ሰብስቢ በመጋቢ ተመስገን አዋኖ ከሐዋሪያት ስራ ምዕራፍ 20 ከቁጥር 1 እስከ 25 ካለው ክፍል "የሐዋርያው ጳውሎስ ሕይወትና አገልግሎት " በሚል ርዕስ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት ለጉባኤው አቅርበዋል።
በጾም ጸሎቱ እግዚአብሔር ያለፈውን በጀት አመት በብዙ ፀጋ ክልሉን ስለረዳ በማመስገን ቀጣይን አመት ለጌታ አደራ በመስጠት ፣ እግዚአብሔር ምድራችን ሰላም እንዲያደርጋት ጸሎት ተካሂዷል።
ጌታ መልካም የጸሎት ጊዜ እንደሰጣቸው አዘጋጆቹ መግለጻቸውንም ቤተ ክርስቲያኒቱ በፌስቡክ ገጿ ላይ አስፍራለች።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
ነሐሴ አርብ 2/2017 ዓ.ም በ 22 ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን የደቡብ ምስራቅ አዲስ አበባና አካባቢው ክልል ጠቅላላ ጉባኤ በጾም ጸሎት ተጀምሯል።
የቀጠና ሁለት ሙሉ ወንጌል አጥቢያ B ኳየር በዝማሬ በማገልገል ጉባኤው እግዚአብሔርን አምልኮአል።
በመቀጠል በቤተ እምነቱ የቦርድ ስራ አስፈጻሚ ሰብስቢ በመጋቢ ተመስገን አዋኖ ከሐዋሪያት ስራ ምዕራፍ 20 ከቁጥር 1 እስከ 25 ካለው ክፍል "የሐዋርያው ጳውሎስ ሕይወትና አገልግሎት " በሚል ርዕስ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት ለጉባኤው አቅርበዋል።
በጾም ጸሎቱ እግዚአብሔር ያለፈውን በጀት አመት በብዙ ፀጋ ክልሉን ስለረዳ በማመስገን ቀጣይን አመት ለጌታ አደራ በመስጠት ፣ እግዚአብሔር ምድራችን ሰላም እንዲያደርጋት ጸሎት ተካሂዷል።
ጌታ መልካም የጸሎት ጊዜ እንደሰጣቸው አዘጋጆቹ መግለጻቸውንም ቤተ ክርስቲያኒቱ በፌስቡክ ገጿ ላይ አስፍራለች።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
❤1
በፓኪስታን በክርስቲያን ልጆች ላይ እየደረሰ የሚገኘው ጥቃት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻቀበ መምጣቱ ተገለጸ።
በባኪስታን የልጆች መብት ኮሚሽን ያወጣው አዲስ ሪፖርት ክርስቲያኖችን ጨምሮ በተለያዩ አናሳ ማህበረሰቦች ውስጥ የሚገኙ ልጆች ከፍተኛ ለሆነ ጥቃት እየተጋለጡ እንደሆነ ያስነብባል። ሪፖርቱ ከፍተኛውን ጥቃት ያስተናግዳሉ ያላቸው ደግሞ የክርስቲያን ቤተሰቦችን ልጆች ነው። ሪፖርቱ በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በክርስቲያን ልጆች ላይ የደረሱ ጥቃቶችን የሚያነሳ ሲሆን ከእነዛም ውስጥ አስገድዶ እምነት ማስቀየር ፣ ያለአቻ ጋብቻ እና የጉልበት ብዝበዛ ተጠቀሰዋል።
ኮሚሽኑ ከፈረንጆቹ 2023 እስከ 2024 ደረስ የልጆች መታገትን ፣ግድያን እና ያለአቻ ጋብቻን አስመልክቶ 27 አቤቱታዎች ቀርበውለታል። እናም ጥቃት ከደረሱባቸው ልጆች መካከል 547 የሚሆኑት ልጆች የሚገኙባት የፑንጃብ ግዛት በሀገሪቱ ከሚደርሱ ጥቃቶች ውስጥ 40 በመቶ የሚሆነውን ትይዛለች።
የተደረገው ጥናትም የሃይማኖት አካታችነት የማይስተዋልበትን የፓኪስታንን አንድ ወጥ ሀገራዊ የትምህርት ካሪኩለም ነቅፏል። በሀገሪቱ የሚገኙ ክርስቲያኖች የማይከተሉትን ሃይማኖት በትምህርት ቤት እንዲያጠኑ እና እንዲማሩ መገደዳቸው የሃይማኖት ነጻነት ከመግታት ባለፈ የትምህርት ውጤት እንደሚጎዳ እና በማህበረሰብ ውስጥ መገለልን እንደሚያስከትል ተጠቅሷል።
የሃይማኖት መሪዎች እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች የፓኪስታን መንግስት አነስተኛ ቁጥር ላላቸው ማህበርሰቦች ሕጋዊ ጥበቃ እንዲያደርግ ፣ የትምህርት ፖሊሲዎችን እንዲያሻሽል እና ተቋማዊ ዝንፈቶችን እንዲያስተካከል ጥሪ እያቀረቡ ይገኛሉ።
መረጃውን ከክርስቲያን ፖስት አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
በባኪስታን የልጆች መብት ኮሚሽን ያወጣው አዲስ ሪፖርት ክርስቲያኖችን ጨምሮ በተለያዩ አናሳ ማህበረሰቦች ውስጥ የሚገኙ ልጆች ከፍተኛ ለሆነ ጥቃት እየተጋለጡ እንደሆነ ያስነብባል። ሪፖርቱ ከፍተኛውን ጥቃት ያስተናግዳሉ ያላቸው ደግሞ የክርስቲያን ቤተሰቦችን ልጆች ነው። ሪፖርቱ በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በክርስቲያን ልጆች ላይ የደረሱ ጥቃቶችን የሚያነሳ ሲሆን ከእነዛም ውስጥ አስገድዶ እምነት ማስቀየር ፣ ያለአቻ ጋብቻ እና የጉልበት ብዝበዛ ተጠቀሰዋል።
ኮሚሽኑ ከፈረንጆቹ 2023 እስከ 2024 ደረስ የልጆች መታገትን ፣ግድያን እና ያለአቻ ጋብቻን አስመልክቶ 27 አቤቱታዎች ቀርበውለታል። እናም ጥቃት ከደረሱባቸው ልጆች መካከል 547 የሚሆኑት ልጆች የሚገኙባት የፑንጃብ ግዛት በሀገሪቱ ከሚደርሱ ጥቃቶች ውስጥ 40 በመቶ የሚሆነውን ትይዛለች።
የተደረገው ጥናትም የሃይማኖት አካታችነት የማይስተዋልበትን የፓኪስታንን አንድ ወጥ ሀገራዊ የትምህርት ካሪኩለም ነቅፏል። በሀገሪቱ የሚገኙ ክርስቲያኖች የማይከተሉትን ሃይማኖት በትምህርት ቤት እንዲያጠኑ እና እንዲማሩ መገደዳቸው የሃይማኖት ነጻነት ከመግታት ባለፈ የትምህርት ውጤት እንደሚጎዳ እና በማህበረሰብ ውስጥ መገለልን እንደሚያስከትል ተጠቅሷል።
የሃይማኖት መሪዎች እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች የፓኪስታን መንግስት አነስተኛ ቁጥር ላላቸው ማህበርሰቦች ሕጋዊ ጥበቃ እንዲያደርግ ፣ የትምህርት ፖሊሲዎችን እንዲያሻሽል እና ተቋማዊ ዝንፈቶችን እንዲያስተካከል ጥሪ እያቀረቡ ይገኛሉ።
መረጃውን ከክርስቲያን ፖስት አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
❤1🙏1